ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, September 21, 2023

''አክቲቪዝም ከጆርናሊዝም'' የደባለቀባቸው ዩቱበሮች በአማራ ክልል የሚፈሰው የመከላከያ እና የአማራ ክልል ህዝብ ደም አልታያቸው ብሏል። በኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሊባሉ ይገባል።


  • የሰው ደም እየፈሰሰ መከላከያና የአማራ ክልል ታጣቂ ኃይል አይነጋገር የሚሉት በውጪ ሀገር ሶፋ ላይ የተቀመጡት መሆናቸውን ልብ ይሏል።
  • የሰላም ንግግሮችን ለማጣጣል የሚሞክሩትን አጥብቀን መቃወም ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታችን ነው።
============
ጉዳያችን 
============

ኢትዮጵያ በወንድማማቾች ጦርነት ስትታመስ 50 ሙሉ ዓመት ዘንድሮ ይሞላታል። የኢትዮጵያ አብዮት በ1966 ዓም ከፈነዳ እነሆ በያዝነው 2016 ዓም 50 ዓመት ይሞላዋል።የወቅቱን ለውጥ ተከትሎ ከተነሳው የቀይሽብር እና ነጭ ሽብር ፍጅት ጀምሮ ከሻብያ እና በኋላ የእርሱ ውላጅ የሆነው ህወሓት ጋር ለ17 ዓመታት የተደረገው ጦርነት መቶ ሺዎችን ገብሮ የሃገሪቱን አንጡራ ሃብት በልቶ፣በጣት የሚቆጠሩ ስደተኞች የነበሯት ኢትዮጵያ ልጆቿ እንደጨው በመላው ዓለም ተዘርተው የወታደራዊ መንግስት ወድቆ የጎሳ ፖለቲካ የሚያቀነቅነው የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት ሌላ የመከራ ምዕራፍ በኢትዮጵያ ላይ ከፈተ።

በ27 ዓመቱ የጎሳ ፖለቲካ የኢትዮጵያ ልጆች ስደት ከአውሮፓና አሜሪካ እንዲሁም ጎረቤት የአፍሪካ ሀገሮች ወደ መካከለኛው ምስራቅ የኢትዮጵያ የነገ ተስፋ የሆኑ ወጣት ልጆች የስደት ዘመን ሆነ። ከግማሽ ሚልዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ባብዛኛው ወጣት ሴት እህቶቻችን በመካከለኛው ምስራቅ ብቻ ተበተኑ፣ኢትዮጵያ የባህር በር የሌላት ባለ 120 ሚልዮን ህዝብ ሆነች። ይህ ሁሉ ጥፋት ከውጭ ብቻ የተሴረ የሴራ ውጤት ብቻ አይደለም። የእኛው በጥቅምና በስልጣን ያበዱ ፖለቲከኞቻችን የተደናበረ የፖለቲካ አዙሪት ውጤትም ነው።

ባለፉት 5 ዓመታትም የኢትዮጵያ የጸጥታ ሁኔታ ችግር ተባብሶ የጎሳ ፖለቲካው የበለጠ አገንግኖ ወጥቶ የክልሎች የግጦሽ ቦታ እና ትንንሽ መንደሮች የእኔ ነው የእኔ ነው ተራ ንትርክ ሁሉ እስከ ሚልዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን የሚያፈናቅል፣ሺዎችን የሚያሰድድ እና ወደ የበለጠ ድህነት የሚከት ሆነ። ኢትዮጵያ የተሻለ መንገድ ለመያዝ ስትታትር አዳዲስ ግጭቶች እየተፈለፈሉ እና ፖለቲከኞቻችን ደግሞ ዘለው እያቦኩት (እነርሱን እሳቱ አይነካቸውም) ህዝቡን ለበለጠ መከራ እየማገዱ ሀገሪቱን የሽብር ምድር ለማድረግ ከላይ ታች እያሉ ነው።

መንግስት በሌላ በኩል የቆረጠ አቋም እና ወጥ የሆነ አሰራር እና የጸጥታ መዋቅር እንደመመስረት በየክልሉ ያሉ የጎሳ አደረጃጀቶች እና ታጣቂዎች ከወለጋ እስከ ቤኒሻንጉል ከጌድዮ እስከ ቦረና ህዝብ ሲያፈናቅሉና ከተሞች ሲያወድሙ የመረረ እርምጃ ከመውሰድ ጋር የተለየ እና አዲስ አቅጣጫ ማስቀመጥ ስለተሳነው ኢትዮጵያ በጎበዝ አለቃ የምትመራ ሀገር እስክትመስል ድረስ ከአንዱ የሀገሪቱ ክፍል ወደ አንዱ የሀገሪቱ ክፍል መሄድ እንደ ትልቅ ዕድል እንዲቆጠር ሆኗል።

ወደወቅታዊው የሀገራችን ሁኔታ ስንመጣ በአማራ ክልል እና በተቀረው የኢትዮጵያ ክፍል ከፍተኛ ቅቡልነት የነበረው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግስት በኦሮምያ ክልል ያለው የብልጽግና የቀድሞው ኦህዴድና በውስጡ የተሰገሰገው የኦነግ ሸኔ ቡድን ባራመዱት የጎሳ ፖለቲካ እና የማንአለብኝነት ጥቃት በተለይ የአማራ ተወላጆች በሆኑት የወለጋ እና ሌሎች ቦታዎች ላይ የፈጸሙት ግፍ አሁን በአማራ ክልል ለተነሳው የጸጥታ መደፍረስ ምክንያት ሆኗል።በእዚህም በብሄርተኝነት የመቀስቀስ ስራው ለብሄርተኞች አመቺ ሆኖላቸዋል።  

''አክቲቪዝም ከጆርናሊዝም'' የደባለቀባቸው ዩቱበሮች በአማራ ክልል የሚፈሰው የመከላከያ እና የክልሉ ህዝብ ደም አልታያቸው ብሏል። በኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሊባሉ ይገባል።

በአማራ ክልል የተነሳው ቁጣ በኦሮምያ ክልል አክራሪ ቡድኖች የፈጸሙት ጥላቻን የተሞላ የግፍ ውጤት መሆኑ ተደጋግሞ ተነግሯል።ይህ ማለት ግን ኢትዮጵያ የመከላከያ ኃይሏን በራሷ ህዝብ ፈጅታ ሌላ የታሪክ ጠባሳ ይቀመጥ ማለት አይደለም። መንግስት በውስጡ ያሉትን በኦሮሞ ስም የሚነግዱትን አክራሪ ብሔርተኞች ማስወጣት ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን ወደ የለየለት የእርስበርስ ጦርነት የሚከተውን የጎሳ ፖለቲካ እና አደረጃጀት በሕግ የማገድ ውሳኔ ድረስ ካልሄደ ነገሮች ከተበላሹ በኋላ እና ሁሉም ነፍጥ ካነሳ በኋላ ''እንደ 1966ቱ የእንዳልካቸው ካቢኔ '' በኋላ ከረፈደ የጎሳ ፖለቲካ ታግዷል ወዘተ ቢሉት አይሰራም። ሁሉም መከወን ያለበት በጊዜው ነው።

ከእዚህ ጋር በተያያዘ በአሁኑ ወቅት በአማራ ክልል ያለው በመከላከያና በአማራ ክልል ታጣቂ (ፋኖ) መሃከል ያለው ግጭት በምንም መልኩ መቆም ያለበትና ያሉት ጉዳዮች ሁሉ ወደ ንግግር መምጣት አለባቸው። ይህ የመነጋገር ጉዳይ ሲነሳ ያዙኝ ልቀቁኝ የሚሉት አክቲቪዝም ከጆርናሊዝም የተደባለቀባቸው ዩቱበሮች ናቸው። እነኝህ ዩቱበሮች ከውጭ ሆነው ''እስከ መጨረሻው ተጫረሱ'' ዓይነት መልዕክት ብቻ ሳይሆን ወደ ንግግር ይመጣ ሲባል ''ይሄ ባንዳ፣የአማራ ጠላት '' እያሉ ከምሁራን እስከ የሃይማኖት አባቶች በመሳደብ እና በማሸማቀቅ ሰው ለሀገሩ ያለውን ሃሳብ በነጻነት እንዳይሰጥ ከሽብር ያላነሰ ተግባር እየፈጸሙበት ነው። የዛሬ 50 ዓመት በኢትዮጵያ የነበረው ቀይ ሽብር ብቻ አልነበረም።የወቅቱ መንግስት ተቃዋሚዎችም ነጭ ብለው የሚጠሩት ሽብር ነበራቸው። በወቅቱ ሁሉም ለሚሰራው ለራሱ እና ለደጋፊዎቹ '' እንደ ቅዱስ ስራ '' እየተወሰደ ይሞከሻሹበት ነበር። ዛሬም በ21ኛው ክ/ዘመን ተቀምጦ '' ብልጽግና የሆነውን በሙሉ ፍጀው፣በለው'' የሚባልበት ጊዜ ላይ ተደርሷል። በሌላ በኩል የፋኖ ታጣቂ ብቻ ሳይሆን ለፋኖ የምትደግፉ ናችሁ እየተባሉ ዜጎች ፍዳቸውን እያዩ ነው። ሁሉም እንደየቀይ ሽብር ዘመን የራሱን ያሞግሳል። የአሁኑን የከፋ የሚያደርገው ለአቅመ ጋዜጠኝነት ያልደረሰ ሁሉ ለዩቱብ ክፍያ ብሎ ሀገር ወዳድ መስሎ ግጭቶጭ እንዲጠመቁ ቀን ሙሉ ላይ ታች ሲል መዋሉ ነው። በወንድማማቾች መሃክል ያለ የደም ወሬ በማዛመት ከዩቱብ የተገኘ ገንዘብ ለቤተሰብስ ጤና ይሆናል? ይህንን በጊዜ የምናየው ነው። ዩቱበሮች ስለየምስኪኑ ገበሬ ቁስል አውሮፓና አሜሪካ ተቀምጠው ሊሰማቸው አልቻለም። የእነርሱ ልጆች ትምህርት ቤት እየሄዱ ሃገር ቤት ያለው የገበሬው ልጅ ህይወት ግን ገና አልተሰማቸውም። ይልቁንም ''ከመከላከያ ጋር አንዳች ንግግር ታደርኛ'' እያሉ የማሸማቀቅ እኩይ ተግባራቸውን ቀጥለውበታል። 

ኢትዮጵያ ከእዚህ በላይ የምትሸከመው የጦርነት ትከሻ የላትም። 50 ዓመታት ያህል ደም ፈሶባታል።መንግስት በኦሮምያ ክልል ያለው ጽንፍ የረገጠ አስተሳሰብና የዕብሪት አካሄዶችን አደብ ማስገዛት ብቻ ሳይሆን የጎሳ ፖለቲካውን የሚያከስም የህግ ማዕቀፍ በቶሎ አውጥቶ ስራ ላይ ማዋል አለበት። በአማራ ክልል ያሉት ታጣቂ የፋኖ አባላትም ከመከላከያ ጋር በቶሎ እርቅ ፈጽሞ እና በክልሉ ሰላም እንዲመጣ በመነጋገር የጋራ ኢትዮጵያን ለመጠበቅ መነሳት አለባቸው። ህዝብ ሁሉንም እየታዘበ ነው።ታዝቦ ታዝቦ ለሰላም አልቆም ያለው ማናቸውም ኃይል ላይ ማለትም መንግስት ላይም ሆነ በአማራ ክልል ያለው ታጣቂ ላይ ድንገት ይነሳል። ከእዚህ ሁሉ በፊት ሁሉም አደብ የመግዣ ጊዜው አሁን ነው። የኢትዮጵያ ገበሬ ደግሞ ከፖለቲከኛው በተሻለ መንግስት ምን ማለት እንደሆነ ያውቃል። የመንግስት ድንበር ይፍረስ የሚል አይደለም። ከመጠን ያለፈ የሕግ መጣስ ያስቆጣዋል። ይህ ቁጣ ግን የታጠፈው ሕግ ተመልሶ ሲዘረጋ ይመለሳል።

ባጠቃላይ የባዕዳን ጣልቃ ያልገባበት የመነጋገር እና ኢትዮጵያ ከገባችበት የፖለቲካ ቅርቃር የሚያውጣ የመፍትሄ መንገድ ከመንግስትም ከፋኖም ይጠበቃል። አሜሪካን አውሮፓ ቁጭ ብለው መንግስት ለመገልበጥ ነው መሄድ ያለብህ የሚለው ስብከት ኢትዮጵያን ወደ መበተን ደረጃ የሚያደርስ አደገኛ አካሄድ ስለሆነ ጆሮ ሊሰጠው የሚገባ አይደለም። መንግስት ይቀየራል።የሚቀየረው ግን በጦርነት ክልልን በማውደም አይደለም። ትግል ሲያስፈልግ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሰላማዊ ትግሎች መንገዶች አሉ።ከእዚህ ባለፈ የምርጫ ሰሌዳን ተከትሎ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ የሚፈልገውን በመምረጥና ድምጹ እንዲከበር በመታገል ወደ የሚፈለገው ለውጥ መምጣት ይቻላል።ቢያንስ በ21ኛው ክ/ዘመን መንግስት ባልሰለጠነ መንገድ በማውረድ ሀገር ከመበተን መታደግ የሁሉም ግዴታ መሆኑን ማወቅ አለብን።ከእዚህ ጋር የሰላም ንግግሮችን ለማጣጣል የሚሞክሩትን አጥብቀን መቃወም ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታችን ነው።

+++++++++++++++++++++++++++++


Saturday, September 16, 2023

Is the biblical ark of the covenant hidden in an Ethiopian church?

በመጽሐፍ ቅዱስ የምናውቀው የሙሴ ታቦተ ሕግ በኢትዮጵያ ተደብቋልን? በሚል ርዕስ የኢየሩሳሌም ፖስት ጋዜጣ ዛሬ ቅዳሜ መስከረም 5፣2016 ዓም ምሽት የጻፈው አዲስ ጽሑፍ።

ጽሑፉ ተመራማሪዎች ታቦተ ሕጉ በኢትዮጵያ ለ3 ሺህ ዓመታት ተደብቆ እንደሚገኝ ይገልጻሉ በሚል መግቢያ ይጀምራል።

ሙሉውን ጽሑፍ ከስር ያንብቡ።

በቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴ የተገነባው የአክሱም ጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን።

Is the biblical ark of the covenant hidden in an Ethiopian church? 

  • Researchers claim the ark hidden for 3,000 years in Ethiopia.
By WALLA! 
Published: SEPTEMBER 16, 2023 19:20
Jerusalem Post
===================
Where is the Ark of the Covenant, the vessel that, according to Jewish tradition and the Bible, safeguarded the Tablets of the Covenant?

The gold-coated ark adorned with a gold wreath once resided in the First Temple until the Babylonian army's destruction in 587 BC. While records don't mention its fate, it's improbable that such a sacred and precious object disappeared unnoticed.

So, did it survive the destruction, and if so, where does it rest today?
The ark, also known as the Ark of God or the Ark of the Testimony, was positioned within the Holy of Holies in the First Temple. It held immense significance, described as the primary "seat of the Shekinah," and it hasn't been seen since the First Temple's ruin.

Sages hold two opinions on its whereabouts.

Rabbi Eliezer and Rabbi Shimon believe the ark was taken to Babylon and destroyed, while Rabbi Yehuda claims it remained in the temple's confines but was later relocated and rediscovered elsewhere. The Ark of the Covenant's location remains a mystery that scholars, adventurers, rabbis, and enthusiasts have sought for over 2,000 years.

A peculiarly shaped stone unearthed years ago in the ruins of an ancient temple near Jerusalem raises the possibility that it may be the "great stone" upon which the Ark of the Covenant rested, housing the sacred Tablets of the Covenant.

On the other hand, a substantial number of Bible scholars propose that the ark's final resting place is a church in Ethiopia. They assert that it was clandestinely transported there from Israel during the reign of King Manasseh of Judah (697 BC to 642 BC), and it has remained hidden there for 3,000 years, meticulously guarded by virginal nuns.

For millennia, the ark's whereabouts, said to possess magical powers and bring death to those who touch it, have been enigmatic. Ethiopian Christians contend that the Ark of the Covenant resides in a chapel within the small town of Axum, where they believe it arrived nearly three millennia ago, watched over by a group of nuns who are forbidden to leave the chapel until their demise.

A report by Fox News suggests that the Church of Our Lady Mary of Zion in Axum houses one of the world's most coveted biblical relics, including the Ten Commandments and Aaron's "staff of miracles."

Numerous Torah scholars are convinced that the Ark of the Covenant was covertly transported from its original resting place beneath the Temple Mount all the way to Africa, carried by Jews expelled from Israel during Manasseh's rule. Since its disappearance, multiple theories about its location have surfaced, including submersion in the Sea of Galilee, concealment beneath the Temple Mount's foundation, surrender to the Americans, and the increasingly supported claim of its presence in Ethiopia.

According to the Bible, the Israelites crafted the Ark of the Covenant in the Sinai desert after leaving Egypt. Its vanishing coincided with the Babylonian conquest of Jerusalem in 587 BC.

One account narrates how the Jordan River stood still as priests carrying the ark crossed it, while other stories describe its role in battles where its mystical powers aided the Israelites. When captured by the Philistines, the ark's presence caused outbreaks of tumors and diseases, compelling them to return it to the Israelites. Some tales even mention death befalling anyone who touched or gazed upon the ark.

As mentioned earlier, certain researchers propose that the Ark of the Covenant traveled extensively before ultimately reaching ancient Israel. According to the Maccabees, it was concealed in a cave on Mount Nebo by the prophet Jeremiah. In Hasmoneans 2, it is recounted how Jeremiah discovered a hidden cave on the mountain and buried the Ark of the Covenant, admonishing exiles not to mark its location until God reunites His people from exile and returns them to their homeland.

Another narrative, currently gaining credence, asserts that the Ark of the Covenant found its way to Ethiopia and now resides in the Church of Our Lady Mary of Zion. According to this belief, Ethiopian Orthodox Christians transported it to Axum through Menelik, the son of the Queen of Sheba and King Solomon of Israel, after Jerusalem's fall in 586/587 BC and the destruction of Solomon's Temple.

Britons also claim the ark's possession, with one theory proposing that the Knights Templar, also known as the Order of the Knights of Solomon's Temple, discovered it in Jebel al-Madhbah in Petra, potentially the biblical Mount Sinai. Some legends suggest the Templars hid the Ark of the Covenant in Ethiopia, while another theory suggests British Baron Ralph de Sudeley, known for generous religious donations, transported it to his estate at Temple (temple) Hardwick. Notably, this location is currently owned by the British Ministry of Defense and is securely sealed.

To this day, no definitive historical theory exists about the Ark's fate, with some researchers even questioning its initial existence.

Curious to find out?

You'll need to wait, as Jewish sources prophesy the ark's revelation near the coming of the messiah. The Ramban wrote that it will be unveiled "in the building of the house or in the future wars before the messianic king."




Sunday, September 3, 2023

የግሪካውያን የኢትዮጵያ ወዳጆች ማኅበር እና በኢትዮጵያ የግሪክ ማኅበረሰብ አመራሮች በጣልያን፣ፈረንሳይና ግሪክ የኢትዮጵያ ክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ሃሚሳ ጋር በአቴንስ ከተማ ተገናኙ። የግሪካውያን የኢትዮጵያ ወዳጆች ማኅበር እኤአ መስከረም 30/2023 አቴንስ ላይ ልዩ ዝጅግት አዘጋጅቷል።

ክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ከኢትዮጵያ ወዳጆች የግሪክ ኮሚኒቲ አባላት ጋር በአቴንስ፣ግሪክ


  • ''በአዲስ አበባ የሚገኘው የግሪክ ኮሚኒቲ ከመንግስት ጋር የገባውን ችግር በተመለከተ ጉዳዩ በፖለቲካና ዲፕሎማሲያዎ ደረጃ የሚፈታ ነው '' ክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ሃሚሳ

==========================
ጉዳያችን ልዩ ዘገባ/Gudayachn Exclusive
===========================
የግሪካውያን የኢትዮጵያ ወዳጆች ማኅበር እና በኢትዮጵያ የግሪክ ማኅበረሰብ አመራሮች በጣልያን፣ፈረንሳይና  የኢትዮጵያ ክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ሃሚሳ እና የኤምባሲው ሁለተኛ ጸሐፊ አዲሱ መልካሙ ጋር በአቴንስ ከተማ መገናኘታቸውን ከሰሞኑ ለጉዳያችን ከኢትዮጵያ ወዳጆች ግሪካውያን ማኅበ አመራሮች የደረሳት ዘገባ ያመለክታል።ከክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ጋር የነበረው ውይይት በአቴንስ ሜልያ ሆቴል የተደረገ ሲሆን፣በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ ወዳጆች የግሪክ ማኅበረሰብ ምክትል ፕሬዝዳንት ሚስተር ጆርጂዮስ ሚካኤልደስ፣የዳይሬክተሮች ቦርድ ተወካይ ኪሜትሪዮስ ስትራጋሊስ እና ከአዲስ አበባ የግሪክ ኮሚኒ ማኅበር ፕሬዝዳንት ኦዲስየስ ተገኝተው ነበር።  

በእዚህ ውይይት ላይ በቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴ ለግሪክ ህዝብ የተከናወነ የግብረሰናይ ተግባር የከወኑበት የአቢሲንያ አደባባይ በአቴንስ ከተማ ምክርቤት ስሙን በቋሚነት የማስመዝገብ ስራ ዙርያ ላይ ምክክር መደረጉን ለማወቅ ተችሏል።በእዚህ መሰረት የኢትዮጵያ ወዳጆች የግሪካውያን ማኅበር ቦታው በአቴንስ ከተማ ምክርቤት እንዲመዘገብ ከአቴንስ ከተማ ከንቲባ ኮስታስ ባኮያኒስ ጋር ስለጉዳዩ መነጋገራቸውን እና ከንቲባው በጎ ምላሽ እንደሰጡ ለጉዳያችን የተላከው የማኅበሩ መረጃ ያብራራል።ክቡር ከንቲባው ማኅበሩ በቦታው ላይ ለማቆም ያቀደው የኢትዮጵያና የግሪክን ታሪካዊ ግንኙነት የሚያስታውስ ሃውልት ስራ በተመለከተ ድጋፋቸው መግለጻቸውን ለማወቅ ተችሏል።

የመስከረም 30/2023 ዓም እኤአ በአቴንስ አቢሲንያ አደባባይ ለሚሰራው የኢትዮጵያና ግሪክ መታሰብይ ሃውልት ማስጀመርያ መርሃግብር በተመለከተ ማብራርያ የተሰጠ ሲሆን በዝግጅቱ ለመታሰብያ ሃውልቱ ማሰርያ የገንዘብ ማሰባሰብያ መርሃግብር የሚኖር ሲሆን ለሃውልቱ ማሰርያ ከሚፈለገው በላይ ገንዘብ ከተገኘ በኢትዮጵያ በቦረና ለውሃ ማውጫ ተግባር እንደሚውል ተወስቷል።

ይህ በእንዲህ እያለ በአዲስ አበባ የሚገኘው የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርትቤት ከትምህርት ሚኒስትር ጋር የተገባው ውዝግብ አስመልክቶ ማብራርያ ለክብርት አምባሳደር ተሰጥቷል።በእዚ መሰረት የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርትቤቱ ጉዳይ ላይ የተነሱትን ውዝግቦች አስመልክቶ ማብራርያ ተሰጥቷል። በአዲስ አበባ የሚገኘው የግሪክ ኮሚኒቲ ትምሕርትቤት በተመለከት ጉዳያችን የዘገብችውን ዝርዝር ጉዳይ በእዚህ ሊንክ ተጭነው ያንብቡ።በእዚሁ ስብሰባ ላይ የአዲስ አበባ ግሪክ ኮሚኒቲ ማህበር ፕሬዝዳንት የኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስቴር በኮሚኒቲው ትምህርትቤት ላይ የወሰደውን እርምጃ አስታውሰው እኛ ወደ ፍርድ ቤት መሮጥ የምንፈልግ ማህበረሰብ ሳንሆን የኢትዮጵያን ህግ የሚያከብር ማህበረሰብ ነን ሲሉ አሳስበዋል።

በውይይቱ ላይ አምባሳደር ዴሚቱ በሰጡት ምላሽ :

በሁለቱ ህዝቦች መካከል ያለው የቆየ ግንኙነት ጠንካራ በመሆኑ በቀጣይነትም ተባብረን መቀጠል አለብን። ለብዙ መቶ ዓመታት ወደ የነበሩ ግንኙነቶች እንደነበሩ ጠቅሰው፣ የትምህርት ቤቱ ጉዳይ በፖለቲካ እና በዲፕሎማሲያዊ ደረጃ የሚፈታ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት የማህበረሰቡን ንብረት የመውረስ ዓላማ እንደሌለው አሳስበዋል።

በአቢሲኒያ አደባባይ በሚሰራው ሀውልት ጉዳይ ላይ የሁለቱን ህዝቦች ግንኙነት ለትውልድ ለማስተላለፍ ጥረት የሚያመላክት በመሆኑ እጅግ ጠቃሚ ተነሳሽነት ነው በማለት አምባሳደሯ አብራርተዋል። ሀውልቱ በጋራ በኢትዮጵያና ግሪክ ተቀርጾ የሁለቱን ህዝቦች የቆየ ግንኙነት የሚያንፀባርቅ እንዲሆን እና የሃውልቱ ምረቃ ላይ የሁለቱ ሃገሮች ጠቅላይ ሚኒስትሮች የሚገኙበት እንዲሆን ምኞታቸውን ገልጸዋል።ከእዚህ በተጨማሪ በጥቅምት ወር ለአበበ ቢቂላ መታሰብያ በአቴንስ አንድዓይነት ዝግጅት ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተነስቷል።

በመጨረሻም የኢትዮጵያውያን ወዳጆች በግሪክ ማኅበር በቀጣይ ከአምባሳደሯ ጋር በማኅበሩ ጽህፈት ቤት ዳግም እንደሚገናኙና በጋራእራት እንደሚመገቡ ተስፋቸውን ገልጸው እጅግ መግባባት ለሰፈነበት ስብሰባ ምስጋናቸውን አቅርበው የዕለቱ ስብሰባ ተጠናቋል።

ከእዚህ በታች የኢትዮጵያውያን ወዳጆች የግሪካውያን ማኅበር ለጉዳያችን ውይይቱን አስመልክቶ የላከው የግሪክኛ ቋንቋ ትርጉም ከእዚህ በታች ይመልከቱ።
=================

MEETING OF THE ASSOCIATION OF GREEKS OF ETHIOPIA (A.G.E.) WITH THE ETHIOPIAN AMBASSADOR

On Thursday, August 24th, at the MELIA Hotel in Athens, a delegation of the Board of Directors of A.G.E., consisting of the 2nd Vice President Mr. Georgios Michaelides, the Treasurer Mr. Theodoros Panas and the member of the Board of Directors Mr. Dimitrios Stragalis, together with the President of the Greek Community Association of Addis Ababa Mr. Odysseas Parris, had a meeting with the Ambassador of Ethiopia to Italy who is accredited in Greece Mrs. Demitu Hambisa Bonsa, who was accompanied by the Second Secretary of the Embassy Mr. Addisu Melkamu Kebede.

The 2nd Vice President, referred to the intervention of the A.G.E. to the Municipality of Athens when rumors circulated about renaming of the historic Abyssinia Square in Monastiraki and the assurance of the Mayor of Athens Mr. Kostas Bakoyannis that there is no such intention. The Mayor supported the proposal of A.G.E. for the placement of a memorial monument and signage.

The 2nd Vice President noted the positive response of the Ethiopian Community living in Greece to the initiative to create this monument that will mark the long-standing relations between the two peoples. He said that the cost will be covered by sponsorships and actions of members and friends of S.E.A and Ethiopian Communities living in Greece and other countries abroad. He stressed that if the amount raised exceeds the cost of the monument, the remaining amount will be allocated to the BORENA area for the creation of a drinking water well, according to the wish of the Ethiopian Community in Greece.

The September 30, 2023 event at Abyssinia Square will mark the beginning of the celebrations for a century of the renaming of the Square by decision of the Municipality of Athens in 1924 to Abyssinia Square after the significant donation given by Ethiopia to the Greek refugees of the Asia Minor Catastrophe, and the over a century establishment of diplomatic relations.

The President of the Greek Community Association of Addis Ababa, reported on actions and claims of the Ethiopian Ministry of Education, which attempted to convert the English section of the Greek Community Schools owned by the Greek Community Association of AA, into a Charitable Endowment. A form that means the transfer of ownership of the school buildings through the Endowment to the Ethiopian State and dispossession of the Community's property. For the operation of the English section, the Greek Community Association of AA has established a new organization provided by the legislation for establishing an INTERNATIONAL SCHOOL from the 2023-24 school year and requested permission, which was not granted. He stressed that we are not a Community that wants to run to court but a Community that operates respecting Ethiopian laws.

He referred to the fact of the appointment of an Interim Administration by designs of the Ministry of Education, without any discussions or consultations, for the management of the English section of the school. The Interim Administration has exceeded its mandate by prohibiting the Board members of the Community to have access to the premises of the Community, issuing orders for the removal of residents from the houses that the community had provided them, etc. Still in excess of its authority, it is involved in purely community matters such as its social policy on indigent people, the management of the Greek St. Frumentius Church, the Cemetery, etc. Lastly they interfere in the Greek Section of the Schools that operate under the Greek Ministry of Education.

He pointed out that in May, the country's auditing mechanisms have taken the accounting documents of the Community for audit. No findings have been announced and the Bank accounts of both the Community and the personal accounts of the members of the Board of Directors of the Community have been frozen, despite the fact that the current Board, it is only one year in office, and since the beginning it met with this situation of interference.

He informed the Ambassador that the ownership of the Community Schools is not the same as the other schools where land was allocated for building. The Greek Community Schools were built on land which was purchased by the Greek community from the donations and sponsorships of its members.

The 2nd Vice President pointed that the Greek Community Association of AA has the full support of A.G.E., since A.G.E. represents the vast majority of the Community members living in Ethiopia at the time of the great exodus, who created and sustained the Community property, and that were forced to leave by the Derg Regime in 1975-76.

The Treasurer, Mr. Panas Theodoros, informed about the Marathon Road Museum and the request of the Municipality of Marathon to enrich the museum with exhibits from Ethiopian marathon runners. He also mentioned the cooperation of the A.G.E. with the "Pelargos" Association, which are families who have adopted children from Ethiopia, to teach Ethiopian culture to these children. From the bilingual books of "Pelargos” a part goes to support the literacy of young people in Ethiopia.

The Ambassador's statement was:

The long-standing relations between the two peoples have been strong and we must continue to deepen them. Relations that go back for hundreds of years.

The issue of the School will be resolved at the political and diplomatic level and she stressed that it is not the intention of the Ethiopian Government to take over the Community property. She regretted the turn the matter had taken.

On the issue of the monument in Abyssinia Square, she said that it is a very important initiative because that will show to future generations the relations between the two peoples. The initiative should be raised to a higher level, with the participation of the Ethiopian Ministry of Tourism and Culture, and when the unveiling ceremony is held, the two Prime Ministers should be invited to be present. She said that they have a wish that the monument should be jointly designed and reflect the long-standing relationship between the two peoples and asked to see the proposal of A.G.E.

She pointed out that they are planning some event for Abebe Bikila in Athens in October, of which they will inform A.G.E. in due time.

Regarding the marathon road museum, the Embassy's Second Secretary said that he would support the effort and took the initiative to find exhibits.

On the part of A.G.E. thanks were expressed for the time the Ambassador took to inform the Association and invited her on her next visit to be received at the A.G.E. offices for a briefing and then to have a dinner.

The whole discussion took place in an extremely friendly and family-like environment and all agreed to continue the constructive channel of communication that has started.

On August 25, a meeting took place between the President of A.G.E. Dr. Alexandros Grous, who came urgently and met with the Ambassador of Ethiopia.

============///==========

Tuesday, August 29, 2023

ኢትዮጵያ በብሪክስ አባል መሆኗ የአፍሪካ ሕብረት ከሀምሳ ዓመታት በፊት በአዲስ አበባ ከተመሰረተ በኋላ የተገኘ የመጀመርያ ከፍተኛው የዲፕሎማሲ ድል ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው።

============
ጉዳያችን ምጥን
===========

ብራዚል፣ሩስያ፣ህንድና ደቡብ አፍሪካ በጥምረት የመሰረቱት ብሪክስን ለመቀላቀል ቬኒዝዌላ፣ኢንዶኔዥያና አልጀርያን ጨምሮ 23 ሀገሮች ያመለከቱ ቢሆንም በመጪው ጥር 1፣2024 ዓም እኤአ ጀምሮ ብሪክስ  የተቀበላቸው ሀገሮች ግን ኢትዮጵያን ጨምሮ ስድስት ሀገሮችን ብቻ እንዲሆኑ በሙሉ ድምጽ ወስኗል። እነርሱም ኢትዮጵያ፣ግብፅ፣ኢራን፣የተባበሩት አረብ ኢምሬት፣ሳውዳረብያ እና አርጀንቲናን ተቀብሏል።

ብሪክስ ኢትዮጵያን ከሳሃራ ሀገሮች በታች በብቸኝነት ሲመርጣት ከአፍሪካ ደቡብ አፍሪካን ሳንጨምር ከሁለቱ አንዱ ማለትም ከግብጽ ጋር መርጧታል። ይህ የብሪክስ ኢትዮጵያን የመቀበል ጉዳይ አንዳንድ የምዕራብ ሀገሮችን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ሀገሮችም ለምሳሌ ናይጄርያ የመሳሰሉ ሀገሮች የተጽዕኖ አቅም በኢትዮጵያ በበለጠ ደረጃ ጥላ እንዳጠላበት በትልጽ ታይቷል። ጉዳዩ ኢትዮጵያ አሁን አሰላለፏ ከእነ ብራዚል፣ኢራን፣የተባበሩት አረብ ኢምሬትና አርጀንቲና ጋር ያለው ጠንካራ የሚባል ኢኮኖሚ አንጻር ያላትን መጪ የማደግ አቅም፣የፈተናዎች የመቋቋም አቅምም፣ ለዓለም ካበረከተችው ታሪካዊ አስተዋጽኦ፣ወሳኝ እና ስልታዊ አቀማመጥ፣የተፈጥሮ ሃብት፣ከአፍሪካ ሁለተኛ የህዝብ ብዛት እና ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ስራ ሁሉ ኢትዮጵያ ተመራጭ ሀገር አድርጓታል።

''ሠላሳ ሚልዮን ህዝብን በአራት ሚልዮን ህዝብ የምንቀይር ሞኝ አይደለንም ''

ሠላሳ ሚልዮን ህዝብን በአራት ሚልዮን ህዝብ የምንቀይር ሞኝ አይደለንም ያሉት በ1969 ዓም በኢትዮጵያ የሩስያው አምባሳደር ነበሩ። ለእዚህ ምላሻቸው መነሻው ደግሞ ሩስያ ሱማልያን ስታስታጥቅ ቆይታ ለምን ወደ ኢትዮጵያ ፊቷን በፍጥነት አዙራ የኢትዮጵያ አጋር ሆነች? የሚል ጥያቄ ሲጠየቁ ነበር። በወቅቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት 30 ሚልዮን ሲሆን ሱማልያ 4 ሚልዮን ህዝብ ነበራት። ዛሬም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከናይጀርያ ቀጥላ ሁለተኛ የህዝብ ብዛት ያላት ባለ 123 ሚልዮን ህዝብ መሆኗ ብቻ በአፍሪካ ቀንድም ሆነ በመካከለኛው ምስራቅ ላይ ያላት ተጽዕኖ በቀላሉ አይታይም። አንዳንዶች ብሪክስ ኤርትራ ካላት የጸረ ምዕራቡ አቋም አንጻር ለአባልነት ይጋብዛታል ብለው የሚያስቡ ነበሩ። ነገር ግን ጉዳዩ የ120 ሚልዮን ህዝብን የመምረጥ ስሌት ለብሪክስ አባላት ከባድ ሂሳብ አይደለም። 
 
ብዙ የአፍሪካ ሀገሮች የብሪክስ አባል ለመሆን ቢያስቡም የሩቅ ህልም ሆኖባቸዋል።

የብሪክስ አባል ሆኖ በቀጣይ ከምዕራብም ሆነ ከብሪክስ አባላት ጋር የልማት አጋርነትን ማጎልበት የብዙ አፍሪካ ሀገሮች ምኞት ነው። በእዚህም በኢትዮጵያ በብዙ በአዎንታዊ መልኩ ቀንተዋል። የናይጀርያ አንዳንድ ጋዜጦች መንደሪኑን ከዛፉ ለመቅጠፍ የዘለችው ጦጣ በዝላይ አለመድረሷን ስታውቅ ድሮም መንደሪኑ አይጣፍጥም ብላ ሳትቀምስ እንደሄደችው ዓይነት ነው። ናይጀርያ እንዴት አመልክታ አልገባችም ለሚለው አንዳንድ ምሁራን ምላሽ ለመስጠት ብሪክስ በቅርቡ ውጤቱ የሚታይ አይደለም በረጅም ጊዜ ነው የሚታየው የሚል ጽሑፍ በመጻፍ ምሁራኑን ለማጽናናት ሞክረዋል።

ከሳሃራ በታች ያሉ ሀገሮች ኢትዮጵያ ያላትን ያህል የምጣኔ ሃብት ነጻነት ስለሌላቸው ዘው ብለው ብሪክስ ውስጥ ቢገቡ በሚቀጥለው ቀን ከባንኮች እስከ ግዙፍ የምጣኔ ሃብት ተቋም ድረስ የተያዙት በውጪ ኩባንያዎች በመሆኑ እንደፈለጉ የመወሰን አቅማቸው የሚታሰብ አይደለም። የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት በምንም መልኩ አሁንም በውጭ ብድር እና እርዳታ የታገዘ ቢሆንም ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች አንጻር በአንጻራዊ መልኩ የተሻለ የተጽዕኖ መቋቋም አቅም ይታይበታል። ከሁሉም ደግሞ ቀድሞ ከነበሩት ሦስት መንግስታትም ጊዜም ቢሆን ኢትዮጵያ አሁንም ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች አንጻር አንጻራዊ ነጻነት ያላት ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ፖሊሲ አውጪው የመወሰን አቅሙ የተሻለ ነው። የብሪክስ መስራቾችም በናይጀርያ እና በኢትዮጵያ መሃል ያለው የመወሰን የነበረ አቅም የገባቸው ይመስላል።

የብሪክስ አባል መሆን ማለት የምዕራብ ግንኙነትን ማራገፍ ማለት አይደለም።

ኢትዮጵያ ካለፉት ታሪኳ ልትማር ይገባል። ብሪክስም ይጠቅማታል፣ከምዕራቡ ጋርም ያላት ግንኙነት ይጠቅማታል።በቀዝቃዛው ጦርነት ዘመን ብዙ ሀገሮች ከአንዱ ጎራ እየተጠቀለሉ ሲገቡ እንደህንድ ያሉ ሀገሮች ደግሞ ገለልተኛ በሚል ድርጅት መስርታ የሁለቱንም የልማት ጥቅም በማግኘት ጊዜውን አልፋዋለች። ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባል ሀገሮች ለምሳሌ ከህንድ እና ከደቡብ አፍሪካ አንጻርም ሲታይ የባህል እና የታሪክ ጋርዮሿ በራሱ ለልማስ ስኬት የሚያመጣው አዎንታዊ አስተዋጾ ቢኖረውም በሚልዮን የሚቆጠሩ ተወላጆቿ የሚኖሩበት እና የቴክኖሎጂ ግንኙነቷም እየሰፋ የመጣው የምዕራቡ ግንኙነቷን ፈጽሞ ገለል ማድረግ አትችልም። አንዳንድ ምሁራን እና ሚድያዎች ጉዳዩን ከቀኝ ወደ ግራ የመዞር ያህል አድርገው ለማቅረብ የሚሞክሩት ትንሽ ብስለት የጎደለው አካሄድ ትክክል አይደለም። በእርግጥ በሳምንቱ መጨረሻ ላይ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የኢትዮጵያ ወደ ብሪክስ የመግባት ጉዳይ አስመልክተው ሲናገሩ ጉዳዩ ከአንድ ጎራ ወደ ሌላ የመሄድ ጉዳይ አለመሆኑን ገልጸዋል። ይህ መሰረታዊ ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያ የማደግ ተስፋዋን በአጋርነት ከቆሙት ጋር ሁሉ አብራ የምትሰራ መሆኗን በተግባር ማሳየት ነገር ግን የበለጠ የሚያግዟት ጋር ተባብራ መስራት አዋጪ መንገዷ ነው።

ኢትዮጵያ በብሪክስ አባል መሆኗ የአፍሪካ ሕብረት ከሀምሳ ዓመታት በፊት በአዲስ አበባ ከተመሰረተ በኋላ የተገኘ የመጀመርያ ከፍተኛው የዲፕሎማሲ ድል ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው።

የኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሆና ከቀዳሚ ስድስት የዓለማችን ሀገሮች ጋር መመረጧ ዛሬም ደጋግመን እኛ እራሳችንን ያላወቅን፣ከሆኑ ዓመታት በኋላ እራሳችንን ዝቅ አድርገን የምናይ እኛ ማን ነን? ማን ነበርን? ዛሬስ የት ላይ ነን? ወደፊስ የምንሄደው? እራሳችንን ሳናውቅ ሌሎች ያወቁን ምናችንን ነው? ብለን ደግመን የመጠየቂያ ጊዜ አሁን ነው። ኢትዮጵያ ላለፉት 50 ዓመታት ገደማ በዓለም ላይ ያላት የዲፕሎማሲ አቅም በተለይ ከንጉሱ ከስልጣን መውረድ በኋላ ደብዝዞ ኖሯል። በንጉሱ ዘመን ከተሰራው የኢትዮጵያን ማዕከልነት እና ዓለም አቀፋዊም ሆነ አህጉራዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ካጎሉት ውስጥ ጉልሁ እና አሁንም ድረስ ቀጣይ ፋና የሆነው የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አሁን የአፍሪካ ሕብረት በአዲስ አበባ የመመስረቱ ጉዳይ ነበር።

የአፍሪካ ሕብረት ጉዳይ ኢትዮጵያን የግዙፍ አህጉራዊ ዲፕሎማሲ የማሳለጥ አቅሟን አሳድጎታል። ከአፍሪካ ሕብረት በኋላ ኢትዮጵያ የባሕር በር አልባ ከመሆኗ እና በምግብ እራሷን ያለመቻሏ ሁሉ ተደማምሮ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ መሪነት አቅም በእጅጉ ከመፈታተን አልፎ ትናንሽ ሀገሮች ከኋላዋ ተነስተው የተሻለ ተጽዕኖ ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ ተመልካች ሆናለች። ከእዚህ ሁሉ በኋላ ኢትዮጵያ ከእነብራዚል፣የተባበሩት አረብ ኢምሬት እና አርጀንቲና ጋር ተጋፍታ ከሳሃራ በታች ካሉ ሀገሮች በሁሉም መስፈርቷ ያለፈውን እና የመጪ ተስፋዋንም ጭምር በሚገባ መርምረው የብሪክስ መስራች ሀገሮች ሲመርጧት ኢትዮጵያን በከፍተኛ ደረጃ ያላትን የዲፕሎማሲ፣ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ግርማ በፍጥነት አሳድጎታል። ይህንን በብዙ ማስረጃዎች ማስረዳት ይቻላል።በእርግጠኝነት ማለት የሚቻለው ግን ኢትዮጵያ በብሪክስ አባል መሆኗ የአፍሪካ ሕብረት ከሀምሳ ዓመታት በፊት በአዲስ አበባ ከተመሰረተ በኋላ የተገኘ የመጀመርያ ከፍተኛው የዲፕሎማሲ ድል ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል መሆኑ ነው። ይህ ደግሞ በርካታ ንግግሮች፣ውይይቶች፣አቅምን አግዝፎ የማቅረብ የተለያዩ ስልቶች እና የነበረ እና ዘላቂ ወዳጅነትን ለማጽናት የተደረጉ በርካታ የዲፕሎማሲ እና ሁለንተናዊ ጥረቶች እንደነበሩ ለመረዳት ከባድ አይደለም።

ለማጠቃለል፣ አሁን የእኛ ቦታ ከእነብራዚል፣አርጀንቲና እና የተባበሩት አረብ ኢምሬት ጋር በእኩል ደረጃ መሆኑና ተፈላጊነታችን በእዚህ ደረጃ መናሩ ለእኛ አልታየን ከሆነ ለሌሎች መታየቱ ግልጽ ሆኗል። የእኛ እንደምንፈለገው ደረጃ መሆን ብቻ ሳይሆን እራሳችንን በምን ያህል የቀረንን ሞልተን በቶሎ ከመረጡንም ከተመረጡት ጋርም በፍጥነት አስተካክለን በፍጥነታቸው ልክ ለመሄድ ተዘጋጅተናል? የሚለውን ጥያቄ መመለሱ ነው ቁም ነገሩ። የማደግ ተስፋችን ከፊታችን ቆሞ እኛ ግን በብሄር ፖለቲካ እና በመንደርተኝነት እየተቧደኑ ከሚገፉን እና ሀገር ከሚበትኑ ጋር ከቆምን ዛሬም ኢትዮጵያ የገጠማትን የማደግ ተስፋ መልሰን የምናጨልም ሆነን የመጪውንም ትውልድ ዕድል ዘጊዎች እንዳንሆን መጠንቀቅ አለብን። ኢትዮጵያ ከሁሉም አጋሮቿ ጋር አብራ እንድትለማ በውስጧ ጋሬጣ የሆኑ ሃሳቦች የሚዘሩባትን መጋፈጥ ብቸኛው አማራጭ ነው።
==================/////===============

Saturday, August 26, 2023

አዲሱ የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ትናንት ዓርብ ነሐሴ 19/2015 ያደረጉት ሙሉ ንግግር።(ቪድዮ)

አቶ አረጋ በመቀሌ የአቶ ሽመልስ ተወካይ ነኝ በማለት ህዝብ ከህዝብ ለማጋጨት የሞከረ ንግግር ያደረጉትን ግለሰብ ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ወቅሰዋል፣ አስጠንቅቀዋል። ሙሉውን ንግግር ይመልከቱ። 
የቪድዮ ምንጭ =አሜኮ


Thursday, August 17, 2023

''አንዱ ሲናገር ሌላው አያቋርጥ!'' የሦስተኛ ክፍል ተማሪዎች ክፍል ውስጥ የሚነገራቸው እና የሚያከብሩትን መመርያ ፓርላማው ገና አልተለማመደውም።

የተከበሩ አቶ ባያብል ሙላቴ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል።

======
ጉዳያችን
======

በእዚህ ሳምንት የተሰበሰበው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ብዙ ኢትዮጵያውያንን የስብሰባ አካሄዱ ደረጃውን የጠበቀ ሆኖ አላገኘውም።የተጀመረ ሃሳብ አዳምጦ ሃሳቡ ላይ ሌላ ሃሳብ ከመስጠት ይልቅ በማኅበራዊ ሚድያ አሉባልታ በሰሙት ወሬ እራሳቸውን እና የወከሉትን ህዝብ ክብር በማይመጥን ደረጃ ንግግሮችን ሲያቋርጡ እና ሃሳቦችም እንዳይሰጡ ሲሞክሩ ትዝብት ላይ ወድቀዋል።

የተወካዮች ምክርቤት አባላት የተሰበሰቡት ኢትዮጵያውያንን ወክለው ነው። ኢትዮጵያውያንን መወከል ማለት ደግሞ የተከበረ ባሕል፣መከባበርና አስተዋይነት አብሮ ሊታይበት ይገባ ነበር። አንድ የምክር ቤት አባል ወደ ምክርቤቱ ሲገባ የፓርቲዬን ሃሳብ በእጅም በእግርም ብዬ ማሳለፍ ብቻ በሚል ከሃሳብ ሙግት ውስጥ የሚገኝ አዲስ ለሃገር የሚበጅ በጎ ሃሳብ ፈልቅቆ ለማግኘት የሚይስችል ስብዕና ይዞ ካልገባ ከሚቀመጥበት ወንበር ብዙ አይለይም። የሚባለውን ሁሉ እየተቀበለ ለማሳለፍ እንጂ በሃሳብ ለመሞገት ያልተዘጋጀ የፓርላማ አባል እቤቱ ቢቀመጥ እና በሌላ መገናኛ መንገድ ድምጹን መላክም ይችላል።

ህዝብ የፓርላማ አባል የመረጠው እንደራሴ ሆነህ በአፍህ ተናገርልኝ፣ሞግትልኝ በአዕምሮህ እኔን ሆነህ አስበህ ሃሳብ አፍልቅልኝ በማለት እንጂ ሌላው የሚናገረውን አዳምጦ በሚገባ እና አሳማኝ በሆነ ምክንያት ከማቅረብ ይልቅ ህጻናት የማያደርጉትን እየተንጫጫ የሚናገር ሰው እንዲያቋርጥ አይደለም።''አንዱ ሲናገር ሌላው አያቋርጥ!'' የሦስተኛ ክፍል ተማሪዎች ክፍል ውስጥ የሚነገራቸው እና የሚያከብሩትን መመርያ ፓርላማው ገና ያልለመደው ትንሽ ቆይቶ በሱማሌ የምናየው ዓይነት የፓርላማ መንጫጫት እንዳናይ እየፈራን ነው። ትልቅ ሰው ባትፈሩ፣ልጆች እየተመለከቷችሁ ነው። እነርሱ በትምህርት ቤታቸው አስተማሪ አንዱ ተናግሮ ሳይጨርስ ሌላው አይናገርም! የሚለውን መመርያ ክፍላቸው ውስጥ አይጥሱትም።ከሰሞኑ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የቀድሞው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የጸጥታ ጉዳይ አማካሪ ሲናገሩ የነበረው የፓርላማ አባላት የተባለው ትክክልም ይሁን አይሁን በአጽንዖት የማዳመጥ ትዕግስት የማጣት ሁኔታ በእርግጥም ከተራ ስነምግባርም ባለፈ የተባለውን ሰምቶ በምክንያት የመሞገት የአቅም ውሱንነት የታየበት ነው።

አሁን ያለው ፓርላማ ከኢህአዴግ/ህወሃት ዘመን ፓርላማ ጋር ሲነጻጸር በሰው ኃይሉ የትምህርት ዝግጅትም ሆነ በልምድ የተሻለ እና አንጻራዊ መሻል አለበት ብለው የሚያስቡ ነበሩ።በክርክር ሃሳብ ሰልቶ እንዲወጣ በማድረግ ለሃገር የተሻለውን መንገድ እንድትጠቁሙ የተቀመጣችሁ የፓርላማ አባላት ህዝቡ ውስጥ የሚሰማውን የተለያዩ ሃሳቦች፣ሙግቶች፣ድጋፎችም ጭምር ሲንጸባረቁ ማየት የምንፈልግበት ቦታ ፓርላማ ነው። ፓርላማው የአንድ የፓርላማ አባሉን ሃሳብ ወደደውም ጠላውም ለማዳመጥ እና ተናጋሪው ሲጨርስ ሃሳብ የመስጠት ትዕግስት ካጣ ህዝቡማ ከመነጋገር ይልቅ ዱላ ልምዘዝ ቢል ምን ሊፈረድበት ነው?

አሁንም አልረፈደም። ፓርላማው እንዴት መነጋገር፣መሞገት እና በነጻነት ሃሳቡን የማንሸራሸር መብቱን ቁጭ ብሎ መክሮ ያስተካክል። በ21ኛው ክ/ዘመን ተቀምጠን እንድ የህዝብ ተወካይ ሲናገር ለመስማት የሚያስችል ትዕግስት እንዴት እንደሚገኝ መማሩ እጅግ አስፈላጊ ነው።

በእዚህ ሳምንት የአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማጽደቅ በተተራው ስብሰባ ላይ አቶ ገንዱ አንዳርጋቸው ሲናገሩ የፓርላማ አባላት ላሳዩት ትዕግስት ያጣ የማቋረጥ ሙከራ የምክር ቤቱ አባል የተከበሩ አቶ ባያብል ሙላቴ እንዲህ በማለት አምርረው ገልጸውታል።



Tuesday, August 15, 2023

በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተሰላም ከተማ ላይ የድሮን ጥቃት እንደሆነ የታመነው የመንግስት ጥቃት በጦር ወንጀለኝነት የሚያስጠይቅ ነው።በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ አጣሪ ኮሚቴም ካስፈለገ መቋቋም ያለበትና በድርጊቱ የሚጠየቁትን በትክክል ለፍርድ ማቅረብ ይገባል።


የቪኦኤ አማርኛ አገልግሎት ሙሉ ዘገባ ከስር ተያይዞ ያገኛሉ።

=======
ጉዳያችን
=======


በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተሰላም ከተማ ላይ የድሮን ጥቃት እንደሆነ የታመነው የመንግስት ጥቃት እንደ የፍኖተሰላም ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ ለቪኦኤ አማርኛ እንደገለጹት በጥቃቱ እስካሁን 26 መሞታቸው የተረጋገጠና 50 በላይ መቁሰላቸው ተረጋግጧል። ድርጊቱን አስመልክቶ የአሜሪካ ድምጽ ራድዮ የአማርኛው አገልግሎት የዐይን እማኞችን አነጋግሮ ያቀረበው ሪፖርት ደረጃውን የጠበቀ እና በስፍራው የነበረውን ሁኔታ ገለልተኛ በሆነ መልክ የተጠናቀረ ሪፖርት መልክ ያለው ነው።

ይህ ጥቃት እንደየዐይን እማኞች ገልጻ ቀደም ብሎ ድሮን በሰማይ ላይ ከመታየቱና ቃኚ አይሮፕላን ከማለፉ ጋር ተያይዞ እና በአካባቢው ሌላ ምንም ዓይነት የከባድ መሳርያ መጠመድ ባለመኖሩ የዐይን እማኞች የድሮን ጥቃት እንደሆነ እና በፒካፕ መኪናው ዙርያ ያልታጠቁ በርካታ ሰዎች መኖራቸው በግልጽ እየታየ የተፈጸመ ጥቃት መሆኑን በእዚሁ ዘገባ ላይ ነዋሪዎች ለቪኦኤ የአሜሪካ ራድዮ የአማርኛ አገልግሎት ተናግረዋል።

ይህ ማለት ድርጊቱ በጦር ወንጀል የሚያስጠይቅና ይህ እንዲፈጸም ትዕዛዝ ያስተላለፈው ማን እንደሆነ መንግስት መርምሮ ጉዳዩን ለህዝብ መግለጽ ያለበት ጉዳይ ነው። በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ አጣሪ ኮሚቴም ካስፈለገ መቋቋም ያለበትና በድርጊቱ የሚጠየቁትን በትክክል ለፍርድ ማቅረብ ይገባል።

የቪኦኤ አማርኛው አገልግሎት ሙሉ ዘገባ ሰኞ ነሐሴ 8፣2015 ዓም (ኦገስት 14፣2023 ዓም)



''አክቲቪዝም ከጆርናሊዝም'' የደባለቀባቸው ዩቱበሮች በአማራ ክልል የሚፈሰው የመከላከያ እና የአማራ ክልል ህዝብ ደም አልታያቸው ብሏል። በኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሊባሉ ይገባል።

የሰው ደም እየፈሰሰ መከላከያና የአማራ ክልል ታጣቂ ኃይል አይነጋገር የሚሉት በውጪ ሀገር ሶፋ ላይ የተቀመጡት መሆናቸውን ልብ ይሏል። የሰላም ንግግሮችን ለማጣጣል የሚሞክሩትን አጥብቀን መቃወም ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታችን ...