ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, May 30, 2016

የጀዋራውያን እና ህወሐታውያን በታዳጊ ወጣቶች መንገላታት ትርፍ ለማግኘት የሚጥሩበት የተሳሳተ የትግል ስልት (የጉዳያችን ማስታወሻ)



የኢትዮጵያ ወጣቶች ላለፉት አራት አስር አመታት በላይ የተቀበሉት መከራ ለአእምሮ የሚዘገንን እና ለመጪው ትውልድ ሰቀቀን ነው።በኢትዮጵያ ወጣቶች ላይ የደረሰውን ሁሉ በእዚህ አጭር ማስታወሻ መዘርዘር ከባድ ነው።ሆኖም ግን ከ1966 ዓም ለውጥ ወዲህ ለተፈጠሩት የፖለቲካ ኃይሎች ሰለባ  በመሆን በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ ወጣት ነው።በእየጊዜው የሚነሱት መንግሥታትም ሆኑ በተቃዋሚ አንፃር የሚቆሙት የሰለባቸው መነሻ እና መድረሻ ወጣቱ ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች በቀይ ሽብር እና ነጭ ሽብር፣ በእርስ በርስ ጦርነቶች፣በስደት፣በሥራ አጥነት እና በረሃብ  የተንገላቱባቸው አመታት አንድም በስልጣን ላይ ለነበሩት መንግሥታት የስልጣን ማስጠበቂያ አጥርነት ወይንም በተሳሳተ መንገድ የሚመሩ የስልጣን እና ህዝብን የመከፋፈል አባዜ የተጠናወታቸው ኃይሎች የስልጣን መወጣጫ መሰላልነት ማለቂያ ለሌለው ፈተና የተዳረጉ ናቸው።

ዛሬ ላይ ሆነን የምንረዳው ጉዳይ የኢትዮጵያ ወጣቶች እና ታዳጊ ወጣቶች ያሉበትን ሁኔታ  የአገሪቱ  በመንግሥትነት የተሰየመውን አካልም ሆነ በብሄር ኢትዮጵያዊነትን የሚያጥላላ ፖለቲካ የሚይራምዱ ተቃዋሚዎች ዘንድ ለሌላ የእልቂት ድግስ እየተዘጋጀ መሆኑን ነው።ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በዘመኗ አይታ የማታውቀው ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚያወሩ ነገር ግን የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ በእየማህበራዊ ሚድያው ላይ በእሳት በማንደድ የሚዘባበቱ፣ በተቃዋሚነት የተሰለፉበት ወቅት ላይ እንገናኛለን።በመጀመርያ ደረጃ አንድ ተቃዋሚ የአንድ አገር ፖለቲካን፣ማኅበራዊ ኑሮ እና ምጣኔ ሐብት እኩል ተጠቃሚነት ጉዳይ ሲያነሳ የአገሪቱን ማንነት በሚንድ እና ሰንደቅ አላማዋን ክዶ የእራሱን ሰንደቅ አላማ ሰቅሎ ሊሆን አይችልም።ይህ የባዕዳን ወረራ እኩይ  አቀራረብ ነው።

በእዚህ አይነት ሂደት ላይ የኢትዮጵውያንን ኢትዮጵያዊነት የሚፈታተኑ መንገዶችን የተከተሉ ሁለት፣ሶስት ተብለው የሚቆጠሩ ቢኖሩም ለእዚህ ፅሁፍ ግን በዋናነት  የሚጠቀሱት ሁለት ክፍሎች  አሉ።እነኝህን ክፍሎች በሁለት ስሞች መሰየም እንችላለን። እነርሱም 'ህወሃታውያን' እና 'ጀዋራውያን' በማለት መጥቀስ እንችላለን።

ህወሃታውያን መጀመርያ የተነሱበት እና በመግለጫቸው (ትግራይ ማኔፌስቶ 1968) ላይ እንደተገለፀው የትግሉ ማጠንጠኛ ትግራይን ከኢትዮጵያ የመገንጠል እና የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ገሸሽ አድርጎ ''የትግራይ''ያሉትን ''ሰንደቅ አላማ '' በሕዝቡ ዘንድ ማስረፅ ነበር።ቆይቶ ግን የትግራይም ሆነ የተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ  አባቶቹ እና እናቶቹ ደማቸውን ያፈሰሱለት አጥንታቸውን የከሰከሱለት ሰንደቅ አላማ ጉዳይ ላይ የማይደራደር መሆኑን ሲረዱ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ አብረው ለመያዝ ተገደዱ።አሁን በሂደት በአዲሱ ትውልድ ላይ ለማስረፅ ባለመቻላቸው የአገሪቱ አንደነትን የሚያናጋ ማናቸውንም የጨርቅ አይነት በእየቦታው እያውለበለቡ የኢትዮጵያን መለያ ሰንደቅ አላማ ማኮሰስ ስራዬ ብለው ተያያዙት።

በተመሳሳይ ደረጃ 'ጀዋራውያን' በውስጣቸው ሁለት አይነት ስሜት ያላቸው ኢትዮጵያውያንን ይዘው እየሄዱ እንደሆኑ መረዳት ይቻላል።እነርሱም 

1ኛ የኦሮሞ ሕዝብ የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ድርሻ እኩል ተጠቃሚ መሆን አለበት የሚሉ ለእዚህም የኦሮሞ ባህላዊ እሴቶች በአግባቡ ተጠብቀው ለመጪው ትውልድ የሚተላለፉ እንዲሆኑ እና ለኢትዮጵያ እድገትም በግብአትነት የራሳቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ የሚፈልጉ እና 

2ኛ የኦሮሞ ሕዝብን ጥያቄ ለብቻው ነጥለው በማስኬድ የህዝቡ የመብት ጥያቄ የእራሱ ወጥ አመራር እንዳይኖረው የሚያደርጉ፣ የኦሮሞ ህዝብ የደረሱበትን በደሎች ለስሜት መኮርኮርያ ብቻ ተጠቅመው በሚስጥር የተደራጁበት የፅንፈኛ እስልምና እምነት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ለመጫን የሚሞክሩ፣ ለእዚህም ስኬት የኢትዮጵያ የሆነውን ነገር በሙሉ የቀደመውታርክንም ሆነ የአሁኑን ሰንደቅ አላማዋን ጨምሮ ከትውልዱ አእምሮ ውስጥ ለማስወጣት የሚጥሩ ናቸው።

የመጀመርያው ማለትም ኢትዮጵያዊነትን ከኦሮሞ ትግል ነጥሎ የማይመለከተው ክፍል፣ ፅንፈኛ አስተሳሰብ ለሚያራምደው የጀዋራውያን ክፍልን ከሚጠይቃቸው ጥያቄዎች ውስጥ ''የኢትዮጵያውያን ኦሮሞ ማሕበረሰብ ትግል ኢትዮጵያዊነትን  ለምን አገለለው?   ለምንስ ሌሎች ኢትዮጵያውያንን ለማግለል ወሰነ? የእዚህ ግቡስ ምንድነው? ለምንድነው የኦሮምያ ትግል መሪ ስውር የሆነው? ይህ አካሄድ ፅንፈኛው እስልምና መሰረት እንዲይዝ የተደረገ ስልት አይደለምን? በሚሉ  መሰረታዊ ጥያቄዎችን ይሰነዝራል።  እነኝህ ጥያቄዎች ደግሞ ብዙ ኢትዮጵያውያን የሚያነሷቸው እና የሚሞግቱባቸው  መሰረታዊ የሃሳብ አመክንዮ (logic) ነፀብራቅ ናቸው።

ከላይ ባጭሩ የጀዋራውያን የትግል ስልት ቀደም ብሎ በእራሱ ውስጥ ባለው ሁለት  የአመለካከት ጫፎች የተወጠረ መሆኑን ተመልክተናል።ከላይ በተጠቀሱት ሁለቱም አስተሳሰቦች ለጊዜው በጀዋራውያን ጥቅል ስም ውስጥ ይግቡ እንጂ የኦሮሞ ኢትዮጵያውያን ጥያቄ እና እንቅስቃሴ ከፅንፈኛ እስልምና እንቅስቃሴ የእራሱ የሆነ አመራር የሚወጣበት እና ለኢትዮጵያ ማገር የሆነው የኦሮሞ ማኅበረሰብ የለውጥ ሐዋርያ የሚሆንበት መንገድ መፈለግ  የኢትዮጵያውያን በተለይ ኦርሞኛ ከሚናገረው ኢትዮጵያው ማኅበረሰብ ወደ አደባባይ መውጣት እና ስለ ኢትዮጵያዊነት እና የኦሮሞ ማህበረሰብ እንደ ሌላው ወገኑ የእኩል መጠቀም እና መብት ጥያቄ መጠየቅ ሲችል ነው። 

የኢትዮጵያ ወጣቶች ቀደም ባሉት አመታት የደረሰባቸው መከራ አልበቃ ብሎ  አሁን በአዲስ መልክ ሌላ የእልቂት እና የስደት ምዕራፍ  ላይ መሆናቸው ይታወቃል። በቅርቡ በኦሮምያ የተነሳው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ መብታቸውን በጠየቁ ወጣቶች ላይ የህወሓት አጋዚ ሰራዊት ከ400 በላይ የሚሆኑ ወጣቶች እና ታዳጊ ወጣቶችን መግደሉ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የልብ ድማት ነው።በእዚህ እንቅስቃሴ ላይ በተለይ  በቤታቸው የእናት አባቶቻቸው የስቃይ ድምፅ ያንገፈገፋቸው ታዳጊ ወጣቶች ያደረጉት እንቅስቃሴ ቀላል የሚባል አይደለም።በእዚህ እንቅስቃሴ ላይ ጀዋራውያን  ከበሰሉት ወጣቶች ይልቅ በ15 እና ከእዛ በታች  የሆናቸው የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ታዳጊ ወጣቶችን ከታንክ እና ወታደራዊ ጅፖች ፊት ባዶ እጃቸውን እንዲሰለፉ በመገፋፋት ያደረጉት ግፊት  እና በምላሹ ሕወሃታውያን በጭካኔ የወሰዱት እርምጃ  ለኢትዮጵያ ወጣት ሌላ አሳዛኝ የመከራ ገፈትን እንዲቀምስ አድርጎታል።ከግድያ የተረፉት በግብፅ እና ሱማልያ በረሃ እንዲሁም በሜዴትራንያን ባህር ለሞት መዳረጋቸው ይታወቃል።

ይህ ብቻ አይደለም የኢትዮጵያን ወጣቶች መከራ በጀዋራውያንም ሆነ በሕወሃታውያን የማያባራ ፈተና ውስጥ  መሄዱ ቀጥሏል።ከግድያው፣እስራቱ እና ስደቱ ተርፎ ሌት ተቀን በብዙ ፈተናዎች ውስጥ አልፎ ለከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከዛሬ ግንቦት 22 እስከ ግንቦት 26/2008 ዓም ለመውሰድ ይዘጋጁ የነበሩ ከ200 ሺህ በላይ ወጣቶች በመላው አገሪቱ 800 በሚሆኑ የፈተና ጣቢያዎች ውስጥ ፈተና እንደጀመሩ ፈተናው ተሰርቆ በመውጣቱ ሳቢያ ፈተናው መሰረዙ ተነግሯቸዋል።ድርጊቱ ትውልዱን በእጅጉ የሚጎዳ ነው።

በእርግጥ ከእዚህ ጋር ተያይዞ የተነሱ ጥያቄዎችበማህበራዊ ሚድያ መንፀባረቁ ይታወቃል።ይሄውም አንዳንድ የጀዋራውያን ማህበራዊ ሚድያዎች ፈተናው መዘግየት አለበት ለፈተና ያልተዘጋጁ ተማሪዎች በተለይ በኦሮምያ ክልል  ለአምስት ወራት አልተማሩምና የሚል ሃሳቦች ተንሸራሽረዋል። ይህ በግልጥ (ኦፊሻል በሆነ መንገድ) ከመግለጥ ይልቅ አሁንም በማህበራዊ ሚድያ በድርጅት መልክ ሳይሆን በግለሰቦች ደረጃ ተሰምቷል።ቀደም ብዬ የጠቀስኩት የኦሮሞ ኢትዮጵያውያን ትግል ኢትዮጵያዊ መልክ እና የታወቀ አመራር እንዳይኖር የመደረጉ ሁኔታ በእራሱ የእዚህ አይነት እንቅስቃሴዎች በማህበራዊ ሚድያ  የተገኙ ከማለት የዘለለ ቅርፅ እና አካል ያለው አደረጃጀት ተከትሎ የሚሰጥ መግለጫ ስለሌለ  አሁንም 'ጀዋራውያን' ከማለት ያለፈ ማብራራት አይቻልም።

ፈተናውን አውጥተን መልሶቹን በትነናል ያሉት የጀዋራውያን ማህበራዊ ሚድያዎችም ሆኑ በኦሮምያ ክልል ላለፉት አምስት ወራት የተረጋጋ የፈተና ሁኔታ አለመኖሩን ከግንዛቤ አስገብቶ ምንም አይነት መፍትሄ ያልሰጡት የህወሃታውያን ክፍል፣ ሁለቱም የኢትዮጵያ ታዳጊ ወጣትን ሕይወት ላይ በመረማመድ የተሳሳተ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚጥሩ ናቸው። በዛሬው እለት ጀዋራውያን በማህበራዊ ድረ-ገፅ 'ድል' ማድረጋቸውን የሚገልጥ ፅሁፍ ሲለቁ በርካታ ኢትዮጵያውያን ስልቱ በእራሱ ከባህር ማዶ ተቀምጦ በአገር ቤት ባሉት የእዚህ ትውልድ ፍሬዎች ላይ በሕወሃታውያን የሚደርስባቸው መከራ አልበቃ ብሎ ሌላ የበቀል ውጋት ያህል የተሰነዘረ አድርገው ቆጥረውታል።

ባጠቃላይ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያውነቷን ከማያውቃት ፅንፈኛው የጀዋራውያን አካል በአገር ቤት ባሉ በወጣቶች እንግልት ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት ከሚሞክር አካልም ሆነ ኢትዮጵያን ላለፉት 25 አመታት በጎጥ ፖለቲካ የከፋፈላት የህወሃታውያን አስተሳሰብ እና ድርጊት የኢትዮጵያን ወጣት የማያባራ መከራ ውስጥ ከትቶል።ኢትዮጵያውያን  ለሁሉም ኢትዮጵያ የጋራ ፖለቲካዊ፣ማህበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ተጠቃሚነት በአንድነት እስካልተነሳን እና ለእዚህም እንደ አገር የሚከፋፍሉንን በሕብረት መግራት ካልቻልን የሚከፈለው ዋጋ ከባድ ያደርገዋል።ለእዚህም የኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን ትግል ካለመሪ እንዳይቀር እና ከፅንፈኛ እስልምና አራማጅ ጀዋራውያን እጅ ወጥቶ ለኦሮሞ ማህበረሰብም ሆነ ለመላው ኢትዮጵያውያን መብት ዘብ በቆሙ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ዜጎች እጅ እንዲሆን ማድረግ አስፈላጊ ነው።እዚህ ላይ ፅንፈኛ ጀዋራውያን ጉዳዩን ከኦሮሞ ማኅበረሰብ ጋር ሌላው ማህበረሰብን ለማጋጨት የተጠቀሙበት ይህ ትውልድ ያልኖረበትን ያለፈ ታሪክ መዘዛም ሆነ ህወሃታውያን የእኩል ተጠቃሚነት እና የመብት ጥያቄ የሚያነሳውን ኢትዮጵያዊ የጥይት እራት የሚያደርጉበት እኩይ ተግባር ሁሉ መገታት የሚችለው አሁንም ኢትዮጵያዊነትን ባከበረ ተቃውሞ እንጂ ኢትዮጵያዊነትን ከመሰረቱ በመካድ እና ሰንደቅ አላማዋን በማጣጣል  የባዕዳን ስሜት ያነገበ የፖለቲካ  አካሄድ በሙሉ በፍጥነት አደብ እንዲገዛ መደረግ አለበት። 




ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Friday, May 27, 2016

Tuesday, May 24, 2016

ማኅበራዊ እሴት እንደ አገር እንድንኖር ካደረጉን ነገሮች ውስጥ አንዱ እና ዋነኛ መሆኑን በኦስሎ የተደረገ ስብስባ ላይ ተገለጠ (ጉዳያችን ዜና)

የስብሰባው ማስታወቂያ 

በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ሚያዝያ 29፣2008 ዓም ባባተሪ አዳራሽ በኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ አዘጋጅነት በማኅበራዊ እሴት ላይ ያተኮረ ትምህርታዊ  ውይይት ተደርጎ ነበር።በውይይቱ  ላይ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በኖርዌይ ሰብሳቢ ወ/ሮ ዙፋንን ጨምሮ ሌሎች ምሁራን እና በኦስሎ እና አካባቢው ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል።

የውይይቱ መርሃ ግብር ከመጀመሩ በፊት የመርሃ ግብሩ መሪ የስብሰባው አላማዎች ማህበራዊ እሴት ምንነትን ማሳወቅ፣እንደ ሕብረተሰብ እና እንደ አገር ያለንበትን ደረጃ ማጤን እና ለመፍትሄው ያለንን ድርሻ መለየት መሆኑ ገልጦ ማሕበራዊ እሴት በሰዎች መካከል እና በማህበራዊ ተቋማት መካከል እና ግለሰቦችም ከእነኝህ ማህበራዊ ተቋማት ጋር ያላቸው ግንኙነት ሁሉ መሆኑን እና የእዚህ ሁሉ ትልቁ ዋጋ መተማመን መሆኑን አብራርቷል።

በመቀጠልም  በማኅበራዊ እሴት ዙርያ ፅሁፎችን ይዘው የቀረቡትን ሶስት እንግዶች ወደ መድረኩ ጋብዟል።

ፅሁፎች ይዘው የቀረቡት: 

1ኛ/ ወ/ሮ ዙፋን አማረ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ሊቀመንበር፣ 

2ኛ/ አቶ እንግዳሸት ታደሰ የኖርወጅኛ አማርኛ መዝገበ ቃላት መፅሐፍ አዘጋጅ እና 

3ኛ/ አቶ አጥናፉ ወ/ማርያም በኖርዌይ አገር ከ24 አመታት በላይ በመምህርነት ያገለገሉ እና አሁንም እያገለገሉ ያሉ ናቸው።

በመጀመርያ ፅሁፋቸውን ያቀረቡት ወ/ሮ ዙፋን ሲሆኑ የእርሳቸው ፅሁፍ በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።ይሄውም: 
- ሀብት በእራሱ ሁለት አይነት መሆኑን እርሱም ሙት ሀብት ወይንም ፍሬ የማያፈራ እና ትርፍ የሌለው እና ሕይወት ያለው እና ፍሬ የሚያፈራ መሆኑን፣
- ሕይወት ያለው ወይንም ፍሬ የሚያፈራ ከሚባለው ውስጥ ማሕበራዊ እሴት አንዱ መሆኑን፣
- ማኅበራዊ እሴት ከሌላው የሚለየው የጋራ መሆኑ እንደሆነ፣
- አስፈላጊነቱ ለጋራ መተማመን፣ስነ ምግባር እና ማሕበራዊ ትስስሮች መሆኑን፣
- ማኅበራዊ እሴት የማይዳሰስ ሀብት እና ከተንከባከብነው እየዳበረ የሚሄድ መሆኑን፣
- ማህበራዊ እሴት በጥርጣሬ በተሞላ መንፈስ ለማስኬድ ከተሞከረ ደግሞ እየቀጨጨ የሚሄድ እና በኃላ አገርንም አደጋ ላይ የሚጥል ደረጃ እንደሚያደርስ ገልጠዋል።

በመቀጠል አቶ እንግዳሸት ታደሰ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥተው አብራርተዋል። እነርሱም: 
- ማኅበራዊ ካፒታል ማለት የማኅበረሰብ የባህል ካፒታል (ፋይናንሻል ያልሆነ) ለምሳሌ አመጋገብ፣ትምህርት፣አለባበስ ሁሉ ላይ እንደሚቀለጥ፣
- የቋንቋ አጠቃቀም አስፈላጊነትን በ1916 ዓም ወደ አውሮፓ የሚመጣ ተማሪ ይሰጠው የነበረው ዝርዝር መረጃ አብራርተዋል፣
- የእድር አስፈላጊነት እና በተለይ በውጭ አገር ለሚኖሩ  ኢትዮጵያውያንም ያለውን ፋይዳ ከኦስሎ አንፃር  በማገናዘብ አቅርበዋል፣
- ከሃይማኖት ተቋማት አንፃር እና አሁንም በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተሳትፎ አንፃር በምሳሌ አስረድተዋል።

በመጨረሻም አቶ አጥናፉ ወ/ማርያም በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ማብራርያ ሰጥተዋል።እነርሱም:

- ትምህርት ከማህበራዊ እሴት አንፃር ያለው አስተዋፅኦ፣
- በተለይ ትምህርት ምን ያህል አንድን ማህበረሰብ እንደሚቀይር ሲያስረዱ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ''መጪው የዓለም ዕድል የሚወሰነው  በተማሩ ሰዎች ነው'' የሚለውን አባባል በመጥቀስ ሰፋ ያለ ማብራርያ ሰጥተዋል፣
- ከኖርዌይ የትምህርት ፖሊሲ አንፃር እንዴት አንድ ሕብረተሰብ እንደሚገነባ በዝርዝር ገልፀዋል፣
- ከኖርዌይ ጋር በማነፃፀር በኢትዮጵያ ያለው አምባገነናዊ ስርዓት ምን ያህል በትምህርት ላይ ውድቀት እንዳደረሰ እና  ተከትሎ የመጣው የትውልድ ክስረት ከቀድሞ የመምህራን ማኅበር ትግል ጋር እያነፃፀሩ አብራርተዋል፣
- በምሳሌነት የሂሳብ ትምህርትን አንስተው በኖርዌይ የሂሳብ ትምህርት ለበርካታ ጊዜ መሻሻሉን እና አሁን ሂሳብ ለማህበራዊ ትምህርት፣ሂሳብ ለተፈጥሮ ሳይንስ ወዘተ በሚል መሰጠት መጀመሩን አውስተው የኢትዮጵያ ትምህርት ለዘመናት መሻሻል የሌለው እና በጥናት ላይ የተመሰረተ ሥራ አለመሰራቱ በማህበራዊ እሴት  ላይ ያለውን አሉታዊ ተፅኖ አብራርተዋል።

በመቀጠለም የሻይ እረፍት ከተደረገ በኃላ የጥያቄ እና አስተያየት የመስጠት ጊዜ ተሰጥቶ በቀረቡት ፅሁፎች ላይ ጥያቄ እና አስተያየቶች ተሰጥተዋል።በተሰጡት አስተያየቶች ላይም :

- ማሕበራዊ እሴት ለኢትዮጵያ የመኖር እና አለመኖር ጉዳይ ወሳኝ የመሆኑን ፋይዳ፣
- በቀደመ ታሪካችንም እድር፣እቁብ፣የቤተዘመድ ማህበር፣ የመሳሰሉት ሁሉ ሕዝብ አብሮ እንዲኖር ያደረጉ  የማኅበራዊ ቋማት መሆናቸው እና አሁን ያሉበት ሁኔታ እየመነመነ መሆኑ፣
- ለእዚህም አሁን በስልጣን ላይ ያለው ስርዓት እነኝህ ማሕበራዊ ቋማትን ሆን ብሎ የማዳከም ሥራ እንደሚሰራ እና በምሳሌነትም በእድሮች ላይ ያለው ማዋከብ እና የመቆጣጠር ተግባር ተጠቅሷል፣
- የሃይማኖት ቋማት እውነቱን የመናገር እና ስለ አገር የመጮህ፣ድሃ ተበደለ ፍትህ ጠፋ ብለው የመናገር ድፍረት አስፈላጊነት ተወስቷል።

በመጨረሻም የመድረክ መሪው የማጠቃለያ ሃሳቦች ሰጥቶ በቀጣይ ጊዜ ውይይቱ በስፋት እና በጥልቀት በኢትዮጵያውያን የጋራ መወያያ መድረክ የሚቀርብ መሆኑ ተገልጦ በዕለቱ ለተገኙት እንግዶች እና ተሳታፊዎች ከፍ ያለ ምስጋና ቀርቧል።



ጉዳያችን GUDAYACHN 

 www.gudayachn.com 

Monday, May 23, 2016

አሜሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወደ 18ኛው ክ/ዘመን የኮንሱላር አሰራር ተመለሰ (ጉዳያችን ዜና)


ኤምባሲው ድረ-ገፁ ላይ የለጠፈው 


  • ጉዳዩ አስቂኝም አሳዛኝም ነው።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውጭ አገራት የሚመድባቸው የኤምባሲ ራተኞች መስፈርቶቹ የትምህርት ዝግጅእና ዓለም አቀፍ ተሞክሮ  ይሆን ድሬ መሆን እና ለስርዓቱ ታማኝነት መሆኑ የታወቀ ነው።አንዳንዶቹ ኤምባሲዎች የቤተ መድ መሰብሰብያ መሆናቸው የተነሳ የአንዱ ዘመድ ከሞተ አብዛኛው ሰራተኛ ጥቁር ይለብሳል እየተባሉ ይታማሉ።የኤምባሲ ሰራተኞች ያንስ በዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ርያ በቂ እውቀት  እንዲኖራቸው የስራው ባህሪ ይጠይቃል። ባለፉት 25 ዓመታት ውስጥ ግን የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች የሰው ይል ይዞታ ከትንንሽ የአፍሪካ አገራት አንፃርም ሲታይ በጣም ዝቅተኛ ደረጃ የሚገኝ ነው። አልፎ አልፎ የሚገኙት በቂ የትምህርት ዝግጅት እና ልምድ ያላቸውም በካድሬ አለቆቻቸው እየተማረሩ አገር ጥለው መሄዳቸውን ቀጥለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ አሜሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ  በጣም ኃላ ቀር አሰራር በ21ኛው ክ/ዘመን ላይ ተቀምጦ ሲያስተዋውቅ ተሰምቷል።ይሄውም '' ከአሁን በኃላ የኮንሱላር አገርልግሎት የሚሰጠው በፖስታ ብቻ ነው ይላል።'' ዛሬ ዓለም የኮንሱላር አገልግሎት በኢንተርኔት በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በሚያጠናቅቅበት ወቅት  የእኛዎቹ ማንም ሰው የምናስተናግደው በፖስታ ብቻ ነው ብለዋል።ይህ የፍርሃት ደረጃ ነው።የእራሱን አገር ዜጋ የፈራ ኤምባሲ የት ይደርሳል? የሚገርመው ደግሞ ይህ አሰራር ያቀላጥፋል እያሉ በካድሬ ቃላት ሲያጅቡት መሰማቱ ነው።የኮንሱላሩ ጉዳይ ኃላፊ ለአንድ ትዩብ  ለምን በፖስታ ብቻ እንዳደረጉ ለተጠየቁት ጥያቄ ሲመልሱ '' በዓል የሆነ ቀን ኢትዮጵያውያን ሳያውቁ ይመጣሉ እናም በፖስታ መሆኑ ለእዚህ ይረዳቸዋል'' ሲሉ ማሾፍ አይሉት ቀልድ መሰል ምላሽ ሰጥተዋል።አሁን ባለንበት ዘመን የፖስታ አገልግሎት በእራሱ ወደ ኤሌክትሮኒክስ ፖስታ ኢትየተቀየረ ነው።የፖስታ ድርጅቶችም አዳዲስ የገቢ መስክ ለምሳሌ የገንዘብ ዋላ አገልግሎት የመሳሰሉትን የሚሰጡት ጥንታዊው የፖስታ አገልግሎት እየቀረ እንደሚሄድ ከወዲሁ ስለተገነዘቡ ነው።

በአሜሪካን አገርም ውስጥ ቢሆን አንድ ተራ ፖስታ በዕለቱ እንደማይደርስ የታወቀ ነው።ቢያንስ አርባ ስምንት ሰዓታት ወይንም ሁለት ቀን በትንሹ ማስፈለጉ አይቀርም።ይህም አንድ ሰው በአካል መጥቶ ጉዳዩን ከሚፈፅምበት ጊዜ የበለጠ ነው ማለት ነው።ሰነዱን የላከ ሰው እስኪመለስበት የሚጠብቀውን ጊዜ ደግሞ ሲታሰብ በጣም እረጅም ነው።አሁን ባለንበት ዘመን ገንዘን ያህል ሀብትም በቁልፍ ቁጥሮች ማውጣት እየተቻለ በካድሬ አቅም የታሰበች ሃሳብ በፖስታ ብቻ መጠቀም ሥራ ያቀላጥፋል እየተባለ ይነገረን ገባ።


ባጠቃላይ የዶ/ር ቴዎድሮስ መስርያ ቤት ከእለት እለት ደረጃው እየወረደ እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ የበለጠ የሚያስተች መስርያቤት እየሆነ ነው።ከሁለት አመታት በፊት ዋሽንግተን የሚገኘው ኤምባሲ ጥታ የሰፈነበትን የዲፕሎማቶች ሰፈር በተኩስ ያናወጠው ስለ ዓለም አቀፍ ሕግ እና ድንጋጌዎች ፈፅሞ  የማያውቅ ካድሬ የመመደቡ ጦስ መሆኑ ይታወቃል።በሌላ በኩል በግብፅ የሚገኘው ኤምባሲ በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር የተሰማሩ ሰራተኞች ባለቤት መሆኑን ማረጋገጣቸውን በሊብያ የነበሩ ኢትዮጵያውያን መናገራቸውን አንዘነጋውም። ለሁሉም የኢትዮጵያ ኤምባሲ በአሜሪካ ኢትዮጵያውያንን የማገኛችሁ በፖስታ ብቻ ነው ብሏል።መምጣት የፈለገ ደግሞ ቀድሞ አሳውቆ ነው እን ድንገት ብቅ አትበሉ ብሏል። ይሁን እንጂ የእንጀራ ልጅ ያልሆነ በፈለገ ዜ እንደሚገባ እና እንደሚወጣ ማንም የሚያውቀው ጉዳይ ነው። ወደፊት ግን እንደ አራት ሎ ቤተ መንግስት አጥር በአጠገቡ አትለፉ እንዳይባል? ያስፈራል።የእራሱን ዜጋ የሚፈራ ኤምባሲ ከእዚህም ሌላ ብዙ ያደርጋል።ለሁሉም ግን የዶ/ር ቴዎድሮስ መስርያ ቤት በአሜሪካ ወደ 18ኛው ክ/ዘመን የጫካ አሰራር ተመልሷል

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Sunday, May 22, 2016

Great fear of another Genocide on North-Western part of Ethiopia, Welqayt-Qabti ወልቃይት ላይ ሌላ የዘር ማጥፋት እንዳይፈፀም! (Gudayachn special Alarm)

‘'በወልቃይት ቃብቲያ በህዝቡና በትግራይ ልዩ ሃይል ፍጥጫው ዛሬ ተጠናክሯል። ከ8ህ በላይ ህዝብ ስብሰባ ወጥቷል። የትግራይ ልዩ ሃይል ስብሰባው ለመበተን ሞክሮ አልተሳካለትም። በህዝቡ ሃይል አፈግፍጓል። የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበረ ነዋሪዎች ተናግረዋል።''ኢሳት ልዩ ዜና ግንቦት 14፣2008 ዓም

'Today in Welqayt-Qabti, there is high tension between the people and Tigray regional special force.Over Eight-thousand people is gathering. Tigray special force has failed to interrupt the meeting. It was obliged to back by strong pressure of the people. Residents inform us they are hearing shooting'' Ethiopian Satellite Television - ESAT special news  Sunday, May 22,2016.
Controversial map of TPLF 

ጉዳያችን Gudayachn Special Alarm
May 22, 2016
Oslo, Norway

According to Ethiopian Satellite Television- ESAT  breaking news, as at of May  22,2016,  over Eight-thousand people gathered at North-west part of Ethiopia, Amhara Administrative region, Welqayt-Qabti (ወልቃይት ቃብቲያ). Welqayt-Qabti is very near to North Sudan and Eritrea plus shares common border with Tigray administrative region of Ethiopia.
     The current Tigrian ethnic-led regime of Ethiopia,TPLF, has been accused of killing over Ten-thousands of Welqayt indigenous people. Welqayt-Qabti residents are Amhara ethnic and fully reflects Amhara ethic culture.  An appeal committee which was fully authorised by the local  people of Welqayt has made failed attempt  to address the conflict to get the necessary attention by the central government which is almost fully dominated by Tigrian ethnic group. The main appeal of the committee, on behalf of the Welqait people, is to request the TPLF-led government to respect the cultural and administrative right of the region. But the response from TPLF was a continuous killing and imprisonment. 
      It is exactly one week, since  the local farmers of Welqayt' 'wereda' has  declared on their refusal to accept any TPLF authority domination on the region. Four-thousand people agreed on this declaration. The declaration gives strong warning to TPLF officials not to come to their ‘wereda’ for any type of administrative purpose.
     Today, according to ESAT breaking news release, over Eight thousand people have again gathered in Welqayt-Qabti wereda to strength their previous declaration of self administration.  On the other hand, the TPLF special army was trying to cease them not to go to the meeting. But strong resist  back the army to the nearest mountainous area.
   An indigenous people of Welqayt area residing in USA, Europe and Australia have exposed a number of documented evidences on TPLF’s massacred  over Ten-thousands of  residents for the past 25 years. TPLF strategic interest in the region is to show its ethnocentric boost of Tigrigna speaker people over indigenous Amhara ethnicity. This was practiced through both  force-full settlment of Tigrigna language speakers on the fertile land of Welqait and  obliging indigenous Amhara  people to  undermine their pre-existed Amhara culture including their  language, Amharic.

     The latest news indicate that TPLF regime is sending more troops to the mentioned conflict area. Many fear, as there is no any guarantee for not happening another genocide by TPLF. Therefore international community is seriously expected to  be aware and  react against the TPLF dictatorial act on innocent Amhara people.

GUDAYACHN ጉዳያችን

Thursday, May 19, 2016

በግንቦት 20 ሰሞን የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ




መብራት ከመጥፋቱ በፊት ማስታወቂያ የሚነግርበት፣
ውሃ አጠራቅሙ ነገ ልጠፋ ነው ብሎ ቀድሞ የምያስታውቅበት ፣
መብራትም ሆነ ውሃ እንመለሳለን ባሉበት ሰዓት የሚመጡበት፣
የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ

ቢሻኝ ተነስቼ እስከ ዳህላክ ሄጄ አደይን የማይበት፣
ከፈለኩ ቄራ ሰፈር አቦይ ጋራዥ ሄጄ በፍቅር መኪናዬን የማሰራበት፣
ገብረ ተንሳይ ኬክ ቤት የማነው የማልልበት፣
በፈለኩት ቋንቋ ታክሲ ውስጥ ጮክ ብዬ ቢሻኝ በኦሮምኛ፣ወይ በትግርኛ ከፈለኩ ወላይትኛ ሳወራ የማልሸማቀቅበት፣
ሰውም ስለምናገረው ነገር ከቁም ነገር ሳይቆጥር በእራሱ ሥራ የምጠመድበት፣
የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ

ለልጆቼ ገበያ በ24 ብር 2 ኪሎ ስጋ የምገዛበት፣
በግ ቢያምረኝ ከእነቆዳው በመቶ ብር የምገዛበት፣
ሩዝ  እና ፓስታ ለአንድ ቀን እራት የበላ ጎረቤት ተቸገረ ተብሎ ጉድ የሚባልበት፣
ዘይት የድሃ እና ሃብታም መለያ ያልሆነበት፣
የሾላ ወተት በላስቲክ ገዝቶ ወደ ቤት መሄድ ሃብታም የማያስብልበት፣
እናት ልጆቿን የሾላ ወተት አጠጣች ተብሎ ከተወራ ነውር የሆነበት፣
ወተት ኮንትራት ከብት ካላቸው ሰዎች መከራየት ቅንጦት ያልሆነበት፣
የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።

የሸዋ ዳቦ በ10 ሳንቲም ገዝቶ መብላት የተማሪ ሥራ የሆነበት፣
ደብረ ዘይት ደርሶ ለመምጣት 5 ብር ብቻ የሚበቃበት፣
የልጆች ደብተር፣እርሳስ መግዛት ያማያስጨንቅበት፣
ለትምህርት ቤት ክፍያ የማይከፈልበት፣
ዩንቨርስቲ መግባት አንሶላ እና ብርድልብስ ብቻ ተይዞ የሚገባበት፣
የውጭ መጋራት ጣጣ የሌለበት፣
የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ወጡ ላይ ብዙ ስጋ የለበትም ብለው የሚያማርሩበት፣
ዳቦ ዩንቨርስቲ በር ላይ ለሚጠርግ ሊስትሮ ሲሰጠው ''አቦ ፓስታ በልቻለሁ'' የሚልበት፣
ሻይ ቤት በአንድ ብር ባለ በርበሬ ስጎ  ፓስታ የሚሸጥበት፣
የቀን ሰራተኛው በሁለት ብር እንጀራ በወጥ የሚበላበት፣
የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።

የአገር መሪዎች በሁለት እና ሶስት ወር ክፍለ ሃገሩን በሙሉ እየዞሩ የምጎበኙበት፣
ዓመት በዓል የከተማው ሕዝብ እንዳይቸገር ዋንኬ በግ የሚመጣበት፣
ዋንኬ በግ ላት የለውም ጮማ ይበዛዋል፣ቆዳው አይረባም እየተባለ የምንቀናጣበት፣
አንድ ሙሉ የዶሮ ወጥ ከ24 እንቁላል ጋር መስራት የሃብታም መለያ ያልሆነበት፣
የዶሮ ዋጋ የበጉን የበጉ ዋጋ የበሬውን ያልተካበት፣
የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።

ከሶስት መቶ ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ወጣት ሴቶች ለአረብ አገር ያልተሸጡበት፣
በእነርሱ ሽያጭ የውጭ ምንዛሪ የሚሰበስብ መንግስት የሌለበት፣
ኢትዮጵያውያን በስደት በዓለም ዙርያ ያልታወቁበት፣
ባህሩ የኢትዮጵያውያንን ስጋ መብላት ሱስ ያላደረገበት፣
እነ ታንዛንያ የመሰሉ አገሮች ባቅማቸው የኢትዮጵያ ስደተኛ አንቀበልም ያላሉበት፣
በዓለም ላይ ሁለት የታወቁ ስደተኞች ብቻ የነበሩበት፣
ኢትዮጵያዊ ሁሉ ትምህርቱን ተምሮ መቼ ወደ አገሬ በተመለስኩ የሚልበት፣
ከዩንቨርስቲ የተመረቀ ሁሉ ሥራ የሚይዝበት
ያ የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።

ሰው ከቤቱ የማይፈናቀልበት፣
ቤቱን በድንገት መንግስት የማያፈርስበት፣
መንግስት የእራሱን ሕዝብ ጎዳና ተዳዳሪ ለማድረግ የማይተጋበት፣
77 ሚልዮን ብር በፕሮጀክት ስም የማይዘረፍበት
200 ሕፃናት የማይጠለፉበት
2000 ከብት የማይዘረፍበት፣
ከግማሽ ሚልዮን በላይ ጎዳና ላይ የወደቁ ጎዳና ተዳዳሪ ሕፃናት ያልበዙበት፣
በሃምሳ አመታት ውስጥ ያልታየ ርሃብ የማይታይበት፣
የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።


ቢሻኝ ተነስቼ እስከ ዳህላክ ሄጄ አደይን የማይበት፣
ከፈለኩ ቄራ ሰፈር አቦይ ጋራዥ ሄጄ በፍቅር መኪናዬን የማሰራበት፣
ገብረ ተንሳይ ኬክ ቤት የማነው የማልልበት፣
በፈለኩት ቋንቋ ታክሲ ውስጥ ጮክ ብዬ ቢሻኝ በኦሮምኛ፣ወይ በትግርኛ ከፈለኩ ወላይትኛ ሳወራ የማልሸማቀቅበት፣
ሰውም ስለምናገረው ነገር ከቁም ነገር ሳይቆጥር በእራሱ ሥራ የምጠመድበት፣
የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።

ግርማ ሞገስ የሌለው ቀላል መሪ በቤተ መንግስቱ የማይጎማለልበት፣
መሪው ከውጭ አገር ሰው ጋር በተገናኘ ቁጥር እና ንግግር ባደርገ ቁጥር ምን ይዘባርቅ እና አገሬን ያሰድብ ይሆን ብዬ የማልሳቀቅበት፣
በአነጋገሩ እና በምላሽ አሰጣጡ የምረካበት፣
በምግብ እራሴን ስላችል ችለሃል ብሎ የማያስፈራራኝ መሪ የማይበት፣
በምክር ቤት ስብሰባ ባለጌ ስድብ የማልሰማበት፣
ኢትዮጵያውያን በሊብያ አለቁ ሲባል ቆይ ዜግነት ላጣራ የማይል መንግስት የማላይበት፣
የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።

ጋዜጠኛ መሆን በአንድ ጦር ሜዳ እራሱን ለሞት ከሰጠ ወታደር እኩል የማይታይበት፣
የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከ40 ዓመት በፊት ከነበረበት የመፃፍ መብት የባሰበት፣
የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ከአርባ ዓመት በፊት የነበረው የመደራጀት መብት የተንኮላሻበት፣
የሰራተኛ ማህበር ለሠራተኞች መብት እኩል ተደራድሮ የህብረት ስምምነት የሚፈርምበት፣
የመምህራን ማኅበር የእራሱ መፅሄት፣አደረጃጀት፣እና መብት ለማስከበር የሚንቀሳቀስበት፣
ተማሪዎች የተሰማቸውን በፅሁፍ የሚገልጡበት፣
ተማሪዎች በመቃወማቸው መምህራን በመሰለፋቸው የጥይት እሩምታ የማይወርድበት፣
ለተማሪ በዱላ ለመምህር አስለቃሽ ጋዝ የሚለቀቅበት፣
 የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።

የኢትዮጵያን ድንበር የማንም ዘላን እንደፈለገ ጥሶ የማይገባበት፣
ጎረቤቶቻችን በእኛ የወታደር አቅም አንፃር ስታዩ ከጥቃቅን ግልገል የሚቆጠሩበት፣
እስር ቤቱ በጋዜጠኛ ፣ፀሐፊ እና ደራሲ ያልታጨቀበት፣
የሃይማኖት አባት በጎጥ እና በመንደር አስቦ ውሎ በማያድርበት፣
እድር በካድሬ ቢሮ ስር ያልዋለበት፣
የቤተ ዘመድ ስብሰባ ሆን ተብሎ እንዲበተን በስውር ያልተሰራበት፣
ሰው ቤተሰቡን የማይፈራበት፣
የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።

አንድ ለአምስት ያልተጠረነፈ ሕዝብ እና አገር ያለበት፣
ኢቲቪ የውሸት ሁሉ አባት ያልሆነበት፣
የኢቲቪ ዜና ፎቶ ከኢራቅ እየተገለበጠ ያልተወሸከጠበት፣
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አውስትራልያ የምትኖር ኢትዮጵያዊት 20 ሚልዮን ዶላር ሎተሪ ደረሳት ብለው ልቤን የማያስደነግጡበት፣
ቆይተውም በስህተት ነው ይቅርታ የማይሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሌሉበት፣
የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።

ኢትዮጵያን በጎጥ ከፋፍለው የሚስቁ ባለስልጣናት የለሉበት፣
ዲያስፖራውን በጎጥ እየከፋፈሉ ፈስቲቫል እያሉ የማይደክሙ ከፋፋዮች የሌለበት፣
ውጭ አገር ልዑክ ሲልኩ በጎጥ የሚልኩ እና የሚሰበስቡ ባለስልጣናት የማላይበት፣
በአንድ ጀንበር 200 ሰው በአዲስ አበባ የማይገድል ፖሊስ የማይበት፣
ከአራት መቶ በላይ ሕዝብ ሰልፍ በሰላማዊ መንገድ ጠየቃችሁ ብሎ የማይገድል መንግስት ያለበት፣
የኢትዮጵያን ድንበር ለሱዳን ለመቁረስ የማይደራደር እና የእራሱን አገር ገበሬ ሽፍታ ብሎ የማይጠራ ጠቅላይ ሚኒስትር የማላይበት፣
የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።
ምን ትሆኑ እንግዲህ የድሮ ስርዓት ናፈቀኝ።በእዚህ በግንቦት 20 ሰሞን አብዝቶ ናፈቀኝ!የተሻለ ስጠብቅ የባሰ መጥቶ የድሮ ስርዓት አስናፈቀኝ።ግንቦት 20 አይለፍልህ!


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።