ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, October 30, 2014

አብዮት ለአምባገነኖች መድኃኒት ነው ስንል የአፍሪካ አብዮት ህንፃ በማንደድ ተጀምሮ በመተራመስ ማለቅ አለበት ማለት ግን ሊሆን አይችልም(የጉዳያችን ምጥን ሃሳብ) እና አሜሪካ ዛሬ የት እንደገቡ ያልታወቁትን የቡኪናፋሶ ፕሬዝዳንት ከስልሳ ቀናት በፊት ዋሽግተን ድረስ ጠርታ እንዴት አሞካሽታ ነበር? (የሶስት ደቂቃ ቪድዮ)

የቡክናፋሶ ፕሬዝዳንት ካምፓዌሪ  እና የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ 

''ወጣቶቹ የሚሉት ሃያ ሰባት  ዓመታት (የፕሬዝዳንቱ  እና የፓርቲያቸው የስልጣን ዘመን)  በጣም  እረጅም ነው....ተስፋ ከሰጡት ውስጥ አንዳቸውንም አልፈፀሙም'' ''Twenty-Seven years is  already too long ...non of the promise was kept'' የቢቢሲ ቴሌቭዥን  ጋዜጠኛ ለይላ አድጆኒ ከቡኪናፋሶ ዋና ከተማ ኦጋዱጉ ዛሬ ጥቅምት 20/2007 ዓም ከዘገበችው።
 ቢቢሲ  ዓለም አቀፍ አገልግሎት ራድዮም አሁንም  በዛሬው ዕለት  ዘገባው ''የቡኪናፋሶውን  ጉዳይ  ብዙ ከሳሃራ በታች ያሉ ሃገራት መንግሥታት በአንክሮ እየተከታተሉት ነው።ብዙ የአፍሪካ ሀገር መሪዎች ለእረጅም ጊዜ በስልጣን የቆዩ ናቸው የዩጋንዳው ሙሰቬኒ እና የሩዋንዳው ካጋሜ እና ሌሎችም በስልጣን ላይ ለእረጅም ጊዜ የቆዩ ፓርቲዎች አሉ'' ብሏል።

የቡኪናፋሶው አመፅ ''የጥቁር አብዮት'' (Black Spring) የሚል ስም ተሰጥቶታል።ሕዝብ ምላሽ ካላገኘ አብዮትን ብቸኛ አማራጭ አድርጎ  መነሳቱ የተረዳ ነገር ነው። ሕዝብ ሲነሳ ግን ፓርላማውን፣ሆቴሉን በእሳት እያነደደ መሆኑ አሳዛኝ ነው።አምስቱ ስርዓተ ማኅበራት ተብለው ከሚጠቀሱት ውስጥ የባርያው ስርዓተ ማኅበር አንዱ የሚገለፅበት የአመፅ መንገድ የአሰሪው መጠቀምያ የሆኑትን የመገልገያ መሣርያዎች ለምሳሌ ማረሻውን እና የመሳሰሉትን መሰባበር ነው።ሕብረተሰብ እያደገ ሲመጣ ይላል የሕብረተሰብ እድገት ትረካ አመፆች የመገልገያ መሳርያዎችን ማጥፋት ቀረ።ምክንያት ከድል በኃላ ለህብረተሰቡ ጥቅም እንደሚውሉ የሰው ልጅ ተገነዘበ።እውነት ነው ዛሬ በሩቅ ምስራቂቱ ሀገር ጃፓን የፋብሪካ ሰራተኞች ዓመፃቸው ብልሃት በተሞላበት ሀገራቸውን እና ንብረታቸውን በማያወድም መልክ መከወን የጀመሩት።

አብዮት የለውጥ ብቸኛ አምራጭ ሆኖ የመምጣቱ እውነታ አምባገነኖች በስልጣን መኖርን የሞት እና የሕይወት ጉዳይ እስካደረጉት ድረስ አይቀርም።ነገር ግን አብዮት ሁሉ የነበረ ህንፃን እና ፓርላማ በእሳት ማንደድ አለበት ማለት አይደለም።ማቃጠል ጀብዱ ሊሆን አይችልም።ተቃዋሚ የመምራት አቅሙ የሚፈተነው እዚህ ላይ ነው።አብዮት መሪ፣መነሻ እና ግብ የተቀመጠለት ሲሆን ህንፃ አያነድም።እንደፈለገ አድርገህ ህንፃውን አንድደህም ቢሆን አብዮቱን አምጣው የሚል ተቃዋሚ እንደማይኖር ሁሉ  ቀድመው ያልመሩትን በኃላ ሊገቱትም ሆነ ሊመሩት ይቸግራል።

ባጭሩ ሕዝብ እምቢተኝነት አጠንክሮ እንዲሄድ ሲነገር ንብረትን ማውደም፣የህዝብም ሆነ የግለሰብ ንብረትን ሕዝብ እራሱ እንዲጠብቅ አብሮ ማስተማር ተገቢ ነው።አዎን! ዋጋ የማያስከፍል አብዮት የለም።ግን የአፍሪካ አብዮት በዝቅተኛ ወጪ እና በአስተዋይ ምሁራን የማይመራበት ምክንያት ምንድነው? የቡኪናፋሶን የዛሬው የፓርላማ መቃጠል አስታከን ስንናገር መቃጠሉ ሳይሆን ግቡ ለውጡ እና እምቢተኝነቱ መሆኑን ማሳየት ተገቢ ነው።መቃጠሉ ያሳዝናል።አምባገነንነትን መቃወም ያስመሰግናል።የምዕራቡ ሚድያ አገላለፅ ለአፍሪካ ውስጠ ወይራ ሆኖብኛልና ነው ይህንን ማለቴ።

አሜሪካ የዛሬው የቢኪናፋሶው አመፅ ሊነሳ ቀናት ሲቀሩት የቡኪናፋሶን አምባገነን መሪ እንዴት እንደምታሞካሽ ከእዚህ በታች ባለው ቪድዮ ይመልከቱ እና የአቶ ኃይለማርያም እና የልዑካናቸው ባለፈው ወር በፕሬዝዳንት ኦባማ የተሞካሹበትን አግባብ ያስታውሱ።
 ''ቡኪናፋሶ ለአካባቢው ሰላምና ፀጥታ ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገች ነው'' የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ዛሬ የት እንደገቡ ያልታወቁትን የቡኪናፋሶ ፕሬዝዳንት  ከስልሳ ቀናት በፊት ዋሽግተን ድረስ ጠርተው ሲያሞካሹ  (የሶስት ደቂቃ ቪድዮ)

ቪድዮ - የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ዩትዩብ
Video Source - US State Department youtube
ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

Tuesday, October 28, 2014

''በሲአይ ኤ የዓለም እውነታ መፅሐፍ መሰረት 96.6 ሚልዮን ከሚሆነው ኢትዮጵያዊ 34% የሚይዙት የኦሮምኛ ተናጋሪ ማህበረሰቦች ውስጥ የኢትዮጵያ መንግስት በአራት ዓመታት ውስጥ ብቻ በሕገወጥ መንገድ ቢያንስ 5000 የሚሆኑትን አስሯል'' ብሉምበርግ

Photo BBC

Amnesty Says Ethiopia Detains 5,000 Oromos Illegally Since 2011

Source - Bloomberg
Ethiopia’s government illegally detained at least 5,000 members of the country’s most populous ethnic group, the Oromo, over the past four years as it seeks to crush political dissent, Amnesty International said.

Victims include politicians, students, singers and civil servants, sometimes only for wearing Oromo traditional dress, or for holding influential positions within the community, the London-based advocacy group said in a report today. Most people were detained without charge, some for years, with many tortured and dozens killed, it said.

“The Ethiopian government’s relentless crackdown on real or imagined dissent among the Oromo is sweeping in its scale and often shocking in its brutality,” Claire Beston, the group’s Ethiopia researcher, said in a statement. “This is apparently intended to warn, control or silence all signs of ‘political disobedience’ in the region.”

The Oromo make up 34 percent of Ethiopia’s 96.6 million population, according to the CIA World Factbook. Most of the ethnic group lives in the central Oromia Regional State, which surrounds Addis Ababa, the capital. Thousands of Oromo have been arrested at protests, including demonstrations this year against what was seen as a plan to annex Oromo land by expanding Addis Ababa’s city limits.

Muslims demonstrating about alleged government interference in religious affairs were also detained in 2012 and 2013, Amnesty said in the report, titled: ‘Because I am Oromo’ – Sweeping Repression in the Oromia Region of Ethiopia.

Government Denial


The state-run Oromia Justice Bureau said the findings were “far from the truth” in a reply to Amnesty included in the report. “No single individual has been and would not be subjected to any form of harassment, arrest or detention, torture for exercising the freedom of expression or opinion.”

The majority of detainees are accused of supporting the Oromo Liberation Front, which was formed in 1973 to fight for self-determination, according to Amnesty.

Senior Oromo politicians Bekele Gerba and Olbana Lelisa were jailed in 2012 for working with the group, which was classified as a terrorist organization by lawmakers in 2011.

“The accusation of OLF support has often been used as a pretext to silence individuals openly exercising dissenting behavior,” Amnesty said.

The bulk of Amnesty’s information came from interviews with 176 refugees in Kenya, Somalia and Uganda in July this year and July 2013. More than 40 telephone and e-mail conversations were also conducted with people in Ethiopia, it said.

Some interviewees said they fled the country because of conditions placed on them when released, such as being told to avoid activism, meeting in small groups, or associating with relatives who were political dissenters, the report said.

Amnesty has been banned from Ethiopia since 2011 when its staff was deported.

To contact the reporter on this story: William Davison in Addis Ababa at wdavison3@bloomberg.net

To contact the editors responsible for this story: Antony Sguazzin at asguazzin@bloomberg.net Paul Richardson, Karl Maier

Saturday, October 25, 2014

''አቶ መለስ ዜናዊ ተመርዘው እንደሞቱ ይጠረጠራል '' ''Meles Zenawi, of Ethiopia, died of suspected poisoning'' በደቡብ ሱዳን ዜና አገልግሎት ድረ-ገፅ ላይ ደቡብ ሱዳናዊው (Dr. John Chuol Kuek) ዶ/ር ጆን ቹል ''የኢጋድ አባል ሃገራት ድብቅ ፍላጎት በደቡብ ሱዳን ቀውስ ውስጥ'' በሚል ርዕስ በፃፉት ፅሁፍ ውስጥ ካሰፈሩት




IGAD Countries Imposed their hidden Interest in South Sudan Crisis


By John Chuol Kuek, PhD


October 24, 2014 (SSNA) -- IGAD stands for Intergovernmental Authority on Development. This organization was founded in 1986 by the following countries: Djibouti, Ethiopia, Somalia, Sudan, Uganda and Kenya, with a focus on development and environmental control. Its mission was revised and upgraded in 1996 to address issues of severe drought and development in the region. In addition, IGAD’s mission expanded to coordinate and balancepolicies in the areas of socio-economic, agricultural development, environmental protection, and political and humanitarian affairs. The creation of IGAD was viewed positively in the region. Eritrea became independent and joined the group in 1993 and South Sudan joined the union and became the eighth member of IGAD in 2011, after celebrating its independence. Initially, IGAD was viewed as an emerging leader by both the African Union, which represents the continent of Africa, and the United Nations.

As IGAD started to implement its programs with good will, the African Union Peace and Security Council approved an IGAD proposal to deploy a Peace Support Mission in Somalia in September of 2006. IGAD played a role of a policeman in the region, trying to keep peace and support developments in Somalia and the surrounding region. On February 21, 2007, the United Nations Security Council approved Resolution 1744, which authorized the deployment of a new African Union Mission to Somalia, relieving theIGAD support mission troops. Reflecting back on the role of IGAD, this coalition of countries was intended to keep peace and bring economic development to the region and not to establish dictatorial empires in the region. IGAD was supposed to assist in the peace-keeping mission by being non-partisan in their politics and not in their support of criminals to stay in power, especially those who killed their own citizens.


IGAD’s Role in South Sudan


At this time, with the current political crisis ravaging South Sudan, this writer, who is South Sudanese and a member of various past UN-sponsored groups that have attempted to bring peace to this country, an important question needs to be asked of IGAD and its member nations: What is the role of IGAD in East Africa and South Sudan at this time? Are IGAD’s intentions honest and genuine, which are to bring peace, or is it to support chaos, anarchy, and political oppression? These questions and many more need to be quickly answered as the crisis in South Sudan continues to escalate beyond a solution. Let us now look at some of the individuals who are intimately involved with IGAD in the region.  

Who is Yoweri Museveni of Uganda, to begin with? Museveni has a long and negative presence in the region. He was involved in rebellions that toppled Ugandan leaders Idi Amin (1971–79) and Milton Obote (1980–85). After the disappearance of these “icons”, the presidents of Burundi and Rwanda and Dr. John Garang of South Sudan all perished in airplane crashes, and Meles Zenawi, of Ethiopia, died of suspected poisoning, I have given Mr. Museveni a new moniker, “the cock among the hens in the region”. This man has a lot of blood in his hands. For example, he is responsible for the death of the two presidents that sparked one of the worst genocides in human race after the holocaust of 80,000 Tutsi in Rwanda. Also, Museveni was suspected in playing a key role in the first Congo war (1996-1997). He has also long been suspected of John Garang’s death, which remains an unsolved mystery today. He has been manipulating three inexperienced leaders, Paul Kagame, Uhuru Kenyatta, Hailemariam Desalegn, and are cronies as is his bodyguard, Salva Kiir.All are simply his puppets. Another example is the implementation of Ugandan troops who are to be found everywhere in the region, and which he is using in an act of demagoguery.  

Moreover, let us examine what has been going on in Somalia recently. Is the conflict in Somalia any different from what is currently taking place in South Sudan? In this conflict, like the one in South Sudan, international “actors”, must either be naïve or simply burying their heads in the sand and denying that a holocaust is taking place. Both international and regional actors have been providing interest-based support, through weaponry or money, to different warring parties in the same country, in a manner suggestive of not really caring who the winner is. In many ways, this is no different than what European empires, such as the British, did in Africa in the past. 

This has made Somalia a chaotic country with anarchy and where killing is simply the rule of the day. As a result, this damage will now take years if not decades to resolve. The international actors, such the Arab and Western states, have been drawn into Somalia’s conflict for various reasons including the prevention of terrorists from establishing foothold in the region to acquiring new battlegrounds and exploiting natural resources. This type of strategy, to conquer and divide, by IGAD members, has made it very difficult for the adoption of a common and unifying position by the Somalians. In this writer’s opinion, there is no doubt that IGAD is in cahoots with a new generation of dictators whose sole purpose in East Africa is to exploit their respective countries. As a result, neighboring countries who falsely label themselves as stable and democraticcountries are benefiting financially from this chaos.   

In the South Sudanese conflict, which really prompts this commentary, Museveni, along with his cronies and the rest of the IGAD leaders came out with a bold statement condemning Dr. Riek Machar, who is considered a legitimate leader amongst many of the populace in South Sudan, and blamed him as the instigator of the Juba Nuer massacre. Museveni swore to capture Machar within in a few days if he refused to give up fighting. Their statement is a clue to their hidden interest in South Sudan. Museveni is the primary driving force behind the conflict in South Sudan. The country at the same time continues to be blind to the fact that Museveni does not like or respect Salva Kiir as the current leader in South Sudan. He portrayed Kiir as a fool. Why has Museveni despised Machar? He views Machar as an emerging leader in the region with a strong and genuine approach toward the governance of South Sudan and similar to Garang. Moreover, Machar has the same type of charisma as Garang did and with the ultimate goal of one day uniting the entire continent of Africa and includingeastern Africa.

Museveni is a confused and unwise leader. He prefers to manipulate and control others for his own self-interests. Given his underlying motives, Museveni now has two missions in the South Sudanese war- to get rid of Machar by any means possible and as well as Salva, and thus opening the door to force his own agenda. A good example is a new military cooperation pact recently signed between Uganda and South Sudan, which paves the way for the South Sudanese government to smuggle guns and ammunitions despite an embargo. This military cooperation is an unnecessary evil at this crucial time of peace negotiations for the people of South Sudan. One of the main reasons that the peace talks became stalled in Addis Ababa is because of the undesired presence of the Ugandan military in South Sudan. The contradiction spelled out by this action is that international parties and IGAD have not opposed such a foreign presence, suggesting that in fact they support this political and military move. This author poses this question: Why should any efforts be made to have a peace agreement in South Sudan when in fact these political bodies have not recognized the blatant violations by Uganda. Has Kiir simply fooled himself into thinking that by agreeing to have the Ugandan military present in South Sudan that Museveni will support him in the end?

Also, why IGAD not serious about this peace process? Here another reason. The peace process in Addis Ababa has been deliberately slowed down due to numerous regional and international interests. Though IGAD is the designated broker of this peace, the international players, including Museveni, hold the key whole process. Troika members also include United States, but unfortunately, seems to be ambivalent or give mixed messages in its relationship to IGAD. The lack of assertiveness on the part of the United States only helps Museveni solidify his position and grip on the political future of South Sudan.  In addition, the organization lacks leaders whose true interests are righteous, genuine, and humane, and who are really motivated to bring true peace and stability in the region. Of the IGAD countries, one must admire and acknowledge Ethiopia for maintaining neutrality in peace process for South Sudan. Unfortunately, this country lacks the financial clout to broker a workable peace initiative.


The Contradictions of IGAD


While IGAD seems to be corrupted by Museveni and others in relation to South Sudan, it has been quite helpful in bringing peace and tranquility to other countries including Somalia. This contradiction is very troubling in light of the human rights struggles that are of parallel concern in both South Sudan and Ethiopia. Are there underlying and hidden payoffs and agendas for IGAD nations in not supporting the peace process in South Sudan?

Within the mission statement of IGAD, great emphasis was placed on this organization serving as the conduit of peaceful resolutions among countries that disagreed on a variety of sociopolitical issues, which in turn would help boost the sustainable development of all member countries in the region. IGAD member states agreed to invest time and money to take effective collective measures to eliminate threats to regional cooperation, to establish effective mechanisms of consultation and cooperation for the peaceful settlement of differences and disputes, and to agree to offer all levels of technical and diplomatic assistance in the resolution of disputes between member states before being referred to other regional or international bodies including the United Nations (IGAD 1996). Within this purpose, three key areas were identified: a.) conflict prevention, management and humanitarian affairs; b.) infrastructure development and food security; and c.) environmental safety control. A good example of where IGAD triumphed was in the peace process that was garnered between Sudan and the new country of South Sudan, which was facilitated by the United States under President George W. Bush.

Thus, IGAD had earned an outstanding grade on that particular mission, and truly holds the position of being a neutral organization whose primary should simply be to help countries resolve both internal and external problems, with no other motives in mind. In the cases of both Somalia and Sudan, IGAD displayed no sense of being corrupted and in fact was extremely fair and equitable in all aspects of the peace processes in both countries. To keep the region safe, IGAD members agreed to not support any party that would attempt to bring down a democratically defined country, and instead would do everything possible to safeguard stability and freedom. This initiative was hijacked by Museveni and Kiir to commence the current conflict on December 15, 2014 and to assassinate to kill Machar and his political colleagues.  Perhaps in the end, only God knew of Museveni and Salva’s plans to harm the nation. At the same time, thank God that Riek and all the political detainees survived. Now that Riek and his political allies survived and spoken the truth, IGAD leaders have no legitimate reason to gang up against the SPLM/A in Opposition. In detailing the truth about IGAD’s interest, I am afraid that some prominent member states will withdraw their membership in recognizing that IGAD has not been fair, but instead partial to certain personalities.


The Ending of IGAD Legitimacy in the Region


South Sudan has been strained recently as other countries in the region have also experienced instability. This could probably be the worst turning point in the region if IGAD member states do not pay attention to the damage they have created and are also supporting. The region needs to look back to what had happened to both Ethiopia and Somalia during the Cold War which led to the end of dictatorial regimes in Ethiopia and Somalia. The newly “emerging leaders” in the post-Cold War era wanted to promote policies of peaceful relations and a new era of cooperation and co-existence. This was one of the ways to unite the East African countries, such as the Horn of Africa and Great Lakes region as a one giant continental business hub for entire Africa.

This promise is now slipping away as the member states started pursuing their individual and perhaps even selfish-interests. Instead of uniting the region, and handling issues with care and dignity, Museveni, Kenya’s Uhuru Kenyatta, and Rwanda’s Paul Kagame have appeared to expand their territories and operate in a trilateral “coalition” in a rather zealous manner with Tanzania and Burundi.

Tanzania has warned that any efforts to sideline it while fast-tracking the East African Federation could cause failure for the whole regional integration project. Dr. Ladislaus Komba, Tanzania’s High Commissioner to Uganda, predicted “doom” for the East Africa Community if alienation between the countries continued. How about between Uganda and Sudan, LRA, and the SPLM/A North? South Sudan invited the SPLM/A North and Darfur groups into the war, fighting alongside the government. The Ugandan military has armed these rebels, hoping they get rid of Machar’s forces and continue through Sudanese territory to help change the regime in Khartoum.  The two countries will start fighting a proxy war, which could lead to a serious confrontation between the two countries. When this happens, what will other IGAD countries like Ethiopia and Kenya do? Will they remain neutral or pick sides? How about other interests around the world, such as the Islamic fundamentalists in West and North Africa? I am going to leave it to those regional analysts to ponder.


Pitfalls on the Current Peace Proposal


Upon studying the IGAD’s current peace proposal for South Sudan, the plan has not really deviated from the idea of having lasting peace in South Sudan.   However, this IGAD proposal fell short of addressing what brought this “senseless war” to this young country in the first place. This proposal infers that IGAD’s plan is not to eliminate the conflict, but rather to help manage it in a productive way. Though IGAD countries have been tirelessly working on emerging regional wars, there have been three major competing interests that have hindered the peace process and which remain unaddressed. These are interests that are based on power, rights, and interests. The three key players in this peace process, IGAD, the government of South Sudan and the SPLM/A in Opposition, have attempted to line up behind these three issues. IGAD should have been the one to identify these issues, but instead has lagged behind suggesting little motivation to resolve problems in the region. 

Power is often expressed through the use of authority, oppression, and the forced separation of people and groups. IGAD member countries have one thing in common which is to remain in power as long as possible, and at any cost. Any resolutions proposed toward the removal of a president in power are viewed by this organization as going against the interests of, or contrary to, IGAD and not in aiding the situation in South Sudan. IGAD member countries were originally expected to use their formal and informal authority to broker a resolution to this country’s problems, but it is heartbreaking to see that they have neglected this fundamental premise stipulated in their guidelines.

In the case of the Juba Nuer massacre, which occurred in December 2013 in South Sudan, the SPLM/A in opposition did not need to conduct any form of research to convene a meeting with IGAD members to prove to them that indeed the massacre took place. This massacre has been documented by various humanitarian groups and the United Nation that it is clearly considered an obvious form of genocide. Why did IGAD mediators not act based on the facts? Now, IGAD is rewarding the very government that just committed this despicable crime with more power to kill more innocent people again and again. The rights-based approach is the card played by the SPLM/A in Opposition to tell the world that the president lost his legitimate position on December 15, and therefore, he could no longer serve as the president. The key players or brokers in this process did not want to hear this fact because they knew that it is real.   

A real and genuine interests-based approach is oriented toward problem-solving based on the needs of those involved, and not based on subjective feelings and politics. The party at fault and even the perpetrator often tries to move forward with the explicit goal of forgetting what happened and move on to a new chapter. The South Sudanese government is playing this card, saying a legitimate government cannot be asked to step aside before its term ends. The IGAD member countries seem to be favoring this claim rather than addressing the root causes of the conflict. That is, they are siding with the current government. This begs a crucial question: Why have the IGAD countries not moved in the direction of pushing for the current leadership to abandon South Sudan since the hallmark of the current government is pure corruption, hatred, and totalitarianism? The answer to this question is rather simple, the IGAD mediators are equally part of the corruption and have no interest in seeing to it that South Sudan become a peaceful and democratic country. In Kenya’s conflict between the Mwai Kibaki and Raila Odinga tribes, Uganda created this very system IGAD is now attempting to impose on the South Sudanese rebels.

Can all three approaches be combined for the benefits of solving this very conflict? The answer of course is YES. All these methods-authority-based, right-based, and interest-based- can be useful and are deemed necessary in this current political situation. As a mediator, you have to acknowledge that such a thing had occurred, but you have to take a tough stand to resolve it. Meeting with warring parties, other parties and civil society to discuss the needs of everyone involved also can be instrumental in moving toward an interest-based solution, which the SPLM/A in Opposition longs for. The IGAD mediators can assist the warring parties to move from their complaints to understanding their own interests. Their complaints are often based on their position or perceived unfairness. They are often all-or-nothing statements and in the end only one person’s solution to the problem. Interests, on the other hand, are the motivations that are often unspoken and based on personal values and experiences. They are the reasons behind the complaint that IGAD favored one side or the other.

The IGAD proposal to ending the war in South Sudan notes 28 items to be implemented by the warring parties and other stakeholders. Below are the five items which I consider to be the most problematic in the peace process.   First, there shall be no third vice president in this federal transitional government if this is what IGAD want to introduce to the South Sudanese people. Second, like Rwanda and Ethiopia in the region, the prime minister in South Sudan should be the one entrusted to implement national policies and leading the government to negotiate what is best for the country as defined by the stakeholders, the citizens of the country. The prime minister shall also be entrusted with the function of formulating the government programs of action in consultation with council of ministers. Third, the prime minister of the TGONU shall be eligible to stand for any public office in the national elections at the end of the transitional period. What in the world the IGAD is doing, proposing a useless prime minister position for the Opposition? I am wondering if this makes sense to IGAD members themselves. This document is an invitation of more conflicts, nothing less. Anybody would disown this cheap and shallow proposal to end this intensive war. It does not address a solution to this war in any way.

Fourth, it would make sense if the IGAD proposes that the executive of the transitional government shall comprise the president, the prime minister and council of ministers. I am not in favor of this model at all any way. Why not using the same system that is already in use? We need a president and a vice president system. Regardless of any of these methods, now, the debate would lie in WHO is going to lead this transitional government of national unity and complete all the steps discussed and approved in the peace talk? Will Salva lead this transitional government until election and be able to follow all the steps to ensure war does not happen again? If this is what IGAD believes and wants, it is not going to solve the problem. It’s indeed better to keep searching for a better scenario until a solution is sorted than reaching a cheap deal now only to return to war in a few months after. Salva would not want to change the status quo at all in South Sudan. He has forgotten the very reason he fought the Khartoum government for and the people who fought with him that he fought to change the status quo. He gestures this already in his circumstantial speeches that he does not want federal system and no Machar again in his government.

Finally, I agree to the fact that a permanent constitution be reconstructed and used by the transitional government, and shall be based on federalism, being mindful of diversity with more power to states. This process will only be achieved under a different leader than Kiir. Once this proposed structure is put in place and lead by a true nationalist, whose interest is to promote peaceful co-existent of all different ethnicities and believes, the country will be peaceful forever.

In closing this author believes that to bring a lasting peace to South Sudan this peace process needs to be forward to the African Union as the second step. IGAD leaders have been playing around with it and got stuck already. They are dancing between the truth and favoritism to their colleague more than solving the war. The South Sudanese people worldwide want to see this war comes to an end soon. They also need to have a model in place that will guarantee their co-existing forever. Salva Kiir made Nuer and Dinka believe that they are enemies to each other’s. This is not true. It was not an intention of the Dinka of South Sudan to kill the Nuer. It was Salva Kiir who wants to remain in power, and was intimidated by the present of Nuer figures who could claim the same right as anybody in South Sudan to run for the president, should an opportunity presents itself.


The author holds a PhD in psychology. He is a South Sudanese living in the United States. He can be reached at kuekjohn@yahoo.com
Source -  SSNA (South Sudan News Agency) 

Please note that posts on GUDAYACHN BLOG may not reflect the view of the blogger.
ጉዳያችን ጡመራ ላይ የሚወጡት ፅሁፎች (ምንጫቸው ከጉዳያችን ጡመራ ውጭ መሆኑ ካልተገለፀ በቀር) የጦማሪውን ዕይታ ላያንፀባርቁ ይችላሉ።

Wednesday, October 22, 2014

ሰበር ዜና- አቡነ ማትያስ በጥቅምት/2007 ዓም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉአባኤ መክፈቻ ንግግራቸውም ከቤተ ክርስቲያን ዋና ዋና ችግሮች ላይ ከማተኮር ይልቅ የቤተ ክርስቲያኒቱን ልጆች በመግፋት ምድራዊውን መንግስትን ማስደሰት ቀጥለዋል።(ጉዳያችን)




የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥቅምት 11/2007 ዓም ከቀትር በኃላ  በምህላ እና በፀሎት መጀመሩ ይታወቃል።በማግስቱ ጥቅምት 12/2007 ዓም ፓትራርኩ አቡነ ማትያስ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ምእመናንን እና የቤተክርስቲያን አባቶችን ያሳዘኑ ንግግሮችን ተናግረዋል።ፓትራርኩ በንግግራቸው አብዛኛውን ክፍል የያዘው የገዢውን ምድራዊ መንግስት ያስደስታል፣ በአጠገባቸው በሙስና እና የቤተ ክርስቲያንን አይን የወጉ ሙሰኞች፣እበላ ባይ አድር ባዮች እና ''የጨለማው ቡድን'' ተብለው የሚታወቁትን ታጣቂ ካድሬዎች ያስደስትልኛል ያሉትን ቃላት እየመረጡ ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ጣታቸውን መቀሰር መርጠዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ዘርፈ ብዙ የአስተዳደር ችግሮች እና የእምነቷ ቀሳጮች ከመቼውም ጊዜ በላይ በከበቧት በእዚህ ፈታኝ ወቅት ማኅበረ ቅዱሳንን የሚያህል ለቤተ ክርስቲያን እና ለአብቶች የሚታዘዙ፣በእውቀታቸው፣በጉልበታቸው እና በገንዘባቸው ቤተ ክርስቲያንን በነፃ የሚያገለግሉ አባላት ማኅበርን ማፍረስ እንደትልቅ የቅዱስ ሲኖዶሱ ቀዳሚ ተግባር አድርገው ማቅረባቸው በቀጥታ የምያስፈፅሙት አካል ተልኮ እንዳላቸው አመላካች ነው የሚሉ ወገኖች  ተበራክተዋል።

ፓትራርኩ በዛሬው ንግግራቸው ''እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመበት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ'' ሐዋርያት ሥራ 20፣28  የሚለው ቃል እና ''ለሁሉም እኩል አባት እሆናለሁ'' ያሉትን እረስተው ለቤተክርስቲያን ልጆች ከለላ መሆኑ ቀርቶ ''ሽብርተኞች'' እያሉ የምነቅፉትን አይዟችሁ ባይ ብቻ ሳይሆን በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መክፈቻ ላይ  ማኅበረ ቅዱሳንን ''በቤተ ክርስቲያን የማይታወቅ ሀብት የሚሰበስብ እና ቤተክርስቲያን ወደ ሁለት የመክፈል አዝማምያ ያለው እና የቤተ ክርስቲያንን መመርያ ለመቀበል ፈቃደኛ ያልሆነ'' የሚል ስም ለጥፈውበታል።

እርሳቸው ይህንን ይበሉ እንጂ የማኅበሩ ሥራ አመራር እና ሥራ አስፈፃሚ አባላት ማኅበረ ቅዱሳን  በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ስር ያለ ማኅበር እንደመሆኑ እና መተዳደርያ ደንቡንም እራሱ ያፀደቀው ሳይሆን ከቅዱስ ሲኖዶስ ተረቆ፣ተሰፍሮ፣ ተቆጥሮ እና በራሱ በቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ ፀድቆ እና ተፈርሞ በተሰጠው ሕግ መሰረት የሚተዳደር መሆኑ ይታወቃል።

ይህም በመሆኑ የማኅበሩ ሥራ አመራር እና ሥራ አስፈፃሚ በተደጋጋሚ ከርሳቸው የስራ መመርያ ለመቀበልም ሆነ በሚያነሷቸው ጥያቄዎች ላይ ለመመካከር በፅሁፍም ሆነ በቃል በተደጋጋሚ እንዲያናግሯቸው ጠይቀው  አንድ ጊዜም ሳያናግሯቸው በአደባባይ ለዋልጌ አባት ነን ባይ ካድሬዎች ተቀምጠው ሲያሰድቡ እና እርሳቸውም ሲወቅሱ መሰንበታቸው ከፍተኛ ትዝብት ላይ ብቻ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያኒቱን ክብር በእዚህ ደረጃ ማውረዳቸው ብዙ ምዕመናንን አሳዝኗል ።በወጣቶች ዘንድ ደግሞ ከፍተኛ ቁጣ ቀስቅሷል።

አንድ  የቤተ ክርስቲያኒቱ  አገልጋይ ፓትራርኩ  ጥቅምት ወር መጀመርያ ላይ ለቤተ ክህነቱ ሥራ አስኪያጅ ሳይነግሩ በጠሩት ህገ ወጥ ስብሰባ ላይ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ደፋ ቀና የሚሉ፣በእዚህም አገልግሎት አገልጋዮቹ በጎርፍ አደጋ፣በመኪና አደጋ እና ለብዙ ጤና መታወክ የተዳረጉ እውነተኛ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ያሉበትን ማኅበረ ቅዱሳንን ''አልሸባብ፣አሸባሪ፣የቤተ ክርስቲያን ንብረት የሰበሰቡ፣ ወዘተ'' እያሉ የግፍ ምላሳቸውን ያስረዘሙባትን ግፉአን  ላይ አስተያየቱን ሲሰጥ ''በሕይወቴ በእዚህን አይነት ደረጃ ሐሰት ነግሳ ስትፎክር፣ ሰው የሚባል ፍጡርም ሕዝብ የሚያውቀውን እውነት በአደባባይ በድፍረት በሐሰት ምላሱ ሲለበልባት አልተመለከትኩም ወደፊትም የምመለከት አይመስለኝም '' ሲል ተሰምቷል።
 ሐሰት ማረፍያ ምላስ አገኘች።ሀገር ያወቃቸው ቀማኞች ''አባታችን'' በሚል የማቆላመጫ ቃል ፓትራርኩ ፊት ንፁሃንን ባልሰሩት ወንጀል ከሰሷቸው።ፓትራርኩም  ቅንድባቸውን አንድ ጊዜ ወደላይ ሌላ ጊዜ ወደታች እያደረጉ አዳነቁላቸው።በእዚህ ብቻ አላበቁም ጠርተው በአንድነት መመካከር፣ቤታቸንን እንዴት እናስተካክል ብለው መምከር ቅሬታቸውንም በግልፅ ጠርተው መግለፅ ያልፈለጉት ፓትራሪክ ከውስጥ ያሉትን እየገፉ ስለውጭው የተጨነቁ መስለው መናገራቸው ሚዛን አልደፋ ያለበት ምዕመን በቀጣዩ ጊዜ ስለሚወስደው የእራሱ እርምጃ የማሰላሰያ ጊዜው መሆኑን ያመነበት ይመስላል።

ከውስጥ ያሉትን የቤተክርስቲያን ነገር ያንገበገባቸውን ''አተላ እና ዘኬ ጋር የሚውሉ'' ተብለው ሲሰደቡ ''ተዉ እንዲህ አይባልም'' ብለው ከመምከር ይልቅ እንደ ተራ የመንደር ሙግተኛ ስድቡን ለማድነቃቸው ከፊታቸው ላይ መደበቅ አልቻሉም።''እድምያችንን' ሸውደን' እንድኖራለን'' የሚሉ 'የዶሮ ማነቅያ' ሰፈር ቃላትን እንጂ የቤተ ክህነቱ ሽታ የሌላቸው ቀሚስ ለባሾች የተከበረውን የቅዱሳን መታሰብያ ''ዝክርን'' ''ዘኬ'' በሚል ፀያፍ ቃል ሲጠቀሙም አሁንም ፓትርያሪኩ ቅር አላላቸውም።

ይህንን የሰሙ ሌላ የጉባኤው ተሳታፊ አባት ከግፉአኑ ጉባኤ ከወጡ በኃላ እንባ ባቀረረ ፊታቸው ''በዓለማዊው ትምህርት መግፋታቸው፣ሱፍ መልበሳቸው የማኅበሩን አባላት ከዝክር ማራቅ ነበረበት? ሱፋቸውን አቧራ እንዳይነካው ''እፍ እፍ'' እያሉ እንዲኖሩ ነበር ምኞታቸው? አልጋቸውን ትተው የማኅበረ ቅዱሳን ቢሮ መሬቱ ላይ ሰሌን አንጥፈው ተኝተው መስራታቸው ነው አሸባሪ ያስባላቸው?'' ሲሉ ጠይቀዋል።
ለማጠቃለል አቡነ ማትያስ ከሰማያዊው አምላክ ይልቅ ለምድራውያኑ ገዢዎች ማድላታቸው የአደባባይ ምስጢር ሆኗል።በአንድ ወቅት ''ይህ ማኅበር የሚሰራውን አውቃለሁ ወጣቶች ናችሁ በርቱ'' ባሉበት አንደበት መንበረ ፕትርክናውን ሲይዙ እነ አባይ ፀሐዬ እና መሰሎቻቸው ለሚሏቸው የሚታዘዙ፣ ሐሰት ሲነገር የማያርሙ አባት መሆናቸውን አስመስክረዋል።በውስጥ ያሉትን ልጆቻቸውን እንዳይወጡ መጠበቅ ሲገባቸው ለመግፋት እና ለማስገፋት አለ የተባለውን የምድራችንን ያሰቅልልኛል ያሉትን  ክስ አንጠፍጥፈው ያርከፈከፉትን በማድነቅ  በልጆቻቸው ደረት ላይ በጭካኔ ሰክተውባቸዋል፣ አሰክተውባቸዋል።

እግዚአብሔር እረኞች ጳጳሳትን፣ካህናትን እና አገልጋዮችን  ከውጭ ያሉትን በጎች በፍቅር እና በትምህርት  ወደ ቤቴ አላመጣችሁም ብሎ የሚወቅስ እና የሚቀጣ ከሆነ ከውስጥ ያሉትን በጎች በሐሰት ፍርድ  ወደውጭ እንዲወጡ (አይወጡም እንጂ ) የሚገፉትንማ በምን አይነት ፍርድ ይቀጣቸው? ለነገሩ ስንዝር ያክል ከቤተ ክርስቲያን የምያፈገፍግ የለም።ይልቁን ክንድ ያህል የበለጠ እንቀርባለን።የበለጠ የቤተ ክርስቲያንን ንብረት መተዳደርያቸው ያደረጉትን በግድም በውድም ይነቀሳሉ።በፊውዳል አስተሳሰብ  ውስጥ እየዳከሩ ፈላጭ ቆራጭ ሆኖ መኖርን እና ለምድራውያን ገዢዎች እየሰገዱ መኖርን ቤተ ክርስቲያን አላስተማረችንም።
 ''እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመበት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ'' ሐዋርያት ሥራ 20፣28
ጉዳያችን
ጥቅምት 13/2007 ዓም (ኦክቶበር 23/2014)

Tuesday, October 21, 2014

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በቤተ ክህነት ውስጥ ሆነው የሚያምሱት እና ማኅበረ ቅዱሳን ላይ እጃቸውን የሚቀስሩቱ ለሃይማኖቱ ክብር ባለው በትግራይ ሕዝብ ታንቅረው የተተፉ ለመሆናቸው እማኝ የሆንኩባቸው አጋጣሚዎች (ከማስታወሻ ደብተሬ)


የዛሬ ስድስት ዓመት ገደማ ይመስለኛል በቀድሞ መስርያ ቤቴ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አብሮኝ ይሰራ የነበረ እና የመንፈሳዊ ወንድሜ የሆነ ወዳጄ ሰርጉ መቀሌ ላይ  ነበር።ሙሽሪት አባት እና እናቷ የመቀሌ ከተማ ነዋሪ ነበሩ።መቀሌን ከእዚህ በፊት ወደ አክሱም ፅዮን መንፈሳዊ ጉዞ  ስንሄድ መቀሌ ጊዮርጊስ ስናርፍ በማደር እንጂ በውል አላውቃትም ነበር።ከተማዋን ለእዚህ ወዳጀ ሰርግ በሄድኩበት ወቅት በቆየሁባቸው ሁለት ቀናት ውስጥ ግን  የአፄ ዮሐንስ ቤተ መንግስትን እና በመቀሌ የማኅበረ ቅዱሳን ማዕከል ፅህፈት ቤት ለማየት ዕድሉ ገጥሞች ነበር።መቀሌ የሚገኘው የማኅበረ ቅዱሳን ፅህፈት ቤት የነበሩት እና መቀሌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት ያሉ  ወንድሞች እና እህቶች ትሕትና እስከመቼም አይረሳኝም።

በተለይ ወደ አክሱም ፅዮን በሁለት የተለያዩ ጊዜያት ከመንፈሳውያን ሰራተኞች ጋር ጉዞ በሄድንበት ወቅት አዳራችን መቀሌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ ነበር። የመቀሌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ትምሕርት ቤት አባላት  ትህትና ከአዕምሮዬ አይጠፋም። በመንፈሳዊ ጉዞው የነበሩትን ከአንድ መቶ ሃያ የማያንሱትን መንገደኞች በሙሉ እግር አጥበው፣ለእያንዳንዳችን ነጠላ ጫማ እና ፍራሽ  ከቤታቸው ሰብስበው አምጥተው፣እራት አብልተው እና ለሚቀጥለው ቀን ጉዞ ስንቅ የሚሆነን እኛ ተኝተን እነርሱ ሌሊቱን ሲሰሩ አድረው የሚሸኙን እነኝሁ የመቀሌ መንፈሳውያን ወጣቶች ነበሩ።

ወደሰርጉ አጋጣሚ ልመልሳችሁ 
እድምተኞች በታደሙበት ሆቴል፣በሰርጉ ምሽት እራት ላይ ከአዲስ አበባ ድረስ አብረውን የሄዱት አባት ለሃያ ደቂቃዎች ያህል ትምህርት አስተምረው ሲጨርሱ ከታዳሚው አንድ ሰው ተነሱ እና በትግሪኛ መናገር ጀመሩ።እጅግ መቆጣታቸው በንግግራቸው መሃል እንባ እና ሳግ ሲተናነቃቸው ያስታውቃል።በመሃል ትግርኛውን ገታ አድርገው በሚጣፍጥ አማርኛ ቀጠሉ ከንግግራቸው መሃከል የማስታውሰው  ''ወንድሞቻችን እንደገባኝ  ከአዲስ አበባ ነው የመጣችሁት። የመቀሌ ህዝብም ተቸግሯል።አሰሙልን! ንገሩልን! ቤተ ክህነት ያሉት ሰዎች ምን እየሰሩ ነው? እየሾሙ የሚልኩት ላይ ጥያቄ አለን።ቅሬታ አለን ስንል ስም ይለጥፉብናል ።መናፍቅ እና ተሃድሶ ከቤተ ክህነት ይውጣልን!አያምታቱን! ንገሩልን! ሃይማኖታችን እየተዋረደች ነው'' እጃቸውን እያወራጩ ነበር የሚናገሩት። የሰርጉ ታዳሚ በሃዘን ከንፈሩን መጠጠ።ሙሽራው እና አብረውን የሄዱት አባት ከአዲስ አበባ መምጣታቸው ብቻ ቤተ ክህነት የሚሰማቸው መስሏቸዋል።እኛ ከአዲስ አበባ መምጣታችን ብቻ ለቤተ ክህነት የቀረብን አድርገውናል።ቆይቶ የሙሽሪት ወላጅ እንዳስረዱን የተናገሩት አዛውንት የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሰብሳቢ በከተማዋም ውስጥ ከቀድሞ መንግስት ጀምሮ የታወቁ እና የተከበሩ አዛውንት መሆናቸው ነገሩን።

ተመሳሳይ ጉዳይ አክሱም ፅዮን አጋጥሞኛል። አክሱም ፅዮን ለመጀመርያ ጊዜ መንፈሳዊ ጉዞ ስሄድ ወደ ስልሳ የምንጠጋ  መንገደኞች በአንድ አውቶብስ ተሳፍረን ነበር  ከአዲስ አበባ የተነሳነው። አክሱም ፅዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያንን፣የአክሱም ሃውልት፣የቅዱስ ያሬድ ቃለ ሙራድ? የተቀበለበት ቦታ እና የንግሥት ሳባ ቤተ መንግስትን ያየሁበት አጋጣሚ ነበር።በአንድ መኪና የመጣው መንገደኛ በሙሉ የሚያድረው ከቤተክርስቲያኑ አጠገብ ከሚገኝ የእንግዶች ማረፍያ ጠበብ ያለ አዳራሽ ነበር።

በምሳ፣በእራት እና በቁርስ ሰዓት ለመንገደኞች ውሃ ማምጣት ኃላፊነት ከተሰጣቸው ውስጥ ነበርኩ። በመሆኑም በቀን ጊዜ ወደ አስር ደቂቃ የሚያስኬድ ሬስቱራንት መሄድ እና ውሃውን በባሊ ማምጣት ነበረብን። በእዚህ መሃል ነበር  ውሃ በነፃ እንድንወስድ የፈቀደልን የሬስቱራንት ባለቤት ጋር መግባባት የቻልነው።ግለሰቡ አዲስ አበባ የኖረ የአክሱም ሰው ነበር።በንግግራችን መሃል ታድያ ባብዛኛው የምናተኩረው በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ዙርያ ነበር።ግለሰቡ ከንግግሮቹ ሁሉ ጎልቶ የሚወጣው  የቤተ ክህነቱ  በሙሰኞች እና ከሃይማኖታዊ ምግባር እና ቀኖና በወጡ አገልጋዮች የበላይነት መመራቱ እንደሚያሳዝነው ነበር።ሁሉን ማውራቱ እዚህ ላይ ባይጠቅምም ከነገረን ውስጥ የሚገረመው ግን የአክሱም ከተማ ምዕመናን በቅርሳቸው ጥበቃ ላይ የሚፈሩት ከባዕዳን እኩል ቤተ ክህነቱ ውስጥ ያሉ እንደ እርሱ አጠራር ''ዘራፊ እና ቀማኛዎችን'' መሆኑን ሲነግረን ሁላችንም በድንጋጤ የተያየንበት ወቅት ነበር።

እነኝህ ሁለት አጋጣሚዎች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በቤተ ክህነት ውስጥ ሆነው የሚያምሱት እና ማኅበረ ቅዱሳን ላይ እጃቸውን የሚቀስሩቱ ለሃይማኖቱ ክብር ባለው  በትግራይ ሕዝብ ታንቅረው የተተፉ ለመሆናቸው እማኝ የሆንኩባቸው አጋጣሚዎች ሆነው አልፈዋል።ዛሬ የማስታወሻ ደብተሬን እንዳነሳ ያደረገኝ ሰሞኑን የተያዘው አዲሱ የቤተ ክህነት አማሳኞች እና የማኅበረ ቅዱሳንን አገልግሎት ቦታ የለየ አስመስሎ የሚያቀርብ ፅሁፍ በማየቴ ነው።በዛሬው እለት በወጣው ፅሁፍ ላይ ''የአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ገዳምን ስም ማኅበረ ቅዱሳን ለማንሳት ይፀየፋል'' የሚል ሙሉ በሙሉ በውሸት የተለወሱ አረፍተ ነገሮች ይነበባሉ።የሚገርመው ነገር ገዳሙ ተረስቶ እና  የሚያስበው አጥቶ በብዙ ድካም እና መንገላታት ከቦታው ደርሶ ለገዳሙ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት ቀርፆ ለገዳሙ ያስረከበ  ማኅበረ ቅዱሳን መሆኑን ፀሐፌው አለማወቃቸው ምን ያህል በመረጃ ዘመን ከመረጃ የራቁ መሆናቸውን አመላክቶኛል።አልያም ሃይማኖትን ለማመስ ከአማሾች ጋር የተባበሩም  መሰሉኝ። ለሁሉም ማኅበረ ቅዱሳን በምን አይነት ፈተና ወደ አባ ሰላማ ገዳም  ተጉዞ ፕሮጀክት እንደቀረፀ እና እንደተገበረ ይህንን  ማያይዣ በመክፈት  ፊልሙን ይመልከቱ እና ይታዘቡ።

ጉዳያችን
ጥቅምት 11/2007 ዓም (ኦክቶበር 21/2014)

Monday, October 20, 2014

''የቀረቡት ንግግሮች መሠረታቸው በውል ባይታወቅም ከስሜት ግን የጸዱ አይደሉም ስሜት ደግሞ አይደለም ለፓትርያርክ ለተራ ክርስቲያንም የተመቸ ወይም የሚጠበቅ አይደለም'' በዶ/ር ተክሉ አባተ


ከእዚህ በታች ያለው ፅሁፍ ከዶ/ር ተክሉ አባተ ጡመራ የተወሰደ ነው።

ፓትርያርክ ብፁዕ አባ ማትያስና ተግዳሮቶቻቸው

ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ አቡነ ማትያስከተሾሙ እነሆ ሁለት ዓመት ሊሞላቸው አራት ወራት ገደማ ይቀራቸዋል:: ቅድመና ድኅረሹመታቸውን ተከትሎ የውይይትና የክርክር መድረኮች በኢትዮጵያም በውጭውም ዓለምተከፍተው ነበር:: የአምስተኛው ፓትርያርክ የብፁዕ አቡነ ጳውሎስ ድንገተኛ ሞት አንዳች ለውጥለቤተ ክርስቲያኗ ያመጣ ይሆናል ብለው የገመቱና የተመኙ ብዙዎች ነበሩ:: ሁለቱ ሲኖዶሶችእርቅ ሊያወርዱ እንደሚችሉ ተተነተነ:: ዳሩ ግን የእርቁ ሂደት ሳያልቅ ምርጫ ተደረገና ብፁዕአቡነ ማትያስ በወሳኝ ድምጽ እንዳሸነፉ ተነገረ:: መንግስት ከነበሩበት አስመጥቶ እንዳሾማቸው::እርሳቸውም ነጭ ልብስ እንደማይለብሱና የቅንጦት ኑሮ እንደሚጸየፉ: ቤተ ክርስቲያን ያጣችውንክብርና ተሰሚነት እንደሚመልሱ ተናገሩ:: «ይህን ማን አየው» በሚል ተስፋ አዲሱ ፓትርያርክየለውጥ ሐዋርያ ሊሆኑ እንደሚችሉ ቅር እያላቸውም ቢሆን የገመቱ ነበሩ::


የጎላ ነገር ሳይሰራ እነሆ ሁለተኛ በዓለ ሲመታቸውን ሊያከብሩ ነው:: ከቀድሞው ፓትርያርክ ጋርአንጻራዊ በሆነ መልኩ ሲወዳደሩ አቡነ ማትያስ ብዙም የመድረክ ሰው አይመስሉም:: በተለያዩጉባዔያትና መገኛ ብዙሃንም የአቡነ ጳውሎስን ያህል ጎልተው አልወጡም:: ከቅርብ ጊዜ ወዲህግን ድምጻቸውናያሉበትሁኔታእየተሰማ የመጣ ይመስላል:: በሆነ ወቅት ላይ በመንግስትካድሬዎች ለሰዓታት እንደታሰሩና እንግልትምእንደደረሰባቸውሲነገርነበር (ይህ እውነት መሆኑንያጣራ አካል ግን የለም):: የእስራታቸው ዜና ከተሰማ ጀምሮ ግን በንግግራቸው ጠንከር ያሉናየፖለቲካ ቃና ያላቸው አቋሞችን ማስተላለፍ የጀመሩ ይመስላል:: በተለይ ከመስከረም ወር2007 የመጨረሻ ሳምንት ጀምሮ ጠንከር ያሉ ጉዳዮችን ጠንከር ባሉ አነጋገሮች ማቅረብጀምረዋል::  

የብፁዕነታቸውን የአመራር ክህሎቶችና ያሉበትን ሁኔታ ለመገምገም ቅርብ ጊዜ በተደረጉናበመደረግ ላይ ባሉ የቤተ ክርስቲያኗ ጉባዔያት ላይ ፓትርያርኩ ያቀረቧቸው ንግግሮች ዋናየመረጃ ምንጭ ናቸው:: አንደኛው መስከረም ፳፯ ቀን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አዳራሽ፣መስከረም ፳፱ ቀን ደግሞ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ  የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራትአስተዳዳሪዎችና ጸሃፊዎችየታደሙበትጉባዔነው::የዚህ ጉባዔ መሪ ቃል ‹‹በአዲስ አበባሀገረ ስብከት የመልካም አስተዳደር አስተሳሰብን ማበልጸግ›› የሚል ሲሆነ ብፁዕነታቸውየመክፈቻ ንግግር በጽሁፍ አቅርበዋል:: ይህ ጽሁፍ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃመምሪያ ድረ ገጽ http://eotcssd.org/the-news/398--q q-.html  
ላይ ይገኛል:: ሁለተኛው የመረጃ ምንጭ ደግሞ ጥቅምት  ቀን፳፻፯ .በጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብሰባ አዳራሽ በተጀመረው ፴፫ኛው የመንበረ ፓትርያርክአጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ላይ ፓትርያርኩ የተናገሩት ነው::ይህም በማደራጃ መምሪያው ድረ ገጽhttp://eotcssd.org/the-news/39 sebeka2007.html
ላይይገኛል::ከነዚህንግግሮችቢያንስ ቀጥለው ያሉትን ጉዳዮችመረዳት ይቻላል::      
    

ከቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ አስተዳደር አካላት ጋር አለመናበብ

የአምስተኛው ፓትርያርክ አንዱና ትልቁ ችግራቸው በየደረጃው ካሉ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደር አካላት ጋር ተናቦ: ተቻችሎና ተስማምቶ አለመስራት ነበር:: የስብሰባ አጀንዳ ከመምረጥ ጀምሮ ውሳኔዎችን እስከማሳለፍና እስከማስፈጸም ባሉ ሂደቶች ቅዱስ ሲኖዶስን ይገዳደሩት ነበር:: በሚያሳድሩት ቀጥታዊና ሥልታዊ ጫና ሲኖዶሱ ጥርስ የሌለው አንበሳ  መስሎ እስከመታየት ደርሶ ነበር:: እንደምንም ተብሎ  የተላለፉ ውሳኔዎች ሳይፈጸሙ የራሳቸው ህይወት ተፈጸመ::

ስድስተኛውም ፓትርያርክ ገና ከጠዋቱ «ብቸኛ ሆኛለሁ» ማለት ጀምረዋል:: እርሳቸው ብቻቸውን እንደሆኑና ሃሳባቸውን የሚሰማ የበላይ አካል እንደሌለ በመረዳታቸው በአጥቢያ ደረጃ ካሉ አለቃዎች ጋር «ዝቅ» ብለው መወያየት እንዳስገደዳቸው በመስከረሙ ጉባዔ አሳውቀዋል:: በንግግራቸውም የደብርና የገዳማት አለቆች ከጎናቸው እንዲቆሙ ተማጽነዋል:: በአጥቢያ ደረጃ ካሉ አመራሮች ጋር መወያየቱ በራሱ ችግር የለውም:: ችግሩ የበላዩ አመራሮች ወይም ቅዱስ ሲኖዶስ በሥራቸው እንዳልተባበራቸው በስሞታ መልክ ለበታች አካላት መቅረቡ ነው:: ይህ ጉዳይ በተለያዩ እርከኖች ያሉ የቤተ ክርስቲያኗ አካላት ላይ አላስፈላጊ ጥርጣሬ ከመፍጥሩም በላይ ሥራን ይበድላል::ይህንንም በተመለከተ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አሥኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የሰጡት መልስ ተጠቃሽ ነው:: ፓትርያርኩ የጠሩት ስብሰባ ግልጽነት የጎደለውና ወቅታዊ ጉዳዮችንም የተመለከተ እንዳልሆነ ብፁዕነታቸው ተናግረዋል:: እንግዲህ ከጠቅላይ ቤተ ክህነትና ከቅዱስ ሲኖዶስ እውቅናና ይሁንታ ውጭ የሚደረግ ስብሰባና የሚተላለፍ ውሳኔ እንዴት ውጤት ይኖረዋል?  በአምስተኛው ፓትርያርክ ዘመን ቅዱስ ሲኖዶስ ያጣውን የመወሰንና የማስፈጸም አቅም ከማራዘም ውጭ ሌላ ምን ፋይዳ አለው? ይህ ተናቦ አለመስራት የቤተ ክርስቲያኗን ሰላምና አንድነት ይፈታተናል:: ቤተ ክርስቲያን የምትፈልገው የአንድ ሰው ወይም አካል ገናናነትን ሳይሆን ተስማምቶና ተቻችሎ ከሁሉም አካላት ጋር መስራትን ነውና ብፁዕነታቸው ከሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር በክብር እንዲሰሩ ክርስትናው ያስገድዳል::  

ወሳኝ የሆኑትን ጉዳዮች ትቶ በጥቃቅን ነገሮች ላይ ማተኮር

ፓትርያርኩ መስከረም ፳፯ ቀን ጉባዔውን ሲከፍቱ ቀጥለው የተዘረዘሩትን አንገብጋቢ የሆኑ የቤተ ክርስቲያኗን ችግሮችን ዘርዝረዋል
v  የምእመናን በቁጥር መቀነስ
v  የቤተ ክርስቲያን ሃብት መቀነስና አብያተ ክርስቲያናት መዘጋት
v  የቤተ ክርስቲያን እሴቶች ለኢትዮጵያ የሚያበረክቱት ጠቀሜታ መቀነስ
v  መዋቅር ዘርግተው ለራሳቸው ጥቅም የሚሯሯጡ ሃላፊዎች መበራከት
v  ከቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች እጅግ የላቀ መንፈሳዊ ተግባር መጥፋት
v  በቤተ ክርስቲያን ስም የሚደራጁ ማኅበራትና ግለሰቦች መዋቅርን አለመከተል
v  ማኅበራትና ግለሰቦች ንብረት ማፍራት ላይ መጠመድና አባቶችን መከፋፈል  

በእውነቱ ከሆነ እነዚህ ጉዳዮች እጅግ አሳሳቢዎች ናቸው.: ቶሎ መፍትሄ ካልተሰጣቸው ቤተ ክርስቲያን ከእግዚአብሔር የተጣለባትን አደራ በተገቢው መጠን ልትወጣ አትችልም:: ዳሩ ግን ከጊዜና ከአቅም ውሱንነት የተነሳ እንዲሁም ከመረጃና ማስረጃ እጥረት የተነሳ ሁሉም ችግሮች በአንድ ጊዜ እኩል ትኩረት አያገኙም:: ለአጀንዳዎች ቅደም ተከተል ሰጥቶ መወያየት የሚያስፈልገውም ለዚህ ነው:: አስተዋይና አዋቂ መሪ የሚያስፈልገውም ለዚህ ነው:: ጥሩ መሪ ሁሉንም ችግሮች የሚፈታ ማለት ሳይሆን ወሳኝና አንገብጋቢ የሆኑትን ለይቶ በማውጣት መፍትሄ የሚሰጥ ማለት ነው:: ፓትርያርኩ ችግሮችን ቢዘረዝሩም ካለው ጊዜ አንጻር ትኩረት ሊሰጧቸው የሚገቡ ጉዳዮች መለየት ነበረባቸው:: የምእመናን ቁጥር መቀነስና የአብያተ ክርስቲያናት መዘጋት እንዲሁም የሙስና መስፋፋት ከማኅበራት ጥቃቅን ችግሮች ጋር እንዴት እኩል ይታያል?

የሚገርመው ግን ረጅም ጊዜ የወሰዱ ጠንካራ ንግግሮች የተካሄዱት ከማኅበራትም በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ብቻ ነበር:: የተወሰኑ የደብር አለቆች (አብዛኛው ችግር ከነሱ ሥራ ጋር እንደሚያያዝ ስላወቁ) የተወረወረውን ጦር አቅጣጫ ቀየሩለት:: ፓትርያርኩም ጉባዔው በማስተዋልና በመንፈሳዊነት መወያየት እንደሚያስፈልግ ከማሳሰብ ይልቅ ለጀሮ በሚሰቀጥጡ ስድብ ነክ ንግግሮች የተደሰቱ መስለው ታይተዋል:: መሪ የሌለው ስብሰባ ሆኖ የተነሳበትን «አስተዳደራዊ አስተሳሰብ ማበልጸግ» መሪ ቃል ሳይመራበት ቀረ:: የአቋም መግለጫ የወጣው ቤተ ክርስቲያኒቷን እያንገላታት ስላለው ስለሙስናና አድሎአዊ አሠራር ወይም ስለምእመናን መባዘንና አብያተ ክርስቲያናት መዘጋት ሳይሆን ስለአንድ ማኅበር ሃብታም መሆን ነው:: በመሆኑም የእለቱ ጉባዔ መነሻውና መድረሻው ያልተጣጣሙ ሆነው ቀርቷል:: ይህም ከአመራር ብቃት ማነስ ወይም ከልዩ ዓላማ መኖር ጋር ሊያያዝ ይችላል:: ሌሎች የቤተ ክርስቲያኒቱ ጉባዔያት የሚጠሩትና የሚመሩት እንዲህ ከሆነ እጅግ አሳዛኝና ፈታኝም ነው:: ብፁዕነታቸው ትልቁን ጉዳይ ከትንሹ ለይተው ካላወያዩና ከሚመለካተቸው አካላት ጋር አብረው ካልሰሩ የራሳቸውን ወይም የሌሎችን አካላት ፍላጎት ከመከተል የሚያግዳቸው አይኖርም:: 

ስሜትን መሠረት ያደረጉ ስሜት ቀስቃሽ ንግግሮች

ንዴትን: ብስጭትን: ቅሬታን: ተስፋ መቁረጥን: ድካምን: ደስታን ወይም ስኬትን መነሻ  ያደረገ ንግግር ሁሉ ስሜታዊ ነው:: አይደለም በመንፈሳዊ ህይወት በዓለማዊ አሠራርም ስሜታዊነት ጥቅም የለውም:: ጥሩ መሪ ማለትም ስሜትን ተቆጣጥሮ ሠራተኞችን ወይም አገልጋዮችን በማስተባበር ዓላማን ማሳካት የሚችል ነው:: ቅዱስ ፓትርያርኩ በልምድ ማጣትም ሆነ በብሶት ወይም በሌላ ምክንያት ስሜትን ሊቀሰቅሱ የሚችሉ ንግግሮችን ከላይ በተጠቀሱት ታላላቅ ጉባዔያት ደጋግመው ተናግረዋል:: ለምሳሌ ያህል ቀጥለው የተዘረዘሩት የፓትርያርኩ ንግግሮች አብይ ናቸው
v  የሚሰማኝ ስላጣሁ ከበታች የቤተ ክርስቲያኒቱ አካላት ጋር መወያየት አስፈለገኝ ወደፊትም ዓመቱን ሙሉ አደርገዋለሁ
v  ማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ቅኝ ገዥ ነው የቤተ ክርስቲያንን ክብርና ሃብት ቀምቷል
v  ይህ ማኅበር በቁጥጥር ሥር እንዲውል አሳስባለሁ
v   እኔ ይኽን ጉዳይ ከራሴ አወርዳለኹ፤ የቤተ ክርስቲያናችን ገንዘቧ፣ ክብሯ ተወስዷል 
v  ቤተ ክርስቲያን ከቅኝ ተገዥነት ትውጣ፤ ካህናቱ ከመከራ ይውጡ
v  ይህችን ቤተ ክርስቲያን ለመጠበቅ፤ አንዷን ቅድስት፣ ኦርቶዶክሳዊትና ታሪካዊት ቤተክርስቲያን ልመራ እንጂ ኹለት ቤተ ክርስቲያን የለችም
v  እኔ ብቻዬን የምሠራው ነገር የለም፤ በዚኽ መግለጫ እንድትሠሩበት ነው የምነግራችኹ
v  በህግና በሥርዓት የማይመራ ማኅበር አሸባሪ የመሆን እድሉ ሰፊ ነው
v  አባ ማትያስ አላበደም፤ መልእክቴን እያስተላለፍኹ ነው ያለኹት፤ መልእክቴን በጸጋተቀበሉ ብዬ እማፀናችኋለኹ

እዚህ ላይ መነሳት የሚገባው ነገር ቢኖር ከዚህ በላይ ለተጠቀሱት ከባድ ንግግሮች የቀረበ መረጃም ሆነ ማስረጃ አለመኖሩ ነው:: እንዴትና በምን ሁኔታና ምክንያት ነው ጠቅላይ ቤተ ክህነትና ቅዱስ ሲኖዶስ የፓትርያርኩን ሃሳብ የማይጋሩ? ማኅበሩስ የቤተ ክርስቲያንን ክብርና ሃብት የቀማው እንዴት ነው? ካህናትንስ እንዴትና በምን ሥልጣን ነው በገዥነት የያዛቸው?ለነዚህና ለሌሎችም ትችቶች መረጃም ሆነ ማስረጃ አልቀረበባቸውም:: ይህ ሆኖ ሳለ እንዴት ተደርጎ ነው የፓትርያርኩ ፍላጎት የሚፈጸመው? «ሃሳቤን በጸጋ ተቀበሉት» ማለታቸውም መረጃና ማስረጃ እንደሌላቸው ጠቋሚ ነው:: አሳማኝ መረጃና ማስረጃ ካለ መለማመጥም ሆነ መለመን አያስፈልግም:: ሁሉም አካል ለእውነት ተገዥ መሆን አለበትና:: የቀረቡት ንግግሮች መሠረታቸው በውል ባይታወቅም ከስሜት ግን የጸዱ አይደሉም:: ስሜት ደግሞ አይደለም ለፓትርያርክ  ለተራ ክርስቲያንም የተመቸ ወይም የሚጠበቅ አይደለም:: ስሜት የጎበኛቸው ንግግሮች የሰውን እንጅ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ስለማያስቀድሙ በቤተ ክርስቲያኒቱ አገልጋዮች መካከል ክፍፍልን ያመጣሉ:: እልህን ከዚያም ቂምን ከዚያም መጠቃቃትን ይጋብዛሉና::   

ማጠቃለያ

ከንግግራቸው እንደምንረዳው ብፁዕ አቡነ ማትያስ ከሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር መልካም ግንኙነት እንደሌላቸውና በዚህም የተነሳ መንፈሳቸው እንደተረበሸ ነው:: በዚህ ሁኔታ ያለ መሪ አይደለም አዲስ ውጤት ሊያመጣ ያለውን ሊንድ ይችላል:: ብፁዕነታቸው በተመረጡበት ወቅት ቤተ ክርስቲያኒቷ ያጣችውን ክብርና አንድነት እንዲሁም ተሰሚነት ለመመለስ ከሁሉም አካላት ጋር እንደሚሰሩ ቃል ገብተው ነበር:: ይህ ግን እስካሁን ሲደረግ ወይም ለመደረግ ሲሞከር አልታየም:: ይባስ ብሎ ጉባዔያት መረጃና ማስረጃ የሌላቸው ተራ ሊባሉ የሚችሉ ክሶችን በማስተናገድ ላይ ይገኛሉ:: ከጥቂት ታዳሚዎች በስተቀር አብዛኞቹ ግራ ከመጋባትና ከመለያየት ባለፈ እየቀረቡ ባሉ ንግግሮች ተጠቃሚዎች ሊሆኑ አይችሉም:: ይህም የቤተ ክርስቲያኒቱን አገልግሎት በእጅጉ ይጎዳል::

ይቅር የማይሉና እርቅን የማያውቁ ባለሥልጣናት እንዴት ወንጌልን ሊሰብኩ ይችላሉ? ያጠፋ አካል ካለ ጥፋቱ በተጨባጭ ተነግሮት ይመከራል: አስተዳደራዊ ርምጃ ይወሰዳል እንጅ በመድረክ የስድብ ናዳ ይወረድበታል? የስም ማጥፋት ዘመቻ እንዴት ይካሄድበታልከላይ ያሉት አባቶች በእንደዚህ ያሉ ነገሮች የሚጠመዱ ከሆነ ምእመናን ማንን አርአያ ሊያደርጉ ይችላሉ??? ምናልባትም የምእመናን ቁጥር መቀነስ አንዱና ትልቁ ምክንያት ይህ የበላይ አካላት አላስፈላጊ ግብግብ ይመስለኛል:: ብፁዕነታቸው ለራሳቸውና ለንግግራቸው ይበልጥ በመጠንቀቅ የአባትነት ሚናቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል:: የይቅርታ: የእርቅ: የአንድነትና የሰላም አርአያ ሆነው መቀጠል ይጠበቅባቸዋል:: ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን የሚፈልጉት ፍጹም መንፈሳዊ አባት እንጅ በሥልጣኑና በኃይሉ የሚመካ መሪ አይደለም::        
ምንጭ -  Abyss

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።