ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, August 3, 2021

ዘግናኝ ነው።በለንደን፣ዴንቨር እና ካርቱም በጅብ የተበላ አስከሬን ከበው ጨፈሩ!?

Picture credit to buzzfeed.com


እህል እንዴት በጉሮሯቸው ወረደላቸው? ተኩሎ መውጣት፣የክት ልብስ አውጥቶ መልበስ፣ማሽካካት እና መደለቁ እንዴት ከሰውነታቸው ጋር ተስማማላቸው? የትግራይ እናቶች ልጆቻቸው በመሶበ የሲብንቶ ፋብሪካ መኪና እየተጫኑ ወደ አፋር እና የአማራ አዋሳኝ  ወረዳዎች እየተወሰዱ ተደፍተው፣የአፋር እና የቆቦ ጅቦች የምሽቱ አልበቃ ብሏቸው በቀን እየወጡ የትግራይ ልጆችን ታፋ፣እግር እና አንገት እየቦጠቦጡ ሲዘነጥሉ፣የአፋር አርብቶ አደር እና የአማራ ገበሬ የትግራይ ወጣቶችን አስከሬን ለመቅበር ሳምንታንት አይበቁኝም እያለ በደቦ ወጥቶ እየቀበረ፣ የሽብርተኛው ህወሓት ቅምጥሎች በአሜሪካ ዴንቨር፣በእንግሊዝ ለንደን እና በሱዳን ካርቱም ድግስ ደግሰው እየበሉ እየጠጡ እና ከበሮ እየደለቁ ሲጨፍሩ አደሩ።

''ትግራይ መከራ የሚመጣው ከበሮ ሲበዛ ነው።ሀገሩ የእግዚኦታ ጸሎት እንጂ ጭፈራ ሲበዛ አይወድም'' የሚለው አባባል የትግራይ እናቶች እና አባቶች የሚናገሩት ነው።እነርሱ እንደሚሉት ድሮ አያቶቻችን ነገሩን ነው።ይህ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ አነጋገር እንደሆነ ይታመናል።ሀገሩ የገዳማውያን የእነ አባ ጴንጤሌዎን፣የእነ አባ ገሪማ፣የእነ አቡነ አረጋዊ የጸሎት  ቦታ እንጂ በዘመኑ እንደተነሱት 'ጉግ ማንጉጎች' የእነ ጌታቸው ረዳ፣ ደብረፅዮን እና ፃድቃን አጉራ ዘለል የጥፋት መልዕክተኞች አይደለም።

በሀገር ውስጥ የትግራይ እናቶችን በአንዲት አንባሻ መጋገርያ እፍኝ ስንዴ አንሰጥሽም ማስፈራርያ (እርሱም ገና በአፋር በኩል በሚገባ የእርዳት እህል ነው) የትግራይ እናት ልጇን ብቻ ሳይሆን በቤቷ ያለውን የሚላስ የሚቀመስ ለህወሓት ካልሰጠች ሞት ይጠብቃታል።ይህ ያስመረራቸው የመቀሌ እናቶች ባለፈው ሳምንት ''ልጆቻችንን አምጡ!'' ብለው ለመሰለፍ ቢሞክሩ በጌታቸው ረዳ የእርዳታ እህል በጠገቡ ቅልቦች ተይዘው በሚያሰቅቅ ሁኔታ ተገርፈው ወደ እስር ቤት ተወርውረዋል።በልጆቻቸው መታፈስ ያዘኑ እና መጠየቅ የሚያስከትለውን መከራ የተረዱ እናት እራሳቸውን በራሳቸው ማጥፋታቸው ያለፈው ሳምንት የመቀሌ ዜና ነበር።

በእዚህ ሁሉ የመከራ ዶፍ ላይ ግን በለንደን፣ዴንቨር እና ካርቱም ቀደም ብለው የህወሓት ጥቅም ተጋሪዎች የሰፋ ሰውነታቸውን እያገላበጡ በትግራይ ወጣቶች እና እናቶች አስከሬን ዙርያ ጨፈሩ።አዳራሹን ክብ ሰርተው ሲዞሩ በመሃል የሚጮህ በጅብ እየተዘነጠለ  ያለ የምስኪን የትግራይ ታዳጊ ሕፃን አስከሬን አለ።የጅቡ ጥርስ ስጋውን አልፎ አጥንቱን ሲሰነጥቅ የሚያሰማው የሲቃ ድምፅ እንዳይሰማቸው ሙዚቃውን ጨምረው!ጨምረው! ይባባላሉ።የአስከሬኑ ሽታ እንዳይሸታቸው እና የአራዊቱ የሰው ስጋ ዝንጠላ የሰቆቃ ድምፅ እንዳይረብሻቸው  አስከሬን ከቦ ከሚጨፍረው ሕዝብ ከፍ ያለ መድረክ ላይ የሚታዩት የድሮ የኪነ ጥበብ ሰዎች እየተባሉ ይጠሩ የነበሩ ናቸው።ኪነ ጥበብ የሁሉም ነች።የኪነ ጥበብ ሰው የሰው ልጅ ሁሉ የሆነ ጥበብን ይዟልና በዘሩ ተጠራርቶ አስከሬን በሞላባት፣የእናቶች ሰቆቃ በጆሮ በሚያቃጭልበት ሰዓት ሕዝብ አያስጨፍርም።

ለመሆኑ ከምን ተፈጥረው ነው? ቆመንለታል የሚሉት የትግራይ ሕዝብ ታዳጊዎቹን እያነቀ ወደ ግንባር የምልከው የህወሓት የሽብር ቡድን እያሞገሱ በትግራይ ልጆች አስከሬን ዙርያ የሚደንሱት? የዴንቨር፣ለንደን እና ካርቱም የህወሓት ቅምጥሎች ጨፋሪዎች ፊት መሽካካት የሚታይበት የደለበ ሰውነታቸው ቅንጣት ታህል በአስር ሺዎች እንደቅጠል የረገፈበት ከትግራይ ማኅበረሰብ የወጡ አይመስሉም።እነርሱ ሞት አይደለም ጠንከር ያለ ፀሐይ እንዳይነካቸው መኪናቸው ውስጥ የአየር ማቀዝቀዣ እየተጠቀሙ የሚሄዱ ቅምጥሎች ናቸው። እራሳቸው ቀስቅሰው በተነሳ ጦርነት ሺዎች እረግፈው እና ጅብ ሰውነታቸውን እየበላው፣ህፃናቱ አድኑን እያሉ እየጮሁ፣ እናቶች ልጆቻቸውን የሚያስገቡበት አጥተው እያለቀሱ፣ቅምጥሎቹ ዴንቨራውያን እና ለንደናውያን በራሱ በጅብ በሚበላው ሕዝብ ስም ድግስ ጠርተው እየበሉ ያወካሉ፣'ትግራይ!' እያሉ ይዘባበታሉ።

በእነርሱ ቤት የእናቶች ለቅሶ የእንባቸው ወላፈን እነርሱን አይነካም፣በእነርሱ ቅንጭር የአስተሳሰብ ልክ ጅብ የሚዘነጥላቸው የትግራይ ታዳጊ ልጆች እና ወጣቶች አስከሬን ዕጣ እነርሱ ቤት እና በልጆቻቸው አይደርስም፣ በእነርሱ ቤት የእነርሱ ልጆች ከምግብ ምግብ አማርጠው የአይስክሬም ቀለም ዓይነት ላይ የሚጣሉ ቅምጥሎች ላይ የትግራይ ልጆች ዕጣ አይደርስም። ፈጣሪ ፍርዱ ከስር ነው።ለሞቱት ሲፈርድ ማን አነሳሳው፣ማን ወጠነው፣ማን እንዴት እና በምን ምክንያት የትግራይ ልጆችን ለጅብ እንዲሰጡ አደረሳቸው የሚለውን ሁሉ መርምሮ ነው።ያን ጊዜ ዛሬ አስከሬን ዙርያ ከቦ የመጨፈር ስነ ልቦና የእብደት እና የአዕምሮ መሰለብ እንጂ የጤነኛ ሰው ሥራ እንዳልሆነ የዛሬ ጨፋሪዎች  ርቱዕ በሆነች ፍርድ እንዲረዱት ይደረጋል። ያኔ ''ትግራይ መከራ የሚመጣው ከበሮ ሲበዛ ነው።ሀገሩ የእግዚኦታ ጸሎት እንጂ ጭፈራ ሲበዛ አይወድም'' የሚለው የትግራይ አያቶች አባባል ዕውነት መሆኑ ይገለጥላችኃል።ለካ ቆመንለታል የምትሉትን ሕዝብ እንዴት ትወዱታላችሁ? ጃል! በሞተበት፣እናቶች እራሳቸውን በሚያጠፉበት ልጆች አስከሬናቸው በጅብ በሚዘነጠልበት ጊዜ መርጣችሁ መጨፈራችሁ።በጭፈራው የታደማችሁ ሁሉ ህሊና ካላችሁ ብቻ መልሳችሁ የሰራችሁትን አስቡት።

በመጨረሻ የናንተ የቅምጥሎቹ የሰሞኑ የጥጋብ ስራ መቼ  በትግራይ እናቶች እና ወጣቶች አስከሬን ዙርያ እየዞራችሁ መጨፈር ብቻ  ሆነ? ኢትዮጵያን አናውቃትም ብላችሁ ሁሉ አቅራርታችሁ ነበር።የአሉላን ስም እየጠራችሁ የምትነግዱ የራስ አሉላ ደመኞች፣በንጉሥ ዮሐንስ ስም ይምትነግዱ እናንት የዮሐንስ አንገት ቆርጣችሁ በካርቱም አድባባይ ገበያ ለገበያ ካዞሩት ጋር የተዋዋላችሁ ባንዳዎች ናችሁ።ኢትዮጵያ ይህንን ሰምታ እኔም አላውቃችሁም የእናንተ ዓይነት አስከሬን ከቦ የሚጨፍር ልጅ የለኝም ብላ መልሳለች።በነገራችን ላይ ኢትዮጵያን አናውቅም ያሉት እና በአዳራሹ የነበሩት ፎቶ እና ቪድዮ በሙሉ አዲስ አበባ ኢሚግሬሽን ቢሮ ገብቷል።ሀገር ቤት ያላቸውም ንብረት ኢትዮጵያን አናውቃትም ላሏት የምትጠብቅላቸው አይመስልም።እናት አላውቅሽም ያላትን ልጅ ንብረት የመጠበቅ ግዴታም የለባትም።እውነታው ይሄው ነው።እየጨፈራችሁ!?

 ================
 ማስታወቂያ / Advertisment
====================
የጓደኞችዎን ወይም የቤተሰብዎን የሞባይል አየር ጊዜ ለማሳደግ ከዚህ በታች ያለውን አገናኝ ጠቅ ያድርጉ።
በአንድ ሁኔታ ውስጥ በሚመገብ ቤት የሚኖር የቤተሰብ እውነተኛ የወዳጅነት ስልክዎ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን የሚመለከት ከስር ሊ መረጃን ይጫኑ - 
Open the link to mobile top up at home


No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...