ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, December 29, 2017

ኢትዮጵያ ከሥርዓት ለውጥ በኃላም ከእራሷ ጋር የታረቀች፣ ከሕዝቡ ባህል እና ስነ ልቦና ጋር የሚሄድ የችግር አፈታት መከተል እንዳለባት የሚያሳይ ልዩ ጥናታዊ ዝግጅት - ሽምግልና እና እርቅ በኢትዮጵያ (ኦድዮ)

  • ከእዚህ በፊት ፈፅሞ ሰምተዋቸው የማያውቋቸው በርካታ የሀገራችን ታሪኮች የተካተቱበት ልዩ  የድምፅ ዝግጅት 
የልዩ ጥናታዊ ዝግጅቱ አቅራቢ = ሸገር ኤፍ ኤም ስንክሳር ፕሮግራም 

ኢትዮጵያ በመንግስት ስርዓት ስትኖር የሃያ ስድስት አመታት እድሜ ያስቆጠረች አይደለችም።ከሶስት ሺህ አመታት በላይ በመንግስት ስርዓት ታቅፋ በየዘመኑ የሚገጥሟትን ፈተናዎች እያለፈች የሄደችበት ምስጢር ከባዕድ ምድር የተፈበረከ ርዕዮት ዓለም በመጠቀም አይደለም።ይልቁንም በሕዝቧ ባህል፣ስነ ልቦና፣መልካም ግንኙነት እና እምነት ሁሉ ጋር በተናበበ መልክ መሪዎቿ ከእያንዳንዱ ግለሰብ እስከ ሹማምንቶቿ ድረስ ያሉትን ችግሮች የሚፈቱባቸው ሃገራዊ የሆኑ ዘዴዎችን በመጠቀማቸው ነበር። የሸገር ራድዮ በያዝነው ታህሳስ/2010 ዓም ስንክሳር በተሰኘ ሳምንታዊ መርሃ ግብሩ 'ሽምግልና እና እርቅ በኢትዮጵያ'' በሚል ርዕስ ተከታታይ መርሃ ግብሮችን አስደምጧል።ኢትዮጵያ እንዴት እንደኖረች እና እንዴት መኖር እንዳለባት ይህ መርሃ ግብር ያመላክታል። ዝግጅቶቹን እስከመጨረሻ ቢያዳምጡ ይጠቀማሉ።

ሽምግልና እና እርቅ በኢትዮጵያ ክፍል አንድ 

ሽምግልና እና እርቅ በኢትዮጵያ ክፍል ሁለት 

ሽምግልና እና እርቅ በኢትዮጵያ ክፍል ሶስት 

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Friday, December 22, 2017

"የስኳር ኮርፖሬሽን እና ፕሮጀክቶቹን አስመልክቶ በዋናው ኦዲተር በወጣው ሪፖርት መሰረት አቃቢ ሕግ ክስ እንዲመሰረት ነበር የጠየቅነው እስካሁን ምላሽ የለም።እየጠበቅን ነው" ዋናው ኦዲተር መስርያ ቤት ድጋሚ ማሳሰቢያ።

ጉዳያችን ዜና / Gudayachn News
  
አቶ ገመቹ ዱቢሶ የዋናው ኦዲተር ቢሮ ኃላፊ 
  • መስርያ ቤቱ ለሕዝብ ይፋ ያደረጋቸው 'ጆሮ የሚጠልዙ' የሌብነት እና ዝርክርክ አሰራሮች በመተሃራ፣ወንጂ እና ተንዳሆ ፋብሪካዎች ላይ ያደረሰውን ጉዳት ያጋልጣል።
በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት መንግስታዊ መስርያ ቤቶች የመስርያ ቤቶችን የተዝረከረከ አሰራር የህወሓትን አምባገነናዊ ማሸማቀቅ በማለፍ በድፍረት ሙስናዎችን ለሕዝብ ይፋ በማድረግ በአቶ ገመቹ ዱቢሶ የሚመራው የዋናው ኦዲተር መስርያቤት አርአያነት ያለው ሥራ ሰርቷል። መስርያ ቤቱ የስኳር ኮርፖሬሽን በአቶ አባይ ፀሐዬ እየተመራ የደረሰበትን ክስረት ለሕዝብ በዝርዝር እና የኦዲት ሕግ እና ስርዓት በጠበቀ መልኩ በማቅረብ እና ሰነዱንም ለክስ በሚቀርብ መልኩ በማስረጃ አስደግፎ በመያዝ በኩልም ብዙ እርቀት እንደሄደ ይነገራል።
ይህም ሃገራዊ ኃላፊነት በሚሰማቸው የመስርያ ቤቱ ኃላፊ እና ሰራተኞቹ ብርቱ ትጋት እንደሆነ ይነገራል።

መስርያ ቤቱ በዛሬው እለት ታህሳስ 13፣2010 ዓም በዋና ኦዲተር ቢሮ ኃላፊው አቶ ገመቹ ዱቢሶ አማካይነት ለሸገር ራድዮ በሰጠው መግለጫ አቶ ገመቹ ዱቢሶ "  "የስኳር ኮርፖሬሽን እና ፕሮጀክቶቹን አስመልክቶ በዋናው ኦዲተር በወጣው ሪፖርት መሰረት አቃቢ ሕግ ክስ እንዲመስረት ነበር የጠየቅነው እስካሁን ምላሽ የለም።እየጠበቅን ነው" ማለታቸው ተሰምቷል።

መስርያ ቤቱ ለሕዝብ ይፋ ያደረጋቸው ስኳር ፋብሪካዎች ጋር የተያያዙ የሌብነት እና ዝርክርክ አሰራሮች 

በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ያለው
ስኳር  እጥረት አቶ መለስ እና ኃይለማርያም እንደሚሉት ሕዝብ በብዛት ስኳር ስለተጠቀመ ነው የሚለው ተረት ተረት ፀሐይ የሞቀው ውሸት መሆኑን ይህንን ሪፖርት የተመለከተ ሰው በቀላሉ መረዳት ይችላል። በእዚህ በህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት እና ተባባሪ ሹማምንት በተመራ የዝርፍያ እና ዝርክርክ ተግባር በኢትዮጵያ ላይ የደረሰው የጥፋት መጠን ሪፖርቱ በገለጠው የገንዘብ መጠን ብቻ ይወሰናል ብሎ መገመት ፈፅሞ እንደማይቻል መረዳት ይገባል።ከእዚህ በታች የዋናው ኦዲተር ቢሮ ያወጣው ሪፖርት በሶስቱ ፋብሪካዎች ብቻ ላይ የተጠቀሰው ዋና ዋናው ብቻ ተዘርዝሯል።

የተንዳሆ ፋብሪካን በተመለከተ 

  • የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ አፈጻጸምን አስመልክቶ ዓመታዊ የግርድፍ መሬት፣ የውሃ ገብ መሬት ርክክብና የሸንኮራ አገዳ ተከላ እቅዶች አለመሳካታቸው፣ የፋብሪካው ግንባታና ተከላ በ6 ዓመት የዘገየ ፕሮጀክት ሆኗል፣ ለፋብሪካው በአማካሪነት ከተቀጠረው ድርጅት ጋር የተገባው ውል ለ7 አመታት መራዘሙና ይህም ወደ 9.5 ሚልየን ብር ጭማሪ (713.4%) እንዲከፈል ማድረጉ፣ ለ499 ቤቶች ግንባታ ከ300 በላይ ለሆኑ ተቋራጮች ካለውል ስራ መሰጠቱ፣
  • በእዚሁ ፋብሪካ በርካታ ማሽነሪዎች ለብልሽት መዳረጋቸው፣ በማስከተልም በህወሓት ጀነራሎች የሚመራው ብረታ ብረት ኮርፖሬሽን ጋር 44 ሚልዮን ብር የሚያወጣ ለማሽነሪ መግዣ  ውል ቢፈራረምም ብረታ ብረት ኮርፖሬሽን ማሽኖቹን ሳይሰራ ከአንድ ዓመት በላይ ስለሆነ የሀገር ንብረት እንደባከነ ገልጧል፣
  • ለፋብሪካው የቲሹ ካልቸር ሥራ በሚል የተመደበው በጀትም ሆነ የወጣው ወጪ ተደብቆ እስካሁን ግልጥ አልተደረገም፣
  • ፋብሪካው ወደ ሥራ ባለመግባቱ ከ300 ሄክታር በላይ ላይ የተተከለው የሽንኮራ አገዳ ወደ ምርት ሳይቀየር እንዲገለበጥ  መደረጉ፣1349 ሄክታር ላይ የነበረ ቀደም ብሎ የደረሰ ሸንኮራ አገዳም ወደ ምርት መግባት ባለመቻሉ እንዲጣል መደረጉ እና ይህ ከፍተኛ ብክነት መሆኑ፣ 
የመተሐራ ፋብሪካን በተመለከተ 
  • የኢታኖል ፕላንት ግንባታና ተከላ ጨረታ ሂደትን የሚያሳይ ሰነድ አለመገኘቱ፤ ለግንባታና ተከላ ከተመደበው መነሻ የኮንትራት ዋጋ በላይ በብልጫ ለተፈጸመው የብር 33,859,495.41 ክፍያ ምክንያቱን የሚገልጽ የውል ማስረጃ አልተገኘም፣
  • የእንፋሎት ሀይል ማቅረብ ባለመቻሉ ከምርት ሊገኝ የሚቻል ከ68,6 ሚልየን ብር በላይ መታጣቱ እንዲሁም በግብዓትነት ሊውል የሚችል  ብር 39,193,770 የሚያወጣ ሞላሰስ መባከኑ ብሎም ብር 3,915,328.10 የሚያወጣ ከተሽከርካሪዎች ነዳጅ ጋር የሚቀላቀል 412,139.8 ሊትር ኢታኖልና ለተለያዩ የመጠጥ ኢንዱስትሪዎች በግብዓትነት የሚሸጥ ብር 2,559,388.99 የሚያወጣ 176,631.4 ሊትር ረክቲፉይድ ስፕሪት አልኮል ባለመመረቱ በድምሩ ብር 6,474,717.09 ሀገሪቱ እንድታጣ መደረጉን ደርሶበታል፣
  • በውል አፈጻጸምና ግዥ በኩል ከስኳር ኮርፖሬሽኑ ግዥ አፈፃፀም መመሪያ ውጪ ግዥ በመፈፀሙ ፋብሪካው ያልተገባ ተጨማሪ ወጪዎች እንዳወጣና በውል ያልታሰሩ ግዥዎችን እንደፈጸመም ተገልጾ በአብነት ለሥራ ላይ አደጋ መከላከያ አልባሳት ተጨማሪ ብር 168,834.89 ለሠራተኞች ዩኒፎርም ግዥ ደግሞ ብር 437,368.75 ተጨማሪ ወጪ ለሁለት አቅራቢዎች እንደከፈለ ተጠቅሷል፡፣
  • የእንፋሎት ሀይል ለማመንጨት የሚያስፈልገውን ውሃ እንዲያጣራ በብር 1,906,362 ለፋብሪካው ተገዝቶ ከህንድ የመጣና ሌሎች ልዩ ልዩ ክፍያዎች ተፈጽመውለት የተተከለ መሳሪያ ፋብሪካው ከሚጠቀምበት ነባር ቴክኖሎጂ ጋር ባለመግጠሙ ምክንያት ከሁለት ዓመታት በላይ አገልግሎት ሳይሰጥ መቀመጡ ለከፍተኛ ኪሳራ አስከትሏል፣
  • በተደረገው የነዳጅ ቆጠራ 3,224.86 ሊትር ፔትሮሊየም እና 8,304.95 ሊትር ዲዝል ከካርድ ባላንስ ጋር ሲነፃፀር አንሶ ተገኝቷል መልስ የሚሰጥ የለም 
  • በሁለት መርከብ ከውጭ ሀገር ተጭኖ ከመጣ ስኳር ውስጥ 3,777 ኩንታል የተበላሸ በመሆኑ ትክክለኛ ማስረጃ ባልተገኘለት መንገድ መቀበሩና ካሳ ያልተጠየቀበት መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ (ዘግይቶ በወጣ ሌላ ምንጭ ተቀበረ የተባለው ውሸት መሆኑ እየተገለጠ ነው።ከእዚህ ይልቅ ወደ ሀገር ውስጥ ከገባ በኃላ ሳይበላሽ እንደተበላሸ ተደርጎ እና እንደተቀበረ የተገለጠው ውሸት መሆኑ እና በድብቅ ገበያ ላይ መሸጡ የሰሞኑ ትኩስ ሆኗል)፣
የወንጂ ስኳር ፋብሪካ በተመለከተ 
  • የስኳር ፋብሪካ ማስፋፊያ የመነሻ ውል ስምምነት ላይ የፋብሪካው መጠናቀቂያ ጊዜ አለመገለጹ በተጨማሪም የፋብሪካ ግንባታና ተከላ ስራውን በአማካሪነት የተከታተለው ኩባንያ ውል ማጠናቀቂያ ጊዜ ለ8 ጊዜ እየተራዘመ ለ9 ዓመታት በመዘግየቱ ከመነሻ ኮንትራት ዋጋው በላይ ዩሮ 4,648,860  (150,190,992.82 ብር) አለአግባብ ተጨማሪ ክፍያ ለኩባንያው መከፈሉን ኦዲቱ አመልክቷል፣
  • የሸንኮራ አገዳ እርሻ ልማት ለማከናወን የመስኖ ግድብና አውታር ግንባታ የወለንጪቲ ቦፋ መስኖ ፕሮጀክት በ3 ዓመት ለማጠናቀቅ ውል ቢገባም ለ2 ዓመት ከ2 ወር ከመራዘሙ በላይ ስራዎቹ በተቀመጠላቸው ጊዜ ባለመጠናቀቃቸው ውሉ 4 ጊዜ የታደሰ በመሆኑ በድምሩ ብር 30,489,214 ከመነሻ ዋጋ ተጨማሪ ክፍያ መፈጸሙ ተገልጿል፣
  • ጂቡቲ ወደብ ተከማችተው የሚገኙ የፋብሪካ እቃዎችን በተመለከተ በፋብሪካው ለኮርፖሬሽኑ የቀረቡ የድጋፍ ጥያቄዎች አለመመለሳቸው፤ ከሞጆ ደረቅ ወደብ ለሚመጡ ዕቃዎች የገንዘብ ጥያቄን አስመልክቶ ብር 22,019,678.78 መከፈል ባለመቻሉ የመወረሻ ጊዜያቸው የተቃረበ 9 ዕቃዎችን በወቅቱ ባለማንሳት ለመጋዘን ኪራይ ብር 393,231.33 መከፈሉ ተመልክቷል፡፣
  • በንብረት አያያዝ በኩል እ.ኤ.አ በ2014/2015 በጀት ዓመት 124 ቀላል እና 41 ከባድ ተሽከርካሪዎች፤ እ.ኤ.አ በ2015/2016 በጀት ዓመት ደግሞ 172 ቀላልና 21 ከባድ ተሽከርካሪዎች በንብረት ቆጠራ ወቅት አለመገኘታቸው እና እነኝህ መኪናዎች የት እንዳሉ ማንም መልስ መስጠት አለመቻሉ፣
ባጠቃላይ የኦዲት ሪፖርቱ በገንዘብ በኩል የደረሰው ጥፋት ላይ ቢያተኩርም በእራሱ በኮርፖሬሽኑ ቀደም ብሎ ለማስፋፍያ በሚል ኢትዮጵያ ከ70 ቢልዮን ብር በላይ መበደሯ እና እስካሁን አንድም ፋብሪካ ወደ ሥራ አለመግባቱ መገለጡ ይታወቃል።ይህ በእንዲህ እያለ ነው ዛሬ ታህሳስ 13፣2010 ዓም የዋናው ኦዲተር ሥራ አስኪያጅ አቶ ገመቹ ከላይ የተጠቀሱት ጉድዮች በሕግ እንዲጣሩ ከማስረጃ ጋር ለአቃቢ ሕግ የላክን ቢሆንም እስካሁን መስርያቤቶቹም ሆኑ አቃቢ ሕግ ምላሽ አልሰጠም።ይልቁንም በባሰ ሁኔታ ችግሮች እየቀጠሉ መሆኑን ይገልጣሉ። ከእዚህ በተጨማሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከ80 ሚልዮን ብር በላይ መፈረም ያለበት ኃላፊ ሳይፈርም ወጪ መደረጉን የኦዲት መስሪያ ቤቱ ቢገልጥም እስካሁን ምላሽ አለመሰጠቱን ዜናው ያብራራል።የኢትዮጵያ የሙስና እና የባለስልጣናቱ የዘረፋ ደረጃ ከምንገምተው በላይ ነው።የስኳር ፋብሪካ ፕሮጀክት ቅሌት በትንሹ ምን ያህል የሰፋ ምዝበራ እንደሚደረግ የሚያሳይ አንዱ ናሙና ነው።በእዚህ መልኩ በእያንዳንዱ ሴክተር ውስጥ ያለውን የዘረፋ ጥልቀት ምን ያህል እንደሆነ ማወቅ ይቻላል።የኦዲት መስሪያ ቤት ለእያንዳንዱ ክሶቹ በቂ በሰነድ የተያዘ ማስረጃ እንዳለው እና ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ የኦዲት ምርመራ ደረጃ መስራቱን አክሎ ገልጧል። 

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Thursday, December 14, 2017

የአድዋ ስርወ-መንግስትነቱን በበለጠ ያረጋገጠው ህወሓት አሁንም በያዘው የመግደል መንገድ ከቀጠለ መውጊያው ለእራሱ ይብስበታል (የጉዳያችን ማስታወሻ )


  • አይናችን የወገኖቻችንን አስከሬን ለመደ ?
  • ኦህዴድ ሳይቀር ያልጠራናቸው እና ያልጋበዝናቸው ታጣቂዎች እንዴት ወደ ክልሉ እንደመጡ እንደማያውቁ እና አለመጋበዛቸውን መግለፁ የይስሙላውም የኢህአዴግ ማዘዣ ጣብያ ሙሉ በሙሉ መፍረሱን ያሳያል።
ኢትዮጵያ ለህወሓት ስልጣን እና ለአድዋ መንደር እና የቤተሰብ ትስስር ሐብት የማጋበስ ሰይጣናዊ ተግባር ሲባል እንድትበታተን ብቻ ሳይሆን አለ የተባለ የህዝቧ ቁስል እየተፈለገ በህወሓት የተንኮል ስለት እየተከፈተ ለዘመናት አብሮ የኖረ ሕዝብ ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገም የልጅ ልጆቹ አብረው እንዳይኖሩ  እለት እለት በቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው ተንኮል በሚያደሩ ባለሙያዎች እልቂት እንደተደገሰለት ይታያል።

ስለ ህወሓት አሁን እዚህ አጭር ማስታወሻ ላይ እንደ አዲስ ለመተረክ የማስታወሻዬ አላማ አይደለም።ምክንያት ብዙዎች በሚገባ ተንትነውታል። አሁን የሰሞኑ የህወሓት ድርጊት (ከእዚህ በፊት የነበረ ተግባሩ ቢሆንም)  ገና ከሃያ ሁለት ዓመት ያልዘለሉ ለጋ ወጣቶችን በሀገሪቱ ከአስራ አምስት ዩንቨርስቲዎች በላይ በሚገኙ ካምፓሶች መኝታ ቤት ድረስ ቦንብ እና ክላሽ የታጠቁ የአጋዚ ሰራዊት እያሰማራ፣ የመኝታ ቤታቸውን በር እየሰበረ ከተማሪ ደብተር እና እርሳስ ሌላ በእጃቸው አንዳች የማያውቁ የኢትዮጵያ የነገ ተስፋዎችን በእየሜዳው ላይ አስከሬናቸውን አነጠፈው፣ደማቸው እንደ ውሃ ፈሰሰ።ከወልዲያ እስከ ነቀምት ያሉ ዩንቨርስቲዎች በሽብር ተወጥረው፣ የእናት የአባታቸውን ፊት ሳያዩ ለማደር የሚደነግጡ ታዳጊ ወጣቶችን በቂም እና በዘረኝነት ጥላቻ በተሞላ ስሜት ቁጥራቸው ያልታወቁ ኢትዮጵያውያውን ሕይወት ተቀጥፏል።

በጉዳዩ ዙርያ ወላጆች ስለልጆቻቸው መረጃ እንዳያገኙ ብቻ ሳይሆን ተማሪዎች ወደ ቤተሰብ ቀርቶ ወደ አካባቢው አብያተ ክርስቲያናት እንዳይሄዱ እና እንዳይጠለሉ አስከሬን በወጣበት ግቢ ውስጥ ተማሪዎች በግድ አርፋችሁ ተማሩ  መውጣት አትችሉም ተብለው ዙርያውን በወታደር እያጠረ የቤተሰብ ሰቀቀን ሳምንት ሆነው ሳምንታቱ አልፈዋል። ይህ ብቻ አይደለም። ተማሪዎቹ ለወላጆቻቸው ደውለው ወይንም በማህበራዊ ሚድያ ደህንነታቸውን እንዳይናገሩ ወይንም በግቢው ውስጥ እየተፈፀመ ስላለው ጉዳይ ለተቀረው ዓለም እንዳይገልጡ የኢንተርኔት እና ስልክ አገልግሎት ቆርጦ ወጣቶቹን ሲያሰቃያቸው ነው የከረመው።

የሰሞኑ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች አዲስ  የሚያደርገው አንዱ እና አይነተኛ ምክንያት በመላው ሀገሪቱ ውስጥ ትግራይን ጨምሮ ግጭቶች መፈጠራቸው እና ይህንን ተከትሎም ቀደም ብለው የተጀመሩ ሕዝባዊ አመፆች በአዲስ መልክ መነሳታቸው ነው።ከእዚህ በተለየ የስርዓቱ ታጣቂዎች አድሏዊ ተግባር በሕዝቡ ዘንድ ብቻ ሳይሆን የኢህአዴግ አባል ድርጅት በሚባለው በኦህዴድ ሳይቀር ያልጠራናቸው እና ያልጋበዝናቸው ታጣቂዎች እንዴት ወደ ክልሉ እንደመጡ እንደማያውቁ እና አለመጋበዛቸውን እንዲሁም በመንግስት ደረጃ የጨለንቆ እልቂትን አለማውገዝ ከመተባበር እኩል መሆኑን የገለጡት  የኦሮምያ ፕሬዝዳንት እና ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች መሆናቸው አድዋ መሩ የህወሓት አካል ከአባል ድርጅቶች ከሚላቸው ጋር የተፋጣበት እርቀትን  ነው። እዚህ ላይ የኦህዴድ  ያልጠራናቸው እና ያልጋበዝናቸው ታጣቂዎች እንዴት ወደ ክልሉ እንደመጡ እንደማያውቁ እና አለመጋበዛቸውን መግለፁ የኢህአዴግ የይስሙላውም ማዘዣ ጣብያ ሙሉ በሙሉ መፍረሱን ያሳያል።

የሰሞኑ የኢትዮጵያ ከራሞት ኢትዮጵያ በቀጥታ በአድዋ የፖለቲካ ስርወ መንግስት እና በቀረው የኢትዮጵያ ክፍል መካከል ቀጥተኛ የጎሳ ግጭት እንዳይፈጠር ያሰጋል።ይህ ግጭት ደግሞ እንደ አዲስ አበባ ባሉ ከተሞች ላይ  የሆነ ቦታ በቀን ሰራተኞች መካከል በተነሳ ጠብ ቢጫር በቀጥታ የአድዋ መንግስት ደጋፊዎች በሕዝቡ ላይ የሚያደርሱት እልቂትም ሆነ በበደል የተማረረው እንዲሁም ልጆቹን ለከፍተኛ ትምህርት ልኮ እንደወጡ የቀሩበት በሚልዮን የሚቆጠር ሕዝብ በቀጥታ ወደ ከፍተኛ የቁጣ መገንፈል እንደሚሸጋገር ምንም ጥርጥር የለውም። ይህንን ሁኔታ ደግሞ እያባባሱ ያሉ የአድዋ መንግስት አድናቂዎች እና የጥቅም ተጋሪዎች  በማኅበራዊ ሚድያ በምስኪኑ ኢትዮጵያዊ ላይ የሚያሳዩት ንቀት እና ስድብ እንዲስተካከል የሚመክር አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን በሕግ የሚጠይቅ የሕግ አካል አለመኖሩ ነው ጉዳዩን የከፋ የሚያደርገው።

ይህ በእንዲህ እያለ ግን ሁለት  አደገኛ ሁኔታዎች በሕዝብ ዘንድ እየታየ ነው። ይሄውም የወገኖቻችን መገደል በእየለቱ በመስማት፣አስከሬን በማየት እና የሚፈሰው ደም በተገቢው ደረጃ የማይሰቀጥጠው ሰው የመኖሩ አደጋ እና ስሜቱ የተነካውም በተገቢ የቁጣ ደረጃ ለመብቱ የመነሳት ፍጥነት በተለይ በአዲስ አበባ እየታየ መሆኑ ነው።ይህ ማለት ከንፈሩን ከመምጠጥ ባለፈ ቁጣውን በተገቢው የማይገልጥ ወይንም እንዳላየ የሚያልፍ ሕዝብ በተለይ በአዲስ አበባ ነዋሪ ዘንድ መታየቱ የአዲስ አበባ ሕዝብ የሚከፍለው ዋጋ እንዳይንር ያሰጋል።ይህ ወቅት  የአድዋ የቤተሰብ መንግስት ስልጣኑን እንዲለቅ፣ ሕዝብ በጎሳ እንዳይተላለቅ የማኅበራዊ እና ሃይማኖታዊ አደረጃጀቶች እንዲጠናከሩ የሚሰራበት ጊዜ እንጂ እንዳላዩ የሚያልፉበት ጊዜ አይደለም።ምሁሩ፣ወታደሩ፣ፖሊሱ፣ተማሪው፣ገበሬው እና የከተማ ነዋሪው በአንድነት በኢትዮጵያዊነት ስሜት የሚነሳበት እና በአድዋ መንደር ስር በመጡ ስብስቦች የሚንቀሳቀሰው የህወሓት ድርጅት በተቻለ መጠን የበለጠ ጥፋት ሳያደርስ የሚንቀሳቀሱበት እንጂ በእየለቱ በማኅበራዊ ሚድያ እና በቴሌቭዥን መስኮቶች ለጋ ወጣቶች አስከሬን እያየን አይናችን ተመልክቶ ከማዘን፣ከመበሳጨት እና ከመቆጨት ባነሰ መልኩ አስከሬን እያየን የመልመድ በሽታ እየተጠናወተን እንደሆነ መመልከት ይቻላል።የወጣቶቹ ሞት የኢትዮጵያ ሞት ብቻ ሳይሆን ነገ ለእያንዳንዱ ቤተሰብ የተደገሰ የጥፋት ድግስ መሆኑን  ተረድቶ በኅብረት ለሃገር ማዳን ተግባር መነሳት ይገባል።

ህውሓት በመላ ሀገሪቱ ላይ አንድ ዓመት ፈጅቶ የፈፀመው እና ብዙዎች ያለቁበት  አዋጅ ለውጥ ያላመጣለት መሆኑን ከተረዳ በኃላ በእያነሳውም በተግባር ግን አዋጁ ወትሮም ኢትዮጵያ ስትገዝበት የነበረው የበደል አይነት ሁሉ እየተፈፀመ እየተተገበረ ነው።የግፍ አገዛዙን  የስልጣን መጠበቂያ አጥር አድርጎ የሚመለከተው የአድዋ ዘመዳሞች መንግስትሬም ኢትዮጵያን በደም እየነከረ  አዲስ አበባን በቅርቡ በአመፅ የምትፈነዳ ከተማ አድርጎ የአመፅ ቀለበት ውስጥ ገብታለች።አዲስ አበባ ትንሽ ምክንያት የሚሆን ኮሽታ ብቻ የምትጠብቅ ከተማ እንደሆነች ለማንም ግልፅ ሆኗል።ይህንን የተረዱ ዓለም አቀፍ ድርጅት ሰራተኛ ኃላፊዎች በሰበብ አስባቡ ከሀገር እየወጡ የምከርሙበት አንዱ ምክንያት ይሄው በማንኛውም ጊዜ ሊፈነዳ እንደሚችል የሚነገረው ሕዝባዊ አመፅ ፍራቻ እንደሆነ ጉዳዩን በእገባ የሚያውቁ የቡና ላይ ወሬ ካደረጉት ሰንብተዋል። ምናልባትም በመጪዎቹ ጥቂት ሳምንታት ውስጥ የአዲስ አበባ ድምፅ አይሰማም ማለት አይቻልም። እዚህ ላይ አስገራሚው ጉዳይ ህወሓት ችግሩ የአድዋ ስርወ መንግስት የጎሳ ፖለቲካ መሆኑን የረሳ እየመሰለ ችግሩ ከአቶ ሃይለማርያም ለማስመሰል አቶ ኃይለማርያምን በመቀየር መፍትሄ ያመጣ ለመምሰል ሽር ጉድ እያለ ነው። ቀድሞም የህዝቡን ድምፅ የመጨፍለቅ ሥራ የሚሰራው  እና ትዕዛዙ ለይስሙላ በአቶ ሃይለማርያም ይምሰል እንጂ ዋና ማዘዣ ጣቢያው የሚመጣው ከህወሓት ቢሮ መሆኑ ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው።ትልቁ ቁም ነገር ይህ ሁሉ እልቂት እየተፈፀመ ያለው የህወሓት መንግስት ስልጣን ለሕዝብ አላስረክብም በቀደድኩላችሁ ቦይ ብቻ ፍሰሱ  የሚል የእብሪት ተግባር ምክንያት መሆኑን ሁል ጊዜ መዘንጋት የሌለበት ነው።ህወሓት ኢትዮጵያ ትጥፋ እንጂ ስልጣን አልለቅም ሂደቱ ሁላችንን ኢትዮጵያውያንን መጪውን በመፍራት አርፈን የምንገዛ አድርጎ የማሰብ የአስተሳሰብ ድህነት ብቻ ሳያሆን  የኢትዮጵያን ሕዝብን ስነ ልቦና ደረጃ ያለመረዳት ችግር ነው።

ባጠቃላይ በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ ከመጥፎ መጥፎ ይመረጣል።ሁሉም መጥፎ አካሄድ ቢሆንብህ የተሻለውን መጥፎ መምረጥ ብቻ አማራጭ የሚሆንበት አጋጣሚ በሀገሮች ታሪክ የሚያጋጥም እውነታ ነው።ሳይንገጫገጩ ያሰቡበት መድረስ የለም። ህወሓት በስልጣን ላይ እያለ ከሚመጣው የመከፋፈል አደጋ ይልቅ የተከፈለው መስዋዕትነት ተከፍሎ ሕዝብ ነፃነቱን ማወጅ እንደሚመርጥ እና አሁን እየሆነ ያለው ሁሉ ሕዝብ  ለበለጠው ትግል ከመነሳት ሌላ አማራጭ እንደሌለው  እንጂ አንዳች ወደ ኃላ እንደማይገፋው ማወቅ ተገቢ  ነው።ችግሩ እየገፋ ስመጣ እና ጉዳይ የትግራይ መሬትን እንደ ሌላው የኢትዮጵያ ፍል መቆርቆር ሲጀምር የአድዋው ስርወ መንግስት በእራሱ በትግራይ ሕዝብም ጭምር አደጋ ላይ መውደቁ አይቀርም።ለእዚህ ነው ህወሓት አሁንም ለእውነተኛ ለውጡ ካልተነሳች መውጊያው ለእራሷ ይብስባታል የምለው። ፈተናው ሲበዛ መውጫው ይጠባል።ህወሓት ከሁሉም ስጋት ውስጥ የገባው የትግራይ ሕዝብ በአድዋው የቤተሰብ መንግስት ላይ ይነሳብኛል በሚለው ስጋት ነው።
ይህንንም  ስለሚያውቅ ነው የትግራይ ተወላጆችን ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ግጭት ውስጥ ለማስገባት አንዴ በስፖርት ሌላ ጊዜ በዩንቨርስቲ ተማሪዎች መሃከል በሚነሱ ጠቦች ሕዝቡን ለማስደንበር የምሞክረው።ለምሳሌ የወልዲያው የስፖርት ጫወታ ግጭት ላይ ህወሓት ቢያንስ በደህንነቱ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ቀድሞ ያውቃል።የአቶ ጌታቸው ቢሮ ግን ጫወታው እንዲሰረዝ አላደረገም። ይልቁንም ለግጭቱ ምክንያት እንዲሆን በከተማው ውስጥ ከትግራይ የመጡ ወጣቶች በፒክ አፕ መኪና እየተዘዋወሩ አላስፈላጊ ቃላት እንዲሰነዝሩ አደረገ።አንድ የስፖርት ጫወታ አይደለም ውጥረት መኖሩ እየታወቀ ቀርቶ ኃይለኛ ዝናብ በመኖሩም ይሰረዛል። ለህወሓት ግን የትግራይ ሕዝብ ብቸኛ ተከላካይ መሆኑን ለመንገር ይህንን ግጭት እያወቀ ሕዝብ እንዲገባ አደረገ።በምላሹ በአዲግራት ዩንቨርስቲ እና ሌሎች ቦታዎች በፈለገው መንገድ ተቀጣጠለለት ህ አካሄድ ለህወሓት መውግያውን ያስለዋል እንጂ መፍትሄ አይሆንም። የመጨረሻው ብሔራዊ ተቃውሞ በመላ ሀገሪቱ አዲስ አበባን ጨምሮ የተነሳ ጊዜ ህወሓት የቀረ እንጥፍጣፊ ሃሳብ ለማስረዳት ፋታ አገኛለሁ ብሎ ካሰበ ፍፁም  ሕልም እንደሚሆን ከአሁኑ ብረዳው ጥሩ ነው።

እስከመጨረሻው ሊያዳምጡት የሚገባ ቁምነገረኛ ዜማ ከአርቲስት ስለሺ ደምሴ - ጋሽ አበራ ሞላ (ቪድዮ ከስር ይመለቱ)



ጉዳያችን GUDAYACHN 

 www.gudayachn.com

Tuesday, December 12, 2017

በሃያኛው ክ/ዘመን የኢትዮጵያን ፊደል በመላው ኢትዮጵያ እንዲዳረስ ያደረጉ የቀኝ አዝማች ተስፋ ገብረስላሴ ሥራ፣ታሪክ እና ስኬት ላይ ያተኮረ ጥናታዊ ፊልም

"ድንቁርና ይጥፋ፣
ዕውቀት ይስፋ!  
ይህ ነው የኢትዮጵያ ተስፋ።"   ቀኝ አዝማች ተስፋ ገብረ ስላሴ መመርያ 

ጉዳያችን/ Gudayachn 

ምንጭ : - ዓውደ ሰብ ዝግጅት 

ክፍል አንድ 

ክፍል 2


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Saturday, December 9, 2017

የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ የኢትዮጵያ የሲቪክ እና የፖለቲካ ድርጅቶች በወቅቱ የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያላቸው ሚና በሚል ርዕስ በቀረበ ውይይት ላይ የአቶ ገረመው እና አቶ ሳሊኒ መነሻ ጽሁፍ (ቪድዮ)

ህዳር 30/2010 ዓም ኦስሎ ላይ የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ የኢትዮጵያ የሲቪክ እና የፖለቲካ ድርጅቶች በወቅቱ የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያላቸው ሚና በሚል ርዕስ በቀረበ ውይይት ላይ የአቶ ገረመው እና አቶ ሳሊኒ መነሻ ጽሁፍ በርካታ ጉዳዮችን በርዕሱ ዙርያ የዳሰሰ ነበር። አቶ ገረመው ንጋቱ እና አቶ ሳልህ አብርሃም የቀረቡ መነሻ ሃሳቦች በርካታ ጉዳዮችን የዳሰሱ ነበሩ። አቶ ገረመው ንጋቱ በግጭት አፈታት (conflict resolution) ላይ የሁለተኛ ዲግሪያቸውን የሰሩ ሲሆን አቶ ሳልህ አብርሃም ደግሞ በኖርዌይ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ራድዮ ኃላፊ ሆነው አገልግለዋል።

አቶ ገረመው ንጋቱ ያቀረቡት 


በአቶ ሳልህ አብርሃም የቀረበው 




ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Wednesday, December 6, 2017

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የሞባይል አፕሊኬሽን አስመረቀ።በሞባይል አፕሊኬሽን የሚጠቀሙ ደንበኞች ለትኬት ከሚከፍሉት ክፍያ የ10% ቅናሽ ያገኛሉ።Ethiopian Airlines introduces new mobile app. Customers will enjoy 10% discount on all mobile bookings.




ጉዳያችን ዜና / Gudayachn News

(Read in English below)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የሞባይል አፕሊኬሽን አስመረቀ።ደንበኞች በአፕሊኬሽኑ ተጠቅመው ቀድመው ቦታ መያዝ፣ትኬት ማውጣት እና የቦርዲንግ ለውጥ ቢኖርም በቀላሉ ለማወቅ ያስችላቸዋል።
ከእዚህ በተጨማሪ በሞባይል አፕሊኬሽን የሚጠቀሙ ደንበኞች ለትኬት ከሚከፍሉት ክፍያ የ10% ቅናሽ እንደሚያገኙ ዜናው ይጠቁማል። ዝርዝሩን አየር መንገዱ ትናንት የለቀቅውን ሙሉ ዜና ከስር ያንብቡ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት ወደ አምስቱም አህጉሮች የሚበር ሲሆን ከአንድ መቶ በላይ መዳረሻዎች አሉት።
ኢትዮጵያ አየር መንገድ ማስታወቂያ አጭር ቪድዮ 


Ethiopian Airlines, the largest Aviation Group in Africa and SKYTRAX certified Four Star Global Airline, is pleased to announce that it has launched a brand new Mobile Application, which encompasses an array of features that enhance customers’ travel experience with simplified and end-to-end options for flight booking and management by using their Android mobile devices. 
On the occasion of the launch of Ethiopian Mobile Application, Mr. Tewolde GebreMariam, Group CEO of Ethiopian Airlines remarked:
 “In the age of “the internet of things” and “Artificial Intelligence” I am very happy that our “mobility” project is fast advancing which enabled us to announce to our esteemed customers that Ethiopian Mobile Application has gone live. The Mobile Application is a critical piece of our overall strategy to bring our customers’ travel experience to another level by leveraging on Information and Communication technology and African Flavored Ethiopian Hospitality.  
With this new Mobile Application, customers will be able to use their mobile devices to book their flights, do their flight check-in, issue their boarding pass and self-board their flights, check the status of their flight, get actual arrival and departure times of ET flights and remain connected and informed throughout their journey in real-time.
As a customer focused airline,we are continuously working very hard to avail cutting-edge and user-friendly solutions that will improve our customers ‘overall experience and meet their ever-increasing expectations.”
Customers will enjoy 10% discount on all bookings made through Ethiopian Mobile App.
Click on the link below to download your Ethiopian Airlines Application.
About Ethiopian
Ethiopian Airlines (Ethiopian) is the fastest growing Airline in Africa. In its seventy plus years of operation, Ethiopian has become one of the continent’s leading carriers, unrivalled in efficiency and operational success.
Ethiopian commands the lion’s share of the pan-African passenger and cargo network operating the youngest and most modern fleet to more than 100 international passenger and cargo destinations across five continents. Ethiopian fleet includes ultra-modern and environmentally friendly aircraft such as Airbus A350, Boeing 787-8, Boeing 787-9, Boeing 777-300ER, Boeing 777-200LR, Boeing 777-200 Freighter, Bombardier Q-400 double cabin with an average fleet age of five years. In fact, Ethiopian is the first airline in Africa to own and operate these aircraft.
Ethiopian is currently implementing a 15-year strategic plan called Vision 2025 that will see it become the leading aviation group in Africa with seven business centers: Ethiopian Express & Ancillary Services; Ethiopian International Services; Ethiopian Cargo Services; Ethiopian MRO Services; Ethiopian Aviation Academy; ET In-flight Catering; and Ethiopian Ground Services. Ethiopian is a multi-award winning airline registering an average growth of 25% in the past seven years. 
For more information about this press release, please contact:
Mrs. Aniley Eshetu
A/Manager Corporate Communications, Ethiopian Airlines
Tel :( 251-1)517-89-07/656/165/913/529

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Thursday, November 30, 2017

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሰላሳ ቀናት ውስጥ በሶስት የአውሮፓ ከተሞች ሶስት አብያተ ክርስቲያናት ገዛች፣ የኦስሎ ቤተክርስቲያን ህንፃ ኮሚቴ ትውልድ አኩሪ እንቅስቃሴ ማድረጉ አስመስግኖታል።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና ምእመናን የተመለከተ የፔው ምርምር ማዕከል አዲስ ዓለም አቀፍ ጥናት ይፋ አደረገ (የጥናቱን ሙሉ ይዘት ይዘናል)



ኦስሎ፣ኖርዌይ ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አቡነ ሕርያቆስ ቀሲስ ካሳሁን እና ዲያቆናት እሁድ ህዳር 17/ 2010 ዓም  ቅዳሴ ሲያሳርጉ 

ጉዳያችን / Gudayachn

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሰላሳ ቀናት ውስጥ  በሶስት የአውሮፓ ከተሞች ሶስት አብያተ ክርስቲያናትን ገዛች

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በሶስት የአውሮፓ ታላላቅ ከተሞች  ሶስት አብያተ ክርስቲያናትን ገዝታለች።እነርሱም በፍራንክፈርት ጀርመን የመድሃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን፣ኦስሎ ኖርዌይ ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት እና ለንደን እንግሊዝ የደብረ ገነት ቅድስት ስላሴ ቤተ ክርስቲያን ናቸው።አውሮፓ ውስጥ ሃይማኖተኛ ሳይሆን በእግዚአብሔር ማመን እና አምልኮት መፈፀም ብርቅ እየሆነ የመጣበት አህጉር ሆኗል።በመካከለኛው ዘመን በአውሮፓ ድንቅ ጥበብ የታዩባቸው በርካታ ህንፃ አብያተ ክርስቲያን ይገኛሉ። እነኝህ አብያተ ክርስቲያናት ግን በሰንበት ቀኖችም ሆነ በበአላት ቀናት በውስጣቸው አምልኮተ እግዚአብሔር የሚፈፅም ምእመናን አይገኙም።በእርግጥ ለአውሮፓውያን የልደት በዓል ዋዜማ አመታዊ ኮንሰርት የሚደረግባቸው አብያተ ክርስቲያናት በዋና ዋና ከተሞች ውስጥ አሉ። 

አሁን አውሮፓ ውስጥ እየሆነ ያለው ከእዚህ የከፋም ነው። አብያተ ክርስቲያናት ለምሽት ክበቦች የመሸጥ እና የመከራየት ዕጣ እየደረሰባቸው ነው።ይህ እየሆነ ባለበት ሰዓት ነው እንግዲህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በሚልዮን የሚቆጠር ዶላር እያወጣች እየገዛች ያለው።ግዥዎቹ የተፈፀሙት በአውሮፓ የሚኖሩ ምእመናን በሚያዋጡት እና ከባንክ በሚገኝ የእረጅም ጊዜ ክፍያ ብድር ነው።
አዲስ የተገዛው  የለንደን እንግሊዝ የደብረ ገነት ቅድስት ስላሴ ቤተ ክርስቲያን 
አዲስ የተገዛው የኦስሎ ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን 
ጀርመን ፍራንክፈር የመድሃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ግዢ ሲፈፀም የደብሩ አስተዳዳሪ መላከ መዊ ልሳነ ወርቅ ሲፈርሙ 

የኦስሎ ቤተክርስቲያን ህንፃ ኮሚቴ ትውልድ አኩሪ እንቅስቃሴ ማድረጉ አስመስግኖታል
ኦስሎ ቅዱስ ገብርኤል አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የህንፃ ጨረታ ሂደት እና ለግዥ የሚሆን የገንዘብ ማሰባሰብ (አብዛኛውን ገንዘብ) ስራውን በአንድ ወር ውስጥ ማሰባሰብ መቻሉ እና ምእመናንን በሚገባ ማንቀሳቀሱ ከፍተኛ አድናቆትን አስገኝቶለታል።የህንፃ ኮሚቴ በቅርብ አመታት ውስጥ በአዲስ መልክ ከተመሰረተ በኃላ መሬት ገዝቶ ቤተ ክርስቲያን የመገንባት፣ አብያተ ክርስቲያናትን መግዛት ወይንም የባህል ማዕከል ገዝቶ ወደ ቤተ ክርስቲያን መቀየር የሚሉ አማራጮችን ይዞ ወደ ሥራ ገብቷል።

ይህ በወጣቶች የተገነባው የህንፃ ኮሚቴ በተለይ ባሳለፍነው ወር ውስጥ የህንፃ ጨረታ ግዢ ሂደት ላይ ኮሚቴው በበቂ መልኩ ያደረገው የአሰራር ብቃት፣ከምእመናን ጋር የነበረው የግንኙነት መስመር እና ሁሉንም ምእመን የማስተባበር ሥራ መሰራቱ ከእግዚአብሔር ፍቃድ ጋር ተጨምሮ ለፍሬ ሊበቃ ችሏል።የህንፃ ኮሚቴው አባላት እንቅልፍ አጥተው ያደሩባቸው ሌሊቶች፣ ከስራ ለበርካታ ቀኖች የቀሩባቸው ጊዜዎች እና በታማኝነት የምመናንን አስተዋፅኦ ጠብቀው ለቤተ ክርስቲያን ጨረታ መልካም ውጤት ቤተ ክርስቲያንን አድርሰዋታል።ከእነኝህ ውስጥ ሁለቱን ክስተቶች ብቻ መጥቀሱ የነበረውን ውጣ ውረድ ሊያሳይ ይችላል።

የእሁዱ ለቅሶ 

የኦስሎ ቅዱስ ገብርኤል አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ህንፃ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ተክሉ ጨረታው በተሰማበት የመጀመርያ እሁድ ከቅዳሴ በኃላ ስለ ጨረታው ምንነት፣ ቤተ ክርስቲያን ያላት ገንዘብ መጠን እና ከባንክ ሊገኝ የሚችለው ገንዘብ እና  ኮሚቴው ሊሰራ ያሰባቸውን ስራዎች አብራሩ።ይህች እሁድ ምእመናን በቤተ ክርስቲያን በስሜት ያለቀሱበት፣ ሁሉም በአንድነት በተሰበረ ልብ ሆነው ምን እናድርግ እያሉ የተመካከሩበት ሰንበት ነበር። በእዚህ ሁሉ መሃል የህንፃ ኮሚቴ አባል ወ/ሮ ሶስና ሳግ በቀላቀለው እና ከውስጧ ፍልቅል ብሎ በወጣ የለቅሶ ድምፅ  እያሰማች ቆመች እና መናገር ጀመረች: -
" እኔ በጣም ይቅርታ አድርጉልኝ ይህንን ነገር ሳልናገረው ማለፍ አልችልም። ትናንት ምሽት ላይ ከአረብ ሀገር ቤተ ክርስቲያን ጨረታ ላይ መሆናችንን የሰማች እህት እያለቀሰች ያወራችኝን ልንገራችሁ።ልጅቷ ከአሳዳርዎቿ ተደብቃ መንገድ ላይ ወጥታ እንደምትደውል ስትነግረኝ እያለቀሰች ያለችኝ 200 ዶላር አለች ከሰራሁት እሷኑ እልካለሁ አለችኝ''  ብላ ወ/ሮ ሶስና ስትናገር ምእመናን ስሜት ይብሱን ተነካ።ለጥቂት ሰኮንዶች ፀጥታ ሰፈነ።በአረብ ሀገር በጉልበት ሥራ የምትሰራ እህት አውሮፓ ላለ ቤተ ክርስቲያን ልቧ ተነክቶ እንቅልፍ አጥታ አምሽታ ምሽት ላይ መንገድ ዳር ወጥታ ስልክ ደውላ ከሰራቻት የወር ክፍያ ላይ 200 ዶላር ለመክፈል ያውም ከእንባ ጋር ለሕንፃ ኮሚቴ አባል ደውላ ጠይቃለች።ጉዳዩ እራስን ለመመልከት እና እኔ ምን አደረኩ? የሚያስብል ልዩ ድባብ የፈጠረ ሰንበት ነበር።

ወ/ሮ ሶስና  ሃብተ ማርያም የቤተ ክርስቲያን ህንፃ ኮሚቴ  ገቢ አሰባሳቢ ክፍል ኃላፊ ባለፈው ዓመት ኮሚቴው ባዘጋጀው ዝግጅት ላይ  ስታስተባብር  
(ቀኑ ቅዳሴ ያለበት  ቀን ሳይሆን ድራማ እና ልዩ ልዩ የገቢ ማስገኛ ዝግጅቶች የቀረቡበት ከኖርዌይ የፍቅር እስከ መቃብር መፅሐፍ ወደ ኖርዌይ የመለሰው ደራሲ እና ልዩ  ልዩ እንግዶች የተገኙበት የምእመናን የጋራ መገናኛ ቀን ነበር። ከጀርባ  ያሉት ያን ጊዜ መላክ ብስራት አባ ሀብተየሱስ  አሁን አቡነ ሕርያቆስ ለልጆች መማርያ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ያዘጋጀውን መፅሐፍ ሲያስተዋውቁ ነው)

 ለሁለተኛ ጊዜ የተራዘመው እና የመጨረሻው ጨረታ ሊጀመር 24 ሰዓታት ሲቀሩት  

የቤተ ክርስቲያኑ የጨረታ ጊዜ ሁለት ጊዜ ተራዝሟል።ለእዚህም ምክንያቱ አዳዲስ አመልካቾች በመምጣታቸው ነበር።የኦስሎ ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጨረታ ልዩ የሚያደርገው አንዱ ምክንያት በኖርዌይ ውስጥ ቤተ ክርስቲያን ለጨረታ ብቻ ሳይሆን ለሽያጭ ማቅረብ ከቆመ አመታት ሆኖታል ሆኖም ግን የእግዚአብሔር ፍቃድ ሆኖ ይህ የተገኘው ቤተ ክርስቲያን ቀደም ብሎ በግለሰብ ተይዞ በመኖሩ ለሽያጭ ሊቀርብ ችሏል።ይህ ምናልባት ከብዙ አመታት በኃላ የሚያጋጥም ዕድል ነው።

በጨረታው ላይ ከአምስት በላይ ድርጅቶች ከመሳተፋቸው በላይ ለሁለት ቀናት ያህል የቆየ እልህ አስጨራሽ ነበር።ከጨረታው ከመጀመሩ 24 ሰዓታት በፊት በሕንፃ ኮሚቴው ውስጥ በወሳኝ አገልግሎት ላይ ከሚገኙት ውስጥ የኮሚቴው ሰብሳቢ ዶ/ር ተክሉ በድቁና ከሚያገልግሉት አንዱ ልጁ እንዳመመው ይሰማል።ይህ ሲሆን ሁለት ቀናት በጨረታ በጋራ ከሚከታተልበት ከአቡነ ሕርያቆስ ቤት ነበር።ሆኖም ግን ልጁን ሄዶ ለማየት አልቻለም።ልጁ ሆስፒታል ደርሶ ሲመለስ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ እዚህ እየጠበቀው ነበር እና አሁንም ሄዶ ማየት አልቻለም።

ዶ/ር ተክሉ አባተ የኦስሎ ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ህንፃ ኮሚቴ ሰብሳቢ

በሌላ በኩል የኮምቴው የሂሳብ ሹም ዶ/ር ዳዊት ሻወል ጨረታው ሊጀመር ሀያ አራት ሰዓታት ሲቀሩት ለስራ ከኖርዌይ ውጭ ወደ እንግሊዝ እንዲሄድ መስርያቤቱ ያዘዋል።ሁኔታው በወቅቱ ሁሉም የኮሚቴ አባላት የመገኘታቸው አስፈላጊነት አንፃር እራሱን የቻለ ድባብ ይዞ መጥቶ ነበር።


ዶ/ር ዳዊት ሻወል የህንፃ ኮሚቴ ሂሳብ ሹም 

በሌላ በኩል ከህንፃ ኮሚቴው ጭንቀት እና ውጥረት በተጨማሪ በኖርዌይ እና በመላው ዓለም የሚኖሩ ዜናውን የሰሙ ኢትዮጵያውያን ውጤቱን በጭንቀት ይከታተሉ ነበር።በመቶዎች የሚቆጠሩ ምእመናን በቫይበር ግሩፕ የተሰባሰቡበት የምእመናን ስብስብ እራሱ የቻለ የጨረታው ገፅታ ነበር።ለሁለት ሳምንታት ከጨረታው በፊት በነበሩ እያንዳንዱ ምሽቶች የሚገናኘው ይህ የምእመናን ግሩፕ በጎፈንድ የተከፈተው ሂሳብ ከመቶ ሺህ የኖርዌይ ገንዘብ በላይ እንዲሰበሰብ አግዟል።

ባጠቃላይ የኦስሎ ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ህንፃ ኮሚቴ አባላት ከሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ እና ከቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ እና የአቡነ ኤልያስ ረዳት አቡነ ሕርያቆስ ጋር በተቀናጀ መልኩ የሰሩት ሥራ ምእመናንን በጣም ያስደሰተ ታሪካዊ ሥራ ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና ምእመናን የተመለከተ የፔው ምርምር ማዕከል አዲስ ዓለም አቀፍ ጥናት ይፋ አደረገ

ፔው የምርምር ማዕከል በዓለም ላይ ባሉ የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት አዲስ ጥናት አውጥቷል።በጥናቱ በዓለም ላይ ከሩስያ ቀጥሎ ከፍተኛ የኦርቶዶክስ አማኞች ያሉባት ሀገር ኢትዮጵያ መሆኗን እና በሰንበት እለት ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ኢትዮጵያ ከፍተኛውን ቁጥር እንደያዘች ይገልጣል። የጥናቱ ውጤት ከእዚህ በታች ይመልከቱ።

Ethiopia is an outlier in the Orthodox Christian world









An Orthodox priest at Nakuto Lab Rock Church, outside Lalibela, Ethiopia. About three-quarters of Orthodox Ethiopians say they attend church every week. (Eric Lafforgue/Art in All of Us/Corbis via Getty Images)
An Orthodox priest at Nakuto Lab Rock Church, outside Lalibela, Ethiopia. About three-quarters of Orthodox Ethiopians say they attend church every week. (Eric Lafforgue/Art in All of Us/Corbis via Getty Images)

Ethiopia has the largest Orthodox Christian population outside Europe, and, by many measures, Orthodox Ethiopians have much higher levels of religious commitment than do Orthodox Christians in the faith’s heartland of Central and Eastern Europe.

The country in the Horn of Africa has 36 million Orthodox Christians, the world’s second-largest Orthodox population after Russia.

Nearly all Orthodox Ethiopians (98%) say religion is very important to them, compared with a median of 34% of Orthodox saying this across 13 countries surveyed in Central and Eastern Europe. About three-quarters of Orthodox Ethiopians say they attend church every week (78%), compared with a median of 10% in Central and Eastern Europe and just 6% in Russia.
Orthodox Ethiopians are more likely than Orthodox Christians in Central and Eastern Europe to wear religious symbols (93% vs. median of 64%), to say they believe in God with absolute certainty (89% vs. 56%), to fast during holy times such as Lent (87% vs. 27%), and to tithe (57% vs. 14%). Indeed, these gaps between Orthodox Christians in Ethiopia and Europe mirror broader differences in religious commitment between people living in sub-Saharan Africa, where religious observance is relatively high among all major religious groups, and those in more secular societies in Central and Eastern Europe.
Orthodox Ethiopians also tend to be more conservative on social issues than are other Orthodox Christians surveyed; they express higher levels of moral opposition to homosexuality, prostitution, abortion, divorce and drinking alcohol. For instance, Orthodox Ethiopians are much more likely to say that having an abortion is morally wrong than are Orthodox Christians in Central and Eastern Europe (83% vs. median of 46%).

Orthodox Christians do not make up a majority of Ethiopia’s overall population: 43% of Ethiopians are Orthodox, while approximately 19% are Protestant and 35% are Muslim. Still, in 2010, the 36 million Orthodox Christians in Ethiopia made up about 14% of the world’s total Orthodox population (compared with a 76% share in Central and Eastern Europe), up from about 3 million in 1910, when Orthodox Ethiopians made up 3% of the Orthodox total. This increase is owed mainly to natural growth in Ethiopia’s population, which rose from 9 million to 83 million between 1910 and 2010.
Ethiopian Orthodoxy is part of the Oriental branch of Orthodoxy, which accounts for approximately 20% of the global Orthodox population and is not in communion with Eastern Orthodoxy, the larger branch, largely due to theological and doctrinal differences.
Note: Read more about the history of Ethiopia’s Orthodox Christians.
Source: - Pewresearch 

ጉዳያችን GUDAYACHN 

 www.gudayachn.com

Wednesday, November 29, 2017

Does TPLF becomes strong or more disintegrate?

Foto: Azeb Mesfin (late PM Meles Zenawi wife) and Aboy Sibhat
+++++++++++++++++++++
Gudayachn
By Getachew Bekele

I was about to go to my bed before the pro-TPLF (Daniel Berhane) social media page small article pushed me back to my computer. His article is trying to tell us, as if this week's TPLF central committee conflict was a strength of the ethnocentric party.
My view regarding the TPLF condition is completely contrary to Daniel. It is quite true that TPLF internal conflict continues also in this week. After more than two months of meeting, four out of nine could be pushed from the central committee membership by force.It is possible to say that they are pushed by force. Because none of them apply to leave their position. This will widen also the big difference among top military officials who are also TPLF members.
The process of overthrowing corrupt central committee members by another corrupt and more dictator members is really meaningless and senseless action for most Ethiopians.The action is a good indicator of the party could not brought the new generation even after more than quarter century of its stay on power. This is  a sign also for ethnocentric ideology complete failure plus the disability to penetrate the strong ideology of Unity. The ideology of 'Unity with differences' and real federalism (federalism not based on ethnicity) is well accepted, more governing and proved ideology among the new generation.
The central committee of TPLF is currently destabilized seriously. Those who have pushed and overthrown from the TPLF central committee membership, including the late PM Meles's wife Azeb Mesfin and Abay Woldu, may mobilize their supporters even from the army top officers to disqualify Aboy Sibhatis group. Therefore there will be more possibility of raising unrest in Ethiopia. This is the fact that the diplomatic and international community should take into consideration.
Generally, Pro- TPLF propagandists like my FB friend Daniel, are attempting as if the party comes out strongly, The reality is showing in contrary . TPLF's level of acceptance and the status of confidence even among EPRDF member bodies has fallen down sharply. TPLF central committee members are well known corrupt people not only in Ethiopia but in East Africa. Therefore all the situation is leading TPLF to be more disintegrate and incapable even to keep peace and stability in Ethiopia

ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

Wednesday, November 22, 2017

ማኅበረ ቅዱሳን በውጭ ለሚኖሩ ሕፃናት እና ታዳጊዎች ማስተማርያ እና መማርያ ሥርዓተ ትምህርት አዘጋጅቶ አስመረቀ።



  • የሥርዓተ ትምህርት ዝግጅቱ ከሁለት ዓመት በላይ ወስዷል፣
  • ዝግጅቱ ከመጀመሩ አስቀድሞ ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ በእንግሊዝ የሚኖሩ ምእመና  ተሳትፈውበታል፣
  • ከሰላሳ ያላነሱ የቤተ ክርስቲያን ወጣት ምሁራን ተሳትፈውበታል፣
  • ጥናቱ የአብያተ ክርስቲያናት ተሞክሮ፣የልጆች የቋንቋ ክህሎት እና የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ደረጃ፣ እንደዚሁም ወላጆች የተሳተፉበት በችግሮች እና የመፍትሔ አቅጠጫዎች ዙሪያ ያተኮረ የመነሻ ጥናት ተደርጎበታል።
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አንዱ እና ፈታኙ ጉዳይ ልጆቻቸውን በሚፈልጉት ሃይማኖት እና ኢትዮጵያዊ ባህል አሳድጎ ለቁምነገር ማብቃት ነው።ይህንን ችግር ለመፍታት የሚያጋጥመው ችግር ደግሞ በባለሙያ የተዘጋጁ ልጆችን የማስተማርያ በቂ ስርዓተ ትምህርት አለመኖር ተጠቃሽ ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ስር የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማዕከል ስር የሚገኘው የተተኪ ትውልድ ሥልጠና ክፍል ይህንን ችግር ለመፍታት ጥረት ሲያደርግ ነበር።

በእዚህም መሰረት ማኅበሩ ላለፉት ሁለት ዓመታት በላይ ለሆነ ጊዜ ወስዶ የሥርዓተ ትምህርቱን አዘጋጅቷል።በእዚህ ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ በእንግሊዝ አገር የሚኖሩ ምእመናን እንደተሳተፉበት የተገለጠው ጥናት አሁን ለውጤት በቅቶ በያዝነው ወር ህዳር 3/2010 ዓም እንግሊዝ ዋና ከተማ ለንደን ከተማ በምትገኘው ደብረ ገነት ቅድስት ስላሴ ቤተ ክርስቲያን መመረቁ ተሰምቷል። 

በስርዓተ ትምህርቱ ምረቃ ላይ ከእዚህ በፊት ሕፃናትን እንዴት እናስተምራቸው በሚል ርዕስ መፅሐፍ ያሳተሙት የዚህ ስርዓተ ትምህርት ዝግጅት አስተባባሪ እና የማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማዕከል ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ጨከነ በላቸው የሥርዓተ ትምህርቱ ዝግጅት ላይ አስተዋፅኦ ያደረጉ ከሰላሳ በላይ የቤተ ክርስቲያኒቱ ምሁራን ወጣቶች መሳተፋቸውን ገልፀዋል።

ከአምስት እስከ ዘጠኝ ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ ለሚገኙ ሕፃናትና ታዳጊዎች ታስቦ የተዘጋጀው ይህ ሥርዓተ ትምህርት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን፣ የአማርኛ ቋንቋ እና የመዝሙር ጥናት የተሰኙ አምስት የትምህርት ዘርፎችን ያካተተ ሲኾን፣ የትምህርቶቹ አርእስትና ይዘቶችም በቤተ ክርስቲያን የሚከበሩ በዓላትንና ወቅቶችን መሠረት በማድረግ የተዘጋጁ ናቸው፡፡

የዜናው ምንጭ = ማኅበረ ቅዱሳን ድረ ገፅ (www.eotcmk.org)
ማን እንደርሱ (መዝሙር) በማኅበረ ቅዱሳን የመዝሙር ልዑክ 


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Saturday, November 18, 2017

የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ በኖርዌይ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ምርጫ ኦስሎ ከተማ ውስጥ አደረገ።

ፎቶ ከኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ በኖርዌይ ድረ-ገፅ የተወሰደ 

ጉዳያችን ዜና  / Gudayachn News 
==========================

የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ በኖርዌይ ዛሬ ህዳር 9፣2010 ዓም በኦስሎ ከተማ "አንቲ ራሲስት ሴንተር" በሚገኘው ህንፃ ስድስተኛ ፎቅ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ባደረገው የአባላት ስብሰባ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላቱን መርጧል። የማኅበረሰቡ አማካሪ ቦርድ አባላት በአቶ የሱፍ፣ ዶ/ር ሙሉዓለም እና ዶ/ር ሰይፉ አስመራጭነት አምስት የስራ አስፈፃሚ አባላት ተመርጠዋል።በእዚህም መሰረት 1/ አቶ ፍቅሩ 2/ ወጣት ስርጉት፣ 3/ወጣት ማርታ 4/ አቶ አያሌው እና 5/ አቶ ለገሰ  ሲሆኑ በሰብሳቢነት አቶ ፍቅሩ ተመርጧል።በእዚህ የስራ አስፈፃሚ ምርጫ ለበርካታ ዓመታት በኖርዌይ የኖሩ ኢትዮጵያውያን በሰጡት አስተያየት የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በረጅም ጊዜ የስራ ዘመኑ ሙሉ በሙሉ በወጣት የሰው ኃይል መተካቱ  መደሰታቸውን በሰጡት አስተያየት ገልጠዋል።

አዲስ የተመረጡት የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በኖርዌይ አምስቱ የስራ አስፈፃሚ አባላት 

የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በኖርዌይ እንቅስቃሴ የጀመረው እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1987 ዓም እንደሆነ የማኅበረሰቡ ድረ ገፅ ያስረዳል።የአዲሱ ትውልድ ወደ አመራር መምጣት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በጋራ ኢትዮጵያዊነታቸውን የሚያንፀባርቁበት የጋራ መድረካቸው እንደሚሆን ተስፋ ተጥሎበታል። የዛሬው ምርጫ ከመደረጉ በፊት የአማካሪ ቦርዱ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚገኙበት የኢ-ሜል መረብ አማካይነት ከሁለት ወራት በፊት ቅስቀሳ ሲያደርግ ነበር። በዛሬው የምርጫ ሂደት የተደሰቱት በኖርዌይ ለረጅም ዓመታት እንደኖሩ የሚነገረው አቶ ካሳ በኢትዮጵያውያን የኢ-ሜል መረብ ዛሬ ማምሻውን በላኩት የደስታ መልዕክት እንዲህ ብለዋል: -

"በጣም የሚመሰገን ስራ ነው የተሰራው በቦርድ ኮሚቲዎች የተደረገው ዝግጅት ለመልካም ውጤት በቃን ዛሬ። እስካሁን አይቸው የማላወቀው ለውጥ ነው ያየሁት አጠር መጠን ያለ ስብሰባ ነበር። እንደዚህ አይነት ደስ የሚል ስብሰባ የመጀሬያ ነው "  ብለዋል።

በሌላ በኩል አቶ መምህሩ በእዚሁ የኢ-ሜል መረብ ላይ በእንግሊዝኛ ማምሻውን ምርጫውን አስመልክተው በሰጡት አስተያየት:- 

" ይህ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንዲከናወን ጥረት ላደረጋችሁ  የቦርድ አባላት እና በምርጫው ላይ ለተሳተፋችሁ ሁሉ ምስጋናዬ የላቀ ነው።ለአዲሱ የስራ አስፈፃሚ ሰብሳቢ አቶ ፍቅሩ እና ሌሎች ተመራጭ አባላት መልካም የስራ ዘመን እመኛለሁ" ብለዋል።

የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ በኖርዌይ የስራ አስፈፃሚ ምርጫ የሚያደርገው በእየሶስት ዓመቱ እንደሆነ ህገ ደንቡ ያዛል። በዛሬው ምርጫ ከስራ አስፈፃሚ አባላት በተጨማሪ ሶስት የቁጥጥር ኮሚቴ አባላትን መርጧል። በመጨረሻም ተመራጭ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የቱንም አይነት የፖለቲካ አመለካከት ይኑረው፣ ከየትኛውም የኢትዮጵያ ክፍል ይምጣ ወይንም ምንም አይነት የሃይማኖት እምነት ይከተል ኢትዮጵያዊነት እና ኢትዮጵያዊነትን ብቻ መሰረት አድርገው ሁሉንም በእኩል ደረጃ እንደሚያገለግሉ በመረጣቸው ሕዝብ ፊት ወጥተው ቃላቸውን ሰጥተዋል።

በዛሬው ስብሰባ ከተገኙት  ውስጥ 

ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት የሆኑም ሆኑ እስካሁን በተለያየ ምክንያት አባል ያልሆኑ  ኢትዮጵያውያን  በደስታ ወይንም በሃዘን ጊዜ ብቻ ዕርዳታ ለመጠየቅ ከመምጣት የማንነታችን መገለጫ እና ቤታችን ወደ ሆነው የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በመቅረብ ድርሻቸውን መወጣት እንደሚገባ መረዳት ይገባል።አንድን ነገር ቀርቦ በመመልከት የሚስተካከለውን እንዲስተካከል ማገዝና በምንም አይነት የአመለካከት ጥግ ላይ ቢሆኑ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ የጋራ የኢትዮጵያዊነት እና ኢትዮጵያዊነት መገለጫ ብቻ መሆኑን ተረድቶ መስራት ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ይጠበቃል። 

በአዲስ ጉልበት መልካም የስራ ዘመን ለአዲሱ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እንመኛለን።


ጉዳያችን GUDAYACHN

www.gudayachn.com

Tuesday, November 14, 2017

ኢትዮጵያዊነት፣ የጎሳ ፖለቲካ እና መፍትሄዎቹ (የጉዳያችን ልዩ ዳሰሳ)




ጉዳያችን / Gudayachn

መግቢያ  

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የምትገኝ የረጅም ዘመን ታሪክ ያላት አገር ነች።ከዓለም መፈጠር ጋር አብራ የሚስተካከል ታሪክ ያላት እንጂ ዘመኗን ቆጥሮ እና ለክቶ መወሰን ከባድ ነው።ለእዚህም ጥንታዊ የታሪክ ቅርሶች እና የፅሁፍ ማስረጃዎች እማኞች ናቸው።ከፅሁፍ ማስረጃዎች ውስጥ ጥንታዊ የሐይማኖት መፃህፍትን መጥቀስ ይቻላል።ሁለቱ የዓለማችን ትልልቅ እምነቶች ቅዱሳን መፃፍህፍቶች መፅሐፍ ቅዱስ እና ቁርአን ከትበው የሚያስነብቡን የኢትዮጵያን ጥንታዊነት ነው።ለምሳሌ መፅሐፍ ቅዱስን ብንመለከት  በምዕራፍ አንድ ላይ ስለአለም አፈጣጠር ከተናገረ በኃላ በምዕራፍ ሁለት ላይ የማንንም አገር ስም ሳይጠራ የሚጠራት ብቸኛ የዓለም አገር ከእስራአልም በቀዳሚነት፣ ኢትዮጵያ ነች።

ኢትዮጵያ ዓረቦች ወደ አፍሪካ ከመግቦታቸው በፊት ግብጽ ይኖሩ በነበሩት ጥቁር ሕዝቦች ዘንድ ደግሞ ኔቶር(ሀገረ እግዝአብሔር) ከዚያ አቢሲኒያ (በንጉሥ አቢስ ስም) ከዚያ ኢትዮጵያ (በንጉሥ ኢትዮጵ ስም) በእነዚህ ስሞች እይተጠራች ኖራለች፡፡ባጭሩ ኢትዮጵያ እያልን የምናወራው ዛሬ በልዩ ልዩ የዘመን አስተሳሰብ እንደ እየሳቢያችን አጥብበን የምናያት አገር ሳትሆን ስለ ዓለም አመጣጥ የምትናገር አገር ነች።እኛ በዘመኑ የጎሳ አስተሳሰብ እራሳችንን ለማሳነስ ብንሞክር ፀባችን ከዓለም ታሪክ እና ከሰው ልጅ ህልውና ጋር መሆኑን ልብ ማለቱ ተገቢ ነው።

በአፍሪካ ነፃነታቸውን ጠብቀው ለመኖር ከቻሉ ሁለት አገሮች አንዷ፣አሁን ዓለም የሚተዳደርበት ዓለም አቀፍ ሕጎችን በዓለም ዲፕሎማሲ እኩል ተከራክራ በቀድሞው የዓለም ማኅበርም ሆነ በአሁኑ የተባበሩት መንግሥታት ምስረታ ላይ ፊርማዋን ያስቀመጠች በጎሳ ስም ሳይሆን ኢትዮጵያ በሚለው ጥንታዊ ስሟ ነው።ኢትዮጵያ  በህዝብ ብዛት ከአፍሪካ ሁለተኛ ስትሆን፣ በቆዳ ስፋት ደግሞ አስረኛ ናት።አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች ዕድሜያቸው ከአንድ ምዕተ ዓመት የሚያንስ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ግን ከጥንት ጊዜ ጀምሮ በንጉሠ ነገሥታት እና ንግሥተ ነግሥታት የተመራች ሀገር ነች የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥት የአመጣጡን ዘር ከክርስቶስ ልደት በፊት እስከ አስረኛው ዓመተ ዓለም ድረስ ይቆጥራል።ባጠቃላይ ኢትዮጵያ ብለን ስንጠራ የእነዚህ ዘመናት ሁሉ መገለጫዋን ኢትዮጵያን ነው እንጂ በተናጥል የአንድ ብሔር ስም አይደለም። 

እንዴ ኤውሮፓውያን አቆጣጠር በ1885 ዓም በበርሊን ጉባኤ  የአውሮፓ ሀያላት ሀገሮች አፍሪካን ሲከፋፍሏት፣ኢትዮጵያ ነፃነቷን ጠብቃለች። ከተባበሩት መንግሥታት በፊት የነበረው የዓለም ማህበር ''የሊግ ኦፍ ኔሽን'' አባል ኢትዮጵያ ነበረች። ከአጭር የኢጣልያ ወረራ ጊዜ በኋላም ከየተባበሩት መንግሥታት ከአፍሪካ መሥራች ብቸኛ አገር ኢትዮጵያ ነች ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ነፃነታቸውን ሲያገኙ፣ ሰንደቅ አላማቸውን በኢትዮጵያ ቀለሞች ማለትም በአረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ላይ ነው የመሠረቱትባት ሀገር ነች ኢትዮጵያ።የኢትዮጵያን ተምሳሌትነት ዛሬ ድረስ የአፍሪካ፣የካሪባን እና የእሩቅ ምስራቅ አገሮች ከህሊናቸው አልጠፋም።

በዓለም ዙርያ በሚገኙ ታላልቅ ዩንቨርስቲዎች ውስጥ የሚገኙ ምሁራን ስለ ፍልስፍና ሲነሳ፣ስለጥንታዊ ታሪክ ሲወራ፣ስለ አፍሪካ የነፃነት ታሪክ ሲወሳ ሁሉ የኢትዮጵያን ምሳሌነት ሳይጠቅስ የሚያስተምር ምሁር የለም።የኢትዮጵያ ጥናት ማዕከላት ያላቸው ዩንቨርስቲዎች በጀርመን፣እንግሊዝ፣ሩስያ እና በቅርቡ ደግሞ በካናዳ ዩንቨርሲዎች በትምህርት ክፍል (ዲፓርትመንት)  ደረጃ ከፍተው ያጠናሉ። በዓለም ካሉ አገራት ለየት ባለ መልኩ በመላው ዓለም የሚኖሩ ምሁራን እየተሰበሰቡ የኢትዮጵያ የጥናት ጉባኤ በዓለም ባሉ ከተሞች በእየ ዓመቱ ይደረጋል።ለምሳሌ የዘንድሮው በዋርሶ፣ፖላንድ ዩንቨርሲቲ መደረጉ ይታወቃል። ይች አገር ኢትዮጵያ ዓለም ይፈልጋታል።ለዓለም ቅርሱ ነች።ዓለም ማንነቱን የሚያጠናባት ቤተ መዘክሩ ነች።በውስጧ የምንኖር ዜጎች እንደፈልገን እንደጥበታችን እና ስፋታችን የምንጥላት እና የምናነሳት አገር አይደለችም። 

ኢትዮጵያ ቀደም ባለው ታሪክ ነገሥታቱ የመጡበትን አካባቢ ጀግንነት ከማውራት ባለፈ የመጡበትን ሰፈር ከኢትዮጵያዊነት ጋርም ሆነ ከጎሰኝነት ስሜት ጋር ሲያቀላቅሉት እና ሲያገዳድሩት አልተስተዋሉም።እርግጥ ነው በታሪካችን የክርስትና ሃይማኖት የበላይነት በየትኛውም የታሪክ ሂደት አንፃር ተንፀባርቁአል።የንጉሡ ወዳጅ ወይንም ባለሟል ለመሆን ከመጣበት ዘር ይልቅ ሃይማኖቱ ሲማርካቸው ተስተውሏል።ለእዚህም አይነተኛ ማሳያ የሚሆነው ከአውሮፓ እና ደቡብ እስያ የፈለሱት በታሪክ 9 ቅዱሳን ተብለው የሚጠሩት እና የነቢዩ መሐመድ ቤተሰቦችን ወደ ኢትዮጵያ መሰደድ መመልከቱ በቂ ነው።የቀደሙት ዓለም አቀፋዊ አስተሳሰብ እና ኃላፊነት ይሰማቸው ነበር እንጂ በአካባቢ ጉዳይ እና ስሜት ተገዢ አለመሆናቸውን መረዳት ይቻላል። መነኮሳቱ በመልክ ነጮች፣በባህል ልዩዎች ይሁኑ እንጂ በራሳቸው ሃይማኖታዊ መንገድ ከመረመሩ በኃላ በፈለጉት ቦታ እንዲኖሩ የፈለጉትን እንዲሰሩ ፈቅደውላቸው ነበር። መነኮሳቱም ገዳማትን ገድመው ግዕዝ ተምረው ብዙ መፃህፍትን ፅፈው ለማለፍ ችለዋል።እነ አቡነ አረጋዊን ከሮም የደብረ ዳሞ ገዳምን ገድመው ለመኖር እና በሀገሪቱ ሙሉ መብት እንዲኖራቸው የተደረጉት ከእዚሁ ጎሳን እና ዘርን ከማያማክለው የመንግስት ስሪት በሚመነጩ ባህርያት በተካኑ የኢትዮያ መሪዎች ውሳኔ ነው። አሁን ያለው ኢትዮጵያን የምንለካበት ልኬት ምን ያህል የወረደ እና የተሳሳተ ትናንሽ ስሜቶች ተገዢ እንደሆነ ለመረዳት እራሳችንን በቀደሙት የእዚች አገር መሪዎች አስተሳሰብ ተገብተን ማሰብ መጀመርን ይጠይቃል። 

 የጎሳ ፖለቲካ ያቆሰላት አገር 


(ማሳሰቢያ - ከእዚህ በታች በሚኖረው ፅሁፍ ''የብሔር ፖለቲካ'' የሚለው ለአገር ስለሆነ  ''ብሔር'' የሚለውን ቃል  አልጠቀምም። ''ርዕሰ ብሔር'' ማለት የአገር መሪ እንጂ የጎሳ መሪ ማለት እናዳልሆነ ሁሉ ማለት ነው። 

የጎሳ ፖለቲካ አለማችን አዲስ ክስተት አይደለም።የአምባገነኖች መሸሸጊያ ጉረኖ ዘረኝነት እና የዘር መርዝ መንዛት ነው። አዶልፍ ሂትለር የጦርነት ጥማቱን ለማርካት ጀርመንን ህዝብ የተለየ ህዝብ አድርጎ ማቅረብ ነበረበት። ¨እናንተ ጀርመን ህዝቦች 'አርያን'ዘሮች ¨ እያለ ይሸነግል ነበር።ሰዎች በባህሪያችን ብልህ የመሆናችንን ያህል ጅልነትም አያጣንም።አንድ አውሬነት የተጠናወተው ግለሰብ የአካባቢ ጉዳይ አንስቶ በቀላሉ የሚነዳን አይነቶች።ሁኔታዎች ስህተት መሆናቸውን የምንረዳው እና የምንነቃው ወደ ትክክለኛ ከብዙ የሰው ልጅ እልቂት በኃላ ነገሩ ዘግንኖ ወደ አእምሮአችን ተመልሰን ስንንቃ ነው።

 ሁለተኛው አለም ጦርነት እልቂት አቶ አዶልፍ ሂትለር ''ጀርመን ሆይ! ¨አንተ እኮ አርያን ዘር ነህ¨ ብሎ ነው አለም ጥፋት እሳቱን የለኮሰው። ሞሶሎኒም ኢጣልያ ህዝብ ኢትዮዽያን መውረር እንዳለበት ለማሳመን ¨ታላቋ ሮማ ህዝብ ሆይየምትለዋን ዘረኝነት ቃል መጠቀም በቂው ነበር። አምባገነኖች ዘር ፖለቲካቸው ሲናድ ይደነግጣሉ፣ይርዳሉ።ስለ እዚህ ዘረኝነትን ይንከባከቡታል::ወደ ስልጣን ለመወጣጫነትም ጥሩ የመጫወቻ ካርድ አድርገው ይጠቀሙባታል።

 የ1960ዎቹ የኢትዮጵያ ትውልድ የለውጥ እንቅስቃሴ ሃሳቦችን ብልጭ በማድረግ ስለ ርዕዮተ ዓለም ብዙም ጠልቆ የማያውቀውን ወታደሩ አጠገቡ ያገኘውን ርዕዮት እንዲጨብጥ አድርጎታል፡፡በእዚህ እንቅስቃሴ ስር የተንቀሳቀሱት ሙሉ በሙሉ ማለት ይቻላል የፓርቲዎቹ አደረጃጀት  ስር ነቀል ለውጥ የሚያቀነቅኑ እና የማርኪዝም ፍልስፍናን እንደ ዋነኛ መተንተኛ ሰነድ የሚጠቀሙ ነበሩ።ኢህአፓ፣ መኢሶን፣ ህወሓት፣ ህግሐኤ (ህግድፍ) ለዚህ ዋቢ ናቸው፡፡ ኢሕአፓ እና መኢሶን ኢትዮጵያን የሚረዱበት እና ለመለወጥ የሚሞክሩት አግባብ የመደብ ቅራኔና  ዋነኛ አንጓ  በማድረግ ነበር፡፡በሌላ በኩል ህወሓት እና ኦነግ የብሔር ቅራኔውን በማስቀደም የብሔረሰቦች መብት መከበር የችግሩ መፍትሄ መሆኑን ያስቀምጣሉ፡፡ ነገር ግን ኦነግ የኤርትራን ጉዳይ ሙሉ ቅኝ ግዛት (Classical colonialism) መሆኑን ገልጾ የኦሮሚያ ጉዳይ ግን የውስጥ /የአቢሲኒያ ቅኝ ግዛት በመሆኑ ኦሮሚያን ከቅኝ ግዛት ነፃ ስለማድረግ እንደሚታገል ይገልፃል፡፡የዚህ አስተሳሰብ ድባብ ዛሬም ድረስ ከዚህ አካባቢ በተገኙ የተወሰኑ ምሁራን ላይ ይንፀባረቃል፡፡ የብሔረሰብን ጉዳይ በዋነኝነት በተመሳሳይ መልኩ የያዘው ህወሓት ስለጎሳ ጉዳይ አብዝቶ የማንሳቱን ያክል ኦነግ ስለ ጎሳ ሲያነሳ ደግሞ አይጥመውም።ምክንያቱም ጉዳዩ የስልጣን ሽምያ እና ጎሳን ሁሉም የሚጠቀመው ለስልጣን መወጣጫ ስልት በመሆኑ ነው።በሌላ በኩል በወታደሩ የተመሰረተው የኢሠፓ (ኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ) ሌላው  መሠረቱን ግራ ዘመም እና ፍፁም ፈላጭ ቆራጭ ቢሆንም በጎሳ አስተሳሰቦች ውስጥ ያልጠነከረ ይልቁንም ለሀገራዊ አንድነት እና ማንነት የሚሰጠው ልዩ ትኩረት ከቀኝ ዘመሞች የተወሰደ መሆኑ ነው፡፡

ዛሬ ኢትዮጵያ 1967ዓም ከነበረችበት ሁኔታበብዙ የተለዩ አዳዲስ ክስተቶች አሉባት።የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ሁኔታዎች ብቻ ሳይሆኑ አንድ ትውልድ አልፎ አዲስ ትውልድ ተተክቷል፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር 30 ሚልዮን  በሶስት እጥፍ ወደ 90 ሚልዮን ተተኩሷል፣የባሕር በሯ ተዘግቷል፣ወጥ የነበረው የመንግስት ስሪት በጎሳ እና ቋንቋ ላይ በተመሰረተ አስተዳደር ተቀይሯል፣ከተሞች በመጠን ሰፍተዋል።በከተማ የሚኖረው ሕዝብ ከገጠሩ ጋር ሲነፃፀር ግን በእነኝህ ሁሉ ሶስት አስር አመታት በኃላም 90 በመቶ ወደ 85 (83) በመቶ ነው ዝቅ ያለው።የህዝቡ የኑሮ ደረጃ አቆጣጠር 1970 ዎቹ ነፃነታቸውን ከተቀዳጁት የአፍሪካ ጥቁር ህዝቦች ለምሳሌ እንደ ናይጀርያ፣ጋና ጋር  አንፃርም ገቢው ዝቅተኛ የሚባል እና ከእጅ ወደ አፍ ነው።በአፍሪካ ቀንድ የነበረን አማላይነት በምድር ጦር፣በአየር ኃይል እና በባህር ኃይል  የበላይነት ነበረን ።ዛሬ ግን በሕዝብ ብዛት እና ዙርያችንን ያሉት የትናንሽ ደካማ ሃገራት መኮልኮል አጉልቶ ካሳየን የበላይነት ባለፈ መድረስ የሚገባንን ደረጃ አለመድረሳችንን ለማረጋገጥ ብዙ ማስረጃ ማቅረብ አያስፈልግም።

ባለፉት አርባ ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ የገጠማት ተግዳሮቶችን በሶስት  መልክ ማስቀመጥ ይቻላል።እነርሱም 
የውስጥ ቁርሾ፣
- ፍፁም አምባገነናዊ አገዛዞች እና 
- ቀጥተኛ እና እጅ አዙር የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነቶች ናቸው።

የውስጥ ቁርሾው በተቻለ መጠን የሚቀልባቸው መንገዶች እንዳይኖሩ እልህ የተጋባው የአምባገነንነት እርምጃዎች በእሳት ላይ ቤንዚን የማርከፍከፍ ያክል ብዙዎች ሳያስቡት ቁርሾውን ለማባባስ ሰበብ እንዲሆኑ ሆነዋል።ደርግ የእርስ በርስ ጦርነቶቹ በተቻለ መጠን ለማቅለል ከውስጥ የነበረበትን የህዝብ ድጋፍ ማጣት ስልጣንን ለሕዝብ በማስረከብ ሊያቀለው አልፈለገም።ይልቁንም ጦርነቶቹ የሰራዊቱን በሥራ መጠመድ ማምጣቱ የታያቸው ወገኖች እንደ መልካም እድልም ተመለከቱት።ለእዚህ ማሳያ የሚሆነን የበዓሉ ግርም ''ኦሮማይ'' መፅሐፍ ላይ የነበረውን የቀይ ኮኮብ ዘመቻ ማስታወሱ ነው።ጋዜጠኛው በዓሉ ግርማ ጦርነቱ በቶሎ እንዳያልቅ እና ሰራዊቱ እንዳያርፍ የሚፈልጉ መኖራቸውን ያሳየበት ፅሁፍ አምባገነኖች ሁል ጊዜ ከብሄራዊ ጥቅም ይልቅ የስልጣን ጥቅም እንድሚበልጥባቸው ያሳያል።

መንግስታዊ የጎሳ ፖለቲካ በኢትዮጵያ 

ኢህአዲግ/ወያኔ ዘመን ደግሞ የውስጥ ቁርሾው በደርግ ዘመን ከነበረው የህዝብን ስልጣን ለሕዝብ የማስረከብ ጥያቄን የመመለስ ሙግት ብቻ ሳይሆን ''መንግስታዊ የጎሳ ፖለቲካ'' በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ማኅበራዊ፣ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ግንኙነት ላይ አደገኛ ጥላ አጠላ።የጎሳ ግጭቱ ከክልሎች የመሬት ግጭት አልፎ እስከ መንደር የከብቶች መሰማርያ ሜዳ ድረስ ኢትዮጵያውያን አጋጨ። ይህ ስርዓት በተለይ ቁጭ ብሎ ህብዝ ከህዝብ ጋር ለማጋጨት የሚሰሩ የደህንነት ሰዎች ያሉት መሆኑ ኢትዮጵያ ምን አይነት አደገኛ ሁኔታ ላይ መሆኗን ያሳያል። 

የእዚህ ፅሁፍ አቅራቢ በአንድ ወቅት ከስርዓቱ አገልጋይ ግለሰብ የቦረና ጉጂን ከኦሮሞ ሕዝብ ጋር ለማጋጨት እንዴት እንደተሳተፈ የተናገረውን ቃል በቃል ከግለሰቡ መስማቱን ያስታውሳል። በመሆኑም ከአሉባልታ ባለፈ ኢህአዴግ/ህወሃት የኢትዮጵያ ህዝብን በመንደር ለማጋጨት ሙሉ ኃይሉን የሚጠቀም ለመሆኑ እማኝ መሆኑን ይገልጣል።በእነኝህ የጎሳ ግጭቶች የተነሱ ፀቦችን ለማስቆም ዋናው ችግር ''የመንግስታዊ የጎሳ ፖለቲካ'' መሰረት ያደረገውን የፌድራል  ስርዓት በትክክለኛ የመሬት አቀማመጥ እና የህዝቦች ታሪካዊ አሰፋፈር መሰረት ያደረገ የፌድራል ስርዓት መቀየር መሆኑ እየታወቀ ኢህአዲግ/ወያኔ የተጋጩትን የጎሳ አባላት መዳኘትን እንደ ትልቅ ግብ እየቆጠረ በዜና እወጃው ላይ በስኬት ዜናነት ማውራቱን ቀጥሏል። ባጭሩ ባወጣው የጎሳ ፌደራሊዝም ስርዓት እና ሆን ብሎ ባጠመዳቸው የማጣያ መረቦች ተጠቅሞ  ህዝብን ካጋጨ በኃላ መልሶ እራሱ በፌድረሽን ምክር ቤት እያየሁት ነው እያለ ያፌዛል።የችግሩ መፍትሄ ግን የተሳሳተው ፖሊሲ እና የተንኮል ሥራ እንጂ የተጣሉትን ለመዳኘት የሚደረግ የማስመሰል ሽር ጉድ አይደለም።

1983 ዓም ተከትሎ “የብሔር ብሔረሰብ መብት” የመፍትሄው ማዕከል  ነው ተብሎ ብዙ ተነግሮለታል፡፡ሆኖም ግን ያለፉት 25 ዓመታት ያሳዩን ከሃያ አምስት አመታት በፊት የነበረውን ሳይንሳዊ ትንተና ነው።የጎሳ ፖለቲካ እና ፌድራሊዝም የግጭት እና የብጥብጥ ምንጭ መሆኑን። ይህ ጎሳ ተኮር ግራ ዘመም አስተሳሰብ ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ታሪክ እና ባህላዊ/ እሴታዊ ማንነቶች ከፍተኛ ንቀት ያለው  ከመሆኑም በላይ ለእነኝህ እሴቶች ዋጋ የሚሰጡትን ሁሉ  እና አስተሳሰብ ተባባሪ የነበሩትን ሁሉ  ከማግለል ጀምሮ በተለያዩ ዘዴዎች ማፈን፣ ማሳደድ እና መጨቆን እንደ ዋና ስልት ይመለከተዋል፡፡

በቪየና ዩኒቨርሲቲ የአንትሮፓሎጂ ትምህርት ክፍል ተመራማሪ የሆኑት / ወንድወሰን ተሾመ እውነተኛ በሆነ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ውስጥ ተቃዋሚ የፖለቲካ ኃይሎች አማራጭ መንግሥት ሆነው አገሪቱ በሕግ እና ስርዓት እንድትመራ የማድረግ ሚናቸው ከፍተኛ ነው፡፡  “ጠንካራ ተቃዋሚ፣ የዴሞክራሲ መወላወል ባለባቸው መንግሥታት ውስጥ ቁጥጥር እና ተጠያቂነትን ስለሚፈጥሩ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት መጎልበት ዋናውን ሚና ይጫወታሉ” በማለት ያስረዳሉ ፡፡
ኢህአዴግ/ህወሃት ሀገሪቱን እንደ ተቆጣጠረ በጥቂቶች ዘንድም ቢሆን ጥቂት ተስፋ አሰንቆ ነበር፡፡ በተለይም በ1994 ዓ.ም የወጣው አዋጅ ቁጥር 82/1994 የፖለቲካ ፓርቲዎችን ምዝገባ ፈቃድ የሚያትት በመሆኑ፡፡ አዋጁ ማንኛውም እድሜው ከ18 አመት በላይ የሆነ ኢትዮጵያዊ ዜጋ የፖለቲካ ፕሮግራም እና የውስጥ መተዳደሪያ ደንብ ካለው በአንቀጽ 4.1 መሠረት የፖለቲካ ፓርቲ ማቋቋም እንደሚችል ይደነግጋል፡፡

የኢሕአዴግ/ህወሃት የመድበል ፓርቲ ውሳኔ ላይ ጥያቄ መነሳት የጀመረው ብዙም ሳይቆይ ነበር፡፡ለይስሙላ ያወጣው ሕግ በተለይ የሀገራዊ /ህብረ ብሔራዊ/ ፓርቲዎችን መደራጀትን በአይነ ቁራኛነት የተመለከተ እና ውስጥ ለውጥ በጥላቻ  የማደናቀፍ ተግባራት የተሞላ ነበር፡፡ በሕጉ መሰረት አንድ ቡድን ሀገራዊ ፓርቲ ለመመስረት 1500 መስራች አባላት ኖሮት ከአራት ክልል የተገኙ ከያንዳንዱ ክልል ቢያንስ ከ15% በላይ እንዲሁም ከፍ ሲል 40% ያልበለጡ መስራቾች መፈረም አለባቸው።ይህ ሁሉ ግን ዛሬ ተረት ሆኗል።መደራጀት አይደለም ሃሳብን ገልጦ አንዲት መስመር መፃፍ ዋጋው አንዲት ጥይት በሆንበት ዘመን ላይ እንገኛለን።

ዶ/ር ወንድወሰን ተሾመ በቪየና ዩኒቨርሲቲ የአንትሮፓሎጂ ትምህርት ክፍል ተመራማሪ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2008 ዓም በዓለም አቀፉ ሰብአዊ ሳይንስ የምርምር መፅሄት ላይ የኢትዮጵያን የኢህአዴግ/ህወሃት የጎሳ ፖለቲካ በሚገልፅ ያወጡት የጥናት ፅሁፍ ገፅ 11 ላይ እንዲህ የሚል ይገኝበታል።

'' የጎሳ ፈድራሊዝም የህወሃት 'ከፋፍለህ ግዛ' ፖሊሲ ሲሆን የተዋቀረበት ዋናው ምክንያትም ስርዓቱ የራሱን ስልጣን ለማስጠበቅ ነው።ሁኔታው ግን አገሪቱን እንዳትከፋፈል ያሰጋል'' ያላል።
''...Ethnic federalism is the ''divide and rule'' policy of the TPLF designed to strengthen its own position and it might lead the country into disintegration'' International Journal of Human Sciences, 2008, 11p).
ethnic federalism is the “divide and rule” policy of the
TPLF designed to strengthen its own positio
n and it might lead the country into
disintegration

የኢትዮጵያ የቅርብ ወቅታዊ ተግዳሮት ምንድን ነው?

ሁለተኛው አለም ጦርነት አንስቶ እስከ 1980 ዎቹ አቆጣጠር ተጋግሎ የቆየው የቀዝቃዛው ጦርነት ኢትዮጵያ ወደራሷ የችግር ፈቺነት አቅም ሳያሸጋግር ''ለመንግስታዊ የጎሳ ፖለቲካ'' አስረክቧት ቀዘቀዘ።ቀድሞ በምዕራባውያን ትምህርት የተዋከበው የእድገት ስልት ቀጥሎ በመጣው በደርግ ሶሽያልስታዊ አስተሳሰብ ተተራምሶ ከዛሬ 24 አመት ገደማ ደግሞ ''መንግስታዊ የጎሳ ፖለቲካ'' ቅርፁም ሆነ ይዘቱ ትውልድ አሻጋሪ እንዳይሆን ሆነ።

ዛሬ የምዕራባውያን ''ሌክቸር'' መሰል አመራርም ሆነ የሶሻልስቱ አለም የማያላውስ ቀጭን ትዛዝ የኢትዮጵያ እራስ ምታቶች አይደሉም።የአካባቢ የአረብ መንግሥታት ግፊት ግን የቅርብ እና ከባድ የኢትዮጵያ ተግዳሮት ነው።ከኢህአዲግ/ወያኔ በፊት የነበሩት መንግሥታት በማዕከላዊነት ይዘውት የነበረውን የሀገር ጉዳይ በጎሳ ስለሸነሸነው ለአካባቢ ''ኢትዮጵያን አረብ ማድረግ አለብን'' እንቅስቃሴዎች እጅግ አመቺ ሁኔታዎችን ፈጥሯል።ኢትዮጵያን አረባዊ የማድረጉ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ላይ ብቻ ሳይሆን በጥቁር ህዝቦች ላይም የተሞከረ እና የታቀደ ይልቁንም እስልምናን ከሃይማኖት ይልቅ ፖለቲካዊ ጥቅሙን ብቻ ነቅሶ የመንቀሳቀስ አላማ የያዘ ነው።ኢትዮጵያን አረባዊ (እስላማዊ ሀገር ) በማድረግ ሂደት ላይ በጉልህ የተሳተፉ ውስጣዊ ኃይላት አሉ።እነርሱም-

1/ የኢህአዲግ/ወያኔ መንግስት  እናፅፈኛ አጋርተብዬ የጎሳ ድርጅቶቹ


2/ኢህአዲግ/ወያኔን እንቃወማለን የሚሉ ግን የመገንጠል አላማን እንደማስፈራርያ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ናቸው።


ለምሳሌ ዑጋዴን ነፃነት ግንበር እና በኦሮሞ ሕዝብ የሚገዘቱ ግን ማኅበረሰቡን የሚጎዱ ተግባራት የተሰማሩ እና ወደ ስልጣን ለመንጠላጠያነት በስልትነት ብቻ የሚጠቀሙበት ናቸው።

እነኝህ ኃይሎች ከእራሱ ከኢህአዴግ/ህወሃት ጋር  የተለያዩ ይምሰሉ እንጂ ያጣላቸው የበላይ ለመሆን የሚደረግ ግፍያ ካልሆነ በቀር የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው።ለምሳሌ ትግራይን የመገንጠል አላማ ይዞ በፕሮግራሙም አካቶ ይንቀሳቀስ የነበረው ህወሓት ዛሬም መንግስት ከሆነ በኃላም የቀድሞ የጎሳ ስሙን ካለመቀየሩም በላይ ለስልጣን ያበቃቸው አጋር ድርጅቶቹ ባብዛኛው በአንድም ሆነ በሌላ ኢትዮጵያን አረባዊ (እስላማዊ) ለማድረግ ከሚሹ ኃይላት በተገኘ የስልጠና፣የቁሳቁስ እና የገንዘብ ድጋፍ የተመሰረቱ ናቸው።ይህንን  ድጋፍ ዛሬም ድረስ እያገኙ ነው።

እነኝህ በተለያየ የጎሳ ድርጅቶች ስም የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች አላማቸውን ለማስፈፀም የሚሞክሩት እና የሚተገብሩት በአፈሙዝ ነው።ይህ ማለት በሌላ አገላለፅ መጭውም የፖለቲካ መድረክ የሚስተናገደው በአፈሙዝ ስልጣን ላይ የሚወጣ የሚደመጥበት ነው ማለት ነው።አሁንም ለሰላማዊ የስልጣን ሽግግር አልታደልንም ማለት ነው።

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ላይ የሚታዩት ኃይሎች

በአሁኑ ወቅት በእኔ እይታ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ኃይሎች አሰላለፍ  3 ናቸው። እነርሱም-

/ የጠነከረ  የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች

እነዚህ ኢትዮጵያን በእራሳቸው የጎሳ ዘውግ እንደ አዲስ ሰባብረው ለመስራት እና እነርሱ በፈጠሯት ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻመኖር የሚፈልጉ፣ለምሳሌ ህወሓት፣ኦብነግንኦነግ መጥቀስ ይቻላል።ኢትዮጵያ የእነርሱ የማቴርያል እና የጎሳቸውን ዝና ያገናል ብለው እስካሰቡ ድረስ የራሳቸውን መንግስት ለመፍጠር ቅድመ ሁኔታ የሚያመቻቹ ናቸው።

/ ለዘብተኛ የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች 

 እነኝህ ኢትዮጵያን እንደ አዲስ መሰባበር እና ለመስራት ብዙም አዋጪ አይደለም የሚሉ -
- የጎሳ ፖለቲካ አለመስራቱን ሲመለከቱ ወይንም ደግሞ ከእድሜ ማርጀትም ሆነ በተለያዩ ምክንያቶች ከፅንፈኛው የጎሳ ፖለቲካ ወደ ለዘበው የጎሳ ፖለቲካ የሚደረገው የማረፍያ ቦታ ነው። ለምሳሌ አንድ አባባል እንጥቀስ
ኢትዮጵያዊ ለመሆን መደራደር እንፈልጋለን አቶ ሌንጮ ለታ በወቅቱ የኦነግ / ሊቀመንበር (ሳሌም መጽሔት፣ ነሐሴ 1984) እዚህ ላይ አቶ ሌንጮ ኢትዮጵያ ሲሉ ፍትህ የጎደለባት ሕግ የታጣባት ወይንም አንድ ብሔር የነገሰባት ከሚል ፅንሰ ሃሳብ ነው ለማለት ይቸግረኛል። እንደዚህ አስበው ቢሆን ኖሮ የጎደለውን ፍትህ በኃይልም ይሁን በምርጫ ማስተካከል አለብን ብለው በተናገሩ ነበር። እራስን ከትልቁ ስብስብ አውጥቶ መነጋገር በራሱ ስህተት ነው።አንድ ሰው የአንድ ቤተሰብ አባልነቱን ካመነ በኃላ ነው ስለ ቤተሰቡ የውስጥ ጉዳይ ልነጋገር የሚችለው።አይደለሁም ካለ ግን ነገሩ ሁሉ እዝያ ላይ ያከትማል።

ለምሳሌ ሀገር ቤት ያሉ እንደነ ኦፍዴን (ኦሮሞ ፌድራላዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ) እና የመድረክ አባል ድርጅቶች ከለዘብተኛ የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች ይመደባሉ።የእዚህ ለዘብተኛ የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች ዋነኛ ስልት በሁለት ይከፈላል። አንደኛው እና ሁሉንም ሊያስማማ የሚገባው መሰረታዊ የጎሳው መብት እንዲከበር እንደ ኢትዮጵያዊነትም ተከብሮ መኖር የሚል ሲሆን፣ሁለተኛው ስልት እና የተወሰኑ አባላቱ ይዘው የሚንቀሳቀሱት አደገኛ አካሄድ ደግሞ የጠነከረ የጎሳ ፖለቲካ አራማጅ ለሆኑት መንገድ ጠራጊ መሆን ነው።ይህ አሳዛኝ እና አደገኛ አካሄድ ነው።አደገኛነቱ ለእራሱ፣ወከልኩት ላለው ጎሳ እና እንደ አገር ደግሞ ለኢትዮጵያም ነው።ፖለቲካ የማታለል ሥራ አይደለም።ቁርጠኘንት፣ለአላማ መታመን፣እና ግልፅ ግብ ይፈልጋል።በእዝህኛው ክፍል ላይ የሚታየው አካሄድ ግን በአገር ቤት ቢሮክራሲው ውስጥ ሁሉ ተሰግስጎ የጎጥ ፖለቲካ ማራመድም ነው እና ጉዳቱ ቀላል አይደለም። 

የአንድነት ኃይሎች

እነኝህ ኃይሎች የብሔር ጭቆና ነበርም የለምም የሚል አስተሳሰብ ያላቸው አንድነት የሚገኙበት ነው። ያለፈውን በደል በማሰብ ብቻ መጪው ማስተካከል አንችልም ለወደፊቱ ግን ኢትዮጵያን ሳንሰባብር  የእያንዱ ግለሰብ እንደ ግለሰብ እና ቡድን እንደ ቡድን መብቱ ይጠበቅ፣ለእዚህም እንስራ፣የሕግ የበላይነት ሲመጣ ጥያቄዎች ሁሉ ምላሽ ያገኛሉ።ቤትህን ለመስራት ቤትህን ማፍረስ የለብህም የሚስተካከለውን በማስተካከል ወይንም በኅብረት እስከሆነ ድረስ እንደገና መስራትም የሚቻለው አሁንም በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር ነው።የሚሉ ናቸው።ከእነዚህ ውስጥ የአገርህን አድን የጋራ ንቅናቄን መጥቀስ ይቻላል።

እነኝህ የአንድነት ኃይሎች አሁን ላለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጥያቄ ምላሽ የሚሆኑ የሚሏቸው  መርሆዎች አሏቸው።በተለያዩ መድረኮች ከሚያንፀባርቁት ሃሳቦች ውስጥ የሚከተሉት ይገኙባቸዋል። እነርሱም :

- በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር ሁሉም የጎሳ ፖለቲካ ችግር ይፈታል

ያለፈውን ታሪክ ዛሬ ላይ ሆነን መልሰን ማስተካከል አንችልም።

- የአሁኑም ሆነ መጪው ትውልድ ስለአለፈው ነገር ሁሉ ተጠያቂ አይደለም።

እመንም አትመንም ሊባል አይችልም።የእራሱን አመለካከት መያዝ ይችላል።

ይልቁን አስፈላጊው ጉዳይ ለነገዋ ኢትዮጵያ ሳንሰባብራት እንዴት በአንድነት እንኑርባት የሚሉት ይጠቀሳሉ።

እነኝህ ኃይሎች ዋነኛ የወቅቱ አደጋ የኢህአዲግ/ወይኔ ስርዓት ነው ብለው ያምናሉ።እርሱ ሲወገድ የተጋረጠው አደጋ ይገፈፋል ብለው ይናገራሉ።

የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች መሰረታዊ ችግሮች


ባለፉት ዘመናት የተደረጉትን ታሪካዊ ሁኔታዎች ዛሬ 21ኛው /ዘመን ላይ ሆኖ ለመገምገም የሚፈልግ ነው።የዛሬ 600 አመት አፄ ዘርያቆብ ለምን እንዲህ አላሰቡም? እንዴት እንዲህ ይላሉ? እያለ በወቅቱ የነበረውን ስነ-ልቦና የማኅበረሰቡን ባህል፣እምነት እና ወግ ሳያጠና እንዲሁ ለዛሬ የኢትዮጵያ እሷነት መነሻ ሰበብ ሲፈልግ ከድሮ ታሪክ ጋር እያዛመደ መማሰን ሙያ ብሎ ይዞታል

የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች ትልቁ ግቡ ስልጣን እንጂ ቆመንለታል ያሉት ጎሳ አይደለም።ቆመንለታል ያሉት ሕዝብ አጥንቱን ከስክሶ ለስልጣን እስክያበቃቸው ድረስ የአዞ እንባ ያነቡለታል።ስልጣን ላይ ሲወጡ ግን ስልጣናቸውን ማደላደል ብቻ ቀዳም ስራቸው ይሆናል።
 / መራራ ከአንድ ዓመት በፊት ላይ ኢሳት ብዙ የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች መገንጠልን እንደ ዋና ግብ አርገው ይናገራሉ ይህ ለምን ይሆናል ብለው ያስባሉ? ተብለው ሲጠየቁ የመለሱት ምላሽ እዚህ ላይ አይነተኛ አስረጅ ይሆናል።

ዶ/ር መራራ ሲመልሱ: ''አይመስለኝም የምኒልክ ቤተመንግስት ከደረሱ ሃሳባቸውን ይቀይራሉ ብዬ አስባለሁ። ህወሃትም እኮ እንዲህ ይል ነበር ምንሊክ ቤተ መንግስት ሲገባ ሁሉን ትቶታል" ብለዋል።

ይህ በህዝቦች ደም መቀለድ ነው።መገንጠልን እና የጎጥ ፖለቲካን እንደማስፈራርያ ''አያጅቦ መጣብህ'' እያለ ሕፃን ልጅን እንደሚያስፈራራ ሰው ይጠቀሙበታል ማለት ነው።እዚህ ላይ ማስረጃው እራሱ ህወሃት ነው።ዛሬ ላይ ሕወሃትን የትግራይ ገበሬ እንዴት ነው የሚገልጠው? አብረውት መሬት ይተኙ የነበሩ የጎጣችን ጉዳይ ነው በረሃ ያወረደን ሲሉ የነበሩ ቤተ መንግስት ሲገቡ እና ሱፍ መልበስ ሲጀምሩ ምነው ዘወር ብለው ለማየት ጊዜ አጡ? የጎጥ ፖለቲከኞች እንዲህ ናቸው።''ከኢትዮጵያ ጋር መደራደር እንፈልጋለን'' ሲሉ የነበሩት አቶ ሌንጮ አሁን የት ናቸው?  በእሳቸው ፖለቲካ ተስቦ እስር ቤት የገባው ምስኪን ኢትዮጵያዊ ወንድሜስ የት ነው? የጎጥ ፖለቲካ ውጤቱም ግቡም ከእዚህ የዘለለ አይደለም።

የጎሳ ፖለቲካ ስልጣን ለመያዝ ደግሞ ዛሬም ሆነ ነገ እንቅፋት ይሆኑኛል የሚለው ''ደንቃራ'' ከፊቱ ይታዩታል። እርሱም- በረጅም ዘመናት የተገነባው ያለፈው እና አሁን በሕዝቡ ልብ ውስጥ ያለው ኢትዮጵያዊነት ነው።ይህ ኢትዮጵያዊነት ደግሞ ባለፈ ማንነት፣ታሪክ፣ባህል እና እምነት ላይ የተመሰረተ ነው።ስለዚህ ዛሬ ሰበብ አስባብ ፈልጎ ያለፈ ማንነትን የሚንዱ ናቸው ያላቸውን የህዝብ ግጭቶችን፣በነበሩበት ጊዜ ጀግና ያስብሉ የነበሩ 21ኛው /ዘመን ግን ክፉ ተግባራትን እና ፈፅመው የሌሉ ታሪኮችን በመፍጠር የኢትዮጵያዊነት መሰረቶች እንዲናዱ ይሞክራል።

ለምሳሌ የብሔር ብሔረሰቦች ጉዳይ እና ፌድራሊዝም አስተዳደሮች በፅንሰ ሃሳብ ደረጃ ባልተፈጠሩበት ዘመን ለምን አልታወጁም ነበር? የሚመስል ''ውኃ ቀጠነ'' ንግግር ኢትዮጵያዊነትን ይሳደባል፣ያናንቃል።ይልቁን ፌድራልዝም በአለም ሳይታወቅ እነ አባ ጅፋር የራሳቸውን ግዛት በራሳቸው ያስተዳድሩ እንደነበር ግን በጋራ ከማዕከላዊ መንግስት ጋር በሚያገናኛቸው ጉዳይ ላይ አብረው ይሰሩ እንደነበር አያስተውልም።በዚህ ክፍል ውስጥ የኢህአዲግ/ወያኔ መንግስትን ጨምሮ በፅንፈኛ የእስልምና እምነት የፖለቲካ አላማቸውን ለማሳካት እስከሚፈልጉት ኃይሎች ድረስ የባለፈውን ታሪክ በዛሬ መነፀር እያዩ ህዝብን ማደናገር እና የዛሬውን ትውልድ በማያውቀው ጉዳይ አበሳውን ሲያሳዩት መመልከት የተለመደ ነው።

አሁን ባለንበት ዘመን በእዚህ አስተሳሰብ ሺዎች ተገድለዋል፣ሌሎች አያሌ ሺዎች ከመኖርያቸው ተፈናቅለዋል።ከእዚህ ሲዘል ደግሞ ማስረጃ ለሌለው ተረት ሁሉ ሃውልት ይሰራ ባይ ነው። የእዚህ አስተሳሰብ አራማጆች ዋና ግባቸው ''እኛ ስልጣን ላይ ከሌለን እና የምንፈልገውን ካልፈፅምን ጭር አይልም'' ባዮች ናቸው።ለእዚህ እኩይ ተግባር የሚተባበራቸው ፀረ-ኢትዮጵያ ኃይል ጋር ለመተባበር ዝግጁ ናቸው።ኢትዮጵያዊነት፣አንድነት እና ህብረት ሲጠነክር ይደነግጣሉ።ምክንያት የእነርሱ አስተሳሰብ በጠንካራ ኢትዮጵያዊነት አስተሳሰብ ፊት ሞገስ እንደሌለው እና እነርሱንም ወደ ስልጣን ኮርቻ ላይ እንደማያፈናጥጣቸው ይረዳሉና።

አሁን ኢትዮጵያ ላለችበት  ፖለቲካዊ ችግር  መፍትሄዎቹ 


1/ የባለፈው በጎውን ይዘን፣ ክፉውን ወቅሰን እና ስላለፈው በሌለበት ጉዳይ ያሁኑን ትውልድ ውቀስ አቁመን ለወደፊቱ ልብ ሰብ መጀመር  

ከሁሉ በፊት መረዳት የሚገባን ጉዳይ አለ።ኢትዮጵያ በአንድ ምሽት በቤተ-ሙከራ ውስጥ የተሰራች ሀገር አይደለችም።የብዙ ዘመናት የህዝቦቿ አብሮ የመኖር፣የመተሳሰብ፣የመሰደድ፣የጦርነት፣የሰላም ሁሉ ውጤት ነች።እኛ የተለያየ ጎሳ የኢትዮጵያ ልጆች ባለፈው ታሪካችን ብዙ አንድ የሚያደርጉን ነገሮች አሉ።ብዙ የዛሬ ማንነታችን ላይ አሻራ ያላቸው ማንም በቀላሉ እንዲነቅላቸው የማይፈቀዱለት የጋራ ታሪክ አለን።በአንፃሩ ደግሞ የሚያሳዝኑ ታሪኮች ባለቤትም ነን።ዛሬ የሚያስፈልገን ያለፈው አንድ የሚያደርጉንን አጉልተን ባለፈው ለተሰሩት ስህተቶችን በትምህርትነት ወስዴግን ግን አሁን ያለውን ትውልድ ባልነበረበት ጉዳይ መውቀሱን ተተን  ወደፊት ስህተቶች እንዳይደገሙ  አርመን መኖር ብቸኛ አማራጫችን ነው።ከእዚህ በዘለለ ባለፈ አሳዛኝ ታሪክ ሊሽር የሚችለው በዛሬው ትልውድ በጎ የታሪክ ተግባር ነው ብለው ማመን መሰረታዊው ገዢ አስተሳሰብ መሆን አለበት

አሁን ሕዝብም የፖለቲካ ፓርቲዎች በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ያላቸውን ግልፅ አስተያየት እና ይህ እይታቸው የነገውን የሀገራችንን መፃኢ ዕድል ማሳያ እንደሆነ አመላካች ነው።ኢትዮጵያ ነገ እንዴት እንድትሆን እንደሚፈልጉ ሁሉ የባለፈው ዕይታቸውም በግልፅ መቀመጥ ያለበት ጊዜ ላይ ደርሰናል።የጎጥ ፖለቲካ ከሃያ አራት አመታት በላይ ዕድል ተሰጥቶታል በቃህ መባል አለበት።ይህ ማለት ማንም ጎሳ በፈለገው  ቋንቋ የመናገር፣በፈለገው መንገድ ባህሉን ማሳደግ፣የእራሱ የሆነ በአገሪቱ ሕግ የሚመራ የእራሱ የመገናኛ ብዙሃን የመክፈት (አሁን እድሉን ያላገኙትን እንደ ትናንሽ ቁጥር ያላቸውን ጨምሮ)፣ በሂደት ደግሞ አገሪቱ ሁለት እና ሶስት ብሔራዊ  ቋንቋ እንዲኖራት ማድረግ ወዘተ በዲሞክራሲ መንገድ የተመረጠ መንግስት ምክር ቤት የሚወስነው ሕዝብ በነፃ የመገናኛ ብዙሃን የሚወያይበት እና በፍቅር የምስማማበት ወይንም ለብዙሃኑ ፍላጎት የሚገዛበት ነው።ይህ ዝርዝር ጉዳይ ነው።አሁን ላይ ሆነን ብዙ ማለት የለብኝ ይሆናል።ግን የጎሳ ፖለቲካ እነኝህን መብት የሚያስከብር የሚመስላቸው የዋሃን ስላሉ እነኝህ መብቶች በኢትዮጵያዊ ጥላ ውስጥ የሚፈቱ እንጂ በጎጥ ፖለቲካ የሚፈቱ አይደሉም ለማለት ነው። 

2/ የጎሰኛነት ስሜት እንደ ኩፍኝ በሽታ ነው ይለቃል።
የሃገራዊ ስሜት ን የተዳፈነ ፍም ነው።
ገራዊ ስሜትን ማዳበር ያስፈልጋል

በአንድ የተወሰነ ርዕዮተ አለም ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ አስተሳሰብም ሆነ በመንደርተኝነት ላይ የተመሰረተ ሥራ የአንድ ሰሞን ግርግርታ ናቸው።የኩፍኝ በሽታ በትክክል በምሳሌነት ይመስላቸዋል።ኩፍኝ የአንድ ሰሞን በሽታ ነች።ካልታከመች አደገኛ ነች።ከታከመች ግን የትም አትደርስም።በዘመነ ደርግ ስለሶሻሊዝም ስህተት ለአንድ የቀበሌ ጥበቃ መናገር እስከሞት የሚያደርስ ፍርድ ሊያሰጥ ይችላል።በወቅቱ ገዳዩ ስለመግደሉ ''ትክክለኛነት'' እርግጠኛ ነበር።ከአመታት በኃላ 'ኩፍኙ' አልፉ ሲመለከተው ግን ስህተቱ ይታየዋል።የጎጥ ስሜት እና መሰረቱ እርሱን ያደረገው የፖለቲካ ዘውግም ይሄው ነው።ዛሬእሞትለታለሁያለውየሰፈርስሜት ነገ በኢትዮጵያዊነት እስኪማረክ ብዙ ይባልለታል።ያኩራራል።ያስደስታል።በሂደት ግን መማርያ ይሆናል።እንደ አቶ ሌንጮ ቀስ ይላል ወይንም ድምፁን አጥፍቶ ይቀራል።
የሃገራዊ ኢትዮጵያዊነት ስሜት ግን ጥብቅ የሆነ ማኅበራዊ፣ስሜታዊ እና ዘመናዊ እሴቶችን ይዞ ከውስጥ እየፈነቀለ ጥላቻ ላይ በረዶ ይከልስበታል።እናም  ዘለቄታዊውን የጋራ ቤታችንን ኢትዮጵያን እንጂ ጎሳዊ ስሜት ይዞ መሄድ አያዋጣም።ስልጣን ከሆነም በኢትዮጵያዊ እውነተኛ ስሜት መነጋገር አንድ ነገር ነው።በወጡበት ጎጥ ስም እየማሉ ወጣቶች እና ሕፃናት ላይ እንዲሁም የሌላ ጎሳን በጥላቻ ዘይት እየቀቡ ሕዝብ ማፋጀት ግን ለጊዜው የተሳካ ቢመስል ውሎ አድሮ የህሊና ቁስል ነው።

3/ጎሰኘነት የጎሳን ስሜት ለመኮርኮር ይጥራል።ሃገራዊ ስሜት ግን 
ለምን ይኮረኩራል።ሕዝብ ለሀገራዊ ጉዳይ ጋ እንዲሰጥ መስራት።

በጎሳ ላይ የተመሰረተ ሁል ጊዜ እጁም፣እግሩም መላ ሰውነቱ የጎሳውን ውሎ፣ብሶት፣ትልቅነት ወዘተ አግንኖ ለማቅረብ ይጥራል።ስራው ሁሉ የጎሳውን ስሜት ለመኮርኮር ነው።ሃገራዊ ስሜትን የሚያንፀባርቅ ግን አቅርቦቱ ሁሉ ሃገሩን አልፎም አካባቢውን ከፍ ሲል ደግሞ ዓለምን ይኮረኩራል።የሚነሱት ጉዳዮች የሌሎችን ሃገራት ጥቅም እና ጉዳት ስለሚመለከት ትኩረት ይስባል።እርግጥ ነው የጎሳ ጥቅም የሌሎችን የሚነካባቸው ብዙ መንገዶች ይኖራሉ።በሀገራት ደረጃ ስናየው ግን ብሔራዊ ጉዳይ ላይ ያተኮረውን ቅድምያ የሚሰጡባቸው ብዙ መንገዶች አሉ።የጎሳ ፖለቲካ  ከማበጣበጥ እና ከመከፋፈል ባለፈ የሚያመጣው  ፋይዳ የለም። ስለሆነም ሃገራዊ ጉዳዮችን ማጉላት የጎሳ ስሜቶችን ማኮሰስ የሚችል ትውልድ መነሳት አለበት።ይህ ማለት ከአንድ ጎሳ  በመወለዳቸው ብቻ በደረሰባቸው በደል ድምፃቸውን ያሰሙትን ሁሉ መኮነን ማለት አይደለም።ከተበደሉት ጋር አብሮ መጮህ ነገር ግን የተነገረውን በደል አስታከው በጎሳው ስም የግል የስልጣን ጥማታቸውን ለማርካት የሚጥሩትን መከላከል አስፈላጊ ነው።



4 / በረጅም ጊዜ የጎሳ ለቲካ እየከሰመ እንዲሄድ የሚያደርጉ 



     ምክንያቶችን ማዳበር እነርሱም: -    

1/ የከተሞች መስፋፋት እያደገ መሄዱ፣
2/ የኢንዱስትሪ መስፋፋት የሚፈጥረው ህብረት እና አንድነት ስለሚኖር፣
3/ የሃይማኖታዊ እና ማኅበረሰባዊ ግንኙነት መጠናከር እያደገ መሄድ እና
4/  የጎሳ ፖለቲካ የሚያመጣው እልቂት እና ግጭት ሕዝብ እየተማረ ስለሚመጣ የሚሉት ይጠቀሳሉ።

በመጨረሻም ኢንጅነር ይልቃል ስለ ጎሳ ፖለቲካ (ጥያቄው የብሔር ፖለቲካን ነው) ሲጠየቁ የተናገሩትን ልጥቀስ-

’'የግለሰቦች መብት ከተከበረ የቡድን መብት ይከበራል።ባህሌ፣ቋንቋዬ፣እምነቴ  እኔ ውስጥ አለ። በቋንቋዬ መናገር የእኔ መብት ነው፣የሙያ ማኅበር መመስረት የእኔ መብት ነው።የእኔ መብት ያልሆነ የቡድን መብት አይኖርም።የግለሰብ መብት ከተከበረ የማይከበር የቡድን መብት የለም።የወለጋን ሕዝብ ለማስተዳደር ከጎጃም ማምጣት የለብንም።የፌድራል አስተዳደሮች የራሳቸውን ቋንቋ መምረጥ እንዳለባቸው የታወቀ ነው።ዛሬ የአንድ ሰፈር ሰው የሌላ ሰፈር ሰው የሚወክልበት ሁኔታ የለም።ይህንን ዘመን አልፈነዋል''

//////////////////////////------///////////////////------/////////////////////////------/////////////////////////------/////////////////
ይህ ፅሁፍ  በኦስሎ፣ኖርዌይ የመወያያ መድረክ ላይ ከሁለት  ዓመታት በፊት በጸሐፊው  ቀርቦ ነበር።በእዚሁ ጉዳያችን ገፅ እና ሌሎች ድረ ገፆች ላይም ከጉዳያችን ገፅ ላይ ከወጣ በኃላ  ተወስዶ ከሁለት ዓመት በፊት ወጥቶ ነበር።


 ጌታቸው በቀለ 
ኦስሎ፣ኖርዌይ 
getachwb221@gmail.com 


ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
www.gudayachn.com

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።