ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, March 29, 2013

አቶ አንዱ አለም አራጌ እንዲህ ብሎ ነበር (ቪድዮ)

በ 2002 ዓም  በኢትዮጵያ የተደረገው ምርጫ ከ 1997 ዓም ወዲህ የተደረገ የመጀመርያው ምርጫ ይሁን እንጂ ውጤቱ 
በአለም አስደናቂ ውጤት የተሰማበት ማለትም ኢህአዲግ 99% ማሸነፉን ያወጀበት ነበር።በወቅቱ በ ኢትዮጵያ ቴሌቭዥን  መስኮት በእስር ላይ የሚገኘው አንዱ አለም አራጌ   እንዲህ ብሎ ነበር።



Monday, March 25, 2013

The Dragon Eating the Eagle’s Lunch in Africa?

by Alemayehu G. Mariam

From-ECADF-Ethiopian News and Opinions.

Flight of the Eagle and pursuit of the Dragon


In June 2011, during her visit to Zambia U.S. Secretary of State Hilary Clinton pulled the alarm bell on a creeping “new colonialism” inAfrica. While dismissing “China’s Model” of authoritarian state capitalism as a governance model for Africa, she took a swipe at China for its unprincipled opportunism in Africa. “In the long-run, medium-run, even short-run, no I don’t [think China is a good model of governance in Africa]…We saw that during colonial times, it is easy to come in, take out natural resources, pay off leaders and leave, …And when you leave, you don’t leave much behind for the people who are there. We don’t want to see a new colonialism in Africa…”

Friday, March 22, 2013

የአቶ አርከበ እቁባይ ሃሳቦች ለህወሓት ለምን አልተስማማውም ?



ዶ/ር አርከበ ዕቁባይ (Photo: William Davison/Bloomberg)


 መጋቢት ወር 2005 ዓም 

ህዳር ወር 1997 ዓም መነሻውን የመስቀል አደባባይ ያደረገው አምስተኛው የኢትዮጵያ የታላቁ እሩጫ ውድድር በጥሩ ሁኔታ ከተከናወኑት ውድድሮች የሚጠቀስ ነበር።በወቅቱ መንግስት የተወጠሩ የፖለቲካ ስሜቶችን በመጠኑም ቢሆን ማላላት የቻለባቸው ጊዜዎች ነበሩ።ከአምስት ወር በኃላ የሚደረገው አጠቃላይ ብሔራዊ ምርጫ፣ብዛት ያላቸው ጋዜጦች፣የውጭ መንግሥታት ስለምርጫው የሰጡት ተስፋ እና ተለያይተው ይሰሩ የነበሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ''ቅንጅት'' በሚል ህብረት ስር መደራጀት ወዘተ አመቱን ኢትዮጵያውያን በተስፋ እንዲጠብቁት ያደረገ ነበር።


በእዚህ መንፈስ ውስጥ ነበር የታላቁ እሩጫን ለመወዳደር ከተሰለፉት ሺዎች ጋር በመስቀል አደባባይ ሰውነታቸውን ከሚያሟሙቁት ጋር የተሰለፍኩት።በወቅቱ ታድያ አስገራሚው ትዕይንት ቀድሞ ኮ/ል መንግስቱ ከሚቆሙበት ሰገነት ላይ ይታይ ነበር። የወቅቱ የአዲስ አበባ ከንቲባ አቶ አርከበ እቁባይ እና አቶ መለስ ዜናዊ ውድድሩን ካስጀመረው ከአትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ጋር ቆመው የሚሮጠውን ሕዝብ በእጃቸው ሰላምታ ይሰጡ ነበር።ጨዋው እና በኢትዮጵያዊነት ስሜት የታሸው የአዲስ አበባ እና የአካባቢው ሕዝብ በተለይ አቶ አርከበ እጃቸውን ሲያነሱ በደስታ እና በእልልታ ያጨበጭብ ነበር።ይህም በልዩ ክብር እና መውደድ ይደረግ የነበረ የክብር ሰላምታ ነበር።

ለአቶ አርከበ የአዲስ አበባ ሕዝብ ለምን ክብር ሰጠ?

የአለም ከንትባዎችን ሃሳቦች በሚገልፀው ድህረ ገፅ (worldmayor.com) ላይ አቶ አርከበ ስለ እራሳቸው በገለፁበት ፅሁፍ ላይ እንድሚነበብው ከእንግሊዝ በቢዝነስ አድምንስትሬሽን የማስተርስ ዲግሪ እና ከኔዘርላንድ በአለምአቀፍ ግንኙነት ሌላ የማስተርስ ዲግሪ እንዳላቸው ይገልፃሉ።ከትምህርት ዝግጅታቸው በላይ አቶ አርከበ ለሕዝብ የተዋወቁበት ትልቁ አጋጣሚ ግን የ አዲስ አበባ ከንቲባ በነበሩበት ጊዜ ነው።አቶ አርከበ በአዲስ አበባ ከንቲባነታቸው ወቅት በሁለት ትላልቅ ሃሳቦች ውስጥ የተወጠሩበት ነበር። የመጀመርያው ቀድመው በኢህአዲግ ውስጥ ያውቁት የነበረው አካባቢያዊ ስሜት ሙሉ በሙሉ አዲስ አበባ ላይ የማይሰራ መሆኑን በመረዳት በፍፁም ፍቅር ለውጥ ለማምጣት መስራት የሚለው ሲሆን ሁለተኛው በአቶ መለስ እና በሌሎች የህወሓት አባላት ''ቀስ በል ብዙ አትሩጥ የፓርቲአችን ፖሊሲ እያየህ'' የሚለው አስተሳሰብ ነበር። በተለይ አቶ መለስ የአቶ አርከበን በሕዝብ መወደድ በታላቁ እሩጫ ጊዜም ሆነ ከእዛ በኃላ በሕዝቡ ልብ ውስጥ እየገቡ መምጣታቸው ቅር እንዳሰኛችው የታወቀው '' የአዲስ አበባ ልማት ቀለም ከመቀባት ያለፈ አደለም'' ያሉት ንግግር ሕዝቡን ካስደመመ በኃላ ነበር።

አቶ መለስ ይህንን ይበሉ እንጂ አቶ አርከበ ለአዲስ አበባ ሁነኛ ለውጥ ያመጡ ግለሰብ ሆነው ይሰሙኛል።እርግጥ ነው በ1997ቱ አገራዊ ምርጫ ኢህአዲግ በአዲስ አበባ እራሱም ያመነበት መቶ በመቶ ተሸንፏል። ይህ ግን የአቶ አርከበን ጥረት የሚያደበዝዘው ሳይሆን እንዲያውም አቶ መለስ በግምገማ ጊዜ አቶ አርከበን ለማሸማቀቅ በጣም የተጠቀሙበት ወርቃማ ጊዜ ሆኖ አልፏል።የአቶ አርከበን በሕዝቡ ውስጥ የነበራቸውን ስብእና ለማኮሰስም ጥሩ አጋጣሚ በመሆኑ አክራሪ ህወሃቶች የህዝብን ድምፅ በጉልበት ከደፈጠጡ በኃላ አዲስ ሥራ የተጀመረ ለማስመሰል (የአቶ አርከበን የስራ ፍሬ በመደበቅ) ብዙ ሲጥሩ ትዝብት ላይ ወድቀዋል።

አቶ አርከበ የአዲስ አበባ ከንቲባ በነበሩበት ጊዜ ከአከናወኗቸው ተግባራት ውስጥ-

1/ የአዲስ አበባን የቆሻሻ አወጋገድ ሥራ ዘመናዊ ማድረግ።

አሁን ባለንበት ዘመን የትላልቅ ከትሞች ቆሻሻ አወጋገድ መንገድ እና መልሶ ለምርት የመጠቀም ሂደት (recycling process)ትልቁ ሥራ መሆኑ ይታወቃል።የአቶ አርከበ ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ በ መንደር ደረጃ የቆሻሻ ማስወገጃ ገንዳ እንዲኖር ከማድረጉም በላይ የስራውን ሂደት የውጭ ኩባንያ በተውሰነ ገንዘብ ስራውን ለመውሰድ ያቀረበውን ኮንትራት ባለመቀበል ስራው የብዙ ሺህ ወጣቶች የስራ ዕድል መፍጠርያ እንዲሆን አድርገዋል።በአሁኑ ጊዜ የአገልግሎት ጥራት ጉድለት ቢስተዋልም ከየትኛውም መንደር ውስጥ የቆሻሻ ገንዳ እና ቤት ለቤት በተወሰነ ክፍያ ሕዝቡን በመጠይቅ የሚሰበስቡ ወጣቶች ስራውን ያከናውናሉ። እዚህ ላይ የስራው መጀመር ብቻ ሳይሆን ወጣቶች ይህንን ሥራ የመስራት ሞራል እንዲኖራችው የአስተሳሰብ ለውጥ እንዲያመጡ ያደረጉት ጥረት የሚዘነጋ አይደለም።እዚህ ላይ መጠቀስ ያለበት የቆሻሻ መሰብሰብ ሥራ እና ወደ ማዳበርያነት እና ሌሎች ምርቶች ለመቀየር ወጣቶቹን የማሰልጠን ሥራ ሌላው ተጠቃሽ ተግባር ነበር።

2/ የአዲስ አበባን ከተማ የአስተዳደር መዋቅር በማስተካከል።

የአዲስ አበባ ከተማ ቀድሞ በቀበሌ እና ከፍተኛ በሚሉ ሁለት የተዋረድ መዋቅሮች ትታወቅ ነበር። በአቶ አርከበ ዘመነ ከንቲባነት ግን ክፍለከተሞች እና ቀበሌዎች ዋና ማዘጋጃ ቤት ይሰራቸው የነበሩ ስራዎች እንዲወርዱ እና ሕዝቡን በቅርብ እንዲያገኙ ሆኗል።ለምሳሌ የመሬት አስተዳደር፣የንግድ ግብር መክፈል፣ልደት፣ጋብቻ ሰርተፍኬት መስጠት እና የመሳሰሉት የአገልግሎት ስራዎች በክፍለከተማ ደረጃ ወርደው መሰራት ችለዋል። ይህም የተቀላጠፈ እና የተሻለ አገልግሎት ለማስገኘት አስችሏል።ከእዚሁ ጋር ተጠቃሹ የውልና ማስረጃ ቢሮ ሲሆን ይህ ቢሮም በተሻለ ፍጥነት የስራ ፍሰቱን ያስተካከለ ቢሮ ነበር።

3/ የሰለጠነ የሰው ኃይል በማሰባሰብ 

አቶ አርከበ የአዲስ አበባ ከንቲባ ከሆኑበት ጊዜ ጀምሮ በተፈጠሩት የስራ መዋቅሮች መሰረት በመጀመርያ ዲግሪ ለነበሩ ብዙ ወጣቶች ሥራ ለማስጀመር ችለው ነበር።በእዚሁ መሰረት ብዙ የዩንቨርስቲ ምሩቃን ሥራ ላይ ተሰማርተው ነበር።በወቅቱ የፖለቲካ አመለካከትን መስፈርት ያላደረጉ የቅጥር ሂደቶችም ታይተው ነበር።ሆኖም ግን ከጥቂት ጊዜ በኃላ እንደ ሪፖርተር ዘገባ ከሰባ ፐርሰንት በላይ የሚሆኑት ስራቸውን ለመልቀቅ ተገደዋል።ይህ የሆነበት ምክንያት የአቶ አርከበን ሁሉን አቀፍ አመለካከት የሚቃወሙ አክራሪ ህወሃቶች የአቶ አርከበን ሂደት እግር በእግር እየተከታተሉ ከመውቀሳቸውም በላይ አዲስ የተቀጠሩትን ወጣቶች ማዋከብና ቆይተውም የተማረ ሁሉ ቅንጅት ነው በሚል እሳቤ ማንገላታት በመጀመራቸው ነበር።አንድ የኢህአዲግ ካድሬ በአንድወቅት አቶ አርከበን ''ከተማ ገባና ሥጋውንም ነፍሱንም ለአዲስ አበባ ሰጠ እኮ አበዛው'' ያሉት አገላለፅ አቶ አርከበ ምን ይባሉ እንድነበር አመላካች ነበር። ምናልባት ካድሬው ትግራይን እረስቶ የሚል ቃና ያለው ይመስላል።አንዳንድ ጊዜ ኢህአድጎች እንደዚህ የወረደ አስተሳሰብ ሲያስቡ ላይገርም ይችላል።ለመንደር ማሰብ ለህወሓት ካድሬዎች አዲስ አይደለም።

4/ እያንዳንዱን ቀበሌ እና ክፍለ ከተማ በኮምፕዩተር ኔትዎርክ ለማገናኘት የስራ ጅማሮ ነበር። 

5/ ለእያንዳንዱ ቀበሌ እና ክፍለከተማ ከስድስት ፎቅ ያላነሰ ምቹ ቢሮ መስራት በእቅድ ደረጃ የተያዘ እና በአንዳንዶች ለምሳሌ ቦሌ ክፍለ ከተማ የተከናወነ።

6/ የአዲስ አበባ ከተማን ዓለም አቀፋዊ ከተማነት ማጉላት ለእዚህም ማስረጃዎቹ 

ሀ/ የቦምባርሌን የልደት በአል በመስቀል አደባባይ ዓለም አቀፋዊ መድረክ ፈጥሮ  ልጆቹ እና የልጅ ልጆቹ ልዩ እንግዳ የሆኑበት ሲ ኤን ኤን ን ጨምሮ በቀጥታ ለዓለም የተላለፈ ፕሮግራም ማዘጋጀት፣ 

ለ/ ታዋቂዋን የአሜሪካ ቱጃር እና የጥቁሮች ተሟጋች ኦፕራን ወደሃገርቤት በመጋበዝ ስለ ኢትዮጵያ እንድትናገር በማድረግ እና 

ሐ/ ለአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች በሙሉ የእያንዳንዱን የአፍሪካ ሃገራት የመንገድ ስያሜ እንዲያገኙ እና ለሁሉም የአፍሪካ አገሮች የኢምባሲ መስርያ ቦታ በመስጠት የሰሩት ሥራ አዲስ አበባን አለመቀፋዊ ባህርይዋን አጉልተውላታል።

ማጠቃለያ 

አቶ አርከበ በከንቲባነታቸው ጊዜ ባሳዩት የስራ ፍሬ ህወሓቶች አልተደሰተም።ህዝቡ ግን ተደስቷል። ለእዚህም ነው ''አቶ አርከበ ኢህአዲግን ለቀው ይውጡ እና በግልዎ ይወዳደሩ እንምረጥዎት'' ያለው። ምንያደርጋል ለምርጫ 97 ላይ ኢህአዲግ አቶ አርከበ ቀርበው በቴሌቭዥን ለኢህአዲግ እንዲሟገቱ ያደረገው አንዱ 'አሱ የህዝብ አደለም የእኛ ነው ለማለት ነበር።'ምንም ቢሰሩም በሃገርጉዳይ ላይ ግን ቀልድ የማያውቀው ሕዝብ ምርጫውን አስተካከለ።አቶ አርከበን እየወደደ ግን ከገቡበት ጉረኖ አልወጣ ስላሉት።የሆነው ሆኖ አቶ አርከበ ምንም ያህል የህዝብ ፍቅር ቢያገኙ ለሕወሃቶች ግን አልተስማሟቸውም።አቶ አርከበ ጥሩ እንደሚሰሩ ያወቁት ህወሃቶች አቶ አርከበን መጀመርያ ወደ ከተማ ልማት ሚኒስትር ቀጥሎ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪነት አወረዷቸው።አሁን ደግሞ ከማአከላዊኮሚቴነትም ተነሱ።ምናልባት እንደሚመስለኝ ክልላዊ ሃሳብ የተጠናወተው ኢህአዲግ አቶ አርከብን ወደ ትግራይ ልማት ወይንም ለአንዱ ሀገር አምባሳደርነት አስቧቸው ይሆናል።ለሁሉም ጊዜ ይፈታዋል።



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Sunday, March 17, 2013

ለ ኢትዮጵያ ማን ይናገርላት?

(ይህ ፅሁፍ በ ህዳር/2005 ዓም በ እዚሁ  በጉዳያችን ጡመራ ላይ የወጣ ነው።)
ባለፈው ወር 'አፍሌ' በምትባል ጣልያን ከተማ ለፋሽስቱ ግራዚያኒ ሐውልት እንዲቆምለት በመደረጉ ኢትዮጵያውያን በየቦታው የተቃውሞ ድምፆች ሲያሰሙ ሰንብተዋል፡፡ የአፍሌ ከተማ ከንቲባ ''ግራዚያኒ ለፍርድ የቀረበው በፀረ ፋሺስት ኢጣሊያውያን ተዋጊዎች ፊት እንጂ በዓለም አቀፍ ችሎት ፊት ቀርቦ አልተፈረደበትም እናም መታሰቢያ ሐውልቱን በመንግሥት ገንዘብ ማቋቋም ስህተት አይደለም፡፡''የሚል ፌዝ ሲናገሩ ተደምጠዋል።

1943 እኤአ የፋሺስቱ የጦር መሪ ባድጎሊዮ ጓደኛውን ጀርመንን በመክዳት ለተባበሩት መንግሥታት እጁን በመስጠት በጀርመን ላይ ጦርነት አወጀ፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ የተባበሩት መንግሥታት አጋር የሆነችው ኢትዮጵያ ሐሳቧን ሳትጠየቅ ግፈኛዎቹ የፋሽስት ቀንደኛ ወንጀለኞች በተባበሩት መንግሥታት እንደ አጋር በመወሰዳቸው የፋሺስት የፓርቲና የጦር መሪዎች ከተጠያቂነት በ ሸፍጥ  አመለጡ። ይህ ማለት ግን ሰሩት ግፍ በሰው ልጅ ታሪክ ታይቶ ያልታወቀ ለመሆኑ አለም የሚያውቀው ነው። ሌላው ቀርቶ ጣልያን አለም መንግሥታት ፊት የፈረመችውን' መርዝ ጋዝ ጦርነት ያለመጠቀም' ስምምነት ወደጎን ተደርጎ ንፁሁ ኢትዮጵያ ገበሬ ላይ የወረደበት መርዝ ውርጅብኝ ኢትዮጵያ ብቻ አይደለም መላው አፍሪካዊ ላይ ብሎም በሰው ልጅ ላይ የተፈፀመ ፍትህ ያላገኝ ግፍ ነው።

በወቅቱ ግራዝያን ኢትዮጵያውያን መጠቀም ስለሚገባው የመሳርያ አይነት ሚስጥር ባስተላለፈው መልክት የ አሜሪካው 'ላይብረሪ ኦፍ ኮንግረስ' የሚገኝ ዶሴ  እንደሚከተለው በሚስጢርጽፎ እንደነበር ያጋልጣል፡፡  “ተልእኳችን እንዲሳካ ከተፈለገ ….በጠላት ላይ እጅግ ከፍተኛ ውድመት ከዚህም በላይ የሞራል ስብራት የሚያስከትለውን ልዩ የሆነ ፈሳሽ ቦምብና ሼል እንደፈለጉ በስፋት መጠቀም ያስፈልጋል፡፡''

ልዑል ራስ ካሳ ደግሞ በወቅቱ ስለነበረው ኢጣልያ ሕዝቡን በመርዝ መፍጀት እና የነበርውን ሁኔታ እንዲህ ይገልፁታል።
ጥቅጥቅ ያለ የዝናብ ዓይነት ፍንጣቂ ሲዘንብብን አገሩ በሙሉ እሳት የተያያዘ ይመስል ነበር፡ቡናማ ቀለም ያለው፣ የማይጨበጥ¸ቆዳን አቃጥሎ የሚበላ እንፋሎት ዓይነት የመርዝ ጋዝ ነበር ወታደሮቻችን ላይ የሚዘንብበቸው፡፡ በዚች ቀን ብቻ ቁጥሩን መናገር የሚያሰቅቅ ወታደሮቻችን አለቁ፡፡ ከሁለት ሺሕ ከብቶች በላይም በመርዙ አለቁ፡፡ በቅሎዎች፣ ላሞች፣ በጎችና የጫካው ዱር አራዊት ሁሉ አየሸሹ ወደ ሸለቆው እየሮጡ ወደ ገደል ገቡ፡፡ (ልዑል ራስ ካሳ፣ ላቀች አክሊሉ ገጽ ገጽ 66/68)

ንጉሠነገሰ ነገስት ቀዳማዊ አፄ ሃይለስላሴ እራሳቸው በፃፉት ''ሕይወቴ እና ኢትዮጵያ እርምጃ በተሰኘው መፅሐፋቸው እንዲህ ብለዋል- “የኢጣሊያ የጦር ጠቅላይ ሹም መቀሌን የኢትዮጵያ ወታደሮች በከበቡ ጊዜ የኢጣሊያ የጦር ሠራዊት መፈታቱን ስለተረዳውና ስለ ሠጋ ሌላ ዓይነት የኤፕሪት አጣጣል አደረገ፡፡ ይህንም አደራረግ አሁን ለዓለም ገልጦ ማስታወቅ የተገባኝ ነው፡፡ በአይሮፕላኖች ላይ የኤፕሪት ውሃ የሚረጭ መኪና ተዘጋጅቶ ሰፊ በሆነው አገር ላይ ሞትን የሚያመጣ ረቂቅ ዝናብ እንዲወርድበት አደረገ፡፡ ….. እጅግ የሚያሳዝን ነገር የሚያመጣ ይህ ብልሃት ተፈጸመበት፡፡ ሰውም ከብቱም አለቀ፡፡ ….. እኔም ወደ ጄኔቭ ለመምጣት የቆረጥኩት የኢትዮጵያ ሕዝብ የደረሰበትን ሥቃይ ለሠለጠነው ዓለም ለማስታወቅ ነው፡፡'' (ቀኃሥ፣ ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ 1 መጽሐፍ ገጽ 255)

ይህ ብቻ አይደለም ግራዚያኒ የካቲት 12/1929 ቀን ተሞከረበት ግድያ ሙከራ ተከትሎ ከተማዋ ነዋሪ ላይ አካፋ፣በዶማ እና በተገኘው መሳርያ ሁሉ ባደረሰው ጭፍጨፋ ሰላሳሺህ በላይ ሕዝብ እና የሚቆጠሩ ቤቶች አንዲት ጀንበር ብቻ መቃጠላቸውን ታሪክ ድርሳናት ያወሳሉ (http://gudayachn.blogspot.no/2012/02/75.html)


እዚህ አይነቱን ''ሰው'' ነው እንግዲህ ጣልያኗ' አሌፍ' ከተማ ሃውልት እና የመናፈሻ በስሙ እንዲቆምለት የከተማዋ ከንቲባ እና ቫቲካን ተወካይ በተገኙበት ያውም በመንግስት ገንዘብ የተመረቀለት።ይህ የሆነው እንግዲህ ኢትዮጵያ ጣልያንም ሆነ ቫቲካን ይፋዊ የሆነ ይቅርታ ባላገኘችበት እና ኢትዮጵያ ለተፈፀመባት ግፍ አለም ፍርድቤት ካሳ ባልተከፈላት ሁኔታ ላይ መሆኑን ልብ ማለት ይገባል። በነገራችን ላይ ጣልያን ገነባችው የሚባለው ቆቃ ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ የጉዳቱ መጠን እና ካሳ አለም ፍርድቤት ባልተዳኘ፣ ግን ጊዜው ወዳጅነትን ለማደስ በሚል የተሰራ መሆኑን መዘንጋት አይገባም።እዚህ ላይ ቫቲካን ቤተክርስትያንንም ሆነ ጣልያንን ይፋ ይቅርታ ተገቢ ካሳ ጋር መፈፀም አለበት ያሉ ኢትዮጵያውያን GLOBAL ALLIANCE FOR JUSTICE: THE ETHIOPIAN CAUSE The Fascist Genocide of Ethiopian People 1935 - 1941 (http://www.globalallianceforethiopia.org/)በተሰኘ ስብስብ ስር ሆነው ድምፃቸውን እያሰሙ ፊርማም እያሰባሰቡ መሆኑን በተለያዩ ጊዜያት መገናኛ ብዙሃን በሰጧቸው መግለጫዎች ማስታወስ ተገቢ ነው። ሆኖም ግን ይህ ግለሰቦች ጥረት እንደመሆኑ በተገቢው መንገድ መንግስት ዲፕሎማሲ ሲታገዝም ሆነ ማበረታቻ ሲደረግለት አይታይም።

ስብስቡ ግን ጥረቱ የሚደነቅ ነው።ጉዳዩ የትውልድ ጥያቄ ነው እና በተለያየ መንገድ ጉዳዩን ከማሳሰብ አለመቆጠባቸውን መጥቀስ ይቻላል። ለምሳሌ እዚሁ ፋሽሽት ግራዝያን ሃውልት እና መናፈሻ ሥራ በመቃወም መስከረም 5/2012 ' GLOBAL ALLIANCE FOR JUSTICE: THE ETHIOPIAN CAUSE' ጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር እና ፕሬዛንቱ በላከው የተቃውሞ ደብዳቤ እንዲህ የሚል ይገኝበት ነበር።



''...Today, Italy must immediately act to halt a handful of right-wing extremists from ruining Italy’s international reputation and credibility. No park or memorial should be named in honor of Rodolfo Graziani and those who perpetuate it should be stopped from doing so. If someone were to paint a portrait of Mussolini on the side of the Coliseum, wouldn’t it be a national imperative to reverse that? We expect such action now to reverse the opening of the “Rodolfo Graziani Park and Memorial” which occurred on August 11, 2012 in the little town of Affile, 50 miles east of Rome.Ethiopians and Italians around the world join the international community in proclaiming: “Never Again!”to genocide and we expect immediate action by the Italian government to revers This disgraceful attempt to celebrate hatred and racism which violates Italy’s own Law N° 205/1993 prohibiting the dissemination of ideas based on superiority or racial and ethnic discrimination...''


ኢትዮጵያ ማን ይናገርላት?

ኢትዮጵያውያን ሮም እስከ ዋሺግተን ድረስ ግራዚያን ሃውልት ሥራ እና መናፈሻ ምረቃ ላይ ተቃውሞ ሰሞኑን አሰምተዋል።ባለፈው ሰኞ ህዳር 26/2004 አሜሪካ የተደረገው ተቃውሞም አንዱ አካል ነው።ግን ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ለምን ዝም አለ?

እስራኤል ሁለተኛው አለም ጦርነት ወቅት ናዚዎች በደረሰባት 'የዘር ማፅዳት' ዘመቻ አሁን ድረስ እስራኤል ፀጥታ ኃይልም ሆነ ዲፕሎማሲው ናዚዎች ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጉዳዮችን ሁሉ ዋዛ አያልፏቸውም። ጀርመንም አይሁድ ላይ ለተፈፀመው ግፍ ማዘኗን በተደጋጋሚ ከመግለፅ አልፋ ጠቅላይ ሚኒስትሯ ይቅርታ ጠይቀዋል።






  


 የተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ ፖስተሮች (ምንጭ:-አባይ ሜዳ ድህረ -ገፅ )                                                                             
 
ወደ እኛ ስንመጣ ግን በመርዝ ሕዝባችንን የፈጀ፣በዋና ከተማችን ላይ አንዲት ጀንበር ብቻ ሰላሳ ሕዝብ በላይ የጨረሰ፣ ሌላም ሌላም ብዙ ግፍ የፈፀመው ግለሰብ ሃውልት ሲቆምለት እና መናፈሻ ሲሰየምለት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መግለጫ ለምን አላወጣም? (እስካሁን አልሰማሁም) ቢያንስ ጣልያንን አምባሳደር ጠርቶ ተቃውሞን አለመግለፅ የት የተማርነው ዲፕሎማሲ ነው? ነው ወይንስ ታሪክ ሁነቱ ገና መግባባት አልተደረሰም? ንግድ ግንኙነት እና እርዳታ እጅ እንዳያጥር ተፈርቶ ከሆነ በጣም አሳፋሪ ድርጊት ነው። የመጀመርያው የመርዝ ገፈት ቀማሽ የነበሩት የተንቤን፣የ አምባላጌ እና የመቀሌ ሕዝብ እና 'እንብኝ  ለሀገሬ ' ብሎ መላው ኢትዮጵያ የዘመተው አርበኛ፣ገበሬ፣ወጣት፣ሕፃን፣ሽማግሌ ደም ገና ሰባ ሰባት አመት እድሜ ላይ መሆኑን ዘነጋነው? ኢትዮጵያውያን በመንግስት ላይ የተቃውሞ ሰልፍ ሊያደርጉ ነው ሲባል ሪፖርት የሚቻኮሉት  ዲፕሎማሲ ቢሮዎቻችን ምነው ኢትዮጵያን  ሰው የሌላት ሀገር አስመሰሏት? ኢትዮጵያ ማን ይናገርላት?
ማስታወሻ፡ ዛሬ መጋቢት8፣2005ዓም ከስድስት ኪሎ ተነስተው ወደ ጣልያን ኢምባሲ የሃውልቱን መሰራት ለመቃወም የተንቀሳቀሱ ወጣቶች በፖሊስ መያዛቸውን ከ አዲስ አበባ የወጡ ዘገባዎች እየገለጹ ነው።ይህ ታላቅ የታሪክ ስብራት ነው። አንድ ወንድሜ በፌስ ቡክ ገጹ ላይ እንደጠየቀው ጣልያን እስካሁን ድረስ ከኢትዮዽያ አልወጣም ኢንዴ? ያሰኛል።


Friday, March 15, 2013

የናታን ጉዳይ ፍርድቤት ሲቀርብ እኛ ሁላችን መቅረባችንን መዘንጋት የለብንም(አጭር ማስታወሻ)


በእዚህ ሳምንት በኖርዌይ ትልቅ ኢትዮጵያን በተመለከተ ከተዘገቡት ጉዳዮች አንዱ እና ዋናው ሕፃን ናታን በኖርዌይ የመኖር ፈቃዱ በፍርድቤት መወሰኑ ነበር።ሕፃንናታን ከወላጆቹ ጋር በግድ ወደ ሃገሩ እንዲመለስ የኖርዌይ የኢሚግሬሽን ይግባኝ ቦርድ (The Immigration Appeals Board (UNE)) ወስኖ የነበረ መሆኑ ይታወቃል።የፍርድቤቱ የእዚህ ሳምንት  ውሳኔ ብዙዎቻችንን አስደስቷል።እርግጥ ነው ይህንን ያህል አንድ ስደተኛ አለምአቀፍ ሕግን ባልተከተለ መንገድ የስደተኛ መብቱ የፍርድቤት ጉዳይ መሆን ነበረበት ወይ? የሚለው እራሱን የቻለ ጥያቄ ቢሆንም።ሆኖም ግን የኖርዌይ የሕግ አሰራርን የተመለከተ ስለሆነ እና ውሳኔው ከሌሎች ሕጎች ጋር የሚኖረው ተቃርኖ አና  ስምምነት ኖርወጅያኖችን ብዙ አከራክሯል።ብዙዎችም መንግስታቸውን ወቅሰውበታል።ከእዚህ ባለፈ ደግሞ በአለምአቀፍ ግንኙነት ላይ የሚያመጣው አንደምታ ብቻ ሳይሆን አሁን በሀገሪቱ ውስጥ እየኖሩ ላሉት አያሌ የውጭ ሀገር ሕፃናት ላይ የፈጠረው የስነ-ልቦና ጉዳት በእጅጉ ተፈርቷል።ለእዚህም ነው የኖርዌይ የመገናኛ ብዙሃንም ሆኑ ዜጎች ጉዳዩን የመነጋገርያ አርስት ያደረጉት።

ለእኔ የሚታየኝ ግን አንድ አሳሳቢ ጉዳይ አለ። ናታን በኖርዌይ ቴሌቭዥን ዜናው ሲቀርብ እርሱ የመጫወቻ ዕቃዎቹን ይዞ ሲጫወት ነው የሚታየው። ሰው  ምን እያወራ እንደሆነ፣በቴሌቭዥን ይቅረብ አይቅረብ የእርሱ ጉዳይ አይደለም።ጫወታ ላይ ነው። ነገ ግንናታን ያድጋል።ሲያድግ ወላጆቹ ያዩትን ፈተና እርሱም ምን ተብሎ እንደነበር ከእነመረጃው ይመለከታል።ያንጊዜ ናታን ጥያቄዎች ይኖሩታል። እንዲህ የሚሉ -
''በሀገሬ ለምን መኖር አልቻልኩም? ለምን አባት እና እናቴ ተሰደዱ? እኛ ኢትዮጵያውያን ሀገር አጥተን ከኢትዮጵያ በብዙ ማይሎች የምትልቅ ሀገር መኖርያ ስጭን እያልን መለመን ነበረብን? '' የመሳሰሉት ጥያቄዎች። ይህን ጉዳይ የማነሳው ወላጆቹን ለመውቀስ አይደለም። በሀገራችን ያለውን ፖለቲካዊ፣ማህበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ችግር እናውቀዋለን።ወላጆቹም ከእዚህ የተለየ ማድረግ የሚችሉት ነገር ሊኖር አይችልም።

የናታን ጥያቄ ግን አሁን ላለነው ትውልዶች ሁሉ ነው። ችግር አለብን።አዎን ሀገራችን የመናገር፣የመፃፍ ወዘተ ችግሮች ብቻ ሳይሆን የማሰብ ነፃነት እራሱ ደብዛው ጠፍቷል።የኑሮው ችግር ተባብሷል።ነገር ግን ናታንን ይህ ጉዳይ አሁን አይመለከተውም ።ሕፃን ነውና።ትውልዱን ግን ይመለከታል።ባእዳን ሃገራት ለተወሰነ ጊዜ ያጠስልሉ ይሆናል።ዘለቀታነት ግን ሊኖራቸው አይችልም።አንድቀን ሀገሬ የማለት ጥያቄ ይነሳል።ዛሬ ያላሰናዱት ሀገር ደግሞ ነገ ሀገር ሊሆን አይችልም።ናታን እና የዮናታን እኩዮች ሀገራቸውን ማየት እንዲችሉ እና ትውልዱም በውጭ ሀገር ፍርድቤቶች እየተንከራተተየመኖርያ ፍቃድ ስጡን’ ብሎ እንደፍልስጤማውያን ሀገር ለማኝ እንዳይሆን፣ናታንም ነገ አድጎ እናንተስ የሀገራችሁን ችግሮች ለመፍታት ምን አደረጋችሁ?ብሎ ሳይወቅሰን ሀገራችንን ማሰናዳትችግሯን መፍታት፣ጉድፏን መጥረግ የእዚህ ትውልድ ዕዳ ነው። የናታን ጉዳይ ፍርድቤት ሲቀርብ እኛ ሁላችን በ አካል ባይሆን በዜግነት መቅረባችንን መዘንጋት የለብንም።
Refer Yonatan case court decisions
Click http://www.norwaypost.no/index.php/news/latest-news/28255-nathan-7-wins-against-the-immigration-appeals-board
http://theforeigner.no/pages/news/norway-immigration-officials-lose-ethiopia-case/ 

አበቃሁ 
ጌታቸው በቀለ 
ኦስሎ 

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።