ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, July 29, 2014

ሰበር ዜና - የአሜሪካ ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ሰብሳቢ ዳና ሮህባራቸ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን የኢትዮጵያ መንግስት በፍጥነት እንዲፈታ የሚጠይቅ ደብዳቤ ፃፉ ''አቶ አንዳርጋቸው መለቀቅ እና ከቤተሰቡ ጋር በፍጥነት መቀላቀል አለበት'' ''He should be released and allowed to return to his family immediately'' Dana Rohrabache,chairman House committee on Foreign Affairs.(የደብዳቤውን ሙሉ ይዘት ያንብቡ)


የአሜሪካ ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ሰብሳቢ ሴናተር  ዳና ሮህባራቸ

 የአሜሪካ ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ሰብሳቢ ሴናተር  ዳና ሮህባራቸ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን የኢትዮጵያ መንግስት በፍጥነት እንዲፈታ የሚጠይቅ ደብዳቤ ሐምሌ 22/2006 ዓም (ጁላይ 28/2014) ፃፉ።የካሊፎርንያ ሪፓብሊካን ወኪል እና የአሜሪካ ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ሰብሳቢ ድረ - ገፅ ላይ እንደተገለፀው አቶ አንዳርጋቸው ላይ የሚደርስ ምንም አይነት ጉዳት በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ልዩነት እንደሚያሰፋው አስጠንቅቀዋል።በምክር ቤቱ አባል ድረ-ገፅ ላይ የወጣው ዜና እና ለአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በቀጥታ የተላከው ደብዳቤ ሙሉ ይዘት ከእዚህ በታች ይመልከቱ።


Jul 28, 2014  Press Release

WASHINGTON – Rep. Dana Rohrabacher on Monday urged Ethiopia’s prime minister to release Andargachew Tsige, a native-born opposition leader with British citizenship who last month was extradicted to the African nation from Yemen under questionable circumstances.

In a letter to Prime Minister Hailemarian Desalegn, the California Republican wrote: “Mr. Andargachew is a British citizen and a leader for political reform in Ethiopia. He should be released and allowed to return to his family immediately. Any maltreatment or harm to him, or other prodemocracy activists, in your country only serves to widen the gap between our two countries.”

Andargachew was traveling from Dubai to Eritrea on June 23 when, stopping over in Yemen, he was forcibly flown back to Ethiopia, which he fled in 2005 following protests of the nation’s elections. He was granted asylum in Britain, where his wife currently lives. British officials have expressed concerns that his extradition was not properly handled.

The activist was charged with terrorism and sentenced to death in absentia. In his letter to the Ethiopian prime minister, Rohrabacher added concerns from the United States. His letter follows:



July 28, 2014



His Excellency Hailemariam Desalegn 

Prime Minister

Federal Democratic Republic of Ethiopia

Office of the Prime Minister

P.O. Box 1031

Addis Ababa, Ethiopia



Dear Mr. Prime Minister,

          According to recent news reports, late last month the Ethiopian government arranged for the international kidnapping of opposition leader Andargachew Tsige and his forcible return to your country.

          Mr. Andargachew is a British citizen and a leader for political reform in Ethiopia. He should be released and allowed to return to his family immediately. Any maltreatment or harm to him, or other pro-democracy activists, in your country only serves to widen the gap between our two countries.

          All legitimate national governments have a responsibility to respect the human rights of their citizens. The current rulers of Ethiopia only continue to isolate themselves by violating the human rights of Ethiopian citizens, especially democratic political leaders. Mr. Andargachew should be released without delay and allowed to return home.



Sincerely,

Dana Rohrabacher

Chairman

Subcommittee on Europe, Eurasia, and Emerging Threats

House Committee on Foreign Affairs

Issues: Foreign Affairs

Source - http://rohrabacher.house.gov/media-center/press-releases/rohrabacher-ethiopia-must-release-opposition-leader-0

Monday, July 28, 2014

ኢቲቪ ለሁለተኛ ጊዜ አቶ አንዳርጋቸውን ያቀረበበት ቪድዮ ዓላማው እና ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሚሰጠው ትርጉም (የጉዳያችን ማስታወሻ)


ኢቲቪ ከአለቆቹ ተዘጋጅቶ የቀረበለትን ቪድዮ ለሁለተኛ ጊዜ አሳይቷል።ፊልሙ ከ አስራ አምስት ጊዜ በላይ ከመቆራረጡ በላይ ባጠቃላይ አንዳችም የተለየ መረጃ ስርዓቱ አለማግኘቱን በትክክል ያሳያል።የተጠቀሱት ስሞች በሙሉ ዓለም ዓቀፍ ሚድያውም የሚያውቃቸው ግለሰቦችን ነው።ከእዚሁ ጋር ተያይዞ ግን ፊልሙ ሲጀምር  ከአቶ አንዳርጋቸው ድምፅ ጀርባ በግርፋት ላይ ያለ ሰው የሲቃ ድምፅ በዕርቀት ይሰማ ነበር።ይህ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ ድርጅቶችም ሆነ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን እንደ ማስረጃ አድርገው ለዓለም አቀፉ ሕብረተሰብ ማሳየት የሚችሉበት ማስረጃ ነው።ለምሳሌ ድምፁን ለብቻው መለየት እና በዓለም አቀፍ ሚድያዎች እንዲሰማ ማድረግን ይጨምራል።አሁን ወደ ሁለቱ ነጥቦች ልመለስ የቪድዮው ዓላማ እና ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሚሰጠው ትርጉም -

1/ የቪድዮው ዓላማ

የቪድዮው ዓላማ ሁለት ናቸው -
ሀ/ የኢህአዲግ/ወያኔ ደጋፊዎችን ለማፅናናት
የመጀመርያው አላማ የኢህአዲግ/ወያኔ ደጋፊዎችን ለማፅናናት ነው።ይህ ማለት ለኢህአዲግ/ወያኔ ደጋፊዎች መረጃ እያገኘን ነው ብሎ ባላገኙት መረጃ ለማፅናናት ነው።በተለይ ለየመን መንግስት የተከፈለው በሚልዮን የሚቆጠር ዶላር ጉዳይ እራሱ በኢህአዲግ/ወያኔ ባለስልጣናት መካከልም መተማመን አልፈጠረም።ከኢህአዲግ/ወያኔ ባለስልጣናት መካከል ማን ማን ነው? የሚለው ጥያቄ ውጅንብር እርስ በርስ ፈጥሯል።ለምሳሌ የኮምፕዩተር ፓስ ዎርድ ለኢትዮጵያ ሕዝብ a b c d  ብሎ የመጥቀስ ጉዳይ በየትኛውም ዓለም ተሰምቶ የማይታወቅ ግን መረጃ ሳያገኙ ''አገኘን'' ብሎ ለማሳመን ''እናቴ ትሙት አግኝቻለሁ እመኑኝ'' ብሎ ደጋፊዎችን ለማሳመን የተሞከረ ሙከራ ነው።ይህኛው ዓላማ ሙሉ በሙሉ አልተሳካም።

ለ/ ሕዝቡን ''እባካችሁ ወደ ትጥቅ ትግል አትግቡ'' ለማለት
ሁለተኛው አላማ ሕዝቡን ለማስፈራራት ነው።አቶ አንዳርጋቸው ከተያዙ ወዲህ የኢትዮጵያ ህዝብ ለትግል መነሳሳት ከፍተኛ መሆን ለኢህአዲግ/ወያኔ ትልቅ ስጋት መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው።ይህንን ለመግታት ደግሞ የተለያየ ስነ-ልቦናዊ ጦርነት ለማድረግ የሚረዳው አቶ አንዳርጋቸው የትጥቅ ትግል 'አድካሚ' መሆኑን ሲናገሩ ማሳየት ነው።እዚህ ላይ ኢህአዲግ/ወያኔ ያልተረዳው ነገር ግን ይህ ጉዳይ ለኢትዮጵያ ሕዝብ አዲስ ነገር አለመሆኑን እና ቀድሞ የሚያውቀው መሆኑን ነው።አዎን!የትጥቅ ትግል አድካሚ ነው።አቶ አንዳርጋቸውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ''ጀግና'' ብሎ ያወደሰበት አንዱ አግባብ እራሱ እኮ ከባዱን የትጥቅ ትግል ከሰላሳ ዓመት የአውሮፓ ኑሮ በኃላም ለሀገራቸው መስዋዕት ለመክፈል መነሳታቸው ነው።ይህ ማለት ኢቲቪ አቶ አንዳርጋቸው ሲናገሩ ባያሳይም ህዝቡ ቀድሞ ያውቀዋል።እናም የፊልሙ ዓላማ እዚህም ላይ ሙሉ በሙሉ አልተሳካም።

2/ ቪድዮው ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሚሰጠው ትርጉም 

ኢህአዲግ/ወያኔ  ትልቁ ክሽፈቱ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከሃያ ሶስት ዓመት በኃላም አለማወቁ ነው።ለእዚህም ጉልህ ማሳያ የሚሆነን ኢቲቪ የህዝቡን ስነ-ልቦና አገኘሁ ብሎ የሚሰራው ፕሮፓጋንዳ እና ኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚያሳድረው ተፅኖ ግን በተቃራኒው የበለጠ የስርዓቱን ደካማነት መሆኑን ስንመለከት ነው።በእዚህ ቪድዮ ላይም ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሚሰጠው ትርጉም ኢህአዲግ/ወያኔ ካሰበው ተቃራኒ መሆኑን በሚከተሉት ሶስት ነጥቦች ማየት እንችላለን።ቪድዮው ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሚሰጠው ትርጉም -
ሀ/ ግንቦት 7 ጠንካራ ድርጅት መሆኑን
ፊልሙ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያሳየው አንዱ ነገር ግንቦት 7 አደረጃጀቱም ሆነ የሰው ኃይሉን ጥንካሬ ነው።ለእዚህም ማስረጃው አቶ አንዳርጋቸው ከጠቀሱት ውስጥ ድርጅቱ  በመረጃ ቴክኖሎጂ (አይ ቴ)ሙያ የተቀላቀሉት ግለሰቦች በ ፒ ኤች ዲ ደረጃ መሆናቸውን ነው።በመረጃ ቴክኖሎጂ ፒ ኤች ዲ ደረጃ የደረሱ ባለሙያዎች ምን ያህል ጥራት ያላቸው ባለሙያዎች መሆናቸውን በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎች የሚመሰክሩት ይህንኑ ነው።የኢትዮጵያ ህዝብም የሚረዳው ከእዚህ የተለየ አይደለም።ህዝቡ ''ለካ ኢህአዲግ/ወያኔ በመረጃው ዘርፍም ተበልጠሻል'' የሚል ሃሳብ ብልጭ ሲልበት አስተውሉ።

ለ/ በሀገር ውስጥም እራሱን አደራጅቶ ስርዓቱን መዋጋት እንደሚችል
በቪድዮው ላይ ህዝቡ እራሱን በሕቡ ማደራጀቱ ከአቶ አንዳርጋቸው አንደበት ተቆራርጦም ቢሆን መስማቱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በሀገር ውስጥ በሕቡም የመደራጀት አስፈላጊነትን አመላክቷል።ነፃነት የሚፈልግ ሕዝብ ነፃነት ስለማጣቱ ማንም ሊነግረው አይችልም።ላለፉት 40 ዓመታት ኢትዮጵያ ያለፈችበት የፖለቲካ ታሪክ የሚያሳየን ይህንን ነው።በሕቡ መደራጀት ኢህአዲግ/ወያኔም እራሱ የኖረበት ነው።ይህንን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያውቀዋል።ዛሬ ግን  ኢቲቪ ለሕዝቡ በአቶ አንዳርጋቸው አማካይነት በማሳሰቡ ጥሩ አጋጣሚ ነው።

ሐ/ ''አሸባሪ'' የሚለው የወል ስም ለኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ መሰጠቱን
ሕዝብ እኮ አስተዋይ ነው።በደንብ ይመለከታል፣ያጤናል በመጨረሻም ፍርዱን ይሰጣል።እስካሁን ኢቲቪ እና ጌቶቹ ''አሸባሪ'' ሲሉ የተሰሙት በትጥቅ ትግል የሚዋጉትን ብቻ አይደለም።ጋዜጠኞችን፣ደራስያንን፣የሃይማኖት ሰዎችን፣ብሎገሮችን፣ተማሪዎችን፣መምህራንን፣ገበሬዎችን እና የከተማ ሰላማዊ ነዋሪዎችን ሁሉ ነው።የኢትዮጵያ ሕዝብ ደግሞ ከእነኝህ ሁሉ ውጭ አይደለም።ይህ ማለት በኢህአዲግ አስተሳሰብ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ ''አሸባሪ'' ተብሎ ተፈረጀ ማለት ነው።ስለዚህ አቶ አንዳርጋቸውን እና ዓላማቸውን ሕዝብ የበለጠ እየወደደው፣እያከበረው እና እየተቀላቀለው ይመጣል።በመሆኑም የፊልሙ ዓላማ ሙሉ በሙሉ ከሽፏል።ህዝቡ ኢህአዲግ/ወያኔን ''አሸባሪ'' የሚለው እራሱ ነፃነት ያጣውን ሕዝብ በሙሉ መሆኑ የታወቀ ነው።ሕዝብ በሙሉ ''አሸባሪ'' ሲባል ደግሞ ያለው አማራጭ አንድ ነው።ነፃነቱን ከአሸባሪ መንግስት መንጭቆ መውሰድ።ይህ የማይቀር መጪው ክስተት ነው።

በመጨረሻም አንዲት ነገር ሳላነሳ አላልፍም በእዚሁ ፊልም ላይ አቶ አንዳርጋቸው ከተናገሩት ለኢህአዲግ/ወያኔ ያልገባው ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያስተዋለው ጉዳይ።አቶ አንዳርጋቸው  ዶ/ር ታደሰን ዛሬም ወያኔዎች ፊት ''ታዴ!'' ነው ያሏቸው።ይህ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያሳየው ነገር አለ።የዓላማ ፅናታቸው በጊዜ እና በቦታ አለመወሰኑን።

ጉዳያችን
ሐምሌ 21/2006 ዓም (ጁላይ 28/2014)

Friday, July 25, 2014

የኢህአዲግ/ወያኔ ባለስልጣናት አልቻሉም እንጂ በሕሊናቸው ገድለዋታል።በእግዚአብሔር ቸርነት እና ለእውነት በቆመው ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ህሊና ግን ማርያም ተርፋለች።

ማርያም ይህላ ኢብራሂም 

የ 27 ዓመት ወጣት ነች።ሁለት ልጆች አሏት።አንዱ ልጇ የተወለደው በሱዳን እስር ቤት ውስጥ ነው።በእስር ቤት የተወለደው ልጇን ከወለደች በኃላ ለመጨረሻ ጊዜ እንደምታገኘው አውቃለች።ከወሊድ በኃላ በሞት እንድትቀጣ የሱዳን ፍርድ ቤት ወስኖባታል።የሰራችው ወንጀል የለም።ወንጀል ተብሎ የተቆጠረባት ክርስቲያን መሆኗ እና እምነቷን ወደ እስልምና አለመቀየሯ ብቻ ነበር።ማርያም ይህላ ኢብራሂም ትባላለች።አባቷ ሱዳናው እናቷ  ኢትዮጵያዊት እና የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ኃይማኖት ተከታይ ነች።ይህ ብቻ አይደለም።ያገባችው ባለቤቷም ክርስቲያን ነው። 

የሱዳን ፍርድ ቤት በማርያም ላይ የፈፀመው ፍርደ ገምድል እና ፅንፈኛ ብይን መላው ዓለምን አሳዘነ።ሆኖም ግን የሱዳን ፍርድ ቤት ግን ግንቦት 15/2014 ዓም እ ኤ አ የወሰነውን የሞት ፍርድ ከመለወጥ ይልቅ የማርያም ልጅ መውለድን ብቻ እንደሚጠብቅ በቀጣዩ ቀን ግን ግድያውን እንደሚፈፅም ደጋግሞ ገለፀ።

ማርያም በደረሰባት የፍርድ ገምድል ውሳኔ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣የኖርዌይ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትርን ጨምሮ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን፣አብያተ ክርስቲያናትን፣ከፍተኛ የዓለማችን ባለስልጣናት እና የመገናኛ ብዙሃን ድምፃቸውን አሰሙ።ማርያም እናቷ የተወለደችባት፣ ከሱዳን ጎረቤት የምትገኘው እና ከአርባ ሚልዮን በላይ የሚሆን ክርስቲያን የሚኖርባት ሀገር ላይ በመሪነት የተቀመጡ የኢህአዲግ/ወያኔ ባለስልጣናት ግን ቃል አለመተነፈሳቸው አሳዛኝ ብቻ ሳይሆን አሰቃቂ ጭካኔ ነው።ጉዳዩ ዓለም አቀፍ ጉዳይ ከመሆኑ አንፃር የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አንዳችም አይነት መግለጫ አልሰጠም።
ማርያም ሮም ስትደርስ የኢጣልያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስቀበሏት 

ኢትዮጵያውያን በአረብ ሃገራት ክብራቸው ተዋርዶ እና በቀላል ዲፕሎማስያዊ ንግግሮች ሊፈቱ የሚችሉ ችግሮቻቸው እንደ ዋዛ በኢህአዲግ/ወያኔ ባለስልጣናት ሳይፈፀሙ በመቅረታቸው ሺዎች ኢትዮጵያውያን ለመከራ ተዳርገው ተመልክተናል።
ዶ/ር ቴዎድሮስን እዚህ ጋር በስም መጥቀሱም ተገቢ ነው።የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንዲት ኢትዮጵያዊት ክርስቲያን በመሆኗ ብቻ የሞት ፍርድ ሲፈረድባት እና መላው ዓለም ስለ ዕምነት መብት እና ለምስኪኗ ኢትዮጵያዊት ሲሟገት የተቃውሞ መግለጫ  ለማውጣት ካልቻለ ስራው ምን ሊሆን ነው? ዶ/ር ቴዎድሮስ መቼም  ዛሬም ''በሳውዳረብያ ላይ ተመጣጣኝ እርምጃ እንወስዳለን'' እያሉ እንደቀለዱት ቀልድ ዛሬም በማርያም ላይም ቀለዱባት ብለን እንገምት ይሆን?

ማርያም በፅናቷ፣በእግዚአብሔር ቸርነት እና በመላው ዓለም ተፅኖ ትናንት ሐምሌ 17/2006 ዓም  ከሞት ፍርዱ ድና ጣልያን ገብታለች።ቢሆንልን ማርያም ከሮም ይልቅ መጀመርያ ወደ እናቷ ሀገር  ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ነበረባት።ኢትዮጵያ ግን በኢህአዲግ/ወያኔ ስር ነች።ኢህአዲግ/ወያኔ ደግሞ  መሬት ለመሸጥ እና ሀገር ለመቸብቸብ እንጂ ለሀገር እና ለወገን  የሚፈይድ ሥራ ለመስራት  ያልታደለ መንግስት የነገሰባት ሀገር ነች።

ማርያም ሮም ስትገባ የኢህአዲግ/ወያኔ ባለስልጣናት ችላ እንዳሏት አለመሆኗን አሳይታለች።የጣልያኑ  ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፈደሪካ ሞሃረን አይሮፕላኗ ውስጥ ገብተው ተቀበሏት።ይህ ብቻ አይደለም ለክብሯ እንድታርፍ የተደረገው ሮም በሚገኘው ክላምፕኖ በተሰኘው ወታደራዊ የአየር ማረፍያ ነበር።የሮም የካቶሊክ ቤ/ክርስቲያን ርዕሰ ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ጋርም ተገናኝታለች።ሮም ጥቂት ቀናት ትቆያለች።ስለ ማርያም ዓለም ሲጮህላት አንዳች ያልተነፈሱት የኢህአዲግ/ወያኔ ባለስልጣናት ግን አልቻሉም እንጂ በሕሊናቸው ገድለዋታል።በእነርሱ አሰራር ማርያም ዛሬ ሞታለች።ብዙዎች ኢትዮጵያውያን በአረብ ሃገራት ለሚደርስባቸው ግፍ የኢህአዲግ/ወያኔ ባለስልጣናት ምንም አይነት ዲፕሎማስያዊ ሥራ ለመስራት አይፈልጉም ሲባል ቀልድ አለመሆኑን ማሳያ ነች ማርያም።ማርያም በኢህአዲግ/ወያኔ ህሊና ተገድላለች።በእግዚአብሔር ቸርነት እና ለእውነት በቆመው ዓለም አቀፉ  ማሕበረሰብ ህሊና ግን ማርያም ተርፋለች።

ጉዳያችን 
ሐምሌ 18/2006 ዓም (ጁላይ 25/2014)

Thursday, July 24, 2014

Wednesday, July 23, 2014

የመርሐ ቤቴ ሕዝብ በተነሳበት ደረጃ የአዲስ አበባ ቂርቆስ ነዋሪም ተነቃንቆ ነበር።የኢትዮጵያ ሕዝብ ግፍን በመረጠው መንገድ ለመመከት እድሉ እጁ ላይ መሆኑን ከመቼውም ጊዜ በላይ የተረዳበት ጊዜ ላይ ነን። (የጉዳያችን ልዩ ዘገባ)



ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ የመርሃቤቴ ሕዝብ አድሎ የተመላበትን እና በሙስና የታጀለ ስርዓትን የሚሸከምበት ትከሻ እንደሌለው በኃይል በታገዘ ተቃውሞ መግለፁ ዓበይት ዜና ሆኖ መክረሙ ይታወቃል።ጉዳዩ የመብራት ኃይል ማከፋፈያ ትራንስፎርመሮችን  ነቅሎ ድርጅቱ ሊያዞረው ወደ ፈለገው ማለትም በዜና ዘገባዎች መሰረት ወደ ትግራይ እንደ ''አውራምባው'' ዳዊት  አገላለፅ ደግሞ ወደ ''ሰሜን ወሎ'' (ሰሜን ወሎ ወደ ትግራይ ከዞረ ሁለት አስር ዓመታት መሆኑን እያስታወስን) ሊወሰድ መወሰኑ የመርሐቤቴን ሕዝብ 'አሁንስ በዛ!' ያስባለው ወቅታዊው ምክንያት ነበር።
ጉዳዩ የወቅቱ ምክንያት ይሁን እንጂ ለ23 ዓመታት ሲነዛ የነበረው የዘረኝነት እና የሙሰኞች አገዛዝ የአካባቢውን ሕዝብ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሚያንገበግበው ጉዳይ እንደነበር ሳይታለም የተፈታ ነው።ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ህዝቡ በየቦታው ተቃውሞውን መቀጠሉን፣'ትራንስፎርመሩን አንወስድም' የሚል ቃል ከአካባቢው የኢህአዴግ/ወያኔ ሹማምንት ተደጋግሞ ቢገለፅም ወደ ስፍራው እየጎረፈ ያለው የኢህአዲግ/ወያኔ ሰራዊት በቀጣይ ቀናት በነዋሪው ላይ ጥቃት ለመፈፀም የታሰበ ሊሆን እንደሚችል የብዙዎች ግምት በመሆኑ ህዝቡ አሁንም በንቃት ከመጠበቅ አልፎ በርካቶች ወደ አካባቢው በረሃዎች እንደወረዱ ለማወቅ ተችሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በያዝነው ወር መጀመርያ ላይ በተመሳሳይ መንገድ የአዲስ አበባ ቂርቆስ ነዋሪዎች (ከለጋሃር ባቡር ጣብያ ጀርባ) የመብራት ኃይል ሰራተኞችን አግተው ማሳደራቸው ለማወቅ ተችሏል።ጉዳዩ እንዲህ ነው።የመብራት አገልግሎት የቆመበት ሕዝብ ደጋግሞ ለመብራት ኃይል ይደውላል።ምሽት ጠብቀው መሄድ ትርፍ ክፍያ እንደሚኖረው የሚያውቁት መብራት ኃይሎች ከምሽቱ 3 ሰዓት ገደማ ይመጣሉ።የሚገርመው መብራት የቆመበትን ምሰሶ ወጥቶ ለማየት የእጅ ባትሪ አልያዙም።ህዝቡ ባትሪ ፈልጎ እንዲያመጣ አዘዙ።ባትሪው መጣ።ሰራተኞቹ በመሰላል ወጥተው መጎርጎር ጀመሩ።የአካባቢው ሕዝብ ከየቤቱ ወጥቶ ዙርያውን ተኮለኮለ። ሰራተኞቹ ከምሰሶው ላይ ወረዱ እና ችግሩ'' የ 'ፍዩዝ' መቃጠል ስለሆነ ከመስርያቤት ነገ ፈልገን እንተክላለን'' ብለው ወደ መኪናቸው ሊሄዱ ሲሉ ህዝቡ ''ፈፅሞ ሳትገጥሙ አትሄዱም ስንት ቀን ካለመብራት ኖርን?'' መንገዱን ዘጋው። ሰራተኞቹ ተማጠኑ።ይብሱን ብዙ ሕዝብ ጎዳና ወጣ።ሰራተኞቹ ወደ መስርያቤት ደውለው አድኑን ብለው ቢማፀኑም የሚሆን አልሆነም።ምሽቱ ገፋ እኩለ ሌሊት ሆነ።ህዝቡ አልተኛም አለ።የፖሊስ ኃይል ተልኮ ለመደራደር ሞከረ።ህዝቡ ''ሕይወታችን ያልፋል እንጂ ፈፅሞ መብራቱ ሳይቀጠል አናድርም'' ብቸኛ እና ቁርጥ መልሱ ነበር።ሕዝብ በተራ እየጠበቀ ሰራተኞቹ ታግተው አደሩ።ፖሊስም ሕዝቡን እንደፈራ አደረ።

በማግስቱ ሌላ የፖሊስ ኃይል ተላከ ህዝቡ ''ለፀብ ዝግጁ መሆኑን እና ህይወቱ ያልፋል እንጂ መብራቱ ሳይቀጠል ወዴትም እንደማይሄድ'' ገለፀ።ብዙ ድርድሮች ተደረጉ።በመጨረሻ ሽማግሌዎች ሃሳብ አቀረቡ።ይሄውም ከሕዝቡ ተወካዮች እና ከመብራት ኃይል ሰራተኞች ጋር ሆኖ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሊሄዱ እና እዝያ በቶሎ እንደሚጠገን የሚገልፅ የማስገደጃ ውል እንዲፈረም የሚል ሃሳብ ቀረበ።በሃሳቡ ህዝቡ ተስማማ።ይህ ሲሆን ሰዓቱ ከረፋዱ 5 ሰዓት ሆኖ ነበር።ሰራተኞቹ ከታገቱ ከ12 ሰዓታት በላይ ሆኗል።
በመጨረሻም የህዝቡ ተወካዮች፣የመብራት ኃይል የታገቱት ሰራተኞች እና ፖሊስ ወደ ፖሊስ ጣብያ ሄደው የመብራት ኃይል መስመሩን በቶሎ እንደሚጠግን የሚገልፅ ውል ፈርሞ እገታው ተጠናቀቀ።እስከቅርብ ጊዜ ድረስ ግን መስመሩ እንዳልተጠገነ መረጃዎች ያሳያሉ።ጉዳዩ ግን አንድ ነገር ያሳያል።ሕዝብ በጉልበቱ የማስፈፀም አቅሙን የማስመለስ ኃይል እንዳለው።ሕዝቡ መሮታል።የኢትዮጵያ ሕዝብ ግፍን በመረጠው መንገድ ለመመከት እድሉ እጁ ላይ መሆኑን ከመቼውም ጊዜ በላይ የተረዳበት ጊዜ ላይ ነን። 

ጉዳያችን 
ሐምሌ 16/2006 ዓም (ጁላይ 23/2014)

Tuesday, July 22, 2014

ኢህአዲግ/ወያኔ በ1983 ዓ ም ስልጣን ሲይዝ የአንድ የኮሌጅ ምሩቅ ደሞዝ ከ250 ዶላር በላይ ነበር።ዛሬ በ2006 ዓም ግን የአንድ ተመራቂ ደሞዝ 72 ዶላር ነው። እድገት ወዴት ነሽ?




የኑሮ ውድነት መድረሻው አይታወቅም 

ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የኑሮ ውድነት በብርሃን ፍጥነት እየተመነጠቀ ነው። እኛም ከሶስት እና አራት ዓመታት በፊት የነበረውን ዋጋ እየጠቀስን ለዛሬ ልጆች ''በእኛ ጊዜ እኮ በ 90 ሳንቲም ታክሲ እንጠቀም ነበር፣በእኛ ጊዜ እኮ አንድ ኪሎ ስጋ በ 22 ብር እንገዛ ነበር፣በ እኛ ጊዜ እኮ አንድ ብር ካለን በ 75 ሳንቲም እስክርቢቶ ገዝተን በ 25 ሳንቲም ጀላቲ ገዝተን ዘነጥ ብለን ጀላትያችንን እየመጠጥን ወደ ቤት እንመጣ ነበር።'' ልንል ነው።
የኑሮ ውድነቱን ከሕዝቡ ገቢ ጋር ለማነፃፀር ፈፅሞ የማይታሰብበት ደረጃ ተደርሷል።እውነት ነው ጥቂቶች በሙስና እና በሕገወጡ የሀገሪቱ አድሏዊ የምጣኔ ሀብት ድልድል ሳብያ የተቀናጣ ሕይወት እየመሩ ነው።የ አራት እና የአምስት ሚልዮን ብር የሚያወጣ መኪና በአዲስ አበባ አውራ ጎዳናዎች ላይ እየነዱ ነው።ምንም ሳይሰሩ የባንክ ሂሳባቸው እያሻቀበ ነው።
በሙስና የነቀዙት ባለስልጣናት በድሃው ሕዝብ ኑሮ እየተሳለቁ ብቻ ሳይሆን ድህነቱ ባለመስራቱ እና ባለመቆጠቡ  የመጣ መሆኑን ነጋ ጠባ በራድዮ እና በቴሌቭዥን ሲነዘንዙት መመልከት ሌላው እራስ የሚያም የሀገራችን ገፅታ ነው።
ሙሰኞቹ ገዢዎቻችን በእዚህ ብቻ አልተመለሱም።ህዝቡ አናት ላይ መሳርያ ደግነው አድገሃል እያሉትም ነው።አላደግንም፣ኑሮ ከበደኝ ማለት በራሱ ወንጀል በሆነባት ሀገር ውስጥ ሕይወት ምን እንደሚመስል በውስጡ ያለ ብቻ ይረዳዋል።
ሰሞኑን የደሞዝ ጭማሪ እንደሚደረግ ተነግሯል።ይህ የደሞዝ ጭማሪ የሚያመላክተው ሁለት መሰረታዊ ነገሮችን ነው።አንደኛው የብር የመግዛት አቅም መቀነሱን በእዚሁም ሳብያ ገበያ ላይ ያለችውን ምርትም ሆነ ከውጭ የሚገባውን ለመግዛት አለመቻሉ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ላለፉት ዓመታት የደሞዝ ጭማሪ ያላየውን ሰራተኛ የኑሮ ውድነቱን የሚመጥን ጭማሪ የተደረገ በማስመሰል መጪውን ምርጫ አስታኮ የሚደረግ ጭማሪ ነው።
ለእዚህም አብነት የሚሆነን ባለፉት 23 የኢህአዲግ/ወያኔ አገዛዝ ዓመታት ውስጥ ምን ያህል የህዝቡ ኑሮ እንዳሽቆለቆለ ስንረዳ ነው።አሁን ባለው የኑሮ ጉስቁልና አንድ ሰራተኛ እንደ ሰው ለመኖር ያውም ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ አይኖርም ብለን ብናስብ ከ1000% በላይ የሚደረግ የደሞዝ ጭማሪ በትንሹ መታሰብ አለበት።ከእዚህ ባነሰ ግን ምንም አይነት ለውጥ አያመጣም።

እድገት ወዴት ነሽ?

በ1983 ዓም  1 ዶላር = 2.07  ሲሆን የአንድ ምሩቅ ደሞዝ 500 ብር  ወደ ዶላር ሲቀየር 250 ዶላር ይሆናል።
በእዚህ ዘመን ኑሮ እርካሽ ነበር። ለምሳሌ፣ የአንድ ኪሎ ስጋ ዋጋ 5 ብር ነበር። አዲስ አበባ የሸዋ ዳቦ ቤት አንድ ዳቦ በ 10 ሳንቲም ይሸጣል። በ 1 ብር ከ 50ሳንቲም  ሽሮ ወጥ ከተሰነገ ቃርያ ጋር አዲስ አበባ ይሸጥ ነበር። አንድ ሊስትሮ ፓስታ በስጎ ከዳቦ ጋር በ 1 ብር መመገብ ይችላል።ለእዚህ ብዙዎች ምስክር ናቸው።በወቅቱ አንድ 200 ብር የሚያገኝ ጡረተኛ  በትንሹ የቤት ኪራይ ከፍሎ 5 የቤተሰብ አባላት ያስተዳድራል።ይህ ማለት ከወር ወር የጤፍ እንጀራ እየበሉ ማለት ነው።

ዛሬ አንድ ዶላር =19.75ሳንቲም ይመነዘራል።ዛሬ የአንድ ተመራቂ ደሞዝ ካልተጋነነ 1,400 ብር(መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች) ከእዚህ ላይ የመንግስት ግብር እና የጡረታ ይቀነሳል።ይህ  በዶላር 72  ይሆናል ማለት ነው። ይህ ማለት አንድ ምሩቅ የዛሬ 23 ዓመት ያገኝ የነበረው 250 ዶላር የነበረ ሲሆን አሁን እያገኘ ያለው ግን 72 ዶላር ብቻ ነው።ይህ ማለት አንድ ምሩቅ ከዩንቨርስቲ እንደወጣ ማግኘት ያለበት 4,840 ብር ነበር ማለት ነው።ይህም የኑሮ ውድነቱን የሚያግዝ ሳይሆን በልቶ ለማደር ብቻ ነው።ዛሬ የሸቀጦች ዋጋ ስንት ነው? ጤፍ ኩንታል 1,600፣ስጋ 90 ብር፣ወዘተ

በእዚህ ስሌት መሰረት የደሞዝ ጭማሪው 200% ቢሆንም የኑሮ ለውጥ አያመጣም።በተለይ በያዝነው ወር መጨረሻ ላይ የነዳጅ ጭማሪ መኖሩ ሲታሰብ ነገሩ ሁሉ ''የእንቧይ ካብ'' ያደርገዋል።
ጉዳያችን
ሐምሌ 7/2006 ዓም (ጁላይ 14/2014)

Wednesday, July 16, 2014

'''የሽንፈት ሰላም ግን ከሽብር ይከፋል።'' ማሪቱ ለገሰ ''እንድያው ዘራፈዋ!'' (ያድምጧት)

''ዘራፍ ዘራፍ በሉ ለሰላም ለፍቅር፣

ለዚች አንዲት እናት ለዚች አንዲት ሀገር።''  

ሰላም ሰላም በሉ ሰላም ፍ ይሞቃል፣

በትግል ያልተገኘ ከጦርም ይልቃል፣

የሽንፈት ሰላም ግን ከሽብር ይከፋል።'' ማሪቱ ለገሰ ''እንድያው ዘራፈዋ!'' (ያድምጧት)



ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

Monday, July 14, 2014

ሰበር ዜና - የእንግሊዝ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከእንግሊዝ ለኢትዮጵያ ዕርዳታ የሚሰጡ ድርጅቶች በሙሉ (የእንግሊዝ መንግሥትንም ጨምሮ) ለኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ቅድምያ መስጠታቸውን እና አለመስጠታቸውን በሚያጣራ መልኩ ሕጋዊ ምርመራ እንዲደረግ አዘዘ



ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት (ሁማን ራይት) ዛሬ ከጥቂት ሰዓታት በፊት ባሰራጨው ዜና  የእንግሊዝ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከእንግሊዝ ለኢትዮጵያ  ዕርዳታ የሚሰጡ ድርጅቶች በሙሉ (የእንግሊዝ መንግሥትንም ጨምሮ) ለኢትዮጵያ የሰብዓዊ  መብት ይዞታ ቅድምያ መስጠታቸውን እና አለመስጠታቸውን በሚያጣራ መልኩ ሕጋዊ ምርመራ እንዲደረግ ያሳለፈውን ውሳኔ  ''ጠቃሚ እርምጃ'' በማለት አሞካሽቶታል።
ውሳኔው በተለይ በቅርቡ ከአርበኛ አንዳርጋቸው ፅጌ መታገት በኃላ የእንግሊዝ መንግስት  ''የባህር ማዶ የልማት ትብብር ድርጅት'' (UK Department for International Development (DFID) ) ለኢትዮጵያ መንግስት የገንዘብ ድጎማ ሊያደርግ የነበረ ከመሆኑ አንፃር የዛሬው ውሳኔ ከፍተኛ መልዕክት ማስተላለፉ አይቀርም።በሌላ በኩል የዛሬው የፍርድቤቱ ውሳኔ ይሄው የልማት ድርጅት (DFID) በበቂ ሁኔታ የኢትዮጵያን የሰብዓዊ ይዞታ ጉዳይ አለመመርመሩን ጠቁሞ በእዚሁ አዲሱ የፍርድ ቤት ውሳኔ መሰረት ሕጋዊ ምርመራ እንዲደረግበት ማዘዙን ያብራራል።
የዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የእርምጃውን ፋይዳ ሲያስረዳ  የድርጅቱ የአፍሪካ ክፍል ተጠሪ የተናገሩትን በመጥቀስ ነው።እንዲህ ይነበባል -

''የእንግሊዝ ከፍተኛው ፍርድቤት ውሳኔ ለሌሎች መንግሥታት እና እርዳታ ሰጪ ድርጅቶች የማንቅያ ጥሪ ነው።ምክንያቱም ሀገራትም ሆኑ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የሚሰጡትን የልማት ፕሮግራም ሁሉ ቅድምያ ከሰብዓዊ ይዞታ አንፃር እንዲመለከቱ ያደርጋል''ይላል።

የዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት (ሁማን ራይት) ስለ እንግሊዙ ከፍተኛ ፍርድቤት የዛሬ ውሳኔ አስመልክቶ ያወጣውን ዘገባ ከእዚህ በታች ይመልከቱ።

Ethiopia: UK Aid Should Respect Rights
Ruling Permits Review of Development Agency’s Compliance
JULY 14, 2014

(London) – A UK High Court ruling allowing judicial review of the UK aid agency’s compliance with its own human rights policies in Ethiopia is an important step toward greater accountability in development assistance.

In its decision of July 14, 2014, the High Court ruled that allegations that the UK Department for International Development (DFID) did not adequately assess evidence of human rights violations in Ethiopia deserve a full judicial review.

“The UK high court ruling is just a first step, but it should be a wake-up call for the government and other donors that they need rigorous monitoring to make sure their development programs are upholding their commitments to human rights,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “UK development aid to Ethiopia can help reduce poverty, but serious rights abuses should never be ignored.”

The case involves Mr. O (not his real name), a farmer from Gambella in western Ethiopia, who alleges that DFID violated its own human rights policy by failing to properly investigate and respond to human rights violations linked to an Ethiopian government resettlement program known as “villagization.” Mr. O is now a refugee in a neighboring country.

Human Rights Watch has documented serious human rights violations in connection with the first year of the villagization program in Gambella in 2011 and in other regions of Ethiopia in recent years.

A January 2012 Human Rights Watch report based on more than 100 interviews with Gambella residents, including site visits to 16 villages, concluded that villagization had been marked by forced displacement, arbitrary detentions, mistreatment, and inadequate consultation, and that villagers had not been compensated for their losses in the relocation process.

People resettled in new villages often found the land infertile and frequently had to clear the land and build their own huts under military supervision. Services they had been promised, such as schools, clinics, and water pumps, were not in place when they arrived. In many cases villagers had to abandon their crops, and pledges of food aid in the new villages never materialized.

The UK, along with the World Bank and other donors, fund a nationwide development program in Ethiopia called the Promotion of Basic Services program (PBS). The program started after the UK and other donors cut direct budget support to Ethiopia after the country’s controversial 2005 elections.

The PBS program is intended to improve access to education, health care, and other services by providing block grants to regional governments. Donors do not directly fund the villagization program, but through PBS, donors pay a portion of the salaries of government officials who are carrying out the villagization policy.

The UK development agency’s monitoring systems and its response to these serious allegations of abuse have been inadequate and complacent, Human Rights Watch said. While the agency and other donors to the Promotion of Basic Services program have visited Gambella and conducted assessments, villagers told Human Rights Watch that government officials sometimes visited communities in Gambella in advance of donor visits to warn them not to voice complaints over villagization, or threatened them after the visits. The result has been that local people were reluctant to speak out for fear of reprisals.

The UK development agency has apparently made little or no effort to interview villagers from Gambella who have fled the abuses and are now refugees in neighboring countries, where they can speak about their experiences in a more secure environment. The Ethiopian government’s increasing repression of independent media and human rights reporting, and denials of any serious human rights violations, have had a profoundly chilling effect on freedom of speech among rural villagers.

“The UK is providing more than £300 million a year in aid to Ethiopia while the country’s human rights record is steadily deteriorating,” Lefkow said. “If DFID is serious about supporting rights-respecting development, it needs to overhaul its monitoring processes and use its influence and the UK’s to press for an end to serious rights abuses in the villagization program – and elsewhere.”

የጉዳያችን ጥንቅር
ምንጭ - http://www.hrw.org/news/2014/07/14/ethiopia-uk-aid-should-respect-rights



Thursday, July 10, 2014

ንቁ! wake up! activist Samrawit speaks out why she needs to involve in politics



 To  see additional poem of Samrawit on Ethiopians suffer in Saudi Arabia click on My Heart Cries To You Mamaye 
or

ሳምራዊት ተሰማ በሳውዲ አረብያ ለተገደሉት ኢትዮጵያውያን በእንግሊዝኛ ያቀረበችው ግጥም(ቪድዮ) 


ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

መንግስታዊ ሽብርተኝነትን የሚሸከም ትከሻ አይኖረንም!!! We cannot Tolerate TPLF/EPRDF’s State Terror! ''ከዚህ በኋላ ለምናደርጋቸው ሀገር አቀፍ ንቅናቄዎች መላው የሀገሪቱ ህብረተሰብ በንቃት ተዘጋጅቶ እንዲጠብቅ ጥሪውን እያስተላለፈ ለዚህም ቁርጠኛ አመራር ለመስጠት ዝግጁነቱን ለመግለፅ ይወዳል'' ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ (English version is also attached)

We cannot Tolerate TPLF/EPRDF’s State Terror! (click  here to read English version)


Press Release by Blue Party Ethiopia / Semayawi Party- Ethiopia/
ሀምሌ 3/2006ዓ/ም
የህወሓት/ኢህአዲግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ዜጎችን በማፈንና በማሰቃየት ብሎም በመግደል የአፈና አገዛዙን ለረጅም ጊዜ ሲያራምድ መቆየቱ ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ በተለይም ባለፉት 10 ዓመታት የህዝብን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማፈን እስራትና ግድያውን ህጋዊ ለማስመሰል የተለያዩ አፋኝ አዋጆችን አውጥቷል፡፡ እነዚህን አዋጆችንም ተገን አድርጎ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና አባለትን፣ ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን፣ እንዲሁም የእምነት ተቋማት መሪዎችን እና በአገዛዙ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ዜጎችን ማሰሩን፣ ማሰቃየቱንና ግድያውን ተያይዞታል፡፡ በህገ መንግስቱ የተካተቱ የሰብዓዊ መብቶችንና ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን በሙሉ የሚጥሰውና የአምባገነንነት ስልጣኑን ለማራዘም ሲል ያፀደቀው የፀረ-ሽብር አዋጅ ከፀደቀበት እለት አንስቶ ኢህአዴግ ለስልጣኔ ያሰጉኛል የሚላቸውን ፍፁም ሰላማዊ ታጋዮችንና ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው በድፍረት የፃፉ ጋዜጠኞችን ብሎም የእምነት ነፃነታችን ይከበር ብለው የጠየቁ የሀይማኖት መሪዎችን በጠራራ ፀሃይ ያለምንም ወንጀል በዚሁ ህገ ወጥ አዋጅ ‹‹የፀረ ሽብር ግብረ ሀይል›› በሚባል ማንነቱ በማይታወቅ የጨለማ ቡድን ወደ እስር ቤት እያጋዘ ይገኛል፡፡
ይህን የሚያጋልጡ ሚዲያዎችንም ለማፈን እስር ቤቶችን ጨምሮ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር እያፈሰሰ የአየር ሞገድ ያውካል፤ በዚህ ሳያበቃ በሀገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን የሚያሰሙ ፖለቲከኞችን ለማሸማቀቅ እንደ ኢሳት ያሉ ሚዲያዎችን የአሸባሪ ልሳን ብሎ በመፈረጅ ሚዲያውን የሚጠቀሙትን ደግሞ ከአሸባሪዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው አድርጎ መወንጀሉን ቀጥሎበታል፡፡ እንደሰማያዊ እምነት ማንም አካል መልእክት የሚያስተላለፍበትን የሚዲያ ተቋም ሊመርጥለት እንደማይችል መንግስት እንዲገነዘበው ከዚህ በፊት በግልፅ ያሳወቀ ሲሆን አሁንም ፓርቲው በዚሁ የፀና አቋሙ እንደሚቀጥል በድጋሚ ይገልፃል፡፡
ባጠቃለይ የዚህን ገዢ አካል የእውር ድንብር ሀገር የማስተዳደር ጉዞ ለመታገል በርካቶች በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ቢሆንም በህወሓት/ኢህአዲግ ግፍና መከራ ተገፍተው ስርዓቱን በሃይል እናስወግዳለን ብለው ሀገር ጥለው የተሰደዱ ዜጎችም እንዳሉ ይታወቃል፡፡ የህወሓት/ኢህአዲግ ማናለብኝነትና የስልጣን ጥመኝነትም በግለሰቦች ላይ ከሚያስከትለው ማህበራዊ ቀውስ በላይ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ አለመረጋጋትን አስከትሏል፡፡ በአሁኑ ሰዓትም ይህ ገዢ ፓርቲ የፈጠረው ስርዓት የሀገሪቷን ሰላማዊ የፖለቲካ ምህዳር በማጥበብ ሀገራችንን ወደ አልተፈለገ አለመረጋጋትና ቀውስ እየመራት ይገኛል፡፡ፓርቲያችንም እነዚህን ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎችም በቅርቡ እየተፈፀሙ የሚገኙ ህገ ወጥ ድርጊቶች ስላሳሰበው ይህን መግለጫ ለማውጣት ተገዷል:-
1. ሰኔ 16 2006 ዓ.ም የየመን መንግስት የዓለም አቀፍ ስምምነቶችንና ድንጋጌዎችን በመጣስና በሰው ሀገር የውስጥ ጉዳይ በመግባት የአማፂ ቡድን ግንቦት ሰባት ዋና ፀሃፊ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን መያዟ ይታወሳል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ ለህወሓት/ ኢህአዴግ ተላልፈው መሰጠታቸውን ከ16 ቀናት በኋላ መታወቁና ይህንንም ሁለቱ ሀይሎች ማመናቸው ተሰምቷል፡፡ ነፃነት በሌለበት ሀገር ዜጎች ሰብዓዊ ክብራቸውን ለማስጠበቅ የሚያደርጉት ጥረት የሌሎች ሀገር መንግስታት የሚያደርጉትን ጣልቃ ገብነት በዓለም አቀፍ ስምምነቶችም ሆነ በተለይ በሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ጥላ የሚያጠላ መሆኑን ግንዛቤ አለመወሰዱ እጅግ የሚያሳዝን ድርጊት ነው፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ከተያዙ በኋላ ላለፉት 16 ቀናት በምን አይነት ሁናቴ እንደቆዩ ህዝብና ቤተሰቦቻቸው እንዲያውቁት አለመደረጉ፤ ስለ አያያዛቸው ሁኔታም በማህበረሰቡና በፓርቲያችን ውስጥ ከፍተኛ ጥርጣሬ እንዲኖር አድርጓል፡፡ሰማያዊ ፓርቲ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሰብዓዊ አያያዝ እያሳሰበው ህወሓት መራሹ የኢህአዴግ አገዛዝ አያያዛቸውን ግልፅ እንዲያደርግ ሰብዓዊ ክብራቸውም እንዲጠበቅ በጥብቅ ያሳስባል፡፡
2. በዚሁ ሳምንት ገዢው ፓርቲ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ የአምባገነኑን መንግስት ህወሓት/ኢህአዲግን ሲታገሉ የነበሩ ፖለቲከኞችን በስመ አሸባሪ ከያሉበት እየለቀመ ህገ-ወጥ እስራት መፈፀሙ ይታወቃል፡፡ ህወሓት/ኢህአዲግ ይህ ግብታዊ ተግባሩ ምንም እንኳን አዲስ ባይሆንም በአሁኑ ወቅት ለውጥን ለማምጣት በቆራጥነት እየታገሉ ያሉ ሰላማዊ ታጋዮችን ማሰሩ በሀገር ውስጥ በህጋዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ፓርቲዎችን ከአማፂ ቡድኖች ጋር ግንኙነት ያላቸው በማስመሰል ሰላማዊ ትግሉን ለማዳከምና መጪውን 2007 ዓ/ም ምርጫ ያለ ተቀናቃኝ ለማለፍ የሚደረግ ህገ ወጥ እንቅስቃሴ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡ የፓርቲያችን ብ/ም/ቤት ምክትል ሰብሳቢ የሆነው አቶ የሺዋስ አሰፋ በሰላማዊ ትግሉ በቁርጠኝነት እየተሳተፈ ባለበት ሁኔታ ለእስር መዳረጉ፤ የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው፤ የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሀላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ከፍተኛ የህዝብ ንቅናቄን በመፍጠር ላይ ያለው የአረና /ትግራይ/ ፓርቲ አመራር አባል የሆኑትን አቶ አብረሃ ደስታ ለእስር መዳረጋቸው ህወኃት/ኢህአዴግ የመጨረሻው መጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ያረጋግጣል፡፡ በመሆኑም አገዛዙ እያካሄደ ያለውን መንግስታዊ ሽብር አቁሞ ለሀገርም ሆነ ለራሱ የሚበጀውን መንገድ እንዲከተል እያሳሰብን የታሰሩት የፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እንጠይቃለን፡፡
በመጨረሻም ፓርቲያችንን መንግስት እያደረገ ያለው ሽብርን የመንዛትና ህግን የመጣስ ተግባሩ መቼም ቢሆን ከሰላማዊ ትግሉ እንደማያቆመውና ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በአፅንኦት እየገለፀ እነዚህንና ከላይ የተጠቀሱትን የገዢውን ፓርቲ መርህ አልባነት፣ ህገ-ወጥነት እና የለየለት አምባገነንነትን አሁን ካለው ነባራዊ እውነታ ጋር አጣምሮ የትግል ስልቱን ደረጃ ከፍ ወዳለ ምዕራፍ ማሸጋገር እንዳለበት አምኗል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በኋላ ለምናደርጋቸው ሀገር አቀፍ ንቅናቄዎች መላው የሀገሪቱ ህብረተሰብ በንቃት ተዘጋጅቶ እንዲጠብቅ ጥሪውን እያስተላለፈ ለዚህም ቁርጠኛ አመራር ለመስጠት ዝግጁነቱን ለመግለፅ ይወዳል፡፡በዚህ አምባገነንነትን ለመታገል በሚደረገው ንቅናቄም በሀገር ውስጥ የሚገኙ ህጋዊና ሰላማዊ ፓርቲዎች፤አለም አቀፍ ተቋማት፤የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፤ሲቪክ ማህበራት፤መላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከሰላማዊ ትግሉ ጎን በጋራ እንድንቆም እንጠይቃለን፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር
ሰማያዊ ፓርቲ
ሀምሌ 3/2006ዓ/ም

Wednesday, July 9, 2014

እጅግ የመረረ ፀረ-ወያኔ ተቃውሞ። የህዝብ ስሜት ኢህአዲግ/ወያኔ ከጠበቀው በላይ ግሏል።Anti TPLF demonistration (ይህንን ፊልም ይመልከቱ)





ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

''የእንግሊዝ መንግስት ባለቤቴ ባፋጣኝ እንዲፈታ መጠየቅ አለበት'' የአቶ አንዳርጋቸው ባለቤት ለቢቢሲ የተናገረቸው። ''UK should demand the immediate release of my husband'' Ms Yemi told to BBC

Opposition leader Andargachew Tsege has appeared on Ethiopian state television, following his disappearance from Yemen last month.
BBC 9 July 2014 Last updated at 09:31 GMT



His UK-based wife Yemi Hailemariam told the BBC she was shocked to see him on television.
Yemen arrested Andargachew while he was in transit at Sanaa airport, and secretly handed him to Ethiopia.
In 2009, Andergachew was sentenced to death in absentia for planning to assassinate government officials.
Andergachew, a UK national, denied the charge.

He is secretary-general of Ethiopia's banned Ginbot 7 movement.
Ms Yemi said it was difficult to see footage of her husband.
"I switched it off quickly. I couldn't watch it," she said.
Ms Yemi said the UK should demand the immediate release of her husband.
"If they want to try him, they must go through the proper channels," she told the BBC.
Ginbot 7 says Andargachew had been on his way from the United Arab Emirates to Eritrea when he was detained at Sanaa airport.
Ginbot 7 (15 May) was named after the date of the 2005 elections, which were marred by protests over alleged fraud that led to the deaths of about 200 people.
Source- BBC 

Tuesday, July 8, 2014

የኢቲቪ የዛሬው የአቶ አንዳርጋቸውን ንግግር ያሳየበት ፊልም ከኢህአዲግ/ወያኔ ስሌት በራቀ መልኩ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሁለት ጉዳዮችን አረጋግጦለታል


ዛሬ ሐምሌ 1/2006 ዓም ኢቲቪ አቶ አንዳርጋቸው የግንቦት 7 ንቅናቄ ፀሐፊን በድብቅ ካሜራ ያነሳውን ፊልም አሳይቷል።አቶ አንዳርጋቸው በተጎሳቆለ ሰውነት ሆነው የተናገሩት ዶ/ር ብርሃኑ ባለፈው ሳምንት ከተናገሩት ጋር ተመሳሳይ ነው።አቶ አንዳርጋቸውን ወያኔ  በየመን ካስያዘ በኃላ ወደ ሀገር ቤት አምጥቶ ከፍተኛ ድብደባ እና ስቃይ እንዳደረሰባቸው ኢሳት ትናንት ከታማኝ ምንጮች ማግኘቱን ጠቁሟል።በዛሬው የኢቲቪ ፊልምም ይህንን መመልከት ይቻላል።
የኢቲቪ ፊልም ለኢትዮጵያ ሕዝብ መልዕክት አስተላልፏል።በባህር ማዶ ከ 30 ዓመት በላይ መኖር ሀገር አያስከዳም፣መማር ለሀገር በረሃ ለበረሃ መንከራተትን አይከለክልም።አቶ አንዳርጋቸው በሳር በተሰራ ጎጆ ፊት ሆነው፣አንዲት ምስኪን ኢትዮጵያዊት ሲያፅናኑ የሚያሳይ ፎቶም አሳይቷል።በወያኔ አስተሳሰብ አቶ አንዳርጋቸውን ያዋረደ እና ዝቅ አድርጎ ያቀረበ መስሎት ነው። ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግን መልክቱ ታላቅ ነው።በረሃ ስለመብትህ የሚታገሉ አሉ።እውነት ነው።የሚል መልዕክት አለው። 
በሌላ በኩል ኢቲቪ ያረጋገጠልን ነገር ዶ/ር ብርሃኑ ስለ አቶ አንዳርጋቸው ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ የተናገሩትን ነው።ዶ/ር ብርሃኑ ያሉትን እና ዛሬ በኢቲቪ አቶ አንዳርጋቸው የተናገሩትን ተመልከቱ።ተመሳሳይ ነው።የኢትዮጵያ ሕዝብም ስለ አቶ አንዳርጋቸው የሞራል ብቃት የተነገረው ትክክል መሆኑን ነው።ይህም ፅናት፣እውነተኝነት እና ከሆድ ይልቅ ሕሊናን የማዳመጥ ፋይዳን አሳይቷል።በተለይ ወጣቱን ወደ ውጭ ለስደት መሮጥ ሳይሆን ለሀገር ነፃነት ታግሎ በሀገር ላይ በኩራት መኖርን ሁሉ አመላክቷል።  

ዶ/ር ብርሃኑ ስለ አቶ አንዳርጋቸው ባለፈው ሳምንት ያሉት  እንዲህ ነበር

 'እንደ አንዳርጋቸው ከራሱ ጋር የታረቀ ሰው አላየሁም''
''በእውነት በጣም እድለኛነት ነው እንዲህ ከውስጥ ከራስ ጋር መታረቅ''
'' አንዳርጋቸው ሊገሉት ቢፈልጉ እየሳቀ ነው የሚሞተው የእነርሱን ከብትነት እያመነ ነው የሚሞተው''
''አንዳርጋቸው መስራት ያለበትን ጨርሶ ወጣቶችን ለመሪነት አብቅቶ አታስፈልገንም ሂድ ተብሎ እንግሊዝ ሀገር መኖር ጀምሯል''


አቶ አንዳርጋቸው ዛሬ በኢቲቪ ዜና እወጃ ላይ በድብቅ ካሜራ የተነሱት ፊልም ላይ ሲናገሩ የታየው -

''እኔ አሁን ከራሴ ጋር ታርቄ ሰላም አግኝቻለሁ''
''እውነቴን ነው የምልህ ተረጋግቼ ያለሁበት ሁኔታ ነው''
''ምንም አይነት ብስጭት የለኝም''
''ምንም አይነት መጥፎ ስሜት አይሰማኝም።የመጨረሻ እርጋታና እረፍት ውስጥ ነው ያለሁት''

ከአቶ አንዳርጋቸው ንግግር የምንረዳው ዶ/ር ብርሃኑ እንዳሉት ስራቸውን  በሚገባ ጨርሰዋል።ለሚያምኑበት በመስራታቸውም  ዛሬም በስቃይ መሃል ሆነው ህሊናቸው ተረጋግቷል።

የዶ/ር ብርሃኑን ንግግር ለመስማት ይህንን  ይጫኑ።

ጉዳያችን 
ሐምሌ 1/2006 ዓም (ጁላይ 9/2014)






Sunday, July 6, 2014

ሰበር ዜና - ግንቦት 7 ንቅናቄ ''ልዩ መግለጫና ተግባሪዊ የመጀመሪያ እርከን የትግል ጥሪ'' በሚል ርዕስ ስር አዲስ የትግል ጥሪ አስተላለፈ።ጥሪው የመን፣እንግሊዝ እና ኢህአዴግ/ወያኔ ላይ ያነጣጠረ ነው


የመንን በተመለከተ

የየመን መንግሥት የዓለም ዓቀፍ ህግም ሆነ የየመን የራሷን ህግ በመተላለፍ መሪያችንን ለእርድ አሳልፎ ሰጥቶብናል። ከመጀመሪያው ጀምሮ ለየመን መንግሥት የተደረገው ተማጽኖ ሰሚ ጆሮ አላገኘም። እስካሁንም ድረስ የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸውን ማሠሩና ለወያኔ አሳልፎ መስጠቱ በይፋ አላመነም። እኛ ባለን መረጃ መሠረት በአይሮፕላን ማረፊያው ከማገት ጀምሮ በልዩ በረራ ወደ ኢትዮጵያ እስከ መላክ ድረስ ያለውን የውንብድና ሥራ በየመን በኩል ሆኖ የሠራው ቀጥታ ተጠሪነቱ ለየመን ፕሬዚዳንት የሆነው የስለላ ድርጅት ነው። በዚህም ሳቢያ የየመን መንግሥት ሊቀለበስ የማይችል እና በቀላሉ የማይፋቅ ታሪካዊ ስህተት ፈጽሟል። የየመን መንግሥትና ሕዝብ ይህን እንዲያውቁት ማድረግ ወቅቱ የሚጠይቀው የተግባር እንቅስቃሴ አካል ነው።
የመንን በተመለከተ የሚቀጥለው ሳምንት ዘመቻችን ግብ ቁጣችንን የየመን ፕሬዚዳንት እና የየመን መንግሥት ብቻ ሳይሆን የየመን ሕዝብም እንዲያውቅ ማድረግ ነው። የሚከተሉት ተግባራት ለአብነት ያህል ተጠቅሰዋል።
  1. ለየመን ፕሬዚዳንት አዲስ መረር ያለ ደብዳቤ ተጽፎ በፋክስና በኢሜል በየመን መንግሥታዊ መሥሪያ ቤቶችና ኤምባሲዎች አድራሻዎች መላክ። በመልዕክት መጨናነቅ ከሚገባቸው የየመን ተቋማት አንዱ አዲስ አበባ የሚገኘው የየመን ኤምባሲ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ሆናችሁ በዘመቻው የምትሳተፉ ጥንቃቄ እንዳይለያችሁ እናሳስባለን፤ የኢንተርኔትና የፋክስ መልክቶችን ስትልኩ ራስን ለጉዳት በማያጋልጥ መንገድ መደረግ ይኖርበታል።
  2. የየመን ኤምባሲዎችን ሥራ ማወክ በሚችሉ ሰልፎችና ተቃውሞዎች ማጨናነቅ። የፕሬዚዳንቱን ፎቶና የአገሪቱን ባንዲራ ማቃጠል። ይህ በውጭ አገራት ብቻ መደረግ ያለበት ነው።
  3. በውጭ አገራት በየከተሞች ለሚገኙ የየመን ኮሚኒቲዎች ደብዳቤ መፃፍና መንግሥታቸውን እንዲቃወሙ መገፋፋት፤ ይህንን ካላደረጉ ግን ከመንግሥታቸው ጎን ተሰልፈው በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት እንዳወጁ የምንቆጥረው መሆኑን በማያሻማ መንገድ መንገር፤
  4. በየመን አየር መንገድና በማናቸው የየመን የንግድ ድርጅቶችና ቢዝነሶች ላይ እቀባ ማድረግ፤ በቢዝነሶቻቸው ላይ አሉታዊ ቅስቀሳ ማድረግ። ይህ ተግባር በኢትዮጵያም ከኢትዮጵያ ውጭም በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን መተግበር የሚኖርበት አቢይ ተግባር ነው።
  5. በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የየመን ቢዝነሶችን መርጦ ምርቶቻቸው እና አገልግሎቶቻቸው እንዲጠሉ ማድረግ። ከእንግዲህ በየመን ገንዘብ የተሠራ ወይም ከየመን የመጣ ብስኩትም ይሁን ሲጃራ የወገናች ደም የነካው እቃ ነው።

 ብርታኒያን በተመለከተ

የእንግሊዝ መንግሥት ማድረግ የነበረበትን እና ማድረግ ይችል የነበረውን ሁሉ አድርጓል ብለን አናምንም። እርምጃው ፈጣን አልነበረም፤ አሁንም አይደለም።
ስለሆነም እንግሊዝን በተመለከተ የዘመቻችን ግብ የእንግሊዝ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት በመንፈጉ መክሰስ እና ከአሁን በኋላም ተገቢውን ትኩረት ሰጥቶ እንዲከታተለውና መሪያችን እንዲያስፈታ መወትወት ነው። የሚከተሉት ተግባራት ለአብነት ተዘርዝረዋል።
  1.  የእንግሊዝ መንግሥትን በህግ መክሰስ (ይህ በንቅናቄው ጽ/ቤት የሚሠራ ሲሆን ዝርዝሩ ወደፊት ይገለፃል)፤
  2. ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲስ ደብዳቤ ጽፎ በፋክስና በኢሜል ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ለኤምባሲዎች በብዛት መላክ። አንዱ ትኩረት የሚደረግበት ኤምባሲ አዲስ አበባ የሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ በዘመቻው የሚሳተፉ ወገኖች አስፈላጊው ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል።
  3. በለንደን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደጃፍ፤ በሌሎች አገሮች ደግሞ በእንግሊዝ ኤምባሲዎች ቁጣ የተቀላቀለበት የተቃውሞ ሰልፎችን ማካሄድ።

 ወያኔን በተመለከተ

ወያኔን በተመለከተ የሚደረጉ ትግሎች በሙሉ ወያኔን ከስልጣን ማስወገድን ያነጣጠሩ መሆን ይኖርባቸዋል። ወያኔም ለመጣል ትልቁን ድርሻ የሚያበረክተው ሕይወታቸውን ለመስጠት የቆረጡ፡ ከቁም ውርደትና ባርነት ለነጻነትና ለፍትህ ከወያኔ ጋር ጉረሮ ለጉረሮ እየተናነቁ እየጣሉ ለመውደቅ ፤ መስዋእት ለመሆን በወሰኑ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችንና የህዝብ ሃይሎች የሚያደርጉት ተግባራዊ እንቅስቅሴ ነው ፤ እንቀላቀላቸው።
በተለያዩ ምክንያቶች ወሳኙን ትግል መቀላቀል የማይችሉ ወገኖቻችን በያሉበት ሆነው ከወያኔ የስለላ መረብ ተጠነቅቀው ራሳቸውን በቡድን ያደራጁ፤ ይህንኑ የሚያግዙ ተግባራት ለመፈጸም ራሳቸውን ያዘጋጁ። እነዚህ ተግባራት ወያኔን በገቡበት እየገቡ በማሳፈር ፤እረፍት በመንሳት፤ የፈፀሟቸውን ወንጀሎች በአደባባይ በመናገር እንዲሸማቀቁ በማድረግ፤ ማንነታቸው ለሸሪኮቻቸው ወይም ለሥራ ባልደረቦቻቸው በመንገር ወዳጅ በማሳጣት፣ ንግዶቻቸውን ኩባንያዎቻቸው እንዲከስሩ በማድረግ የፋናንስ አቅማቸው በማዳከም ረገድ የሚኖራቸው አስተዋጽኦ ቀላል እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል። ከዚህ አኳያ ሊደረጉ ከሚገቡ ተግባራት የሚከተሉት በምሳሌነት ተዘርዝረዋል።
  1. በምዕራቡ ዓለም በተለያዩ ሽፋኖች ተሰግስገው ያሉት እና የሚመላለሱ ወንጀለኞች የወያኔ ሹማምንትና ደጋፊዎችን ለፍርድ ለማቅረብ መደራጀትና እንደየሀገሩ ሁኔታ አግባብ ያላቸውን የህግ መሳሪያዎች መጠቀም፤
  2. በመላው ዓለም የወያኔ ኤምባሲዎችና የኮንሱላር ጽ/ቤቶች ሥራ መሥራት የማይችሉበት ሁኔታ መፍጠር፤
  3. በመላው ዓለም የወያኔ አባላትና ደጋፊዎችን ከያሉበት (ከሰፈር፣ በዩኒቨርስቲዎች፣ በንግድ የተሰማሩ ..) በማደን ማስነወር፣ ማግለል፣ ማዋረድ፤ ከእነሱ ጋር አንዳችም የንግድም ፡ የሥራ ፤ የማኅበራዊ ትብብርና ግንኙነት አለማድረግ፤ ፊት መንሳት ፤ በሥራዎቻቸው ላይ አሉታዊ ቅስቀሳዎችን ማካሄድ። የወያኔ አባላትንና ደጋፊዎችን በሁሉም ዓይነት ግንኙት ማግለል፡ አለመተባበር በኢትዮጵያም ውስጥ በስፋት በሥራ ላይ መዋል ይኖርበታል።
  4. በማናቸውም የዓለም ክፍል ለሥራ ወይም ለሽርሽር የሚዘዋወሩ ከፍተኛ የወያኔ ሲቪል፣ የወታደራዊና የደህነት ባለሥልጣኖችና የጦር መኮንኖችን እየተከታተሉ ማሸማቀቅ፣ ማስነወር፣ መውጫ መግቢያ ማሳጣት፤ በየትኛውም የዓለም ክፍል ተቀባይነት እንደሌላቸው በሕዝብ ላይ ለፈጸሙት ወንጀሎች ሁሉ የሕዝብ ቁጣ ዒላማ እንዲሆኑ እንደልባቸው መፏላል እንዳይችሉ ማድረግ። በኢትዮጵያ ውስጥ ሕዝብ ራሱ በቡድን አደራጅቶ ለወያኔ ታጣቂዎች ጥቃት ሳያጋልጡ አድብቶና አስልቶ ተመሳሳይ ድርጊቶች መፈፀም
  5. የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በወያኔ አገዛዝ የሚመሩ እንዲሁም በወያኔ ኤፈርት ስር ያሉ ኩባንያዎች፤ቢዝነሶች ላይ እቅባ ማድረግ፤ የሸቀጥና የአገልግሎታቸው ተጠቃሚ አለመሆን፤ በእነሱ ላይ አሉታዊ ቅስቀሳ ማድረግ፤ በልዩ ልዩ መንገዶች ሥራቸውን ማጨናገፍ ማደናቀፍ፤ አሻጥሮችን በተደራጀ መልክ፣ በጥናትና በብልሃት ተግባራዊ ማድረግ። ይህ በኢትዮጵያም በመላው ዓለም በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ተግባሪዊ መደረግ ይኖርበታል።
  6. በዌስተር ዩኒየን፣ በመኒ ግራም እንዲሁም በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፤ በመካከለኛው ምሥራቅ በወያኔ ደጋፊዎች በመሠርቱዋቸው ልዩ ልዩ የገንዘብ ላኪ ድርጅቶች በኩል ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ አለመላክ፤ በየአካባቢው አማራጭ የገንዘብ መላኪያ መንገዶችን መፈለግ፤ እነዚህ በሌሉባቸው አካባቢዎች የፈጠራ ችሎታን በመጠቀም ገንዘብ ለዘመድ አዝማድ በወያኔ በኩል ሳይላክ የሚደርስበትን ሁኔታ መፍጠር፤ የወያኔን የፋሽታዊ አገዛዝ አንዱና ዋነኛ ምሰሶ የሆነውን የውጭ ምንዛሪ የማድረቂያ ዘዴዎችን ሁሉ በመፈለግ ተግባሪዊ በማድርግ የወያኔን በዘረኝነትና በዘረፋ የተገነባ የገንዘብና የኢኮኖሚ አቅም ማዳከም፤ መቦርቦር፤ መናድ።
  7. ከወያኔ ጋር የሚሠሩ የውጭ አገር ድርጅቶች ከወያኔ ጋር ያ ያላቸውን ሽርክና እንዲያቋርጡ መወትወት፤ አልሰማ ካሉ በቢዝነሳቸው ላይ አሉታዊ ቅስቀሳ ማካሄድ። (የእነዚህን ዝርዝሮች በተከታታይ ይገልጻሉ)
  8. የምዕራብ አገራት ዩኒቨርስቲዎች ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግኑኝነት እንዲመረምሩ ማሳሰብ። በተለይ ደግሞ ሳያስተምሩ ለወያኔ ሹማምንቶች ዲግሪ የሚያድሉ ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆችን ማስጠንቀቅ፤ ተግባሮቻቸውን ለተማሪዎቻቸው ጭምር መንገር (ለምሳሌ University of Greenwich ከ International Leadership Institute ጋር ያለውን ግኑኝነት እንዲሰርዝ፣ እስከዛሬ የሰጣቸውንም የማስትሬት ዲግሪዎች እንዲመረመር የሚጠይቅ ደብዳቤ ጽፎ በብዛት በፋክስ መላክ፤ ተመሳሳይ ደብዳቤ Open University እና ከወያኔ ጋር ተሻርከው ለሚሠሩ ዩኒቨርስቲና ኮሌጆች መላክ)
  9. ይህ ዘመቻ ለጊዜው በወያኔ ላይ ያነጣጠረ ቢሆንም፣ የሕዝቡን የነፃነትና የፍትህ ጥረት የሚያደናቅፉ የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ አገር ዜጎች በሆኑ ቱጆሮችና ከወያኔ ጋር የተያያዙ የንግድ ቤቶችና ኩባንያዎች የዘመቻው ዒላማ ሊሆኑ ይችላሉ። (ዝርዝራቸውን በተከታታይ እናወጣለን)
በመጨረሻም የወጣቱ የማያልቅ የፈጠራ ችሎታ ከላይ በዝርዝሩ ውስጥ ያልተካተቱ ሆኖም ግን ውጤታማ የሆኑ የተቃውሞ መግለጫ ዘዴዎች ያፈልቃል ብለን እናምናለን። ስለሆነም ዘመቻውን በየአካባቢው በሚገኝ ሀሳብና ፈጠራ ማዳበር ይቻላል። ይህ ዘመቻ ወያኔ ከስልጣን እስኪባረር ድረስ በየጊዜ እየከረረ መሄድ እንዳለበት ታሳቢ አድርጎ መነሳት ይኖርበታል። ስለሆነም በየጊዜው አዳዲስ ነጥቦችን ተግባሪዊ የትግል ስልቶችን እንጨምራለን።
ለመላው የአትዮጵያ ሕዝብ፣ በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ሁሉ፣ ለሁሉም የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ሁሉ በኅብረት በጋራ ሆነን፤ ትከሻ ገጥመን ለተግባሪዊ ትግል በቁርጠኝነት እንድንነሳ ጥሪያችንን እናቀርባለን ።
ይህ ዘመቻ ወያኔን ከስልጣን ለማባረር ምድር ላይ ከምናደርገው የመረረ ትግል ጋር ሲቀናጅ የሚፈለገውን ውጤት ስለሚያስገኝ ለነፃነቱ ግድ ያለው ዜጋ ሁሉ በሙሉ ኃይሉና አቅሙ ተሳትፎ እንዲያደርግ ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አገራዊ ጥሪ ያቀርባል።
በመስዋዕትነት ድልን እንቀዳጃለን !!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

Friday, July 4, 2014

''ዘ ጋርድያን'' the guardian የእንግሊዝ ጋዜጣ ስለ አቶ አንዳርጋቸው መታገት እና የእንግሊዝ መንግስት ጉዳይ ዛሬ የፃፈው።በጋዜጣው አይጠቀስ እንጂ ሌሎች ዘገባዎች ጉዳዩ ቀጠናውን አዲስ ፍጥጫ ውስጥ እንደሚከት እየተናገሩ ነው።


source - http://www.theguardian.com/world/2014/jul/04/uk-accused-extradition-ethiopia-andargachew-tsige
The Foreign Office has been accused of failing to act to prevent theextradition to Ethiopia of an opposition leader facing the death penalty.
Andargachew Tsige, a British national, is secretary general of an exiled Ethiopian opposition movement, Ginbot 7. He was arrested at Sana'a airport on 23 June by the Yemeni security services while in transit between the United Arab Emirates and Eritrea.
"The British knew he was being held in Yemen for almost a week but they did nothing," said Ephrem Madebo, a spokesman for Ginbot 7. "We are extremely worried about Mr Andargachew, because the Ethiopians kill at will."
The Foreign Office, which called in the Yemeni ambassador earlier this week, said it was urgently seeking confirmation that Andargachew was in Ethiopia.
"If confirmed this would be deeply concerning given our consistent requests for information from the Yemeni authorities, the lack of any notification of his detention in contravention of the Vienna convention and our concerns about the death penalty that Mr Tsege could face in Ethiopia," the Foreign Office said in a statement.
It added: "The UK opposes the death penalty in all circumstances as a matter of principle … We continue to call on all countries around the world that retain the death penalty to cease its use."
Ginbot 7 is among the largest of Ethiopia's exiled opposition movements. The party was founded by Berhanu Nega, who was elected mayor of Addis Ababa in 2005. Refusing to accept the result, the prime minister, Meles Zenawi, declared a state of emergency, which was followed by days of protest and clashes on the streets of the capital.
Berhanu Nega was jailed, and founded Ginbot 7 on his release. Accused of attempting to overthrow the Ethiopian government, he and Andargachew Tsige were sentenced to death in absentia. Ginbot 7 was declared a terrorist organisation. The party says it stands for the peaceful end to what it describes as the Ethiopian dictatorship.
Andargachew was travelling to Eritrea, which has clashed with Ethiopia since a border war between the two countries ended in June 2000.
The Eritrean authorities host a number of exiled Ethiopian movements, including some attempting to overthrow the Ethiopian government.
Ana Gomes, a Portuguese member of the European parliament who led the EU observer mission to the 2005 Ethiopian elections, has written to William Hague, calling on the UK foreign secrertary to intervene on Andargachew's behalf, saying: "I urge you now to do the utmost to ensure the release and protection and his return to the United Kingdom as soon as possible."

Thursday, July 3, 2014

''ይህ ልብ የሚሰብር ዜና ነው በምንም ዓይነት አንገት የሚሰብር ግን አይደለም።በእዚህ አንገቱን የሚሰብረውን ሰው ያክል አንዳርጋቸው የሚፀየፈው ሰው የለም።አንዳርጋቸውን እኔ አውቀዋለሁ።ወያኔዎች እሱን በመያዛችን እናገኛለን የሚሉት ነገር ካለ ምንም ነገር አያገኙም።አንዳርጋቸው ትግሉን አንድ ምዕራፍ አሻግሮት ጨርሷል።አመራር ማብቃት ያለበትን ወጣቶችን አብቅቷል።አሁን ሂድ ጨርሰናል ተብሎ ለንደን መኖር ጀምሯል።ከአሁን በኃላ ብንወድቅም እየታገልን ነው የምንሞተው ብንሞትም እየገደልን ነው የምንሞተው።አሁን ጌሙ ተቀይሯል። ዛሬ ብዙ ሰዎች ሲያለቅሱ ሰምቻለሁ ግን አንዳርጋቸውን የምትወዱት ከሆነ አንዳርጋቸው የታገለለትን ዓላማ ነው መውደድ ያለባችሁ አንዳርጋቸውን አይደለም።አንዳርጋቸው ለቅሶ አይደለም የሚፈልገው አሁን አንዳርጋቸው የጀመረውን ትግል ዳር የሚያደርሱ ታጋዮች ነው የሚፈልገው።'' ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የግንቦት 7 ንቅናቄ ሊቀመንበር ዛሬ የተናገሩት (ቪድዮ)



ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

'' UK where is your citizen Ato Andargachew? Yemen release Andargachew now!''ኢትዮጵያውያን ኦስሎ፣ኖርዌይ በሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ፊት አቶ አንዳርጋቸውን አስመልክተው ሰልፍ አደረጉ

የእንግሊዝ ኤምባሲ በኦስሎ (UK Embassy in Oslo, Norway )

ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 26/2006 ዓም (ጁላይ 3/2014) ኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ በሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ፊት ለፊት ቁጥራቸው ከ150 በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያን የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በየመን መንግስት ኃይሎች መታገትን በመቃወም ተቃውሟቸውን ገልፀዋል።ሰልፉ የተዘጋጀው ''የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ'' በጠራው መሰረት ሲሆን የእንግሊዝ ኤምባሲ የተመረጠበት ምክንያት አቶ አንዳርጋቸው የእንግሊዝ ዜግነት ያላቸው በመሆኑ ነው።

በሰልፉ ላይ ከተሰሙት መፈክሮች መሃከል '' ዩኬ ዜጋሽ የት ነው? የመን አቶ አንዳርጋቸውን ልቀቂ! አቶ አንዳርጋቸው የዲሞክራሲ ተሟጋች እንጂ አሸባሪ አይደለም!'' የሚሉ ይገኙባቸዋል።ሰልፉ ፍፁም ኢትዮጵያዊ ጨዋነት የተሞላበት እና የእንግሊዝ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት እንድትሰጥ የማድረግ ዓላማ የያዘ ነበር።

በመቀጠልም  በሰልፉ አስተባባሪ  ''የዲሞክራሲ ለውጥ በኢትዮጵያ'' አማካይነት ለእንግሊዝ ኤምባሲ የተዘጋጀውን ደብዳቤ የእንግሊዝ አምባሳደር በኖርዌይ ተወካይ ወደ ሰልፈኞቹ መጥተው ከመረከባቸውም በላይ ለተሰላፊዎቹ ባደርጉት ንግግር ''ጉዳዩን የእንግሊዝ መንግስት በአንክሮ እየተከታተለ ነው እኛም ከየመን መንግስት ጋር የሚደረጉ ግንኙነቶችን ለማከናወን ጥረት ላይ ነን'' በማለት ተናግረዋል።

በመጨረሻም ሁኔታዎች ለውጥ ካላሳዩ ቀጣይ ሰልፎች እንደሚኖሩ በተለይ በመጪው ማክሰኞ በመላው ዓለም በሚገኙ የየመን ኤምባሲ እንደሚደረግ እና የመን በኦስሎ ኤምባሲ ስለሌላት በሌሎች የአውሮፓ ከተሞች የሚደረጉ ሰልፎች ላይ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቦ የሰልፉ ፍፃሜ ሆኗል።

ጉዳያችን 
ሰኔ 26/2006 ዓም  (ጁላይ 3/2014)

Wednesday, July 2, 2014

የእያንዳንዱ ሰው ጥረት ዋጋ አለው ''የመን ፖስት'' የየመን የእንግሊዝኛ ዜና ድረ-ገፅ የአቶ አንዳርጋቸውን በየመን የፀጥታ ኃይሎች መታገት የኢትዮጵያውያንን ዜና ምንጮች ጠቅሶ ዛሬ ዘግቧል።ለየመን ፕሬዝዳንት የተፃፈውን ግልፅ ደብዳቤም ለየመን ሕዝብ አስነብቧል

የድረ-ገፁን ዘገባ ከእዚህ በታች ባለው ማያያዣ (ሊንክ) ይክፈቱ


http://yemenpost.net/Main.aspx?ID=5&SubID=Andargachew 

'ክርስትና የዋህንን በአድርባይነት መርዝ እየወጉ እና እየተሽሞነሞኑ የሚኖሩበት ሕይወት አይደለም'' በክርስትና ስም ''አትናገሩ'' ለማለት ለሚዳዳቸው የበግ ለምድ ለባሾች ምላሽ ትሁንልኝ


ዛሬ  (ስሙን አልጠቅሰውም) ማንነቱን የማላውቀው ግን ፋይሉ አናት ላይ ነጠላ ለብሶ የተነሳ ፎቶ በትልቁ የለጠፈ የፌስ ቡክ ገፄ አባል እንዲህ የሚል መልዕክት በውስጥ መስመር ላይ ለጠፈለኝ። '' አይ ክርስትና-----ቤተክርስቲያንን ማገልገል አይሻልህም? '' ወዘተ የሚሉ ቃላት ይዟል።ግለሰቡን ከእዚህ በፊት ስለማላውቀው ፋይሉን ከፍቼ ማየት ጀመርኩ።ፕሮፋይሉ ላይ በትልቁ ነጠላ ለብሶ የተነሳውን ፎቶ ለጥፏል።ከወደ አናቱ የሀገራችን ክፍል መሆኑን ፋይሉ ይናገራል።ወደውስጥ ገባሁ።አንዱ ክፍል ላይ አቶ መለስን ፎቶ በትልቁ ለጥፎ የአምላክ ያህል ''ውዳሴ መለስ'' ድርሰት ብጤ ለጥፏል።ቀጠልኩ መጎርጎሬን  በሌላ ቀን አቶ ኢሳያስን ለጥፎ ከውክሊክ ያገኘውን ታሪካቸውን ተርጉሞ ምንጭ ውክሊክ ብሎ አያይዞታል።በተለይ በእዚህኛው ክፍል ላይ አቶ ኢሳያስ ''በነፃ ምርጫ የተመረጡ በዲሞክራሲ የሚያምኑ'' የሚል ጨምሮበታል። እናም ቀደም ብዬ ከቅንነት ሃሳብ የሰጠ የመሰለኝ ሰው አሳዘነኝ እና ለእርሱ እና በቤተክርስቲያን ስም ለሚያጭበረብሩ ሁሉ እንዲህ ማለት ፈለኩ።

ለወዳጄ እና ለመሰሎችህ (የማስታወሻዬ አርዕስት ነች)  
ክርስትና የማጭበርበርያ ጉረኖ አይደለም።ክርስትና እንደ እባብ እየተቅለሰለሱ የዋሃንን የሚነድፉበት የሸለምጥማጦች ጅራፍ አይደለም።ሰው በክርስትና ውስጥ ሲኖር ፍርሃት፣አድርባይነት፣ጥቅምን ማስቀደም እና እኔ ብቻ 'ደረቴ ይቅላ ሆዴ ይሙላ' የሚል ከሆነ ክርስቲያን ባይሆን ይመረጣል።ክርስቲያን በመንግስት ዘረኝነት ሲታወጅ ከንፈር እየመጠጠ ዘረኝነትን የሚጠየፈውን መፅሐፍ ቅዱስ ይዞ ሕዝብ ከሚያታልል እራሱን ወደ ትልቅ ባህር ቢወረውር ይሻለዋል።ክርስቲያን የሰው ዘር በሙስና እና በአድልዎ ሲሰቃይ መቃወም ካልቻለ ባይፈጠር ይበጀዋል። ክርስቲያን ሰዎች ሲሰደዱ ያሰደዳቸውን ቡድን ከመውቀስ ይልቅ በቤተ ክርስቲያን ስም በስዱዳን ቁስል  ላይ የመርዝ እንጨቱን ከላከ ፍርዱ አይቀርለትም።ክርስቲያን ሰዎች ሲታሰሩ ለታሰሩት መጮህ ካልቻለ እራሱን በራሱ በሰይጣን የጥቅም አሽክላ እንደተበተበ እና ቤተክርስቲያን እየሄደ የዋሃንን የሚሸነግል ይሁዳ ቢባል ሲያንሰው ነው።

በሀገራችን ዘረኝነት ነገሰ በክርስትና ስም እንዳላዩ ያለፉ ቃል ላልተነፈስን ወዮልን፣
በሀገራችን የዋሃን ንፁሃን ምንም የተደበቀ አጀንዳ የሌላቸው መውጫ መግቢያቸው የሚታወቅ  (ዞን 9 መጥቀስ ይቻላል) በግፍ ታሰሩ።በክርስትና ስም እኛ የቤተክርስቲያን ነን እያልን ቃል ያልተነፈስን ወዮልን!
በሀገራችን ሰዎች በዘራቸው እና በቋንቋቸው ብቻ እየተለዩ ከኖሩበት ስፍራ በግፍ ተባረሩ (ሐረር፣ወለጋ፣ጉርዳፈርዳ፣ጅጅጋ፣ወዘተ) አይናችን እያየ በክርስትና ስም እኛ የቤተክርስቲያን ነን እያልን ቃል ያልተነፈስን ወዮልን!
የሀገራችን ድንበር እየተቆረሰ ለባዕዳን በሙስና እና በሀገር ክህደት ተቸበቸበ።በክርስትና ስም እኛ የቤተክርስቲያን ነን እያልን ቃል ያልተነፈስን ወዮልን! 
ኢትዮጵያውያን በባዕዳን እየታሰሩ በእየቦታው ሲንገላቱ ''ታስሬ አልጠየቃችሁኝም'' የምትለዋን ቃል ወደጎን ትተን በክርስትና ስም እኛ የቤተክርስቲያን ነን እያልን ቃል ያልተነፈስን ወዮልን! ለታሰሩት፣በዘር እና በቋንቋ አድልዎ እየተደረገባቸው ለተንገላቱት፣በኢትዮጵያዊነታቸው እየተለዩ ለሚታሰሩት መጮህ ክርስትና ነው። ክርስትና በሙስና ፊታቸው ለሚያብለጨልጩ እና በዘረኝነት ለሰከሩ እና ሃገራቸውን ለጥቅም ለሸጡ ወንጀለኞች በመቆም ወይም በአድርባይነት ዝም በማለት አይገለጥም።ክርስትና የዋህንን በአድርባይነት መርዝ እየወጉ እና  እየተሽሞነሞኑ የሚኖሩበት ሕይወት አይደለም።

ጉዳያችን 
ሰኔ 25/2006 ዓም (ጁላይ 2/2014)

Tuesday, July 1, 2014

የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን መታሰርን ለመቃወም የግንቦት 7 አባል ወይንም ደጋፊ መሆን የለብኝም። ኢትዮጵያዊ መሆኔ ብቻ ይበቃል Open letter to Abd Rabbuh Mansur Hadi: President of Yemen Arab Republic



አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ከእንግሊዝ ሀገር በየመን ሀገር በኩል ወደ ሶስተኛ ሃገር  ሲያልፉ በየመን የፀጥታ ኃይሎች ታግተዋል።ይህ በኢትዮጵያዊነት ላይ የተሰነዘረ የንቀት በትር ነው።
አቶ አንዳርጋቸው የጭፍን ጥላቻ አስተሳሰብ ሰለባ አይደሉም።በስልጣን ላይ ላለው ኢህአዲግ/ወያኔ ኢትዮጵያዊ የሆነ መንግስት እንዲሆን በርካታ ጠቃሚ ሃሳቦች ሰጥተዋል፣ለኢትዮጵያ የሚበጀውን መንገድ አመላክተዋል፣በ1997 ዓም ምርጫ ወደ ሀገር ቤት መጥተው ምርጫው በሰላማዊ መንገድ እንዲከወን አስተዋፆ አድርገዋል፣የሰላማዊ ትግል አስፈላጊነትን ለበርካታ ጊዜ ሰብከዋል።የሚሰማቸው አላገኙም።
ዛሬ ላይ የትግል አቅጣጫቸውን ቀይረዋል።በእዚህ  የትግል ምርጫቸው የሚደግፍም ሆነ የሚቃወም ሊኖር ይችላል። አቶ አንዳርጋቸው ግን በየመን መንግስት መታሰርን በዝምታ የማለፍ  ሕሊናዊም፣ኢትዮጵያዊም  ሆነ ሰዋዊ ሞራል ግን ማንም ሊኖረው አይችልም።
የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን መታሰርን ለመቃወም የግንቦት 7 አባል ወይንም ደጋፊ መሆን የለብኝም። ኢትዮጵያዊ መሆኔ ብቻ ይበቃል።

ጉዳያችን
ሰኔ 24/2006 ዓም (ሐምሌ 1/2014)


Open letter to Abd Rabbuh Mansur Hadi: President of Yemen Arab Republic


by Mulat Hailu
yemen-andargachew


The people of Ethiopia are Shocked and disappointed over the illegal detention of Andargachew Tsige, Secretary General of Ginbot7 Movement for Justice, Freedom and Democracy by Yemen security forces during his transit flight in Yemen.

Mr. Andargachew is an Ethiopian origin and British citizen who has been struggling for prevalence of democracy in Ethiopia. He has devoted himself to the true cause of Ethiopian people, the inevitable desire for democracy. Though foiled successfully, the criminal dictatorial regime in Ethiopia has attempted to assassinate the leader Andargachew in November 2013. Mr. Andargachew is hero for Ethiopian people and is one of the icons of democracy in the nation.

The Senna Security forum that has been signed under former president of Yemen, Ali Abdullah Saleh and former dictator of Ethiopia Melse Zenawi which lead TPLF to establish surveillance base in Yemen for surveillance and phone tapping on Ethiopian opposition has been serious concern for Ethiopian people. The illegal detention of Mr. Andargachew, by Yemen Security forces since June 23, 2014 has no ground and is grave concern for the people of Ethiopia. We urge the government of Yemen to immediately free Mr. Andargachew and the Yemen security forces not to transfer him to the criminal regime in Addis under any circumstance. Yemen has no ground to detain Mr. Andargachew who has been tirelessly working for prevalence of democracy in Ethiopia. We request the government of Yemen to carefully evaluate its long term interest and lasting cooperation with the people of Ethiopia and avoid short termism in dealing with dictatorial regime in Ethiopia. The long historical relationship between the people of the two sisterly nations has endured, in spite of changing regimes, on the basis of mutual cooperation. The people of Ethiopia considers the act of transferring Mr. Andargachew to the dictatorial regime in Ethiopia as direct attack on its long aspiration and struggle for genuine democracy in the nation. We hereby request President Hadi not to take any steps that will jeopardies the long lasting relationship between the people of the two sisterly nations and to order the immediate release of Mr. Andargachew. Thank you in advance for your serious consideration.

Open letter source - ECADF
             http://ecadforum.com/2014/07/01/open-letter-to-president-of-yemen/




ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።