ጉዳያችን - GUDAYACHN
ጉዳያችን - በጉዳያችን ሚድያ፣ኮምኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት የሚዘጋጅ ሲሆን ከ2003 ዓም ጀምሮ በድረ-ገፅ ላይ የነበረ በአሁኑ ጊዜ ከአንድ ሚልዮን በላይ ጎብኚዎች ያሉት ገፅ ነው። Gudayachn is prepared by Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant Organization. It has been online since 2011. Currently, Gudayachn is being visited by over One-million readers from all over the world.
Tuesday, August 11, 2026
የኢትዮጵያ የባሕር ኃይል አዛዥ ኮሞዶር ጌታቸው ስዩም በምፅዋ የኢትዮጵያ የባሕር በር ላይ እጅ አልሰጥም ብለው ያፈሰሱት ደም ዛሬም በባሕሩ ዳር ላይ ይጣራል።
Monday, August 3, 2026
በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጉዳይ ዛሬም ከምንጊዜውም በላይ የቅዱስ ሲኖዶስን የአፈጻጸም ጥብቅ ክትትል ትፈልጋለች።በሺህ የሚቆጠሩ ምእመናን ችግር ላይ ናቸው።
=============
ኢትዮጵያና ግሪክ
- አቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው ለአራት አስርተ ዓመታት ምእመናን ሲገለገሉባት የነበረችው የኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን በአጽራረ ቤተክርስቲያን በሆኑ በቤተክርስቲያን ውስጥ ፊሽካ ከመንፋት እስከ ደም ማፍሰስ ወንጀል በፈጸሙ እና አሁንም ጉዳያቸው በሕግ የተያዘ ግልሰቦች እና እራሱን ኪኖቲታ በማለት በሚጠራ የዕድር አደረጃጀት በፈጠሩት ሁከት አማካይነት ቤተክርስቲያኒቱ በግሪክ መንግስት እንድትዘጋ ሆነ።
- ቤተክርስቲያኒቱ ከተዘጋች ወዲህ በአቴንስ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሚያስቀድሱበት ቦታ በተለይ በአቴንስ ከተማ ውስጥ አለመኖሩና ቤተክርስቲያኒቱን በግሪክ በሕጋዊነት እንዲያገለግሉ የተመደቡት ሊቀስልጣናት አባ ኪሮስ ጸጋዬ ወደ ግሪክ በቶሎ አለመምጣት መጪው የፍልሰታ የፆም ወቅት ሳይቀር ምእመናን ተቸግረው እንደሚያሳልፉ ቅዱስ ሲኖዶስም የሚያውቀው ጉዳይ ነው።
- ይህ በእንዲህ እያለ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በአቡነ ኤልያስ ቤተክርስቲያኒቱን ያወከውን የዕድር አደረጃጀት (ኪኖቲታን) ማዕከል ያደረገ በሆቴል ያደረጉት ''ጉባዔ'' አይደለም ሌላ የራሱ የኪኖቲታ ስር ናችሁ የተባሉ ምእመናንን ሳይቀር ማሰባሰብ ያልቻለ ብቻ ሳይሆን በቅዱስ ሲኖዶስም ምንም እውቅና የሌለው የጉባዔው ምንነት እና ሆቴል የተመረጠበትም ምክንያት ሳይታወቅ ተድበስብሶ ይሄው ሳምንታት ነጎዱ።
- ቤተክርስቲያኒቱ በስሟ የተገዛውን ከስድስት ሺህ ካሬ በላይ ስፋት ያለው በአውሮፓ የመጀመርያዋ የሆነውን ገዳም በተመለከተ ምን ደረሰ፣ይህ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ንብረት ነው ብሎ የሚከታተለው ሊቀጳጳስም ሆነ ሀገረስብከት ሳይኖረው ስምንት ዓመታትን ያሳለፈበት እውነታ ዛሬም መሬት ላይ ያለ ዕውነታ ነው።
- አቡነ ኤልያስ በግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር በኩል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በግሪክ ያላቸው የኃላፊነት ደረጃ በግልጽ እንዲነገረው በአዲስ አበባ የሚገኘውን የግሪክ ኤምባሲ ቤተክሕነት ድረስ ሄዶ እና የሚመለከተውን መምርያ ተገናኝቶ እንዲገለጽለት ጠየቀ።
- የግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር ይህንን ጥያቄ ያቀረበበት ምክንያት አቡነ ኤልያስ ተደጋጋሚ ደብዳቤ በተለይ ወደ የግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር በመላክ በግሪክ ያለውን ጉዳይ እኔ የምቆጣጠረው ነው በሚል ከጊዜያዊ አስተዳዳሪ ምደባ ጀምሮ በሚልኳቸው ደብዳቤዎች የሚኒስቴር መስርያቤቱ ግራ ስለተጋባ ነበር።
- በእዚህ መሰረትም መስመር ኤምባሲው ወደ ቤተክሕነት ልዑክ ልኮ የአቡነ ኤልያስ የኃላፊነት መጠን በቤተክርስቲያን ሲጋበዙ መባረክ ብቻ መሆኑ ተገለጸለት።ይህ የማጣራት ሂደት በግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር ከደረሰው በኋላ አቡነ ኤልያስ በግሪክ በተጋበዙበት ቦታዎች የመባረክ ተግባራትን እንጂ በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በተመለከተ ማናቸውም ጉዳዮች የሚከወኑት እና የተፈጻሚነት ደብዳቤዎች የሚመጡት ከቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ መሆኑን የሃይማኖት ሚኒስቴር አረጋገጠ።
- በእዚህም መሰረት ምንም እንኳን እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት እና ደንብ መሰረት የሃገረስብከቱ ሊቀጳጳስ ሚና ከፍተኛ ቢሆንም ከግሪክ አንጻር ግን የሃይማኖት ሚኒስቴር ባረጋገጠው የሕግ ተቃርኖ ትንተና መሰረት አቡነ ኤልያስ በአሁኑ ጊዜ በግሪክ ቤተክርስቲያን የመመስረትም ሆነ የማስቀጠል እንዲሁም በሃይማኖት ሚኒስቴር በኩል አስተዳዳሪ የመሾም መብት እንደሌላቸው በግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር በኩል የታወቀ ነው።
- ለእዚህም ነው አንዳንድ በኪኖቲታ በኩል ያሉ ምእመናን ወንድሞች እና እህቶች ቤተክርስቲያን ልንገዛ ነው፣ገንዘብ አዋጡ ስትባሉ ሁለቴ አስቡ። አሰራሩ እንደዛ አይፈቅድም ገንዘቡን ለመዝረፍ ያሰፈሰፉ ዙርያችሁን አሉ እያልን ደጋግመን የምንመክረው።
- በግሪክ ለምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የሚመደበው በቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ መሆኑ ለግሪክ የኃይማኖት ሚኒስቴር በድጋሚ ግልጽ ስለሆነ አሁንም ቅዱስ ሲኖዶስ የመደባቸው ሊቀ ስልጣናት አባ ኪሮስ ጸጋዬ ሲመጡ ብቻ ነው ቤተክርስቲያኒቱ በግሪክ ያላት የማስፈጸም አቅም የሚከፈተው።ይህ በግሪክ ያለው ተጨባጭ ሁኔታ ነው።
- የሊቀስልጣናት አባ ኪሮስ ጸጋዬ የግሪክ ጉዞ በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ልዩ ክትትል በሚከተሉት ሁለት መንገዶች መከታተል እና ማስፈጸም ይችላል።
- በአዲስ አበባ የሚገኘው የግሪክ አምባሳደርን ቅዱስ ፓትርያሪካችን ጠርተው ቤተክርስቲያኒቱ የመደበቻቸው አባት ወደ ግሪክ ተጉዘው በፍጥነት አገልግሎት እንዲጀምሩ እንዲያደርጉ ውይይት ማድረግ እና ለግሪክ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንም ደብዳቤ በመጻፍ ቤተክርስቲያኒቱ ቅሬታዋን ማቅረብ አለባት።
- የግሪክ ሀገረ ስብከት አንዱ የገጠማት ችግር ሀገረስብከቱን አስተባብሮ የቤተክርስቲያንን ችግር ከመፍታት ይልቅ በግል እና የሀገረስብከቱን መዋቅራዊ አቅም ባገለለ መልክ ከግለሰቦች ጋር በሚደረግ ግንኙነት ብቻ ለመምራት የሚሞክሩት የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ አካሄድ መሆኑ ፀሐይ የሞቀው እና ሊቀጳጳሱን የሚቀርቡ ሁሉ እጅግ ያዘኑበት ጉዳይ ነው። በመሆኑም ሀገሩን እና ዘመኑን የዋጀ የሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ምደባ አሁንም በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከቅዱስ ሲኖዶስ የምትጠብቀው አሁንም አንገብጋቢው ጉዳይ እና ቅዱስ ሲኖዶስም ከእዚህ አንጻር የጉዳዩን አንገብጋቢነት ለመረዳት መዘግየቱ አሁንም ድረስ በቅርብም ሆነ በሩቅ ያሉ የቤተክርስቲያኒቱን አባቶችም ሆነ ምእመናንን ግራ ያጋባ ጉዳይ ነው።
- በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ምደባ ጉዳይ ከቤተክርስቲያን ጉዳይነት በዘለለ የሀገር ገጽታ፣ ከእዚያም ሲያልፍ የኢትዮጵያና የግሪክ የረጅም ጊዜ ትስስር ነጸብራቅም ስለሆነ የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓ ዴስክ እና በጣልያን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲም በጥብቅ ተከታትሎ ሊያስፈጽመው የሚገባ ጉዳይ ነው።በውጪ የሚኖረው ማኅበረሰብ የራሱን ኃይማኖት በተገቢ መንገድ ማከናወን አለመቻሉ ከቤተክሕነትም አልፎ የኢትዮጵያውያን ጉዳይ ያገባኛል የሚል ማናቸውም ቢሮ ይመለከተዋል። ስለሆነም የተጠያቂነቱ አድማስ በቀላሉ የሚወሰን አይደለም።
Tuesday, July 14, 2026
የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።
- የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት።
Wednesday, July 8, 2026
Tuesday, June 2, 2026
7ኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24፣2018 ዓም በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ተጠናቋል።
- ስለምርጫው ዝርዝር ጉዳይ ምን ያውቃሉ?
✓ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ 42 ፓርቲዎች እና 73 የግል ተወዳዳሪዎች ለተለያዩ ምክር ቤቶች ዕጩዎች የቀረቡበት ነው።
✓ በዚህ ምርጫ በአጠቃላይ 2,198 ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲሁም 8,736 ለክልል ምክር ቤቶች መቀመጫዎች በዕጩነት ቀርበው ተወዳድረዋል።
✓ በዚህም በምርጫው የተወዳደሩት አጠቃላይ ዕጩዎች ቁጥር 10,934 ዕጩዎች መሆናቸውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ ያመለክታል።
✓ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለክልል ምክር ቤቶች ከፍተኛውን ዕጩዎች ያቀረቡት ሦስት ፓርቲዎች ናቸው።
✓ በዚህም ገዢው ብልጽግና 2,950 ዕጩዎችን በማቅረብ ቀዳሚ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) 1,256 እና ሦስተኛው ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 1,032 አቅርበዋል
✓ ሌሎች ፓርቲዎች እና የግል ተወዳዳሪዎችም በተለያየ ቁጥር ለተለያዩ ምክር ቤቶች መቀመጫ ለማግኘት ዕጩዎችን በምርጫው ላይ እንዲወዳደሩ አቅርበዋል።
✓ በአማራ ክልል ከሚገኙ 138 የምርጫ ክልሎች መካከል በስምንቱ ምርጫ እንደማይደረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ብሎ ማስታወቁ ይታወሳል።
✓ በአማራ ክልል ድምጽ የማይሰጥባቸው 8ቱ የምርጫ ክልሎች በደቡብ እና ምዕራብ ጎንደር፣ በአምባሰል እንዲሁም በደጋ ዳሞት የሚገኙ መሆናቸው ተገልጿል።
✓ በትግራይ ክልል ከሌሎች የአገሪቱ ክልሎች ጋር በአንድ ላይ ምርጫ አልተካሄደም።
✓ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዋ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ሰኞ ዕለት ድምጽ በማይሰጥባቸው ስምንት የምርጫ ክልሎች ወደፊት እንዲመርጡ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
✓ በትግራይም 38 ወንበሮች ክልሉ በምርጫ ቦርድ በተቀመጠው የምርጫ ሒደትና ሕግ መሰረት የሚካሔድና ወንበሮቹ ክፍት ሆነው ይጠብቃሉ።
✓ ትናንት ግንቦት 24፣2018 ዓም የተደረገው ብሔራዊ ምርጫ 501 ዕጩዎችን ወደ የሕግ መወሰኛው ወይንም የተወካዮች ምክርቤት የሚያስገባና ምስክርም 25፣2019 ዓም በሚከፈተው የኢትዮጵያ ምክርቤት አዲሱ መንግስት ሥራ ይጀምራል።
✓ በእዚህ ምርጫ የኢትዮጵያን የመንግስት ስሪት ምርጫውን በማደናቀፍ ዕቅድ ተግባር የሸረቡ የቅርብና የሩቅ ቡድኖች በኢትዮጵያ ሕዝብ ጥንቁቅና የቆረጠ የምርጫ ተሳትፎ በእጅጉ ተበሳጭተዋል።
በሰባተኛው የኢትዮጵያ ምርጫ የተሳተፉ ብሔራዊና የክልል ፓርቲዎች ዝርዝር:-
ምንጭ:- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድምንጭ:- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
Friday, May 29, 2026
ከሰባተኛው የኢትዮጵያ ምርጫ በቀጣይ የሚታዩ የሚታዩት ሦስት እውነታዎች
Thursday, April 30, 2026
በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።
የኢትዮጵያ የባሕር ኃይል አዛዥ ኮሞዶር ጌታቸው ስዩም በምፅዋ የኢትዮጵያ የባሕር በር ላይ እጅ አልሰጥም ብለው ያፈሰሱት ደም ዛሬም በባሕሩ ዳር ላይ ይጣራል።
በአስመራ የተወለዱት የኮሞዶር ጌታቸው ባለቤት፣በአዲስ አበባ የተወለዱት ልጆቻቸው ዛሬ ላይ ሆነው የሚነግሩን አለ ሙሉ ቪድዮውን ይከታተሉ።
-
በቀሲስ መንግሥቱ ጐበዜ ሉንድ ዩንቨርሲቲ ፣ ስዊድን (ቀሲስ መንግስቱ ጎበዜ በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ አርኪኦሎጂ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና በሉንድ ዩንቨርስቲ የዶክትሬት...
-
The Ethiopian herald News Paper August 20 , 2020 BY STAFF REPORTER Addis Ababa ************************** (EPA) ADDIS ABABA - Over sixty-mil...
-
አድሚራል ጄምስ ስታርቪድስን =============== ጉዳያችን /Gudayachn =============== ብሉምበርግ የተሰኘው የአሜሪካ ድረገፅ በፖለቲካ እና ፖሊሲ አምድ ስር የአድሚራል ጄምስ ስታርቪድስን አሜሪካ ኢትዮጵ...




















