Monday, March 9, 2026

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የሰሞኑ ከራሞት ልዩ ሪፖርታዥ

የ2018 ዓም የጥምቀት በዓል አከባባር በአቴንስ ኪዳነምሕረት 


በእዚህ ጽሑፍ ስር የሚከተሉትን ንዑስ ርዕሶች ያገኛሉ፡ 
  • በአሁኑ ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱን እና ምእመናንን  የሚያምሷት እነማን ናቸው?
  • እራሱን ''የሲኖዶስ አስፈጻሚ ኮሚቴ'' እያለ የሚጠራው ማን ነው?
  • የቡድኑ ''ሶማትዮ ማኅበር'' እና  ''ቀሲስ አየለ'' የሚለው አጀንዳው
  • ''ቤተክርስቲያኑ እንዲዘጋ እንፈልጋለን'' የአማሳኝ ቡድኑ የእየሳምንቱ ፉከራ
  • የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ምእመናን በአማሾች ሲታመሱ ያደረጉት ምንድን ነው?
  • በአሁኑ ጊዜ የምእመናኑ አንድነት እና ሕብረት የበለጠ ጠንክሮ ወጥቷል።

መግቢያ

በጥንታዊቷ እና ቀደምት የክርስትና መገኛ ከሆኑት ሀገሮች ውስጥ በሆነችው ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የዓመታት ችግር ፈቺ በሆነ መልክ ሪፖርት እንዲዘጋጅ ቋሚ ሲኖዶስ በወሰነው መሰረት የተቋቋመው እና ከቤተክሕነት፣ከኖርዲክ እና ግሪክ ሀገረስብከት እና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የተገኙበት ልዩ አጣሪ ኮሚቴ በግንቦት 2016 ዓም ለቅዱስ ሲኖዶስ ካቀረበው ሪፖርት መግቢያ ላይ የቀረበው ጽሑፍ በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አመሰራረት ላይ ጥሩ ማብራርያ ይሰጣል። የሪፖርቱ መግቢያ እንዲህ ይነበባል፡ 

''በእአአ1996 ዓ/ም (1989) የግሪክ የሃይማኖት ተቋማት ሕጋዊ የዕውቅና ምዝገባ አስመልክቶ ባወጣው አዋጅና መመሪያ መሠረት “በአቴንስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” ቃለ ዓዋዲው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ አንድ ውስጠ ደንብ በሕግ ባለሙያዎች ተዘጋጅቶና በሀገሪቱ መንግሥት ዐዋጅ ጸድቆ ለምዝገባ በመቅረቡ የአቴንስ ምክሐ ደናግል ቅድስት ኪዳነ ምኅረት ቤተ ክርስቲያን በሀገሪቱ የሃይማኖት ተቋማት ምዝገባ ዕውቅና አገኘች፤ ይኽ አሁን (ሶማቲዎ) እየተባለ የሚጠራው ነው፤ በወቅቱ የነበሩት የሰበካ ጉባኤ አባላትም ይኽንኑ ጉዳይ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ (ዶ/ር) አምስተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ አሳውቀዋል፡፡ ዕውቅናው ለቤተ ክርስቲኒቱ ተጨማሪ የሕግ ሰውነት የሰጣት ሲሆን እአአ ከ1994 ዓ/ም ጀምሮ ለነበረባቸው የሰነድ ተቀባይት ችግርም መፍትሔ መስጠቱ ሰበካ ጉባኤው በላከው ደብዳቤ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ይኽ የሶማቲዎ (ማኅበር) የግብር መለያ ቁጥር (Tax No) 997874156 ሲሆን “AΙΘΙΟΠΙΚΗΣΟΡΘΟΔΟΞΗΣ ΕΚΚΛΗΣΙΑΣ ΤΗΣ ΑΘΗΝΑΣ” በሚል ንብረት ለማፍራት፣ ገንዘብ
ለማንቀሳቀስ፣ በግብርና ተያያዥ ክፍያዎች አፈጻጸም ዙሪያ ያሉ ችግሮችንም ለመፍታት ተችሏል፡፡በኋላም ብፁዕ አቡነ ገሪማ (ዶ/ር) ባጸደቁት የኮሚቴዎች ስም መንፈሳዊ አገልግሎቱ ቀጥሏል፡፡''

ይህ ሪፖርት ቅዱስ ሲኖዶስ ተቀባይነት ያገኘ እና ከቤተክሕነት ረዳት ፕሮፌሰር መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል፣ ከስዊድን ዶ/ር ቀሲስ አባተ፣ከፊንላንድ፣ሄልሲንኪ ከደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስትያን የሀገረስብከቱ ጸሐፊ መልዓከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ፣ከሀገረስብከቱ የሕግ ክፍል ምክትል ሰብሳቢ አቶ ደምስ በግሪክ ያሉ ሁሉንም ወገኖች አነጋግረው በመጨረሻ ምክረ ሃሳብ አክለው ያዘጋጁት ልዩ ሪፖርት ነው። በእዚሁ ሪፖርት መሰረት ቅዱስ ሲኖዶስ በመጋቢት/2017 ዓም አቡነ ጢሞቲዎስ እና አቡነ ጴጥሮስ ያሉበት ልዩ ልዑክ ግሪክ ድረስ ልኮ የግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ጉዳይ ለማየት ተሞክሯል። ከብፁአን ሊቃነ ጳጳሳት የአቴንስ ጉዞ ተከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ክሕነታቸው ተይዞ የነበረው የአባ ወልደሚካኤልን ስልጣነ ክሕነት የመለሰ ሲሆን ለአቴንስ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን በሕገ ቤተክርስቲያን መሰረት አዲስ አስተዳዳሪ ሊቀስልጣናት አባ ኪሮስ ጸጋዬን መድቦ፣በአሁኑ ጊዜ ምእመናን የአዲሱን አስተዳዳሪ መምጣት በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።ይህ በአሁኑ ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱ የምትገኝበት ተጨባጭ እውነት ነው።

 በአሁኑ ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱን እና ምእመናንን  የሚያምሷት እነማን ናቸው?

ቅዱስ ሲኖዶስ ለቤተክርስቲያኒቱ በቂ ክትትል በማድረግ ተገቢውን ስራ ቢያከናውንም ከመጀመርያ ጀምሮ የቅዱስ ሲኖዶስን ሲኖዶሳዊ ውሳኔ ሲቃወሙ የነበሩ፣በኋላም በአጉራ ዘለል እና ፍጹም ኢትዮጵያዊም ሆነ ኦርቶዶክሳዊ ትብሃል ባልሆነ መንገድ ቤተክርስቲያኒቱን ለማመስ የሚሞክሩት እጅግ ጥቂት የሆኑ ግለሰቦች እነማን እና ምን እንደሚፈልጉ ለመግለጽ መጀመርያ ማንነታቸውን መግለጹ ያስፈልጋል።

አማሾቹ እነማን ናቸው? 
  • የመጀመርያው ቡድን ውስጥ ያሉት በጣት የሚቆጠሩት ለዓመታት የግሪክ አቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪነት ዘመን ማለት ቀድሞ አባ ዮሐንስ፣በኋላም የነበሩት ንቡረዕድ አባ ኃይለልዑል ገሪማ ቤተክርስቲያኒቱን ሲያስተዳድሩ በቤተክርሲቲያኒቱ ገንዘብ እንደ የግል ንብረት ሲጠቀሙ የነበሩ፣ወደ ሃገርቤት ከግሪክ ከቀረጥ ነጻ በቤተርክስቲያን ደብዳቤ ሲያስገቡ እና አብረዋቸው ሲሞዳሞዱ የነበሩ የቡድን አባላት የመጀመርያ ተጠቃሽ ናቸው ናቸው።ከእዚህ ቡድን አባላት ውስጥ በሕገወጥ መንገድ የቅስና እና የድቁና ማዕረግ ሳይገባቸው የተቀበሉ ያሉበት ነው። ይህ ቡድን አባላቱ በአሁኑ ጊዜ ከአራት የማይበልጡ ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ ሰላማዊ በመምሰል በምዕመኑ ውስጥ መለያየት የሚነዛ፣በአደባባይ እየተቅለሰለሰ ቤተክርስቲያንን ለማመስ ከሚሮጡ ጋር ከአስተባባሪነት እስከ በቀጥታ ሃሳብ በመስጠት በአጽራረ ቤተክርስቲያንነት የተሰለፈ ግለሰብ አለበት።ይሄው ግለሰብ በሀገርቤትም በንዋየ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ ቀደም ብሎ በቅዱስ ዑርዔል ቤተክርስቲያን በሕገወጥ መልክ ሱቅ የነበረው እና በአሁኑ ጊዜ በሌላ ቦታ ሱቅ ያለው ሲሆን፣ ከግሪክ የሚመጡ እቃዎችን ከቀረጥ በነጻ በማስገባት ከፍተኛ ምዝበራ ላይ የተሰማራ ግለሰብ ነው።
  • በሁለተኛው ቡድን ውስጥ የሚገኙት በጣት የሚቆጠሩ የአማሽ ቡድን አባላት በቀደመው የሰበካ አባላት የነበሩ፣የቤተክርስቲያኒቱን ንብረት በአግባቡ መያዝ አለመቻል ብቻ ሳይሆን፣እስካሁንም ሪፖርት እንዲያቀርቡ እና ንብረት እንዲያስረክቡ በቅርቡም ጭምር ተጠይቀው አሻፈረኝ ያሉ፣ከተለያዩ የስለት የወርቅ ስጦታዎች እስከ የቤተክርስቲያኒቱን ሚኒባስ አላስረክብም ብለው መኪናው በሕግ እንዲያስረክቡ ተደርገው ሌሎቹን በተመለከተ በምእመኑ በተቋቋመ አጣሪ ኮሚቴ ሪፖርት ቀርቦ ምላሽ ያልሰጡ፣ከሰንበት ትምሕርት ቤት ቲሸርት ሸጦ ገንዘቡን በአደባባይ ወደ ኪሱ የከተተ እና እስከ ሁለት ሺህ ኢሮ ከሰንበት ትምሕርት ቤት ንዋየ ቅዱሳን መሸጫ ሱቅ በድፍረት ጠፋብኝ ብሎ የተዘባበተ ግለሰብ ያለበት ቡድን ነው።

  • በሦስተኛው ቡድን ውስጥ የሚገኙት አሁንም በጣት የሚቆጠር ቡድን ያለበት ቡድን ባንዳ እና ባዳ የሚባለው ቡድን ነው። በእዚህ ቡድን ውስጥ የሚገኙት ጸረ ኢትዮጵያ አቋም መመረዛቸው በስራቸው ያስመሰከሩ ናቸው። በእዚህ ውስጥ ለኢትዮጵያ ባዳ የሆኑ ነገር ግን ለቤተክርስቲያን የሚቆረቆሩ መስለው እኛኑ መስለው የሚያምሱ ናቸው። ዓላማቸው የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ከግሪክ መንቀል፣ምእመኑን ማወክ፣ኢትዮጵያውያን በቤተክርስቲያናዊ እና ብሔራዊ ስሜታቸው እንዳይኮሩ ማድረግ እና የኢትዮጵያን ስም በግሪክ ማኅበረሰብ ዘንድ ማጠልሸት ነው።

    በእዚህ ውስጥ በቅስና የሚገኙ፣በቀድሞ ሰበካ ውስጥ የነበሩ እና ከኋላ ሆነው በኢትዮጵያውያን ላይ የሚጎነጉኑ ''አካይስት'' አስተሳሰብ ያላቸው የበሉበትን የኢትዮጵያን ወጪት ሰባሪ አሳፋሪዎች ናቸው። ከእነርሱ ጋር አብረው ያሉት ባንዳዎች የቤተክርስቲያን ጉዳይን ለዘመኑ የጥፋት ስራ ለማዋል የቋመጡ ከባዳ ጋር አብረው ቆመንለታል ለሚሉት የረከሰ የባንዳ ተግባር በቤተክርስቲያን ስም ለውሰው ለመንቀሳቀስ የሚሞክሩ አሳፋሪዎች ያሉበት ነው። እዚህ ላይ በኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ስም ፌስ ቡክ ከፍቶ ላለፉት ስባት ዓመታት ያህል የቤተክርስቲያኒቱን ስም ሲያጠለሽ፣የአባቶችን ክብር ሲያዋርድ የኖረ እና እራሱን በመንፈሳዊ ማኅበር ውስጥ ሽጉጦ በአሁኑ ጊዜ ደግሞ አንዴ አዲስ አበባ ቤተክሕነት ሌላ ጊዜ አቴንስ ፖሊስጣብያ በር ላይ እየተንገዋለለ የዘረኛ መርዙን ሸሽጎ የባንዳነት ተግባሩን የሚሰራ ዲያቆን የተካተተበት ነው። ይህ ዲያቆን በተለይ ለዓመታት የግሪክ ጉዳይ እንዳይፈታ በአንድ የቤተክሕነት አባት አገላለጽ ሲናገር ''የእባብ መርዝ የሚተፋ'' ያሉት ግለሰብ በሀገረ ስብከቱና በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መሃል ችግር እንዲፈጠር የሰርክ ጉባዔ ቀመስ በሆኑ ጥቅሶች ምእመኑን በፌስቡክ ሲያምስ የኖረ እና አሁንም እያመሰ የሚገኝ ግለሰብ ነው።

  • በአራተኛ ቡድን ውስጥ ያሉት ጥቂት ግለሰቦች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነትን ለመበረዝ የሚቅበዘበዙ ቡድን አባላት ናቸው። በእዚህ ስር ያሉት ከቤተክርስቲያኒቱ ዶግማና ቀኖና ውጪ በሆነ መልክ መሰረተ እመነቷን ለመበረዝ ምእመኑን ለመክፈል የሚሮጡ የሃይማኖት ቀሳጮች ናቸው።እነኝህ በቤተክርስቲያን ውስጥ ኦርቶዶክሳውያን የሚመስሉ ነገር ግን ቤተክርስቲያኒቱ እንድትጠላ በቀጥታ በማናቸው ቤተክርስቲያንን በሚያውኩ ተግባራት ውስጥ ይሰማራሉ። 
ከላይ የተጠቀሱት አራት ቡድኖች ሲደመሩ ከ15 አይበልጡም።ቤተክርስቲያኒቱን የሚበጠብጡት በእዚህ ያህል ያሉ ቁጥር ያላቸው ናቸው። አራቱም ቡድኖች አዲስ የመጡ ስደተኞችን ለመያዝ በብዙ ጥረት የእኩይ ተግባራቸው ተባባሪ ለማድረግ ቢሞክሩም፣ ሁሉም የተንኮላቸው ተባባሪ ስላልሆኑ ዛሬም በጣት የሚቆጠሩ የቡድኑ አባላት ቀርተዋል። 

እራሱን ''የሲኖዶስ አስፈጻሚ ኮሚቴ'' እያለ የሚጠራው ማን ነው?

በመጋቢት/2017 ዓም ወደ አቴንስ የመጣው የቅዱስ ሲኖዶስ ልዑክ ከተመለሰ በኋላ ከላይ በአራት የአስተሳሰብ እና የፍላጎት ውጥረት ውስጥ የገባው ወደ 15 የሚቆጠር ቡድን ከሃገረስብከቱ ሊቀጳጳስ ባገኘው አረንጓዴ መብራት እራሱን ''የሲኖዶስ አስፈፃሚ ኮሚቴ'' በማለት አንድ መቶ የማይሞላ ተከታይ ይዞ በፌስቡክ ተከሰተ። ቡድኑ የሰረቀው፣የባዳው እና የባንዳው እንዲሁም የሃይማኖት ቀሳጩ ቡድን በጋራ የተሰበሰበበት ቡድን ነው። 

የቡድኑ ''ሶማትዮ ማኅበር'' እና  ቀሲስ አየለ የሚለው አጀንዳው

በአቴንስ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ለማመስ የሚንቀሳቀሰው 15 ሰዎች የያዘው ስብስብ ከእውቀት ነጻ የሆነ ቤተክርስቲያኒቱ ቀድሞ ጀምሮ በግሪክ መንግስት የተመዘገበችበትን ''ማኅበር '' ወይንም ''ሶማትዮ ''  የሚለውን ስም የቤተክርስቲያን መስደብያ ቋንቋ አድርጎታል። ቤተክርስቲያኒቱን እንደፈለጉ አድርጎ ለመዝረፍ እና ለማጥፋት አልመች ያለው ይሄው አደረጃጀት መሆኑን ስለሚያውቁ በከፍተኛ ጥላቻ የቤተርክስቲያኒቱን አደረጃጀት ማጥላላት ዋና ስራ አድርገው ይዘውታል።ቡድኑ በራሱ ''የብሪፍ ኬዝ'' ተንቀሳቃሽ የቤተክርስቲያን ስም የሚነገድበት ማኅተም ይዞ የሚዞር ሲሆን አደረጃጀቱም በእድር መልክ ''ኪኖኒታ'' በሚል አደረጃጀት የኖረ ነገር ግን አድራሻውን በቦርሳ ይዞ የሚዞር ነው።

ይህ የተለያየ ፍላጎት ያዘለው ቡድን ከሰሞኑ ይዞ የመጣው በግሪክ የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ከአስር ዓመት በፖሊጎኖ የምትገኘውን የኪዳነምሕረትን ቤተክርስቲያን ትተው የሄዱትና ከቅርብ ወራት ወዲህ ተመልሰው የመጡት ቀሲስ አየለን በአጀንዳነት ይዞ መጥቷል።ቀሲስ አየለ ወ/ጻድቅ በቅዱስ ሲኖዶስ በደብዳቤ ቁጥር 397/408/2018 ሐምሌ 23/2017 ዓም ባደረገው ስብሰባ መሰረት በየትኛውም የቤተክርስቲያን አስተዳደር እንዳይገቡ ያገደ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ የተሰጠ ማናቸውም ጊዜያዊ ደብዳቤ በሕገ ቤተክርቲያን አንቀጽ 28 መሰረት የተሻረ መሆኑን ደብዳቤ የተጻፈባቸው መሆኑ እየታወቀ ቡድኑ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ በመጻረር ቀሲስ አየለን የብጥብጥ አጀንዳ ለማድረግ ሞከረ። 

በእዚህ መሰረት ቀሲስ አየለ ከላይ ከተጠቀሰው ቡድን ጋር በመሆን እስካለፈው እሑድ ድረስ በተለያዩ ሳምንታት ለ6 እሑዶች ጊዜ የሰንበት ቅዳሴ እንዳይቀደስ ከማወክ አልፈው ምእመናን ላይ ፖሊስ በመጥራት ቤተክርስቲያኒቱ ዙርያ ያሉ ነዋሪዎች ጭምር እንዲታወኩ አድርገዋል።ይህንን ጉዳይ የተመለከተው ምእመን ከአንድ ሳምንት በፊት መክሮ ቀሲስ አየለ መቅደስ የሚገቡት አዲሱ አስተዳዳሪ ከመጡ በኋላ ጉዳዩ በካሕናት ጉባዔ ከታየ በኋላ ነው የሚለውን ሃሳብ ወደጎን በማድረግ ወደ መቅደስ እንዲገቡ በሚለው ጉዳይ ላይ ሃሳብ ከተሰጠ በኋላ ባለፈው ሳምንት እሑድ ወደ መቅደስ እንዲገቡ ሲጠየቁ ቀድሞም ምክሩ ከአማሽ ቡድኑ ጋር ስለነበረ የአማሽ ቡድኑ ባሳለፍነው እሑድ የካቲት 29፣2018 ዓም በቤተክርስቲያን ውስጥ ገብተው የሚከተሉትን ጸያፍ ተግባራት ፈጸሙ። ይሄውም፡
  • ቤተክርስቲያን ውስጥ በካሕናት ላይ እጅግ አስነዋሪ ስድብ፣እና ለመደብደብ መገባበዝ፣
  • በቤተክርስቲያን ወንበር ላይ ቆመው ፊሽካ እየነፉ የቡናቤት ስድቦች መሳደብ፣
  • በፉጨት እና ከዘፈን ባልተናነሰ ድምፅ ማቅራራት፣
  • የቤተክርስቲያንን ወንበር እየገለበጡ መዘባበት እና ሌሎች እጅግ ለአእምሮ የሚከብዱ ተግባራትን በቤተክርስቲያን ውስጥ ሲፈጸም ተስተውሏል።
''ቤተክርስቲያኑ እንዲዘጋ እንፈልጋለን'' የአማሳኝ ቡድኑ የእየሳምንቱ ፉከራ።

በአቴንስ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ከአርባ ዓመታት የቆየችበት ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን ከአጠገቡ በሚገኘው በግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ስር የሚተዳደር በመሆኑ እና በአማሳኝ ቡድኑ የየሳምንቱ እጅግ ነውረኛ የሆነ የስድብ እና የረብሻ ተግባር የተነሳ የአካባቢው ነዋሪ እንዲታወክ ሆኗል። የረብሻው አንዱ ዓላማ የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን መበተን በመሆኑ የአማሳኝ ቡድኑ ቀንደኞች ''ቤተክርስቲያኒቱ እንድትዘጋ ነው የምንሰራው '' እያሉ በአደባባይ ሲናገሩ ብዙ ጊዜ ተሰምተዋል፣ በማኅበራዊ ሚድያም ይህብንኑ ያልተገራ ነውራቸውን ሲለጥፉ ይታያሉ። በእርግጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ከአቴንስ ከተማ ቅርብ ርቀት የሚገኝ ሌላ በገዳምነት የነበረ ይዞታ አላት። ይህ ግን በእየእሑዱ ለሚኖረው ቅዳሴ እርቀት አለው።ይህንኑም ገዳም ይሄው አማሳኝ ቡድን በርካታ ወረቀቶችን ወደ የግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር በመላክ ገዳሙን ለማሳሸግ ሞክሯል።

ከእዚህ በተጨማሪ የማለዳ ኪዳን በሚደረግባቸው ቀናት በማለዳ ቤተክርስቲያን በር ላይ እየቆሙ ካሕናትን መሳደብ እና መተናኮል የአማሽ ቡድኑ ተግባር ከሆነ ቆይቷል። ይህንንም ላለፉት ተከታታይ የእሑድ ሳምንታት ቅዳሴ እንዳይቀደስ በመረበሽ እና ቤተክርስቲያኑ ሲከፈት ደግሞ ካላይ እንደተጠቀሰው በጸያፍ ተግባር በመሳደብ እና ፊሽካ ጭምር በማጮህ ቤተክርስቲያንን በማወካቸው የዐቢይ ጾም ከገባ ጀምሮ አንድም እሑድ ቅዳሴ ማድረግ አልተቻለም። እዚህ ላይ ይህ የቤተክርስቲያን አማሽ ቡድን የህገረስብክቱ ሊቀ ጳጳስ ድጋፍ አለን በሚል ስለሚኩራሩ ''ምእመኑን ከቤተክርስቲያን እናስወጣለን '' የሚል ፉከራ ሲያሰሙ ለአፋቸው አያዳልጣቸውም።

የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ምእመናን በአማሾች ሲታመሱ ያደረጉት ምንድን ነው?

"እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።" (የሐዋርያት ሥራ 20:28) የሚለው ቃል ዛሬ በግሪክ በሚኖሩ ምእመናን ጆሮ ላይ የሚጮህ ድምፅ ነው። በግሪክ ምእመናን ለዓመታት አልቅሰዋል፣ገንዘባቸውን አውጥተው የገዙትን ገዳም ገዳም አድርጎ የሚባርክላቸው አባት አጥተው ተንከራተዋል፣ ለቤተክርስቲያን ያወጡት ገንዘብ በሌቦች ተወስዶ ከሌባ ጋር ሲተናነቁ ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በተጻፈ ደብዳቤ ለሰረቁት የእውቅና ደብዳቤ እየተሰጠ ባለፈው ዓመት ምእመኑን ሲያገለግሉ የኖሩት ካሕናት ስልጣነ ክሕነታቸው ''ከምእመን ያለፈ ስልጣን የሌለው ግለሰብ በጻፈልኝ ደብዳቤ መሰረት'' በሚል ለመያዝ ማስፈራርያ ተጽፏል። ቤተክርስቲያኒቱ ከግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር ጋር የሚኖራት ግንኙነት በድብቅ እና የአማሹ ቡድን በሚሰሩት ደባ የታጀለ በመሆኑ በአሁኑ ጊዜ የቤተክርስቲያኒቱ ክብር በግሪክ ቢሮዎች ውስጥ ዝቅ ያለ እንዲሆን የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል። ሌላው ቀርቶ አሁን በፖሊጎኖ የምትገኘው የኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ከባለቤቷ የግሪክ ቤተክርስቲያን ጋር ያለው ግንኙነት ቤተክርስቲያኒቱን ለአማሹ ቡድን ለመስጠት በሚደረገው አድሏዊ ሕገወጥ ግንኙነት ምክንያት የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ክብር ዝቅ የሚያደርግ ግንኙነት በመደረጉ ከፍተኛ ቅሬታ እንዲፈጠር ሆኗል።በእዚህም ሳብያ የግሪክ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪም በጉዳዩ ተማረው ቅሬታ አቅርበዋል።

ሌላው ቀርቶ ቅዱስ ሲኖዶስ የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ እንዲሆኑ የመደባቸው አባት ሊቀስልጣናት አባ ኪሮስ ፀጋዬ ወደ ግሪክ መጥተው አገልግሎት እንዲጀምሩ ለማድረግ የሚደረግ የድጋፍ እንቅስቃሴ ከሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስም ሆነ ከሀገረስብከቱ አንጻር የሚታይ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ አይታይም።ጉዳዩ የቤተክርስቲያን መሆኑ ቀርቶ የአማሽ ቡድኑ ጋር በሚደረጉ ሕገወጥ እና ቤተክርስቲያንን ማዕከል ያላደረገ ግንኙነት የህገር እና የቤተክርስቲያን ክብር ጉዳይ መሆኑ ቀርቶ ተራ የእልህ እና የሴራ ትብተባ ውስጥ እንዲገባ ሲሞከር ይታያል። ይህ ልብ የሚሰብር በግሪክ የምትገኝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰቆቃ ድምፅ ነው።ጉዳዩን ቅዱስ ሲኖዶስ በአንክሮ እና በአፋጣይ ማየት ያለበት ጉዳይ ነው።የምንናገረው ስለየግል ጉዳይ አይደለም ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለተሰቀለበት፣ስለተገረፈበት እና ስለሞተበት የምእመናን ጉዳይ ነው። ስለሆነም ማንንም ሳያፍሩ እና ሳይፈሩ እውነቱን መናገር ክርስቲያናዊ ግዴታ ነው።

በአሁኑ ጊዜ የምእመናኑ አንድነት እና ሕብረት የበለጠ ጠንክሮ ወጥቷል።

''ክርስቲያን እና ሚስማር ሲመቱት ይጠብቃል።'' እንዲሉ፣ በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን ቤተክርስቲያናቸው ላይ የሚሰነዘሩትን የአማሳኞች ጥቃት ለመመከት ብቻ ሳይሆን ቤተክርስቲያኒቱ ወደ ግማሽ ክ/ዘመን ያህል ከአንድ ሰንበት ትምሕርት ቤት ባልበለጠ አነስተኛ ቤተክርስቲያን የመቆየቷ ቁጭት ጨምሮ እና በአጠቃላይ ወደየተሻለ አገልግሎት ለማሸጋገር ከመቼውም ጊዜ በላይ ቆርጦ የተነሳበት ጊዜ አሁን ነው። እንደ አንድ ምእመን አገላለጥ ''ኪዳነ ምሕረት የቤተክርስቲያኒቱ የቆዩትም፣ድንገት ደራሾችም፣ባዳውም ሆነ ባንዳው ተለይቶ ጠልሏል።የጠለለ ነገር እዳው ገብስ ነው።'' እንዳሉት ምእመናን በግሪክ የምትገኘውን ቤተክርስቲያን ከአጽራረ ቤተክርስቲያን እና ከአማሽ ቡድን ለመገላገል የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሷል።ለእዚህም ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ ተነስቷል። የአማሽ ቡድኑ የአማንያኑን የትሕትና መንገድ ሁሉ ከበጎ ከመመልከት ይልቅ በተሳሳተ መንገድ መመልከታቸው የስሌት ችግር ካልሆነ በቀር ሌላ ሊሆን አይችልም። ስሌት ክፉ ነው።ቤተክርስቲያን ከሕይወት በላይ ነች። የእዚህን ምእመን ኃይማኖታዊ መነሳሳት ቅዱስ ሲኖዶስ የጎደለውን በመሙላት፣የሃገረ ስብከት ችግርን በመፍታት እና ለቤተክርስቲያኒቱ የተመደቡትን አባት በፍጥነት ወደ ግሪክ የሚመጡበትን ማናቸውንም መንገድ በመጠቀም እና በማሳካት አስፈላጊው ሁሉ እንዲከናወን በግሪክ የሚኖሩ ምእመናን ጥያቄ ነው።
======================////===========

Monday, February 23, 2026

Urgent Justice to the Ethiopian Orthodox Tewahido Church in Greece. Attention: The Hellenic Ministry of Education, Religious Affairs department, and the Athens Police


Under this special report, you will find the following subtitles: 
  • The Ethiopian Orthodox Church foundation in Greece.

  • The Ten years Controversy of the Ethiopian Orthodox church in Greece.

  • The results of the 2025 Bishops' visit to Athens.

  • The Greek Ministry of Religion is expecting a prompt and positive response regarding the Ethiopian Orthodox Tewahido Church Patriarch's letter.

  • Greek security forces should take immediate action against criminals who are attempting to terrorize the Ethiopian Orthodox Church believers in Athens.

  • To Generalized
===================
Gudayachn Special Report
===================

The Ethiopian Orthodox Church foundation in Greece.

The Ethiopian Orthodox Tewahido Church and the Greek Orthodox churches are among the ancient churches in our Globe. The first Ethiopian Orthodox Tewahido Church patriarch, ''Aba Fremnatos or Selama'', a Greek origin, visited Ethiopia in the 4th century. In our modern world, the Ethiopian Orthodox Tewahido Church, founded in Hellenica, goes back about half a century.

In accordance with the 1996 (1989) proclamation and directives regarding the legal recognition and registration of Greek religious institutions, the “Ethiopian Orthodox Tewahedo Church of Athens” was registered as a religious institution in the country, and an internal regulation was prepared by legal experts and approved by the government of the country. The Church of the Holy Virgin of Athens, the Holy Covenant of Mercy, was registered as a religious institution in the country; this is now called (Somatio); the members of the Synod at that time informed His Holiness Abune Paulos (Dr.), the Fifth Patriarch of Ethiopia, about this matter. The recognition gave the church additional legal personality and also solved the problem of receiving documents that had been processed since 1994, according to a letter sent by the Synod. This association has a tax number (Tax No) of 997874156 and was established under the name “AΙΘΙΟΠΙΚΗΣ ΟΡΘΟΔΟΞΗΣ ΕΚΛΛΗΣΙΑΣ ΤΗΣ ΑΘΗΝΑΣ” to raise funds, raise funds, and resolve problems related to religious issues. Later on, the spiritual service continued under the name of the committees approved by His Holiness Patriarchal of the Ethiopian Orthodox Tewahido Church, Abune Gerima (Dr.).

The Ten-Years Controversy of the Ethiopian Orthodox church in Greece

The Ethiopian Orthodox Tewahido Church in Greece faced challenges at different levels. The challenges have continued over the past ten years, and the sources of challenges originated from two different bodies. These were the Holy Synod of the Church in Ethiopia (recently adjusted and corrected the problem) and the misuse of resource administration by the former church committee, which exposed the church to theft.

The results of the 2025 Bishops' visit to Athens

In March 2025, the Holy Synod of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church sent two bishops to Athens to visit Greece based on the report of the previously appointed Special Study Committee on the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Greece. The bishops, Abune Timothy and Abune Petros, were tasked with investigating the church’s affairs and presenting a recommendation to the Holy Synod.

During their stay in Athens, the bishops announced the reinstatement of Abba Woldemikhael's priesthood, which had been suspended nine years ago. They, the bishops, then announced that a new administrator would be appointed for the Ethiopian Orthodox Tewahido Kidane Mihret Church in Athens and returned to Ethiopia to report the situation to the concerned Holly synod. 

The Greek Ministry of Religion is expecting a prompt and positive response regarding the Ethiopian Orthodox Tewahido Church Patriarch's letter.

The Holy Synod members of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, which came to Athens in March 2025, returned to Ethiopia and selected Abba Kiros Tsegaye, who is well known for his extensive experience and spiritual services, as the head of the Ethiopian Orthodox Church in Athens. Abba Kiros Tsegaye’s assignment letter to administrate the Ethiopian Orthodox Tewahido Church in Greece was written by the Patriarch of the Ethiopian Orthodox Church, His Holiness Abune Mathias, directly to the Ministry of Religion, which is under the Greek Ministry of Education.

Currently, it is quite clear that the Greek Ministry of Religion’s failure or delayance to respond promptly after the letter has caused great dissatisfaction among Ethiopians residing in Greece. The hot issue, currently, is that the Ministry of Religion needs to provide the necessary permission to Abba Kyros Tsegaye to enable him to get the necessary entry visa to Greece. There are reports that the Ministry of Religion will respond to the matter soon and will allow Abba Kyros to come to Greece, and this is eagerly awaited by thousands of Ethiopian Orthodox Tewahido church followers in Greece. In this case, the Greek government and the Ministry of Religion should pay close attention to this critical issue. The issue is not only a religious issue, but it has a diplomatic and historical relations issue. 

Greek security forces should take immediate action against criminals who are attempting to terrorize the Ethiopian Orthodox Church believers in Athens.

The Ethiopian Orthodox Church, which was designated by the Ministry of Religion and its administrator, has been exposed to terrorists who are engaged in fraud and theft and who are also terrorizing the prayers at the place of ''Bohali 12 Polygono'' in Athens. The terrorists (Ethiopians gave them a nickname) are still creating problems among the believers and in the church that is waiting for the new administrator, Aba Kiros Tsegaye. 

The individuals involved in this terrorist act are very few but known for their crime in Greece. For example, on November 10, 2024, after an assassination attempt was made by the same terrorist group in the church, the police arrived on time, and the injured person was taken to the hospital by ambulance. The case is under legal and criminal proceedings.

Since then, these terrorist individuals have been terrorizing the people verbally, mentally, and even physically on social media, and by phone also. To your surprise,  these individuals have not only made many attempts to call the police as if they were victims. Their negative action has also extended to conspiracies to create conflict between Greece and Ethiopia.

On the recent two Sundays, 15 and 22 February 2026, for example, the terrorists affected the praying time of the church, insulted the people, and threatened the priests physically. They attempted to push in by force the unauthorized priest by the Ethiopian Orthodox Tewahido Church in Bohali, 12. The priest was prohibited from entering by an Ethiopian Orthodox Tewahedo church administrative issue in Greece, which was decided by the Ethiopian Orthodox Tewahedo permanent Holy Synod. Here again, the terrorist teams called the police as if they were victims. However, thanks to the hardworking and honest Athens police who took the rioters out of the church and took them in a police car, and following them out, hundreds of gathered the church followers sang a spiritual song with the image of the Holy Covenant of Mercy and thanked God and the police for taking out the illegal entrants to the church. Currently, the individuals who are intimidating women and children are still trying to break down the church's door located at Polygono, Bohali 12. This has happened as of  Monday, February 23, 2026, and has not yet stopped till now. 

To Generalized

In general, the Ethiopian Orthodox Church in Greece is awaiting a quick response from the Greek Ministry of Religion. The new administrator appointed by the Holy Patriarch, Abba Kiros Tsegaye, should be brought to Athens as soon as possible. In addition to that, the Greek police should not only stop the harassment and beatings of the church followers by terrorists, but also bring the terrorists to justice. Greece and Ethiopia are countries with a history and friendship that goes back more than 3000 years. The Greek Orthodox Church and the Greek community school in Ethiopia are being governed under the highest state protection and in accordance with the laws and regulations of the country. Similarly, the Ethiopian Orthodox Church in Athens also needs attention. This is the voice of the majority. This article should be taken as a primary source of information. Long live the great Greece!

___________________________///_____________________

Wednesday, February 4, 2026

Ethiopia Builds Africa’s Monumental GERD Using Solely Own Resources, Says PM Abiy.



Ethiopia has constructed the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD)—one of Africa’s largest infrastructure projects to date—entirely using its own resources, with no foreign loans or external assistance, Prime Minister Abiy Ahmed told lawmakers on Tuesday.

Prime Minister Abiy presented his government’s mid-term performance report to the House of Peoples’ Representatives, that included a question and answer with the members of parliament.


According to the Prime Minister, the $5 billion hydroelectric generation and a pioneering project on the continent, was realized through Ethiopian determination and strong government-led project oversight.

It cannot be said that a government which successfully completed the Grand Renaissance Dam without a single birr of aid or loan is incapable of carrying out major projects, according to the reform-minded prime minister. “Ethiopia did not take even one birr in aid or loans for the Renaissance Dam; it is a collective national project realized through the firm determination, resilience, and unity of heroic Ethiopians who stood together and worked tirelessly.”

Beyond the GERD, Ethiopia is also advancing with similar other infrastructural projects, including the second-largest hydroelectric power station in Africa, the Koysha Hydroelectric Project.


The government has actively managed the construction of related infrastructure, including a fertilizer factory, gas refinery, and other mega projects. The GERD, built on the Abbay River, is Africa’s largest hydroelectric dam and a symbol of Ethiopia’s ambition to become a regional energy hub.

With more than 5,000 MW of installed capacity, GERD provides power domestically and to neighboring countries. The dam is also crucial for water regulation, irrigation, and boosting economic development, making it a strategic asset not only for Ethiopia but for the entire region.

Ethiopia emphasized that the GERD is a testament to national pride, technical expertise, and Africa-driven development, underscoring Ethiopia’s commitment to using its resources to secure a sustainable and prosperous future for its citizens.

GERD was inaugurated earlier in September with regional leaders attending, and blessing the hydro scheme as being vital for regional integration.

Ethiopia has already been exporting electricity to Sudan, Djibouti and Kenya as part of the regional power interconnection, while the country plans to expand exports to Tanzania and other countries of the Eastern and Southern Africa regions.


Source :  Pulse of Africa


===============///=============



የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የሰሞኑ ከራሞት ልዩ ሪፖርታዥ

የ2018 ዓም የጥምቀት በዓል አከባባር በአቴንስ ኪዳነምሕረት  በእዚህ ጽሑፍ ስር የሚከተሉትን ንዑስ ርዕሶች ያገኛሉ፡  በአሁኑ ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱን እና ምእመናንን  የሚያምሷት እነማን ናቸው? እራሱን ''የሲ...