ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, April 30, 2016

ሰበር ዜና - በዴር ሱልጣን የሚገኘው የኢትዮጵያ ይዞታ ላይ ትናንት በስቅለት በዓል ወቅት ግብፆች ሁከት ለማንሳት ሞክረው ነበር ( Gudayachn exclusive)



ለጉዳያችን በደረሰ መረጃ መሰረት በኢየሩሳሌም ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ጎልጎታ፣ ዴር ሱልጣን የሚገኘው የኢትዮጵያ ይዞታ ላይ ትናንት ሚያዝያ 29/2008 ዓም በስቅለት ዕለት ግብፆች በቦታው ይገባናል ሁከት ለማስነሳት ሞክረው ነበር።በስፍራው ለትንሣኤ በዓል የመጡ እና በእስራኤል የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ''አባቶቻችን ባቆዩት ቅርስ ላይ መቃብራችን እዚሁ ይሆናል'' ብለው የመጣውን ለመቀበል በዝግጅት ላይ እንዳሉ በመካከል የእስራኤል ፖሊስ ገብቶ ጉዳዩን ለማብረድ ችሏል።ግብፆች የእዚህ አይነቱን ግርግር በዴር ሱልጣን የኢትዮጵያ ይዞታ ላይ ሲፈፅሙ ይህ የመጀመርያ አይደለም።የዴር ሱልጣን ጉዳይ በሁሉም ወገኖች ትኩረት የሚሻ እና በተለይ በእስራኤል የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ገዳማቱን የማስከበር ኃላፊነታቸውን በተደራጀ መልክ መወጣት እንዳለባቸው የሁሉም እምነት ነው። 

ከእዚህ በታች የኢትዮጵያ ይዞታ የሆኑ ገዳማት በኢየሩሳሌም የሚገኙባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ይረዳን ዘንድ ከቀሲስ ፋሲል ታደሰ ገፅ ላይ የተገኘውን ፅሁፍ  የገዳማቱን ቦታ የሚገልፀው ክፍል ብቻ እንደሚከተለው ቀርቧል።

የኢትዮጵያ ገዳማት በኢየሩሳሌም

የኢትዮጵያና የእስራኤል ግንኙነት በዘመነ ብሉይ በንግሥተ ሳባ ወደ ሰሎሞን በመሄዷ የተጀመረ መሆኑ የተረጋገጠ ነው፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሕዝበ ኢትዮጵያ ለበዓል /ሊሠግዱ/ ወደ ኢየሩሳሌም እየተጓዙ ኖረዋል፡፡ በመሆኑም ከዴር ሱልጣን ጀምሮ የኢትዮጵያ ቦታዎች አሏት፡፡ 

1.    ዴር ሱልጣን፡- ንግሥት ሳባ ከክ.ል በፊት በ1013 ዓመተ ዓለም ገደማ ኢየሩሳሌም ስትሄድ ሠራዊቷን እና ጓዟን ያሳረፈችበት ቦታ ነው፡፡ 1ኛ ነገ. 10፣ 2ኛ ዜና. 9÷1-9 ቀራንዮ (ጎልጎታ) አጠገብ ይገኛል፡፡ በተለያዩ የተንኮል ተግባራት ዋናውን ግብጻውያን የወሰዱት ሲሆን አሁን የአርባዕቱ እንስሳ እና የቅዱስ ሚካኤል ታቦታት የሚገኝበት ጠበብ ያሉ ቤተመቅደሶች እና በጥም ጠባብ የሆኑ የመነኮሳት ማደሪያዎች ይገኙበታል፡፡ 

2.   ቅዱስ ፊልጶስ፡- የኢትዮጵያ መንበረ ጵጵስና የሚገኝበት ሲሆን የገዳሙ ጽ/ቤት እና ኢትዮጵያዊውን ጀንደረባ ባጠመቀው በቅዱስ ፊልጶስ ስም ቤተክርስቲያን ይገኛል፡፡ በአፄ ዮሐንስ ትእዛዝ መ/ር ወልደሰማዕት በ1883 ዓ.ም የገዙት ቦታ ነው፡፡ 

3.   ደብረገነት ኪዳነምህረት፡- አሮጌ ከተማ ከሚባለው ውጪ በነቢያት መንገድ አጠገበት ትገኛለች፡፡ የመነኮሳት መኖሪያ የእንግዶች መቀበያ እና አዳራሽ በመግቢያዋ የሚገኝ ሰፋ ያለ ይዞታችን ሲሆን ወደ ገዳሙ የሚወስደው መግቢያ መንገድም “ርሆብ ኢትዮጵያ” ተብሎ ይጠራል፡፡  ቦታው በ1882 ዓ.ም አፄ ዮሐንስ በላኩት ወርቅ የተገዛ ሲሆን ሕንጻውን ያስፈጸሙት በ1885 ዓ.ም. አፄ ምኒልክ ናቸው፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ይዞታቸው በኢሩሳሌም ከተማ የሚገኙ ናቸው፡፡ 

4.   አቡነ ተክለሃይማኖት/አልአዛር/- በኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ 12ሺህ ሜትር ካሬ ስፋት ለው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ይዞታ ሲገኝ በጽድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ስም ቤ/ክ ታንጿል፡፡  የኢትዮጵያን መካነ መቃብር በዚህ ይገኛል፡፡ አፄ ኃ/ሥላሴ ያስገዙት ቦታ ሲሆን በአቡነ ፊልጶስ ጊዜ በ1953 ዓ.ም. ተመሠረተ፡፡ 


5.   ቅድስት ሥላሴ፡- በዮርዳኖስ ወንዝ አጠገብ ከሩብ ጋሻ የማያንስ ቦታ ሲኖር የቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ተሰርቷል፡፡ ነገር ግን በአረቦችና በእሥራኤል ጦርነት ምክንያት በአካባቢ ሰው ሊኖር ባለመቻሉ ታቦቱም መነኮሳቱም ተዘዋውረው በኢያሪኮ ይኖራሉ፡፡ ቤተክርስቲያኑ በ1925 ዓ.ም. በእቴጌ መነን የጠተሠራ እንደነበረ ይነገራል፡፡ 

6.   ቅዱስ ገብርኤል፡- በኢያሪኮ ከተማ ለብዙ ጊዜያት የአትክልት ቦታ ሆኖ የቆየው የኢትዮጵያ ይዞታ የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ይገኝበታል፡፡ ቦታውን የሠጡት ወ/ሮ አማረች ዋለሉ በኋላ እማሆይ አማረች የተባሉ እናት በ1928 ዓ.ም ገዝተውት ለገዳሙ ሰጥተዋል፡፡ 

7.   ቤተልሔም፡- በምድረ ፍልስጥኤም ጌታችን ከተወለደበት ቦታ አጠገብ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ይገኛል፡፡ ቦታው ልዑል ራስ ካሣና ልዑል መኮንን ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጡ ያስገዙት ነው፡፡ 

                                                 
ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com 

Thursday, April 28, 2016

ዞን 9 ጦማርያን መሰረቱን ስዊዘርላንድ ያደረገው የ''ማርቲን ኤናልስ'' ዓለም አቀፍ ሽልማት አሸናፊ ሆኑ! Zone 9 - Ethiopia - Martin Ennals Award 2016 Finalist!

ማርቲን ኤናልስ በአውሮፓ ሰብአዊ መብት ድርጅት፣አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣በአውሮፓ ህብረት፣የስዊዝ ልማት ትብብር ድርጅት፣የእንግሊዝ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ፊንላንድ መንግስት፣የስዊዘርላንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ሌሎች ድርጅቶች የሚደገፍ ድርጅት መሆኑን ድርጅቱ ድረ-ገፁ ላይ ይገልጣል።ዞን 9 ያሸነፉበት የማርቲን ኤናልስ ሽልማት የመስጠት ስነ-ስርዓት በመጪው ጥቅምት/2009 ዓም ስዊዘርላን ውስጥ ይሰጣል።

Martin Ennals

http://www.martinennalsaward.org/index.php?option=com_content&view=frontpage&Itemid=1&lang=en  


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.comPublish Post

Monday, April 25, 2016

Saturday, April 23, 2016

የአፄ ኃይለ ስላሴ የልጅ ልጅ ልዑል ኤርምያስ ሳህለ ስላሴ ትናንት አርብ ጀማይካ ገቡ የአገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ህዝቡ አቀባበል አደረጉላቸው Prince Ermias Sahle Selassie, grandson of Ethiopian Emperor Haile Selassie I arrived at Jamaica.

 

ልዑል ኤርምያስ እና ልዕልት ሳባ ከበደ 
PRINCE Ermias Sahle Selassie & Princess Saba Kebede

 ጃማይካ ኦብሰርቨር ዓርብ ሚያዝያ 14፣2008 ዓም እንደዘገበው አፄ ኃይለ ስላሴ ጀማይካን የጎበኙበት 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ለመገኘት  ለሶስት ቀናት ጉብኝት የንጉሡ የልጅ ልጅ እና የዘውድ ምክር ቤት ሰብሳቢ  ልዑል ኤርምያስ ሳህለ ስላሴ ከባለቤታቸው ልዕልት ሳባ ከበደ ጋር ጃማይካ ገቡ በማለት ገልጧል።ልዑሉ  ኪንግስቶን አየር ማረፍያ ሲደርሱ የሀገሪቱ ሚኒስትሮች እና ''የኮመን ዌልዝ'' ተወካይ እንዲሁም በርካታ ጀማይካውያን በከበሮ እና በሆታ አየር ማረፍያ ድረስ በመሄድ ተቀብለዋቸዋል።

ከዋሽግተን ወደ ጀማይካ የበረሩት ልዑል ኤርምያስ በአየር መንገድ አቀባበል ከተደረገላቸው እና ጋዜጣዊ መግለጫ ከሰጡ በኃላ በቀጥታ ወደ ጀማይካ ዋና ከተማ ከንቲባ የተዘጋጀላቸው ልዩ ዝግጅት አምርተዋል።

ልዑል ኤርምያስ ጀማይካ አርብ ሚያዝያ 14፣2008 ዓም ሲደርሱ በሚኒስትሮች እና ህዝቡ አቀባበል ሲደረግላቸው  (Photo: Jamaica Observer )

ልዑሉ በሀገሪቱ ከፍተኛ ዩንቨርስቲ ተገኝተው ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም ይህንን ብለዋል:

''You are the future …very bright people who would become future prime ministers, future scientists; but the important part of education is that you also have morality that goes with it that distinguishes what is right from what is wrong; what is just and what is unjust. Too many times today ...we turn against what may seem a challenge because it doesn’t seem to resolve anything. What makes the difference and what makes leaders [are] principled commitments and if you work hard there is nothing you can’t achieve,” Prince Ermis 

''በመጨረሻም ልዑሉ ንግግራቸውን ሲያጠናቅቁ የዩንቨርስቲው ተማሪዎች የልዑሉን እጅ በደስታ እየተሻሙ ሲጨብጡ ታይተዋል'' በማለት ጃማይካ ኦብሰርቨር ዘግቧል።

ጃማይካ ኦብሰርቨር ስለ ልዑል ኤርምያስ የጀማይካ ጉብኝት የፃፈውን ሙሉ ሪፖርት ከእዚህ በታች ያንብቡ።

Irie moment Rastas turn out in numbers for Emperor Selassie’s grandson visit

BY RACQUEL PORTER Observer staff reporter porterr@jamaicaobserver.com
Friday, April 22, 2016 

PRINCE Ermias Sahle Selassie, grandson of Ethiopian Emperor Haile Selassie I, arrived in the island yesterday to much fanfare among the local Rastafarian community.
Prince Ermias, who was accompanied by his wife Princess Saba Kebede, is here on a three-day visit to participate in activities to commemorate the 50th anniversary of his grandfather’s visit.
Hundreds of Rastafarian men, women and children flocked Norman Manley International Airport in Kingston, where the ‘prince’ arrived on a flight from the United States at minutes before noon.
But the Rastafarians, who were beating drums, chanting verses, and smoking marijuana, said the gathering was nothing compared to what was seen half-a-century ago.

Following a press conference, Prince Ermias — who lives in Washington, DC — emerged from the airport building and walked to the car park accompanied by Minister of Culture Olivia Grange, Transport Minister Mike Henry, and representatives of the Commemoration Committee and the Republic of Ethiopia. He greeted the crowd of Rastafarians and thanked the people of Jamaica for hosting him.
He then journeyed to the National Heroes Park where he was greeted by Mayor of Kingston Dr Angella Brown Burke, before placing a wreath at the shrine of national hero Marcus Garvey.
“…We are focusing on making sure that we represent our custom; practise lifestyle, as Rastafarians, to be involved and, I pray that everything works out. I give thanks to the brethren and the sistren dem who have been focusing on the tradition of Rastafarians over the period,” Bunny Wailer, the only living member of the Wailers singing group, told the
Jamaica Observer.
Prince Ermias and his entourage also made stops at the University of Technology, University of the West Indies, The Mico University, and Jamaica College, where he was greeted by former prime minister Bruce Golding, who attended the school.
Golding, who said he remembered vividly Emperor Selassie’s visit in 1966, said the spiritual leader visited at a time of great significance when Rastafarians were oppressed and ostracised by society. He said Emperor Selassie’s visit created a platform on which Rastafarians were able to command the respect that they deserved.
Prince Ermias, in his response, thanked the Jamaica College family for the warm reception.
“You are the future …very bright people who would become future prime ministers, future scientists; but the important part of education is that you also have morality that goes with it that distinguishes what is right from what is wrong; what is just and what is unjust. Too many times today ...we turn against what may seem a challenge because it doesn’t seem to resolve anything. What makes the difference and what makes leaders [are] principled commitments and if you work hard there is nothing you can’t achieve,” Prince Ermias told a group of Jamaica College boys.
Earlier at The Mico University, trainee teachers who shook Prince Ermias’ hands declared that there would not be any hand-washing for rest of the day as they wanted to cherish the moment.
“I am very elated to share in such a historical moment. I feel as if I am reliving a moment when Selassie I was here. So, to be a part of the festivity today, I am very proud,” declared history major, Rachel Dale.

Source:   Jamaica Observer 
click here to read Jamaica observer 

ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

Wednesday, April 20, 2016

የጋምቤላው ጉዳይ ያልተሰሙ መረጃዎች እየወጡ ነው


''12 ሰዓት ሙሉ ጭፍጨፋው ሲደረግ ጋምቤላን ከኑኤር ዞን የሚያገናኘው መንገድ 1 ሰዓት ብቻ የሚወስድ ሆኖ ሳለ ሰራዊቱ እንዴት አልደረሰም?'' የዲያስፖራ ኑኤር ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ መንግስት ከፃፉት ደብዳቤ የተወሰደ።
የዲያስፖራ ኑኤር ማህበረሰብ አባላት ፔቲሽን ተፈራርመው ለአቶ ኃይለማርያም የፃፉት ደብዳቤ ደቡብ ሱዳን ዜና አገልግሎት በድረ-ገፁ ላይ ለጥፎታል። ደብዳቤው ጥቃቱ በኢትዮጵያ አፈር ላይ ሲፈፀም የኢትዮጵያ ሰራዊት የት ነበር? የኢትዮጵያ ሰራዊት ቶሎ እንዳይደርስ ምን አዘገየው? 12 ሰዓት ሙሉ ጭፍጨፋው ሲደረግ ጋምቤላን ከኑኤር ዞን የሚያገናኘው መንገድ 1 ሰዓት ብቻ የሚወስድ ሆኖ ሳለ 12 ሰዓት የፈጀው ጭፍጨፋ ሲካሄድ ሰራዊቱ እንዴት አልደረሰም? የኢትዮጵያ ሰራዊትን ምን አዘገየው? የሚል እና ሌሎችም ጥያቄዎች የያዘ ደብዳቤ ለአቶ ኃይለማርያም መላኩን ለማወቅ ተችሏል።
በሌላ በኩል ቪኦኤ አማርኛው አገልግሎት የደቡብ ሱዳን መንግስትን ህፃናቱ እንዲመለሱ እንዲያደርግ የሚጠይቅ መግለጫ የአውሮፓ ህብረት ዛሬ አውጥቷል።ይህ በእራሱ የኢትዮጵያ መንግስት እንደመንግስት እየሰራ ነው ወይ? የሚል ጥያቄ አስነስቷል።የአውሮፓ ህብረት ነው የኢትዮጵያ መንግስት ነው መግለጫ ማውጣት ያለበት? ክስተቱ ኢትዮጵያ መንግስት እንደሌላት ሌላው ማሳያ ሆኗል።
የኑኤር ማህበረሰብ ዲያስፖራ አባላት የኢትዮጵያን መንግስት የወቀሱበት ደብዳቤ ከእዚህ በታች ያንብቡ

An open letter to Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn

By Duach R.Mach Your Excellency, April 18, 2016 (SSNA)



We are very distraught by the death of our innocent civilians (children, women, and elderly people) who were recently massacred by Murle tribe of South Sudan.

e write this petition letter to you to consider our message as your greatest priority. How could we consider ourselves as citizens of the country where our mothers, fathers, Children, and all vulnerable people are not fully protected by the Federal Government?
Recent fighting lasted for many or long hours which allowed the attackers to kill as many civilians as they wanted.
Where were our Defense Forces, as well as our government officials at this horrible moment?
We are writing this letter on behalf of the Nuer Ethiopian Community, residing in the United States of America. We want to assure to you that the unceasing death of Ethiopian civilians is the point of these Murle tribe attacks, and is really going to be a long-term problem if there is no real action taking place to dissuade them. Any believable action from Ethiopian Defence Forces regarding this killing is needed as quick as possible.

On Friday April 15, 2016, 280 vulnerable, innocent people were killed and nearly 150 others were wounded by large group of 4,000 well equipped militias carried out on Ethiopia soil (Kebeles). Very miserable again! Therefore, the killing of 280 civilians within 12 hours, including children, elderly and woman by the South Sudanese Murle tribe, must be put in the books. Why? Is this true the killing was carried out by South Sudanese and killed these civilians on Ethiopian government watch? The Nuer Community in Diasporas is very suspicious... if so, what is the reason for them to kill more than 280 innocent civilians, abduct 108 children, and take 5,000 head of livestock in the recent massacre?

Questions: Where was the Ethiopian military at the time these murders happened in Kebeles? What delayed Ethiopian Defense Forces from rescuing innocent civilians as soon as possible, while the fighting was raging for more than 12 hours? Meanwhile, the two major roads linking Gambella to Nuer Zone are less than an hour, and from Lare to Mading Kebele is prominently wide open? What really caused our Defense Forces to not arrive before Murle finished murdering civilians?

Whatever the case, the Ethiopian Federal Government should take major action very swiftly, and very quickly, without any hesitation, to bring those children to their parents. Otherwise this will be repeated again and again. Does this mean the government of Ethiopia doesn’t care for innocent Ethiopian civilians as long as the authorities are safe for themselves? We have seen such kinds of killing, abduction, invasion and aggressive provocation against Ethiopian citizens, and we have never seen any reaction from the government. This time will not be the same as 9 years ago when the Murle attack happened in Ngor Kebele (Teluth) and later in Palbol Kebele, 7 years ago and the Ethiopia authority failed to act against attackers as they should.

Henceforth, we strongly condemn this barbaric killing by the extremists who attacked and killed the innocent civilians, abducted children, and took thousands of livestock by the hard-headed tribe Murle. This extremist group claims to be the Murle tribe from South Sudan, but are in fact misrepresenting the tribe’s hatred. The entire region of Gambella strongly condemns all sorts of violent acts carried out by the South Sudanese and must not be tolerated. On April 16, 2016, Regional President Ato Gatluak Tut went to all Kebeles, and confirmed the deceases, the wounding of hundreds of civilians, and the many abducted children. He also confirmed the attackers used heavy weapons and wore military uniforms.

A letter send to Prime Minister Haile Mariam Desalegn detailed the circumstances confirming that there has been South Sudanese military involved in the killing. This includes all forms of violence, such as abducted children and severe physical damaged in all Kebeles. The Prime Ministry of Ethiopia must express his statement to the South Sudanese government, condemning the killings in the strongest possible terms, as well as the killing of civilians and abducted children. Also, the government of Ethiopia must demand to the government of South Sudan and her militias to immediately bring back these total of 125 abducted children to their parents.

Gambella Regional population issued statements in which they strongly condemn the killings and urged the government that those responsible be held accountable.

Recent killings have also sparked outrage to entire population of the region. The Region astonishment over the killings of the civilian population by neighborhood are a flagrant violation of international law. Your Excellency, Prime Minister Haile Mariam Desalegn, this is an outrageous crime against such young children, who shall protect this country in the future from enemies; you must put it in real consideration as quick as possible. The savage and despicable attacks on civilians are outrageous. Why did Ethiopia’s almighty military power fail to react so quickly and used air fighting jets? Why didn’t the Ethiopia Defense Force use main road as they can?

In conclusion---Our thoughts and prayers are with the loved one of those killed and seriously injured. We stand together with the people of Gambella Ethiopia in this time of sorrow. Condemning the violence and barbarism committed by the Murle tribe of South Sudan will never be forgotten. Such a massacre cannot go unpunished. More than 280 people, mostly civilians, have been killed in Nuer Zone, and the total children abducted from the Gambella Region this month alone is 125. For instance, the Bolim-Kun Wareda, Mangok Kebele, Chatyier Kebele, Banyrial Kebele and Madiang Kebele, attackers were declared by the South Sudanese Militias to be no retaliation to any reason that were drawn by Ethiopia, particular the major Zones, the Nuer Zone and the Anyuak Zone. The same militias also coordinated another attacked on Anyuak Zone, Jor Kebele and other surrounding Kebeles, took at least 11 children, and killed dozens innocent civilians The Nuer community condemns all these sorts of evil acts. This must not be tolerated.

The Nuer Community in Diaspora stands in solidarity with the families who have lost their loved ones during this difficult time. Our thoughts and prayers are with them. We know Ethiopian Defense Forces always was, always is and always will be strongest Forces ever! We condemn these horrific crimes in the strongest terms possible.

The author lives in the United States. He can be reached at drmach31@yahoo.com .

Source: SOUTH SUDAN NEWS AGENCY  April 18, 2016

Tuesday, April 19, 2016

የስብሀት ነጋ ምልምሎች ቤተ ክርስቲያኒቱን ሲያምሷት (ዘአዲስ Ze Addis)



ከእዚህ በታች ያለው ፅሁፍ የተገኘው ከዘአዲስ (Ze Addis) ገፅ ነው
በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተደረገው ድብድብ 62 ሰዎች ቆስለዋል
******************************************************
ኦርቶዶክሱ ዝምታውን እስካልሰበረ ድረስ ገና ይቀጥላል::የፍርሃት ክርስትና ይቁም:: መብታችንን እናስከብር!!
====================================
የህወሀት( ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ) መስራችና ኮማንደር የነበሩት ያያኔው ታጋይ ፤ ያሁኑ ዶክተር አረጋዊ በርሄ በቅርቡ A Political History of the Tigray People’s Liberation Front ( 1975-1991) የተሰኘ መጽሐፍ አሳትመዋል። መጽሐፉ አስራ ሁለት ምእራፎችና 355 ገጽ ያሉት ሲሆን በይዘቱም በርካታ ጉዳዮችን ይዳስሳል።

የመጽሐፉ ደራሲ ደግሞ የህወሀት የፖሊት ቢሮ አባልና ከህወሀት ጥንሥስ ጀምሮ ፖሊሲ አውጪ አመራር ስጭና አዋጊ ስለነበሩ በተራ አባላቶቸ የማይታወቁ በርካታ ሚስጥሮችን ይፋ አድርገዋል። መጽሀፉ ÷ ስለ ብሔር ፓለቲካ አደገኛነት ÷ ስለ ማሌሊት ማኒፌስቶ 1976 አና ትግራይን ስለመገንጠል የነበረውን ውዝግብ÷ ስለ ስብሀት ነጋና መለስ ሚስጥራዊ ሰንስለቶች÷ ስለ ጦርነቱ ÷ ከኤርትራው ኢሳያስ ጋር ስለነበረው ፍቅርና ጠብና አሁን ድረስ እያዋጉ ስላሉት መሰረታዊ ምክንያቶችና ሌሎች ብዙ አስገራሚ ሚስጥሮችን ይተነትናል።
you can find the book here. Just click and read pages 299 -302
እኔን ግን የሳበኝ ህወሀት ወይም ወያኔ ÷ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን ላይ ከበረሀ ጀምሮ የሰራውን ደባ የሚያትተው ክፍል ነው።ዶክተር አረጋዊ በዚሁ መጽሀፋቸው ምእራፍ አስር ላይ “Neutralizing the Church and Mobilizing Muslims “ በሚለው ንኡስ ርእስ ስር ህወሀት የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያንን እንዴት እንደተዋጋትና አሁን ቤተ ክርስትያና ውስጥ የሚታዩት አበይት ችግሮች በሙሉ ህወሀት ከበረሀ ጀምሮ ያቀዳቸው መሆኑን በዝርዝር አስቀምጠውታል።
ወያኔ ቤተክርስትያንን መታገል ለምን ፈለገ?
ይህን መጽሀፍ ሳነብ ዋናው ጥያቄዬ የነበረው ፤ “ወያኔ ቤተክርስትያንን መታገል ለምን ፈለገ? “ የሚለው ነበር።ወያኔ በወቅቱ ቤተክርስትያንን አምርሮ መታገልና ማዳከም የፈለገበትን ምክንያቶች ዶክተር አረጋዊ አንድ ባንድ አስቀምጠውታል።በሚገርም ሁኔታ አንዱና ዋናው ምክንያት የቤተክርስትያኗ ብሔራዊ አስተምህሮ ÷ መገንጠልን መቃወምና የሀገሪቱን አንድነት ደጋፊ መሆንና በባንዲራና መሰል ኢትዮጲያዊ መገለጫዎች ላይ የነበራት አስተምህሮ እንደሆነ እንዲህ ሲሉ አስቀምጠውታል።

“A combination of factors made relations between TPLF and the EOTC church difficult …the church taught its followers to respect their allegiance to the Ethiopian state and was, in effect , a school for national consciousness, using national symbols such as the flag in all religious and social events. No church ever conducted major ceremonies without hoisting the Ethiopian flag – an act also regularly observed …’ page 244
“The pragmatic TPLF understood the church’s role in village social life and its support for the unity of the country .It also understood a possible alliance between the Church with its forces that stood against socialism and nationalization of the land as well as separatism .The church was viewed as a force standing in the way of TPLF. …there was no doubt that it wanted to subordinate the church to its cause” page 245

የአኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በህዝቡ ውስጥ ያላት ተቀባይነትና ቤተ ክርስትያና በሀገር አንድነት ላይ ያላት ጽኑ አቋም ፡ እግዚአብሄር የለም ብሎ የሚያስተምረውን ሶሺያሊዝምን መቃወሟና በባንዲራ ላይ ያላት ጽኑ አስተምህሮናና የመገንጠል ተቃዋሚ መሆኗ በወያኔ ጥርስ ውስጥ እንድትገባ ምክንያት እንደሆነ ዶክተር አረጋዊ እማኝነታችውን ከገለጡ በሁዋላ ወያኔ ቤተከርስትያኗ ላይ ያሳረፈውን በትር እንዲህ ሲሉ ጠቅሰውታል።
የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተክርስትያንን ማደንዝዝና መቆጣጠር በብሔራዊ ማንነትና በሀገር አንድነት ላይ ቤተክርስትያኗ የያዘችው ጽኑ አቁዋም ያበሳጨው ህወሀት ቤተ ክርስትያኗን ለማደንዘዝና ለመቆጣጠር የለኮሰውን ባለ ሶስት ዘርፍ የጥቃት ዘመቻ እንዲህ ሲሉ ይዘረዝሩታል:
አንደኛ ፡ ቤተክርስትያኗ በህዝቡ ዘንድ ያላትን ማህበራዊ ተሰሚነት ማዳከምና የቤተ ከርስትያኗ መንፈሳዊ ጉዳዮች ሳይቀሩ በካድሬ በሚመሩ ህዝባዊ ጉባኤዎች እንዲወሰኑ ማድረግ
“the second step was to try and move the socio economic focus of life from the church to the peoples assemblies. All administrative and social activities were taken over by the associations and the baitos and even church affair such as the rights and obligations of the church and its followers fell under the jurisdiction of the assemblies. The capacity of the church to mobilize and influence waned. The church lost its status as mediator in conflicts, rights over spiritual and familiar issues because the new political authorities….”
የሚገርመው ቤተክርስትያኗ በራሷዋ መንፈሳዊ ጉዳዮች ላይ እንኩዋን ለመወሰን መብቱን አጣች። በ 1970ዎቹ እና ሰማነያዎቹ ህወሀት ነጻ አወጣሁዋችው በሚላቸው ቦታዎች በሙሉ የቤተ ክርስትያን መንፈሳዊ ውሳኔዎች በካድሬና በካድሬ በሚመሩ ስብሰባዎች መወሰን ጀመሩ።
ሁለተኛው ደግሞ የቤተ ክርስትያኗን አመራር በሙሉ በህወሀት ካድሬዎች ማስያዝና የቤተክርስትያኗን አመራረ ሙሉ በሙሉ ግእዝ በሚናገሩ ካድሬዎች መተካት እንደነበረ እንዲህ ሲሉ ይገልጹታል
“thirdly , the TPLF launched a series of conferences or seminars for selected parish priests in 1970 to win them over. The underlying motive of the seminars was to isolate the church in Tigray from the wider Ethiopian Church in order to foster Tigraian nationalism along the lines of the TPLF strategic objective. Suppressed Tigraian nationalism was invoked to challenge the dominant Ethiopian Orthodox Church. The initial wereda seminars for the priests were conducted by an eloquent TPLF fighter,Gebre Kidan Desta, a graduate of the theological College at Addis Ababa university .The themes of the seminars were to replace the Ethiopian Church authority by TPLF – minded church and the language in the church with Tigrigna and ultimately, to further Tigraian nationalism and identity ‘ page 246
የቤተ ክርስትያኗን ሀይል ለማዳከምና ለመቆጣጠር መነኮሳት በማስመሰል ትልልቅ ገዳማት ውስጥ ካድሬዎችን በማስረግና በማስሾም በስብሐት ነጋ የሚመራ የስለላ ቡድን ለዚሁ ጉዳይ ሲባል መዋቀሩን እንዲህ ይገልጹታል
“this process involved the mobilization of parish priests and ordinary Christians to isolate them from the church national hierarchy. To weaken church authority, an intelligence group was formed under Sibhat Nega to infiltrate the wel-established monasteries in Tigrai, such as Debre Damo , by planting TPLF members’ camouflaged as monks and influencing church activities in the interests of TPLF”
+++++++
የማነ ዘመንፈስ ከትግርኛ ጋዜጣ አንባቢነት ተነስቶ : የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ለምን እንደሆነ እካሁን ምስጢሩ ካልገባችሁ ;-ይሄ ነው:: በየቦታው ባሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስትያናት ላይ የሚፈጠረው ውዝግብ - ምክንያቱ ምን እንደሆነ ማወቅ ካሻችሁ -ይሄ ነው:: 
ኦርቶዶክሱ ዝምታውን እስካልሰበረ ድረስ ገና ይቀጥላል::የፍርሃት ክርስትና ይቁም:: መብታችንን እናስከብር!!

ዘአዲስ (Ze Addis)  

ቪድዮውን ከእዚህ በታች በመጫን ይመልከቱ https://www.facebook.com/100008042808114/videos/1706908829587194/



Sunday, April 17, 2016

ጣይቱ የተሰኘ ደረጃውን የጠበቀ የኢትዮጵያውያን ሬስቱራንት ባለፈው ቅዳሜ በኦስሎ፣ኖርዌይ ተከፈተ

Ny Ethiopian Restaurant er åpen i Oslo.
New Ethiopian Restaurant is open in Oslo.

ኦስሎ የተከፈተው የጣይቱ ሬስቱራንት ዋና መግቢያ 

ቅዳሜ ሚያዝያ 8/2008 ዓም በኦስሎ፣ኖርዌይ ደረጃውን የጠበቀ ጣይቱ የተሰኘ አዲስ ሬስቱራንት ተመረቀ።እርግጥ ነው በውጭ አገራት የኢትዮጵያ ሬስቱራንቶች እና ሆቴሎች ብዙም አዲስ ዜና የማይሆንባቸው ከተሞች አሉ።ይህ ግን ለኦስሎ አዲስ ዜና ነው።ምክንያቱም በስፋቱም ሆነ በደረጃው ባለፈው ቅዳሜ የተመረቀውን ጣይቱ የኢትዮጵያውያን ሬስቱራንትን የሚያክል የለም።ለእዚህ ነው የእዚህ ሬስቱራንት መከፈት በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ደስታን የፈጠረው።በትናንት የምረቃው ስነ ስርዓት ላይ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሬስቱራንቱን አጨናንቀውት ውለዋል።ከሁሉም ፊት የሚነበበው የደስታ ስሜት ነበር። በባዕድ አገር እየኖሩ የእራስን ባህል የሚያስተዋውቅ ሲገኝ ለምን አንደሰት?


የሬስቱራንቱ ውስጣዊ ክፍል 

አንደኛ ፎቅ ቨረንዳ 

የኢትዮጵያ ቡና እና ባህላዊ ክፍል 

የአንድ አገር ሕዝብ ባህል ከሚገለጥባቸው መገለጫዎች ውስጥ አለባበስ እና አመጋገብ ተጠቃሽ ናቸው።እኛነታችንን ለባዕዳን ከምናሳይበት እና ከምናስተዋውቅበት ውስጥ አንዱ አመጋግባችን ነው።በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያውያን ምግብ በዓለም ላይ ታዋቂ ከሆኑት ከህንድ እና ቻይና ምግቦች እኩል ተፈላጊነታቸው ቀላል አይደለም።እርግጥ የህንድ እና የቻይና ሬስቱራንቶች በካፒታል ደረጃ እና በዘመናዊ የንግድ አመራር የሚለዩበት መንገድ እንዳለ ሆኖ ማለት ነው።

ደንበኞች መስተንግዶ ላይ 

በርካታ አውሮፓውያን እና አሜሪካውያን የማያውቁት አገር ሄደው የሚመገቡት ምግብ እንደማይስማማቸው ሲረዱ ቶሎ ብለው ወደ ድረ-ገፅ ገብተው የሚፈልጉት የኢትዮጵያውያን ሬስቱራንቶችን ነው።የኢትዮጵያን ምግብ ጣፋጭነቱ ብቻ ሳይሆን  ለጉዞ ተስማሚ እንደሆነ በርካታ የውጭ ዜጎች ይስማሙበታል። እዚህ ላይ የሚያሳዝነው ግን የኢትዮጵያ አየር መንገድ  የኢትዮጵያ ምግብ ለመንገደኞቹ አያቀርብም።እንጀራ መብላት እፈልጋለሁ ያለ መንገደኛ በእራሱ አገር አየር መንገድ ውስጥ ሆኖ የፈረንጅ ምግብ እንጂ እንጀራ አይሰጠውም።የአውሮፓ እና የአሜሪካ ትልልቅ ''ሱፐር ማርኬቶች'' ግን የኢትዮጵያን እንጀራ ለገበያ አቅርበው ለሕዝባቸው እና ባብዛኛው ለኢትዮጵያውያን እንዲቀርብ ፈቅደዋል።አንድ ቀን በኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ውስጥ እንጀራ በወጥ እናይ ይሆናል።መቼም የእራሳችንን ነገር ሁል ጊዜ ዝቅ የማድረግ አባዜ አለብን።

የሬስቱራንቱ  ፊተኛ ክፍል 

ወደ ኦስሎ አዲሱ ጣይቱ ሬስቱራንት ልመለስ እና ይህ በሁለት ወጣት ኢትዮጵያውያን ኢንተርፕረነሮች  የተከፈተው ጣይቱ ሬስቱራንት ለኦስሎ ከተማ ማዕከል የአምስት ደቂቃ ብቻ እርቀት ያለው ሲሆን ለባቡርም ሆነ ለአውቶብስ ትራንስፖርት አመቺ በሆነው ጎዳና ዳር ላይ የሚገኝ ነው።በነገራችን ላይ የእዚህ አይነቱ ደረጃውን የጠበቀ ሬስቱራንት በኦስሎ ከተማ መኖር የኦስሎ ከተማን የልዩ ልዩ ባህል መገለጫነት የሚያጎላ እና የአፍሪካውያን አንዱ የባሕል ማሳያ ቦታ ይሆናል።ወደ ኦስሎ ጎራ የሚል ኢትዮጵያዊም ሆነ የሌላ አገር ዜጋ ትንሿን ኢትዮጵያን የሚመለከትበት አንዱ እና አይነተኛ አማራጭ ቦታ ጣይቱ ሬስቱራንት ይሆናል።

ከእዚህ ጋር ተያይዞ ሌላው ሳይገለጥ መታለፍ የሌለበት ጉዳይ።በአዲስ አበባ ሳይቀር በርካታ ሆቴሎች እና የንግድ ድርጅቶች ኢትዮጵያዊ የሆነ ስም እየጣሉ በባዕዳን ስም በሚጠሩበት በእዚህ ወቅት  ጣይቱ ሬስቱራንት የመጀመርያው የኢትዮጵያ ሆቴል ስም በሆነው እና በስመ ጥር ንግስት ጣይቱ ስም መጠራቱ የኢትዮጵያን ስም ለውጭው ዓለም ለማስተዋወቅ የእራሱ ድርሻ አለው። ጣይቱ ስትነሳ የመጀመርያ ሆቴል ስራዋ፣የጦር ስልት አዋቂነቷ፣የመንግስት አማካሪነቷ፣ በውጫሌ  ውል አንቀፅ 17  እንዲመረመር በማድረግ የዓለም አቀፍ ሕግ አዋቂነቷ እና ኢትዮጵያዊት ባለሙያ እናት መሆኗ ሁሉ ይታወሳል።አሁንም  ኢትዮጵያውያን ኢንተርፕሬነሮችን ያብዛልን



በሬስቱራንቱ ሌላኛው  ክፍል የሚገኘው ምሳ በመሶበ ወርቅ 

ጣይቱ ኢትዮጵያ ሬስቱራንት አድራሻ: Toyen data 2, 0190, Oslo
                                                               Greenland Basar 


ጉዳያችን GUDAYACHN
ሚያዝያ 9/2008 ዓም

 www.gudayachn.com

Thursday, April 14, 2016

ምግብ የመብት ጉዳይ ነው። መንግስት በረኃቡ ጉዳይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊከሰስ ይችላል።የዩንቨርስቲ ተማሪዎች፣የከተማ ነዋሪዎች እና ገበሬዎች ሁሉ ለተራበው ሕዝብ መጮህ ካለባቸው ወቅቱ አሁን ነው! (የጉዳያችን ማስታወሻ)

የተባበሩት መንግሥታት የምግብ መብት ጉባኤ (Photo:- srfood.org)

እንደ ዓለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶች ዘገባ በኢትዮጵያ ከሚኖረው ሕዝብ ከአምስቱ አንዱ ርኃብ አደጋ ላይ ነው። ዓለም አቀፍ የሕፃናት አድን ድርጅት - ዩኒሴፍም ዘገባውን ስያጠናከር በኢትዮጵያ የስድስት ሚልዮን ሕፃናት ሕይወት አደጋ ላይ ነው ብሏል።በሌላ በኩል በከተማ የሚኖረው ሕዝብ የኑሮ ውድነቱ ጣርያ ነክቶበታል።የብሔራዊ ባንክ ጥናት እንደሚያሳየው የዋጋ ግሽበቱ ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ 12% ደርሷል።ዓለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶች 90 ቀናት የእርዳታ ማሰባሰብያ መርሃ ግብር አዘጋጅተዋል።በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ግን በይፋ እንዳይጠይቁ ታግደዋል። (Ethiopian government stops fundraising campaign by UN agencies)
ይህ ጉዳይ ዓለም አቀፍ ወንጀልም ነው።ምግብ ከመኖር ህልውና በላይ የሰብአዊ መብት ጉዳይም ነው። መንግሥታት፣ግለሰቦች እና ኩባንያዎች ሰዎች ምግብ እንዳያገኙ ለሚያደርጉት ማናቸውም እንቅስቃሴ እና ኃላፊነት ያለመወጣት ተግባር ሁሉ በሕግ እንዲጠየቁ ዓለም አቀፍ እንቅስቃሴ ከተጀመረ ጥቂት አመታት ተቆጥረዋል

ምግብ የሰብአዊ መብት ጉዳይ ነው (Right to food) የሚለውን መመርያ በአገራቸው ለተግባራዊነቱ ሥራ ከሚሰሩት አገራት ውስጥ ኤልሳ ልቫዶር፣ዮርዳኖስ እና ህንድ  ይገኙበታል።የምግብ መብት ዓለም አቀፍ ሕግ የማድረግ እንቅስቃሴ የመነጨው ከተባበሩት መንግስታት የምጣኔ ሀብት፣የማኅበራዊ እና የባሕል መብት ፅንሰ ሃሳብ ሲሆን እኤአቆጣጠር በ2012 ዓም 160 አገራት ጉዳዩን ከፍ ወዳለ ዓለም አቀፍ ሕግ ቅረፃ ለማሳደግ የመግባብያ ፊርማቸውን አስቀምጠዋል።የመግባብያ ሰነዱ አገራቱ ምግብ የመብት ጉዳይ መሆኑን የሚያሳይ ፖሊሲ በአገራቸው እንዲያወጡ እና በዓለም አቀፍ ደረጃም ተግባራዊ እንዲሆን ያሳስባል። 

በእዚህም መሰረት በ20013 እኤአ ህንድ የምግብ መብት ሕግን በብሔራዊ ሕግ ውስጥ አካተተች።ምግብ የመራብ እና አለመራብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን መንግሥታት ብሔራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ግዴታቸውን የመወጣታቸው እና ያለመወጣታቸው ጉዳይም ጭምርም ነው።ለአንድ ሕዝብ ምግብ እንዳይደርሰው ማድረግ ከዘር ማጥፋት ወንጀል እኩል ያስጠይቃል።የምግብ ጉዳይ የኢትዮጵያቴሌቭዥን ሲመቸው ስለረሃብ ሳይመቸው ዘፈን የሚያቀርብበት ጉዳይ አይደለም።በኢትዮጵያ የሰው መብት ከሚታሰበው እና ከሚገመተው በላይ በአምባገነኑ ስርዓት ስለተረገጠ ጉዳዩን አቅልሎ የማየት አዝማምያ ይስተዋላል።ሆኖም ግን ጉዳዩ ቀላል ጉዳይ አይደለም። የሚወራው ስለ ሚልዮኖች ሕይወት ነው።የተራበው የኖርዌይን ሕዝብ ሶስት እጥፍ የሚሆን ሕዝብ ነው።ይህ ሕዝብ እንደ ምንም ነገር ዝም ሊባል አይገባም።

የምግብ መብት ጉዳይ ዓለም አቀፍ እንቅስቃሴ በአገራት የውስጥ ፖሊሲ ከመግባት ባለፈ መንግሥታት ፍርድ ቤት አስቁሞ አስፈርዷል።በኔፓል 1998 የአገሪቱ ከፍተኛው ፍርድ ቤት መንግስቱን ምግብ ለሕዝቡ ባለማዳረሱ ምግብ እንዲያከፋፍል ፈርዶበታል።በህንድም በተመሳሳይ መልክ የእርዳታ ድርጅቶች ተሰብስበው የህንድን መንግስት  ለሕዝቡ  ምግብ ባለማድረሱ  የሚል ክስ መስርተው አስፈርደውበታል።

በመጨርሻም  ምግብ ለሕዝብ እንዳይደርስ የማድረግ ሂደት ከቢሮክራሲያዊ ድክመት ባለፈ በአገር ውስጥ የሚፈጥረው የውስጥ ቅራኔ ቀላል አይደለም።በአሁኗ በህወሓት የጎሳ ፖለቲካ የተከፋፈለች ኢትዮጵያ ውስጥ ምግብ እንዳይደርስ የተደረገው አካባቢ ከጎሳ ጭቆና አንፃር ሊመለከተው ስለሚችል ጉዳዩ ውስብስብ ችግር ይዞ መምጣቱ አይቀርም።በመሆኑም የኢትዮጵያ ሕዝብ መንግስት እየደበቀ ያለውን ርኃብ በግልፅ በአደባባይ በመቃወም የተሻለ ብሔራዊ መግባባት እና አንድነት መፍጠር ይችላል።የተራበው አካባቢ ሕዝብ በርቀት የሚኖረው ወገኑ እንደሚያስብለት የማሳያው እና ሌላው አንድነት የመፍጠርያ አጋጣሚም ነው።ስለተራበው ሕዝብ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች፣ምሁራን፣የከተማ ነዋሪዎች እና ገበሬዎች ሁሉ መጮህ ካለባቸው ወቅቱ አሁን ነው።ሚልዮኖች ከመርገፋቸው በፊት ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንድረስለት።



ጉዳያችን Gudayachn
 www.gudayachn.com

የመረጃ ማጣቀሻዎች

http://www.ohchr.org/EN/Issues/Food/Pages/FoodIndex.aspx

http://www.fao.org/3/a-i4145e.pdf

http://www.srfood.org/en/un-special-rapporteur-archive

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።