ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, September 30, 2016

´´የአማራ ብሔርተኝነት አገንግኖ በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ላይ እየወጣ ነው´´ ዋዜማ ራድዮ ውይይት ያዳምጡ።



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

የአሰብ አየር ማረፍያን እና ባሕር ኃይል ጣብያ በየመን ሁቲ ሺያት ሚሊሻዎች ተጠቅቶ ነበር Yemen’s Houthi forces attack Eritrea’s Airport, Navy base



Source = Sudan Tribune 

An Eritrean opposition group, Red Sea Afar Democratic Organization (RSADO) on Wednesday said that Yemen’s Houthi group have attacked the international Airport of Assab, a port city in the Southern Red Sea Region of Eritrea.
JPEG - 25.8 kb
A Houthi Shiite rebel carries his weapon as he joins others to protest against Saudi-led airstrikes at a rally in Sanaa, Yemen on 1 April 2015 (Photo: AP/Hani Mohamed)
Ibrahim Haron, leader of the armed opposition group told Sudan Tribune that Houthi forces stationed in the island of Hanish and Zagar have also attacked the headquarters of the Eritrean naval forces in Assab by firing mortar rockets thereby causing a serious damage.

The attack comes days after reports disclosed that Saudi Arabia has transferred some 5,000 Yemeni militants to Eritrea for military exercise in the Red Sea country.
According to the reports, Riyadh is transferring the militants from Aden to Eritrea’s Assab port to go under military trainings and then be sent to the Saudi provinces bordering Yemen to back the Saudi led war in Yemen.
The Eritrean government has dismissed the reports saying “a preposterous lie peddled for some ulterior motives”The opposition leader said Eritrean authorities have imposed a tight security cordon in the areas following Monday’s attack.
Ibrahim said Eritrea government motive to cooperate with the Saudi-led coalition is because Asmara has a long standing border dispute with Yemen.The countries had previously engaged in a bitter war with Yemen over the disputed Islands of Hanish and Zagar.
In 1998, the international Tribunal of the international Committee ruled the islands in favour of Yemen; Eritrea however refused to accept the ruling.He added that Eritrea had been serving as a base for military training for anti-Yemen groups in order to create destabilization and instability in Yemen and in the region at large.
“When the situation in Yemen changed and appeared new events and the emergence of coalition forces, Eritrea favoured the Arab coalition to ensure financial, political and military gains” Ibrahim told Sudan Tribune by telephone from the Eritrean-Ethiopian common border.

ERITREAN PILOT DEFECTS

Meanwhile the Eritrean opposition group today alleged that an Eritrean Air force pilot has defected to Saudi Arabia by flying a military Aircraft.According to opposition officials, the Eritrean pilot defected on Tuesday along with his two aides becoming the latest members of the Eritrean Air force to defect from the reclusive east African Sea nation.The Captain pilot and two of his aides flew to Jizan region in south of the Kingdom of Saudi Arabia.The defectors have asked for political asylum but it is not yet clear if the kingdom has grant them an asylum.

Ibrahim said the latest defection is a big blow to President Isaias Afeworki led regime.
He says it is an apparent sign of growing discontent of the air force personnel and the military against the oppressive region.In previous years, there have been defections in thousands from the Eritrean army, navy and air forces as the regime retains grip on power for over two-decades.President Isaias has been in power since the country gained independence from Ethiopia in 1993.

Sudan Tribune September 21,2016


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Tuesday, September 27, 2016

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ´´የወያኔ አገዛዝ እና የኢትይጵያ ወደፊት´´የሚለው ፅሁፋቸውን በተመለከተ የገቡኝ እና ያልገቡኝ ነጥቦች

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም 

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ሶስተኛው ትውልድ ላይ ሆነው የኢትዮጵያን ጉዳይ እድሜ ዘመናቸውን ያልተዉ እና አሁን በእርጅና ዘመናቸውም ለችግሮች መፍትሄ ያሉትን ከመስጠት የማይደክሙ ኢትዮጵያ በዘመናዊ ዘመኗ ካፈራቻቸው ጥቂት ትጉ  ምሁራን ውስጥ ናቸው።ዛሬም ፕሮፌሰሩ አሁን ኢትዮጵያ ለገባችበት የፖለቲካ ችግር መፍትሄ ያሉትን´´የወያኔ አገዛዝ እና የኢትይጵያወደፊት´´ በሚል ርዕስ በድረ-ገፃቸው ላይ አስነብበውናል።

ፅሁፉን አንብቤዋለሁ።የምስማማበት እና የማልስማማበት ወይንም የማያስኬድ ነው የምላቸው ነጥቦች አሉኝ።ነገር ግን ርዕሴን የማልስማማበት ከማለት ያልገባኝ በሚለው ማስቀመጡ የተሻለ እንደሆነ ተሰምቶኛል።ላለመስማማት ለማለት ፅሁፍ በእራሱ ሁሉንም ነገር አይገልጥም እና እርሳቸው ያዩበት የዕይታ ጥግ እና ምክንያቶቹን በደንብ ቃል በቃል እየጠየኩ የተረዳሁ ቢሆን ነበር።ሆኖም ግን ያ ባልሆነበት ሁኔታ አለመስማማት የሚለውን ያልገባኝ የሚለው አገላለፅ የተሻለ ሆኖ ተሰምቶኛል።
የፕሮፌሰር መስፍን ፅሁፍን ባጠቃላይ ዋና መልዕክቱን በሶስት ነጥቦች የሚጠቃለል ይመስለኛል። እነርሱም : -

1/ የወቅቱ ጥያቄ ወያኔን ማውረድ ነው ግን ትግራይን ካላሳተፈ ለውጡ  ውጤታማ አይሆንም፣

2/ አሁን በስልጣን ላይ ያሉት የሕወሓት ባለስልጣናት ከሚመሰረተው  ነፃ የተወካዮች ምክር ቤት ዋስትና እና የኑሮ ድጎማ ማግኘት  እና

3/ የትግራይ ሕዝብ ከሕወሓት ወይንም ከኢትዮጵያዊነት አንዱን ይምረጥ።ኢትዮጵያዊነቱን ቢመርጥ ይሻለዋል።የሚሉት ናቸው።

1/ የወቅቱ ጥያቄ ወያኔን ማውረድ ነው ግን ትግራይን ካላሳተፈ ለውጡ ውጤታማ አይሆንም 

የወቅቱ ጥያቄ ወያኔን ማውረድ ነው። ትክክል ነው።ይህ እራሱ ወያኔ በተግባሩ ሕዝቡን ገፍቶ ያመጣው የኢትዮጵያ ሕዝብ የህልውና ጥያቄ ነው። ትግሉ የትግራይን ሕዝብ ማሳተፍ እና ወያኔን ማሳተፍ በሚለው መካከል ትክክለኛ መስመር ቢሰመርበት ግን ጥሩ ነው ባይ ነኝ።ምክንያቱም የትግራይ ህዝብን ችግር ከኢትዮጵያ ችግር ጋር እንዲቆላለፍ ያደረገው ሕወሓት መሆኑ እስከተገለፀ ድረስ የትግራይ ችግር ከሚባል የሕወሓት ችግር ተብሎ ቢጠቀስ የበለጠ ገላጭ ይሆናል።ይህ ማለት ትግራይን ማሳተፍ እንደ ሀገር አካል የሚለውን እሳቤ በሚገባ ያሳያል ማለት ነው።

ፕሮፌሰር በፅሁፋቸው ላይ ´´ኢትዮጵያን በትግራይ ገመድ፣ ትግራይን በኢትዮጵያ ሰንሰለት አስሮ የያዘው ወያኔ ገመድና ሰንሰለቱን እንዲበጥስና ሁለቱም ነጻ ማድረግ የሚቻለው እንዴት ነው? ወይም ትግራይንም ሆነ ኢትዮጵያን ሳይጎዳ ገመዱንና ሰንሰለቱን መበጠስ የሚችል ሌላ ማን ነው?የሚል ነው፡፡´´ ይላሉ።እዚህ ላይ ሁለቱንም ነፃ ማድረግ የሚለው መፍትሄው ህወሓት ተነጥሎ ሲመታ ወይንም እራሱን ሲያከስም ነው። ለማክሰምም ሆነ ለመመታት ደግሞ የትግራይ ሕዝብ እራሱን ከሕወሓት በፈቃዱ ለይቶ ፕሮፌሰር መጨረሻ ላይ እንደጠቀሱት ኢትዮጵያዊነቱን ሲያስበልጥ እና በፖለቲካም ሆነ ምጣኔ ሀብት ለእራሱ ከማድላት አስተሳሰብ ወጥቶ  እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ክፍል እኩል ተሳታፊ ሲሆን ነው።

በወያኔ ማውረድ ጥያቄ ውስጥ ግን ሰላማዊ ትግል ነው ወይንስ የትጥቅ ትግል የሚል ብዥታ በአሁኑ ወቅት አለ ብዬ አላምንም።የሰላማዊ ትግል ሁሉንም በአንድነት በተቀናጀ መልክ ማሳተፍ ከቻለ እና ፅናትን ካሳየ አዋጭ ለመሆኑ የሚከራከር የለም። ሆኖም ግን በወራት ውስጥ በሺህ የሚቆጠር አስከሬን ለሚከምር ወያኔ የሰላማዊ ትግል ነው ወይንስ ትጥቅ ትግል የሚል ክርክር ከቆመ ቆይቷል።ስለዚህ ብዥታው አለ የሚለው አባባል አልገባኝም።በሌላ በኩል ለውጡ ትግራይን ማሳተፍ አለበት አዎን!ነገር ግን የግድ ወያኔ በየትኛውም መልክ ማለትም በፖለቲካ፣በምጣኔ ሃብት ወይንም በማኅበራዊ መልክ ለውጡ ላይ የመሪነት ሚና ሊኖረው አይገባም።ይህ የመሪነት ሚናውን ያጎላዋል የሚለው ስጋቴን የሚያጠናክረው ፕሮፌሰር በመቀጥለው ተራ ቁጥር  2 ላይ በጠቀለልኩት ሀሳባቸው ውስጥ ነው።

2/ አሁን በስልጣን ላይ ያሉት የሕወሓት ባለስልጣናት ከሚመሰረተው ነፃ የተወካዮች ምክር ቤት ዋስትና እና የኑሮ ድጎማ ማድረግ   

ፕሮፌሰር በፅሁፋቸው ላይ  በሚመሰረተው ነፃ የተወካዮች ምክር ቤት ላይ ተጣርቶ የተገኘው ሀብት እንዴት እንደሚከፋፈል ሲገልፁ 
´´ተጣርቶ የተገኘው ሀብት (የማይንቀሳቀስ ንብረትን ጨምሮ) እንደሚከተለው ሊደለደል ይቻላል፡– ይህ መነጋገሪያ ሀሳብ ብቻ ነው፡–
- ለትግራይ ልማት፤
- ለሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች ልማት፤
- ለትግራይ የጦር ጉዳተኞች፤ ለእያንዳንዳቸው መጠነኛ ዘመናዊ መኖሪያ ቤት፣
- ለትግራይ የሟች ቤተሰቦች፤ ለእያንዳንዳቸው መጠነኛ ዘመናዊ መኖሪያ ቤት፣ 
- ለሌሎች ኢት. የሟች ቤተሰቦች፤ ለእያንዳንዳቸው መጠነኛ ዘመናዊ መኖሪያ ቤት፣
- ለሌሎች ኢትዮጵያውያን የጦር ጉዳተኞች፤ ለእያንዳንዳቸው መጠነኛ ዘመናዊ መኖሪያ ቤት፣
- ለወያኔ መሪዎች፤ ለመኖሪያ የሚያስፈልጋቸውን ጡረታ መስጠት፤´´ ይላሉ።

እዚህ ላይ ገና ባልተሠራ ሥራ ላይ ምቀኝነት ልገልፅ አይደለም።ነገር ግን ይህ ሃሳብ ባጭሩ ወያኔ በአገር ውስጥ እና በውጭ ያለውን ሀብት በሰላም መልሶ እንደገና እንዲደለደል ይፈቅዳል ከሚል እሳቤ የመነጨ ይመስላል።እሺ! እንደተባለው ሆነ እንበል።የወያኔ መሪዎች የሚጠየቁበት እልቆ መስፈርት የሌላቸው በኢትዮጵያ ላይ እንደ አገር የተፈፀሙ ወንጀሎች ጉዳይስ? እንዲሁ በደምሳሳው ይታለፉ? አሁንም እሺ እንደተባለው ወንጀሉ ሁሉ ተትቶ ፕሮፌሰር እንዳሉት  ´´ለወያኔ መሪዎች መኖርያ እና ጡረታ መብት ተሰጣቸው´´ እንበል።ይህ ለመጪው ትውልድ  ምን ያስተምራል? ነገ ማንም በጎሰኝነት ተነስቶ የፈለገውን ያህል ዘርፎ እና አገር አጠራምሶ ጡረታ እና መኖርያ እየሰጠን እናኑረው ? ወይንስ በትክክለኛ ዳኝነት በነፃነት እና ምንም አይነት የሰብአዊ መብቱ ሳይጣስ ለፍርድ ቀርቦ ክፍት በሆነ ችሎት እንስማ እና የህሊና ዳኝነት  ወስደን የታመመውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁስል እናድን? የመፍትሄ ሃሳቡ በእራሱ አልገባኝም። ያጠፋ ሰው ገና ለፍርድ ቀርቦ ጉዳዩ ሳይታይ የጡረታ እና ድጎማ መቁረጥ ላይ ከሄድን ፍትሃዊነትን እንደናፈቅን ሌላ ክ/ዘመን ልንዘልቅ አይደለም ወይ?

በሌላ በኩል የትግራይ ልማትን ከቀሪው ኢትዮጵያ ጋር በእኩል ድርድር የቀርቡበት መንገድ ግልፅ አይደለም።የመጪዋ ኢትዮጵያ ናፍቆታችን እኩልነት የሚያስተዳድረን መንግስት የማግኘት ነው እንጂ አሁንም የኢትዮጵያ ሌሎች ክልሎችን ከትግራይ ጋር እየመዘነ  የሚያስቀምጥ መንግስት አይደለም።ለምሳሌ ተጣርቶ ከተገኘው ሀብት ሲደለደል ለትግራይ ልማት፣ብሎ ለተቀረው የኢትዮጵያ ክልል ልማት የሚለው አገላለፅ በእራሱ ግልፅ አይደለም። ትግራይ የኢትዮጵያ አካል ነች።ኢትዮጵያዊነት በትግራይ ይገለፃል።ትጋራይነትም በኢትዮጵያ ይገልፃል ካልን ለምንድነው የኢትዮጵያ ሀብት እኩል ለጋምቤላውም  ሆነ ለሱማሌው ስናከፋፍል የትግራይንም በተርታ አስቀምጠን በነባራዊ ሁኔታ የማናየው? በመጪው ምክር ቤትም የትግራይ ልማት በእራሱ አንድ አጀንዳ ሆኖ ከኢትዮጵያ በተዘረፈው ንብረት  ቅድምያ ተቀምጦ የተቀረው በሚል ስማቸው ያልተጠቀሱ የኢትዮጵያ ክልሎች ተብለው መቀመጣቸው እራሱ ምቾት ይሰጣል ወይ? ይህንን አካሄድ እራሱ የትግራይን ሕዝብ ወደነበረበት የተሳሳተ የአስተሳሰብ ጥግ የሚገፋ አይደለም ወይ? ደግሞስ ላለፉት 25 ዓመታት በትግራይ የተሰራው ልማት ትግራይ ለማዕከላዊ መንግስት ባስገባችው የቀረጥ ልክ ነው እንዴ? ብሎ ሂሳብ ውስጥ የሚገባ ቢነሳ መልሱ ምን ይሆናልና ነው በመጪው ምክር ቤትም ላይ የትግራይ ልማት የኢትዮጵያ የብቻ እና ዋናው ጉዳይ ሆኖ ከሌላው ቀሪ የኢትዮጵያ ሕዝብ ልማት ጋር እኩል ሚዛን የሚቀመጠው።እዚህ ጋር እኩል ሚዛን ስል በተናጥል እንጂ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ልማት ተመጣጣኝ የሀብት ድልድል መኖር የለበትም እያልኩ አይደለም።ሚዛኑ ግን  አልገባኝም።

3/ የትግራይ ሕዝብ ከሕወሓት ወይንም ከኢትዮጵያዊነት አንዱን ይምረጥ።ኢትዮጵያዊነቱን ቢመርጥ ይሻለዋል።

ይህ ጥሩ ሃሳብ ነው።እንዲያውም የእዚህ አይነቱ ሥራ እና ምክር ላለፉት አስር ዓመታት በደንብ ተደርጎ በተለይ ለትግራይ ሀገር ወዳድ  እና ወያኔ ወለድ ምሁራን መነገር ነበረበት።ዛሬ ሕወሓት የትግራይን ሕዝብ እጅ እና እግሩን በጥቅም እና ሌላው ኢትዮጵያዊ ሊያጠፋህ ነው የሚል የማስደንበርያ  ንግግር ግራ ሳይጋባ ቢሆን ባማረ ነበር። አሁንም ግን ይህ መነገር ያለበት በኢትዮጵያዊነቱ አምኖ ነገር ግን በማንነቴ በሕወሓት ተረገጥኩ ለሚለው ቀሪው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይሆን ለእራሱ ህወሃት ሕልውናዬ ነው በሚል የተሳሳተ አስተሳሰብ ለሚባዝነው  የትግራይ ሕዝብ ነው። እዚህ ላይ ፕሮፌሰር ያስቀመጡት አማራጭ ልብ ላለው በጣም ትክክለኛ ይመስለኛል።ኢትዮጵያዊ ነትን በማፅናት እና የትግራይ ብሔርተኝነትን በትዕቢት በማቀንቀን መካከል ያለው ትርፍ እና ኪሳራ በትትክል ተቀምጧል። ፕሮፌሰር የትግራይ ሕዝብ ያለውን ሁለት ምርጫዎች ሲያስቀምጡ እንዲህ ብለዋል - 

ምርጫ አንድ፡ የትግራይ ሕዝብ እንደጥንቱ እንደጠዋቱ ታሪኩን ይዞ በኢትዮጵያዊነቱ ይቀጥላል፤ በኢትዮጵያዊነት ታሪኩ በግምባር-ቀደም ተሰልፎ በፖሊቲካም ሆነ በመንፈሳዊ ጸጋው የኢትዮጵያዊነት ግዴታውን ይወጣል፤ ይህ ምርጫ የኢትዮጵያዊነት ግዴታ ነው፤ ይህ ምርጫ ታሪካዊ ግዴታ ነው፤ ይህ ምርጫ የዜግነት ግዴታን ከጎሣ ግዴታ ማስቀደም ነው፤ ይህ ምርጫ ከጨለማው ዘመን ወጥቶ ወደሃያ አንደኛው ምዕተ-ዓመት መሸጋገር ነው፤ ከሁሉም በላይ ይህ ምርጫ የሰፊ ሀብት ባለቤትና የመቶ ሚልዮን ዜጎች ማኅበረሰብ አባል ያደርጋል፡፡
ኢትዮጵያ የትግራይ ነች፤ ስለዚህም ትግራይ ኢትዮጵያን ነች፤ ሁለቱ አይለያዩም፤ ይህንን ወያኔም በሚገባ የተረዳው ይመስላል፤ አለዚያ ከጎንደር፣ ከላስታም፣ ከራያም፣ ከጎንደርም … የሚለቃቅመው ለምንድን ነው!

ምርጫ ሁለት፡ የትግራይ ሕዝብ የወያኔ መሣሪያ እንደሆነ ይቀጥላል፤ ይህ ሲሆን ትግራይ በመሠረቱ ከኢትዮጵያ ይገነጠላል ማለት ነው፤ በትግራይ ዙሪያ ኤርትራ በሰሜን፣ በደቡብ ደግሞ ጎንደር፣ ወሎና አፋር ይገኛሉ፤ ወያኔ ሆን ብሎ ትግራይን ከኤርትራ፣ ከጎንደር፣ ከወሎና ከአፋር ጋር አጋጭቶ ደም እንዲቃቡ አድርጓል፤ (በትግራይ ዙሪያ ያሉትን ብቻ ለማንሳት ነው እንጂ ከጂጂጋ እስከጋምቤላ፣ ከወሎ እሰከሲዳሞ ቦረና የግፍ ጠባሳዎች አሉ፤) ስለዚህም ትግራይ በወያኔ ስር ሆኖ ከአነዚህ ከከበቡትና በጠላትነት ከተፋጠጡት ሕዝቦች ጋር ዘለዓለም ሲቆራቆዝ ሊኖር ነው፤ ዙሪያውን ካሉት ሕዝቦች ሁሉ ጋር መቆራቆዝ የትግራይን ሕዝብ ያደኸያል፤ የትግራይ ሕዝብ መሸሻ ስለሌለው በአጥንቱ እየሄደ የወያኔ አገልጋይ ይሆናል፤ ኢትዮጵያና ኤርትራ በምሥራቅ በአሰብ በኩል፣ በምዕራብ በጎንደር በኩል የልማትና የጋራ ደኅንነታቸውን ይመራሉ፤

ባጠቃላይ ፕሮፌሰር ያቀረቡት ሃሳብ ከብዙ አስተሳሰቦች አንፃር አንዳንድ አከራካሪ ነጥቦች ቢኖሩበትም ለትግራይ ሕዝብ ምናልባት የኢትዮጵያን የነፃነት እና የእኩልነት ጥያቄ  ላይ ከምሩ ማሰብ እና ሕወሓት አይኑን አስሮ ወደሚመራው ገደል መግባት እንደሌለበት የሚያሳየው ሌላው ትልቅ የደውል ማንቂያ ነው። የትግራይ ሕዝብ በሆይ ሆይታ በታጠቀው መሳርያ የትቢት ፕሮፓጋንዳ የሚነዙለት ሕወሐቶች የስልጣን ወንበራቸው ሲያጋድል  እንዴት ጥለውት እንደሚሄዱ እና የሚቀረው ነገር ከቀሪው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ያጋጩት ቁርሾ ብቻ እንደሚሆን ማወቅ አለበት። ዛሬ ወንበር ላይ ተቀምጠው የምናያቸው እነ አባይ ፀሐዬ፣ አባይ ወልዱ ሳምሶናይታቸውን ይዘው ትተውት እንደሚሄዱ የትግራይ ሕዝብ ካላመነ ከታሪክ አልተማረም ማለት ነው። ኮ/ል መንግሥቱም አገር ትተው ይሄዳሉ ብሎ የሚያምን የቀድሞ ሰራዊት አባልም ሆነ ኢትዮጵያዊ አልነበረም። ግን ሆኗል።በመሆኑም የትግራይ ሕዝብ ፕሮፌሰር የጠቀሱትን ምርጫ አንድ ማለትም ኢትዮጵያዊነትን ተቀብሎ  በኢትዮጵያዊነት ታሪኩ በግምባር-ቀደም ተሰልፎ በፖሊቲካም ሆነ በመንፈሳዊ ጸጋው የኢትዮጵያዊነት ግዴታውን መወጣት የወቅቱ ጥያቄ ነው።እዚህ ላይ ግን የትግራይ ሕዝብ አለመሳተፍ የትግሉን ዋጋ ያንረው እንደሆነ እንጂ  በማንኛውም ወጪ የኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃነቱን ይቀዳጃል።ይህ እንደማይቀር ህዝቡ የቆረጠበት ደረጃ በእራሱ አመላካች ነው። የናዚዎች ፈቃደኝነት የዓለምን ሕዝብ ለነፃነት እንዳላበቃው ሁሉ የጥቂት ሕውሐት አመራሮች እና አቀንቃኞቻቸው ፍቃደኛ አለመሆን የኢትዮጵያን ሕዝብ በነጻነቱ ድል ከማድረግ አያግደውም።


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Monday, September 26, 2016

ሰበር ዜና - አቡነ አብርሃም በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት በአደባባይ ገሰፁ።Ethiopian Orthodox Tewahido Church synod member and Archbishop Abune Abraham strongly criticised the current regime of Ethiopia.


አቡነ አብርሃም የምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

አቡነ አብርሃም የምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ መስከረም 16፣2009 ዓም በባህርዳር በተከበረው የደመራ መስቀል በዓል ላይ ለተሰበሰበው ምዕመን ስለ እውነት  በአደባባይ መስክረዋል። በአሜሪካ የዲሲ እና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም የነበሩት አቡነ አብርሃም በእዚሁ  አገልግሎታቸው በምእመናን በተለይ በወጣቶች ዘንድ ከፍተኛ ፍቅርን አትርፈው እንደነበር ብዙዎች ይመሰክራሉ። በተለይ በምእመናን መካከል የሚነሱ ግጭቶችን በማስታረቅ እና መናገር እና መስማት የማይችሉ ወጣቶች መንፈሳዊ አገልግሎት በምልክት እንዲማሩ ያደረጉት ጥረት ተጠቃሽ ነው።ከአሜሪካ አገልግሎታቸው በመቀጠል የምስራቅ ሐረርጌ እና የጅጅጋ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው አገልግለዋል።በአሁኑ ወቅት የምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናችው።

አቡነ አብርሃም በዛሬው የባህር ዳር ደመራ ላይ ከመሰከሩት እውነት ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል። 
´´ 
´´ችግሩ ያለው ከመሪዎች እንጅ ከተመሪ አይደለም ....መንግስትን ና የራሱን ሚድያ ገስጹ የህዝብ ጥያቄ መመለስ አለበት ....እኔ ከመፍራቴ አንጻር በዓሉ ባይከበር ደስተኛ ነበርሁ ነገር ግን አባቶቼን ሳይ በየሳምንቱ ቢከበርም አይቆጨኝም።ትናንት አስከሬን እያወጣ አልቅሱ ሲለን ነበር።.....የህዝቡ ጥያቄ መመለስ አለበት። .....ወታደር ከዚህ በኋላ የሰላምን ምላጭ እንጅ የመሳሪያን ምላጭ መሳብህን አቁም።....በየሀገሩ በስደት ያለው ወገናችን መመለስ አለብት ። ......እኛ አባቶች የምናገረውን በተገቢው መልኩ ለህዝብ የማታቀርቡ የመንግስት ሚድያ ካላስተካከላችሁ ከዚህ በኋላ አደባባዩ አትገቡም።እኛ የተናገርነውን ትቆራርጡ ታቀርቡ እና ምእመኑ ምን አባት አለን እንዲል ታደርጋላችሁ። ክርስቲያን እውነት ይናገራል።.......ለእዚች አገር መጠበቅ ቤተ ክርስቲያን አስተዋፅኦ ትልቅ ነው።ቤተ ክርስቲያን ስለ ወታደርም ትፀልያለች።ሕዝብ የሚጠብቁትን ጠብቅ እያለች የምትፀልይ ይህች ቤተ ክርስቲያን ነች።ስለዚህ ልትደመጥ ይገባታል።አንድ ሰው ባልሰራው ከታሰረ፣እግዚአብሔርስ እንዴት ዝም ይላል።ሁላችንም እንደወንድምነት እንተባበር። ስንት ወገናችን በበረሃ አለቀ።........ዛሬ ስጋት ነው።አሁን የመጣው ሕዝብ ለሃይማኖቴ ልምጣ ብሎ የመጣ እንጂ ማንም ይጠብቀናል ብሎ አይደለም የመጣው።......

........ያለ በደላቸው የታሰሩት ወንድሞቻችን መፈታት አለባቸው። .....ጠላትን እንዳላንበረከኩ አባቶቻችን ፤ዛሬ ለምን እርስ በእርስ ተከፋፈልን? የተሸከምነው መሳሪያ ከክርስቶስ መስቀል አይበልጥም። .....ወታደሮችና ድንበር ጠባቂዎች ስለ እናንተ ቤተክርስቲያን ስለምትጸልይ የሷ ልጆች ናችሁና ደም አታፍሱ። ´´ የሚሉ ይገኙበታል።

አቡነ አብርሃም ይህንን ሲናገሩ ምእመናን በእልልታ እና በእንባ ስሜታቸውን ይገልፁ ነበር።ከዛሬው የባህርዳር ደመራ በኃላ አቡነ አብርሃም ሕዝብ ወደ ቤቱ ሳይገባ እኔ አልገባም በማለት ህዝቡ ከሄደ በኃላ በእግራቸው ወደ ቤታቸው በፖሊስ ታጅበው ሄደዋል።

በቅዱስ ሲኖዶስ አባል ደረጃ በመስቀል ደመራ ላይ አሁን በስልጣን ላይ የሚገኘው የሕወሓትን መንግስት በግልጽ ስገሰፅ የአቡነ አብርሃም የመጀመርያው ይሆናል። አቡነ አብርሃም እናከብርዎታለን።በእዚህ የመከራ ዘመን ለኢትዮጵያ እንደ አቡነ ጴጥሮስ በአደባባይ ስለ እውነት የመሰከሩ ምስክር ሆነዋልና።እርስዎ የተጋረደውን አዚም ገፈውታል።ፈለግዎን ተከትለው ሌሎች አባቶችን ድምፅ አሁንም በብዛት መስማት እንፈልጋለን። ድምፅ ብቻ አይደለም ምእመኑን በመከራው ሰዓት አብረው እየተንገላቱ የሚያፀኑ ካህናት መብዛት አለባቸው።

አቡነ አብርሃም ያደረጉት ንግግር ኦድዮ ለመስማት ይህንን ይጫኑ ።


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Sunday, September 25, 2016

አዲስ የሽምቅ ተዋጊ ደቡብ ሱዳን ውስጥ ተመሰረተ መንግስት የመቀየር ዓላማ አንግቧል። NEW REBEL MOVEMENT FORMED IN SOUTH SUDAN


September 25, 2016 (JUBA) - South Sudan’s former minister of agriculture minister, Lam Akol, has formed a new rebel faction after spending several weeks of consultations with different unarmed and armed opposition parties in the country.

Lam Akol, chairman of South Sudan’s main opposition party (AFP/Samir Bol Photo)

Akol, according to a statement issued over the weekend and extended to Sudan Tribune has named the new rebel group as National Democratic Movement (NDM) and said that his aim is to overthrow by all means the government of South Sudan under the leadership of President Salva Kiir.

“The National Democratic Movement was born to wage the struggle, together with others in the field, against the totalitarian, corrupt and ethnocentric regime in Juba that is bent on dragging our country into the abyss,” the statement reads in part.

Akol, who previously chaired the Democratic Change Party (DCP) said he resigned and left the party last month because the members and the other leaders of the DCP believed in peaceful dialogue and non-violence as the only means to bring about change in South Sudan.

He described his new rebel faction as a front bringing together the social and democratic political forces as well as civil society activists, who want the political discourse in the country to be centred on the “transformation of the centuries-old conditions of extreme poverty, ignorance, illiteracy and cultural backwardness of the masses of our people.”

The movement, it explained, is founded on the principles and concept of national democratic revolution based on the core values of freedom, equality, justice and fraternity, and solidarity anchored in historical and philosophical perspectives. These values, it stressed, translate into fundamental rights and freedoms as provided for in the UN Conventions of civil, political, economic, social and cultural rights.

The political statement of the NDM set out in details what the NDM stands for and how to rid the people of the totalitarian ethnocentric regime in Juba and replace it with a pro-people inclusive government.

“It must be clear from the outset, the NDM is not just for change of personalities in Juba to replace them with others of the same feathers; it is out for a radical change in the country that will bring about genuine state-building and nation-building,” it emphasized.

He also said his new faction will closely work with the Sudan People’s Liberation Movement (SPLM-IO) under the leadership of the former First Vice President, Riek Machar.

It is not clear from whether the prominent politician will get military forces for his new faction.

(ST)

Source - Sudan Tribune, September 25,2016 


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Wednesday, September 21, 2016

ዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ በኢትዮጵያ ታሪክ የት-መጣነት(origin) ጉዳይ ባደረጉት ጥናት ላይ የተደረገ ቃለ መጠይቅ (ኦድዮ)

ከእዚህ በታች ያለው ጽሁፍ እና የዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ ያደረጉትን ቃለ መጠይቅ (ኦድዮ) በጉዳያችን ገፅ ላይ ከሶስት አመታት በፊት ማለትም በ2005 ዓም  ተለጥፎ ነበር። ዛሬ እንደገና ቃለ መጠይቁን ማውጣቱ አስፈላጊ ሆኗል።በአሁኑ ወቅት የዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ በእዚህ ቃለ መጠይቅ ላይ ያነሳቸውን ነጥቦች በመጽሐፍ አትሟቸዋል።
=======================================
  
''እኛ ኢትዮጵያውያን ታላቅ ሕዝብ ነን።እራሳችንን ዝቅ ማድረግ አይገባንም።ለምን ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር አለች አሁን? ይህ ማለት ኢትዮጵያን ያስጠሩ ሰዎች ቀድመው ነበሩ ማለት ነው።......ቀድሞ 'ኢትዮጵ' የሚባል ሰው ስለነበረ ነው።ለሀገር ሲሆን 'ኢትዮጵያ' አሰኛት እናም ከእርሱ ዘር የተወለድነው ሁሉ ኢትዮጵያውያን እንባላለን።እኔ ኢትዮጵያዊ አይደለሁም ጃማይካ ነኝ ወዘተ ብልም ሃቁ እንዳፈጠጠ አለ።ይህ ሰው የኢትዮጵ ልጅ ስለሆንኩ እኔ ሁላችንም ብታምኑም ባታምኑም፣ብትክዱትም ባትክዱትም  ሁላችንም የእርሱ ልጅ ነን።እርሱ ከየት መጣ ለሚለው በሚወጣው መፅሐፌ ላይ ተዘርዝሯል። እኛ ኢትዮጵያውያን ከየት እንደመጣን ከስር መሠረታችን የሚታወቅ እንጂ ሜዳ ላይ የተልን አይደለንም።ማንነታችን በትክክል የተመዘገበ እና የታወቀ ከማንም በላይ በእዚህ ምድር ላይ ከአይሁዳውያንም ቀዳሚ ነን።''

በመቀጠል ዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ ስለ ኩሽ፣ሴም፣ሰለሞናውያን ስርወ-መንግስት፣ስለ የኦሮሞ ሕዝብ ከጥንት ጀምሮ በኢትዮጵያ ንግስና ታሪክም ሆነ የፖለቲካ ሕይወት ውስጥ የነበረውን ታሪክ ሁሉ በሰፊው ተንትነዋል።''ለእዚህ ሁሉ ታሪክ ማስረጃ ምንድነው?'' ተብለው ሲጠየቁ እንዲህ መልሰዋል- 

''ታሪኩ እስከ ዛሬ አንድ ሺህ አመት ድረስ  በደንብ ይታወቅ ነበር።ዮዲት ጉዲት ስትነሳ መፃህፍትን ሁሉ ስታጠፋ እና  የአክሱም መንግስት ሲፈርስ 'አክሱማይ ሲራክ'  የተባለ ሰው  ፅሁፉን ይዞ ወደ ኑብያ(የአሁኗ ሱዳን) ተሰዶ እዝያው ሞተ።በኃላ ንጉስ ላሊበላ ከኢየሩሳሌም ስደት ሲመለስ መፅሐፉን ከኑብያ ወስዶ አፃፈው።በኃላ ግን የግብፅ ጳጳሳት ታሪኩን ለማስጠፋት ብዙ ሰሩ።አንዱ ምክንያታቸው መፅሐፉ ከጥንት የኢትዮጵያ ታሪክ ጀምሮ እስከ ዮዲት መነሳት ጊዜ ብቻ የሚናገር ሳይሆን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአይሁድ ማስተማር ሳይጀምር ለኢትዮጵያውያን ለሶስት አመት ያክል ቀ 22 ዓመቱ እስከ 25 አመቱ ድረስ ማስተማሩን በትክክል ይናገር ነበርና ነው።በእዚሁ መሳደድ ዳግም መፅሐፉን ይዘው አባቶች ወደ ኑብያ ተሰደዱ። ......መፅሐፉ የዛሬ 50 አመት ገደማ አንድ መነኩሴ ኑብያ ከፈራረሱ ህንፃዎች መካከል ሱዳናውያን የጥንት መፃህፍት መኖራቸውን ነገረዋቸው አግኝተው ወደ ኢትዮጵያ አመጡት።ከእዛ ወዲህ በተቆራረጠ መልክ መፅሐፉ ታትሟል።'' ብለዋል።
የታሪክ ምርምር ቀጣይ ነው። ዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ በማስረጃ የተደገፈ የምርምር ውጤታቸውን አቅርበዋል።በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ እራሱን የቻለ መረር ያለ ምርምር ማስፈለጉን የሚያመላክት ነው።ቃለ ምልልሱ ሙሉውን በአንክሮ ሊሰሙት የሚገባ ነው።ያዳምጡት።
 የቀድሞው የኢቲቪ ዝነኛ ጋዜጠኛ ብዙ ወንድማገኘሁ  በፓልቶክ ስሟ (ሙያዬ) አወያይነት ይህ ዶ/ር ፍቅሬ ያደረጉት ቃለ መጠይቅ የተካሂደው  ኢትዮጵያ የመወያያ መድረክ ፓልቶክ (ECADF)  ነው። 
በቃለ መጠይቁ መጀመርያ ላይ የሚሰማው ፉከራ እና የእንግሊዝኛ ንግግር  የዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ ነው የቃለ መጠይቁ አካል ስለሆነ በትዕግስት ማዳመጡን ይቀጥሉ።





ጉዳያችን GUDAYACHNgetachewb221@gmail.com

Tuesday, September 20, 2016

መላከ ብስራት ቆሞስ አባ ሀብተየሱስ የኦስሎ ቅዱስ ገብርኤል አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ጳጉሜን 5፣2008 ዓም ወቅታዊውን ሁኔታ አስመልክተው ያስተማሩት ትምሕርት



መላከ ብስራት ቆሞስ አባ ሀብተየሱስ የኦስሎ ቅዱስ ገብርኤል አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ጳጉሜን 5፣2008 ዓም በኦስሎ፣ኖርዌይ  በኢትዮጵያ ማኅበረሰብ እና የኢትዮጵያ የጋራ መወያያ መድረክ በፒ ሆቴል ያዘጋጁት የ2009 ዓም የአዲስ ዓመት መቀበያ እና የኢትዮጵያ ቀን በሚል ተዘጋጅቶ  በነበረው የውይይት እና የፀሎት መርሃ ግብር ላይ የሰጡት ትምሕርት።
በቪድዮ መሃል የሚመጣው ተንቀሳቃሽ ምስል  በዕለቱ የቀረበው ጭውውት አካል ነው።በትምሕርቱ መሃል በመታየቱ በቅድምያ ይቅርታ እንጠይቃለን።



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Monday, September 19, 2016

የወጣት ንግሥት ይርጋ ወደ ስቃይ እስር ቤት መግባት ሚልዮን ኢትዮጵያውያን ሴቶችን ውደ ትግሉ ሜዳ ይጠራል !

ንግስት ይርጋ በጎንደር ሰልፍ ላይ 


  • ወጣት ሴቶች ለነፃነት ትግሉ የሚነሱበት አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ። 
  •  የአንዳርጋቸው ፅጌ መታሰር ሚልዮኖችን ወደ ትግሉ ሜዳ እንዳስገባ ሁሉ የንግሥት ወደ መሰቃያ ቦታ መውሰድ ሚልዮን ኢትዮጵያውያንን ወደ ትግል ሜዳ ያስገባል።
ወጣት ንግስት ይርጋ በጎንደር በተደረገው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ስሜቷ ተነክቶ በሰልፉ መካከል ከእንባ፣እልህ እና ሲቃ ጋር ነበር በሰልፉ የተሳተፈችው።ከኢህአዴግ ሰራዊት ጋር አብሮ ተሰልፎ ደርግን የታገለው በኃላም በሱዳን የተባበሩት መንግሥታት ሰላም አስከባሪ ሰራዊት ውስጥ በብቃቱ ተፈልጎ አገሩን የወከለው በመቀጠልም የታገልኩት ትግራይ ሁን ተብዬ እንድገደድ አይደለም ስነ ልቦናዬም፣ባሕሌ እና የአኗኗር ዘይቤዬ የእኔም ሆነ የሕዝቤ የአማራ ነው።የግድ ትግሬ ሁን አትበሉኝ! ብሎ በሕጋዊ መስመር ተከትሎ ከአስተባባሪ ኮሚቴዎች ጋር በመሆን መብቱ የጠየቀውን ኮ/ል ደመቀ ዘወዱ  ፎቶ ግራፍ በትሸርት አድርጋ ከስር ´´አማራ አሸባሪ አይደለም´´በሚል ፅሁፍ ሰልፉን የተቀላቀለችም ወጣት ታጋይ ንግስት ይርጋ በወያኔ ወታደሮች መታፈኗ እና ወደ አዲስ አበባ መወሰዷን ´´የጥፋት ዘመን´´ መጽሐፍ  ፀሐፊ ሙሉቀን ተስፋው በገፁ ላይ ባሰፈረው ዜና ገልጧል።

የሕወሓት እስር ቤቶች በሴቶች ላይ የሚፈፅሙት ግፍ በሰው ህሊና ከሚታሰበው በላይ ነው።ከእዚህ በፊት በቂልንጦ እስር ቤት ሴት እስረኞች ላይ ምን እንደደረሰ የዞን 9 ታሳሪ ወጣትን ታሪክ ማስታወስ በቂ ነው።በሌሊት እራቁቷን እንድትመጣ እየተደረገ በርካታ በደሎች በማንነት ላይ ያተኮረ ስድብን ሁሉ ጨምሮ ተፈፅሟል።በንግሥት ይርጋ ላይ ደግሞ ምን አይነት ፋሽሽታዊ ሥራ እንደሚሰራ መገመት ይቻላል። ይህ ሁኔታ በእራሱ የኢትዮጵያ ወጣት ሴቶችን በአዲስ መልክ የሚጣራ አዲስ እና ልዩ ለነፃነት የሚደረግ የትግል ጥሪ ነው።በሴትነት እና በማንነት ላይ የተነሱ ፋሽሽቶችን ዝም ብሎ መመልከት አይቻልም።ከአገር ቤት እስከ ውጭ ያሉ ሴቶች የነፃነት ትግሉን በአዲስ መንገድ የሚቀላቀሉበት አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ። ሕወሓት በማሰር እና በማፈን ትግል የምታዳክም ይመስላታል።የአንዳርጋቸው ፅጌ መታሰር ምልዮኖችን ወደ ትግሉ ሜዳ እንዳስገባ ሁሉ የንግሥት ወደ ስቃይ እስር ቤት መግባት ሚልዮን ኢትዮጵያውያን ሴቶችን ውደ ትግሉ ሜዳ ያስገባል።

ከእዚህ በታች የወጣት ንግስት መታፈን አስመልክቶ ሙሉቀን ተስፋው የለቀቀውን ዜና አንብቡት።

ወጣቷ የነጻነት ታጋይ ንግሥት ይርጋ በወያኔ መታፈኗ ተሰማ፥

ወጣት ንግስት ይርጋ፥ አርብ መስከረም 6 ቀን 2009 ዓ.ም ከጎንደር ከተማ ተነስታ፥ በታች አርማጭሆ ሳንጃ ከተማ ወደ ሚገኘው ቤቷ ስታመራ መንገድ ላይ ታፍና ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ የማሰቃያ ቤት መወሰዷ ታውቋል።
ወጣት ንግስት ይርጋ ተፈራ፥ ሰሞኑን ጎንደር በተቀሰቀሰው ሕዝባዊ ንቅናቄ ላይ ባደረገችው የማስተባበር ተሳትፎ በከተማው ታዋቂነትን ያተረፈች፥ ገና በሃያዎይቹ መጀመሪያ የእድሜ ክልል የምትገኝ፥ ምንም ወንጀል የሌለባት ወጣትና ፍትህ ፈላጊ ታዳጊ ዜጋ መሆኗ ነግሯል።

ወጣት ንግስት ወደ ትግሉ የገባችውና በሕዝብ ዓይን ጎልታ መታየት የጀመረችው፥ የወልቃይት ማንነት ኮሚቴዎችን በሕገ ወጥ መንገድ ዓፍነው ለመውሰድ በመጡ የወያኔ ታጣቂዎችና በኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የመከላከል እርምጃ ምክንያት ጎንደር ላይ በተቀጣጠለው ሕዝባዊ ተቃውሞ፥ ሰልፍ በመምራትና በማስተባበር ባደረገችው ከፍተኛ እንቅስቃሴ ነበር።

ይህች ወጣት ንግስት የአማራ ተጋድሎ በመባል የሚታወቀውን ሕዝባዊ ንቅናቄ የተቀላቀለችው ቂሊንጦና ቃሊቲ እስር ቤት ጓደኛ ለመጠየቅ ሂዳ ባየችው የወጣት ኢትዮጵያውያን እስረኞች ብዛትና የአማራ እስረኞች ስቃይ፥ በተለይም ከገጠሪቱ ጎንደር ባልሰሩት ወንጄል ታፍነው ተወስደው መዳረሻቸው ሳይታወቅ ለእረጅም ጊዜ ያለጠያቂ ሲሰቃዩ ላየቻቸው ወገኖቿ ጩኸትና የመከራ ድምጾች ምላሽ ለመስጠት እንደሆነ ያጫወተቻቸው የትግል አጋሮቿ ይናገራሉ።

ምንጭ = ሙሉቀን ተስፋው 
(https://www.facebook.com/muluken.tesfaw?fref=ts) 


Saturday, September 17, 2016

Thursday, September 15, 2016

በተራራማ መሬት ላይ የእርከን ሥራ ለትግራይ ያስተማረ ኮንሶ እየተገደለ፣እየተሰደደ ነው እንድረስለት!


የኮንሶ ሕዝብ በደቡብ ከሚገኙት በታሪክ፣በጠንካራ ሰራተኝነት እና ከሁሉም ጋር ተግባብቶ በመኖር ከሚታወቁት ሕዝብ መካከል ኮንሶ አንዱ እና ዋናው ነው። ኮንሶ ከኢትዮጵያ ውጭ በዓለም አቀፍ ደረጃም ኢትዮጵያን ስመ ጥር ካደረጉ የአገራችን ክፍሎች አንዷ ነች።የጀርመን ድምፅ ራድዮ የአማርኛው አገልግሎት እኤአቆጣጠር ሰኔ 30፣2011 ዓም ኮንሶን አስመልክቶ ´የኮንሶ ባህላዊ ይዞታ በአለም የቅርሥ ማህደር´´በሚል ርዕስ ስር ባስተላለፈው ፕሮግራም ላይ ስለ ኮንሶ ቅርሶች በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ መመዝገብ እንዲህ ብሎ ነበር። 

´´የተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት UNESCO ከትናንት በስትያ የኮንሶ ህዝብ ባህላዊ የመኖርያን አካባቢ በተባበሩት መንግስታት ስር እንደተመዘገበ ይፋ አድርጎአል። ድርጅቱ ከሰኔ አስራ ሁለት እስከ ሰኔ ሃያ ሁለት አመታዊዉን እና ሰላሳ አምስተኛዉን ጉባኤ በዋና ጽፈት ቤቱ ፓሪስ ላይ ያደረገ ሲሆን ከአለም አገራት የተሰባሰቡ የባህልና ቅርጽ ጥበቃ ባለሞያዎችም ተካፋይ ነበሩ። ድርጅቱ ከአፍሪቃ ዘንድሮ በአለም ቅርሥነት የመዘገባቸዉ ነገሮች በአምስት አገራት የሚገኙ ሲሆኑ፣ ከእነዚህ ውስጥ ከኢትዮጵያ፣ የ400 አመት እድሜ እንዳለዉ የተነገረለት የኮንሶ ማህበረሰብ ባህላዊ የመኖርያ ስፍራ አንዱ ነው´´ (http://www.dw.com/am/የኮንሶ-ባህላዊ-ይዞታ-በአለም-የቅርሥ-ማህደር/a-6560771) ይላል።

ኮንሶ በእርከን ሥራ በዓለም ላይ ቀደምት ተሞክሮ ካላቸው ቦታዎች ውስጥ ትጠቀሳለች።ብዙ የድህረ ምረቃ ጥናቶች በኮንሶ ዙርያ ተሰርተዋል።ዛሬ የቅርስ እና የታሪክ እንዲሁም የህዝብ በሰላም መኖር የሚያባንነው የህወሓት ስርዓት የደቡብ ህዝቦች አስተዳደርን በጀርባ እየገፋ የኮንሶን ሕዝብ እየገደለ ነው። ኢሳት በሰሞኑ ዘገባው በኮንሶ ከ9 መንደሮች በላይ ወድመዋል።ከ3ሺህ ሕዝብ በላይ ተሰዷል። በትናንትናው እለት ብቻ 26 ሰዎች አንዲት ነፍሰ ጡር ጨምሮ በጥይት ተገድለዋል። የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ አማርኛው አገልግሎት እኤአ መስከረም 14፣2016 ባስተላለፈው ዘገባ ላይ እንዲህ ይላል -

´´ከጳጉሜ 5, 2008 ዓ.ም. ምሽት ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ የመከላከያ ሰራዊት ኮንሶ በሚገኙ የተለያዩ ቀበሌዎች ነዋሪዎች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን በጥቃቱም ቁጥሩ ያልታወቀ ሰው ሕይወት መጥፋቱን፤ በዞኑ ፖሊስ ጣቢያም የዐስራ አራት ሰው አስክሬን እንደሚገኝ እንደተናገራቸው ገልጸው በርካታ ቤቶች መቃጠላቸውን ፣ ወደ 1000 ሺህ የሚጠጉ አባወራዎች ቀያቸውን ጥለው መጥፋታቸውን በሕዝብ እንደተመረጡ ከሚነገረው የኮሚቴ አባላት አንዱ አቶ ገመቹ ገንሴ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል። እሳቸው በተጨማሪ ለዚህ ሁሉ ተጠያቂው የደቡብ ክልል መንግሥት ነው ይላሉ።´´ (http://amharic.voanews.com/a/konso-resident-representative-claim-14-dead-where-regional-government-admit-for-6-dead/3509332.html?nocache=1)

ይህ ሁሉ መከራ ኮንሶ ላይ የወረደው ለምን በዞን ደረጃ እራሴን ላስተዳድር ብሎ በመጠየቁ ብቻ ነው።ይህንን ጥያቄሕጉ 15 ሺህ ሰው ብቻ እንዲጠይቅ ቢያዝም ኮሚቴው ግን ከ50 ሺህ ሕዝብ በላይ አስፈርሞ በወረዳው ምክር ቤት አፀድቆ እና ሕጋዊ መስመርን ተከትሎ ከክልሉ እስከ ፈድሬሽን ምክር ቤት ድረስ እንደጠየቀ  12 አባላት ያሉት  የኮሚቴው አባል አቶ ገመቹ ደንፌ ለአሜሪካ ድምፅ ራድዮ የካቲት 7፣2016 እኤአ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ላይ አብራርተዋል።የተሰጣቸው ምላሽ ግን ´´ይህ የሚሆነው በኢህአዴግ መቃብር ላይ ብቻ ነው´´ የሚል እንደነበር የኮሚቴው አባል ይገልፃሉ።
(http://av.voanews.com/clips/VAM/2016/02/06/9c0f1a2f-006e-4f3f-b61c-41eb67eab7fe.mp3)

በኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ላይ ያለው ኮኮብ የብሔር ብሄረሰብ መብት ማሳያ ነው እያለ የምመፃደቀው ስርዓት ለእዚህ አይነቱን  ቀላል የህዝብ ጥያቄ ተደፈርኩ በሚል ጀብደኝነት እና ታሪካዊ ህዝብን በማጥፋት የኢትዮጵያን መልክ ማጥፋት እና የእራሱን አዲስ ታሪክ መፃፍ  የሚፈልገው ሕወሓት የኮንሶን ሕዝብ ከደቡብ ህዝቦች አስተዳደር ጀርባ ሆኖ እርስ በርስ እያጫረሰው ነው።ኮንሶ የኢትዮጵያ ክብር ነው። ኮንሶ የኢትዮጵያ አንዱ ፊት ነው።ይህ ሕዝብ የሕወሓት ህገ መንግስት አይጠብቀውም። እኛ ኢትዮጵያውያውያን ብቻ ነን  የምንደርስለት።የእርከን እርሻ ትግራይን ያስተማረ ኮንሶ ሕዝብ እየተገደለ ነው።እንድረስለት።




ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Sunday, September 11, 2016

´የጥፋት ዘመን´ የተሰኘ በጋዜጠኛና ደራሲ ሙሉቀን ተስፋው በዐማራ ሕዝብ ላይ የተፈፀመ የዘር ማፅዳት የሚያጋልጥ ጥናታዊ መፅሐፍ ገበያ ላይ ነው

የመጽሐፉ የፊት ሽፋን  
´´ወጣቱ ጋዜጠኛና ደራሲ ያቀረበልን በማያሻማ መረጃ የተደገፈ መጽሐፍ ታሪካዊና ወቅታዊ ነው´´  ዶ/ር አክሎግ ቢራራ 
´´ይህ መጽሐፍ ማንኛውም የኢትዮጵያ ህልውና የሚያሳስበው ሰብዓዊ ፍጡር ሊያነበው የሚገባ ነው።´´ዶ/ር አሰፋ ነጋሽ 
291 ገፆችን የያዘው ይህ መጽሐፍ በዐማራ ሕዝብ ላይ ከ1983 እስከ 2007 ዓም ድረስ የተፈፀሙትን ግድያዎች እና እንግልቶች በማስረጃ አስደግፎ ያሳያል።
በ1967 ዓም በማነፌስቶው ላይ የዐማራ ሕዝብን በጠላትነት መፈረጁን በግልፅ ያሳወቀው ሕወሓት ላለፉት 25 ዓመታት የፌድራል ሕጉ እንዲኮላሽ ከማድረግ ጀምሮ ምን ሲያደርግ እንደነበር በግልፅ እና በዝርዝር ያስረዳል።
ለወደፊቷ ኢትዮጵያ ይህ ክፉ ተግባር እንዳይደገም ሁሉም ዜጋ ቢያነበው ኃላፊነት እንዲሰማው ያግዛል።
መጽሐፉ  በአውሮፓ እና አሜሪካ በከፍተኛ ደረጃ ተነባቢነት እያገኘ ነው። የመፅሐፉ አዘጋጅ እና ፀሐፊ ጋዜጠኛ እና ደራሲ ሙሉቀን ተስፋው ለኢሳት የሰጠው ቃለ መጠይቅ ከእዚህ በታች ባለው ቪድዮ ይመልከቱ።


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Wednesday, September 7, 2016

የህወሓት አባላት እና ደጋፊዎች አምስቱ ግለሰባዊ እና ተቋማዊ ጠባዮች



ህወሓት በትግል ወቅት ለእርዳታ የመጣውን እህል በጎን ስትሸጥ የሚያሳይ (ፎቶ ቢቢሲ 


መነሻ 

በእዚህ ፅሁፍ ውስጥ የህወሓት አባላት እና ደጋፊዎች ማለት እራሱን የሕዝባዊ ወያኔ አርነት ትግራይ ብሎ የሚጠራው ድርጅት አባላት እና ደጋፊዎች ማለትም እራሳቸውን በግልፅ እና ስውር አባልነት የሚንቀሳቀሱ፣በተለያየ ጥቅሞች ሕልውናቸው ከድርጅቱ ጋር የተሳሰረ እንደሆነ የሚያምኑትን ሁሉ ያጠቃልላል። እዚህ ላይ ´´ህወሓት ማለት የትግራይ ሕዝብ ነው የትግራይ ሕዝብ ማለት ህወሓት ነው´´ የሚለውን የሳሞራ የኑስ ንግግር ተከትለው የሚያስቡ ካሉ ቢያንስ እኔ በአሁኑ ሰዓት እዚህ ድምዳሜ ላይ ስላልደረስኩ የሳሞራ እና አድናቂዎቻቸው ሃሳብ ሆና ትቆይ። በእዚህ መንገድ የሚያስቡ የማሰብ መብታቸውን እያከበርኩ ጊዜ የሚፈታው ስለሆነ በእሱ ላይ ጊዜ መውሰድ አልፈለኩም።ሆኖም ግን ይህ ፅሁፍ እራሳቸውን በቆይታ፣በስልጠና እና ባላቸው ማኅበራዊ ግንኙነቶች ሁሉ የህወሓት አባላት እና ደጋፊዎች የተላበሷቸውን አምስቱ ግለሰባዊ እና ቋማዊ ጠባዮችን  ለመግለፅ እሞክራለሁ።እነኝህ አምስት ጠባዮች ከከፍተኛው እርከን እስከ ታች ያለው ካድሬ ድረስ በመጠን እየተለያዩ የሚንፀባረቁ ናቸው።ሆኖም ግን እያንዳንዱ እንቅስቃሴያቸውን በንቃት መገንዘብ እና መመልከት ይጠይቃል።

የእዚህ ፅሁፍ አቅራቢ እነኝህን ፀባዮች እንዲሁ በግምት የሚያቀርባቸው ሳይሆኑ በአገር ቤትም ሆነ በውጭ ባለበት ጊዜ በሥራም ሆነ በማኅበራዊ እና ቤተሰባዊ ግንኙነት ሁሉ የተመለከተው ምልከታ ስለሆነ ፅሁፉ በተራ ግምት እና መላ ምት ላይ የተመሰረተ አለመሆኑን መገንዘቡ ተገቢ ነው። 

አምስቱ  ፀባዮች 

1. ድብቅነት 

ህወሓት አባላት፣ደጋፊዎች እና ድርጅቱ እራሱ ሕይወታቸው የተመሰረተው በድብቅነት ላይ ነው።ሀብታቸው፣ የሚሰሩት ሥራ፣ ማንን እንደሚወዱ እና እንደሚጠሉ ሁሉ በግልፅ ለእራሳቸው ሰው ካልሆነ በቀር አይገልጡም።ለምሳሌ አንድ ከእነርሱ ካምፕ ውጭ የሆነ ሰው ምን ያህል ጥሩ እና ምክንያታዊ ቢሆን ስለ ጥሩነቱ እና ምክንያታዊነቱ ከሚከራከሩት ይልቅ ቀድመው በተደበቀ ጥላቻ ውስጥ ሆነው ለሌላ ሰው ግን ጥሩነቱን ይናገራሉ።እዚህ ላይ አንዳንድ ማስረጃዎች ልጥቀስ።አቶ መለስ አቶ አዲሱን በአደባባይ ሲያሞግሱ ትሰማላችሁ።አቶ አዲሱ በአቶ መለስ ሞት ላይ አልቅሰዋል።አቶ መለስ ግን አቶ አዲሱ ከስልጣን የወረዱ ቀን ´´ኢትዮ ፈርስት´´ በአቶ አዲሱ መሰናበት ምን ተሰማዎት? ሲባሉ አቶ መለስ ´´ብዙ ሳይዘባርቅ መውረዱ ´´የሚል ቃል ሳያስቡት ተጠቀሙ (ይህ በዩቱብ መመልከት ይቻላል)። የአቶ መለስ ፈገግ እያሉ መግደል የህወሓቶች የተለመደች የድብቅነት ሕይወት አንዱ መገለጫ ነው። 

ሌላው የድብቅነት መገለጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ክስተቶች ውስጥ እራሳቸው ፈፅመው ሌሎች እንዳደረጉት የሚሰሩት ድራማዎች ናቸው።አሁን እየታወቀ መጣ እንጂ በአማራው ሕዝብ በደቡብ ክልሎች መሰደድ፣መገፋት ጉዳይ ሁሉ ከጀርባ የሕግ ድጋፍ ሲሰጡ የነበሩ የህወሓት ሰዎች ናቸው።ይህ የድብቅነት ጠባይ ከፍተኛ ደረጃ የደረሰበት አንዱ ማሳያ ደግሞ ከአቶ መለስ በኃላ ውሳኔ ሰጪው አካል ተሰውሮ ውሳኔ እየሰጠ አቶ ኃይለ ማርያምን ከፊት ማስቀደሙ ነው።አሁንም በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየተሰሩ ያሉ በርካታ ድብቅ ስራዎች እንደሚኖሩ ካለፉ ታሪኮች መረዳት ይቻላል።

2/ ተንኮል እና ሴረኛነት 

ተንኮል እና ሴራ በህወሓት እና በአባላቱ ዘንድ እንደ ትልቅ ዝና እና ገድል ይቆጠራል።ይመስለናል እንጂ የአቶ መለስ አድናቂዎች ህወሓቶች እና ደጋፊዎቻቸው አቶ መለስን የሚያደንቁበት ዋና ምክንያት እና እነርሱ በአደባባይ ´´ችሎታ´´የሚል ሽፋን ይስጡት እንጂ ብዙ ህወሓቶች እና ደጋፊዎች የሚያደንቁበትን መንገድ ጠጋ ብላችሁ ስትጠይቁ  የሚነግሯችሁ በህወሓት ላይ ያንዣበበው የስልጣን ተግዳሮቶች ሁሉ አቶ መለስ እንዴት በተንኮል እና በሴራ እንደተሻገሩ ሲናገሩ ትሰማላችሁ።ለእዚህም የ1997 ዓም ከቅንጅት ጋር ያደረጉት ድርድር እና ክህደር እንደ ትልቅ ገድል ሲወራ መስማት በህወሓት መንደር መስማት የተለመደ ነው። ስለዚህ ተንኮለኛ እና ሴረኛ የህወሓት አባልም ሆነ ደጋፊ እንደ ትልቅ ዝና ይነገርለታል።በጤናማው ዓለም ግን ይህ የክፉዎች ተግባር ነው።ለእዚህ ነው የሚሰሩትን ተንኮሎች እና ሴራዎች በተመለከትን ቁጥር በማኅበራዊ ሚድያ ሁሉ ሳይቀር በጤነኛ ዓለም አስተሳሰብ እሳቤ እያሰብን ስንብከነከን እንውላለን።ለሕወሐታውያን ግን ይህ ከትልቅ ጀብዱ የሚቆጠር ነው።

እስረኛ ሊያመልጥ ሲል ገደልነው፣እሳት በእስር ቤቱ ውስጥ ተነሳ፣ ታክሲ ውስጥ አሸባሪ ቦንብ አፈነዳ፣ በሀውዜን እና ሐሙሲት ገበያ ላይ አይሮፕላን ደበደበ፣ የኦሮምያ ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ኩምሳ አረፉ፣ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ እስር ቤት ለሞት የሚያደርስ ህመም ታመሙ፣ የብሔራዊ ባንክ ወርቅ ተዘረፈ፣ ይቀጥላል በርካታ ጉዳዮች የተንኮል እና የሴረኝነት ውጤቶች ብዙ ናቸው።ህወሃታውያን ደግሞ  በእዚህ ሁሉ ተንኮል ይቁራሩበታል።በግለሰብ ደረጃ ስታገኙአቸውም ተንኮልን እንደ ትልቅ እውቀት ይቆጥሩታል።

ህወሓቶች እና ደጋፊዎቻቸው ተንኮል እና ሴራ ሲሰሩ እየሳቁ ነው እንጂ በተጨማደደ ፊት አይደለም።የአገሬ እና የድርጅቴ ሰው አይደለም ባሉት ላይ ግን ተንኮል ሲያደሩ የሚጀምሩት ከቤተሰብ ነው።የመጀመርያ ኢላማቸው ቤተሰቡን መከፋፈል ነው።የህወሐቶች ሰለባ የሆኑ በርካታ ቤተሰቦች እና ወዳጆች ባላወቁት መንገድ ተቃቅረው ቆይተው ጉዳዩን ሲመረምሩት የወያኔ ሴራ እንደሆነ ይረዱታል።በህወሓት ዘንድ የምትናቅ እና የተንኮል ድር የማይደራባት ትንሽ መርፌ የለችም።በአንድ ድርጅት ውስጥ ከበር ካለው ዘበኛ እስከ የበላይ አለቃ ድረስ ተንኮል ለመሸረብ ደጋፊዎቻቸውን በማሰለፍ ታጥቀው ይነሳሉ።የኢትዮጵያ ቴሌ መስርያቤት፣ የመብራት ኃይል፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ሌሎችም በህወሓት የዘር መርዝ ተወግተው የቆሰሉ እና በርካታ ባላሙያዎችን እየወጉ እና ባላጠፉት ጥፋት እየወነጀሉ ከስራ አባረዋል፣የበይ ተመልካች ሆነዋል።በዘመነ ህወሓት  የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት ሥራ አስኪያጆች እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አንድ ሥራ አስኪያጅ እንዴት ሥራ እንደለቀቁ  ማስታወስ በቂ ነው።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሥራ አስኪያጅ እስከ 1980ዎቹ መጨረሻ እና 90ዎቹ መጀመርያ የነበሩት በእስር እንዲማቅቁ የተደርጉበት እና ሌላው ሥራ አስኪያጅ ጧት በመኖርያ ቤታቸው ሞተው የተገኙበት ሁኔታ እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሥራ አስኪያጅ በመሆን ያገለገሉ ግለሰብ እንዴት ስራቸውን እንዲለቁ እንደተደረገ ለአብነት ማንሳቱ የህወሓትን ተንኮል እና ሴራ ግልፅ አድርጎ ያሳያል።

3/ ሰው መሳይ በሸንጎነት 

ህወሓቶች እና ደጋፊዎቻቸው የሚታወቁበት እና የትካኑባት አንዷ መንገድ በሰው ፊት እና በአደባባይ ሰው መስሎ መታየት ነው።ህወሓት በውጭ ዓለም ስሙ በክፉ ሲነሳ የሚያመውን ያህልምንም አያመውም።ግለሰቦቹም እንዲሁ ናቸው።በአደባባይ ስትመለከቷቸው የሃይማኖት ሰዎች፣ወደ እምነት ቦታዎች አዘውትረው በመሄዳቸው ቀድመው የሚታዩ፣ ፌስ ቡክ ገፃቸው ላይ የክርስቲያንም ሆነ የእስልምና እምነት ዋጋ የሚሰጣቸውን ነገር ሁሉ በመለጠፍ ፍፁም ሃይማኖተኛ ለመምሰል የሚቀድማቸው የለም።በማኅበራዊ ኑሮም ቀድመው ልሙት ባይ ይሆናሉ።ይህ ሁሉ ግን ከሀዘነታ ሳይሆን ከስልት አንፃር ብቻ የሚፈፅሙት መሆኑን ቆይታችሁ ጥረዱታላችሁ።

አንዲት በፈስ ቡክ ገፅ ላይ ነጠላ ለብሳ ወይንም ስትፀልይ የምታዩአት ወይንም የምትመለከቱት የህወሓት አባል ወይንም የተባይ ተጋሪ በገሃዱ ዓለም ላይ ያላቸው እምነት ያስደነግጣል።እነኝሁ ሰዎች በአደባባይ ስለሚሞተው ሕዝብ ስታወሯቸው የሃይማኖታቸውን አማልክት በመጥራት ስለምሞተው እና ስለሚታሰረው ሕዝብ አንዳች ጉዳይ እንደሌላቸው በድፍረት ሲናግሩ አፋቸውን አያደናቅፋቸውም።

4/ ዘረኝነት 

ለህወሓት እና ደጋፊዎቻቸው የእነርሱ መንደር ብቻ የበላይ አድርጎ የሚጠቀሙበት አንድ አባባል አለ። ´´ምንትስ አስር ይውለድ´´ የምትል።በግለሰብ የህወሓት አባላትም ሆኑ ደጋፊዎች ዘንድ ከእነርሱ መንደር ውጭ ላለ ሰው መጀመርያ ሞቅ ያለ ፈገግታ ሲያሳዩ ትመለከታላችሁ።በአጋጣሚ ዘወር ካላችሁ ፊታቸው በጥላቻ ሲገላምጧችሁ ትመለከቱና ፈገግታው የውሸት መሆኑን ትረዳላችሁ። በምንም ደረጃ የሚገኝ ሰውን በሰውነቱ ብቻ መመልከት ክልክል መሆኑ በህወሓት መንደር የተከለከለ ነው። ለምሳሌ አንድ ሰው በጠባዩ፣ በመልካም ስራው፣ በችሎታው ሳይሆን ቀድመው የሚፈርጁት ከእነርሱ ሰፈር በመወለዱ እና ባለመወለዱ ነው። እነርሱ መንደር ከተወለደ እንደ አዋቂ፣ አስተዋይ እና የኢትዮጵያ ጠቃሚ ዜጋ እንደሆነ ያስባሉ ብቻ ሳይሆን ይደመድማሉ።ለምሳሌ አንድ መስርያ ቤት ውስጥ ሄደው ያገኙት ሰራተኛ ከእነርሱ መንደር ካልተወለደ በመስርያ ቤቱ ውስጥ የተቀጠረው የሆነ ተንኮል በህወሓት ላይ ሊሰራ እንጂ በኢትዮጵያዊነት ፍቅር ነው ብለው ላለማመን አይምሯቸውን ዘግተውታል።

የህወሓት እና ደጋፊዎቹ ዘረኝነት የሚገለፀው በተለያየ መንገድ ነው።ከእነዚህ ውስጥ ዋነኛው እና አንዱ የእነርሱ ያልሆነ ያሉትን ማግለል እና አድልዎ መፈፀም ነው።በግለሰብ ደረጃ ያገሏችኃል።በንግድ ድርጅት ደረጃ፣በእምነት ድርጅት ደረጃ፣በማኅበራዊ ግንኙነት ሁሉ ያላቸውን ትስስር የሚፈፅሙት ´´በመንደር ውልደት´´ ከሚመስላቸው ጋር ብቻ ነው።አንድ ሰው የቱንም ያህል መልካም ሰው መሆኑ በጥላቻ እና ማግለል መርዝ ከመነደፍ አያድነውም።ይልቁንም ትውልዱ እየተጠቀሰ ይነቀፋል፣ ሲብስ ደግሞ ከአሸባሪ አይ ኤስ ኤስ ጋር ሁሉ እየተነፃፀረ ይሰደባል። እራሳቸውን የተለዩ ፍጥረቶች አስመስሎ ለማቅረብ መሞከር እና መኮፈስ የሕወሃቶች እና ደጋፊዎቻቸው ዋነኛ መለክያ ነው።     

የህወሓት ዘረኝነት አይን ያወጣ እና እፍረተ ቢስ በሚባል ደረጃ የታየ ነው።የጦር ሰራዊቱን መኮንኖች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ፣የአዲስ አበባ አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ፣ከፍተኛ የመንግስት ሹሞች እና ቁልፍ ቦታዎችን፣ከፍተኛ የንግድ ስራዎችን፣በውጭ አገራት የሚገኙ ኤምባሲ ሰራተኞች እና አምባሳደሮችን ሲወርድ በአዲስ አበባ በቀበሌ ደረጃ ሊቀመንበሮች እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሻንጣ አውራጅ እና ጫኝ ድረስ ከአንድ አካባቢ የመጡ መሆናቸውን ብቻ መጥቀሱ የጉዳዩ አሳፋሪነት እና አይን አውጣነት በሚገባ ያሳያል።

5/ ስግብግብነት 

ህወሓት እና ደጋፊዎቹ የሚለዩበት አንዱ ፀባይ ስግብግብነት ነው።እነርሱ ያልቀደሱት ቅዳሴ እንደማያርግ፣እነርሱ ሃሳብ ያልሰጡበት የጥናት ወረቀት እንደማይሳካ፣ እነርሱ በሽርክና ያልገቡበት ኩባንያ እንዲፈርስ፣እነርሱን የማያወድስ ፅሁፍ አሸባሪ፣ ለእነርሱ ድርጎ ያልሰጠ ነጋዴ አጭበርባሪ በማለት ሁሉም ቦታ መግባት ይፈልጋሉ። እድር ውስጥ፣ጉልት የምትሸተውን፣የቀን ሰራተኛውን ሌላው ቢቀር እራሳቸው የሾሙትን ጠቅላይ ሚኒስትር ሳይቀር ከምህዋራቸው የሚወጣ ስለሚመስላቸው ተስገብግበው ሁሉም ላይ ለመታየት ይፈልጋሉ።

በገልሰብ ደረጃ ስትመለክቷቸው እምነት ቤቱ ቀድመው ፃድቃን ለመሆን ከመስተንግዶ እስከ መዝሙሩ፣ ከእርዳታ ሰጪ እስከ ወጥ ቤት ሁሉ ፊታቸውን ማስመታት ስራዬ ብለው ይይዙታል።በተለይ የኅብረተሰቡ የጋራ መገለጫዎች እንደ እድር፣አብያተ ክርስቲያናት፣መስጊዶች፣ የንግድ ማኅበራት፣የሰራተኛ ማኅበራት፣ ሌላው ቀርቶ የቤተሰብ ማኅበራት ውስጥ ሁሉ ምን እንደሚደረግ ለማዳመጥ እንዲገቡ ይደረጋሉ። ህወሓቶች ይህንን የሚያደርጉት ከላይ የተጠቀሱት ድብቅነት፣ተንኮል እና ዘረኘነት ከማኅበረሰቡ መልካም ባህርያት ጋር ፈፅመው የተቃረኑ ስራዎች እንደሆኑ ስለሚያውቁ በከፍተኛ የራስ መተማመን እጦት እና ጥርጣሬ ማዕበል ይመታሉ። ስለሆነም  የታክሲ ሹፌሩም ሆነ ተሳፋሪው፣አስተማሪውም ሆነ ተማሪው፣ ዲያስፖራውም ሆነ የአገር ነዋሪውን ሁሉ ይጠረጥራሉ።ለእዚህ ነው አንድ ኮሽታ በተሰማ ቁጥር በእነርሱ አጠራር ጠላቶቻቸው እስከ ሚኒስቴር ማዕረግ ደረጃ ድረስ እንደ ገቡባቸው በፍርሃት እና በድንጋጤ የሚናገሩት።

ባጠቃላይ ህወሓት እና ደጋፊዎቹ ከላይ የጠቀሱትን አምስት ጠባዮች ሲይዙ በአንድ ቀን እና ምሽት የመጡ ሳይሆኑ ለእራሳቸውም ሳይታወቃቸው ቀስ በቀስ በድርጅታቸው ደረጃ እና በግለሰብ ደረጃ ያደጉ ናቸው።ይህ ግን ለእነርሱ ላይታወቅ ይችላል።ይህ ደግሞ አሁን ያደረሳቸው ደረጃ እራስን ዝቅ አድርጎ ከማየት የመነጨ አጉል ጀብዱ የተቀላቀለበት ፍፁም ጭካኔ ቀድሞ ከነበረው አድጎ እና ገዝፎ ወደ ባሰ ፋሽሽታዊ ደረጃ አሻግሯቸዋል።ለእዚህ ማሳያዎቹ ሰሞኑን በኦሮምያ፣ጎንደር እና ጎጃም የሚፈፀሙት አረመንያዊ ድርጊቶች ናቸው።ግድያዎቹ የፍርሃት፣በእራስ ያለመተማመን እና ከፍርሃትም የሚመነጩ ናቸው። አንዳንዶች ደጋፊዎቻቸው አረመንይያው ድርጊቶችን እንደ ጀግንነት ሲቆጥሩላቸው ይስተዋላል። ይህ ግን ትክክል አስተሳሰብ አይደለም።በእራስ መተማመን ያለው እና አቅም ያለው ድርጅትም ሆነ ግለሰብ የእራሱን ወገን በመፍጀት እርካታ እና ጀግንነት ሊሰማው ባልተገባ ነበር።ለእዚህ አይነቱ የህወሓት ፀባያት መፍትሄው ስርዓቱ እራሱን ጠግኖ ሌላ አውሬ እንዲሆን መፍቀድ በአገርም ሆነ በሕዝብ ላይ እንደመቀለድ ይቆጠራል። ህወሓት እንደ ድርጅት እና ደጋፊዎቹ በርካቶችን እየወጉ ገድለዋል፣በየዋህ ልቦና የቀረቧቸውን በፈገግታ መርዝ እያስላሱ አምክነዋቸዋል። ለእዚህ ማሳያ እንዲሆን አንድ ጉዳይ ብቻ አንስቼ ላብቃ።ሰሞኑን በኢትዮጵያ በህወሓት እና በቀረው ሕዝብ መካከል ያለው ግብግብ ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ እና አቶ በረከትን ጨምሮ በጎንደር ሲኒማ አዳራሽ በጠሩት ስብሰባ ዱላ ቀረሽ ንግግር እና እሮሮ በመጨረሻም አዳራሹ በድንጋይ ተደብድቦ ሾልከው አዲስ አበባ መጥተው ሳለ። በሕወሓታዊ ሽሩድ አቀራረብ አቶ አባይ ፀሐዬ፣በረከት ስምዖን፣ዶ/ር ካሱ ኢላላ እና አባ ዱላ አይናቸውን በጨው አጥበው፣የውሸት ፈገግታ እያሳዩ እና እየተቅለሰለሱ ስልጣን አንልቀቅ ግን እንታደስ የሚል አጀንዳ ይዘው በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ብቅ አሉ። ህወሓቶች ማለት እንዲህ ናቸው።ያልተመቻቸው ጊዜ ስያሞግሱ ያሰሙሃል ዘወር ስትል የመውጊያ እና የጥላቻ ጦራቸውን ይስላሉ።ሕዝብ በ1997 ዓም ሆ! ብሎ ሲነሳ እንደራደር ይሉሃል።ጉዳዩ የበረደ ሲመስላቸው ´´ኢህአዴግ ሾላ አይደለም በድንጋይ የሚወርደው´´ይሉሃል። እነአቶ በረከትም ነገረ ህወሓትን በካድሬ አንደበታቸው ሊያነበንቡልህ በኢቲቪ መስኮት ቀለስለስ እያሉ የቀረቡት ለማታለል እንጂ በተመሳሳይ ሰዓት ግድያ እና እስር በንፁሁ ኢትዮጵያዊ ላይ እየተፈፀመ ነው።ህወሓት እና ደጋፊዎቹ በጋራ የምጋሯቸውን ፀባያት ከድርጅት እስከ ግለሰቦች ድረስ በጥንቃቄ መመልከት እና መከላከል የያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው።ህወሓትን በሚገባ እወቁት።ደጋፊዎች ጋሻ ጃግረዎችንም ፀባይ ተረዱ።ፈፅሞ ከኢትዮጵያዊነት ባህሪ የተለየ መሆኑን ትረዳላችሁ።     





ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

Monday, September 5, 2016

በስደት የሚገኘው የቅዱስ ሲኖዶስ ብፁአን አባቶች ከጳጉሜን 1 እስከ መስከረም 3 ድረስ ብሔራዊ የጸሎትና የሐዘን ቀን እንዲሆን አውጀዋል (የውሳኔውን ሙሉ ቃል ያንብቡ)



ብፁዕ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያሪክ ዘኢትዮጵያ  

ስመ አብ፣ ወወልድ፣ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! 

“አቤቱ ሕዝብህን አዋረዱ፣ ርስቱንም አስቼገሩ፣ ልቴቲቱና ድሃአደጉን ገደሉ ግዚአብሔር አያይም፣የያዕቆብ አምላክ አያስተውልም አሉ።” /መዝ 935/ 

በመላው የአገራችን ኢትዮጵያ ክፍሎች የምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ በቅድሚያ ተወልዳችሁ ባደጋችሁበት በአያት በቅድመ አያቶቻችሁ ርስት ላይ፥ በሰላምና በነጻነት እንዳትቀመጡ ፣ በጨካኞችና በነፍሰ ገዳዮች ተከባችሁ ለስደት የተዳረጋችሁ፣ ቆስላችሁ በሆስፒታልና በየመንገዱ ወድቃችሁ በስቃይ ላይ ለምትገኙ ልጆቻችን፣ታስራችሁ ያለፍትህ በጨካኞች እጅ የምትሰቃዩ ሁሉ፥ በመከራ ያሉትን የሚያጽናና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ፍጹም ሰላምና ምሕረትን በእናንተ ላይ እንዲያበዛ ሎታችንን ሁሉ ወደሚሰማና ወደሚያይ ወደ ልዑል እግዚአብሔር እናቀርባለን። ነፍሳችሁን ከገዳዮች ለማዳንና በእኩያን እጅ ላለመውደቅ፣ ወገኖቻችሁን ከፋሽስቱ የህወሐት ወራሪ ይል ለመታደግ ለምትባዝኑ ልጆቻችን ሁሉ፣ የኃያሉ እግዚአብሔር በቃና ምሕረት ከእናንተ ጋር ይሆን ንድ ልዑል እግዚአብሔርን እንማልዳለን! ፍትህንና ነፃነትን በመጠየቃችሁና ማንነታችን ይጠበቅልን በማለታችሁ ምክንያት፣ በቀያችሁ እንደ በግ በግፈኞች ለታረዳችሁ፣ በጨካኞች እጅ በከንቱ ደማችሁ ለፈሰሰው ልጆቻችን በሙሉ፣እግዚአብሔር አምላክ የሰማዕታትን ክብርና እረፍት እንዲያጎናጽፍልንና በግፍ
የፈሰሰውን ንጹህ ደማችሁን ይበቀልልን ዘንድ፣ በጥልቅ ሐዘን ውስጥ ሆነን ወደ እውነተኛው ፈራጅና ተበቃይ አምላካችን፣ በመሪር ለቅሶና በብዙ ሐዘን ውስጥ ሆነን እንጮሃለን።ለሟች ቤተሰቦች እንዲሁም ለመላው ህዝባችንም መፅናናት ይሰጥልን ዘንድ ቅዱስ እግዚአብሔርን እንለምናለን። በመላው አገራችን ላይ እየደረሰ ባለው እልቂት፥
የቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት በሙሉ የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንገልጻለን።

ውድ ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን !

ይህን መግለጫ በምናስተላልፍበት በዚህ ሰዓት፣ የወያኔ ኢሕአዴግ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ባስተላለፉት የዘር ፍጅት ትእዛዝ መሠረት፣ የጎንደርና የጎጃም ህዝብ በምላ በመንግስት ወታደሮች እየተጨፈጨፈ እንደሆነ፣ አካባቢውም የጦር ቀጣና እንደሆነ፣በቅሊንጦ እስርቤት የተሰሩ የህሊና እስረኞች ላይ ጥቃት መፈጸሙን በመገናኛ ብዙሃን እየሰማን ነው። ሕዝባችን በገሩ እንደ ሰው በነጻነት የመኖር መብቱን ተነጥቆ በታጠቀ የመንግሥት ሠራዊት እየተገደለና እየተዋከበ በብዙ እንግልትና መከራ ላይ እንደሚገኝ ለማረጋገጥ ችለናል። በጎንደር እና በጎጃም ሕጻናትና እናቶች ሳይቀሩ በመሣሪያ እየተደበደቡና እየተገደሉ ነው። ዛሬ ሕዝባችን ተዋርዶ ፣ ድሆችና አቅመ ቢሶች በግፍ እየተገደሉ መንገድ ላይ በሚጣሉበት ወቅት ላይ እንገኛለን። በብዙ የሚቆጠሩ ወጣቶች ታስረው ኢሰብአዊ የሆነ ግፍ እየተፈጸመባቸው ይገኛል። በሥልጣን ላይ የሚገኘው የሕወሐት ዘረኛ ቡድን ይህ የግፍ ድርጊቱን ዓለም እንዳያውቀው፣ ስልክና ኢንተርኔት የመሳሰሉ የመገናኛ ብዙሐን መንገዶችን በመዝጋት የጎጃምና የጎንደርን ሕዝብ አፍኖ በማሰቃየት ላይ ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት በመምላ ሐገሪቱ የሚገኙት ሕዝቦች በጨካኞች አገዛዝ ቀንበር ሥር በመሆናቸው፣ከገዢው ጥቅመኞች በቀር ሰላምና ነጻነት የሚሰማቸው ጎች በአገራችን የሉም።

በአሁኑ ሰዓት ሕዝባችን የሚገደለው አብረን እንኑር፣ ነገር ግን ርስታችንን አትቀሙን ስላለ ነው፤ አሁን ሕዝባችን የሚገደለው በአንዲት ሃገር እንጂ በመከፋፈል አናምንም፣ አማራ ወይም ኦሮሞ ወይም ትግሬ ወዘተ እያላችሁ አትከፋፍሉን በማለቱ ነው። ሕዝባችንም ለዚህ ሁሉ መከራ የተዳረገው በገራችን ሕዝብ የመረጠውና ዲሞክራሲያዊ መንግሥት ስለሌለ፣ ያለው መንግሥት ነኝ ባይ አካል በሕዝብ እኩልነትና በሃገር አንድነት የማያምን፣ ዘረኝነትና ሙሰኝነት የተጠናወተው ፍጹም አምባገነን ቡድን በመሆኑ ነው። በአሁኑ ወቅት በመላ ሃገሪቱ ይልቁንም በጎጃም፣ በጎንደርና፣ በኦሮሞ ሕዝብ ላይ የታወው ጦርነት ለገሩ አንድነት ከኢትዮጵያውያን ወንድሞቹ ጋር ክቡር ዋጋ ሲከፍል የኖረውን ሕዝብ ዘርና ተተኪ ትውልድ ለማጥፋት ነው። የኢትዮጵያን ታሪክ ለማጥፋት ቆርጦ የተነሣው፣ ይህ ዘረኛ መንግሥት ሕልሙን ለማሳካት የቻለውን ግፍ ቢፈጽምም አይሳካለትም፤በመሆኑም ሕጋዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፥ ለገራችን ህልውናና ለሕዝባችን ደኅንነት መረጋገጥ ሲባል፣ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን የምትችሉትን ታደርጉ ዘንድ ከዚህ የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥቷል።  

1. ከጳጉሜ አንድ  ጀምሮ እስከ መስከረም ስት ድረስ ብሔራዊ የጸሎትና የሐዘን ቀን እንዲሆን ታውጆአል! 

መንግሥት አስተዳድረዋለሁ በሚለው ሕዝብ ላይ ጦርነት አውጆ፣ የንጹሐን ልጆቻችን ደም በምድራችን ላይ በግፈኞች በየዕለቱ እንደ ጎርፍ እየፈሰሰና አቅመ ደካማ አረጋውያንና ሕፃናት ረዳት አጥተው በጭንቅ እየዋተቱ ስለሆነ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በቤቱ ለዘመን መለወጫ እንደ ቀደሙት ዘመናት ሁሉ እርድ አርዶ፣ ድግስ ደግሶና፣ ተድላ ደስታ እንዳያደርግ በጥብቅ አዘናል። ጊዜው ብሔራዊ የሐዘን ጊዜ ስለሆነ፣ ሁሉም ሕዝብ ቢቻል በህብረት ካልተቻለ በግል በመሆን በጸሎትና በምሕላ ለአንድ ሱባኤ ያህል ወደ እግዚአብሔር እንዲጮህ ቅዱስ ሲኖዶስ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪውን ያቀርባል።

2. ለኢትዮጵያ የመከላከያና የጸጥታ እንዲሁም የጦር ሠራዊት አባላት በሙሉ! 

ግብር እየከፈለ፣ ደመወዝ እየሰጠ በሚያኖራችሁ፣ ከአብራኩ በአስገኛችሁ ሕዝብ ላይ ከመተኮስና የገዛ ቤተሰባችሁን ከመግደል የበለጠ ምድራዊ ወንል የለም። ይህ አድራጎት በምድርም በሰውና በህሊናችሁ ፣ በሰማይም በእግዚአብሔር ት ያስፈርድባችኋል። ሕዝባችሁን እየገደላችሁ ከምትሞቱ ከሕዝባችሁ ጎን ተሰልፋችሁ በክብር ብትሰዉ ሕያው ታሪክ ሠርታችሁ ታልፋላችሁ። ዛሬ ከህወሃት ጎን ተሰልፋችሁ የምትሞቱት ሞት ገር ነጻ ሊያወጣ ዘምቶ ከባእዳን ጋር ተዋግቶ በክብር ሞተ የሚያስብል አይደለም፤ የጎጃምን ፣ የጎንደርን፣ የኦሮሞን፣ የኮንሶን ህዝብ ሊያጠፋና ሊገል ዘምቶ ሞተ ነው የሚያስብለው፤ ወገኑን ሲገድል ሞተ መባል ትሻላችሁን? ወይስ ስለሕዝቡ መብት ሲታገል ሞተ መባል? ይህ ሥርዓትና መንግሥት ያልፋል፣ ይሻራል፤ታሪክ ግን ሁልጊዜም አሸናፊ ነውና እስከ ዓለም ፍጻሜ ይኖራል።ስለዚህ ለሕዝባችሁና ለወገናችሁ ክብር ስትሉ ለከፋፋዩና ነፍሰ ገዳዩ የሕወሃት አምባገነን ቡድን መሣሪያ እንዳትሆኑና በወገናችሁ ላይ እንዳትተኩሱ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል። ከዚህ አባታዊ ምክራችን ተላልፎ ንፁሐን ወገኖቹን የሚገል፣ የሚያንገላታ፣ የሚያስርና፣ የሚደበድብ እንዲሁም ለዚህ ክፉ ቡድን ጥቆማ እየሰጠ የሚያሳስር ሁሉ፣ ቅዱስ ሲኖዶሱ በሥልጣነ ጥሮስ ወጳውሎስ አውግዞታል!ከህወትና ከቅጥረኛ ገዳዮች ጋር የሚተባብረውን ሁሉ የኢትዮጵያ ህዝብ “ውጉዝ ከመ አርዮስ” ብላችሁ ከህብረታችሁ እንደትለዩት ቅዱስ ሲኖዶሱ በእግዚአብሔር ሰም ጥሪውን ያቀርባል።

3. የትግራይ ሕዝብ በአምባገነኖች ጥይት ከሚረግፈው የአማራና የኦሮሞ ወገኖቹ ጋር እንዲሰለፍ ጥሪ እናቀርባለን! 

የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ዘር ነው! የህወሃት አምባገነን መሪዎች ለስልጣናቸው ማራዘሚያ ሲሉ ብቻ ለትግራይ ህዝብ የቆሙ ለማስመሰል ያልሄዱበት መንገድ የለም።ክርስቲያኑ ሕዝብ ወገናችሁ ነው “አክሱም ከተማዬ ትግራይ ወንድሜ እኅቴ” ብሎ የሚያምን መሆኑን ያምታውቁት ነው፤ ለእናንተም ሁሉም አገራችሁ ነው፤ እንደ ልባችሁ የምትኖሩበት ንብረት የምታፈሩበት ክፉ ቀን የምታሳልፉበት በሥጋ በደም የተሳሰራችሁ ሕዝቦች ናቸሁ። አማራም ሆነ ኦሮሞ ጠላታችሁ አይደለም፤ ሆኖም አያውቅም፤ ጎንደርም ሆነ ጎጃም ወይም ወለጋ የጠላታችሁ ምድር አይደለም።ለትግራይ ህዝብ የሚያስብ ማንኛውም ሃይል ቢኖር ቅድሚያ የሚሰጠው ለትግራይ ህዝብ ወዳጅ ያበዛለታል እንጂ ወዳጆቹን ወደ ጠላትነት አይቀይርበትምነበር።ስለሆነም ህወሃት ለትግራይ ህዝብ ዙሪያውን በጠላት እንዲከበብ እያደረግ እንጂ በወዳጅ እንዲምበሸበሽ እያደረገ እንዳልሆነ ትላንት በትግራይ ህዝብ ስም ከኤርትራ ህዝብ ጋር ዛሬ ደግሞ ከአማራና ከኦሮሞ ህዝብ ጋር እያደረገ ያለውን ጦርነት ማስተዋል ያሻል። ዘመን ሰጠን ብለው ከአብራካችሁ የተከፈሉ ልጆቻችሁ አማራና ኦሮሞ ወንድሞቻችሁንና እህቶቻችሁን በቀያቸው በነጻነት እንዳይኖሩና እንዲሳደዱ ሲያደርጉ ዝም ብሎ ማየት አይገባችሁም፤ ተዉ ልትሉ ይገባል። በፈርኦን ዘመን እንደ ተደረገው ዛሬ በምድራችን ወንድ ልጅ እንዳይኖር እየተለቀመ ሲገደል ይኸው 25 ዓመት ሆነ። ይህ ሕዝብን አብሮ የሚያኖር አድራጎት አይደልም፤ በዚህ በደል ውስጥም መተባበር የለባችሁም። ቀን ያልፋል ዘመን ይለወጣልና ወደፊት ልጆቻችሁን የሚያስወቅስ ታሪክ ሲሠራ ዝም ብሎ ማየት የለባችሁም። ይልቁንም ቀን ከጣለው ሕዝባችሁ ጋር አብራችሁ ልትሰለፉ አብራችሁ ልትሞቱ ይገባል። የአንድነት መገለጫው ደስታውንም ዘኑንም አብሮ መካፈል ነውና።

በተለይም የትግራይ ተወላጅ ምሁራን ህወሐት የገባበትንና ለትውልድ የሚተርፍ መዘዝ በጭፍን ከመደገፍና በዝምታ ከማየት ወጥታችሁ በግልጽ ልትቃወሙና ይህን እኩይ ድርጊት ልታስቆሙ ይገባል። የትግራይን ህዝብ አስተባብራችሁ ያለምንም ማመንታት ከኢትዮጵያ ህዝብ ጎን ልትቆሙና ህወሃት በአማራና በኦሮሞ ህዝብ ላይ የሚያደርሰውን የዘር ፍጅት እንድታወግዙና ራሳችሁን ከዚህ ክፉ ሥራ እንድትለዩ በኢትዮጵያ አምላክ፤ በኃያሉ እግዚአብሔር ስም ጥሪያችን ይድረሳችሁ።


4. የጎንደር፣ የጎጃምና፣ የኦሮሞ ህዝብ በአካባቢያችሁ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆችን ከምንጊዜውም በበለጠ መንገድ ትንከባከቡና ደህንነታቸውን ትጠብቁ ዘንድ አባታዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን! 

ሁሉም ኢትዮጵያዊ መታወቂያ አርማው እንግዳ ተቀባይነቱ ነው። ይልቁንም ክርስቲያኑ ህዝባችን በዚህ ምግባሩ የሚወዳደረው እንደሌለ መላው ዓለም በሚገባ ያወቀዋል። ዛሬ ሕዝባችንን እየገደለ ያለው ቡድን መለያ ባህሪው፣ የተለያዩ እኩይ መንገዶችን በመጠቀም ህዝብን በህዝብ ላይ ወንድምን በወንድሙ ላይ እንዲነሳ በማድረግ በማጋጨት ነው። ለአለፉት 25 ዓመታት አማራውን ከኦሮሞው፥ ኦሮሞውን ከሌላው ብሔር ለማጣላት ያልሞከረው ዘዴ አልነበረም። ምንም እንኳ በመጠኑ የተሳካለት ቢመስልም በአርቆ አሳቢው የኢትዮጵያ ህዝብ ትዕግስትና ጨዋነት የተነሳ የህወሐት አላማ ሊከሽፍ ችሏል። በዚህ ሰአት የህወሃት የፍጅት ተንኮል ኢላማ የሆኑት የትግራይ ተወላጆች ናቸው። ስለዚህ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም የአማራና የኦሮሞ ህዝብ በአካባቢያቸው የሚገኙትን የትግራይ ልጆች እንዲከባከባቸውና ደህንነታቸውንም ሆነ ንብረታቸውን ከህወሃት የእጅ አዙር ጥቃት ነቅቶ እንዲጠብቅና የሰይጣንን ራ እንዲያከሽፍበት ቅዱስ ሲኖዶሱ አደራ ይላል።

5. የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነት ሆኖ የዘር ፍጅት ከታወበት ወገኑ ጎን በጽናት እንዲሰለፍ ማሳሰብ!በሃገራችን የምትገኙ ወገኖቻችን ሆይ! የሚደርስባችሁ ግፍና ጭቆና ቅዱስ ሲኖዶስን እጅጉን ያሳዝነዋል፤ ሕመማችሁ ሁሉ ይሰማናል። 

ሞታችሁ ሁሉ እጅግ ያስለቅሰናል። ይህንን ከባድ የመከራ ቀን እግዚአብሔር እንዲያሳጥረው ቅድስት ቤተክርስቲያን በጸሎት እና በምልጃ ከእናንተ ጋር ናት። እግዚአብሔር ይህን ክፉ ዘመን ያሳልፈዋልና በርቱ፤ ስለ ነጻነቱ የሚሞት ሕዝብ ሁልጊዜ አሸነፊነውና አይዟችሁ በርቱ። ነጻነቱ የተነጠቀ ሕዝብ ሆኖ ከመኖር ስለነጻነት ታግሎ በክብር መሞት እንደሚሻል የቅዱሳት መጻህፍትም ሆነ የገራችን ታሪኮች ይነግሩናል። ክርስቶስ ዓለምን ያዳነው በሞቱ ነውና! የሕዝባችንም ሞትና መከራ በእግዚአብሔር ፊት እየታ ስለሆነ በግፈኞች የፈሰሰው ደማችሁ ኢትዮጵያን ነጻ እንዲሚያወጣት ቅዱስ ሲኖዶስ ያምናል። በዚህ ክፉ ጊዜ ሕዝብ በግፍ ሲጨፈጨፍ መሐል ሰፋሪ ሆኖ መመለከት፣ ከህሊናም ሆነ ከእግዚአብሔር ፍርድ አያድንም። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት በመቆም እራሱንና ወገኑን ከጥፋት ለማዳን የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነት ጥቃት ከሚደርስበት ወገኑ ጎን በጽናት እንዲሰለፍ ሲኖዶሱ ጥሪውን ያቀርባል። 

በመጨረሻም ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና ለሚመለከታቸው ሁሉ 

በሃገራችን በኢትዮጵያ ፍትህ በመጓደሉ፣ ሕዝባችን በተፈጥሮ ከእግዚአብሔር የተሰጠው መብቱ በመገፈፉ፣ ሕዝብን የሚለያይና አገር ገዳይ ዓላማን በሕግና በመመሪያ መልክ ቀርጾ ሕዝብን መለያየትና አገርን መበታተንን እንደ ለቲካ መሣሪያ አድርጎ የሚጠቀመው በሥልጣን ላይ ያለው አካል ሕዝባችን ለእልቂት፣ ለረብ፣ ለስደት አሳልፎ የሰጠ አካል በመሆኑ፣ ለሕዝቡ ክብር፣ አንድነት፣ መብትና፣ እኩልነት የማይሠራ በመሆኑ ማንም እንደ መንግሥት ሊቀበለው አይገባም። አንድ መንግሥት መንግሥት የሚሰኘው ለሁሉም ሕዝቦች መብት እና ነጻነት በእኩልነት ሁናችሁ በመነሣት አሁን በመሳሪያ ጊዜያዊ የአደራ መንግስት እንዲቋቋምና በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሃገር ክብር እና አንድነት የሚያስብ ሕዝባዊ መንግስት በሀገሪቱ ውስጥ እንዲፈጠር ሁሉም አገሩንና ወገኑን የሚወድ   ኢትይጵያዊ ሁሉ እንዲረባረብ ቅዱስ ሲኖዶስ መንፈሳዊ የአደራ መልዕክቱን ያስተላልፋል።

´´ ልዑል እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ´´


"ከመንፈሳዊ ሰላምታ ጋር"



ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።