ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, September 29, 2019

በኦሮሞ ማኅበረሰብ ውስጥ ያሉት አቴቴ፣ጨሌ፣ዋቀፈና፣እሬቻ የጣኦት አምልኮ ናቸው? ወይንስ አይደሉም?

''ለጣኦት የተሰዋ አትብሉ'' ክርስትናም እስልምናም ያዛል።
እሬቻ የፀሐይ አምላክ ልጅ ኦራ ከተሰኘ ጣኦት ጋር ይገናኛል።
ይህንን ልዩ ዶክመንተሪ 'ኦድዮ' እስከመጨረሻው ካዳመጡ በኃላ ለጥያቀዎቹ መልስ ያገኛሉ።
(ልዩ ጥናታዊ ዶክመንተሪ የራድዮ ዝግጅት ያድምጡ)
========================
ሸገር ራድዮ ስንክሳር  መርሐግብር  ርዕስ = ''አቴቴ''
መርሐግብሩ አየር ላይ የዋለው መስከረም 10/2019 ዓም (ሴፕቴምበር  22/2019 ዓም)


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Sunday, September 22, 2019

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በምዕመኖቿ ላይ የሚፈጸመው ግፍና መከራ እንዲቆም፣ ዛሬ ዕሁድ ብቻ ከሰላሳ በላይ በሚሆኑ የኢትዮጵያ ከተሞች ሰልፍ ተደረገ።የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ሰልፎቹን ተቀላቅሏል።ለንደንም ሰልፍ ነበር።(ከሃያ በላይ ፎቶዎች ይመልከቱ)

Breaking news ethiopia ሰበር ዜና ኢትዮጵያ 

in over thirty cities in ethiopia, Hundred Thousands TAKE TO STREETS TO PROTEST REPEATED ATTACKS AGAINST Ethiopian orthodox tewahido church (see over 20 pictures)

Today Ethiopian Orthodox Tewahido church followers and religious leaders have another round huge demonstration, protesting burning of the churches and repeated attacks on its followers, was held in over thirty cities in Ethiopia and in London. Last thursday,there was similar demonstration in Washington DC in front of Ethiopian Embassy. Muslim Ethiopians have also joined in all demonstrations showing their solidarity with Ethiopian christians.(see photos below Amharic version)
ጉዳያችን ዜና / Gudayachn News
 መስከረም 11/2011 ዓም (ሴፕቴምበር 22/2019 ዓም)
=================
 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን እና አባቶች በቤተ ክርስቲያንና ምዕመኖቿ ላይ ግፍ የፈጸሙት አካላት በሕግ እንዲጠየቁ፣በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚደረጉ ጥቃቶች እንዲቆሙ እና መንግስት ለችግሩ ትኩረት እንዲሰጥ በመጠየቅ  ከሰላሳ በላይ በሚሆኑ የኢትዮጵያ  ከተሞች ዛሬ  ሰልፎች ተካሂደዋል።
በያዝነው ሳምንት አጋማሽ ላይ በዋሽንግተን የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን እና አባቶች በኢትዮጵያ ኤምባሲ ፊት ለፊት ሰልፍ ያደርጉ ሲሆን ዛሬ በለንደን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ በተገኘበት ሰልፍ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል።በሀገር ቤት የተደረገው ሰልፍ ከሰላሳ በላይ በሚሆኑ ከተሞች የተደረገ ሲሆን ከእነኝህ ውስጥ  በባሕር ዳር፣ በደብረ ማርቆስ፣ በብቸና፣ በደጀን፣ በሞጣ፣ በደብረ ብርሃን፣ በማጀቴ፣ በጫጫ፣ በአረርቲ፣ በመሐል ሜዳ፣ በፍኖተ ሠላም፣ በቡሬ፣ በመርዓዊ፣ በእንጅባራ፣ በደባርቅ፣ በዳባት፣ በአዲ አርቃይ፣ በጯሂት፣ በወልድያ፣ በቆቦ፣ ሮቢት፣ በላልይበላ፣ በውጫሌ፣ በወረኢሉ፣ በደላንታ፣ በኮን፣ በዳንግላ፣ በዱር ቤቴ፣ በአዲስ ዘመን እና በሌሎችም ከተሞች ተካሂደዋል፡፡
በልዩ ልዩ ከተሞች የተደረጉ ሰልፎች ፎቶዎች ከእዚህ በታች ይመልከቱ።
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia

Ethiopia
Ethiopia

Ethiopia

Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Washington DC


London
ለንደን /London

ለንደን /London


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Wednesday, September 18, 2019

Huge Protest Held Against the Persecution of the Orthodox Church in Ethiopia

  • Large numbers of Muslims also joined the protests in support of their Christian compatriots.


On Sunday 15th September 2019 in the Ethiopian capital of Addis Ababa and other towns across Ethiopia, thousands of people poured into the streets to protest against the unprecedented atrocities that are being committed against the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church and her faithful.
While the organizing committee in Addis Ababa had postponed the demonstration by two months to give time for talks with government bodies, the demonstrations outside Addis Ababa took place.

Reports from Bahir Dar, Gondar, Dessie, Kombolcha, Jimma, Debre Berhan, Debre Tabor, Tsegede, Dessie, Kombolcha and Gondar states that large numbers of Muslims also joined the protests in support of their Christian compatriots.
In Addis Ababa however, there was a very large police presence on the streets to prevent the demonstrators reaching Mesqel Square from their respective Church compounds. However, the demonstrators thronged the compounds of several Churches in the city (by singing, clapping and ululating,) demanding an end to the persecution of the Orthodox Church.
Huge banners thanking Patriarch Krill of Moscow and All Russia and President Putin of the Russian Federation were on display as well.
The above video shows protesters on the grounds of the Lideta Le Mariam (Nativity of the Virgin Mary) Monastery, in the large courtyard between the two Churches of the Monastery.
Source: OCP

Source : Serbian Orthodox Church 

Monday, September 16, 2019

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞችን ሁሉን አቃፊ የሆነ ፖለቲካዊ ዕሳቤ መሰረት ያደረገ የፖለቲካ ፓርቲ በመመስረት እና ሚናውን በማስፋት የኢትዮጵያ ህልውናን በትክክል ማረጋገጥ ይቻላል። (ጉዳያችን ሃሳብ)

በእዚህ ፅሁፍ ስር የሚመከተሉትን ንዑስ ርዕሶች ያገኛሉ - 

  • የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች በፖለቲካ አደረጃጀት ተደራጅተው ቤተ ክርስቲያኒቱን ሊታደጉ ይገባል፣
  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞችን ሁሉን አቃፊ የሆነ ፖለቲካዊ  ዕሳቤ ምንድነው?
  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያበረከተችውና አሁን ያለችበት ፈተና፣
  • ''ኢትዮጵያን ለመምታት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን ምታ!'

================================
ጉዳያችን / Gudayachn
መስከረም 5/2012 ዓም (መስከረም 16/2019 ዓም)
=================================

ወቅታዊው ሃገራዊ ሁኔታ

የኢትዮጵያ ውስጣዊ የፖለቲካ ሁኔታ ዓይነተኛ አያያዥ ኃይል ካላገኘ ከኢሕአዴግ መሰነጣጠቅ ተከትሎ የሀገሪቱ ፖለቲካ ማባርያ ወደ ሌለው የእርስ በርስ እልቂት እንዳይመራ ያሰጋል።ክልሎች በራሳቸው የታጠቀ ኃይል በማደራጀት ላይ ተጠምደዋል።ሌላው ቀርቶ ክልሎች ያላቸውን የሚሊሻ ብዛት ራሱ ማዕከላዊ መንግስት የሚያውቀው አይመስልም።ይህ ደግሞ አደገኛ መንገድ ነው።ዛሬ መስከረም 5/2012 ዓም የኬንያው ዘ ስታንዳርድ ጋዜጣ በኢትዮጵያ እና ኬንያ በኩል ያለው መንገድ መዘጋቱን መዘገቡን ጠቅሶ ዋዜማ ራድዮ በፌስ ቡክ ገፁ ላይ ገልጧል።በሌላ በኩል ሸገር ኤፍ ኤም ራድዮ  በምሽት የዜና እወጃው ላይ በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር  አምባሳደር መለስ ዓለምን ደውሎ ባናገራቸው መሰረት ጉዳዩ ውሸት ነው በሚል በደፈናው ለአዲስ ዓመት ለማክበር ሞምባሳ ነበርኩ የእኛ እና የኬንያ ግንኙነት ጥሩ ነው።በሚሉ ንግግሮች አልፈውታል። እንደ ዘስታንዳርድ ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ኬንያ ድንበሩን ለመዝጋቷ ምክንያቷ ሕገ ወጥ ንግድ በመበራከቱ መሆኑን እና በየቀኑ ከ30 እስከ 50 የሚደርሱ ካሚዮኖች ጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ የተለያዩ ሕገ ወጥ ሸቀጦችን ወደ ኢትዮጵያ እንደሚያግዙ እና ብዙዎቹ መጋቢ መንገዶችን ስለሚጠቀሙ ታከስ ሳይከፍሉ የሚገቡ መሆናቸውን በመጥቀስ ነው።እነኝህ መሣርያዎች ወደ ኢትዮጵያ የሚያስገባው ማን ነው? ለምን ተግባር? መንግስት በአግባቡ ድንበር እየጠበቀ ነው? መንግስት መዋቅር ውስጥ  በተለይ በኦዴፓ ውስጥ የገቡ የመንግስት ኃላፊዎች ድንበር ጠባቂዎች፣የግምሩክ ባለስልጣናት ከፅንፍ ኃይሎች ጋር ተባብረው  የጦር መሳርያ እንዲገባ እያደረጉ ላለመሆናቸው ዋስትናው ምንድነው? 

ይህ በጣም ወቅታዊውን የኢትዮጵያ ሁኔታ ለማሳየት የቀረበ ማሳያ ነው እንጂ በመንግስታዊው መዋቅር ውስጥ የሚታየው ወጥ ያልሆነ እና የልዩ ልዩ ኃይሎች መጠቀምያ የሆነው ቢሮክራሲ ኢትዮጵያ ወደ አደገኛ ሁኔታ እየሄደች ለመሆኑ ማሳያዎች ናቸው። ጠቅላይ ምንስትር ዓቢይ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ቅዳሜ መስከረም 3/2012 ዓም ለሸገር ''ጨዋታ'' በተሰኘ ፕሮግራም ላይ ቀርበው ሲናገሩ ''የመንጋ ሂደት በአዲሱ ዓመት የሚቀጥል አይሆንም'' ሲሉ ተደምጠዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በእዚህ ቃለ መጠየቃቸው ላይ  ባብዛኛው የሚነበብባቸው የየዋህ ፖለቲከኛ እሳቤዎች እንጂ መረር ያለ የኢትዮጵያን አድነት በሚያቅፍ መልኩ የማዕከላዊው መንግስትን ሚና የሚያጎላ ሆኖ አልታየም።ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያነሱት የመደመር ዕሳቤ  በትክክልም የሚያማልል ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ መልካም መንገድ የሚያስዝ ሊሆን ይችላል።ይህ ግን ከጠንካራ የማዕከላዊ መንግስት የማስፈፀም አቅም ጋር ካልሄደ ተግባራዊነቱን አሳሳቢ ያደርገዋል።


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያበረከተችውና አሁን ያለችበት ፈተና 


ኢትዮጵያ በዘመናት ጉዞዋ እንደ ጅማት እና ክር ሆኖ ታሪክ ማንነቷን ካቆዩት ውስጥ ቀዳሚዋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ነች።ከክርስቶስ ልደት በፊት በሕገ እግዚአብሔር እና በኦሪት ስርዓት የፀኑ ነገስታቶቿ በአራተኛው ክ/ዘመን በብሔራዊ ሃይማኖት ሆኖ በቤተ መንግስት የታወጀው ክርስትና እስከ 20ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ድረስ በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ሕይወት ላይ የራሷን አሻራ ከማቆየቷ በላይ ኢትዮጵያ በነፃነት እንድትዘልቅ መንፈሳዊ እና ሞራላዊ ልዕልና በማጎናፀፍ የመሪነት ሚና ተጫውታለች።ከእዚህ በተጨማሪ ቤተክርስቲያኒቱ ከፊደል ገበታ እስከ ከፍተኛ የፍልስፍና እሳቤዎች እንዲሁም መሪ ነገሥታቱን ከልጅነታቸው በሞራል፣በመንፈሳዊ ሕይወትና በፍትሃዊ አሰራሮች ሁሉ አሰልጥና ለመሪነት በማብቃት የቤተ ክርስቲያን ድርሻ ብቸኛ እና መተኪያ የሌለው ሆኖ ከሁለት ሺህ ዘመናት በላይ  የዘለቀ አንፀባራቂ ታሪክ ነው።ይህ በእንዲህ እያለ ግን ላለፈው ግማሽ ክፍለዘመን በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ የደረሰው ፈተና በርካታ ጥፋት በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ከማድረሱም በላይ በውጤቱ ኢትዮጵያ አንድ በሞራል እና በመንፈሳዊ ሕይወት የበለፀገ ትውልድ በማጣቷ ምክንያት  በጎሳ የሚያምን፣ሙሰኛ እና በገዛ ወገኑ ላይ ገጀራ የሚያነሳ ትውልድ በኢትዮጵያ ምድር  እንዲበቅል ምክንያት ሆኗል።


ከእዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በቅርብ በኢሕአዴግ ውስጥ በመጣው የጥገናዊ ለውጥ ተከትሎ ቤተ ክርስቲያንቷ በባሰ አደገኛ ሁኔታ ላይ ወድቃለች።ይሄውም ለውጡን ተከትሎ ወደ ሀገር የገቡት  የጎሳ እና አክራሪ የፅንፍ ኃይሎች ጋር ኢሕአዴግ በገጠመው ግንባር በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ  ቀጥተኛ ዘመቻ ከፍቷል።ለእዚህም ማሳያው የኦሮምያ ቤተ ክህነት ለመመስረት የተደረገው ሙከራ ላይ የመንግስት ስውር ድጋፍ፣ ብፁዓን ጳጳሳት መንግስትን ባናገሩበት ሂደት ያገኙት አጥጋቢ ያልሆነ ምላሽ እና ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን መንግስት  ለሚደርሰው ጥፋት ለማስቆም እርምጃ ይውሰድ የሚለውን ጥያቄ ለመጠየቅ በሚልዮን የሚቆጠር ሕዝብ በጎንደር፣ደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ደብረ ታቦር እና ሌሎች ከተሞች ያደረጉት ሰልፍ በኢትዮጵያ የመንግስት ዜና ማሰራጫዎች አለመዘገቡ ትልቅ ቁጣ በመላው ሀገሪቱ ፈጥሯል።ከእዚህ በተጨማሪ ሰሚ ያጣው የቤተ ክርስቲያኒቱን ህንፃዎች የማቃጠል እና ምመናኗን የማሰደድ ተግባር ሁሉ የሚመሩት የቤተ ክርስቲያኒቱን  እሳቤዎች የሚያስጠብቅ የፖለቲካ ፓርቲ አስፈላጊ መሆኑን ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞችን ሁሉን አቃፊ የሆነ ፖለቲካዊ  ዕሳቤ ምንድነው?


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አማኞች ሁሉን አቃፊ የሆነ ፖለቲካ ኢትዮጵያን ዘመናት አሻግሯል።

  • አቃፊው ፖለቲካ የእስልምና መስራች መሐመድ ቤተሰቦችን ተቀብሎ ያስተናገደ ፖለቲካ ነው።
  • አቃፊው ፖለቲካ የይሁዲ  እምነት ተከታዮችን ከአንድ ሺህ ዓመት በላይ አስጠልሎ ወደ ሀገራቸው የሸኘ አቃፊ ፖለቲካ ነው። 
  • አቃፊው ፖለቲካ ከምፅዋ እስከ ሞያሌ፣ከፈርፈር እስከ አኮቦ ከእስልምና አማኞች ጋር ጎን ለጎን በአንድነት እና በመከባበር የዘለቀ፣ኢትዮጵያን እንደ ደም ስር እና ጅማት ያስተሳሰረ አቃፊ ፖለቲካ ነው። 
  • አቃፊ ፖለቲካው ኢትዮጵያ በፋሺሽት ጣልያን ስትወረር ከደቡብ እስከ ሰሜን ሕዝብ አስተባብሯል።
  • አቃፊ ፖለቲካው በየትኛውም ዓለም ያልታየ መከባበርን፣እምነት ያልለያቸው ኢትዮጵያውያን በአንድ እድር፣እቁብ፣ሰርግ እና ሃዘን ሁሉ እንዴት እንደሚኖሩ አስተምሮ በፍቅር አስተሳስሯል።
ይህ አቃፊ ፖለቲካዊ እሳቤን ለመናድ መሞከር ኢትዮጵያን ለመናድ የመሞከር የእብደት ሥራ አሁን በኢትዮጵያ እየተሰራ ነው። የእብደት ስራውን እየሰሩ ያሉት የፅንፍ የጎሳ ድርጅቶች እና ኦዴፓ ውስጥ የተሰገሰጉ አደገኛ  ግለሰቦች እና የውጭ ተባባሪዎቻቸው ቅንጅት ሁሉ ነው።

''ኢትዮጵያን ለመምታት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን ምታ!''

ኢትዮጵያ በዘመኗ ሁሉ የመጡባት ጠላቶቿ ቀዳሚው የኢትዮጵያ ኃይል አለበት ብለው የደመደሙት እና ቀድመው የሚያጠቁት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ነው።በዘጠነኛው ክ/ዘመን መጨረሻ ላይ የተነሳችው እና የአክሱም ስርወ መንግስት የናደችው ዮዲት ጉዲት ተብላ በታሪክ የምትጠራው ሴት እና ሰራዊት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የተቀናጀ ዘመቻ በማድረግ፣በማቃጠል እና እና ምዕመናንን በመፍጀት  ኢትዮጵያን ለማዳከም ሞክራለች፣ከክልበኃላ 1500 ዓም በኃላ የተነሳው እና በቱርክ የታገዘው ግራኝ መሐመድ የመጀመርያ ኢላማው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ነበረች። ቱርካዊ አማካርዎቹም ሆኑ ግራኝ መሐመድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን በመበተን ኢትዮጵያን ገልብጦ እንደፈለገ ሊሰራት ሞክሮ አልተሳካለትም።ግራኝ መሐመድ ይህንን ያድርግ እንጂ ሁሉን አቃፊዋ ቤተ ክርስቲያን ግን የግራኝ መሐመድን ካባ ሳይቀር በቅርስነት ይዛ መርጦለ ማርያም ቤተ ክርስቲያን በሙዚየሟ  በመስታወት አስቀምጣ ለጎብኚዎች አሁን ድረስ ታሳያለች።


በ1928 ዓም ኢትዮጵያን የወረረው ፋሺሽት ጣልያን  ዋና ኢላማው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ነበረች።ፋሺሽት ጣልያን የቤተ ክርስቲያኒቱን ጳጳሳት አቡነ ጴጥሮስን ጭምር በአደባባይ በጥይት ከመደብደብ እስከ በአንድ ቀን በመቶዎች የሚቆጠሩ የደብረ ሊባኖስ መነኮሳትን ገደል በመጨመር ሁሉ  ጥፋት በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ አድርሳለች።ዛሬም  የባዕዳን ተልኮ አስፈፃሚዎች የፅንፍ ጎሰኘንት አራማጆች እና በመንግስት መዋቅር ውስጥ የተሰገሰጉ አስፈፃሚዎች በመንግሥትነት ተከስተው ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማጥፋት ግልጥ ዘመቻ ላይ ናቸው።ይህ የጥፋት እና የጥላቻ ስሜታቸውን መታገስ አቅቷቸው ምእመናኑ በአደባባይ ያሰሙትን ድምፅ ግብር ከፍሎ ለሚያስተዳድራቸው ሕዝብ የመገናኛ ብዙሃን እንዳይዘግቡ በማገድ እኩይ ተግባር ተገልጧል።ይህ ብቻ አይደለም ቤተ ክርስቲያኒቱ ከጅጅጋ እስከ ሲዳማ፣ከከፋ እስከ ጅማ በቃጠሎ ስትጠቃ እና ምዕመናኗ ሲሰደዱ የሚከላከል መንግስታዊ አካል አለመኖሩ ቤተ ክርስቲያኒቱ በመልካም እሳቤዎቿ ላይ ተመስርታ ልጆቿን በፖለቲካ አደረጃጀት መደራጀት የወቅቱ ቀዳሚ እና ዋነኛ ጥያቄ አድርጎታል።

የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች በፖለቲካ አደረጃጀት ተደራጅተው ቤተ ክርስቲያኒቱን ሊታደጉ ይገባል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ራሷን የቻለች የኢትዮጵያ የደም ስር እና የጀርባ አጥንት አያያዥ ነች።በኢትዮጵያ የተነሱ ቅራኔዎች ሁሉ ለመፍታት የቤተ ክርስቲያኒቱ ሚና የግድ አስፈላጊ ነው።ቤተ ክርስቲያኒቱ እስከ 1966 ዓም ድረስ መንግስታዊ ጥበቃ ስለነበራት የሀገር አንድነትም ሆነ ሰላም ተጠብቆ ለመቆየት ችሏል።በአሁኑ ወቅት የቤተ ክርስቲያኒቱን ቅርስ፣ማንነት፣የጋራ እና አቃፊ ዕሴት ሁሉ ጠባቂ አጥቶ ከፍተኛ አደጋ ላይ ነው። አሁን ይህንን የሚጠብቅ ንጉሰ ነገስት መንግስት የለም።ይህንን ክፍተት በዘመናዊው የፖለቲካ መንገድ ማለትም የተደራጀ ተገዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲ ወይንም አደረጃጀት ኢትዮጵያ ከሌላት ለሀገሪቱ እንደ ሀገር ለመቀጠል እጅግ አደኛ ነው። 

ይህ ማለት ቤተ ክርስቲያኒቱ በፖለቲካ አደረጃጀት ትደራጅ ማለት አይደለም።የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ  ሂደት ሁሉ የነበረ ወደፊትም የሚኖር እና ምድራዊውን ሳይሆን ሰማያዊ ሕይወትን መሰረት ያደረገ ነው። ሆኖም ግን ''የቄሳርን ለቄሳር'' ካለ መፅሐፉ የእግዚአብሔርን ጉዳይ ስናወራ የቄሳርን ሥራ ግን ረስተነዋል።በመሆኑም ቤተ ክርስቲያኒቱ ቀድሞ በነገሥታቱ ሕጋዊ ከለላ የነበራት ቤተ ክርስቲያን በዘመናዊው የፖለቲካ አደረጃጀት የተደራጁ ልጆች  ባለመነሳታቸው ከመቼውም ጊዜ በላይ አደገኛ ክፍተት ተፈጥሮባታል።ክፍተቱ ደግሞ በቀጥታ በሀገሪቱ ሁለንተናዊ አንድነት መፍረስ ላይ በትክክል እየተንፀባረቀ ነው።ለእዚህ ነው የኦርቶዶክሳውያን ፖአለቲካዊ አደረጃጀት ክፍተቱን የመሙላቱ ፋይዳ አንገብጋቢ የሚያደረገው።

ይህንን ክፍተት ይህ ትውልድ መሙላት ካልቻለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ለአደጋ የሚያጋልጣት ትውልድ እንዳይሆን ያሰጋል።ይህ ጉዳይ የሃይማኖት ልዩነት የሚፈጥር የሚመስላቸው አሉ።አንዳንዶች  ሌሎችም በሃይማኖት እንዲደራጁ በር የሚከፍት ነው የሚሉም አሉ።ሆኖም ግን አሁን የኢትዮጵያን አንድነት ለማምጣት የእስልምናም ሆነ የሌሎች እምነቶች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን በተስፋ እንደሚጠብቁ መረዳት ያስፈልጋል።አሁን ያለው የኢትዮጵያን የነበረ ዕሴት መናድ ላይ ማንኛውም  ኢትዮጵያዊ የዕምነት ድርጅት አይስማማም።ምክንያቱም ጉዳዩ የህልውና ጉዳይ ነው።የመጥፋት እድሉ ሁሉም ላይ የመጣ ነው። ስለሆነም የጋራ ኢትዮጵያዊ ዕሴት ጎልብቶ በፖለቲካ ኃይልነት መውጣት እና  የኢትዮጵያን እሴቶች ከበታኝ ኃይሎች መታደግ ወቅታዊ እና አንገብጋቢው ጉዳይ መሆኑን የማይረዳ የማንኛውም የእምነት ድርጅት  የለም። በእርግጥ ኢትዮጵያን ለመበተን የሚያልሙ ኃይሎች ይህ ጉዳይ አይዋጥላቸውም። ኢትዮጵያን ለመበተን እንደሚያስቡት የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን መበተን ፈፅሞ በቅርብ የማይሳካላቸው ግን ጊዜ የሚወስድ ድምፅ አጥፍቶ ውስጥ ውስጡን በመሄድ ብቻ ሊሳካ እንደሚችል ያስባሉ።

ለማጠቃለል የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች ተደራጅተው ቤተ ክርስቲያኒቱን ሊታደጉ የሚገባበት ወሳኝ እና ታሪካዊ ጊዜ ላይ ነን።መልፈስፈስ እና መዘግየት በራሱ አደጋ አለው። አንዳንድ የዋሃን ዛሬም ፖለቲካ ከእምነት ጋር ይጣረሳል፣ እያሉ ስሌት ውስጥ የሚገቡ ይኖራሉ።እነኝህኞቹ ንጉስ ዳዊት ንግስናው፣ንጉስ ሰለሞን ሀገር ማስተዳደሩ፣ንጉስ  ቆስጠንጢኖስ በእናቱ ንግስት ዕሌኒ አማካይነት የክርስቶስን መስቀል ማግኘቷ ሁሉ ፖለቲካ ብለው ይተዉት እያሉ ነው። ነገሥታቱ አብርሃ ወአፅብሃ  ለሀገር መትረፋቸው፣ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ ኢትዮጵያን ወደ ስልጣኔ መስመር መምራታቸው ሁሉ  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ይዘው መሆናቸውን የመዘንጋት ያህል ነው። አሁንም ወቅቱ ኢትዮጵያ እራሷን በአግባቡ የምታይበት ወሳኝ ጊዜ ነው። በድጋሚም  የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች ተደራጅተው ቤተ ክርስቲያኒቱን ሊታደጉ ይገባል።ጉዳዩ ከተራ ሰላማዊ ሰልፍ እና ድርድር በላይ ከፍ ያለ አደገኛ ሁኔታ ነው የሚታየው።

አለን ሁሉን በእግዚአብሔር አልፈን (ቪድዮ)


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Friday, September 13, 2019

የሰልፉ ቀን መቀየር ጥያቄውን አጠንክሮ የሚያወጣ ነው::ቀጣይ ስራዎች ምን መሆን አለባቸው:?

ጉዳያችን/ Gudayachn
መስከረም 3/2012 ዓም (ሴፕቴምበር 14/2019 ዓም )
++++++++++++++++++++++++++++++
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እየደረሰባት ያለውን ቃጠሎ፣ምእመናኖቿን ላይ የደረሰው እንግልት እና ስደት እንዲቆም ሶስት ዓላማዎች የያዘ ጥያቄ መንግስትን ለመጠየቅ ለመስከረም 4 ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የነበረው ዕቅድ ለጥቅምት 30 መተላለፉን አስተባባሪው ኮሚቴ ዛሬ መስከረም 2/2012 ዓም ገልጧል።ሰልፉን በተመለከተ ጉዳያችን ላይ የወጣው ዝርዝር ዘገባ ለማንበብ  ይህንን  ገፅ ይጫኑ።

የሰልፉ ጥሪ መደረጉ በራሱ ምን በጎ ነገር አመጣ?

የሰላማዊ ሰልፉ መጠራት በራሱ የሚከተሉትን መልካም ነገሮች ይዞ መጥቷል። እነርሱም -

  • ከቤተ ክህነት እስከ  ቤተ መንግስት የኦሮቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተፅኖ ከማሕበራዊው ጉዳይ በላይ የተሻገረ አገር አንቀጥቅጥ አጀንዳ የማንቀሳቀስ አቅሙ ታይቷል።
  • ከጠቅላይ ሚኒስትሩ እስከ ክልል ባለስልጣናት ድረስ የቤተ ክርስቲያን አጀንዳ ለውይይት ቀርቧል።
  • እጅግ የጠነከረ ኦርቶዶክሳዊ አንድነት እና መተሳሰብ እና መናበብ ፈጥሯል።
  • አጀንዳው ዓለም አቀፍ ህብረት ፈጥሯል።በአሜሪካ እና አውሮፓ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት  ጥያቄውን ደግፈው እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
  • ኦርቶዶክሳዊው ወጣት በመጪው ጊዜ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲያውቅ ጥሩ ማሳሰቢያ ሆኖታል።
  • ኦርቶዶክሳዊው ከመንግስት ጋር ጨምሮ የመደራደር አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ ከፍ አድርጎ መጥቷል።
  • ቤተ ክርስቲያን ውስጣዊ አስተዳደራዊ መዋቅሯን ለማሻሻል ያላትን ኃላፊነት ከመቼውም ጊዜ በላይ አጎልቶታል።
  • የጎጥ ፖለቲካውን አደናብሮታል።ኦርቶዶክሳዊው ህብረት የጎጥ ፖለቲካውን የመደርመስ አቅም እንዳለው በግልጥ አመላክቷል።
አሁንም ችግሩ ግዙፍ ነው

ከላይ የተጠቀሱት መልካም ገፅታዎች የድል መጨረሻ ተደርገው የሚቆጠሩ አይደሉም። በትንሽ ነገር የረኩ መስሎ መቅረብ በራሱ ትልቁ ችግር ነው።በአሁኑ ደረጃ ምንም የተሰራ ነገር የለም።ከላይ የተጠቀሰው መልካም ተፅኖ እንዳለ ሆኖ ፣በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ያጠላው  ጥላ ግን ገና አልተገፈፈም።ይልቁንም በእንቅስቃሴው ሳብያ የኦሮዶክሳውያኑ መነቃቃት ለበታኝ ኃይሎች እንደ  ድንገተኛ መብረቅ አስደንግጧ ቸዋል።ቀድሞም በስጋት ሲያዩአት የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን ለመጉዳት አሁን በደነበረ መንፈስ ምንም ከማድረግ አይመለሱም።ከእዚህ በተጨማሪ መንግስት መዋቅር ውስጥ የተሰገሰጉት የፅንፍ ኃይሎች የመንግስትን ፖሊሲ  የሚያስፈፅሙ መስለው ቤተ ክርስቲያኒቱን ለመጉዳይ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም።ሰሆነም አሁንም ችግሩ ገና ግዙፍ ነው።

በቀጣይ ምን ይደረግ? 

አሁን ባለው የሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ የሚከተሉት ተግባራት ቢከናወኑ መልካም ነው። እነርሱም - 

1ኛ) የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ እራሱን በሚገባ ማጠናከር አለበት።ይሄውም ግብ እና የውስጥ መተዳደሪያውን አዘጋጅቶ ከኮሚቴ በዘለለ ስያሜውን ከፍ አድርጎ እና የስራ ዘርፍ አውጥቶ  መንቀሳቀስ፣

2ኛ) ከኮሚቴ ከፍ ባለ ደረጃ የተደራጀው አካል ለጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ቀርቦ ቡራኬ እና መመርያ መቀበል፣

3ኛ) ከኮሚቴ ከፍ ባለ ደረጃ የተደራጀው ኮሚቴ ውጫዊው የቤተ ክርስቲያኗ ጉዳይ ላይ ከማትኮሩ በተጨማሪ  የማኅበራት ሕብረት ከመፍጠር ባለፈ የቤተክርስቲያን ውስጣዊ አስተዳደር ማዘመን ላይም በውስጡ ያሉትን አካላት የማስተባበር ስራውን መቀጠል፣

4ኛ) የጥያቀዎቹ ምላሾች በተለይ ቤተ ክርስቲያንቷን ከሚገዳደሯት አካሎች አንፃር ፈረንጆቹ እንደሚሉት  ''የካሮት እና ዱላ'' ፖሊሲ መከተል ።ቤተ ክርስቲያንን የሚገዳድሯት አካሎች በፀሎት እና በልመና የሚመለሱ አይደሉም።በሰላማዊ መንገድ ካሮት እንደሚያስፈልገው ሁሉ ተፅኖ መፍጠርያ ልዩ ልዩ  መንገዶች ማቀድ ያስፈልጋል።ከእዚህ ውስጥ አንዱ ሰልፍ ሊሆን ይችላል።ሰልፍ ግን ባብዛኛው  ትልቅ የተፅኖ መፍጠርያ መንገድ ይሆናል እንጂ ሌሎች ሰላማዊ የተቃውሞ መንገዶች እና የሕግ አገልግሎት ሁሉ የያዘ ጠንካራ አካሎች ያስፈልጋሉ። ይህ አሰራር በተለይ በመንጋ ለሚያስቡ የፅንፍ ኃይሎች ትምህርት ሰጪ በሆነ መንገድ የማስፈፀም አቅሙን ያሳድገዋል፣

5ኛ) ኦርቶዶክሳዊነት ላይ ያጠሉት ጥላዎች  ፅንፍ የያዙ አክራሪ እስልምና ኃይሎች፣ የሉላዊነት (ግሎባላይዜሽን) እና ሌሎች ስጋቶች ዙርያ ጥርት ያለ መረጃ ኮሚቴው መስጠት ወይንም ልዩ የማንቅያ ትምህርቶች እንዲሰጡ መግፋት።

6ኛ) እንቅስቃሴው ዓለም አቀፍ እንቅስቃሴ መልክ እንዲይዝ እና ሁሉን አቃፊ እንዲሆን ማድረግ  እና ከመንግስት የተጠየቁት ምላሾች ከተገኙ በኃላ ኮሚቴው እራሱን ከፍ ወዳለ ደረጃ ማሳደግ እና በአባቶች ቡራኬ ማቆየት  የሚሉት ተጠቃሾች ናቸው። 

ከምዕመናን  ምን ይጠበቃል።  

ምዕመናን ሁለት ቁልፍ ተግባራት ይጠበቅባቸዋል። አንድኛው በሕበረትም ሆነ በግል በየትኛውም ቦታ በሀገር ፍቅር ጉዳይ፣በሀገር አንድነት ጉዳይ ላይ ሁል ጊዜ ቀዳማዊ ተፅኖ ፈጣሪ መሆን እና ከአስተባባሪ ኮሚቴው የሚመጡ መመርያዎችን በማክብበር በህብረት ተፅኖ የመፍጠር አቅሙን ማሳደግ። የሚሉት ተጠቃሾች  ናቸው።

አዎን! ኦርቶዶክሳዊው ማኅበረሰብ ላይመለስ ተነስቷል።ለኦርቶዶክሳዊውም ከኢትዮጵያዊነት ውጪ ሌላ አጀንዳ የለም። ኦርቶዶክሳዊው ማህበረሰብ ኢትዮጵያዊነቱን ደግሞ ማንም እንዲነጥቀው ዕድል መስጠት የለበትም።የኢትዮጵያን ዕጣ ከሚወስኑት የሀገሪቱ ባለመብት ዜጎች ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ኦርቶዶክሳውያንን ዘሎ ምንም አይነት ፖሊሲ መቅረፅ እንደማይቻል አሁንም ትምህርት ሰጪው መሆን ያለበት ኦርቶዶሳዊው ወጣት ነው።  በኢትዮጵያ ፖለቲካ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ሕይወት ውስጥ  ሁሉ የኦርቶዶክሱ   ማኅበረሰብ መብቱን የማስከበር ሚና በከፍተኛ ደረጃ የማሳደግ ስራው አሁንም የሁሉም ባለ ድርሻ አካል ግዴታ መሆኑን ማወቅ አለብን።ስለሆነም የሰላማዊው ሰልፍ ወደ ጥቅምት 30/2012 መራዘም ከላይ የተጠቀሱትን ተባራት ከማከአወን ባለፈ የመደራደር አቅምን የሚያሳድግ ዕድል ከመስጠቱ በላይ አደረጃጀቱ እስከ ገጠር ድረስ የመድረስ እና ተፅኖ የመፍጠር አቅም ማሳደግ አስፈላጊ ነው። 

አንተውም ከቶ! (ቪድዮ)
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ከመስከረም 4 ቀን በአዲስ አበባ የተጠራው የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ
++++++++++

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሐገረ ስብከት ካህናት፣ ሰባኪያን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ኅብረት፣ የመንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት ና ምሩቃን እና የመንፈሳዊ ማኅበራት ተወካዮች እና በመስከረም 4 ቀን በዲስ አበባ ሊካሄድ የታሰበው ሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪዎች ሰላማዊ ሰልፉን አስመልክቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
በአገራት የታሪክ ግንባታ ላይ የሃይማኖት የተቋማት አስተዋጽኦ ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል፡፡ በተለይ ተቋማቱ ከአገራቱ እድሜ የማይተናነስ የዘመን ርዝማኔ ሲኖራቸው ከሚተረከው የአገሪቱ ታሪክ ላይ የእነርሱ እጅ ያልገባበትን፣ አሻራቸው ያላረፈበትን ዘርፍ ለይቶ ለማውጣት እስኪከብድ ድረስ የአገር ታሪክ እና የሃይማኖት ተቋሙ ታሪክ እንደ ድርና ማግ የተገመደ ሲሆን ይስተዋላል፡፡
በአገራችን በኢትዮጵያ ያለውም እውነታ ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ የሌሎቹ እምነቶችና ባህሎች አስተዋጽኦ እንዳለ ሆኖ ኢትዮጵያን ያለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማሰብም ሆነ የወደፊት እጣዋንም በአዎንታዊ መንገድ መተለም ፈጽሞ አይቻልም፡፡ የኢትዮጵያን ታሪክ የቤተ ክርስቲያኗን ስም ሳያነሱ ለመተረክ መሞከር እስከሚያዳግት ድረስ ቤተ ክርስቲያን የአገር የልብ ትርታ ሆና ኖራለች፡፡ በአገራችን ስልጣኔ ላይ ዘርዝሮ ለመጨረስ የሚያዳግት አሻራን አሳርፋለች፡፡
ምእመኗን ሌት ከቀን ስለሳላም በማስተማር እርስ በእርሱ በመከባበር እና በፍቅር ከመኖር አልፎ የሌላውን እምነት እና ባሕል አክብሮ እንዲኖር አድርጋለች፡፡ ትምህርት የመንግስት የፖሊሲ አካል ባልነበረበት ዘመን ትምህርት ሚኒስተር፣ ባህል እና ቱሪዝምን ማሳደግ ቦታ ባለገኝበት ዘመን የባህል እና የቅርስ ጠባቂ ሆናለች፡፡
አገር በተወረረበት ዘመን ጽላቷን ሳይቀር ተሸክማ ከጦሩ ፊት ተሰልፋለች፡፡ ዓለምና አገር ለሥነ- ጽሑፍ፣ ለሥነ ሥዕል፣ ለኪነ- ጥበብ፣ ለኪነ-ሕንጻ እና መሰል ጥበቦች ባእድ በነበረበት ዘመን ለአገራችንና ለዓለም እስከ ዛሬ የሚመራመርበትን የጥበብ ፋና አብርታለች፡፡ ከግብርና እስከ ሥነ ከዋክብት፣ ከዘመን አቆጣጠር እስከ መድኃኒት ቅመማ፣ ከሕግ ቀረጻ እስከ ደን ልማት፣ ከቤተሰብ አስተዳደር እስከ ስነ-መንግሥት፣ ከዜማ ፈጠራ እስከ ማኅበራዊ እሴት ግንባታ ያላትን ኃብተ ጥበብ ሁሉ ለኢትዮጵያ እያበረከተች ከራሷ ሕልውና በላይ ስለ አገር ኖራለች፡፡ በየትኛውም የታሪክ ዕይታ እና መንገድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ሊደራደር ከመጣ አካል ጋር ለውይይት የተቀመጠችበት ዘመን የለም፡፡ እርሷ እየነደደች እና እየከሰመች አገርን አጽንታለች፡፡ ለዚህ ውለታዋ ግን ወሮታ የጠየቀችበት፣ ለዚህ መስዋእትነቷ ዘካሪ የሻተችበት ዘመን የለም፡፡
ይሁንና ወርቅ ላበደረ ጠጠር እንዲሉ ዛሬ ዛሬ በኢትዮጵያ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ጡት የመንከስ ያህል አጠያያቂ ምልክቶች እየታዩ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ በአገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፤ ካህናት እና ምእመናን ተወልደው ባደጉባት ምድር ታርደዋል፣ ያፈሩት ሃብት ንብረትም ሁሉ የእሳት አሊያም የቀማኛ ቀለብ ሆኗል፤ከሕጻን እስከ አረጋዊ፣ ካልጋ ቁራኛ እስከ ነፍሰ ጡር ድረስ ኦርቶዶክሳዊያን አንስቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተደፍረዋል፡፡ መከራ የበረታባቸው ለዘመናት የኖሩበትን ቀየ ለቀው ወደማያውቁት ቦታ ተሰደዋል፡፡ በጠረፉ የኢትዮጵያ ክፍል የተጀመረው ሃይማኖትን መሠረት ያደረገ ጥቃት ወደ መሃል ከተማ በሚያስደንቅ ፍጥነት እየገሰገሰ ይገኛል፡፡
ይህ ሁሉ ሲሆን እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች እና ምእመናን ከዛሬ ነገ ጉዳዮን የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ይፈቱታል በሚል ተስፋ የየመንግስት ተቋሙን በር ስናንኳኳ ቆይተናል፡፡ ቢሆንም ጩኽታችንን በሚፈለገው ፍጥነት የሚሰማ የሚፈታም ሆነ መልስ የሚሰጥ አካል አልታየም፡፡ ከዚህም ሲያልፍ ለሁሉም ችግር ኃይል እና ነውጥ መፍትሔ ተደርጎ በሚወሰድበት በዚህ ዘመን ለሰላም እና ለአገር ባለን ጥልቅ ፍቅር ሕጋዊ ጥያቄ አቅርበን በሕግ ከተሾመው ሕጋዊ አካል ሕጋዊ መፍትሔ መፈለጋችን በሚያሳዝን ትርጉም እየተሰጠው እና ከፍርሃት እየተቆጠረ መሳለቂያ ከመሆን የዘዘለ ጠብ የሚል መፍትሔ ሊመጣ አልቻለም፡፡
በመሆኑም እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ከተማ የምንገኝ ካህናት፣ የሰባኪያን እና ዘመሪያን ኅበረት፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ፣ የመንፈሳዊ ማኅበራት ማኅበራት፣ የወጣቶች እና የጎልማሶች ማኅበራት ኅብረት፤ የነገረ መለኮት ምሩቃን እና የመንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ኅብረት፡ በመስከረም 4 ቀን 2012 ዓ/ም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ጥሪ ማድረጋችን ይታወቃል፡፡
ይህ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ከቀረበበት ማግስት ጀምሮ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ራስ ከሆነው ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጀምሮ፣ በአገርም ይሁን በውጩ ዓለም ያሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች ሁሉ በአንድ ልብና መንፈስ በታላቅ ቁጭት ያሳየውን የመንፈስ ዝግጅት እና ተነሳሽነት በቃላት ሊገልጹት ከሚችሉት በላይ ነበር፡፡ ከብረት የጠነከረው ይህ የኦርቶዶክሳዊያን ኅብረት እና ተነሳሽነት እናቱ ስትታመምበት እያንዳንዱ ኦርቶዶክሳዊ አርፎ እንደማይተኛ እና የትእግስቱን ያህል ቁጣውም ምን ያህል የገዘፈ እንደሆነ ለብዙዎች ትልቅ ትምህርት የሰጠ እንደሆነ ሁሉም የተረዳው እውነታ ነው፡፡
በተጨማሪም ስለ አገር ሰላም፣ ስለ ሕዝቦች አንድነት፣ ፍትሕና እውነተኝነት የሚገዳጋቸው የሌሎች እምነቶች ተከታይ ወንድም አኅቶቻችን ሁሉ ህመማችንን ተጋርተው ከጎናችን እንደሚቆሙ እየገለጹልን ይገኛሉ፡፡
ዛሬ በጋራ መሰለፋችን እና ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ክብር በአንድ መቆማችን በብዙ ልመና ሊከፈቱ ያልቻሉ ጠንካራ በሮችን ለማስከፈት ችሏል፡፡ በዚህም መሠረት አስተባባሪ ኮሚቴው
1. ጳጉሜ 5/ 2011 ዓ.ም ከጠቅላይ ሚኒስተር ጽ/ቤት ተወካይ፣ ከፌድራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር፣ ከአዲስ አበባ ም/ከንቲባ እና ጽ/ቤት ተወካዮች ጋር
2. ጳጉሜን 6/2011 ከኢ.ፌ.ድ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር
3. መስከረም 2/2012 ዓ/ም ከኦሮምያ፣ ከደቡብ፣ ከአማራ፣ ከሶማሌ ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች ጋር በአካል ተገናኝተን ውይይቶችን የጀመርን ሲሆን ከሐረሪ እና ቤኒሻንጉል ክልሎች እና ከድሬዳዋ መስተዳድር ጋር ለውይይት ቀጠሮ ተይዟል፡፡
4. መስከም 2/2012 ዓ/ም ከፌድራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር፣ አዲስ አበባ፣ ኦሮምያ፣ አማራ፣ሱማሌ፣ ቤኒሻንጉል፣ ድሬዳዋ እና ሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽነሮች ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡ በነዚህ ውይይቶችም ከአሥር ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ኮሚቴው ይዞት የተነሳውን እና ቤተ ክርስቲያኗ ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት ለመፍታት በየክልሎቹ ዝርዝር ማስረጃ ቀርቦ ውይይት እንዲደርግባቸው እና ለጥቄዎቹምምላሽ እንዲሰጣቸው እና በቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ ከላይ ከተጠቀሱት የመንግስት አካላት ጋር ውይይት በማድረግ በባለቤትነት ችግሩን ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ .
በመንግስት ጥያቄያችንን ሁሉ ይመልሰዋል የሚል እምነት ባይኖረንም በየደረጃው ያሉ አካላት ቸልታ እና የማናለብኝነት ስሜት ወጥተው ለቤተ ክርስቲያናችን ዘብ ሲቆም መመልከት እንሻለን፣ አገራችን ደጋግመን እንደምለው አንዳንዱ የፈለገውን ከሕግ የተጻረረ ተግባር በተለይ በኦርቶዶክሳዊያን ላይ እየፈጸመ ያለአንዳች ጠያቂ የሚኖርባት ሌላው ደግሞ ስለአገር እና ስለአንድነት በሚወስደው ኃላፊነት የተሞለበት አካሄድ እየተገፋ ከሌሎች ጋር ሲገነባት በኖራት አገር ላይ ባይተዋር ሆኖ የሚሰደድባት አገር መሆኗ ተቋጭቶ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እጁን ያነሳ ሁሉ የሚጠየቅባት፣ ጣቱን የቀሰረው ሁሉ የሚሰበስብባት ለፍትህ የሚተጋ መንግስት ያለባት አገር ስትሆን መመልከት ሕልማችን ነው፡፡
እየጮህን ያለነው የኦርቶዶክሳዊያን ብቻ ሰላም ይከበር ብለን አይደለም፣ የእምነት ነጻነት ሰፍኖ አገራችን በእምነታቸው የተነሳ የተደፉ አንገቶች ቀና ብለው ሁሉም በመከባበበር የሚኖርባት ሰላማዊ አገር ስትሆን ለመመልከት ነው፡፡ ይህ እስኪሆን ድረስ ከራሳችን እምነት ተከታዮች ጎን ብቻ ሳይሆን በእምነታቸው የተነሳ ከሚገፉት ጎን ሁሉ በማስመሰል መንፈስ ሳይሆን ከአያት ቅድም አያቶቻችን በወረስነው ለፍትህ የመወገን መንፈስ አብረን እንቆማለን፡፡ ለዚህ ነው ጉዟችን ኦርቶዶክስን ብቻ ሳይሆን አገርን ጭምር ለመታደግ የታለመ ነው የምንለው፡፡ በመሆኑም ስለሃይማኖታችን እና ሥለአገራችን ሰላም ስንል እነዚህ ሁሉ ጥያቄዎቻችን እንኪመለሱ ድረስ ትግላችንን በሰላማዊ መንገድ እንደምንቀጥል ቃላችን የጸና ነው፡፡
የተከበራችሁ ኦርቶዶክሳያን እና ኦርቶዶክሳዊያት በዚህ መንፈስ እና ዓላማ ተቃኝቶ የተጀመረው የኅብረት ጉዟችን ከገዳም እስከ ከተማ ድረስ ካሉ አባቶች ጋር በመመካከር እና በጸሎታቸው በመታገዝ ከዚህ አድርሰነዋል፡፡ በብዙዎቻችሁ ውስጥ ያለው የመንግስት አካላት ቃል ከመግባት የዘለለ እርምጃ ላይሄዱ ይችላሉ የሚለው ስጋት ግን በእኛም ውስጥ ስላለ፤ ከላይ ያልናቸውን ጥያቄዎቻችንን በቅድመ ሁኔታ ጭምር አቅርበን እስክንወያይ እና የሚመጣውን ተግባራዊ ለውጥ ለመመልከት እስክንበቃ ድረስ ለመስከረም 4 ቀን 2011 ዓ/ም የጠራነውን ሰላማዊ ሰልፍ በሁለት ወራት በመግፋት የተገባልን ቃል የማይተገበር ከሆነ አሊያም የሚያረካ ካልሆነ ለጥቅምት 30 ቀን 2012 ዓ/ም ሰላማዊ ሰልፉ የሚደረግ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
እኛ የዚህ ሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪዎች በሚደረገው በየትኛውም ውይይት ላይ ከራሳችን ፍላጎትም ይሁን አንዳንዶች ከሚሰጉት የፍርሃት መንፈስ በጸዳ ስሜት የቤተ ክርስቲያናችንን እና የእናንተን የእምነቱን ተከታይ ኦርቶዶክሳያን ፍላጎት እና ጥያቄ ብቻ አስቀድመን የምንቆም መሆናችንን በህያው እግዚአብሔር ስም ቃል እየገባን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እውነተኛ ልጆች ሁሉ ያሳያችሁት ተነሳሽነት እና ኅብረት ሳይሸራሸፍ ለችግራችን ሁሉ ቁልፍ መፍትሔ በሆነው ጸሎታችሁ፣ በሃሳባችሁ እና በቻላችሁት ነገር ሁሉ ከጎናችን እንድትቆሙ በእናት ቤተ ክርስቲያን ስም ጥቄያችንን እናቀርባለን፡፡
በዚህ አጋጣሚ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በምናደርገው እና በምናቀርበው ጥያቄ ዙሪያ ከሕዝበ ክርስቲያኑ ጋር የምንመካከርባቸው ሰፋፊ መድረኮችን የምናዘጋጅ እንዲሁም ቢያንስ በአሥራ አምስት ቀን አንድ ጊዜ የተለያዮ መንፈሳዊ እና ሕዝባዊ መገናኛ ብዙሃንን በመጠቀም የእያዳንዱን የውይይት ሂደት፣ውሳኔ፣ውጤት እና ቀጣይ አቅጣጫ ለሕዝብ ይፋ በማድረግ ምእመናን እና የኦርቶዶክሳዊያን ሰላም እና ድኅንነት የሚያስጨንቃቸው አካላት ሁሉ የውይይቱ አካል እንዲሆኑ ለማድረግ የምንጥር መሆናችንን ቃል እንገባለን፡፡
እግዚአብሔር አምላክ የቤተ ክርስቲያናችንን እና የአገራችንን ሰላም ይመልስልን!!!!
መስከረም 4 ቀን በአዲስ አበባ የተጠራው የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ
መስከረም 2 ቀን 2012 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ


Monday, September 9, 2019

ሰበር ዜና - ጅማ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ዛሬ ጥቃት ለመፈፀም ተሞክሯል።የሽብር ጥቃት እየደረሰ የመንግስት ለዘብተኝነት ብዙዎችን አስቆጥቷል።


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች በደረሰባቸው በደል ሳብያ -
  • ለመንግስት አቤት ለማለት የሄዱ ጳጳሳት በቂ ምላሽ ሳያገኙ መመለሳቸው እና ይህንን ተከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ያወጣው መግለጫ በመንግስት ሚድያዎች በሚገባ ሳይተላለፍ ሶስተኛ ቀኑን ማሳለፉ።
  • እራሱን የኦሮምያ ቤተ ክህነት አደራጅ ኮሚቴ  በማለት የሚጠራው ቡድን እንደ ቅዱስ ፓትርያሪኩ እራሱን ሰይሞ የአዲስ ዓመት መልካም ምኞት በኦኤምኤን ቴሌቭዥን ሲያስተላልፍ መታየቱ፣
  • በጅማ በአደባባይ ዛሬ ሰኞ ጳጉሜን 5 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ንዋየ ቅድሳት ለማቃጠል የተደረገው ሙከራ እና ምሽቱን የጅማ ሕዝብ ወጥቶ ቤተ ክርስቲያኑን እየጠበቀ መገኘቱ ሁሉ ከፍተኛ ቁጣ ቀስቅሷል።
ቅዱስ ሲኖዶስ ወቅታዊውን የቤተ ክርስቲያን ሁኔታ ላይ አስቸኳይ ጉባኤ ካካሄደ በኃላ ጳጕሜን 2 ቀን 2011 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በመግለጫው ተራ ቁጥር 4 ላይም  የሚከተለው ጥሪ ለመላው የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ተላልፏል፡፡
“እየደረሰ ያለውን ግፍ እና መከራ በሀገራዊ የኃላፊነት ስሜት ታግሶ እና ችሎ፤ ሞቱ፣ እሥራቱ፣ ዛቻው፣ ስደቱ እና እንግልቱ ሳይበግረው ሀገር በአንድነት እና በፍቅር እንዲሁም በመተሳሰብ እንድትቀጥል ታሪክ የማይረሳው መሥዋዕትነት እየከፈሉ ያሉትን አገልጋይ ካህናት እና መላውን ምእመናንን እንዲሁም ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በአጠቃላይ መላው የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ላሳያችሁት ትዕግስት የተመላበት ሀገራዊ ኃላፊነት ቅዱስ ሲኖዶስ በእጅጉ እያመሰገነ እንደ አሁን ቀደሙ ሁሉ ትዕግስት የተመላበት ሀገራዊ ኃላፊነታችሁ እንደተጠበቀ ኾኖ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ እየደረሰ ያለውን፣ ወደፊትም ሊደርስ የታቀደውን ግፍ እና ጥፋት በአንድነት እና በኅብረት ከእኛ ከመንፈስ ቅዱስ አባቶቻችሁ ጋር በመሰለፍ በጽናት ቤተ ክርስቲያናችሁን እንድትጠብቁ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡”

ቅዱስ ሲኖዶስ በሰጠው መግለጫ መሰረት ኦርቶዶክሳውያን የሀገሪቱን ሕግ አክብረው የደረሰባቸውን ግፍ ለማሳሰብ ለመስከረም 4 ቀን ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ተገቢውን ፈቃድ ጠይቀዋል።የሰልፉ አስተባባሪዎች የአዲስ አበባ አስተዳደርን ለማስፈቀድ በጠየቁት ጥያቄ ላይ እንደ ገለጡት ሰልፉ ሶስት ዓላማዎችን የያዘ ነው።እነርሱም -

1ኛ / በካህናት፣ ምእመናን እና ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት ለመቃወም፣ ለሁሉም አካላት ለማሳወቅ እና እንዲቆም ለመጠየቅ፣
2ኛ/ አጥፊዎች በሕግ እንዲጠይቅ እና በቀጣይም ተመሳሳይ ጥቃት እንዳይደርስ መንግሥት ሕጋዊ ዋስትና እንዲሰጥ፣
3ኛ/ በዚህ ጥቃት መስዋዕትነት ለተቀበሉ አካላት ቋሚ መታሰቢያ እንዲቆም፣ በሃይማኖታቸው ምክንያት የተፈናቀሉ ሰዎች ወደ ነበሩበት እንዲመለሱና ለሚገባው አካል ተገቢው ካሳ እንዲከፈል ለመጠየቅ የሚሉት ናቸው።

የሰልፉ አስተባባሪዎች-  
★ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት፤ 
★ የመንፈሳዊ ኰሌጅ ተማሪዎችና ምሩቃን፤ 
★ በሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን፤ 
★ የወጣቶችና ጎልማሶች ማኅበራት ኅብረት፤
★ የሠለስቱ ምዕት ማኅበራት ኅብረት፤
★ የአእላፋት ድምፅ የካህናትና ምእመናን ተናሥኦት ኅብረት፤
★ የጽዋ ማኅበራት 

ሲሆኑ ሰልፉ ፍፁም ሰላማዊ የማንኛውም የፖለቲካ እንቅስቃሴ ተቀጥላ ያልሆነ፣ ሆኖም ግን በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ የተፈፀሙ የሽብር ድርጊቶች ሁሉ እንዲቆሙ መንግስት ኃላፊነቱን እንዲወጣ የሚያሳስብ ነው። 


በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚደርሰው በደል ለማስቆም መስከረም 4 ቀን የሚደረገው ሰልፍ ዓለም አቀፍ መልክ ይዟል።ቅዱስ ሲኖዶስ ያወጣውን መግለጫ በመደገፍ እና በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ የሚደርሰው በደል መቆም አለበት በሚል በጀርመን እና በስዊድን የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት መግለጫ ያወጡ ሲሆን መስከረም 4 በተመሳሳይ ቀን በሰሜን አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ እና በጀርመንም ሰልፉ እንደሚደረግ ተሰምቷል።በተጨማሪም የኢትዮጵያ ቆንስላ ባለባቸው በሎሳንጀለስ እና ሚኒሶታ ተመሳሳይ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተሰምቷል።

ኦርቶዶክሳውያን ለታወጀባቸው ሽብር በዋናነት ተጠያቂ የሆኑት የፅንፍ የሃይማኖት እና የብሔር ቡድን ተጠያቂ ሲሆን በውስጥ ፅንፈኛ ብሔርተኞች እና የአካባቢው ሽብርተኛ ቡድኖች እንዳሉበት ይጠረጠራል። ዓላማው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ማዳከም እና ከሕዝቡ መነጠል በመቀጠልም ሙሉ በሙሉ ለመምታት መሆኑ በብዙ ማስረጃዎች የተረጋገጠ ነው።

ይህ በእንዲህ እያለ ግን መንግስት አሁንም ተገቢውን ምላሽ ለቤተ ክርስቲያኒቱ አለማድረጉ እና ግልጥ የሆነ የሽብር ሥራ የሚሰሩትን የጦር ሰራዊቱ አስፈላጊውን ፀጥታ የማስከበር ሥራ እንዳይሰራ ተገቢው መመርያ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ አለመሰጠቱ እንደ ትልቅ እንቅፋት ተቆጥሯል። በመሆኑም ቤተክርስቲያኒቱን እና ከሃምሳ ሚልዮን በላይ የሚሆነውን ሕዝብ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ሀገሪቱን አደጋ ላይ የሚጥል አሰራር ከመንግስት እየታየ ነው።

በመሆኑም ኦርቶዶክሳውያን ጉዳዩን በቀላሉ ተመልክተው እጃቸውን አጣጥፈው የሚቀመጡበት ጉዳይ ሳይሆን ከሊቅ እስከ ደቂቅ በሰላማዊ መንገድ ለቤተ ክርስቲያኑ ዘብ መቆም ያለባቸው እጅግ ወሳኝ ወቅት አሁን ነው።



ተዋህዶ  ሃይማኖቴ መዝሙር (ቪድዮ)


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Sunday, September 8, 2019

በዘር የሚያምኑ ሚድያዎች ዕድሉ እስከተሰጣቸው ድረስ የሩዋንዳ ችግር ኢትዮጵያ በር ላይ እንደሆነ ማወቅ አለብን።ኢትዮጵያ ''ሲሬስ'' ችግር ውስጥ ገብታለች:: አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ኦስሎ፣ኖርዌይ የተናገሩት (ጉዳያችን ልዩ ዘገባ -Gudayachn exclusive)


ከጉባኤው ተሳታፊዎች በከፊል 

ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ቅዳሜ ጳጉሜን 2/2011 ዓም አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የቀድሞው አርበኞች ግንቦት 7 ዋና ፀሐፊ በኦስሎ፣ኖርዌይ የምስጋና ዝግጅት ተዘጋጅቶላቸው ነበር።በዝግጅቱ ላይ ቁጥሩ ከፍ ያለ የኖርዌይ ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ የቀድሞው አርበኞች ግንቦት 7 በኖርዌይ ለሚኖሩ እና ባለፉት ዓመታት ለዲሞክራሲ ትግል  አስተዋፅኦ ላደረጉ ኢትዮጵያውያን የምስክር ወረቀት የተሰጠ ሲሆን  የምስክር ወረቀቱን የቀድሞው የድርጅቱ ከፍተኛ አመራር ዶ/ር ሙሉዓለም እና አቶ አንዳርጋቸው ሰጥተዋል።

በዝግጅቱ ላይ አቶ አንዳርጋቸው በቅርቡ ያሳተሙትን ''ትውልድ አይደናገር እኛም እንናገር'' ቅፅ 1 መፅሐፍ ዙርያ ማብራርያ የሰጡ ሲሆን ከመፅሐፉ ጋር ተያይዞ ለተነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ ከመስጠታቸው በላይ በወቅታዊ ጉዳይ ዙርያ ያላቸውን ሃሳብ ለተሰብሳቢዎች አካፍለዋል።በእዚህ ዘገባ ላይ በተለይ በዋናነት  በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተናገሩትን እና በተወሰነ ደረጃ ደግሞ በመፅሐፋቸው ዙርያ ያነሷቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረት ይደረጋል።

ወቅታዊ የኢትዮጵያን ሁኔታ በተመለከተ

አቶ አንዳርጋቸው የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ የገለጡበትን ዓረፍተ ነገር የኢትዮጵያ ጉዳይ ግልጥ ያልሆነ መንገድ ላይ ነው ያለው። የመፍረስ አደጋ ያንዣበባት ለመሆኑ ምክንያቱ ብሔርን መሰረት ያደረገው ህገ መንግስት ነው በሚሉ ዓረፍተ ነገሮች ሲሆን በመቀጠል ወቅታዊ የኢትዮጵያን ሁኔታን በተመለከተ የሚከተሉትን ነጥቦች አንስተዋል።እነርሱም -
  • የማዕከላዊ መንግስት የመምራት ሚና በሌለበት ሁኔታ እና ክልሎች በታጠቀ ኃይል ተጠናክረው እያለ ማንኛውንም ችግር  ለመፍታት አስቸጋሪ ነው።
  • የተረኝነት ስሜት የሚለው ችግር አሁን ቢሰማም ነገ የሚያስበውም እንዳይቀጥል የሚሰራው ሥራ ነው  ወሳኙ።ተረኛ ስሜት ሁሉም ጋር አለ።ኦሮሞው ውስጥ ኦዴፓ የተረኝነት ስሜት የሚያራምድ እንዳለ ሁሉ ዓማራ ውስጥም እንዲሁ አለ።
  • እኔ መቼም አልጋ በአልጋ ላይ ነን ብዬ አላውቅም።እኔ ከእዚህ በፊት እንዳልኩት ለውጡ ትልቁ ስህተቱ በራሱ ኢህአዴግን ይዞ ለለውጥ መነሳቱ በራሱ ስህተት አለው።
  • ትልቁን አጀንዳ ትተን ትንንሾቹ አጀንዳ ላይ ብቻ ከተጠመድን ሳናውቀው ከጠላቶች ጋር እየተባበርን ነው ማለት ነው።
  • ኢትዮጵያ ''ሲሬስ'' ችግር ውስጥ ገብታለች።ከእዚህ በፊትም እንዳስቀመጥኩት በእዚህ የጎጥ ፖለቲካ ከቀጠልን  በፐርሰንት እንዳልኩት 80% አደጋ ውስጥ ስትሆን 20% ነው የመዳን ዕድሏ።
  • የኢትዮጵያ ፈዲራሊዝም ለክልሎች ስልጣን ሰጥቶ ማዕከላዊውን አዳክሟል።ይህ በየትም ዓለም የሌለ ነው።ህንድ ትልቅ የፌድራል አስተዳዳር ያላት ሀገር የክልል አስተዳደሮች መሳርያ የመታጠቅ መብት የላቸውም፣ሌላው ቀርቶ ማዕከላዊ መንግስት የክልል ምክር ቤቶች የወሰኑትን ውሳኔዎች ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት አለው።
  • በዘር የሚያምኑ ሚድያዎች ዕድሉ እስከተሰጣቸው ድረስ የሩዋንዳ ችግር ኢትዮጵያ በር ላይ እንደሆነ ማወቅ አለብን።

  • ኢትዮጵያ ውስጥ ክልሎችን መለያየት እና ሀገር ማድረግ ፈፅሞ አይቻልም።የሚሞክር ካለ ቀጥታ ማባርያ የሌለው ጦርነት ውስጥ ነው የሚገባው።ቼክ እና ስሎቫክ ሲለያዩ በቀጥታ መለያየት የቻሉት ጥርት ያለ ልዩነት ከድንበር ጋር  ስላላቸው ነው።ኢትዮጵያ ውስጥ የተዋሃደ ሕዝብ ነው ያለው።ነገ ተነስቶ አንዱ ክልል ልገንጠል ቢል በማግስቱ ድንበሩ ላይ ያለ ነው ጦርነት የሚከፍቱት።
  • አሁን መሰራት ያለበት ትልቁ ስልታዊ ሥራ ማዕከላዊ መንግስትን ማጠናከር ነው።የታጠቁ የክልል ኃይሎች ትጥቅ መፍታት እና የዘር ፕሮፓጋንዳ የሚነዙ ሚድያዎች መስተካከል አለባቸው።ማዕከላዊ መንግስት ስልጣን በሌለው ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ ምርጫ እና ሌሎች ስራዎች ሁሉ ከባድ ናቸው።
  • ዓማራን በተመለከተ ''ታርጌት'' ሆኗል ወይ? አዎን! ይህንን እኔ ወያኔዎች ውስጥ ቀድሜ የተናገርኩ እኔ ነኝ። 
  • ኢትዮጵያ ውስጥ ዓማራነት ከኢትዮጵያዊነት የሚለይ ነገድ ማውጣት ከባድ ነው።አማርኛ በራሱ ያሰባሰበው ማኅበረሰብ እንጂ ወደ ነገድ አደገ ማለት አይቻልም።ይህ ነው ኢትዮጵያን እስካሁን እንደ ኢትዮጵያ ሆና ፀንታ እንድትቆም ያደረጋት።
  • ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚባለው ቢያንስ ከሁለት ብሔር የወጣ ውሁዱ ኢትዮጵያዊ እስከ 40% መድረሱ ነው የሚነገረው እና ኢትዮጵያዊነትን ትተን ወዴት ነው የምንሄደው?


ለአቶ አንዳርጋቸው ስጦታ ሲበረከትላቸው 

ትውልድ አይደናገር እኛም እንናገር በተሰኘው መፅሐፍ በተመለከተ የሚከተለውን ብለዋል -


  • መፅሐፉን እንድፅፍ ያነሳሳኝ ከ1966 ዓም ጀምሮ የተንሳው እንቅስቃሴ መሰረቱ ምን እንደሆነ ለመግለጥ ነው ከ1870 የጀመርኩት።
  • መፅሐፉን በተመለከተ የሚነሱ ሃሳቦች በትክክል አንብቦ ወጥ የሆነ ሂስ ሳይሆን ብጥስጣሽ  ሃሳቦች ናቸው ያየሁት። ከእዚህ የተገነዘብኩት ብዙዎች መፅሐፉን አላነበቡትም ብዬ ገምቻለሁ።
  • መፅሐፉ ላይ ከተነሱት ሃሳቦች አንዱ ''የአያቶቼ ጥጃ ማሰርያ'' የሚለው አዲስ አበባን በተመለከተ የጠቀስኩት ላይ ሃሳቡን ብዙ ሰው የተገነዘበው አይመስለኝም።እኔ ሃሳቤ አዲስ አበባ የአዲስ አበባ ሆና ሳለ ከተማዋ ላይ የሌለ የይገባኛል ጥያቄ  እና ሌሎች ቃላት የሚያነሳው ከአዲስ አበባ በርቀት ወለጋ ወይንም አርሲ ያሉ ናቸው።እኔ ያልኩት ከተማው ጉዳይ ያገባኛል ለማለት ከሆነ እዚሁ የኖርኩት እኔም የሚመለከተኝ የቅርቡ ሰው አያቶቼ ጥጆች ያሰሩበት እያለሁ የሩቁ ሰው ለምን መለያየት ይፈጥራል ከሚል ነው።ይህ ነው የሃሳቡ ጭብጥ።
  • አዲስ አበባ የሰፋችው በሠራዊት እነርሱን ተከትሎ በመጣው የሴተኛ አዳሪ፣ሰራተኛው ነው የሚለውን ከራሴ ያመጣሁት ከራሴ አይደለም ከራስ ዕምሩ የወሰድኩት ነው።ይህ ሃሳብም በከተማው ባለቤትነት ካነሳችሁ የከተማው ባለቤትነት እና ከተማዋን የገነቡት ዝቅተኛው የከተማው ነዋሪ ነው፣ይህንን ሕዝብ ወዴት ልትገፉት ነው? ለሚለው ጥያቄ ምላሽ እንዲሆን ነው።
  • መፅሐፉን እስከመጨረሻው ያነበበ ሰው የሚረዳው እና እኔም ላንፀባርቀው የሞከርኩት ኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነትን ነው።መፅሐፉን አንብቡት እና ሂስ ብትሰጡ ደስ ይለኛል።መፅሐፉ ላይ ብዙ ጠቃሚ ጉዳዮች አሉበት። የቻይናው ማኦ ሴቱንግ በፃፈው ላይ ከጃፓን ጋር ለመዋጋት እንደ ኢትዮጵያውያን የደፈጣ ውጊያ ማድረግ ከቻልን ብቻ ነው ልናሸንፍ የምንችለው ያለበት እና ሌሎች በርካታ ነጥቦች መፅሐፉ ውስጥ ተካቷል።
በመጨረሻም አቶ አንዳርጋቸው በመርሃግብሩ ከመዘጋቱ በፊት የተዘጋጀላቸው ልዩ ስጦታ ተበርክቶላቸው የመርሃግብሩ ፍፃሜ ሆኗል።



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Friday, September 6, 2019

በኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን ላይ ሰሞኑን የነበረው ሁኔታ ለቤተክርስቲያን የደወል ድምጽ ነው::ወደፊት ምን ይሰራ?


ጉዳያችን GUDAYACHN
ጳጉሜን 1/20119 ዓም (ሴፕቴምበር 7/2019 ዓም)

ያሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከሲኖዶሳዊ እውቅና ውጪ በኦሮምያ ክልል የቤተ ክህነት አደራጅ ኮሚቴ ነን ያሉ በእነ ቀሲስ በላይ የሚመራው ቡድን ቀዳሚ አጀንዳ ሆኖ ሰንብቷል።በሰላሳ ቀናት ውስጥ ምላሽ ይሰጠኝ የሚል የማስፈራርያ መግለጫ የሰጠው ኮሚቴ መግለጫ ከመስጠቱ በፊት መግለጫ ይሰጥበታል በተባለው አዳራሽ (በኦሮምያ የባህል ማዕከል) ወጣቶች ጉዳዩን በመቃወም ተሰብስበው ከሄዱ በኃላ፣ ወጣቶቹን ለመበተን ብቻ መግለጫው ቀርቷል በሚል የማታለያ ንግገር ወጣቶቹ እንዲሄዱ ከተደረገ በኃላ፣ኦኤምኤን  እና አዲስ ቲቪ ወደኃላ ቀርተው መግለጫው እንዲሰጥ መደረጉ ለማወቅ ተችሏል።

መግለጫው ሕጋዊ ሰውነት ያላትን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቀደም ብላ በቅዱስ ሲኖዶስ አማካይነት በኦሮምያ የቤተ ክህነት አደራጅ ኮሚቴ የተባለ አካል እንደማታውቅ አስታውቃ ነበር። ጉዳዩን ተከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ከነሐሴ 30 ጀምሮ በተፈጠረው ቤተክርስቲያንን የማወክ ሙከራ ዙርያ ስብሰባ የተቀመጠ ሲሆን በእዚሁ ዕለት የኦሮምያ ክልል  ምክትል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ተወካይ ሙ/ጥ/ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የተገኙ ሲሆን በቀጣዩ ቀን ጳጉሜን 1 ቀን ብፁዓን አባቶች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ጋር በቤተ ክርስቲያኒቱ ችግሮች ዙርያ ተወያይተዋል።

በኦሮምያ ክልል የተቀጥላ ቤተ ክህነት አደራጆች ጀርባ 


በኦሮምያ ክልል  የተቀጥላ ቤተ ክህነት ለማደራጀት  የተገዳደሩት አካላትን በመደገፍ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እጃቸው ያለበት አካሎች የመንግስት ባለስልጣናት፣የፅንፍ ጎሳ ፖለቲካ አራማጆች፣የአክራሪ እስልምና ተከታይ የሆኑ እና የህወሓት አክትቪስቶች አሉበት።በመሆኑም እነኚህ አካላት በፕሮፓጋንዳ ለቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደር መገዳደር ሽፋን ሲሰጡ ተስተውለዋል።


ከእዚህ በተጨማሪ በቅርቡ የታየው በፅንፈኛ የኦሮሞ ብሄርተኞች እና በህወሓት ቡድን መሃል እንደአገናኝ ሆነው የሚንቀሳቀሱ አካሎች በኦሮምያ የቤተ ክህነት አደራጅ ኮሚቴ እያለ እራሱን የሚጠራውን ቡድን ሲያወድሱ ተስተውሏል። ለምሳሌ የሰሜን አሜሪካ የትግራይ ልማት ማኅበር ሰብሳቢ አቶ አሉላ  በኦኤምኤን ቴሌቭዥን ላይ ቀርቦ ሲናገር  የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ጨምሮ በኢትዮጵያ ያሉት ቤተ እምነቶች ''የደርግ ቤተ እምነቶች ናቸው'' በማለት ሲነቅፍ ተሰምቷል።


ቀጣይ የቤተ ክርስቲያን አደጋዎች

አሁን ባለው ሁኔታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ግልጥ በሆነ አደጋ ላይ እንደሆነች እየታየ ነው።ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ ማደርያ ሆና አደጋ ላይ ነች ማለቱ በራሱ አስቸጋሪ ቢሆንም፣በሰው ሰውኛው የመረዳት አቅም ግን ግልጥ የሆኑ አደጋዎች ከፊቷ ተደቅነዋል።የመጀመርያው አደጋ በኦሮምያ ክልል ቤተ ክርስቲያኒቱን  ለማወክ የሜፈልጉ ቡድኖች  ሙከራ ሲሆን፣ ሁለተኛው  ቤተ ክርስቲያኒቱን በኃይል ለመቆጣጠር የሚደረግ ጥረት ነው።ይህ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለመቆጣጠር የመሞከር ሂደት ከጀርባው ሌላ ኃይል ያለ በማስመሰል እና ተራ ውንብድና አስመስሎ በማይፈልጉት ካህን ላይ ጥቃት ማድረስን ሁሉ ይጨምራል።ባጭሩ ተራ ዱርየዎች በማደራጀት የሚፈልጉትን ለማስፈፀም መሞከርን ሁሉ ይጨምራል ማለት ነው።በእዚህ ሂደት ውስጥ ግን መንግስት በአግባቡ መቆጣጠር ካልቻለ የቤተ ክርስቲያን ጉዳት ብቻ ሳይሆን የሚከተለው የሰው እና የንብረት መጥፋትም ሁሉ ሊያስከትል ይችላል። ለእዚህ ደግሞ ዋናው ምክንያት የታችኛው የመንግስት መዋቅር ተገቢ ጥበቃ ለቤተ ክርስቲያን እያደረገ አለመሆኑ ነው።

ወደፊት ለችግሩ መፍትሔነት ምን ይሰራ?


የሚከታተሉት ዋና ዋና ተግባራት መሰራት የሚገቡ ስራዎች ቢሆኑ ተገቢ ይመስለኛል። እነርሱም  -


ቤተ ክርስቲያን 


  • በፍጥነት ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ልዕልናዋን መልሳ ማስከበር።በሀገር ውስጥ በራሷ መርሃግብር በመሄድ ሃገራዊ የእርቅ ፣የሰላም እና የልማት መርሃግብሮች እያዘጋጀች መሄድ ይኖርባታል፣ለምሳሌ በትግራይ ሕዝብ እና በዓማራ መካከል ሕዝብ ለሕዝብ የማገናኝት ሥራ፣የፀጥታ አደጋ ይኖርባቸዋል በተባሉ ቦታዎች ቀድማ በመገኘት፣
  • ለእዚህም ውስጣዊ አስተዳደሯን በአጭር ጊዜ ማዘመን፣
  • በቤተ ክርስትትያንቱ የገንዘብ ብክነት የሚጠየቁ ሰዎች በቤተክርስቲያኒቱ ፍትህ መንፈሳዊ እና በቤተ ክርስቲያኒቱ ስርዓት መሰረት ብይን እየሰጠች ከቦታቸው እያነሳች ውስጧን ማስተካከል እና በሁሉም የአገልግሎት ክፍሎቿ አቅም ያለው የሰው ኃይል ማግኘት፣
  • ብቃት ያለው የሚድያ አገልግሎት እንዲኖራት ማድረግ፣
  • የውጭ ግንኙነቷን ማሳደግ ለምሳሌ ከእህት አብያተ ክርስቲያናት ጋር፣
  • ሀገር አቀፍ የወጣቶች መርሃ ግብር በብዛት ማዘጋጀት 
  • በማኅበራዊ ዘርፍ አገልግሎቷን ማስፋት፣
ከምእመናን ከሚጠበቁት ውስጥ 
  • ምእመናን ከመቸውም ጊዜ በበለጠ  በየትኛውም የቤተክርስትያኒቱ ጉዳይ መከታተል ፣
  • በቤተ ክርስቲያን እና ልጆቹ ላይ ምንም አይነት የማስፈራርያ አደጋ ቢፈፀም በፅናት ከቤተ ክርስቲያን  ጋር መቆም እና መመከት፣
  •  ምዕመናን ከፖለቲካ ጉዳይ ራሳቸውን ማራቅ አቁመው በብዛት እና በጥራት ወደ ፖለቲካው ዓለም ገብተው ሀገራቸውን የመምራት እና ኃላፊነት የመውሰድ እንቅስቃሴ ማድረግ፣
  • የቤተ ክርስቲያን የሕግ ክፍል  በአዲስ መልክ ማጠናከር እና ጀረጃውን ከፍ  እንዲል ማስድረግ።
የሚሉት ተጠቃሾች ናቸው።

ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ርስቲያንን የማያውቁ ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ ጥላቻ ያለባቸው ግለሰቦች  በኢትዮጵያ የፖለቲካ  የስልጣን ተዋረድ ውስጥ ስልጣን ላይ በብዛት መኖራቸው ቤተ ክርስቲያንን እየጎዳ ለመሆኑ ምንም አሌ የሚባል ጉዳይ የለውም።ሁኔታው ለቤተ ክርስቲያን ደወል ነው።ደውሉን ሰምቶ ቤተ ክርስቲያንን ለማገዝ መነሳት ከምእመናን ይጠበቃል።

የዓለም ማዕበል ጎርፍ 

ጉዳያችን/Gudayachn
ሴፕቴመብር  7/2025 ዓም) 





Sunday, September 1, 2019

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ የሚታየው የመንግስት አያያዝ በኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ጦርነት ሊያስነሳ ይችላል (ጉዳያችን ልዩ እና ወቅታዊ )

 ''ቀሲስ'' በላይ ሐጂ ጃዋር እና ሌሎች የመታሰቢያ ፎቶ 

ጉዳያችን GUDAYACHN
 ነሐሴ 27/2011 ዓም (ሴፕቴምበር 2/2019 ዓም)
======================
በእዚህ ፅሁፍ ስር የሚከተሉትን ርዕሶች ያገኛሉ - 
>>   የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የምስራቅ አፍሪካ እና  
        የመካከለኛው ምስራቅ የኃይል ሚዛን መለኪያ ነች፣
>>    የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በልዩ ልዩ ቋንቋ መቀደስ፣ማስተማር ትከለክላለች? 
>>   በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ የሚታየው የመንግስት አያያዝ በኢትዮጵያ 
        በአጭር ጊዜ ጦርነት ሊያስነሳ ይችላል:: እንዴት ?
>>   ቤተ ክርስቲያኒቱን የናቁ መንግሥታት ''የውሃ ላይ ኩበት'' እና 
>>    መፍትሄው።

         
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ባጭሩ አገላለጥ 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ውስጥ ካለው ሕዝብ ከግማሽ በላይ የሚሆነውን ሕዝብ የያዘች፣ከቤተ መንግስት እስከ ታች የገበሬ መንደር ድረስ መዋቅር ያላት፣በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ እንቅስቃሴ ላይ የቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተፅኖ ያላት፣ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት ህልውና፣መልካም ስም ሁሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ ዘመን የማይሽረው ሚና ሁሉ የያዘች ታላቅ ተቋም ነች። ባለፉት ሠላሳ ዓመታት ውስጥ ደግሞ ቤተ ክርስቲያኒቱ ከደቡብ ኮርያ እስከ ደቡብ አሜሪካ ከአውስትራልያ እስከ ሰሜን አሜሪካ፣ከደቡብ አፍሪካ እስከ ሰሜን የአውሮፓ ጫፍ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት ገዝታ ዓለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን ሆናለች።ከእዚህ በታች ያለው ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያኒቱን ጉዳይ ስናነሳ እነኝህ ሁሉ ጉዳዮች ከግንዛቤ መግባት አለባቸው ማለት ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የምስራቅ አፍሪካ እና የመካከለኛው ምስራቅ የኃይል ሚዛን መለኪያ ነች። 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከአንደኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የኢትዮጵያን የኃይል ሚዛን ብቻ ሳይሆን  የስነ-መንግስት፣የስልጣኔ፣የሰላም እና የጦርነት ሁኔታ ሁሉ የሚወስን ወሳኝ ኃይል ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ አፍሪካም ሆነ ለመካከለኛው ምስራቅ ነበራት፣አሁንም አላት።ይህ አባባል የተጋነነ የሚመስለው ካለ በአንክሮ ከእዚህ በፊት የነበረውን ግንዛቤ እና እውቀት መልሶ ከመፈተሽ ሌላ አማራጭ የለውም። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በአራተኛው ክ/ዘመን ክርስትና ብሔራዊ ኃይማኖት ሆኖ  በታወጀበት በአክሱም ዘመነ መንግስት ንጉስ ኤዛና በሶስት ቋንቋዎች ማለትም በግሪክ፣ሳባዊ እና ግዕዝ ቋንቋዎች አስቀርፆ ባስቀመጠው የታሪክ ማስረጃ ንጉሡ እስከ መሐል አፍሪካ፣እና እስከ ደቡብ የዓረብ ግዛቶች ሁሉ ዘልቆ በሄደባቸው ዘመቻዎች ሁሉ ጉልበቱ ኃይማኖቱ እንደነበረ በገለጠበት ታሪካዊ ማስረጃ  የቤተ ክርስቲያኒቱ ወሳኝ ፖለቲካዊ ኃይል እና ወታደራዊ የበላይነት ከሞራል ልዕልና እስከ መንፈሳዊ ዕምነት መሰረት እንደሆነች ለመረዳት ይቻላል።

''የዘመነ ክርስትና አክሱም ተብሎ የሚታወቀውን ወቅት (ከ4ኛው እስከ 10ኛው ክ/ዘመን) የኢትዮጵያ ስልጣኔ በአሕጉሩ ካሉት ሌሎች ስልጣኔዎች የተለየ ሆኖ እንዲያድግ ካበቁት ነገሮች አንዱ ነው'' (የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ከመጀመርያው እስካሁኑ ዘመን፣አንድርዘይ ባርትንስክ እና ዮአና ማንቴል-ኒችኮ፣ ትርጉም ዓለማየሁ አበበ፣2006 ዓም፣ገፅ 21)

የኢትዮጵያ ታሪክ ከአክሱም ዘመነ መንግስት ውድቀት በኃላ፣በ11ኛው ክ/ዘመን የተነሳው የዛግዌ ስርወ መንግስት ከቅዱስ ላልይበላ ድንቅ ስልጣኔ እስከ 16ኛው ክ/ዘመን ድረስ የነበረው የኢትዮጵያ ታሪክ እና በ16ኛው ክ/ዘመን የኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን የመላ አፍሪካን ታሪክ ለመቀየር የተነሳው በቱርክ የታገዘው የመሐመድ (ግራኝ መሐመድ) ዘመቻ ደቡብ ጎንደር ላይ እስኪቀጭ ድረስ ይህ ነው የማይባል ጥፋት አድርሷል። ጦርነቱ ባይቀጭ ኖሮ ዛሬ የምዕራብ፣የምስራቅ እና የመካከለኛው አፍሪካ ሀገሮች በሙሉ የጦርነቱ ገፈት መቅመስ ብቻ ሳይሆን የእስልምና እምነት በውድ ሳይሆን በግድ እንዲጫንባቸው በተደረገ ነበር። ሆኖም ግን የኃይል ሚዛኑን በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ደረጃ ብሎም የመካከለኛው ምሥራቅን  ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ የወረራ ተፅኖ ሁሉ  ሚዛኑን እንዲጠብቅ ያደረገችው በመንፈሳዊም ሆነ በሞራል ልዕልና ቀድማ የተገኘው እና በኢትዮጵያ የነገሱ ነገስታትን በሁለት በኩል የተሳሉ (በመንፈሳዊውም ሆነ በዓለማዊው) ሰይፍ እንዲሆኑ ያበቃች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ነች።ቤተ ክርስቲያኒቱ  ከመንፈሳዊ ተቋምነት ባለፈ የአፍሪካ እና የመካከለኛው ምስራቅ የኃይል ሚዛን መሆኗ ያልገባቸው  መንግሥታት ከ1967 ዓም እስካለንበት ዘመን ድረስ፣ከላይ እንደተገልጠው ለቤተ ክርስቲያኒቱ ተገቢውን ክብር፣ምክር እና ህልውና ተገቢውን ዋጋ ሳይሰጡ ''የውሃ ላይ ኩበት'' እንደሆኑ አልፈዋል።ወደፊትም ተገቢው መስመር ላይ እስካልመጡ ድረስ ይሆናሉ።

ቤተ ክርስቲያኒቱን የናቁ መንግሥታት ''የውሃ ላይ ኩበት'' 


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን በተለይ ላለፉት ግማሽ ክፍለ ዘመን ወደ ቤተ መንግስት የመጡ መንግሥታት ማለትም የደርግ መንግስት፣የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት እና በጥገናዊ ለውጥ ውስጥ የሚገኘው የአሁኑ የኢህአዴግ መንግስታት የቤተ ክርስቲያኒቱን አቅም፣የአለት ድንጋይነት እና ጥልቅ የሆነ ከህዝብ ጋር ያላት ቁርኝት ስላልተረዱት ወንበራቸው ሳይፀና ውኃ ላይ እንደሚንሳፈፍ ኩበት ስንገዋለሉ እየሰነበቱ ከስልጣናቸው አይወድቁ አወዳደቅ እየወደቁ ታሪካቸው እንደ ''ምናምንቴ'' ታሪክ ለወቅ ሳይበቃ እንደቀሩ እና እንደሚቀሩ  በግልጥ የታየ እና የሚታይ እውነታ ነው።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ የሚታየው የመንግስት አያያዝ በኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ጦርነት ሊያስነሳ ይችላል:: እንዴት ?

መጋቢት 24/2010 ዓም የኢህአዴግ መንግስት በኢትዮጵያ ጥገናዊ ለውጥ ለማምጣት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይን በመሰየም ካስታወቅ በኃላ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አንድ ወሳኝ ተግባር  በጠቅላይ ሚንስትሩ እና በአስተዳደራቸው  ተወስዷል።እርሱም ከ1984 ዓም በኃላ በስደት የሚገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ፓትርያርክ  ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ወደ መንበረ ጵጵስናቸው እንዲመለሱ እና የተሰደዱ አባቶች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ በውጤቱም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አንድ ቅዱስ ሲኖዶስ እንዲኖራት መደረጉ  ነው።ይህ ማለት ግን በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ የሚገኙ አባቶች ቀደም ብለው ለእርቅ የሄዱባቸው  በርካታ ሂደቶች በህወሓት በተለይ በአቦይ ስብሐት የግል ጣልቃ ገብነት ሳይቀር መደናቀፉ ሳይዘነጋ ነው። 

ከእዚህ በተለየ ግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላለፉት ሃያ ዘጠኝ ዓመት እና ለውጡ ከተጀመረበት ከ2010 ዓም አጋማሽ ጀምሮ ከፍተኛ መከራ በቤተ ክርስቲያኒቱ ምዕመናን ፣ካህናት እና ህንፃ ቤተ ክርስቲያን ላይ ሳይቀር  ሆን ተብሎ የማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶ ቆይቷል።እነኝህን ጥፋቶች ደግሞ መንግስት ከመከላከል ይልቅ በአንድአንድ ቦታዎች ላይ የሚገኙ የመንግስት ባለስልጣናት በቀጥታ ተሳታፊ ሆነው መገኘታቸው እና በማዕከላዊ መንግስትም ምንም አይነት የማረምም ሆነ የሕግ ማስከበር ሥራ አለመታየቱ  በመንግስት ላይ ከፍተኛ ጥርጣሬ እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል።

ይህ በእንዲህ እያለ ባሳለፍነው ሳምንት ውስጥ ቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ እጅግ አደገኛ የማናጋት ሙከራ በስልጣን ላይ ባለው የኢህአዴግ/ኦዴፓ ባለስልጣናት እና ፅንፈኛ የአክራሪ ኃይሎች ጥምረት ተጀምሯል።ጉዳዩ አደገኛ የሚያደርገው በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይሆን በምስራቃውያን አብያተ ክርስቲያናት  ሁሉ ጥብቅ የሆነውን የተዋረድ እና ወጥ የአስተዳደር መስመር ( Eastern Orthodox Church Hierarchy) በተፃረረ መስመር ማንም ያልደፈረውን አደገኛ መንገድ በተከተለ መልክ ''የኦሮምያ ቤተ ክህነት አደራጅ ኮሚቴ'' በሚል እራሱን ያደራጀ ቡድን ቀሲስ በላይ የተባሉ ''ካህን'' ይዞ የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅርንም ሆነ ማናቸውንም ጉዳይ  የማውጣት እና የማፅደቅ ስልጣን ያለውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ቅዱስ ሲኖዶስ ስልጣን በመጋፋት መግለጫ  ነሐሴ 26/2011 ዓም በይፋ መግለጫ መስጠቱ ነው።ይህ ቡድን መግለጫውን ከመስጠቱ በፊት የቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ አካል ቅዱስ ሲኖዶስ ይህ ቡድን የማይታወቅ መሆኑን እና በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም መናገር እንደሌለበት በይፋ መግለጫ መስጠቷ ይታወቃል። ሆኖም ሕጋዊ ሰውነት ያላት ቤተ ክርስቲያን ቡድኑን አላውቀውም ብላ እየተናገረች ቡድኑ መግለጫ ሲሰጥ መንግስት ጥበቃ ከማድረግ አልፎ በኦሮምያ የባህል አዳራሽ መግለጫው እንዲሰጥ ማድረጉ  መንግስት እጁ እንዳለበት በግልጥ የሚያመላክት ነው።መንግስት እጄ የለበትም ካለ ለተሰራው ስህተት ይቅርታ ጠይቆ እና  ስህተቱን የማረምያ ጊዜውን ተጠቅሞ  ማስተካከል አለበት።

በቀሲስ በላይ እንደሚመራ የምናገረው ቡድን ውስጥ የተሰበሰቡ ''ካህናት'' በሚል ስም ሲሰባሰቡ የሰሩት መሰረታዊ ስህተት ከማተኮር በፊት ቡድኑ ለማስመሰል ''ሲኖዶስ በአንድ ሲኖዶስ ስር ነን፣የምንፈልገው ከእዚህ በፊት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የመንግስትን የአስተዳደር መስመር ተቀትላ የሀገረ ስብከት መዋቅሯን ታስተካክል ነበር እና አሁንም የኦሮምያ ቤተ ክህነት ያስፈልጋል ይህንን መዋቅር ደግሞ በ30 ቀን ውስጥ ካልተፈጠረልን የራሳችንን መዋቅር እንፈጥራለን'' የሚል ድፍረት፣ዕብሪት እና ማን አለብኝነት የተሞላበት  መግለጫ አውጥቷል።መግለጫውን የኢትዮጵያ ቴሌቭዥንም ሆነ የመንግስት ሚድያዎች አላረገቡትም ብቻ ሳይሆን በመግለጫው ፊት የሚታየው ሁለቱም የኦዴፓ ቴሌቭዥን እና የሀጂ ጃዋር  ቴሌቭዥን መናገርያዎች ብቻ መሆኑ ጉዳዩ በአንድ ስብስብ ውስጥ ያሉ የፅንፍ ኃይሎች ሥራ መሆኑን በትክክል  የሚያሳይ ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን እንዲያፈርስ ተልኮ የተሰጠው ቡድን መሰረታዊ ተቃርኖ ከክርስትና ከራሱ  ጋር ነው።ክርስትና የጎጥ አሰስላለፍ የሚያስቀድም ሃይማኖት አይደለም።ክርስቶስ አሕዛብን ከአይሁድ፣ምሥራቅን ከምዕራብ ሰሜንን ከደቡብ ሳይለይ ለሁሉም ራሱን ሰጥቶ ከሲኦል የሰውን ልጅ ሲያድን የእዚህ አካባቢ ሕዝብ ከሌላው በላይ ክርስትና ይቀበል ብሎ አይደለም።የቄስ በላይ እና ቡድናቸው መሰረታዊ ስህተት  አስተዳደራዊ መሻሻሎች ላይ ጥይቄ ያለው አካል የቤተ ክህነቱ አስተዳደር እንዲሻሻል አብረን እንጠይቅ ብቻ ሳይሆን አይደለም በኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ያለው መዋቅሯ እንዲስተካከል  በቅዱስ ሲኖዶስ መስመር በኩል መጠየቅ ሲገባው የኦሮምያ ክርስቲያኖች የኔን መንደር ልጆች ብቻ ለማፅደቅ እሰራለሁ የሚለው ዕሳቤ በራሱ ትልቅ ስህተት እና ጎጠኛ የመከፋፈል ተግባር ነው።ከእዚህ በተጨማሪ ግን  የቡድኑን መሰረታዊ ስህተት በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ በአገልግሎት ላይ የሚገኙት  መምህር ቀሲስ ታደሰ ወርቁ እንደሚከተለው የሂደቱንም ሆነ የድርጊቱን ህገ ወጥነት በማኅበራዊ ሚድያ  ገፃቸው ይገልጣሉ። 
''ነሐሴ 26 ቀን 2011 ዓ.ም በኦሮሞ ባሕል ማዕከል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ስም የሚካሔደው መርሐ ግብር÷ የኦሮሚያ ‹‹ቤተ ክህነትን›› የማወጅ መርሐ ግብር እንጂ÷ የጋዜጣዊ መግለጫ መርሐ ግብር አይደለም፡፡ ለዚህ የዕወጃ መርሐ ግብር ከፍተኛ የገንዘብ እና የፕሮፖጋንዳ ድጋፍ ከአሮሞ ጽንፈኛ ፖለቲከኞች እንደተደረገም መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡ ገንዘቡም የሚውለው በዋነኝነት ከአዲስ አበባ ዙሪያ ለሚመጡ ተመልማይ ተሳታፌዎች ለአበልና ለመጓጓዣ ወጪዎች እንደሆነም እየተነገረ ነው፡፡ እንዲህ ዐይነቱን ግብራዊ ተጓዳኝነት ስንመለከት÷ ራሱን የኦሮሚያ ‹‹ቤተ ክህነት›› አደራጅ ኮሚቴ ብሎ የሚጠራው ስብስብ አጀንዳው ‹‹በቋንቋችን እንማር›› ሳይሆን÷ጽንፋዊነት በወለደው መለካዊነት(በቅጥረኝነት) በሀገራዊና በቤተ ክርስቲያናዊ አንድነት ላይ ስንጥቅ መፍጠር መሆኑን እንረዳለን፡፡
ለዚህም ይመስላል ሦስት ነገሮችን የደፈሩት፡፡ የመጀመሪያው ከቤተ ክርስቲያኒቱ ይሁንታ ውጭ ስሟን መጠቀማቸው ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ሰውነት ያላት የእምነት ተቋም ናት፡፡ ይህ ሕጋዊ ሰውነቷ ደግሞ ስሟንም ይጨምራል፡፡በዚህ መሠረት ያለ እርሷ ይሁንታ ስሟን መጠቀም ወንጀል ነው፡፡ ድርጊቱም ሕጋዊ ሰውነትነቷን በሕገ ወጥነት መጋፋት ነው፡፡ ሁለተኛው ወንጀል መሆኑን እያወቁ አርማዋንና ስሟን በመጠቀም ማኅተም ማስቀረጻቸው ነው፡፡ በሀገራችን ሕግ መሠረት የአንድን ተቋም አርማና ስም ተጠቅሞ ማኀተም ማስቀረጽ ወንጀል ነው፡፡ስብስቡ ይህን ወንጅል ፈጽሟል፡፡ ሦስተኛው የቤተ ክርስቲያንን የማኅተም ቀረጸ አሠራርና ሕግን መተላለፋቸው ነው፡፡ በሕገ ቤተ ክርስቲያን መሠረት ማኅተም የማስቀረጽ ሥልጣን የተሰጠው ለትንሣኤ ማተሚያ ድርጅት ብቻ ሲሆን፤ማኅተም የመቅረጽ ሥልጣን ደግሞ የተሰጠው ለትንሣኤ ዘጉባዔ ማተሚያ ቤት ብቻ ነው፡፡ ሕገ ቤተ ክርስቲያን እንደሚደነግገው በቤተ ክርስቲያኒቱ ያሉ ተቋማት ሁሉ ማኅተም ለማሰቅረጽ ሲፈልጉ÷የሚቅረጸውን ማኅተም በትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት በኩል ለትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት ይልኩና ማተሚያ ቤቱም ቀርጾ ማኅተሙን ለአሳተሚ ድርጅቱ ይመልሳል፡፡ እንዲቀረጽላቸው የጠየቁ አካላትም አስፈላጊውን ክፍያ ፈጽመው ማኅተማቸውን ከማሰተሚያ ድርጅቱ እንዲወስዱ ይደረጋል፡፡ከዚህ አኳያ ስብስቡ ይህን የቤተ ክርስቲያናችን የማኅተም አቅራረጽ ሕግ በመተላለፍ ማኅተም አስቀርጾ ተገኘቷል፡፡ ሁለቱም የቤተ ክርስቲያን ተቋማት(አሳታሚ ድርጅቱና ማተሚያ ቤቱ) የስብስቡን ማኅተም እንደማያውቁ ተረጋግጧል፡፡ ይህ ደግሞ ሌላ ወንጀል ነው፡፡
ራሱን የኦሮሚያ ‹‹ቤተ ክህነት›› አደራጅ ኮሚቴ ብሎ የሚጠራው ስብስብ÷ ከቤተ ክርስቲያናችን የማኅተም አቀራረጽ ሕግና አሠራር ውጭ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ስም ማኅተም አስቀርጾ ተገኘቷል፡፡ማኅተሙም በትንሣኤ ዘጉባዔ ማተሚያ ቤት እንዳልተቀረጸ ተረጋግጧል፡፡ እንዲህ መሆኑ ደግሞ ሌላ ጥያቄ እንድናነሳ ያደርገናል፡፡ ማኅተሙ በምንድ ፈቃድና የት ተቀረጸ ? የሚለው ነው፡፡ ምክንያቱም በሀገሪቱ ሕግ መሠረት ማኅተም ለማስቀረጽም ሆነ ለመቅረጽ ሕጋዊ ሰውነትን ገንዘብ ማድረግ ይጠይቃል፡፡ የሕግ ሰውነትን ለማግኘት ደግሞ በዋነኝነት ሁለት አማራጮች አሉ፡፡አንደኛው በሕግ ሥልጣን በተሰጠው መንግሥታዊ ተቋም ተመዝግቦ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ይዞ መገኘት ነው፡፡ ሁለተኛው በሕግ ሰውነት በአለው ሕጋዊ ተቋም ሥር ተደራጅቶ ሕጋዊና መዋቅራዊ ዕውቅና ማግኘት ነው፡፡ ይህ ስብስብ ደግሞ ሁለቱንም የሕጋዊ ሰውነት አማራጮችን አሟልቶ አይገኝም፡፡ ወይም ራሱን የቻለ ሕጋዊ ተቋም ሆኖ በመንግሥት አልተመዘገበም፡፡ አሊያም ደግሞ ሕጋዊ ሰውነት ካላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊና መዋቅራዊ ዕውቅና አለገኘም፡፡ከዚህ አንጻር ስብስቡ በሕግ ፊት ሕገ ወጥ ከመሆኑም በላይ÷ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም ወንጅል እየፈጸም ሰለሚገኘ ተጠያቂ ሊሆን ይገባል፡፡
በዚህ መሠረት ኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚተዳደረው በኦሮሞ ባሕል ማዕከል÷ ምንም ዐይነት ሕጋዊ ሰውነት የሌለው ስብስብ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም መርሐ ግብር ለማካሔድ ሕጋዊ መሠረት የለውም፡፡ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥትም ሆነ የኦሮሞ ባሕል ማዕከል አስተዳደር ያለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ይሁንታ ለሕገ ውጡ ስብስብ መርሐ ግብር ማካሔጃ አዳራሽ የመፍቀድ ሕጋዊ ሥልጣን የለውም፡፡ ‹‹ መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፤›› የሚለውን ሕገ መንግስታዊ ጥሰትንም ያስከትላል፡፡ በብሔር ተዛምዶነት የሚፈጽም አድሏዊነትም ይሆናል፡፡ ስብስቡም በሌላ ስም መስብሰብ መብቱ ነው፡፡በዚሁ አግባብ ማዕከሉም አዳራሽ መስጠት መብቱ ነው፡፡ ያለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ይሁንታ÷ በስሟ መርሐ ግብር ለማካሔድ መጠየቅም ሆነ መፍቀድ ግን ወንጀል ነው፡፡'' የመምህር ቀሲስ ታደሰ ወርቁ ፅሁፍ መጨረሻ።
ከላይ በመምህር ቀሲስ ታደሰ ወርቁ እንደተገልጠው ጉዳዩ ህገወጥ የሆነው በቡድኑ ብቻ ሳይሆን የቡድኑ ተባባሪ የሆኑ በመንግስት መዋቅር ውስጥ ያሉ ሁሉ ለመሆናቸው የኦሮምያ የባህል ማዕከልን መጥቀስ ይቻላል። ይህ ሁኔታ ወዴት ያመራል? ባጭሩ ካለምንም ማጋነን ኢትዮጵያን ወደ አጭር ጊዜ ጦርነት ይመራታል።ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? ለሚሆነው ባጭሩ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ አሰላለፍ ያሃይል ሚዛኖች እና የቤተ ክርስቲያኒቱ ታላቅ ማኅበራዊ መሰረት መመልከት በቂ ነው።
የኢትዮጵያ የወቅቱ ፖለቲካ በተለያዩ የብሔር ኃይሎች ውጥረት የሚታይበት ብቻ ሳይሆን ፈጣን ግጭት የሚፈልጉ ኃይሎች በከፍተኛ ደረጃ በውስጥም ሆነ በውጭ አሰፍስፈው የሚፈልጉበት አደገኛ ወቅት ነው። በውስጥ የዓማራ ብሔር ገንግኖ እንዲወጣ ከታች ገበሬው እስከ ምሁሩ ድረስ አሁን ያለው መንግስት  ''ፀረ ኦርቶዶክስ፣በፅንፈኛ የእስልምና እና የኦሮሞ አክራሪዎች የሚመራ'' የሚለው አባባል በከፍተኛ ደረጃ  ከመሰራጨቱ የተነሳ ባብዛኛው የታጠቀው የእዚህ አካባቢ ሕዝብ ይህንን አባባል የሚያረጋግጥለት የበለጠ መረጃ ማለትም እንደ እዚህ ሳምንቱ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን የመክፈል ተግባር በመንግስታዊ አካላት ጭምር እየተሰራ መሆኑ እንደተሰማ በቀጥታ ጦርነት ይከፍታል።በየቦታው አለመረጋጋት እንደ ሰደድ እሳት ይነሳል።
በሌላ በኩል በለውጡ ያልተደሰተው የህወሓት አመራር ይህንን የኦርቶዶክስ የመከፈል ሂደት የሚያቀጣጥል አዝማምያ እየታየበት ነው።በሰሜን አሜሪካ የትግራይ ልማት ማኅበር ሰብሳቢ እና የህወሓት አክቲቪስት  አሉላ ሰለሞን በማኅበራዊ ድረ ገፅ ላይ በአለፈው ሳምንት በለቀቀው ፅሁፍ የኦሮምያ ቤተ ክህነት መመስረት ጥያቄ ላይ  መልካም ምኞቱን ገልጦ፣ትግራይም ተመሳሳይ መስመር በቅርቡ ትከተላለች ብሏል። እዚህ ላይ የስልጣን ጥመኞች እና ጎጠኛ ፖለቲካ አራማጆች እንዲሁም ዓለም አቀፍ የፅንፍ ፖለቲካ አራማጆች ከስልጣናቸው በላይ ስለማይታያቸው አይሳካላቸውም እንጂ ቤተ ክርስቲያኒቱ ብትወድም ጉዳያቸው አይደለም።
እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት ዋናው ቁምነገር በኦሮምያ ስም የተነሳው ቡድን የኦሮምያን ሕዝብ የማይወክል ነገር ግን ዓላማው በክልሉ ያሉትን ምዕመናን እና አብያተ ክርስቲያናት ለማገት የሚንቀሳቀስ አካል መሆኑ ነው። ይህ ሁኔታ ደግሞ በራሱ በኦሮምያ ውስጥም ከፍተኛ ጦርነት መቀስቀሱ የማይቀር ነው።ምክንያቱም በኦሮምያ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በኦዴፓ በራሱ ውስጥም የፅንፍ ኃይሉ የፖለቲካ ሥልጣንንም ሆነ አብያተ ክርስቲያናትን እንዲቆጣጠር  የማይፈልጉ ከ90% በላይ ሲሆኑ ጥቂቶች ፅንፈኞች በመደራጀታቸው እና የመንግስት ቢሮክራሲን በመቆጣጠራቸው ብቻ ድምፃቸው ስሰማ ይታያል። ቀሲስ በላይ በ2002 በተጭበረበረ የፓርላማ ምርጫ የፓርላማ ተወካይ የሆኑበት እና በፕሮፌሰር መርጋ የሚመራው አንድም ተአማኒ ሥራ ያልሰራው የምርጫ ቦርድ አባል የሆኑበት የስራ ሂደት ሁሉ በአግባቡ እንዲመረመር ወቅቱ የግድ ይላል
የኢትዮጵያ ኦርቶድክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚሰራው ደባ በቀጥታ የዶ/ር ዓብይን መንግስት ወደ ጦርነት ውስጥ የተዘፈቀ መንግስት እንደሚያደርገው፣የጦርነቱ አቅጣጫም ከሁሉም አቅጣጫ እንደሚሆን፣ከሀምሳ ሚልዮን በላይ ተከታይ ያላት፣በርካታ የስራ አጥ የሆነ እና በመንፈሳዊ ልዕልና ስሜቱን ገትቶ ለመንግስት  ታዞ እንዲኖር ያገዘችው ቤተ ክርስቲያን በእዚህ አይነት ደረጃ ለመከፋፈል እየተሞከረ ለመሆኑ ማረጋገጫ ከካህናቱ ስሰማ በቀጥታ የየትኛውም ኃይል መሳርያ የመሆን ዕድል አለው። በእዚህ ላይ መንግስት የፅንፈኛ ኃይሎችን የመግታት ሥራ ላይ እና የቤተ ክርስቲያኒቱን ብሔራዊ ህልውና ማስጠበቅ ሲያቅተው የፅንፍ ኃይሎችም የለመዱትን የኃይል ተግባር በቤተ ክርስቲያን ላይ አጠናክረው ይቀጥላሉ። እዚህ ላይ ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምስራቅ የሃይማኖት አክራሪ ኃይሎች ጋር ከሱማሌ እስከ አርሲ  እና የባሌ ቆላማ ቦታዎች ሁሉ ውጥረት ያለባት ሀገር ነች።እነኝህ ሁሉ ኃይሎች የመጀመርያ ኢላማቸው  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ነች። ለእዚህ ነው ቤተ ክርስቲያኒቱን የመጠበቅ እና መብቷን የማክበር አቅም የሌለው መንግስት በጊዜ ስልጣኑን መልቀቁ አዋጪ የሚሆነው።
በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ የሚነሱ የመከፋፈል ተግባሮች ጦርነት የማስነሳት አቅማቸው ከገበሬው ብቻ አይደለም። ከምሁሩ እና ከጦር ሰራዊቱ ጋር ሁሉ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ባለፉት ሰላሳ ዓመታት  ውስጥ ብቻ ከመቶ ሺህ በላይ ከዩንቨርስቲ የተመረቁ ወጣቶቿን በሚገባ በሥርዓቷ  እና በሀገር ፍቅር ስሜት እና ሃገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን ተረድተው እንዲያድጉ አድርጋለች። ይህ ሥራ በእያንዳንዱ ዩንቨርስቲ ውስጥ የተማሩ ምሑራን ላይ የተሰራ የቤተ ክርስቲያኒቱ ትልቅ የክፍለ ዘመኑ ገድል ተብሎ ሊጠራ የሚችል እና ዛሬ ማንም ሊቀለብሰው በማይችለው ደረጃ የሚገኝ ነው። ዛሬ ቤተ ክርስቲያኒቱን ህንፃዋን ማቃጠል ትችል ይሆናል እንጂ በመቶ ሺህ ምሑራን ልቦና ውስጥ እና በሚልዮን የሚቆጠሩ በቤተ ክርስቲያናቸው ፍቅር በነደዱ ምዕመናን ውስጥ ያለችውን ቤተ ክርስቲያን ልታነዳት አትችልም። እነኝህ ልቦች በብሮክራሲው ውስጥ እስከ ጦር ሰራዊቱ ውስጥ አሉ። የቤተ ክርስቲያኒቱን ህልውና ስትፈታተን  የጦርነቱ አድማስ በእዚህ ደረጃ እያሰፋህ እየሄድክ መሆኑን አለመረዳት በራሱ ሌላው የአስተሳሰብ ድክመት ነው። ይህ ሁሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ማለት ኢትዮጵያ ማለት ለመሆኑ ከበቂ ማስረጃ በላይ ነው። የቤተ ክርስቲያኒቱን ቅዱስ ሲኖዶስ ለመንካት ስትሞክር ፀቡ ከህዝብ ጋር ነው።ፀቡ ቀላል ፀብ ቢሆን ጥሩ ነበር።ግን አይሆንም።መንግስት በተደጋጋሚ ሊያስብበት የሚገባው እና ለፅንፈኛ ኃይሎች መንበርከኩን ከቀጠለ በመንግስት መዋቅር ላይ ያለው እምነት የተሟጠጠበት ሕዝብ መብት እንዴት እንደሚከበር እና ፅንፈኛ እንዴት እንደሚንበረከክ በትክክል ለማሳየት ወደ ተግባር ይገባል።


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በልዩ ልዩ ቋንቋ መቀደስ፣ማስተማር ትከለክላለች? 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ለሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ወርዶላቸው ከሰባ ሁለት በላይ ቋንቋ የወረደላቸውን ቀን የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን ብላ የምታከብር እና ሕዝብ በአፍ መፍቻ ቋንቋው መማር፣መቀደስ እና ማምለክ እንዳለበት ታምናለች።የግድ ይህ የተለየ መለኮታዊ ቋንቋ ነው ብላ የምታስተምረው እና ሕዝብ የምታስገድድበት ተግባር የላትም።ስለሆነም የሰው ኃይል እና የገንዘብ አቅም ውሱንነት ካልሆነ በቀር በአፋን ኦሮሞ እና ሌሎች ቋንቋዎች ማስተማር ብቻ ሳይሆን ጳጳሳት እና ካህናት የተለያዩ የቋንቋ ችሎታ እያየች ነው ወደ አህጉረ ስብከት የምታሰማራው።የኦሮምኛ ቅዳሴ መፅሐፍ ጨምሮ የፀሎት መፃህፍትን ከማዘጋጀት አልፋ ከወለጋ እስከ ሐረር ባሉ አጥብያዎች በኦሮምኛ ቅዳሴ ሕዝቡን ማገልገል ከጀመረች ቆይታለች። የእዚህ ፅሁፍ አቅራቢ በአዲስ አበባ ዙርያ ቡራዩ ፀደንያ ማርያም ቤተ ክርስቲያን በኦሮምኛ ቅዳሴ ሲሰጥ በአንድ ንግሥ በዓል ላይ ተገኝቶ ምስክር ከሆነ ብቻ ከአስራ አምስት ዓመት በላይ ሆኖታል። ቤተ ክርስቲያኒቱ በአፋን ኦሮሞ አሳትማ ለምዕመናን አሰራጭታ ከሃያ አመታት በላይ ከምትገለገልባቸው ውስጥ የሚከተሉት ተጠቃሾች ናቸው። እነርሱም - ውዳሴ ማርያም፣ቅዳሴ እግዚእ፣ቅዳሴ ማርያም፣ቅዳሴ ሐዋርያት እና ሌሎች፣ሌሎች የሥርዓት መጻሕፍት፣በርካታ የነገረ ሃይማኖት መጻሕፍት፣በርካታ መንፈሳዊ መዝሙራት ሲኖሩ የቤተ ክርስቲያኒቱ አካል የሆነው የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቭዥን መደበኛ የመንፈሳዊ መርሃ ግብር በአፋን ኦሮሞ ከጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል።ከመስከረም ወር ጀምሮ ማኅበሩ ከሚጀምረው አዲስ የሃያ አራት ሰዓታት ስርጭትም የአፋን ኦሮሞ መርሃግብር አንዱ እና ዋናው ነው።ስለሆነም አሁን የተነሱት ቡድኖች ዓላማ ሌላ መሆኑን በእዚሁ አንፃር መረዳት ይቻላል።

ይህንኑ የቡድኑ ተግባር ቤተ ክርስቲያን የማፍረስ ተግባር መሆኑን የተረዱት እና የወለጋ ፍሬ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ፣ የሰሞኑን የቀሲስ በላይ እና ግብረ አበሮቹ እንቅስቃሴ በመቃወም ሲናገሩ -


" እኔ መጀመሪያ ስሾም የቀደስኩት በኦሮሚኛ ነበር። ብዙ አገልግሎቶችን በኦሮምኛ ነው የምናከናውነው። የነዚህ ሰዎች አላማ ምንድነው ?!! ቅዱስ ሲኖዶስን ማክበር ያስፈልጋል። ከዛ ያፈነገጠ አካሄድ ከባድ መለኮታዊ ቅጣት አለው። እኔ በአንዲት ቤተክርስቲያን ፥ በአንድ ቤተክህነት አምናለው። ከዚህ ውጭ የሚደረግን እንቅስቃሴ ነፍሴን አስይዤ እፋለመዋለው !!! የአባቶቼ አደራ አለብኝና።" ብለዋል።
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል 
መፍትሄው  
መፍትሄው የችግሩ ግልባጭ ነው።አሁን በምንኖርበት ዓለም ማንም የማንንም መብት ጨፍልቆ እንዲኖር ሊፈቀድለት አይገባም።ልዩነትን ማክበር እና ሀገር የጋራ ሃይማኖት የግል የሚለው አባባል ሁሉንም የሚያስታርቅ ነው። ሃይማኖት ምድራዊ ስርዓትን ብቻ የያዘ አይደለም።ሰማያዊ ሕግ እና ስርዓት መሠረትነት ነው የምድር ሕጎቹን የሚመሰርተው። ስለሆነም በሃይማኖት ውስጥ ፍርሃት ፈፅሞ አይታወቅም።በሃይማኖት የመጣ ማናቸውም ምድራዊ ኃይል በእምነቱ ውስጥ ላለው ሁሉ ኢምንት ነው።የአድዋ ጦርነት በወቅቱ ለነበሩ አባቶቻችን የፀረ ቅኝ ግዛት ብቻ አይደለም።ከሞት በኃላ የመኮነን እና የመፅደቅ ጉዳይም ነበረበት። የቅዱስ ጊዮርጊስን ታቦተ ሕግ ይዘው ሲዘምቱ እና ካህናቱን ፍቱን ብለው ወደ ጦርነቱ አውድማ ዘለው ሲገቡ ተዋህዶ እምነታቸውን በካቶሊክ የሚያስቀይር ወታደር እንደመጣ ሁሉ ስላወቁ ነው። በአፄ ሱሱንዮስ ዘመን በአንድ ቀን እስከ ስምንት ሺህ ገበሬ መስዋዕትነት አያምልጥህ! እየተባባለ እየተጠራራ የተሰዋው የእምነት ጉዳይ ስለሆነ ነው።ሃይማኖት የህዝብ ስስ ብልት ነው።ከሰውነት ውስጥ ስስ የሆነው ብልታችን በትንሽ መርፌ ቢነካ ግዙፉን ሰውነት እንደሚያንዘፈዝፈው ሁሉ፣ሃይማኖትም እንዲሁ መላ ሀገር ያንቀጠቅታል። ስለሆነም በመፍትሄነት መንግስት ከሌሎች ስራዎቹ ቀድሞ የሚከተሉትን ቢያደርግ ኢትዮጵያን ከጦርነት መታደግ ይቻላል።
ይሄውም -  
  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ሰውነት ማክበር እና ማናቸውም ተግባር የቤተ ክርስቲያኒቱ ደንብ፣ሕግ እና ስርዓት ከሚያዘው ውጭ በውጫዊ አካል ምንም ነገር እንዳይፈፀም መንግስት ዋስትና መስጠት፣ሕጋዊ እና የፀጥታ ሥራ መስራት ይህንንም በተግባር ለሕዝቡ ማሳየት፣
  • ቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ የተሳሳተ የፅንፍ አመለካከት ያላቸው ባለስልጣናት ሚዛናዊ አስተያየት እንዲኖራቸው የቤተ ክርስቲያኒቱን ማኅበራዊ፣ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ አስተዋፅኦ እንዲረዱ የማድረግ ሥራ በመንግስትም ሆነ በሁሉም አካላት መስራት፣
  • ኢትዮጵያን ለማሳደግ አሁንም ካሉት እድሎች ውስጥ አንዱ እና ዋናው የቤተ ክርስቲያንን ሚና ማጎልበት መሆኑን በልማት አካላት ሁሉ ተገቢው ግንዛቤ መስጠት እና ለቤተ ክርስቲያኒቱም ዕድል መስጠት፣
  • ቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መሻሻል ሲኖዶሳዊ በሆነ መንገድ ብቻ እንዲፈፀም፣ይህ እንዲሆን መንግስት በበጎ ጎኑ ግፊት ማድረግ አለበት።ከእዚህ በተጨማሪ የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደራዊ መሻሻል ሲከናወኑ ከቤተ ክርስቲያኒቱ የገንዘብ ጥቅም ሲያገኙ የነበሩ የትንኮሳ ሥራ እንዳይሰሩ መንግስት በቂ ጥበቃ እና የሕግ ከለላ መስጠት፣
  • የቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር ከተሻሻለ በኃላ ቤተ ክርስቲያንን አንዷ እና ዋናዋ የልማት አጋር አድርጎ በሀገሪቱ ሕግ፣ፖለቲካ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ጉዳይ ላይ ተሳታፊ እንድትሆን ሁኔታዎችን ማመቻቸት። ይህ ጉዳይ በሃይማኖት የለሹ የደርግ ዘመን ሳይቀር የቤተ ክርስቲያኒቱን ሚና ተረድቶ በወቅቱ በነበረው ሸንጎ (ፓርላማ) ቅዱስ ፓትርያሪኩ እንዲገኙ ያደርግ ነበር።ይህ ጉዳይ አሁንም በብዙ ሀገሮች የሚደረግ ነው። ዋናው የልማት አጋር ትቶ ኢትዮጵያን አለማለሁ ማለት ከንቱ ልፋት ነው። ለምሳሌ በመንገድ ላይ የሚለምኑ ዜጎችን ጉዳይ እፈታለሁ ብሎ የአዲስ አበባ መስተዳድር ሲነሳ ለዘመናት በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ድሆችን አስጠልላ መግባ የምታሳድረው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ያማከረ የለም።ቤተ ክርስቲያኒቱ ግን የማኅበራዊ ዋስትና  በሺህ ለሚቆጠሩ ነዳያን በመስጠቷ ምክንያት ከተሞች ከከፍተኛ የፀጥታ ችግር መዳናቸውን መንግስት ራሱ ረስቶታል። ቤተ ክርስቲያን ግን ኃላፊነቷን እየተወጣች ነው።አስተዳደራዊ መዋቅሯ ቢስተካከል ደግሞ ለበርካታ የመንግስት ችግሮች መፍትሄው አላት።
  • የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በአንዳንድ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገሮች እና የሉላዊነት አቀንቃኝ ሀገሮች ጭምር እንደ ስጋት ስለምትታይ በከፍተኛ በጀት ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማጥፋት ዓለም አቀፋዊ ሴራ መኖሩን መንግስት መረዳት አለበት።ይህ ጉዳይ በተለይ አሁን ካለንበት የሱማሌ እና በኤርትራ ቆላማ አካባቢዎች ከሚንቀሳቀሱ የአክራሪ እስልምና ኃይሎች አንፃር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚነሱ የማናጋት ስራዎች ስረ መሰረታቸው የት ድረስ እንደሆነ መንግስት ሊያጠናው ይገባል።የቀሲስ በላይ እና አጃቢ ፅንፈኞች ግብ ምንድነው? እውን ለኦሮሞ ሕዝብ የታሰበ ነው? ወይንስ የቤተ ክርስቲያኒቱን አንድነት ማናጋት፣በመቀጠል በኢትዮጵያ ውስጥ ግርግር መፍጠር እና የኢትዮጵያን ፖለቲካ ለአክራሪ እስልምና እንቅስቃሴ አጋልጦ በኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች ላይ አዲስ የመከራ ቀንበር ለመጫን? ከአስር ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ውስጥ በደህንነት መስርያቤቱ የሚታወቅ አንድ ወንጀል አለ። ይሄውም ፅንፈኛ የሙስሊም እንቅስቃሴ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ታላላቅ የአብነት መምህራንን የመግደል ፕሮጀክት ነበር።በእዚህ ፕሮጀክት መሰረት ጎንደር ውስጥ የሚገደሉ የአብነት መምህራን ስም እና አገዳደሉን የያዘ መረጃ በደህንነት ቢሮ ተይዞ ግለሰቦቹም ከውጭ ሀገር ፅንፈኞች ጋር ሁሉ ግንኙነት እንዳላቸው የተደረሰበት መረጃ (ለሕዝብ አልተገለጠም እንጂ) እንደነበር ይታወቃል።ስለሆነም መንግስት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የሀገር ጉዳይ መሆኑን ማወቅ አለበት። ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይም ''ኦርቶዶክስ ሀገር ነች።አንዳንድ ኦርቶዶክሳውያን የኦርቶዶክስ ጉዳይ የእነርሱ ብቻ ይመስላቸዋል። የሀገር ጉዳይ ስለሆነ ሁላችንም ይመለከተናል'' ማለታቸው ይታወሳል። ይህንን ሲሉ ጉዳዩ በደንብ ገብቷቸዋል ብዬ አስቤ ነበር።አሁን ግን በሰሞኑ የቤተ ክርስቲያኒቱ አደጋ አንፃር መውሰድ የሚገባቸውን ርምጃ እና ኃላፊነት በደንብ ያጤኑት አይመስልም።ስለሆነም አሁንም ሰላም ወዳዱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይህ የለውጥ ዕድል እንዳይታጠፍ  መንግስት ከፅንፈኛ ኃይሎች በቶሎ ራሱን መለየት አለበት።
በመጨረሻም ለማጠቃለል፣የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከአክሱም ስልጣኔ እስከ ኮምፕዩተር ዘመን ስትኖር፣በምድራዊ ጥበብ አይደለም።ልዩ መንፈሳዊ ኃይል ቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ አለ። ከህገ ልቦና እስከ ህገ ኦሪት፣ከሕገ ኦሪት እስከ ህገ ወንጌል ኢትዮጵያ በእምነት ውስጥ የኖረች ሀገር ነች። አርዮስ ሲነሳ ነበረች፣ንስጥሮስ ሲነሳ ነበረች፣ሉተር ስነሳ ነበረች፣ሉላዊነት ሲነግስ አለች።ወደፊትም እርሷን እና የዕምነት ፍልስፍናዋን የሚረታ ምድራዊ ኃይል የለም።ምንም ማድረግ አይቻልም።አለማመን መብትህ ነው። በፈለከው እምነት ውስጥ መኖር እግዚአብሔርም የሰጠው መብት ነው።ሰው እጁን ከፈለፈው ውስጥ የመክተት መብት አለው።ቢፈልግ ውሃ ውስጥ ካሻው እሳት ውስጥ ካልፈለገ አጣምሮ መቀመጥ። ይህ ሁሉ መብት ነው።እግዚአብሔር በእዚህ ሁሉ እርሱ መልካም ነው ወዳለው እስክትመጣ እድሜ እየሰጠ ይታገስሃል።እራስህን ችለህ መቀመጥ አቅቶህ እርሱ ከሕገ ልቦና እስከ ህገ ወንጌል ያሻገራትን የኢትዮጵያውያንን ሃይማኖት ስትነካ ግን ግለሰብ ሆንክ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ሃብታም ሆንክ ድሃ፣ ሃያል ሆንክ ደካማ መንግስት አይታገስህም።ይህንን የምለው በተረት ተረት ወሬ አይደለም።ቤተ ክርስቲያኒቱን ከፋሺሽት ጣልያን እስከ ግራኝ መሐመድ፣ከጋዳፊ እስከ መካከለኛው ምስራቅ አንዳንድ የፅንፍ መንግሥታት ተገዳድረዋታል፣ቤተ ክርስቲያን ዛሬም አለች።እነርሱ ግን አይሆኑ ሆነው የሉም። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ''ሰይጣን ቀስቱን ወረወረ ፣ ዝናሩን ጨረሰ ቤተ ክርስቲያንን ግን አላጠፋትም''  እንዳለ፣ቤተ ክርስቲያን ፈፅሞ ልትጠፋ አትችልም።ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት የሰይጣን ማደርያ መሆን ደግሞ ሌላው የጥፋት ጥፋት ነው።
ሰላም ለኢትዮጵያ ያድልልን።  
ጉዳያችን/Gudayachn 


ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።