ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, March 25, 2012

ከ ታላቁ የ ዋልድባ ገዳም ጋር የ መንግስት ንትርክ ትርፍና ኪሳራው ሲሰላ


ብዙ ነገሮች መርፈዳቸው ያስታውቃል። ዛሬ ስለ ሃይማኖት፣መንግስት፣ልማት፣ወዘተ አዲስ ማብራርያ መስጠት  በራሱ እንዲህ ብየ ነበር ለማለት  ያህል የተሰነዘረ የ ቃላት ስብስብ ብቻ እየመሰሉኝ ከመጡ ከረምረም ብሏል ።
ዛሬ ላይ ሆነን የነገን ተስፋ ስናማትር  እንደትውልድ እና ሀገር የማያስቀጥሉን ጋረጣዎች ከፊታችን ተቀምጠው በትክክል አፍጠው እየመጡ ነው።አላየንም ብሎ  ችግሩን ላለመተው ሰው መሆን ብቻውን አስገዳጅ  መመዘኛ ይመስለኛል።ድሮ ድሮ ቤተመንግሱ ሕዝብ ምን እያለ እንደሆነ ለማወቅም ሆነ የተከፋበትን ጉዳይ ለመረዳት ነገሥታቱ ''እረኛ ምን አለ?'' ብለው ጉድለታቸውን ይለኩበት ነበር አሉ ። ዛሬ ደግሞ ምናልባት ''ፌስ ቡክ ምን አለ? ኢንተርኔት ምን አለ?'' ሳይሆን አይቀርም።የሚያሳዝነው  ግን መፍትሄ ለመስጠት ሳይሆን ማን ከነማን ጋር ቆመ? ለማለት መሆኑ ነው። 
ሰሞኑን በ ሀገራችን በቤተ እምነቱና ቤተ መንግስቱ በሁለት ጎራ ሆነው ቤተ መንግስቱን እየሞገቱት ነው።አንድም የ እስልምና እምነት ተከታዮች ወንድሞቻችን  ''መጅልሱ'' ይውረድ ብለው ባቀረቡት ጥያቄ፣ ሌላም የ ኢትዮጵያ ቤተክርስትያን መነኮሳት አባቶች ና ምእመናን  ''የ  ዋልድባ ገዳም ይዞታ  ይከበር'' ብለው። ለሁለቱም ቤተመንግስቱ መልሶችን ሰጥቷል ። መልሶቹ ግን አስገራሚ፣አስደናቂ እና አሳዛኝም  ናቸው። የሚመሩትን ሀገር ባህል ና አምነት በአግባቡ አለመረዳት ለካ ምን ያህል ትልቅ በሽታ ነው ጎበዝ!።የ ችግሩ ዋነኛ መነሻ ይሄው  አትዮጵያን ለማወቅ ኢትዮጵያዊ ሆኖ መፈጠር አልያም ህብረተሰቡ ውስጥ እይተከባበሩ ማደግን የግድ ይላልና።

በ ሁለተኛው ዓለም  ጦርነት መዳረሻ በ 1928 ዓም ኢትዮጵያ በ ኢጣልያ ተወራ በነበረችበት ወቅት  የ ኢትዮጵያ መወረር ካንገበገባቸው ብርቅዬ የ ባህር ማዶ ሰዎች መሃከል አንግሊዝያዊትዋ ወ/ሮ ሲልቭያ ፓንክረስ ይጠቀሳሉ። አኚህ የ ኢትዮጵያ ታሪክ ምሁሩ የ ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስ እናት ከ ነፃነት በሁዋላ ኢትዮጵያ መኖራቸው ና ቀብራቸውም አዲስ አበባ በሚገኘው በ መንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ መሆኑ ይታወቃል። አሁን ግን ልነግራችሁ የፈለኩት ስለ ወ/ሮ ሲልቭያ ፓንክረስ የ ልጅ ልጅ አሉላ ፓንርክረስ ነው። አሉላ በ ኢትዮጵያ ታሪክ የተሳበ ወጣት ብቻ ሳይሆን የ ማህበረሰቡ የ አኗኗር ዘይቤ በራሱ የሚማርከው ወጣት  ነው።ባልሳሳት ከ ስድስት ዓመት በፊት ይመስለኛል ከ አዲስ አበባ ከ 5oo ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኝ የገጠር አንዲት ከተማ ከመስርያቤቴ ባልደረቦች ጋር ባንድነት  ገዳም ለመሳለም በሄድኩበት ጊዜ  አዳፋ ጋቢ ለብሶ በከተማዋ መንገድ ላይ ሲሄድ አየሁት።እኔ ና ጉአደኞቼ በሚቀጥለው ቀን ለሚኖረን ጉዞ ለመዘጋጀት በ ጊዜ እራት በልተን ለመተኛት እራት የሚገኝበትን  ቤት እያሰስን ነበር። ከ አዚህ በፊት በቴሌቭዥን የማውቀው አሉላ ለምን እዚህ  መጣ ? ደግሞስ ለምን የ አደፈ ጋቢ አርጎ ይሄዳል? እኔና ጉአደኛዬ ግራ ተጋባን።በሁአላ ግን ተጠግተን ሰላምታ ተለዋውጠን  እራት አብረን እንድንበላ ጠየቅነው አላቅማማም እሺታውን ገለፀልን። በ እራት ሰዓታችን በተቀላጠፈ አማርኛው ሁሉን ተረከልን። ባጭሩ እርሱ የ ''ሶሻል ዎርክ''ትምርቱን አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ እያጠና መሆኑን፣ አሁን እዛች ከተማ ውስጥ ከመጣ አራት ወራት ማስቆጠሩን፣ለጥናቱ እንድረዳው ትንሽ  ቤት ተከራይቶ መንደር ውስጥ እንደሚኖር እና ይህም ለ ጥናቱ አስተዋፆው  እንደሆነ  ተረከልን። በነገራችን ላይ አሉላ ጥናቱን ሲሰራ ከ ህዝቡ ጋር አብሮ እየኖረ፣ጠላ ቤት አብሮ እየሄደ፣ጠጅ ቤት አብሮ እየጠጣ መሆኑን ሲነግረን። ህዝብን ማወቅ ሁሉን ነገሩን መሆን እንደሚገባ ትልቅ ተሞክሮ የሚያዝበት መሆኑን  ያስተምረናል። ለ እዚህ ነው ኢትዮጵያን ለማወቅ ኢትዮጵያዊ ሆኖ መፈጠር አልያም ህብረተሰቡ ውስጥ እይተከባበሩ ማደግን የግድ የሚለው።
ሃይማኖት ና መንግስት እስከ ደርጉ ዘመን
በ ኢትዮጵያ ታሪክ ቤተመንግስት ከ ቤተ ክህነት ጋር ባብዛኛው እየተባበሩ አልያም ቤተ ክህነቱ ቤተመንግስቱን እየመከረ ቤተመንግስቱም እየተመከረ ኖረዋል።ይህ ሁኔታ በ 1966 ቱ አብዮት ድረስ ቀጥሎ ታይቷል። የ አብዮቱ መምጣት ቤተ ክርስትያን የነበራትን የመሬት ምሪት (ምንም  የቤተ ክርስትያን ይዞታዋን  በቀጥታ አላዘዘችበትም የሚሉ ቢኖሩም) መወሰዱ በ ምመናን አስተዋፅኦ ና በ አዲሱ የ ቤተክርስትያን መዋቅር '' የ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ'' በሚል እራሷን ለመቻል ጥረት አደረገች።በዚህ ብቻ ለምግፋት አለመቻሏን ያየ ደርግም በ አካፋ ንብረቷን ወስዶ በ ማንክያ  በ ዓመት የ ሁለት ሚልዮን ብር ድጎማ ለ ቤተክርስትያን ይሰጥ እንደነበር በ ወቅቱ ጉዳዩን የሚያውቁ የሚናገሩት ነው። በ ዘመነ ደርግ ቤተክርስትያን እምነቷን ለማስፋፋት ከ ኮሚኒስታዊ አስተሳሰብ ና ፍልስፍና አንፃር ፊት ለፊት የተጋፈጠችበት፣ቅዱስ ፓትርያርኩ  ሰማአትነት የተቀበሉባት፣ብዙዎች አንደ ሊቀ ትጉሃን  ቀሲስ ጌጡ (አሁን በ ስዊድን ስቶኮልም የሚገኙት) በ ባሌ ጎባ ከተማ እግዝያብሔር አለ ብለው ለ ሃይማኖታቸው በ አደባባይ ተናግረው ለ እስር የተዳረጉበት፣ለ ደርግ ቅርበት ያላቸው የ ሶሻሊስት ርአዮት አቀንቃኝ የነበሩት ልጆቻቸውን ክርስትና ለማስነሳት ፈርተው በ ድብቅ የምፈፅሙበት ቤተክርስትያን ና ምመኖችዋ አሳዛኝ ወቅት ላይ የነበሩበት ጊዜ ነበር።
ይህ በ እንዲህ እያለ ግን ደርግ የ ሃይማኖትን በ ህብረተስቡ ውስጥ ያለውን ሚና አልረሳውም። እንደ ወቅቱ አገላለፅ ህብረተሰቡ በ ኮሚኒስታዊ አስተሳሰብ '' 'እስኪነቃ' ድረስ ሃይማኖትን አለማራቅ'' የሚል ''ራሽያው'' አስተሳሰብ ነበረው። ለ ዚህም ይመስላል የ እስልምና አና የ ክርስትና ሃይማኖቶች መሪዎች በ ወቅቱ ''ብሔራዊ ሸንጎ'' ተብሎ በሚጠራው የመንግስት  ምክርቤት ስብሰባ እንዲገኙ የሚያደርገው።በነገራችን ላይ የ ወቅቱ ምክርቤት የ ይስሙላ ምርጫ ''ኢሰፓ'' (የ ኢትዮጵያ ሰራተኞች  ፓርቲ ) ያሸነፈው ወንበር ና ባለፈው ምርጫ ኢህአዴግ አሸነፍኩ ካለው የ ምክር ቤት  ወንበር ብዛት መካከል ያለው ልዩነት የ ደርግ ከ አንድ ፐርሰንት በታች የሚበልጠው መሆኑ ነው። ይሄውም ደርግ መቶ ፐርሰንት ሲያሸንፍ አህአዴግ ግን ዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ምናምን ፐርሰንት ማሸነፉ ነው።
ሃይማኖት ና መንግስት በ ዘመነ ኢህአዴግ

ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘ ጀምሮ በጣም የሚፈራቸው (ሊገቡት ስላልቻሉ ሊሆን ይችላል) ግን ሊፈራቸው የማይገባው የነበሩ ሁለት ነገሮች አሉ። እነርሱም- የመጀመርያው ''ምርጫ'' ሲሆን ሁለተኛው '' ሃይማኖት'' ነው።የ ምርጫው ይቆየንና ሃይማኖትን ግን ለምን ይፈራዋል? ብለን ስንጠይቅ ስለ  ሁለት ምክንያቶች መሆኑ  ይታዩኛል። እነርሱም :-

Friday, March 16, 2012

የ ኤርትራ ጉዳይ ና የ ሃያ አንደኛው ክ/ዘመን ልጆች አስተሳሰብ


በ ካርታ ጫወጣ ጎበዝ አደለሁም። ግን ጆከር የተባለች ካርታ መኖሯን አውቃለሁ።ጆከር ካርታ በ ሁሉም ቦታ ስለምትገባ በ ካርታ ጫወታ ጆከር የደረሰው ሰው የማሸነፍ እድል ስላለው ፊቱ በ ፈገግታ ይሞላል።
  የ አትዮጵያ ና የ ኤርትራ  ጉዳይን መሪዎቻችን   የ ፖለቲካ መጫወቻ ''ጆከር''  ካርድ  ካደረጉት  ቆዩ።  ፕሬዝዳንት ኢሳያስም ሆኑ ጠቅላይ ሚ/ር  መለስ ይችን ''ጆከር'' የተባለችውን የ ካርታ ካርድ በየሀገራቸው ይጫወቱበታል። በስልጣን ላይ ለመቆየት ይችን የ ኢትዮጵያ ና ኤርትራ ካርድ ትመዘዛለች፣ትርገበግባለች፣ትውለበለባለች፣በ ንግግር ላይ ጣል ትደረጋለች፣አስፈላጊ ሲሆን ደሞ ወደ ፋይል ክፍል ትገባና ስትጠራ የ አራዳ ልጅ  ''ከች በ ኮረኮንች'' አንደሚለው ''አንደገና ጆከር አንደገና'' ተብላ ትመዘዛለች።

የ ሃያአንደኛው ክፍለ ዘመን ልጆች  አዲሱ አስተሳሰብ

በ ሃያኛው ክ/ዘመን አጋማሽ የተነሳ የ ኤርትራ ጉዳይ ይሄው  እስከ ትናንትና ምሽት ድረስ ካርዱ እየተመዘዘ በሰው ሕይወት መቀለዱ ቀጥሏል። ይህን ችግር የፈጠረው ትውልድ ወደድንም ጠላንም እያለፈ ነው። በእናታቸው  ከ እንደርታ (ትግራይ) የሚወለዱት ፕሬዝዳንት  ኢሳያስም ሆኑ በ እናታቸው ከ ዓዲቇላ(ኤርትራ) የሚወለዱት ጠቅላይ ሚ/ር መለስ ዜናዊ ለምን የ ጆከሯን ካርታ በየጊዜው  እየመዘዙ ሕዝቡን እንደምያሰቃዩት የሁሉም ሰው ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው ።
አንድ ነገር ግን መገንዘብ ይቻላል ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ህዝቡ የ ፖለቲከኞችን ልፈፋ ወደጎን ትቶ ነገሮችን የምያጠናበት ጊዜ ላይ መድረሱን ማንም ልብ ያለው ያለ አይመስልም። ኢሳያስም ሆኑ መለስ ካለ አንዳች ''ሃይ'' ባይ በ ፈለጉት መንገድ ላለፉት ሃያ አመታት የመሩት ሀገር ዛሬ ላይ ሲመለከቱት ብዙ ታሪካዊ ስህተቶች መኖራቸውን አፋቸው ባይናገረው ህሊናቸው ይፈርደዋል።ሁለቱም  ባለፉት ሃያ አመታት በታሪክ ታይቶ ያልታወቀ ስደተኛ በመላው ዓለም ማፍራታቸው  ቢያንስ  ለ ህዝቡ ያልሰሩት አልያም ያጎደሉት  ብዙ ሥራ መኖሩን ካልነገራቸው ጉድ  ነው።
አዎን! በ አልፈው ታሪካችን በጎ ዘመን የመኖሩን ያህል የ ፈተና ዘመን አልነበርም ማለት አይቻልም። ግን ቀይ ሽብር  አስመራ ላይ ሲሰማ አዲስ አበባም  በተመሳሳይ መንገድ ትታመስ ነበር። በየዘመኑ የነበሩ ፈተናዎች   በታሪክ አጋጣሚዎች የ ጦርነት አውድማ ያልሆኑ ቦታዎች ቢኖሩም መከራው ግን ያልጎበኘው ቤት አለ ማለት  ይከብዳል። ከዚህ ሁሉ በላይ ግን አንድ ደስ የሚል ሁሉንም የሚያስማማ ነጥብ አለ ። ይሄውም   እንደ ሕዝብ ተነስቶ  ሕዝብ በ ሕዝብ ላይ የሰራው በደል አለ ማለት ታሪካዊ ሂደቱን ና ክስተቱን አለማጠን ብቻ ነው ሳይሆን ተራ የ ፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ከመሆን የሚያልፍ አለመሆኑን ሁሉም መረዳቱ ነው። አሁን ቆም ብሎ የሚያስብ ትውልድ  ይመጣ ዘንድ መስራት አስፈላጊ ነው። ብዙዎች የተዘጋ ታሪክ የሚመስላቸው ግን ፖለቲካ፣ምጣኔ ሃብታዊ ትስስር፣ባህል፣ሃይማኖት፣ጆግራፍያዊ አቀማመጥ ወዘተ የ ሕዝቡን ችግር ከ ኢሳያሳዊ  ና መለሳዊ የ መለያየት ፖሊሲ በዘለለ ማሰብን የግድ ይላል።



ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።