- የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት።
ጉዳያችን - GUDAYACHN
ጉዳያችን - በጉዳያችን ሚድያ፣ኮምኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት የሚዘጋጅ ሲሆን ከ2003 ዓም ጀምሮ በድረ-ገፅ ላይ የነበረ በአሁኑ ጊዜ ከአንድ ሚልዮን በላይ ጎብኚዎች ያሉት ገፅ ነው። Gudayachn is prepared by Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant Organization. It has been online since 2011. Currently, Gudayachn is being visited by over One-million readers from all over the world.
Tuesday, July 14, 2026
የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።
Wednesday, July 8, 2026
Tuesday, June 2, 2026
7ኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24፣2018 ዓም በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ተጠናቋል።
- ስለምርጫው ዝርዝር ጉዳይ ምን ያውቃሉ?
✓ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ 42 ፓርቲዎች እና 73 የግል ተወዳዳሪዎች ለተለያዩ ምክር ቤቶች ዕጩዎች የቀረቡበት ነው።
✓ በዚህ ምርጫ በአጠቃላይ 2,198 ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲሁም 8,736 ለክልል ምክር ቤቶች መቀመጫዎች በዕጩነት ቀርበው ተወዳድረዋል።
✓ በዚህም በምርጫው የተወዳደሩት አጠቃላይ ዕጩዎች ቁጥር 10,934 ዕጩዎች መሆናቸውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ ያመለክታል።
✓ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለክልል ምክር ቤቶች ከፍተኛውን ዕጩዎች ያቀረቡት ሦስት ፓርቲዎች ናቸው።
✓ በዚህም ገዢው ብልጽግና 2,950 ዕጩዎችን በማቅረብ ቀዳሚ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) 1,256 እና ሦስተኛው ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 1,032 አቅርበዋል
✓ ሌሎች ፓርቲዎች እና የግል ተወዳዳሪዎችም በተለያየ ቁጥር ለተለያዩ ምክር ቤቶች መቀመጫ ለማግኘት ዕጩዎችን በምርጫው ላይ እንዲወዳደሩ አቅርበዋል።
✓ በአማራ ክልል ከሚገኙ 138 የምርጫ ክልሎች መካከል በስምንቱ ምርጫ እንደማይደረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ብሎ ማስታወቁ ይታወሳል።
✓ በአማራ ክልል ድምጽ የማይሰጥባቸው 8ቱ የምርጫ ክልሎች በደቡብ እና ምዕራብ ጎንደር፣ በአምባሰል እንዲሁም በደጋ ዳሞት የሚገኙ መሆናቸው ተገልጿል።
✓ በትግራይ ክልል ከሌሎች የአገሪቱ ክልሎች ጋር በአንድ ላይ ምርጫ አልተካሄደም።
✓ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዋ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ሰኞ ዕለት ድምጽ በማይሰጥባቸው ስምንት የምርጫ ክልሎች ወደፊት እንዲመርጡ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
✓ በትግራይም 38 ወንበሮች ክልሉ በምርጫ ቦርድ በተቀመጠው የምርጫ ሒደትና ሕግ መሰረት የሚካሔድና ወንበሮቹ ክፍት ሆነው ይጠብቃሉ።
✓ ትናንት ግንቦት 24፣2018 ዓም የተደረገው ብሔራዊ ምርጫ 501 ዕጩዎችን ወደ የሕግ መወሰኛው ወይንም የተወካዮች ምክርቤት የሚያስገባና ምስክርም 25፣2019 ዓም በሚከፈተው የኢትዮጵያ ምክርቤት አዲሱ መንግስት ሥራ ይጀምራል።
✓ በእዚህ ምርጫ የኢትዮጵያን የመንግስት ስሪት ምርጫውን በማደናቀፍ ዕቅድ ተግባር የሸረቡ የቅርብና የሩቅ ቡድኖች በኢትዮጵያ ሕዝብ ጥንቁቅና የቆረጠ የምርጫ ተሳትፎ በእጅጉ ተበሳጭተዋል።
በሰባተኛው የኢትዮጵያ ምርጫ የተሳተፉ ብሔራዊና የክልል ፓርቲዎች ዝርዝር:-
ምንጭ:- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድምንጭ:- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
Friday, May 29, 2026
ከሰባተኛው የኢትዮጵያ ምርጫ በቀጣይ የሚታዩ የሚታዩት ሦስት እውነታዎች
Thursday, April 30, 2026
በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።
Monday, April 20, 2026
በጠ/ሚ/ዐቢይና ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ላይ በውሸት ወሬ የዘመቱት ''አፈ-ጊንጦች'' በቴዲ አፍሮ ዘፈን ሊሸሸጉ ሲሞክሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ እየሳቀባቸው ነው።
- ''የብሔር እና የጎሳ ፖለቲካ አራማጅ ናቸው፣''
- ''ከጀዋር የጽንፍ ሃሳብ ጋር አብረው ይሄዳሉ፣''
- ''ኢትዮጵያን መከፋፈል ይፈልጋሉ፣''
- ''የእገሌ ጎሳ ጠላት ናቸው፣''
- ''የእገሌ ጎሳ ወዳጅ ናቸው፣''
- ''ባሕርዳር ላይ፣ወለጋ ላይ አዲስ አበባ ላይ የተገደለው ሁሉ በእሳቸው ነው፣''
- ሰሞኑን በኢራን የተዘጋው የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ በእሳቸው ነው ለማለት ሩብጉዳይ የቀረው አሉባልታ ወዘተ በአፈ ጊንጦች ተነዛ።
Monday, March 9, 2026
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የሰሞኑ ከራሞት ልዩ ሪፖርታዥ
- በአሁኑ ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱን እና ምእመናንን የሚያምሷት እነማን ናቸው?
- እራሱን ''የሲኖዶስ አስፈጻሚ ኮሚቴ'' እያለ የሚጠራው ማን ነው?
- የቡድኑ ''ሶማትዮ ማኅበር'' እና ''ቀሲስ አየለ'' የሚለው አጀንዳው
- ''ቤተክርስቲያኑ እንዲዘጋ እንፈልጋለን'' የአማሳኝ ቡድኑ የእየሳምንቱ ፉከራ
- የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ምእመናን በአማሾች ሲታመሱ ያደረጉት ምንድን ነው?
- በአሁኑ ጊዜ የምእመናኑ አንድነት እና ሕብረት የበለጠ ጠንክሮ ወጥቷል።
በጥንታዊቷ እና ቀደምት የክርስትና መገኛ ከሆኑት ሀገሮች ውስጥ በሆነችው ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የዓመታት ችግር ፈቺ በሆነ መልክ ሪፖርት እንዲዘጋጅ ቋሚ ሲኖዶስ በወሰነው መሰረት የተቋቋመው እና ከቤተክሕነት፣ከኖርዲክ እና ግሪክ ሀገረስብከት እና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የተገኙበት ልዩ አጣሪ ኮሚቴ በግንቦት 2016 ዓም ለቅዱስ ሲኖዶስ ካቀረበው ሪፖርት መግቢያ ላይ የቀረበው ጽሑፍ በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አመሰራረት ላይ ጥሩ ማብራርያ ይሰጣል። የሪፖርቱ መግቢያ እንዲህ ይነበባል፡
በአሁኑ ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱን እና ምእመናንን የሚያምሷት እነማን ናቸው?
- የመጀመርያው ቡድን ውስጥ ያሉት በጣት የሚቆጠሩት ለዓመታት የግሪክ አቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪነት ዘመን ማለት ቀድሞ አባ ዮሐንስ፣በኋላም የነበሩት ንቡረዕድ አባ ኃይለልዑል ገሪማ ቤተክርስቲያኒቱን ሲያስተዳድሩ በቤተክርሲቲያኒቱ ገንዘብ እንደ የግል ንብረት ሲጠቀሙ የነበሩ፣ወደ ሃገርቤት ከግሪክ ከቀረጥ ነጻ በቤተርክስቲያን ደብዳቤ ሲያስገቡ እና አብረዋቸው ሲሞዳሞዱ የነበሩ የቡድን አባላት የመጀመርያ ተጠቃሽ ናቸው ናቸው።ከእዚህ ቡድን አባላት ውስጥ በሕገወጥ መንገድ የቅስና እና የድቁና ማዕረግ ሳይገባቸው የተቀበሉ ያሉበት ነው። ይህ ቡድን አባላቱ በአሁኑ ጊዜ ከአራት የማይበልጡ ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ ሰላማዊ በመምሰል በምዕመኑ ውስጥ መለያየት የሚነዛ፣በአደባባይ እየተቅለሰለሰ ቤተክርስቲያንን ለማመስ ከሚሮጡ ጋር ከአስተባባሪነት እስከ በቀጥታ ሃሳብ በመስጠት በአጽራረ ቤተክርስቲያንነት የተሰለፈ ግለሰብ አለበት።ይሄው ግለሰብ በሀገርቤትም በንዋየ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ ቀደም ብሎ በቅዱስ ዑርዔል ቤተክርስቲያን በሕገወጥ መልክ ሱቅ የነበረው እና በአሁኑ ጊዜ በሌላ ቦታ ሱቅ ያለው ሲሆን፣ ከግሪክ የሚመጡ እቃዎችን ከቀረጥ በነጻ በማስገባት ከፍተኛ ምዝበራ ላይ የተሰማራ ግለሰብ ነው።
- በሁለተኛው ቡድን ውስጥ የሚገኙት በጣት የሚቆጠሩ የአማሽ ቡድን አባላት በቀደመው የሰበካ አባላት የነበሩ፣የቤተክርስቲያኒቱን ንብረት በአግባቡ መያዝ አለመቻል ብቻ ሳይሆን፣እስካሁንም ሪፖርት እንዲያቀርቡ እና ንብረት እንዲያስረክቡ በቅርቡም ጭምር ተጠይቀው አሻፈረኝ ያሉ፣ከተለያዩ የስለት የወርቅ ስጦታዎች እስከ የቤተክርስቲያኒቱን ሚኒባስ አላስረክብም ብለው መኪናው በሕግ እንዲያስረክቡ ተደርገው ሌሎቹን በተመለከተ በምእመኑ በተቋቋመ አጣሪ ኮሚቴ ሪፖርት ቀርቦ ምላሽ ያልሰጡ፣ከሰንበት ትምሕርት ቤት ቲሸርት ሸጦ ገንዘቡን በአደባባይ ወደ ኪሱ የከተተ እና እስከ ሁለት ሺህ ኢሮ ከሰንበት ትምሕርት ቤት ንዋየ ቅዱሳን መሸጫ ሱቅ በድፍረት ጠፋብኝ ብሎ የተዘባበተ ግለሰብ ያለበት ቡድን ነው።
- በሦስተኛው ቡድን ውስጥ የሚገኙት አሁንም በጣት የሚቆጠር ቡድን ያለበት ቡድን ባንዳ እና ባዳ የሚባለው ቡድን ነው። በእዚህ ቡድን ውስጥ የሚገኙት ጸረ ኢትዮጵያ አቋም መመረዛቸው በስራቸው ያስመሰከሩ ናቸው። በእዚህ ውስጥ ለኢትዮጵያ ባዳ የሆኑ ነገር ግን ለቤተክርስቲያን የሚቆረቆሩ መስለው እኛኑ መስለው የሚያምሱ ናቸው። ዓላማቸው የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ከግሪክ መንቀል፣ምእመኑን ማወክ፣ኢትዮጵያውያን በቤተክርስቲያናዊ እና ብሔራዊ ስሜታቸው እንዳይኮሩ ማድረግ እና የኢትዮጵያን ስም በግሪክ ማኅበረሰብ ዘንድ ማጠልሸት ነው።
በእዚህ ውስጥ በቅስና የሚገኙ፣በቀድሞ ሰበካ ውስጥ የነበሩ እና ከኋላ ሆነው በኢትዮጵያውያን ላይ የሚጎነጉኑ ''አካይስት'' አስተሳሰብ ያላቸው የበሉበትን የኢትዮጵያን ወጪት ሰባሪ አሳፋሪዎች ናቸው። ከእነርሱ ጋር አብረው ያሉት ባንዳዎች የቤተክርስቲያን ጉዳይን ለዘመኑ የጥፋት ስራ ለማዋል የቋመጡ ከባዳ ጋር አብረው ቆመንለታል ለሚሉት የረከሰ የባንዳ ተግባር በቤተክርስቲያን ስም ለውሰው ለመንቀሳቀስ የሚሞክሩ አሳፋሪዎች ያሉበት ነው። እዚህ ላይ በኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ስም ፌስ ቡክ ከፍቶ ላለፉት ስባት ዓመታት ያህል የቤተክርስቲያኒቱን ስም ሲያጠለሽ፣የአባቶችን ክብር ሲያዋርድ የኖረ እና እራሱን በመንፈሳዊ ማኅበር ውስጥ ሽጉጦ በአሁኑ ጊዜ ደግሞ አንዴ አዲስ አበባ ቤተክሕነት ሌላ ጊዜ አቴንስ ፖሊስጣብያ በር ላይ እየተንገዋለለ የዘረኛ መርዙን ሸሽጎ የባንዳነት ተግባሩን የሚሰራ ዲያቆን የተካተተበት ነው። ይህ ዲያቆን በተለይ ለዓመታት የግሪክ ጉዳይ እንዳይፈታ በአንድ የቤተክሕነት አባት አገላለጽ ሲናገር ''የእባብ መርዝ የሚተፋ'' ያሉት ግለሰብ በሀገረ ስብከቱና በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መሃል ችግር እንዲፈጠር የሰርክ ጉባዔ ቀመስ በሆኑ ጥቅሶች ምእመኑን በፌስቡክ ሲያምስ የኖረ እና አሁንም እያመሰ የሚገኝ ግለሰብ ነው። - በአራተኛ ቡድን ውስጥ ያሉት ጥቂት ግለሰቦች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነትን ለመበረዝ የሚቅበዘበዙ ቡድን አባላት ናቸው። በእዚህ ስር ያሉት ከቤተክርስቲያኒቱ ዶግማና ቀኖና ውጪ በሆነ መልክ መሰረተ እመነቷን ለመበረዝ ምእመኑን ለመክፈል የሚሮጡ የሃይማኖት ቀሳጮች ናቸው።እነኝህ በቤተክርስቲያን ውስጥ ኦርቶዶክሳውያን የሚመስሉ ነገር ግን ቤተክርስቲያኒቱ እንድትጠላ በቀጥታ በማናቸው ቤተክርስቲያንን በሚያውኩ ተግባራት ውስጥ ይሰማራሉ።
በእዚህ መሰረት ቀሲስ አየለ ከላይ ከተጠቀሰው ቡድን ጋር በመሆን እስካለፈው እሑድ ድረስ በተለያዩ ሳምንታት ለ6 እሑዶች ጊዜ የሰንበት ቅዳሴ እንዳይቀደስ ከማወክ አልፈው ምእመናን ላይ ፖሊስ በመጥራት ቤተክርስቲያኒቱ ዙርያ ያሉ ነዋሪዎች ጭምር እንዲታወኩ አድርገዋል።ይህንን ጉዳይ የተመለከተው ምእመን ከአንድ ሳምንት በፊት መክሮ ቀሲስ አየለ መቅደስ የሚገቡት አዲሱ አስተዳዳሪ ከመጡ በኋላ ጉዳዩ በካሕናት ጉባዔ ከታየ በኋላ ነው የሚለውን ሃሳብ ወደጎን በማድረግ ወደ መቅደስ እንዲገቡ በሚለው ጉዳይ ላይ ሃሳብ ከተሰጠ በኋላ ባለፈው ሳምንት እሑድ ወደ መቅደስ እንዲገቡ ሲጠየቁ ቀድሞም ምክሩ ከአማሽ ቡድኑ ጋር ስለነበረ የአማሽ ቡድኑ ባሳለፍነው እሑድ የካቲት 29፣2018 ዓም በቤተክርስቲያን ውስጥ ገብተው የሚከተሉትን ጸያፍ ተግባራት ፈጸሙ። ይሄውም፡
- ቤተክርስቲያን ውስጥ በካሕናት ላይ እጅግ አስነዋሪ ስድብ፣እና ለመደብደብ መገባበዝ፣
- በቤተክርስቲያን ወንበር ላይ ቆመው ፊሽካ እየነፉ የቡናቤት ስድቦች መሳደብ፣
- በፉጨት እና ከዘፈን ባልተናነሰ ድምፅ ማቅራራት፣
- የቤተክርስቲያንን ወንበር እየገለበጡ መዘባበት እና ሌሎች እጅግ ለአእምሮ የሚከብዱ ተግባራትን በቤተክርስቲያን ውስጥ ሲፈጸም ተስተውሏል።
======================////===========
የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።
Foto : Fana digital የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም...
-
The Ethiopian herald News Paper August 20 , 2020 BY STAFF REPORTER Addis Ababa ************************** (EPA) ADDIS ABABA - Over sixty-mil...
-
አድሚራል ጄምስ ስታርቪድስን =============== ጉዳያችን /Gudayachn =============== ብሉምበርግ የተሰኘው የአሜሪካ ድረገፅ በፖለቲካ እና ፖሊሲ አምድ ስር የአድሚራል ጄምስ ስታርቪድስን አሜሪካ ኢትዮጵ...
-
(በጌታቸው በቀለ የጉዳያችን ገፅ አዘጋጅ) ''ሰኔ እና ሰኞ ሲገጥም ጥሩ አይደለም'' የሚለውን አባባል በተለምዶ ይነገራል።ለምን? ለሚለው ምላሽ ግን አላገኘሁም።ሰኔ እና ሰኞ ገጠመ ለመጥፎ አባባል ...




















