ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, December 31, 2022

የእነደብረጽዮን ወደ አዲስ አበባ መምጣት ለፖለቲካዊ እርቅ ወይንስ ለአገራዊ እርቅ?



=============
ጉዳያችን ምጥን
=============

በኢትዮጵያ ፌድራን መንግስት እና በህወሃት መሃከል በደቡብ አፍሪካ ከተደረገው የሰላም ስምምነት ወዲህ የሰላም ሂደቱ በፍጥነት እየሄደ ነው። በሂደቱ ላይ ግን ከኢትዮጵያ ወገንም ሆነ ከህወሃት ወገን ያለው ትችት እንደቀጠለ ነው።ሁሉንም ወገን ያስማማው እና ያስደሰተው አንዱ እና ብቸኛው ጉዳይ የትግራይ ህዝብ በተለይ በከተሞች ያለው ህይወት ወደነበረበት ቦታ የመመለስ ሂደቱ መፋጠኑ ነው።የመብራት እና የስልክ አገልግሎት የጀመረ ሲሆን የባንክ አገልግሎትም በሁሉም ቅርንጫፎች ባይሆንም አገልግሎት ጀምረዋል። በቅርብ ቀናት ደግሞ ሙሉ በሙሉ ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ይህ በእንዲህ እያለ በመንግስት ወገን የተሄደበትን ሂደት የሚተቹት በተለይ የመርህ ጥሰት የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አፈጉባዔ በድንገት የአሸባሪነት ፍረጃ ያልተነሳለት ህወሃት ጋር መገናኘታቸው ከፍተኛ ትችት ከማስነሳቱ በላይ መንግስት ለራሱ ሕግ ያለውን የማክበር ደረጃው ጥያቄ ላይ ጥሎታል።ፓርላማው በትናንትናው ዕለትም ባደረገው ዝግ ስብሰባ የራሱ የብልጽግና አባል የፓርላማ አባላትም በከፍተኛ ደረጃ የአካሄድ ስህተቱን አስመልክተው አስተያየት ሰጥተዋል።

በሌላ በኩል የህወሃት ደጋፊዎች በሃሰት የውጭውን ዓለም ''ጀኖሳይድ ተፈጸመ ሺዎች ተደፈሩ'' እያሉ ሲዋሹ ስለነበር የአሁኑ የህወሃት እርቅ የሚይዙት የሚጨብጡትን አሳጥቷቸዋል።በተለይ እነደብረጽዮን ወደ አዲስ አበባ መምጣት እና ''ፋሽሽት '' እያሉ ሲሰድቡት ከነበረው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ይገናኛሉ የሚለው ዜና እንደሰሙ ድበረጽዮን እና ጌታቸው ድሮም ለዶ/ር ዐቢይ በስውር ሲሰሩ የነበሩ ናቸው የሚል ርቀት ያህል ሄደዋል።

በእዚህ ሁሉ መሃል ግን በትግራይም ሆነ በቀረው የኢትዮጵያ ክፍል ያለው ህዝብ ሰላም መምጣቱን ከከፍተኛ ስጋት ጋር ተቀብሎታል።
ዛሬ ሰላም ሆነ ማለት ግን ቀጣይ ነው አይደለም የሚለውን ምላሽ በጥራት ይሰጣል ማለት አይደለም።ይህ ሰላም የመጣው የኢትዮጵያ መከላከያ ከጥምርጦሩ ጋር ሆኖ የትግራይን 90% በላይ ከተማና ገጠር ነጻ ካወጣ በኋላ መሆኑ ይህ ድል ባይመጣ ኖሮ ህወሃት መቼም ወደ ድርድር ጠረንጴዛ እንደማይመጣ የታወቀ ነው።ይህንን መሰረታዊ ጉዳይ ስናስብ ነው ይህ እርቅ ፖለቲካዊ ነው ወይንስ ሃገራዊ እርቅ ነው? የሚል ጥያቄ እንድንጠይቅ የሚያስገድደን።

አሁን ባለበት ደረጃ በመንግስት እና በህወሃት መሃከል የተደረገው ስምምነት ፖለቲካዊ ነው።ፖለቲካዊ እርቅን ወደ ሃገራዊ እርቅ ለመውሰድ እና በፖለቲካዊ እርቅ የታረቁት ሁሉ ከመስመሩ እንዳይወጡ የሚያደርግ የህዝብ አስገዳጅነት የሚኖረው እርቁ ሃገራዊ እርቅ መሆን ከቻለ ብቻ ነው።የኢትዮጵያ ህዝብ ድሮም ከህወሃት ጋር የነበረው ጦርነት በኢትዮጵያ ህልውና ላይ ህወሃት በመዝመቱ እና ከአሁን በኋላ የህወሃትን የበደል ቀንበር መሸከም የሚችል ትከሻ ስለሌው ነው።

ፖለቲካዊ እርቅን ሃገራዊ እርቅ ለማድረግ የሚነሱ በርካታ ጉዳዮች አሉ።ሃገራዊ እርቅ ርትዕ የሆነች ፍትሕ ይፈልጋል።የተበደለው እና የተዘመተበት ሃገር እና መከላከያ ነውና ይህ ወንጀል ለወደፊቱ ትውልድም እንዳይቀጥል አንድ ዓይነት ያጠፋው የሚቀጣበት የተበደለም የሚካስበት ዓይነተኛ መንገድ ይፈልጋል።በአፋር እና በአማራ ህዝብ ላይ የተፈጸመው በደል እና የግፍ ዓይነት ለፈጻሚዎቹ የሚያስተምር የፍርድ ሂደት ያስፈልጋል። በተመሳሳይ በትግራይ ህዝብ ላይ የተፈጸመ የህግ ጥሰት በመከላከያ አባላት በኩል የተፈጸመ ካለ መንግስት ከእዚህ በፊት በጀመረው የማጣራት ሂደት መሰረት አጣርቶ ለፍርድ ማቅረብ አስፈላጊ ነው።

ሰላም የሚጠላ የለም።በትግራይ የሚኖረው ሰላማዊ ህዝብ የመሰረተ አገልግሎት ማግኘቱ እና ከሁሉም በላይ ለሁለት ዓመታት በህወሃት ከታገተበት እገታ በመከላከያ እና ጥምር ጦር ብርቱ መስዋዕትነት ከእገታው ተላቆ ከተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር መገናኘቱ ሁሉ ያስደስታል።ከእዚህ ሁሉ ጋር ግን እርቁ የቀድሞ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች እርቅ እንዳይመስል ህወሃት የተጣላው ከአገር ጋር ነው እና አገራዊ እርቅ የሚሆንበት መንገድ ቢፈለግ መልካም ነው።ይህ ሲባል ደግሞ ከአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር የሚደረገውን ምክክር ይጠብቅ ማለት አይቻልም።ሌላም ጥያቄ አለ።በኢትዮጵያ መከላከያ ላይ ህወሃት ጥቃት ሲፈጽም ከኢትዮጵያ ጎን ቆማ የተራዳችው የኤርትራ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ እነደብረጽዮን መጥተው የእርሳቸው አለመገኘት ፍትሃዊ አያደርገውም የሚሉ አሉ።የአዲስ አበባ ህዝብ ደግሞ ''ኢሱ! ኢሱ!'' ማለት እንጂ ደብረጽዮን! ማለት አልለመድም።አሁን ባለው ተጨባጭ ነባራዊ ሁኔታም አይልም።አቶ ኢሳያስስ እሺ ብለው ይመጣሉ ወይ? 

ይህ በእንዲህ እያለ በህወሃት እና በመንግስት መሃል የተደረገው የሰላም ስምምነት በሚፈልጉት መጠን እጃቸውን መጥለቅ ያልቻሉት አንዳንድ የምዕራብ መንግስታት ብሽቀት እንደፈጠረባቸው ተሰምቷል።የብሽቀቱ መነሻ ደግሞ ሁለት ናቸው። አንዱ የአፍሪካ ሕብረት በእዚህ ያህል አቅም አደራድሮ በመቶሺዎች የተሰለፉበትን ጦርነት ወደሰላም ማምጣቱ አንድ የተሞክሮ ልምድ ሆኖ አፍሪካ ያለማንም የምዕራባውያን ጣልቃገብነት ወደፊት እንድትራመድ ያደርጋትና ጥቅማችንን ማሳካት አንችልም የሚል ሲሆን፣ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ስምምነቱ በቶሎ አይጠናቀቅም የተራዘመ ክርክር ውስጥ ይገባሉ የሚለው የሃገራቱ ግምት አለመሳካቱ ነው።ድርድሩ በጣም ቢራዘም ኖሮ እነኝሁ የውጭ መንግስታት በተለያየ አጀንዳዎች እየበለቱ ጉዳዩን አክርረው ጥቅማቸውን ለማስከበር ያመቻቸው እንደነበር ያምናሉ።ባለፈው ዓርብ ወደ መቀሌ የበረሩት ዲፕሎማቶች ስብሰባው ላይ ነበር ለማለት እንጂ በቀጥታ የሚገቡበት እና ከእነ ኦባሳንጆ ጋር የሚስተካከል ቀጥታ ሚናቸው ታይቶ ለአፍሪካውያን ይህንን ሰራን የሚያስብል አንዳች ለሚድያ የሚበቃ ጉዳይ ይዘው አልመጡም።ይህ ማለት አሜሪካ የመሳሰሉ ሃገሮች እጅ በተዘዋዋሪ አይታይም ማለት አይደለም።ነገሮች በቶሎ ባይቋጩ ኖሮ ከእዚህ በበለጠ መልኩ የስቴት ዲፓርትመንት በየቀኑ መግለጫ ሲሰጥ እና በኋላም ሂደቱን በእጃቸው ሙሉ በሙሉ ለማስገባት አይሞከርም ማለት አይቻልም።

ለማጠቃለል፣የሰላም መምጣት የማስደሰቱን ያህል ህወሃት የሸር ፖለቲካውን መልሶ እንዳይረጭ ህዝብ ዋስትና ይፈልጋል።ማንም ደግሞ ህወሃት የሰራው ወንጀል ተለባብሶ  ታልፎ፣እርቁም ፖለቲካዊ እርቅ ብቻ ሆኖ ፍትህ ሳይጨምር ከሄደ ስጋታችን ያይላል።ስጋቱ ደግሞ ይህንን ለማስተካከል የሚነሳ ሌላ የህዝብ ንቅናቄ ተነስቶ ከምርጫ ፖለቲካ የራቅን ሌላ ፍትጊያ ውስጥ የምንገአብ ሃገር እንዳንሆን ከመስጋት የሚመነጭ ነው።የጀርመን ህዝብ የናዚ ፓሪትን ከሽንፈቱ በኃላ በዕርቅ ልፍታው ቢል ኖሮ ዛሬ ለደረሰበት የልማት ደረጃ አይደርስም ነበር።የጣሊያን ህዝብ የሞሶሎኒ ፋሺሽት ፓርቲ በጥምር መንግስት ውስጥ ይቆይ ብሎ ቢተውው ኖሮ ዛሬ ምናልባት የምናውቃት ጣልያን ላትኖርትችላለች።ህወሃትም ከእርቁ በኋላም ታደሰ ወረደ በግልጽ እንዳሉት የእርቁ ዓላማ እርሳቸው ጠላት የሚሏቸውን የኢትዮጵያ መንግስት እና የኤርትራ መንግስትን መከፋፈል መሆኑን ተናግረዋል።በመሆኑም ፖለቲካዊ እርቅ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ሲጠፉ አብሮ ይጠፋል።አገራዊ እርቅ ኝ ያሻግራል።በመሆኑም እነደብረጽዮን አዲስ አበባ መጥተው እርቁን ይፈጽማሉ የሚለው የሰሞኑ ወሬ ጥያቄ ይዞ መጥቷል። ይሄውም እርቁ ፖለቲካዊ ነው ወይንስ አገራዊ? የሚል ነው።
==========////=======

Wednesday, December 28, 2022

የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በታላቅ ግርማ ሞገስ በሰዓታት ውስጥ ከመቀሌ አሉላ አባነጋ አየር ማረፍያ ጀምሮ መቀሌን መቆጣጠር ይጀምራል!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ


በእዚህ ምጥን ጽሑፍ ስር ፡ 
  • ምስጋና ለኢትዮጵያ ህዝብ ይገባዋል፣
  • አድናቆት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አመራር ያስፈልጋል።
  • የትግራይ፣አፋር እና አማራ ክልሎች በጋራ በየትኛውም ወገን ለሞቱ ወገኖች ለሦስት ቀናት የሃዘን ቀናት ቢያውጁ፣ 
  • የኢትዮጵያ ሕዝብ ዐይኑን በጨው ሳይሆን በአጃክስ አጥቦ ለታየው የህወሃት አመራር እንዴት ዓይነት ንስሃ እንደሚገባ እየጠበቀ ነው።
=========
ጉዳያችን ምጥን
=========

የኢትዮጵያን አንድነት ለማስጠበቅ የደም እና የአጥንት መስዋዕትነት የከፈለው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በታላቅ ግርማ ሞገስ ከሰዓታት በኋላ የመቀሌን አሉላ አባነጋ አየርማረፍያን ጨምሮ መቀሌን ይቆጣጠራል።መከላከያ ላለፉት ተከታታይ ወራት የህወሓትን ታጣቂ ኃይል በተቀናጀ እና ልዩ በሆነ ኦፕሬሽን በሦስት አቅጣጫዎች በመግባት የትግራይ ሁሉንም ከተሞች ነጻ ካወጣ በኋላ መቀሌን በቅርብ እርቀት ከቦ መቆየቱ ይታወቃል።በእዚህም መሰረት ወደ መቀሌ የመግባቱ ሂደት እንደተጀመረ ህወሓት ትጥቅ ለመፍታት እና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ለመደራደር በመስማማቱ መከላከያ መቀሌን ከቦ እንዲጠብቅ ታዞ ነበር።በመቀጠል በፕሪቶርያ፣ደቡብ አፍሪካና ናይሮቢ፣ኬንያ ድርድር ከተደረገ እና ህወሃት ትጥቅ ለመፍታት በፊርማ ካረጋገጠ በኋላ መከላከያ ወደ መቀሌ ከሰዓታት በኋላ በታላቅ ግርማ ሞገስ ወደ መቀሌ እንደሚገባ ታውቋል።

ምስጋና ለኢትዮጵያ ህዝብ ይገባዋል!

የኢትዮጵያ ሕዝብ ህወሃት በከፈተው ኢትዮጵያን የመበተን ዘመቻ ወቅት ኢትዮጵያ አንድነቷን ጠብቃ እንድትኖር ከህይወት መስዋዕትነት እስከ ንብረቱ ከፍሏል። እዚህ ላይ ግን ለማንሳት የምሞክረው ህዝብ ውስጣዊ አንድነቱን ከመጠበቅ ባለፈ ህወሃት ህዝቡን ለማጫረስ በትግራይ ህዝብ እና በቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ መሃል ግጭት ለመፍጠር የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ቢከፍትም በመሃል ሃገር በሚኖሩ በሚልዮን የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች ላይ አንዳች የግጭት ኮሽታ ሳይሰማ እርስ በርሱ ተደጋግፎ የህወሓትን የመሃል ሃገር የግጭት ድግስ አክሽፏል።ለእዚህም ምስጋና ይገባዋል።

አድናቆት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አመራር ያስፈልጋል።

ኢትዮጵያ ባለፉት አራት ዓመታት ውስጥ እጅግ ፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አልፋለች።ይህም ሆኖ ደግሞ እጅግ ጥበብ የተሞላበት እና ትዕግስት የሚፈልግ አመራር የሚያስፈልግበት ጊዜ ነበር።የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አመራር ከህወሃት ጋር የሰላም መንገድ ለመከተል የቻለውን ሁሉ አድርጓል።የሰላም ጥረቶቹን በተመለከተ ይህንን ሊንክ ተጭነው ማዳመጥ ይችላሉ።

በእነኝህ ሁሉ ጥረቶች ሳይሳኩ ሲቀሩ እና የኢትዮጵያ አንድነት አደጋ ላይ ሲወድቅ ደግሞ በቀጥታ ወደ ጦር ግንባር በመዝመት ለኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን መሪ መሆናቸውን አሳይተዋል።ይህ ብቻ አይደለም በአሁኑ የሰላም ሂደት ላይም በርካታ ውጣ ውረዶችን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያን ብቻ በመመልከት ብዙ ጉዳዮችን በትዕግስት እንዳለፉ እና አሁን ለተደረሰበት የሰላም ሂደት ደረጃ እንዲደርስ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብቻ ሳይሆን የአጠቃላይ አመራሩ ጥረት እና ቅንነት የተሞላበት ሂደት ያደረገውን አስተዋጾ ለመረዳት ይቻላል።ለእዚህ የሰላም ሂደት የመንግስት አመራር ሚና በቀላሉ የሚታይ አይደለም።ይህንን ለመረዳት አንድ ሰው ቤተመንግስት ውስጥ መሆን የለበትም። የህወሃትን እኩይ አካሄድ በመመልከት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና አመራራቸው ለሃገር ሲባል ብዙ ትዕግስት ለማድረጉ በቀላሉ ማወቅ ይቻላል።

የትግራይ፣አፋር እና አማራ ክልሎች በጋራ በየትኛውም ወገን ለሞቱ ወገኖች ለሦስት ቀናት የሃዘን ቀናት ቢያውጁ፣

በአማራ እና በአፋር ክልል በህወሃት ዘመቻ በብዙ ሺህ ሰላማዊ ዜጎች ላይ እልቂት ተፈጽሟል፣ሴቶች ተደፍረዋል፣ንብረት ተዘርፏል።በተመሳሳይ መንገድ በትግራይ በህወሃት አስገድዶ ዘመቻ እንደ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አደራዳሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የናይጀርያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ገልጻ ከሆነ ከግማሽ ሚልዮን በላይ ህይወቱ አልፏል።

ይህ በእንዲህ እያለ በትግራይ ቤተሰባቸውን ያጡ ሰዎች ለቅሶ እንዳይቀመጡ የህወሃት ካድሬዎች እያስፈራሩ እንደሆነ ተሰምቷል።ከእዚህ ሁሉ በላይ ግን በሦስቱ ክልሎች በጦርነቱ የብዙ ሰው ቤት በሃዘን ተውጧል።ሃዘን ደግሞ ጊዜ ተወስኖለት ስሜቱን መግለጹ በራሱ የሰላም ሂደት ነው።አብሮ መብላት ብቻ ሳይሆን አብሮ ማልቀስም ያስማማል።እዚህ ላይ በቀረው የኢትዮጵያ ክፍል ወለጋን ጨምሮ የነበረው የሞት ቁጥር ሳይገባ በሦስቱ ቦታዎች ብቻ ሃዘን ለምን? የሚል ጥያቄ ሊያስነሳ ይችላል።ሆኖም ግን ይህ የሶስት ክልሎች በአንድነት በሚጋሩበት ቦታ የነበረው የንጹሃን እልቂት ቁጥር እና ውድመት እጅግ ከባድ በመሆኑ ብቻ ሳይሆን በቀጣይም ተመሳሳይ ችግር የፖለቲካ አካሎች ቢያስቡም ህዝብ ግን ባለው ጊዜ ህመሙን በጋራ ሃዘን አስታሞ በመጪው ጊዜም ህወሃት መልሶ ወደ ግጭት እንዳይመራው ውስጣዊ አንድነቱን ማጠናከሩ ጥቅም አለው።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ዐይኑን በጨው ሳይሆን በአጃክስ አጥቦ ለታየው የህወሃት አመራር እንዴት ዓይነት ንስሃ እንደሚገባ እየጠበቀ ነው።

ለእዚህ ምንም ዓይነት ማብራርያ አያስፈልገውም።የህወሃት አመራሮች ከግማሽ ሚልዮን በላይ ህዝብ አጫርሰው በከረቫት ብቅ ብለው መታየታቸው እና አለማፈራቸው የኢትዮጵያ ህዝብ የእየቤቱ መነጋገርያ ነው።አሁን ለራሳቸው ንስሃ ገብተው ዳግም ኢትዮጵያን ከልብ ይቅርታ ይጠይቃሉ ወይንስ በለመዱት አፋቸው ደልለው መልሰው ሃገር ያምሳሉ? የሁሉም ጥያቄ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ግን እየጠበቀ ነው።

በመጨረሻም አሁን ኢትዮጵያ እየሄደችው ያለው መንገድ ወደ ጽኑ ሰላም እና አንድነት እንዲመራልን ለእዚህም አምላኳ እንዳይለያት የሁላችንም ጸሎት ሊሆን ይገባል።
=================////=========

Monday, December 19, 2022

ወቅታዊው የኢትዮጵያ ሁኔታ በተመለከተ ልናውቅቸው የሚገቡ አምስት ወሳኝ ዐበይት ጉዳዮች


========

ጉዳያችን
=========

የጎሳ ጉዳይ በተመለከተ በምናስበው ደረጃ አይደለም።


የኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ሲነሱ በተለይ አዕምሮ የሚረብሹ ጉዳዮች በዜና ሲነገሩ ብዙ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈጥሩት የስሜት መዋዥቅ አና የተስፋ መቁረጥ ስሜት ቀላል አይደለም።በተለይ በአብዛኛው የፖለቲካ ጉዳዮችን ሳይሰሙ የኖሩ ወይንም በግማሽ ልብ አልፎ አልፎ የሚከታተሉ ኢትዮጵያውያን በድንገት የሚሰሟቸው ክፉ ዜናዎች መጪውን በከፋ ደረጃ እንዲያዩ ያደርጋቸዋል።ይህ ደግሞ ወደ ዲያስፖራው ማኅበረሰብ ሲመጣ አጅግ የከፋ ይሆናል።ዲያስፖራው በሚኖርበት ሀገር የተረጋጋ አካባቢያዊ ሁኔታዎች ከመኖራቸው አንፃር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ክፉ ነገር ብቻ የሚናገሩ የውጭ ሚድያዎች አና እንደ አሸን የፈሉት የዩቱብ ገፆች ሁሉ የሚሉት በአዕምሮ ላይ የሚፈጥሩት ጠባሳ ቀላል አይደለም። የእዚህ ዓይነት ዜናዎች ተጠራቅመው ተስፋ የቆረጠ አና ስሜታዊ ውሳኔ የሚወስን ማኅበረሰብ የመፍጠሩ አደጋም ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ ነው።


ይህ ማለት በኢትዮጵያ በፅንፍ ኃይሎች እና በሰሜኑ ህወሓት በጫረው ጦርነት ሳብያ እየጠፋ ያለው ሕይወት ቀላል ነው ወይንም በንፁሃን ላይ የደረሰው ሁሉ የሚቃለል ነው እእስከ አፋር አና አማራ ክልል ሁሉ የሆኑትና ዜጎች ላይ የደረሰው ሞት፣ስደት አና የንብረት መውደም አጅግ አሳዛኝ ነው።የሆነው ሁሉ ግን ዳግም እንዳይሆን አና የበለጠ ኢትዮጵያን አንዳይጎዳይ መጪውን ማስተካከል የሚጀመረው የዜጎችን የአዕምሮ ሁኔታ በሚገባ በመቃኘት አና የጠነከረ እንዲሆን በማድረግ ነው።


በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ የእርስበርስ የብሔር (ጎሳ) ግንኙነት በህዝብ ደረጃ የተበላሸ የሚመስላቸው፣አንዳንዱ ከወጣበት አካባቢ ውጭ ያለው ሁሉ አስጊ አድርጎ የማየት አደጋ አለ። ይህ ከበቂ መረጃ በራቀ መልኩ እራስን በአጥፊ ዩቱበሮች አና ሚድያዎች ልክ ወስኖ የመኖር የስህተት መንገድ ነው።ነባራዊ ሁኔታውን ለመረዳት ግን የኢትዮጵያ የጎሳ ግጭቶች ባህሪዎች የተለዩ አና ወደ ሕዝብ አንዳይመጡ የሚያደርጋቸው በርካታ ተፈጥሯዊ ጉዳዮች አሉ።ይህ ማለት አሁን ካለንበት ሁኔታ አንጂ ሕዝቡም ሆነ መንግስት በጋራ መሰረታዊ ለሆኑ የምጣኔ ሀብት አና ፖለቲካዊ ጉዳዮች መፍትሄ ካልሰጠን ለወደፊቱ ትውልድ የምናወርሰው አደጋ የለም ማለት ግን አይደለም።


ኢትዮጵያ የተለየች ሀገር የሚያደርጋት አና የጎሳዊ ጉዳዮች የሀገሪቱን ስር አንደማይነቅል በአርግጠኘትን መናገር የሚቻለው በሚከተሉት መሰረታዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ነው።

  • ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው ሕዝብ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው ቢያንስ ከሁለት ጎሳ የሚወለድ ነው።ነገር ግን ይህ የህብረተሰብ ክፍል አሁን ያለው የፖለቲካ አደረጃጀት አግልሎታል።ለመብቱ ሲነሳ ግን ኢትዮጵያዊነት ቦታውን ያስከብራል።

  • በኢትዮጵያ የጎሳ ግጭቶች ከመንግስት ባለስልጣናት የሚነሱ አልያም የፖለቲካ ድርጅቶች በቢሮ ቀምመው የሚሰሯቸው አንጂ ታሪካዊ የግጭት መሰረት ይዘው የሚመጡ አይደሉም።ይህንን ለማብራራት ብዙ ቦታ ስለሚወስድ አንዳለ አስቀምጠዋለሁ።እውነታው ግን ይሄው ነው።

  • በኢትዮጵያ የተደረጉ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምን ያህል ጎሳን አየቀሰቀሱ ቢመጡም ኢትዮጵያ በቅኝ ተገዝታ ስለማታውቅ አና በማኅበረሰቡ ውስጥ የቆየ የመለያያ ሥራዎች አንደ የሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ስላልተተከሉ ሕዝብ በራሱ ማኅበራዊ መስተጋብር የሚያመክንበት የራሱ አሰራር አለው።ይህ አሰራር ደግሞ በማኅበራዊ ትስስር ብቻ ሳይሆን በታሪካዊ መንገዶች ሁሉ የተሰናሰለ ነው።


ከላይ ለተነሱት ነጥቦች ማስረጃ የሚሆነን የቅርቡን ከህወሓት ጋር የተደረገውን ጦርነት አና በወለጋ አየሆነ ያለውን መመልከት በቄ ነው።ህወሓት የትግራይን ሕዝብ የቀረው ኢትዮጵያዊ ሊያጠፋህ ነው የሚል የሐሰት ፕሮፓጋንዳ ሲነዛ ከሦስት አስር ዓመታት በላይ ሆኖታል።ይህንን ዘመቻውን በማድረግ የትግራይ ሕዝብ ሁሌ አየደነገጠ አንድኖር አና ህወሓት ከሌለ የማይኖር አድርጎ አንዲያስብ ብዙ ሰርቶበታል።ይህ ሁሉ ዘመቻ ፍፃሜ ለማድረስ ደግሞ መከላከያ ላይ የተቀናጀ ጥቃት በመፈፀም  ከሃያ ዓመታት በላይ አብሮት የኖረውን ብቻ ሳይሆን ከሕዝቡ ጋር ተዋልዶ አና ተዛምዶ የኖረውን የትግራይ ማኅበረሰብ ለማቆራረጥ ሞከረ።ይህ ብቻ አይደለም።በአማራ አና አፋር ሕዝብ ላይ ሦስት ዙር ወረራ ሲያደርግ የትግራይን ሕዝብ ከአማራ አና ከአፋር አቆራርጦ የፍርሃት ስሜቱን በማናር አና ህወሓት ከሌለ ትግራይ አትኖርም የሚል ስሜትም ለመፍጠር በማለም ነበር አጅግ የሚዘገንኑ ግፎች በሰላማዊው የአማራ አና አፋር ሕዝብ ላይ አንዲፈፀም ያደረገው።የህወሓት ፍላጎት የጠላትነት ስሜት በማናር የትግራይ ሕዝብ ለህልውና በሚል ከህወሓት ጋር አብሮ ገደል አስቀመግባት ድረስ ለመያዝ ያለመ ነበር።ከአዚህ በተጨማሪ በመሃል ሀገር ከሚኖሩ በሚልዮን የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች ላይ ሌላው ሕዝብ ይነሳል ይህም የትግራይ ሕዝብ ከህወሓት ጋር የበለጠ ያጣብቀዋል የሚል ከንቱ ስልት ይዞ ነበር የግፍ ስራውን ሲፈፅም የነበረው። ይህ የህወሓት ሕልም ግን አልሰራም።በመሃል ሀገር በሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ላይ ሕዝብ አንዳችም የተለየ መልክ አላሳየም።ህወሓት ወንድሙን ወሎ አና አፋር ላይ የገደለበት መሃል ሀገር የሚኖር ኢትዮጵያዊ ጎረቤቱ የትግራይ ተወላጅ ተጠይቂ አንዳልሆነ ጠንቅቆ ያውቃል።

በተመሳሳይ መንገድ በወለጋ የተፈፀመው በንፁሃን በአብዛኛው  የአማራ ተወላጆች አና አንዲሁም  የኦሮሞ ማኅበረሰብ ላይ የደረሰው የጅምላ ግድያ አቀናባሪው የፖለቲካ ድርጅቶች አንጂ ሕዝብ አንደህዝብ ተነስቶ የፈፀመው አይደለም።ለምሳሌ በወለጋ ለዓመታት የኖሩ የአማራም ሆነ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ጎረቤቴ ተሰብስበው አንዲህ ዓይነት ግፍ ፈፀሙብኝ ያኛው መንደር ሰው በአዝህኛው መንደር ሕዝብ ላይ ይህንን አደረገ የሚል ክፉ ወሬ አልተሰማም። በፖለቲካ ድርጅቶች የተደራጁ የታጠቁ ኃይሎች አና የአነርሱ የሴል አካላት ከልዩ ኃይል ወይንም በመንግስት መዋቅር ውስጥ ተሸሽገው የፈፀሙት ወንጀል ነው በኢትዮጵያ አየታዬ ያለው።የፖለቲካ ድርጅቶች አና በመንግስት ውስጥ የተጠለሉ ወንጀለኞች መሆናቸውን ሕዝብ ስለሚያውቅ በጥቃቱ የሚሰደዱትን ስደተኞች ቦታ ቀይረው በሰፈሩበት ሁሉ የሚረዳቸው የአካባቢው ማኅበረሰብ ማለትም የኦሮሞም የአማርም ማኅበረሰብ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል።


ከላይ በትግራይም ሆነ በወለጋ ለሆኑት ሁሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደህዝብ ያለው ጥንቁቅነት፣የይቅርባይ መንፈስ ይዞ ነገ ላይ የሚያሻግር ሥራ ላይ ማትኮሩ አና አሁንም የፖለቲካ ድርጅቶች አና በመንግስት ውስጥ የተጠለሉ ወንጀለኞች የሚሰሩበትን ወንጀል ወደ ጎረቤቱ ሳያጋባ የመኖር ጥበቡን ማድነቅ አና ይህንን አጉልተን ማሳየት አስፈላጊ ነው።ከብዙ መጥፎ ነገሮች ውስጥ መልካም ነገሮችም አሉ አና ይህንን የኢትዮጵያን ሕዝብ መልካም ነገር አውጥተው የሚያሳዩ ሚድያዎች ስለሌሉ አና ክፉ ክፉው ብቻ ስለምነገረኝ አራሳችንን ሳናውቅ አንድንኖር አየተደረግን ነው።ባለው አጋጣሚ ግን ይህንን መልካም ጉዳይ አሁንም አጉልቶ አና ተጨባጭ ታሪኮችን ይዘው ሚድያዎች ሊመጡ ይገባል።ይህ ደግሞ አሁን ያለውን ትውልድ አንድነት ለማጠንከር ብሳይሆን ለመጪው ትውልድ አንዴት ይህንን ጊዜ አንዳለፍን ማሳያ ተጨባጭ ትምህርት ስለሚሆንም ጭምር ማለት ነው።



በአእምሯችን ላይ ሚድያዎችና የመንደር ወሬዎች የፈጠሩብንን ጥቃቅን ቀበሮዎች እንንቀላቸው።


ሕዝብ ዝምብሎ አይለያይም መጀመርያ አዕምሮ ላይ የመለያየት ጥቃቅን ቀበሮዎች በእየለቱ እንእንዲፈጠሩ ይደረጋል።ጥቃቅን ቀበሮዎቹ ሌላው ሕዝብ መጥፎ እንደሆነ የማሰብ፣እራስ ከተወለዱበት አና የመጡበት አካባቢ ውጭ ያለ አደገኛ አና አጥፊ ነው የሚል የሐሰት ትርክት በየአለቱ የምንሰማው የማኅበራዊ ሚድያ መጥፎ ጎርፎች የሚመጣ ነው።በማኅበራዊ ሚድያ ላይ የሚጣሉት አንዱን ጎሳ ከሌላው የሚያብጠለጥሉ አና የራስን ጎሳ የሚያሞካሹ ጥቅሶች፣ንግግሮች አና የምናከብራቸው ሰዎች የተሳሳተ የጥላቻ ሃሳቦች ሁሉ በጥቃቅን የጥላቻ ቀበሮዎች አእምሮአችንን ይበክሉታል። ይህ አጅግ አደገኛ ሁኔታ ነው።በአዚህ ዓይነት ስሜት ውስጥ ሰዎች የሚያውቁትን ጎረቤት ብቻ ሳይሆን  የተለይ የጎሳ አባል ነው የሚሉትን የሚያውቁትን አና አብረው ለዘመናት የኖሩትን ዘመድ ሳይቀር ሳያውቁት ክፉ ስሜት አንድሰማቸው ያደርጋል። ስለሆነም ሰውን በሰውነቱ የማክበር አና የተሳሳተ ቢኖርም የሚታርም መሆኑን የማመን ስብእና ማዳበር ያስፈልጋል።ይህንን ለማድረግ ያማያስፈልጉ የውሸት ትርክቶችን አለመስማት፣ጆሮን ከመጥፎ ወሬ መጠበቅ አና የሰውነት ክብርን ጠብቆ መኖር ያስፈልጋል። ይህንን ለማድረግ ደግሞ በተለያየ ጊዜ ወደ አእምሮ የገባውን ጥቅቅን የጥላቻ ቀበሮ መንቀል ያስፈልጋል።


ኦሮሞ ሁሉ ወንድሜ ነው፣ትግራይ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ወገኔ ነው፣አማራ ሁሉ ወገኔ ነው፣ሱማሌ ቤተሰብ ነው፣አፋር የአኔው ነው አያልን በአግባቡ አእምሮ የማከም ሥራ ያስፈልጋል። ይህንን በተገቢው መንገድ መስራት የሚገባቸው ሚድያዎች አሁንም፣ አሁንም ብዙ ይጠበቅባቸዋል።



ኢትዮጵያን የሚመራ መሪ በማጥላላት የኢትዮጵያን ርዕይ ለማጨለም መሞከር የተለመደው የባዕዳን ስልት በመሆኑ እንንቃ! 


ችግሮችን ሁሉ የሀገር መሪ ላይ አስቀምጦ የሚፈለገውን ሀገር ማፍረስ የቀዝቃዛው ጦርነት አንዱ ስልት ነው።ይህ ስልት በወቅቱ የምስራቁ ጎራ ሊጠቀምበት አልቻለም።ምክንያቱም የምዕራብ ሀገሮች መሪዎች ተቀያያሪ ናቸው። በተወሰነ ጊዜ ምርጫ ማድረጋቸው መሪዎቻቸው በስልጣን አስካሉ ድረስ ላለው አጭር ጊዜ ኢላማ ቢደረጉም አዳዲስ ተመራጭ መሪዎች ከአዲስ ሃሳብ ጋር ስለሚመጡ የህዝቡንን ስሜት የመግዛት አቅማቸው ከፍ ያለ ሆኗል።በአዚሁ የቀዝቃዛው ጦርነት ጊዜ የምዕራቡ ዓለም ግን በምስራቁ ዓለም ለነበሩ መሪዎች ላይ በሚገባ ተጠቅሞበታል።በጊዜው የነበሩት የኢትዮጵያ መሪ ኮለኔል መንግስቱ ኃይለማርያም አንዱ ሰለባ ነበሩ።የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ አና ምጣኔ ሃብታዊ ችግሮች ሁሉ ተጠያቂ ተደርገው አንዲቀርቡ የተደረጉት ኮሎኔል መንግስቱ ነበሩ።በአዚህም የኮሎኔል መንግስቱ መወገድ ብቻ የኢትዮጵያን ችግር ይፈታል የሚል ቂላቂል ሃሳብ ተጠቂ የሆነው ተራው ሕዝብ ብቻ ሳይሆን በኮሎኔል መንግስቱ ዙርያ የተሰበሰቡ ከፍተኛ ባለስልጣናት መሆናቸው የፕሮፓጋንዳው ኃይል ምን ያህል አንደሰራ አአላካች ነው።ለአዚህም ነው ግንቦት 13፣1983 ዓም ኮሎኔል መንግስቱ ከኢትዮጵያ መውጣታቸውን አስመልክቶ በወጣው የመንግስት መግለጫ ላይ ‘’የኮሎኔል መንግስት ከስልጣን መወገድ ለአገራችን ሰላም አስፈላጊ በመሆኑ’’ የሚል ዓረፍተ ነገር የተጨመረበት እና ለኢትዮጵያ ሕዝብ በራድዮ አና ቴሌቭዥን የተነበበው።በጊዜው መንግስቱ ኃይለማርያም ከአስፈሪ ሰው ጋር ብቻ ሳይሆን ከመጥፎ ነገር ጋር ሁሉ የተዛመደ ተደርጎ አንድሳል ተሰርቶ ነበር።


በቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ የስልጣን ማብቅያ ላይም የታየው ይሄው ነው።ንጉሱን የማጥላላት ዘመቻ ውስጥ ውስጡን በተቻለ መጠን በተለይ በወቅቱ በነበረው ወጣት ዙርያ ተሰርቷል።ኢትዮጵያን ወደዘመናዊ አስተዳደር ለማምጣት ከትምህርት አስቀ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ድረስ ብዙ የሰሩት ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ላይ የተደረገው የማጥላላት ዘመቻ አስቀ ቤተሰባቸው ድረስ አንዲዘልቅ ከመሞከሩ የተነሳ የራሳቸው ልጆች ብቻ ሳይሆኑ በወቅቱ የነበሩት ባለስልጣናት ሳይቀሩ ከንጉሡ ጋር አብረው ለኢትዮጵያ መፍትሄ ለማምጣት አስከመዘናጋት አድርሷቸዋል።በወቅቱ ጥቂት ምሁራን ብቻ ችግሩን ከንጉሡ ጋር ብቻ ማያያዝ አና የአርሳቸው መወገድ ብቻውን የኢትዮጵያን መፍትሄ አንደማያመጣ ይልቁንም አርሳቸውን በቦታቸው በሀገር ክብርነት አስቀምጦ አስተዳደሩን በሕዝብ በተመረጠ መንግስት መቀየር አስፈላጊ መፍትሄ ነው ያሉት አንዴ ደራሲ አና ዲፕሎማት ሐዲስ አለማየሁ ያሉ ምሑራን ብጎተጉቱም የሰማቸው የለም።ይልቁንም የጥላቸው ዘመቻ ንጉሡ አፍሪካ ላይ የነበራቸውን የቅኝ ግዛት አንዳስጣሏቸው ያሰቡ ቅኝ ገዢ መንግሥታት ጭምር የተደገፈ ስለነበር አና ሕዝቡም ንጉሡ የሁሉ ችግር መነሻ ተደርገው ስለተነገሩት አና ይህንኑ በየዋህነት የተቀበሉ የጦር መኮንኖች ሳይቀሩ ንጉሱን በቭኦልስዋገን መኪና ከቤተመንግስት ወደ አራተኛ ክፍለጦር ይዞ መሄድ አንደትልቅ ጀብዱ ቆጠሩት።በወቅቱ የነበረው ወጣትም የኢትዮጵያ ችግር ሁሉ የሚወገድ መስሎት ጨፈረ።


ዛሬም ያለንበት ጊዜ ተመሳሳይ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይን በኢትዮጵያ ላይ የጥቅም ፍላጎት ያላቸው ኃይላኑ መንግሥታት በመጀመርያ የስልጣን ዘመናቸው አካባቢ በጣም አሞገሷቸው።በማሞገስ ብቻ አልቆሙም የኖቤል ተሸላሚ መሆናቸውን አድንቀው ፃፉ።የኢትዮጵያ ሕዝብም ከፍተኛ ድጋፉን ገለፀ።በመቀጠል ችግሮች ሲፈጠሩ የችግሮቹ ሁሉ ምንጭ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ናቸው የሚል የሞኛሞኝ ሃሳብ በበታኝ ኃይሎች መስተጋባት ጀመረ።ይህንኑ ሃሳብ የሚቀምር አራሱን የቻለ ቡድን ከህወሓት አስቀ ኦነግ አና በአማራ ስም ከሚነግዱ አክራሪ ቡድኖች አስከ ባህር ማዶ የደህንነት ቡድኖች በአንድነት አየተገመደ ለፕሮፓጋንዳነት ዋለ።አዚህ ላይ ብዙ ሰበብ መስጠት ይቻል ይሆናል። በኢትዮጵያ የተፈፀሙት ግድያዎች፣ስደቶች አና የንብረት መውደም ምንም አንኩዋን አያንዳንዱን ጉዳይ በዝርዝር መመርመር ቢያስፈልግም መንግስትን አይመለከተውም አያልኩ  አይደለም።ነገር ግን አያነሳሁ ያለሁት በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ችግሮች ሁሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ናቸው የሚል የጅላጅል ሃሳብ በአእምሯቸው ለምመላለስ አና ይህንኑ አንደመፍትሄ ለሚመስላቸው ዜጎች ቆም ብለው አንድያስቡ ደጋግሜ አየነገርኩ ነው።


አዎን! ጧት ማታ ዓቢይ! ዓቢይ! የሚል ንግግሮች በአያንዳንዱ የኢትዮጵያ ችግሮች ላይ የሚነገሩት ሆን ተብሎ አና የተለመደ የስነልቦና ዘመቻ መሆኑን ልብ ማለት ይገባል።ለምሳሌ የህወሃቱ ጌታቸው ረዳ አና በኢትዮጵያ ጥቅም ላይ የቆሙ ከባአዳን ድርጎ የምላክላቸው ዩቱበሮች ስንት ጊዜ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ስም አንደሚጠሩ ቁጠሩት።ይህ በአጋጣሚ የሚመስለው ካለ ተሞኝቷል።በስነ ልቦና አማካሪዎች የተጠና አና ችግሩን በዋናነት የጥፋት አጀንዳቸውን ለማስፈፀም አላስቻለኝም ያሉትን መሪ ስም ደጋግሞ በጥላቻ በመጥራት ከህዝብ መነጠል አና ሕዝብ የችግሩ ሁሉ ምንጭ መሪው ነው ብሎ አንድያምን አና በርሱ ላይ አንድነሳ ለማድረግ የሚሞከር ሙከራ ነው።በቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ላይ አና በኮ/ል መንግስቱ ላይ የተፈፀመው ይሄው ነው።የኢትዮጵያ ችግር መውጫ ሌላ መንገድ ምሑራኑ አንዳይፈልጉ በጭፍን ፕሮፓጋንዳ የኢትዮጵያ ችግር የሚወገደው ንጉሡ አና ኮለኔሉ ሲወገዱ ነው የሚለውን የጅል ሃሳብ አብረው አቅደው ሲያስፈፅሙ የነበሩትን ባለስላጣናት ሁሉ አታለሉበት።አንድ ሀገር ምንም ልምድ የሌላው መሪ ይዛ ችግር ለመፍታት ከምትሞክር በአንድሳምንትም ቢሆን በመምራት ልምድ ያለው መሪ የችግሮችን አፈታት አና መጪውን የመረዳት አቅም አለው።


ስለሆነም ዛሬም ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ላይ የሚከፈቱ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎች ግብ ሕዝብ የችግሩ ብቸኛ መፍትሄ የአርሱ አለመኖር አንድመስል አና በኃላ ኢትዮጵያውያን መሪ በድንገት አጥተው በሚያደርጉት ሹክቻ የባአዳን አራት ለማድረግ የታሪካዊ ጠላቶቿ ዋና ግብ ነው።ልብ ያለው ልብ ይበል።መሪ ሲሳሳት ባለበት ለማረም አና ሲወርድም በሥርዓት አና በሕግ ይህም በምትፈልገው ጊዜ መጥቶ የሚያማክርበት አመቺ ሁኔታ ተፈጥሮ አንጂ በማጥላላት አና በመገፍጠር ኢትዮጵያን አናጠፋ ይሆናል አንጂ ያለፈውን ስህተቶች አያርምም።አዚህ ላይ መሪዎች የማይወቀሱ፣የማይቀሰሱ ናቸው የሚል መልአክት አያስተላለፍቁ አይደለም።ለአዚህ ሕዝቡም ምድያዎችም መሞገት አለባቸው።ነገር ግን ለሀገር ያላቸውን የመሪነት ሚና አና የሰብአዊ መብታቸውን በሚያጥላላ ደረጃ መሄድ ከራስ አልፎ መጪውን ትውልድ መበከል ነው።መሪዎችን ኢላማ አድርጎ የችግሮች ሁሉ ምክንያትም መፍትሄም አድርጎ ማቅረብ ግን ታሪካዊ ስህተት ነው።



ማክበር የሚገባንን የያዝነውን የፖለቲካ አቅጣጫ ምሕዋር አለመልቀቅ 


መንግስት አንዴት ይመሰረታል? የሚለው ጥያቄ ሁሌ ሊያቀራክሬን አይገባም።መንግስት ወደ ቤተመንግስት የሚገባው ወደፊትም መቀጠል ያለበት መንገድ ለጊዜው አንድ መሆኑን በትክክል ማመን ይገባል።ችግር በተፈጠረ ቁጥር ትንንሽ ዘውድ መድፋት የሚፈልግ ሁሉ አንዴ በክላሽ ሌላ ጊዜ የራስን ስም ለማግነን በመዋተት የኢትዮጵያን ሕዝብ መከራ የሚያሳዩት ስልጣን ከምርጫ ውጪ ሊገኝ ይችላል በሚል ነው።የያዝነው የፖለቲካ አቅጣጫ አና ምሕዋሩ ስልጣን በምርጫ የሚለው ነው።ይህንን ማዳበር አና ወደ የበለጠ ጥራት ያለው የምርጫ ሂደት ለማሳደግ ሁልጊዜም መስራት ይገባል።ለአዚህ ደግሞ የሚድያው፣የሕግ አውጪው አና ሕግ አስፈፃሚው አንዲሁም የሁሉም ዜጋ ጥረት ይጠይቃል።ስለሆነም ህዝብም አቅጩን መንገር ያለበት ከምርጫ ውጪ የስልጣን መንገድ የለም ነው።ያለው መንግስት ያልተስማማው በመጪው ምርጫ ላይ ለመስራት ይነሳ።ከአዚህ በተለየ ሌላው መንገድ ዝግ በምሆኑን ደጋግሞ መንገር አና ማሳየት በራሱ የብዙ ሰላም ምንጭ ነው።



የምጣኔ ሀብት አድገት ለማምጣት የሚደርገው ጥረትን ወደ መስዋአትነት ደረጃ ማስመንደግ 


ሀገር የሚያፈርሰው የፖለቲካ ስርዓት መፈረካከስ ብቻ አይደለም።የምጣኔ ሃብቱ አለመስተካከል አና ቀጣይነት አና ተከታታይ ትውልድን የሚያሳትፍ የአድገት ሂደት ላይ አለመገኘት በራሱ ሀገር ያፈርሳል።በድህነት ውስጥ የሚዳክር ተከታታይ ትውልድ ለባአዳን ባርነት የመሰጠቱ አደጋ የበዛ ነው።ቀጣይነት አና ተከታታይ አድገት ሲኖር የትውልዱ ተስፋ ይለመልማል።በሀገሩ ላይ ያለው ተስፋም ከፍ ያለ ስለሚሆን ለበለጠ ፈጠራ ይነሳሳል።በመሆኑም የምጣኔ ሀብት አድገት ለማምጣት የሚደረገው ጥረት የህልውናችን አንዱ አካል መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል።ህልውና መሆኑን ከተረዳን የህልውና ጉዳይ በተራ ጥረት አና ያዝ ለቀቅ በሚደረግ ሥራ ለውጥ ማምጣት አይቻልም ማለት ነው።

ለማጠቃለል፣ኢትዮጵያን ውጤታማ ወደሆነ የእድገት ደረጃ ለማሸጋገር በትክክል የሚቻልበት መስመር ላይ ሆነን በተሳሳቱ አስተሳሰቦች እና ተስፋ መቁረጥ ወደኃላ የመሄድ ምንም ዓይነት ችግር አንዳይገጥም ሁሉም ከተለመደው አና በመንጋ ከሚሄድ እሳቤ መውጣት አስፈላጊ ነው።የመንግስት ስርዓት ትክክለኛውን መስመር አንዳይለቅ ጋዜጠኞች ተግተው መስራት አለባቸው።ይሄውም ችግሮችን ነቅሶ ከመፍትሔ መፈለግ ጋር ለሕዝብ ማድረስ ይገባል።ህዝብም አንደህዝብ በጋራ በውስጡ ልከፋፍሉት የሚሞክሩትን የሚመለሰውን በፍቅር አና በማስተማር፣የማይመለሰውን ደግሞ በሕግ በማረቅ ስራዎች መስራት ያስፈልጋል።ለእዚህም የተለያዩ ማኅበራዊ አደረጃጀቶች፣የህዝብ ንቅናቄዎች እና ግለሰብ ምሑራን ከላይ የተጠቀሱትን አምስት ጉዳዮች ላይ በጋራ መግባባት አና ግንዛቤ አንድኖር ቢሰራ ብዙ ነገሮች ይቀላሉ።ኢትዮጵያም በሚፈለገው መልክ ከምትፈልገው ደረጃ ለመድረስ አጅግ የተቃና ጎዳና ይሆንላታል።

=============///======

Friday, December 16, 2022

ብልጽግና የኢትዮጵያ የነገ ተስፋ የሆኑ ልጆቿን የሚከፋፍል አጀንዳ በአዲስ አበባ እያራመደ ነው።አስገራሚው ነገር የፓርቲው የሌሎች ክልል አባላት ይህንን ሃገር በታኝ አጀንዳውን ለማስቆም ምንም ጥረት ሲያደርጉ አለመታየታቸው ነው።



  • ድርጊቱ ምንም ዓይነት የጎሳ ፖለቲካ ቅብ ለመቀባት ቢሞከር የድርጊቱ ዋና ግብ የኢትዮጵያን መጪ ትውልድ መከፋፈል እና ኢትዮጵያን ማዳከምን መድረሻው ያደረገ የመርዝ ብልቃጥ ነው።
  •  በምድር ላይ ያለ ማንም መንግስት የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማውን የሚገዳደር  የአንድ ክልል ሰንደቅ ዓላማ እና መዝሙር ተማሪዎቹ እየዘመሩ እርስበርሳቸው እንዲከፋፈሉ ሲያደርግ ተሰምቶ አያውቅም።

=========
ጉዳያችን ምጥን
=========

አንድ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ብልጽግን በጎሳ ፖለቲካ የማያምን እንደሆነ ሲናገሩ '' እኛን ብልጽግናዎችን አትከፋፍሉን።እኛ ብልጽግናዎች ከዘር የተከፋፈለ አስተሳሰብ የጸዳን ነን። እኛ የምንሰራው ለአንዲት ኢትዮጵያ ነው።'' ማለታቸውን አስታውሳለሁ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ይበሉ እንጂ በብልጽግና ውስጥ የተሰገሰጉ ህዝብ የሚያውቃቸው ዋልታ ረገጥ የለየላቸው አክራሪ የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች ግን መኖራቸው የአደባባይ ምስጢር።ይህም በመሆኑ ዛሬ ላይ ኦሮምያን እንደ አንድ ሃገር የምትመስላቸው ለሕግም ለሕዝብም የማይገዙ ጡቷን አጥብታ ያሳደገቻቸው ኢትዮጵያ ነገ ልጆቿ በአንድነት እና በፍቅር ተምረው አድገው እኩል ብሔራዊ ስሜት እንዳይኖራቸው ለማድረግ እንቅልፍ ያጡ ፖለቲከኞች የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ''እኛን አትከፋፍሉን በጎሳ አናስብም '' ካሉት ከብልጽግና ውስጥ ነው።

ሰሞኑን የብልጽግና ኦሮምያ ክልል ተወካዮች በየትኛውም የሕግ አግባብ የሌለ እና የኢትዮጵያ የነገ ተስፋ ልጆች ነገ አድገው እንዳይግባቡ ለማድረግ ከፋፋይ ዘመቻ በይፋ ተከፍቶባቸዋል። በየትኛውም የዓለም ክፍል የሌለ በአንድ ትምሕርት ቤት ውስጥ ሁለት መዝሙር እና ሁለት ሰንደቅ ዓላማ ለመስቀል ከራሱ ከብልጽግና የተወከሉ የአዲስ አበባ ባለስልጣናት ካለምንም እፍረት በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን እና ፋና ብሮድካስት እየቀረቡ ይህንን የመከፋፈል አጀንዳ ሲመጻደቁበት መታየታቸው ነው።

በአዲስ አበባ ትምሕርት ቤቶች የኦሮምያ ክልል ዓርማ  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ በሚገዳደር መልኩ እንዲሰቅል፣የክልሉ መዝሙርም የሃገሪቱን ብሔራዊ መዝሙር በሚጋፋ መልኩ እንዲዘመር የአዲስ አበባ ክልል አስተዳደር ባለስልጣናት የጀመሩት ተግባር የኢትዮጵያን መጪ ትውልድ ለመበተን ያለመ እና የባዕዳን ተልዕኮ ያለበት ነው።ምንም ዓይነት የጎሳ ፖለቲካ ቅብ ለመቀባት ቢሞከር የድርጊቱ ዋና ግብ የኢትዮጵያን መጪ ትውልድ መከፋፈል እና ኢትዮጵያን ማዳከም ነው።ይህ ምንም ዓይነት ምርምር የማይጠይቅ ግልጽ እና ጥርት ያለ ጉዳይ ነው። በምድር ላይ ያለ ማንም መንግስት የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማውን የሚገዳደር  የአንድ ክልል ሰንደቅ ዓላማ እና መዝሙር ተማሪዎቹ እየዘመሩ እርስበርሳቸው እንዲከፋፈሉ ሲያደርግ ተሰምቶ አያውቅም።

የኢትዮጵያ ሕዝብ የቱ ጉዳይ ምን ያህል እርቀት ሃገር እንደሚበትን፣የትኛው በትዕግስት ቢታለፍ ለጊዜው ችግር እንደሌለው ጠንቅቆ እና ልቅም አድርጎ ያውቃል።የቱ ጋር መሞት እንዳለበት የቱን በትዕግስት ማለፍ እንዳለበት ይረዳል። ችግሩ መሪዎቹ ያወቁት ሲመስላቸው አያውቁትም።የተረዱት ሲመስላቸው ሁል ጊዜ እንደ እንግዳ ደራሽ ሲደናገሩ ህዝቡ ቀድሞ ከፊታቸው ይደርሳል። በሰሞኑ የአዲስ አበባ ተማሪዎች የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማን እና መዝሙር በሚጋፋ መልኩ የኦሮምያ ክልል መዝሙር እና ዓርማ እንዲዘመር እና እንዲሰቀል የሚወተውቱት ባለስልጣናት በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን እና በፋና እየቀረቡ የሚናገሩት አሳፋሪ፣አንድ ፊደል ቆጥርያለሁ ኢትዮጵያ ጡቷን አጥብታ አሳድጋኛለች ብሎ የሚያስብ ዜጋ የማይናገረው ኃላፊነት የማይሰማው ንግግር ነው።

በመጀመርያ ከከንቲባ አዳነች ጀምሮ ምክትል ከንቲባው አቶ ዣንጥራር እና የአዲስ አበባ ክልል አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ ከንቲባዋ ሕዝብ ሲያወያዩ የተናገሩት አቶ ዣንጥራር በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ታኅሳስ 6/2015 ዓም የተናገሩት እና ታኅሳስ 7/2015 ዓም አቶ ሳምሶን መለሰ ደግሞ በፋና ቴሌቭዥን ቀርበው ሲናገሩ ጉዳዩን የአዲስ አበባ ህዝብ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ኦሮምኛ የሆኑ ኢትዮጵያውያን በቋንቋቸው እንዳይማሩ ከመፈለጉ አስመስሎ ለማቅረብ ብዙ ሲጋጋጡ ማየት እራሱን የቻለ ድራማ ነው። ይህ በራሱ የተቀመጡበትን የሕዝብ ወንበር ክብር አለመስጠት ነው። አቶ ሳምሶን ፋና ቴሌቭዥን ላይ ጋዜጠኛ ዳዊት መስፍን ደጋግሞ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ላይ አይደለም ጥያቄው እያለው መልሶ ወ/ሮ አዳነች እና አቶ ዣንጥራር ሲሉት የነበረውን ስለአፍ መፍቻ ቋንቋ ለማስረዳት በመሞከር ዋናውን ጥያቄ ለማለፍ የሞከረው ሙከራ አስቂኝ ነበር።ጋዜጠኛ ዳዊት ግን አልለቀቀውም ደጋግሞ ወደ ዋናዋ ጥያቄ ''በአዲስ አበባ የኦሮምያ ዓርማ እና የክልል መዝሙር ከብሔራዊ መዝሙር ጋር እንዲዘመር የሚያዝ የሕግ አግባብ አለ ወይ?'' በማለት ጠየቀ።

የእዚህን የጉዳያችን ምጥን የማጠቃልለው ድርጊቱ ምን ያህል የኢትዮጵያን መጪ ትውልድ ለመከፋፈል የታለመ የባዕዳን እጅ እንዳለበት የሚያመለክተውን መልዕክት ከላይ በፋና ቴሌቭዥን ዓርብ ታኅሳስ 7/2015 ዓም አቶ ሳምሶን መለሰ በግልጽ አስቀምጠውታል። በእዚሁ ቃለ ምልልስ ላይ ጋዜጠኛ ዳዊት ጠየቀ -
''የኦሮምያ ዓርማ እንዲሰቀል ያደረግነው እና የክልሉ መዝሙር እንዲዘመር የተደረገው ኦሮምኛ የሚማሩ ልጆች ስላሉ ነው ብለዋል።አዲስ አበባ ደግሞ ብዙ ብሔሮች አሉ እና ነገ ሌሎቹ ኢዲስ አበባ በቋንቋቸው ሲማሩ እነርሱም የክልላቸውን ሰንደቅ ዓላማ እንዲሰቀል፣የክልላቸውም መዝሙር እንዲዘመር ታደርጋላችሁ?''

አቶ ሳምሶን የአዲስ አበባ ትምሕርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሲመልሱ ''አዎን እናደርጋለን '' ነበር ያሉት።

ይህ ምላሽ በራሱ የሚገልጸው የኦሮምያ ክልል መዝሙር፣ዓርማ የተባለው ሁሉ ግቡ የኢትዮጵያን መጪ ትውልድ ዋና እምብርት የሆኑትን ትምሕርትቤቶች ማዕከል አድርጎ ኢትዮጵያዊ ብሔራዊ ስሜትን ማጥፋት እና መከፋፈል ነው።ይህ ደግሞ እየተሰራ ያለው በብልጽግና ውስጥ ከፍተኛ ባለስልጣናት በብሔር ከተደራጁ የጽንፍ ኃይሎች ጋር እጅና ጓንት ፈጥረው እያራገቡት ያለው አጀንዳነው።ብልጽግና የኢትዮጵያ የነገ ተስፋ የሆኑ ልጆቿን የሚከፋፍል አጀንዳ በአዲስ አበባ እያራመደ ነው።አስገራሚው ነገር የፓርቲው የሌሎች ክልል አባላት ይህንን ሃገር በታኝ አጀንዳውን ለማስቆም ምንም ጥረት ሲያደርጉ አለመታየታቸው ነው።

==========////==========

ይሄንን በልጅነቱ በኢትዮጵያ ፍቅር የተቃጠለ ትውልድ ለመበተን ነው ዓላማው።
የዜግነት ክብር!



Monday, December 12, 2022

ህወሓት ቀርጾ የሰጠውን የኦሮምያ ክልል ዓርማ እና ደርሶ የሰጠውን መዝሙር ከልሉ ውጭ በአዲስ አበባም ካልዘመርኩ ማለት የጽንፈኝነት የመጨረሻው ጥግ ነው።የአዲስ አበባ ህዝብ ኢትዮጵያውያን በፈቃዳቸው ኦሮምኛ አይማሩ አላለም።ይህንን በሃሰት የሚያራግቡ አመራሮች ቆም ብለው ማሰብ አለባቸው።



  • አዲስ አበባ ከኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ጎን የአፍሪካ ሕብረት ሰንደቅ ዓላማ ብትሰቅል ይመጥናታል።
  • አሁን በአዲስ አበባ የኦሮምያ ሰንደቅ ዓላማ እና የክልሉን መዝሙር በተመለከተ ያሉት አራት እውነታዎች 
  • የኦሮምያ ክልል ህዝብ በጊዜ መንቃት አለበት።
  • መንግስት ማድረግ የሚገባው 
==========
ጉዳያችን ምጥን
==========
ዛሬ ታህሳስ 3፣2015 ዓም በአዲስ አበባ ሽሮሜዳ አካባቢ በሚገኘው እንጦጦ አምባ ትምህርት ቤት  እና የአየርጤና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የኦሮሚያ ክልል ዓርማ እና መዝሙር ተማሪዎች በግዳጅ እንዲዘምሩ በተደረገ ሙከራ ሳብያ ድጋሚ ተቃውሞ ተነስቷል::አዲስ አበባ የሁሉም ብሔሮች መኖርያ ሆና ሳለ የአንድ ክልል ዓርማ ይሰቀል የሚሉ በፌደራል አስተዳደር ስር የተሸሸጉ የፅንፈኛ ቡድኖች ዋና አቀንቃኞች ናቸው::በዛሬው ውሎ ከሽሮሜዳ ወደ አሜሪካ ኤምባሲና ወደ ጉስቋም ማርያም የሚወስደው መንገድ ለተወሰነ ጊዜ ዝግ ነበር::እዚህ ላይ ማወቅ የሚገባን ጉዳይ በኃይል ለመጫን የሚሞከር ማናቸውም ዓይነት ባሕል እና አመለካከት የበለጠ በህዝብ እየተጠላ ይመጣል::ይህ የታሪክ ሀቅ ነው::አሁን ይዘመር እየተባለ ያለው የኦሮምያ ክልል መዝሙር በህወሓት ተደርሶ ለኦሮምያ ክልል የተሰጠ ሲሆን መዝሙሩ በይዘቱ ከፋፋይና የቂም ቃላትን የያዘ ነው::የመዝሙሩ ይዘት ምንም ይሁን ምን፣አዲስ አበባ እንደ አንድ በህገ መንግስቱ እንደተመሰረተ ክልል የራሷ የሆነ የውስጥ መተዳደርያ ደንብ ሊኖራት ይገባል።ይህ መብት የክልል የመስፋፋት ፖሊሲ የያዙ የጽንፍ ኃይሎች እንደፈለጉ ከሕግ ውጭ እንዲፈነጩ አረንጓዴ መበራት እያሳዩ ያሉት አሁንም በስልጣልን ላይ ያሉት የቀድሞ ኦህዴድ እና ዘግይተው የተቀላቀሉት የኦነግ የጽንፍ አራማጆች ናቸው።

ዛሬ በአንዳንድ የአዲስ አበባ አንዳንድ ትምሕርትቤቶች የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማም ሆነ የኦሮምያ ዓርማ ሳይሰቀል ትምሕርቱ የተካሔደባቸው አካባቢዎች አሉ:: የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ሳይሰቀል በትምህርትቤቶች ሳይሰቀል ትምሕርት ማስተማር በራሱ የመንግስት ብቻ ሳይሆን የሀገር የአንድነት ዓርማ ከተማሪዎች አዕምሮ በማራቅ የማድረግ ሙከራ ብቻ ሳይሆን የሕገመንግስት ጥሰት ነው።የመንግስት ህልውና መገለጫው የሰንደቅ ዓላማ በሚገባው የመንግስት ተቋማት ትምሕርትቤቶች ጨምሮ በሥነስርዓት መሰቀሉ አንዱ እና ዋነኛው ነው።

አሁን በአዲስ አበባ የኦሮምያ ሰንደቅ ዓላማ እና የክልሉን መዝሙር በተመለከተ ያሉት አራት እውነታዎች 
  • በእዚህ ጊዜ አጀንዳው የተነሳበት ምክንያት በኦሮምያት ክልል ውስጥ በጽንፈኛው የኦነግ ሸኔ የቀረውን የክልሉን የኦሮምኛ ተናጋሪ አንዱን የኦህዴድ ሌላውን የሸዋ ኦሮሞ እያለ እየከፋፈለ ስለሆነ በእዚህ ሳብያ በተነሳው የክልሉ የውስጥ ውጥረት እንደ ማብረጃ ተደርጎ ተወስዷል።
  • በእዚሁ የመከፋፈል አጀንዳ ላይ የጋራ የክልሉ አጀንዳ በመፍጠር የውስጥ አንድነት ያመጣል በሚል ይህ የባንዲራ ጉዳይ ተፈልጓል።
  • በኦሮምያ ክልል እና በአዲስ አበባ አስተዳደር ውስጥ እና በአዲስ አበባ ዙርያ ጋር በተቀናጀ የተፈጸሙ ዘግናኝ የሙስና ዘራፊዎች በሰሞኑ የመንግስት እንቅስቃሴ ሊመቱ እንደሆነ ስላወቁ ይህንን የባንዲራ አጀንዳ ማንሳት እና ክልሉ እንዳይረጋጋ እና ቀጥሎም መንግስትን ማዋከብ ተፈልጓል።
  • በእዚህ ሁሉ እንቅስቃሴ ላይ ከውስጥ ሆነው በአዲስ አበባ አስተዳደር ውስጥ በክፍተኛ አመራር ላይ ያሉ ከጽንፈኞቹ ጋር የሚሰሩ አሉ።እነኝህ ከሁሉም ገለልተኛ መስለው ሁሉንም እየወቀሱ ግን የጽንፍ ኃይሉን የሚደግፉት አጀንዳውን በይበልጥ ከመንግስት ወገን ሆነው በማራገብ ነው።
የኦሮምያ ክልል ህዝብ በጊዜ መንቃት አለበት።
  • አሁን በትምሕርትቤቶች ውስጥ ህጻናቱን ኦሮሞ የሆነ እና ያልሆነ የሚል ክፍፍል ለመፍጣር በንጹሃን አዕምሮ ላይ ወንጀል መስራት ተጀምሯል።ይህንን የኦሮሞ ህዝብ በስሙ የሚደረገውን ንግድ ሊቃወመው ይገባል።
  • የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የጸናችው በእነ ጀነራል ጃጋማ ኬሎ፣ ኮሎኔል አብዲሳ አጋ እና በሌሎች ሚልዮኖች የኦሮሞ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ነው።ዛሬ ከህወሃት የተሰጣቸውን ዓርማ እና መዝሙር ይዘው አዲስ አበባ ላይ ህዝብ ለመከፋፈል የሚነሱ የጽንፍ ኃይሎችን መቃወም ከኦሮምኛ ተናጋሪው ኢትዮጵያዊ ይጠበቃል።
መንግስት ማድረግ የሚገባው 
  • ፌድራል መንግስት ላይ ተቀምጠው እንደኦሮምያ ክልል አስተዳደር ኢትዮጵያን ለማስተዳደር የሚሞክሩትን በጊዜ አደብ ማስገዛት አለበት።እነኝህ ናቸው የአዲስ አበባ ህዝብ ጥላቻ ስላለበት ነው የሚል የተሳሳቱ ቃላትን በመግለጫዎቻቸው ላይ እየሰነቀሩ ጉዳዩን ሌላ ቅርጽ እንዲይዝ የሚያደርጉት። የአዲስ አበባ ህዝብም ሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ ኢትዮጵያዊ የሆነ የማንም ክልል ቋንቋ ማንም በፍላጎቱ አይማር የሚል ቅሬታ የለውም። 
  • አዲስ አበባ በተለየ መልኩ የሁሉም ክልል መኖርያ መሆኗን የኦሮምያ ክልል የጽንፍ ኃይሎች እንዲያውቁ ለመጨረሻ ጊዜ ማሳወቅ ብቻ ሳይሆን ህገመንግስቱ በሚያዘው መሰረት አዲስ አበባን መብቷን ሊያከብርላት ይገባል።አዲስ አበባ ከኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ጎን የአፍሪካ ሕብረት ሰንደቅ ዓላማ ብትሰቅል ይመጥናታል።
  • በሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች በአዲስ አበባም የሰንደቅ ዓላማ አሰቃቀል ሥነ ስርዓት በተለይ በትምህርት ቤቶች በሚገባ እንዲተገበር ልዩ የቁጥጥር ሥርዓት ማውጣት አለበት። ዛሬ በአዲስ አበባ ከእዚህ በፊት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ይሰቅሉ የነበሩ ሁሉ ከጭቅጭቅ በሚል ያልሰቀሉ መኖራቸው ተሰምቷል። ይህ የመንግስት የመኖር እና አለመኖር መገለጫ አንዱ ማሳያ ነው። በሃገሪቱ ዋና ከተማ የሃገሩ ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማን በአግባቡ ማሰቀል ያልቻለ መንግስት ማለት ትርጉሙ ብዙ ነው።
ለማጠቃለል የሰንደቅ ዓላማ ጉዳይ ከኦሮምያ ክልል አርማ እና ህወሓት ቀርጾ የሰጠውን የኦሮምያ ክልል ዓርማ እና ደርሶ የሰጠውን  መዝሙር ከልሉ ውጭ በአዲስ አበባም ካልዘመርኩ ማለት የጽንፈኝነት የመጨረሻው ጥግ ነው።የአዲስ አበባ ህዝብ ኢትዮጵያውያን በፈቃዳቸው ኦሮምኛ አይማሩ አላለም።ይህንን በሃሰት የሚያራግቡ አመራሮች ቆም ብለው ማሰብ አለባቸው።እደግመዋለሁ፣በፍላጎቱ ማንም በቋንቋው አይማር በሚል የአዲስ አበባ ሕዝብ አልተቃወመም።አዲስ አበባ የሁሉም ክልሎች መኖርያ ስለሆነች አንድ ክልል ለብቻው ተነጥሎ ዓርማውን በትምሕርትቤቶች መስቀሉ ግን አደጋ አለው ሕገመንግስታዊም አይደለም እያለ ነው።ከጭቅጭቅ በሚል አጓጉል አካሄድ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ያልተሰቀለባቸው ትምሕርት ቤቶችም በፍጥነት ሰንደቅ ዓላማውን መስቀል ሕገመንግስታዊ ግዴታቸው ነው!

Thursday, December 8, 2022

ክቡር ጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ ትናንት በጽሑፍ ዛሬ ደግሞ በቀጥታ ንግግር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያስተላለፉት መልዕክት ፍጹም ኢትዮጵያዊ እና ታሪካዊ መልዕክት የያዘ ነው።በአጽንኦት ማዳመጥ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ፋንታ ነው።


  •  ከሃሰተኛ ዩቱበር ተንታኞች እራስን ለመጠበቅ ከምንጩ አድምጦ በተሰጠን አዕምሮ ተጠቅመን ማገናዘብ፣ ጤናማ አስተሳሰብ ነው።
  • የዛሬውን የንግግራቸው እና የትናንቱን የጽሑፍ መልዕክት፣ ሁለቱንም በቪድዮ እና ኦድዮ ከስር ያገኛሉ።



የትናንቱ የጽሑፍ መልዕክት በንባብ

የቪድዮ ምንጭ = ፋና ብሮድካስት

Tuesday, December 6, 2022

ኢትዮጵያ የጎሳ ፖለቲካን መርዝነት የተረዳ መሪ አላት ወይ? እንደርሱ ችግሩን የተረዱ የመንግስት ባለስልጣናትስ አሉ ወይ? መልሱ አዎን! ነው። መሪዎቿ ከሁሉ በፊት የሰው ህይወት ለመታደግ መንቀሳቀስ አልነበረባቸውም ወይ? አሁንም መልሱ አዎን! ነበረባቸው ነው።ኢትዮጵያውያን! ወቅታዊውን ችግር በቅንጥብጣቢ ጊዜያዊ መፍትሔ አንፈታውም።



ለውስጣዊ የጸጥታ ችግሮቻችን መፍትሔነት ሦስቱ መፈታት ያለባቸው መሰረታዊ ጥያቄዎች።


==========
ጉዳያችን ምጥን
==========
በማንነት ጥቃት ኢትዮጵያውያን ሲገደሉ፣ሲታሰሩና ሲሰደዱ ዓመታት ተቆጠሩ።በተለይ ባለፉት አራት ዓመታት እጅግ ጽንፈኛ እና ዘረኛ አደረጃጀት የነበራቸው እንደ ኦነግ ያሉ አደረጃጀቶች ወደ ሃገር ውስጥ ገብተው በፌድራል እና በተለየ በኦሮምያ ክልል ከልዩ ኃይል አባልና አመራር እስከ የክልሉ ምክርቤት ድረስ ገብተዋል። ይሄው ኃይል የነበረውን የኢትዮጵያን የመጥላት እና በአማራ ላይ የተተረከለትን ትርክት እና እራሱ የፈጠራቸውን ፈጠራዎች ይዞ ትውልድ በክሏል። 

በወለጋ በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ላይ ዘርን መሰረት አድርጎ እየተፈጸመ ያለው የሰሞኑን ጥቃት ከእዚህ በፊት ከነበረው በተለየ የክልሉ ልዩ ኃይል ከእዚህ በፊት በርካታ በደሎችን እና ግድያዎችን ቢፈጽምም እንደ የሰሞኑ ያለ ከሸኔ ጎን ተሰልፎ መንደሮችን እየለየ አብሮ የሚያጠቃ ሆኖ ዓይን ያወጣ ተግባር የለም።አሁን ክልሉ እራሱን መቆጣጠር ያቃተው ልዩ ኃይሉ በራሱ እንደፈለገው የሚሔድ ሆኗል።በሌላ በኩል እራሳቸውን ለመከላከል የተነሱ ሚሊሻዎችም ኢትዮጵያ ሃገራችን ነች መንግስት ካልተከላከለልን እራሳችንን እንከላከላለን ብለው ቢያንስ ቤተሰባቸውን ሊከላከሉ እየታገሉ ነው። በእዚህ ሁሉ መሃል እዚህም እዚያም ክፉ አካሄዶች ይኖራሉ።በምንም መለክያ ግን አማራ በሚል ዘርን በመለየት የተፈጸመውን ያህል ግፍ ግን በሌላው አልታየም።ከአርባጉጉ እስከ ጉርዳፈርዳ፣ከወለጋ እስከ ሻሸመኔ በጥላቻ ያልተፈጸመ የግፍ ዓይነት የለም።

የብዙዎች አፍ ማሟሻ በተለይ የወለጋው ዓይነት ችግር ሲፈጠር በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የስድብ ውርጅብኝ ማውረድ ነው።አንዳንዶች ደግሞ መንግስት ቢቀየር መፍትሔ የሚመጣ፣አብዮት ቢካሄድ ኢትዮጵያ የምትቀየር ወይንም የእኛ ትውልድ ሰፈር ሰው አራት ኪሎ ቢገባ መፍትሄ የሚገኝ ሁሉ ነገር ጸጥ የሚል ይመስለናል። ይህ ሞኝነት ነው። በ1966 ዓም የኢትዮጵያ አብዮት ይዞት የተነሳው መሰረታዊ የህዝብ ተገቢ ጥያቂዎች ቢኖሩም የመንግስት ስሪቱን በሆይ! ሆይ! እና ድንጋይ በመወርወር ያፈረሱት ዛሬ ድረስ የማይለቀን የሃገር ውርደት አብሮ እንዳመጣ መካድ አይቻልም። ዛሬም የችግሩን ሥር መረዳት እና መፍትሄውም አንዱን ክር ለማሰር ሌላውን መፍታት ዓይነት እንዳይሆን ሁሉን ያማከለ መሆን አለብት። ይህ ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ከማንም የዓለም ክፍል በተለየ የብዙ ችግሮችን የማለፍ እና በይቅርታ መጪውን መሻገር የሚችል ህዝብ ነው።ይህንን ሌላ እማኝ መጥራት አያስፈልግም የሰሜኑ ጦርነት ቆመ ሲባል ህዝብ የቂም በትሩን ሳይመዝ ወደ ቀሪ ህይወቱ ሄደ እንጂ እንዲህ ሆኜ እንዲያ ተደርጎ በሚል ክርክር ውስጥ አልገባም። ይህ ትልቁ ግን ያላደነቅነው ዕሴታችን ነው። ስለሆነም ዛሬም ይህንን ችግር የመፍታቱ ክህሎት እኛው ጋር አለ።

ወደ አንዱ መገለጫ እና የብዙ ንጹሃን ኢትዮጵያውያን በተለይ የአማራ ተወላጅ በሚል የተገደሉበት፣የተዘረፉበት እና የተሰደዱበት የወለጋው ጉዳይ ስንመጣ ኦነግ ሸኔ የብሔር ጥያቄውን ወደ የመሬት ጥያቄ በማውረድ የኦሮሞ ህዝብ እና የአማራ ህዝብን ለማጋጨት የሞከረበት ሙከራ ሰሞኑን ወደ አደገኛ ደረጃ እየተቀየረ ነው።ወለጋ የኦሮሞ መሬት ብቻ ጎጃም የአማራ መሬት ብቻ ወይንም ጅጅጋ የሱማሌ ብቻ የሚለው አስተሳሰብ መሰረታዊ የአስተሳሰብ ችግር ብቻ ሳይሆን የህወሃት/ኢህአዴግ የተከለው መርዝ ነው። መርዙ አለ።ልንክደው አንችልም።የሰዎች አስተሳሰብ ቀይሯል።ይህንንም መሬት ላይ ያለ ሃቅ ነው አንክደውም። መፍትሔዎቹ በአጭር ጊዜ ቆራጥ አቋም የሚፈልጉ እና በረጅም ጊዜ የሚሰሩ ሥራዎች ይፈልጋል።

ኢትዮጵያውያን! ወቅታዊውን ችግር በቅንጥብጣቢ ጊዜያዊ መፍትሔ አንፈታውም። 

ቅንጥብጣቢ ጊዜያዊ መፍትሔዎች ችግሩን አይፈቱትም።የፖለቲካ አደረጃጀቶች እና ክልሎች በህዝቡ ስም በሚያደርጉት ጊዜያዊ ስምምነት እና ጎን ለጎን በመቀመጥ በሚደረግ ዲስኩር አይፈታም።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን በወለጋ ጉዳይ ላይ ቸልተኝነት አሳይተዋል የሚሉ የብዙዎች ድምጽ ነው።ይህ ቸልተኝነት የሚገለጸው ችግሮች በተፈጠሩ ጊዜ የሚያሳዩት የምላሽ እና የቁጣ መጠን በሚድያ አልታየም ብቻ ሳይሆን ወዲያው የጦር ኃይል አዝምተው ንጹሃንን ለመታደግ አልቻሉም የሚለው ነው። ይህ ተገቢ ጥያቄ ነው።ማናቸውም ችግር ከመታየቱ በፊት የማይተካው የሰው ህይወት መታደግ ይቀድማል።የጸጥታ ችግር አተናተን እና ቅድምያ ዝግጅት እና ህዝብን የመከላከል ደረጃ መንግስት በኦሮምያ ክልል ያሳየው መዝረክረክ የትም አልታየም።የሻሸመኔን ጥቃት እና የወለጋ የሰሞኑ ሁኔታዎች በቂ ማሳያዎች ናቸው።

ከእዚህ በተለየ ግን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከኦነግ ጋር አንድ አድርገው የሚያዩ ሰዎች ሁሌ የሚረሱት ጉዳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢህአዴግ ስር ሆነው ከኦነግ ጋር የነበረውን የአይጥና ድመት መሳደድ፣በኋላም ይሄው ቡድን በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ከናይሮቢ ድረስ ሰው ልኮ ግድያ መሞከሩን እና ወለጋ ላይም የጠቅላይ ሚኒስትሩን ህይወት ለመቅጠፍ ተደጋጋሚ ሙከራ ማድረጉን ይረሱታል።ምክንያታዊ ዕሳቤዎች መልካም ናቸው።አሁን በወለጋ ባለው በሰሞኑ ጉዳይ በኦነግ ሸኔ በኩል በዋናነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፋኖን እንዳዘመቱ ነው ቅስቀሳ የተያዘው።ሌላው ቀርቶ የጨፌ ኦሮምያ ምክርቤት አባላት ሳይቀሩ በትናንትናው ዕለት በመንግስት ላይ እየዘመቱ የሸኔን ቀጥተኛ አቋም ያንጸባረቁ ለእዚህ ሁሉ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የኦሮሞ ጠላት አድርገው ነው ያቀርቧቸው። 

በመሆኑም ይህንን ችግር በስሜት እና በግርግር የሚፈታ አይደለም።የጉዳዩ ቁልፍ ያለው እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣የኢትዮጵያ ህዝብ እና የመከላከያ ኃይል በቅደም ተከተል መመለስ ያሉባቸው  እና ለመልሱም ሁሉም ሊያግዛቸውም የሚገባው የችግሩ ማጠንጠኛ ቁልፍ የሚሆነው አሁንም በሦስቱ ጥያቄዎች አመላለስ ላይ ነው።ኢነርሱም ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የኢህአዴግ/ህወሃት እና ኦነጋዊ የጎሳ ፖለቲካን እንዴት መንቀል ይችላሉ? ህዝቡስ ይህንን በምን ያህል ደረጃ ለማገዝ ቆርጦ ይነሳል? የሕግ የበላይነት እንዴት ይከበራል? የሚሉት ናቸው።መልሶቹን መስጠት ያለብንም ሁላችንም የሚመለከቱን ጥያቄዎች እንደየደረጃችን እነኝህ ይመስሉኛል።
=================

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...