ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, April 30, 2013

ሰበር ዜና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከሁለት ሺህ አመት በላይ በዘለቀ ታሪኳ የምዝገባ ፈቃድ ማንም መንግስት ያልጠየቃትን ኢህአዲግ እንደ አዲስ መመዝገብ አለባት አለ።ምንጭ የዳንኤል ዕይታዎች ድህረ ገጽ


ከ2000 ዓመት በኋላ እንደ አዲስ እንመዘገባለን፣ እንደ አዲስም እንታወቃለን

ምንጭ-የዳንኤልዕይታዎችድህረገጽ (http://www.danielkibret.com/2013/04/2000.html)
ሰሞኑን የፌድራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሃይማኖት ተቋማትን ለመመዝገብ የወጣ ረቂቅ መመሪያ› የሚል ወረቀት አስተያየት ይሰጥበት ዘንድ ለእምነት ተቋማት አሠራጭቷል፡፡ ይህ መመርያ የያዛቸውን ጉዳዮች እያንዳንዳቸውን እየነጠሉ መመልከት ያስፈልጋል፡፡ ይህንንም ወደፊት የምናደርገው ይሆናል፡፡ ለአሁኑ ግን መመሪያውን ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ነባራዊ፣ ሉዓላዊና መንፈሳዊ ጠባያት ጋር በማዛመድ ብቻ እንመለከተዋለን፡፡
1.       መመሪያው የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዩ ሁኔታ ከግምት ያላስገባ ነው
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላለፉት 2000 ዓመታት በምድሪቱ ላይ የኖረች፣ የሰበከች ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ ክፉውንም ሆነ ደጉንም እኩል የቀመሰች፣ እንዲያውም የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በመሆንዋ ብቻ ልዩ ጉዳት የደረሰባትም ናት፡፡ በጣልያን ወረራ ጊዜ የተሠውትን ጳጳሳትና መነኮሳት ማሰቡ ብቻ ለዚህ የቅርብ ምሳሌ ነው፡፡ ይህቺ ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ሂደት ውስጥ በሀገሪቱ ሃይማኖታዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ውስጥ ልዩ የሆነና የማይተካ ሚና ተጫውታለች፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ተመሥርታ ሀገሪቱንም መሥርታለች፡፡
ይህንን ሁሉ ዘንግቶ በ2005 ዓም ላይ ቤተ ክርስቲያኒቱን እንደ አዲስ ተመዝገቢ፣ እንደ አዲስ ፈቃድ አውጭ፣ እንደ አዲስ ደንብና መመሪያሽን አምጭ ማለት እጅግ አሳዛኝም አስገራሚም ነገር ነው፡፡ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱም ራሱ ከፈለገ መረጃ ሰብስቦ መመዝገብና ማወቅ ነበረበት እንጂ ሰነድ አምጭ፣ ደንብ አስገቢ፣ ፈቃድ አውጭና ልወቅሽ ማለት አልነበረበትም፡፡

 ሀ/ የሚኒስቴሩ አንድን የሃይማኖት ወይም የእምነት ተቋም የሚመዘግበው የመመሥረቻ ጽሑፍ፣ መተዳደርያ ደንብና የመሥራቾቹ ቃለ ጉባኤ ሲቀርብለት ነው (ዐንቀጽ 7 ቁ.1) ይላል፡፡ አሁን ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የትኛውን ደንብ ነው የምናቀርበው? ዲድስቅልያ፣ ሲኖዶስ፣ ግጽው፣ አብጥሊስ፣ ፍትሐ ነገሥት፣ ሕገ መነኮሳት፣ ሥርዓተ ሕግ ወቀኖና፣ የኒቂያ ቀኖና፣ የቁስጥንጥንያ ቀኖና፣ የኤፌሶን ቀኖና፣ የሎዶቅያ ቀኖና፣ የቅርጣግና፣ ስንቱን? የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱስ የትኞቹን ሊቃውንት ሰብስቦ ነው ይህንን ሁሉ ሕግ አጥንቶ ከሕገ መንግሥቱ ጋር ይጋጫል ወይስ አይጋጭም ብሎ አስተያየት የሚሰጠው፡፡
በሌላም በኩል የመሥራቾች ቃለ ጉባኤ መቅረብ አለበት ይላል፡፡ እኛ የነማንን ቃለ ጉባኤ ነው የምናቀርበው? የሐዋርያትን ነው ወይስ የሠለስቱ ምዕትን? የኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ ነው ወይስ የአብርሃ አጽብሐን፣ የተሰዓቱ ቅዱሳንን ነው ወይስ የአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃንን?
ለ/ ቅርንጫፍ መክፈትን በተመለከተው በዐንቀጽ 14 ላይ ስለተከፈቱት ቅርንጫፎች አድራሻና አመራሮች በ30 ቀናት ውስጥ ለሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ማሳወቅ ይገባል ይላል፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የ35ሺ አጥቢያዎቿን የሰበካ ጉባኤያት፣ የ110 ገዳማቷን አበምኔቶችና ምርፋቆች፣ ከስድሳ የሚበልጡትን አህጉረ ስብከቶችን ሥራ አስኪያጆች የመመሪያ ኃላፊዎች ሁሉ ታስመዘግባለች ማለት ነው?
ሐ/ በዐንቀጽ 23 ላይ ማንኛውም የእምነት ተቋም የተመረጡ መሪዎችና የሥራ ኃላፊዎችን ከዓመታዊ ሪፖርቱ ጋር ማቅረብ እንዳለበት ይደነግጋል፡፡ ለመሆኑ ከቤተ ክርስቲያን አንፃር ‹የሥራ ኃላፊ› የሚለው ምን ማለት ነው? ክህነታዊ ኃላፊነትን ነው ወይስ አስተዳደራዊ ኃላፊነትን? ታድያ ጳጳስ ስትሾም፣ ካህን ስትሾም ቆሞስ ስትሾም፣ ዲያቆን ስትሾም፣ ንፍቅ ዲያቆን ስትሾም፣ አናጉንስጢስና አንባቢ ስትሾም ማሳወቅ ሊኖርባት ነው ማለት ነው? ለመሆኑስ በእነዚህ ላይ መወሰን ያለበት የፌድራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ነው ወይስ መንፈስ ቅዱስ? ለመሆኑ ዝርዝሩን ከተቀበለ በኋላ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ባይስማማ ጳጳሱ ከጵጵስናው፣ ካህኑ ከክህነቱ ይሻራል ማለት ነው?
ደግሞስ ቤተ ክርስቲያን ከላይ የጠቀስናቸውን የሥራ ኃላፊዎች ዝርዝር በየዓመቱ የምታስገባ ከሆነ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ መዝገብ ቤት በምን ያህል እንዲሰፋ ሊደረግ ነው? ያውም ስማቸውን ፣ ዕድሜያቸውን፣ የመኖርያ አድራሻቸውን፣ የስልክ ቁጥርና የኃላፊነት ድርሻቸውን ሁሉ ማካተት ያስፈልጋል ይላል፡፡ ስለዚህ በየገዳማቱ የሚገኙ አባቶች አበምኔት ለመሆን፣ መጋቢ ለመሆን ወይም ጓል መጋቢ ለመሆን የመኖርያ አድራሻና ቢመንኑም የስልክ ቁጥር ያስፈልጋቸዋል ማለት ነው፡፡
መ/ በዐንቀጽ 27 ላይ እንደ አስፈላጊነቱ የምዝገባና የተሰጠውን ሕጋዊ ሰውነት ፈቃድ ሊያግድ ወይም ሊሠርዝ ይችላል ይላል፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ ያ የእምነት ተቋም አገልግሎቱን መስጠት አይችልም ማለት ነው፡፡ ስለዚህ አንድ የጠቅላይ ቤተ ክህነት መምሪያ ሰነድ አሟልቶ፣ ጊዜ ጠብቆ ፈቃዱን ሳያድስ ቢቀር ቅዳሴ ይቆማል፣ ሰዓታት ይታገዳል፣ ጾም ይቋረጣል፣ ክርስትና ይቀራል፣ ተክሊል አይኖርም፣ ፍትሐት አይደረግም፣ ገዳማት ይዘጋሉ፣ አጥቢያዎች ይታጎላሉ ማለት ነው? በዮዲትና በግራኝ፣ በጣልያንና በደርቡሽ የመከራ ዘመን ያልተቋረጠው፣ እግዜር የለም ባለው የደርግ ዘመን እንኳን ያልቆመ ውዳሴና ቅዳሴ፣ ሰዓታትና ማኅሌት፣ ፍትሐትና፣ ክርስትና በአንድ ሰርተፊኬት እጥረት ይታገዳል ማለት ነው? ታድያ ይሀ የእምነት ነጻነት ነው ተብሎ ሊነገርለት ይችላል? 
2.    መመሪያው የጋኑን በምንቸት ለመክተት የሚሞክር ነው
የቅርብ ዘመናት የሕዝብና ቤት ቆጠራ ውጤቶት ከኢትዮጵያ ሕዝብ መካከል 97% የሚሆነው ‹ሃይማኖተኛ› መሆኑን ገልጠውልናል፡፡ ሃይማኖት በሀገሪቱ ውስጥ ወሳኝ ሚና ካላቸው ነገሮች ዋነኛው ነው፡፡ የሕዝቡን ኑሮ፣ ጤና፣ አመለካከት፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ ከሚወስኑት ጉዳዮች ዋነኛውም ሃይማኖት ነው፡፡ ይህ ሁሉ እየታወቀ ሃይማኖትን ያህል ነገር የሚወስንን ነገር በአንድ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤት መመርያ ማውጣት እንዴት ተቻለ? በተለይም ይህ መመሪያ ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ አንጻር የቤተ ክርስቲያኒቱን ሉዓላዊነት የሚሽርና የቤተ ክርስቲያኒቱን ዓለም ዐቀፋዊ ጠባይ የሚገዳደር ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱን እንደ አንድ ማኅበር፣ መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም ወይም ድርጅት እንድትመዘገብ፣ ፈቃድ እንድታወጣና ፈቃድ እንድታድስ፣ ችግር ከገጠመም ፈቃድዋን ተነጥቃ ሕልውናዋን እንድታጣ የሚያዝ መመሪያ እንዴት ነው ቢያንስ የሀገሪቱ ከፍተኛው አካል የሆነው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንኳን ሳያየው በመመሪያ ደረጃ ብቻ እንዲወጣ የተፈለገው? የጋኑን በምንቸት ማለትም ይኼ ነው፡፡

  1. መመሪያው በአዲሱ ዘመን ንቅናቄ መንፈስ የወጣ ይመስላል
መመሪያው ሲወጣ የፍልስፍና መሠረቱ የአዲሱ ዘመን ንቅናቄ (The New Age Movement) የሚባሉትን የፕሮቴስታንት ክፍልፋዮች መሠረተ ሃሳብ መነሻ ያደረገ መሆኑን የሚጠቁሙ ነገሮች አሉ፡፡ ሃይማኖትን ለመመሥረት አነስተኛ ቁጥር ማስቀመጥ፣ ሃይማኖትን መመዘግብና እንደ ማንኛውም ድርጅት ፈቃድ መስጠትና መንጠቅ የመሳሰሉ ሃሳቦች ከእነዚህ አዲሱ ዘመን ንቅናቄ ፕሮቴስታንቶች ሃሳቦች የተወሰዱ ናቸው፡፡ ሌላው ቀርቶ እንደ አድቬንቲስት፣ ሜኖናይት፣ ሜቶዲስት የመሳሰሉ ጥንታውያንና ባለ መሥመር ፕሮቴስታንቶች (main line protestants) ይህንን ሃሳብ አይቀበሉትም፡፡ የእነዚህ ክፍልፋይ ፕሮቴስታንቶች ዋናው መርሕ ደግሞ ሊበራልነት ነው፡፡ እጅግ የሚገርመው ነገር ኢሕአዴግ ደጋግሞ የሚወቅሰው የሊበራል አስተሳሰብ እንዴት በፌድራል ጉዳዮች ሚኒስቴር በኩል የሃይማኖት ተቋማት የምዝገባ መመሪያ ሆኖ ሊመጣ እንደቻለ ነው፡፡
መመሪያው እምነትን በተመለከተ ሊበራል የሆነውን ሃሳብ የሚከተሉትን የምዕራብ ሀገሮች ልምድ እንጂ ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙባቸውንና በዚህ ረገድም ነባርና ጥብቅ ሕግ ያላቸውን የምሥራቅ ሀገሮችን ልም ያካተተ አይመስልም፡፡ እንደ ግሪክ፣ ጣልያንና አርመን፣ ሩሲያና ሌሎች ሀገሮች ልምዶች በመመሪያው ውስጥ አይታይም፡፡
መመሪያው በአዲሱ ዘመን ንቅናቄ ፕሮቴስታንቶች መንፈስ የተዘጋጀ ነው የሚያስብለው ሌላው ነገር የተጠቀመባቸው ቃላት ናቸው፡፡ ሚኒስትሪና ፌሎውሺፕ፣ ቅርንጫፍ፣ የሚሉትን ቃላት ሲጠቀም፣ አጥቢያ፣ ሀገረ ስብከትና ገዳም የሚሉትን ቃላት ግን ለመጠቀም አልፈለገም፡፡
በአጠቃላይ መመሪያው እጅግ ከባድን፣ ታላቁንና ውስብስቡን የሀገሪቱን የሃይማኖት ጉይ አቅልሎ የተመለከተ፣ ከልኩ በላይ የሰፋውን ነገር፣ ከልኩ በታች ያጠበበ፣ የሀገሪቱን ነባር ባህልና ጠባይ ከግምት ያላስገባ፣ ኢትዮጵያን ዛሬ የተመሠረተች አድርጎ የሚቆጥር፣ ከሚያመጣው መፍትሔም የሚፈጥረው ችግር የሚበዛ ነው፡፡ መጀመርያውኑ ከዚህ የሚያንሡ ጉዳዮች በተወካዮች ምክር ቤት እየታዩ የ75 ሚሊዮንን የሃይማኖት ጉዳይ በአንድ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤት መመሪያ ለመደንገግ መሞከር ስሕተት ነው፡፡ በሁለተኛ ደረጃም ሕጉ ነባሮቹን ከአዲስ ተመሥራቾች ያልለየ ነው፡፡
በመሆኑም የቤተ ክርስቲያን አባቶችም ሆኑ ምእመናን በጥንቃቄ ሊያዩት ሃሳባቸውን በግልጥ ሊሰጡበትና የቤተ ክርስቲያንን ሉዐላዊነት በሚያስከብር መልኩ እንዲሄድ ሊያደርጉት ይገባል፡፡
ምንጭ-የዳንኤልዕይታዎችድህረገጽ (http://www.danielkibret.com/2013/04/2000.html)

ከእዚህ በታች ያለው ከጉዳያችን ጡመራ  የተሰጠ አስተያየት ነው


ይህ ጉዳይ አጅግ አጅግ አደገኛ ችግር ይዞ የሚመጣ ነው።በሌላ አነጋገር ቤተ ክርስቲያኒቱን ለመክፈል የሚደረግ ጥረት አካል ነው። ከእዚህ በፊት በነበረው ሁኔታ በ ኢትዮጵያ ሕግ በብሄራዊነት የሚታወቀው ''የ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተውህዶ ቤተክርስቲያን'' የሚል ብቻ ነበር።ማንም በእዚህ ስም ቢመጣ ሕጋዊ አይደለም።ይህ ሕግ በመጀመርያ ደረጃ የሚቃረነው የቤተክርስቲያንቱን አንድነት ነው።ከ እዚህ በፊት አንዳንዶች በቤተክርስቲያኒቱ ስም ሌላ ፈቃድ ለማውጣት ሲሞክሩ ጉዳዩ በእንጭጩ የተቀጨው ቤተክርስቲያኒቱ በነበራት ሕጋዊ መሰረትነት ነው።አሁን መንግስት ''እንደ አዲስ መመዝገብ የሚለው''   ሂደት ምን ማለት ነው? ምዝገባ ማለት በትንሹ የሚከተሉትን ማለት ነው።

1/ ቤተክርስቲያንን ለመክፈል የታቀደ ነው።
ማንም በሆነ ''ዶግማ መሰል'' ልዩነት ከቤተክርስቲያኒቱ ተለይቼ ፍቃድ ይሰጠኝ ቢል በትይዩ የተመዘገብችው ቤተክርስቲያን ፍርድ ቤት ልትከሰስ እና ንብረት እንድታካፍል ልታደርግ ትችላለች።ይህ ደግሞ በህንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የታየ ነው።ይህ እንደሚሆን ደግሞ መንግስት አይጠፋውም፣

2/ መንግስት ቤተክርስቲያንቱን አላውቃትም ማለቱ ነው።
አብራችሁ የኖራችሁት ሰው በድንገት ስምህን ንገረኝ፣ማነህ/ማነሽ? ብላችሁ የአእምሮ በሽተኛ ካልሆነ በቀር አላውቅህም/አላውቅሽም ማለቱ ለመሆኑ አያጠራጥርም፣

3/ የሀገሪቱን ታሪክ፣ክብር፣ማንነት  እና 'የት መጣሽነት' በሙሉ ሰርዞ አዲስ ታሪክ ለመፃፍ የተጀመረ ፕሮጀክት አፈፃፀም 
አካል ነው።
በመሆኑም ይህ ጉዳይ ከእዚህ በፊት በተበጣጠሰ መልክ ሲነገሩ፣አንዳንዶች  እንደ ቀድሞው የህወሓት መስራች አቶ ገብረመድህን አይነቶች ደግሞ ከፅሁፍ ማስረጃ ጋር የወያኔ እቅድ በኢትዮጵያ ቤተርክስቲያን ላይ ያስነበቡንን ትክክለኛነት የሚያመላክት  ማስረጃ ነው። በመጨረሻም በግንባር ቀድምትነት ከትግራይ አክሱም እስከ ሞያሌ ከሐረር እስከ ኢልባቦር  በውጭ የሚኖረው የቤተክርስቲያኒቱ አማኝም ሆነ ያልሆነ በአንክሮ ተመልክቶ ሊቃወመው የሚገባ ለወደፊቱም ዘለቂታዊ ስራዎችን ማሰብ የግድ የሚል መሆኑን አመላካች ጉዳይ ነው።
ጌታቸው 
ኦስሎ 

Sunday, April 28, 2013

TIME FOR BEGENA

TIME FOR BEGENA

    Source- The Reporter April 13,2013
This time around during the lent season, while traveling in mini-bus taxis, having coffee at a café, or wandering around the churches one can hear the deep-sonorous voice.
Ten strings hanging from a short bar at the top joined by two parallel sticks and a leather-made sound-box at the bottom are the parts of this very ancient and biblically played instrument called the Begena (an instrument that belongs to the family of the lyre.) Begena, which is also named as the Harp of King David, has distinguishing features that differentiate it from the harp. The number of strings, the construction of the wooden frame in which the strings are coiled and the way the musicians handle it to play are the visible differences that anyone can point out. It is a kind of psaltery that dates back some five thousands years roughly estimated to be some 3,800 years before the birth of Christ.


Ethiopians were introduced to such a sensuous and spiritually powerful musical instrument through either of the two commonly cited ways. The first, that makes its argument depending on the analogy of Ethiopia’s archaeological evidences that puts it as the origin of human beings, and the second relies on the historical travel that the Queen Sheba made to King Solomon of Israel. Whatever the way to be introduced to the instrument, it at once became the most prestigious Ethiopian traditional musical instrument. Nevertheless, it has never come on the way it could be played together with others to perform a secular music because of the profound and rigorous relation it has with religion. It was first played in the palaces to enchant the kings and queens and also at ceremonious events inside churches and outside the churches like on weddings based on biblical and historical accounts. 


Although a number of Ethiopians were playing it, including the kings and the queens, there were a few who became popular enough playing it on media and public gatherings. It was during the reign of Haileselassie I that the first preceptor, Aleka Tessema Woldeamanuel was called to the capital to teach at the Entoto Secondary School. The then 12-year-old Alemu Aga became one of the first boys who stepped into the classroom. Alemu, who is well acclaimed for playing the begena and of course enjoys much reverence, has been the most important musician to play the instrument. He has played a large repertoire of ecclesiastical songs with it and trained more than 600 students. Moreover, he has become very popular in the international arena playing the begena. He has had many opportunities to play it oversees, still having several concerts every year.


Today, Alemu is 62 years old and says that he is in absolute amazement of how happy and successful he has managed to become through his music. Now, he is someone who can teach, play and research.



“I was trained only because my parents wanted me to grow up learning religious practices, and it has influenced me much further, I couldn’t lead my life without it,” he told The Reporter.



The 8th London African Music Festival, World Harp Congress, International Council for Traditional music and Festival De Mosique Des Montagness Du Monde are some of the events he has attended so far. Éthiopiques Vol. 11, recorded by Buda Musique of Francis Falceto’s featured him exclusively. Other music producers in Europe also recorded his songs with other fellow musicians. Alemu sees himself lucky enough that he could always be remembered with begena, but there were other famous begena players before Alemu. The late Demissie Desta for example, who is often seen as a pioneer for playing begena in the emperor’s palace.



Begena, which is often listened to during the lent fasting season of the Ethiopian Orthodox Tewahdo Church, is almost never heard during other times. Due to its tremendous power and spiritual connectivity, it has always been preferred to be listened in the sacred days of dedication that connect the faithful with the Lord. The vibration of the paired strings produce a sound that deeply connects with the audience. Eventually, they will start to react calmly to the sound produced by the begena. According to many, the instrument has the power to calm people from stress. This is of course reveled in the Bible that the King Saul was elated by the play whenever the young David played it. According to some researchers who visited Alemu, the single string can vibrate a thousand times within a second. Vibration therefore remains a particular character of the begena. Stephanie Feser (Ph.D.) an ethnomusicologist from Belgium was one of the visitors who conducted research with him for her dissertation for two years.



At the time of the Emperor during lent, even the state broadcaster and music shop around town played begena compositions rather than other secular songs.



“There is no rule or principle that bans the begena from being played outside of the fasting seasons” Alemu says.  There were attempts made by some artists to play the begena at other times than the fasting seasons, they further went on orchestrating it with other traditional musical instruments on stage; it, however, failed, since the public did not accept it. “The people didn’t want to listen to the begena outside of the fasting season and it didn’t have any harmony with the mixing of the orchestration either,” he says. The deep sound it produces and the vibration it releases cannot be harmonized with others musical instruments easily.



The begena is mostly associated with men because many believe that the instrument mostly produces shallow and thunder like sounds, which goes in line with the natural voice color of men. But nowadays women are playing the begena, and playing it perfectly. Empress Tayitu was one of the first women who played it wonderfully. Now, many young women, particularly in the church are playing it. One of those vibrant begena players is Genet Alemayehu. She has played it for seven years now starting it in her youth. Inspired by male players she often observed in the church and later became well aware of some women who played, including the Empress. What she feels is the euphoria that takes her into the kingdom of her Lord. An accountant by training and a begena teacher at Gorgorios Spiritual School, the only school where begena is taught, she feels that there will be more enrollments of young women who want to study the begena. She argues that what many feel about the traditional connection between the instrument and men does not mean that naturally, women cannot play it, since it can be played through a medium or low scale. “The begena can be adjusted according to the kind of voice one can produce, and it can be played in different styles unlike that of the men’s,” she told The Reporter.



Kinfu Weldegebriel is one of the million Ethiopians who adores the sound of the begena and always listens to it during the time of prayer and fasting. He plays it in his car in the morning and in the evening. He never listens to other music. He  does not even turn the radio on. “This is the time that attracts me to my faith. The begena is something that makes me fell jovial when the fasting season is remembered,” he says.



Like many others, he does not have any trend that influences him to listen to it unless it is fasting season. He doesn’t even think of it at other times, but the very first thing he does when the fasting season approaches is purchase a begena tape or disk. In fact this is not a trend that Kinfu does alone, it seems to be a culture amongst many Orthodox Christians. Because of this religious tendency that makes the connection between the begena and Orthodox Christian fasting, most Muslims have never thought that they could listen to it like other traditional music. Murad Ahmed, spare parts retailer, says that it is only because of such thinking that many Muslims refrain from listening to it, likewise most Christians don’t listen to Menzuma, a religious music that often comes along with the fasting season of Ramadan. “Still I think it does not matter if we listen to it as traditional music,” he says.



What remains so contentious about its purpose as a traditional musical instrument is whether or not it could be used together with other instruments to compose songs. However for many, it seems unrealistic, considering there have been many failed attempts to prove it.



“It is impossible for the begena to be mixed with other traditional instruments because of its calm sound that would be swallowed by the sharp sounds produced by other string instruments like the Krar,” Alemu says. Many seem to agree that the begena is best when it is heard alone. For some, it is of course a band that plays a kind of grooved music in a complete rhythm. Even, there is no chance to think about others while listening to it. The vibration and the buzzing sound that comes out as the singer hums deeply would certainly make it a single-orchestration indeed. The begena is currently being promoted worldwide by Alemu and he believes that the opening of a school is one step. Still a lot of research needs to be done, he concludes

LISTN TO ALEMU AGA's  BEGENA (open the below video)

Source- The Reporter English Edition.

Friday, April 26, 2013

በቤንሻንገል ክልል መተከል ዞን በጵሪ ቀበሌ ተፈናቅለው በድጋሚ ተመለሱ የተባሉ የአማራ ተወላጆች የደረሰባቸውን በደል ለሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ሲገልጹ የሚያሳይ ቪዲዮ ተለቀቀ።ቪድዮውን ይመልከቱ።Semayawi party (Ethiopia opposition party) leaders visiting Benshangul region where thousands of Ethiopians were looted and evicted because they are only from Amhara ethnic.(Vidio)

በቤንሻንገል ክልል መተከል ዞን በጵሪ ቀበሌ ተፈናቅለው በድጋሚ ተመለሱ የተባሉ የአማራ ተወላጆች የደረሰባቸውን በደል ለሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ሲገልጹ የሚያሳይ ቪዲዮ ተለቀቀ።ቪድዮውን ይመልከቱ።

Semayawi party (Ethiopia opposition party) leaders  visiting 

Benshangul region where thousands of Ethiopians were looted and evicted because they are only from Amhara ethnic.(Vidio)



ክፍል አንድ

ክፍል ሁለት


Thursday, April 25, 2013

የግብፅ የኒኩለር ማብላያ ግንባታ፣ሩስያ፣ምዕራባውያን እና ኢትዮጵያ



ግብፅ እና ሩስያ ወዳጅነታቸውን እያጠናከሩ ነው። የግብፁ ፕሬዝዳንት ሙሐመድ ሞሪስ እና የሩስያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ሞስኮ ላይ ባደረጉት ውይይት በአለመቀፋዊ እና አካባቢያዊ ጉዳዮች ላይ ለመተባበር ተስማምተዋል።ግብፅ ከአለመአቀፉ የገንዘብ ድርጅት የ 4.8 ቢልዮን ዶላር ብድር ለማግኘት በንግግር ላይ መሆኗ ይታወቃል።

April 19, 2013. Russian President Vladimir Putin, second right, before the news conference on the results of his meeting with the President of Egypt Mohamed Morsi, third left, in Sochi.(RIA Novosti / Mikhail Klimentyev) (photo from rt.com)

ባለፈው ሳምንት የግብፁ ፕሬዝዳንት ሙሐመድ ሞሪስ ጉብኝት ውስጥ ጎልቶ የወጣው ጉዳይ ግብፅ እ.ኤ.አቆጣጠር በ1986 ዓም አቁሜዋለሁ ያለችውን የኒኩለር ማብላያ ግንባታ በ 2011 ዓም ፕሬዝዳንት ሙባረክ ጉዳዩን እንደገና ቀስቅሰው ለዓለም አቀፍ ጨረታ አቅርበውት የነበረ እና ለጊዜው ወሬው ጠፍቶ የነበረውን ጉዳይ ሩስያ ልታንቀሳቅሰው የመሆኑ ጉዳይ ነው።

ሮም ለግራዝያኒ ሐውልት የተሰጠው ገንዘብ ታገደ!

የ ፋሺሺት ግራዝያኒ ሃውልት በ ኢጣልያ የመገንባቱን ሂደት አዲስ አበባ በመቃወም ሰልፍ የወጡትን ፖሊስ በመደብደብ እና ወደ እስር ቤት በመውሰድ የተንገላቱበት ጉዳይ የኢትዮጵያ መንግስት የሃገሪቱን አንኳር ብሄራዊ እና ሉአላዊነት ጉዳዮች ላይ ተቆርቋሪነት ባለማሳየት  ያስመሰከረበት አንዱ ማሳያ ሆኖ አልፏል።ኢጣልያ ግን የሃውልቱ መስርያ ገንዘብ ማገዷን እየተናገረች ነው።ለኢትዮጵያ የጮሃችሁ ለእውነት የቆማችሁ ፍሬው የመታየቱ አንዱ ማሳያ ነው።
ይህ ዜና ከ ጀርመን ድምጽ ራድዮ የሚያዝያ 23/2013 እ ኤ አቆጣጠር አማርኛው አገልግሎት ድህረ ገጽ ላይ  የተገኘ ነው።እንዲህ ይላል።


''ሮም ለግራዝያኒ ሐውልት የተሰጠው ገንዘብ ታገደ

ለኢጣልያው ፋሺስት ጀነራል ግራዝያኒ መታሰቢያ ሐውልት መሥሪያ የተመደበው ገንዘብ ትናንት እንዲታገድ መደረጉን የኢጣልያ ባለሥልጣናት አስታወቁ ። ሐውልቱ የተሰራበት አፊሌ  የተባለችው የግራዝያኒ የትውልድ ከተማ የሚገኝበት የላዝዮ ግዛት ባለሥልጣናት  ገንዘቡን የሰጠነው ተጭብረብረን ነው ሲሉ አስታውቀዋል ። የላዝዮ ፕሬዝዳንት ኒኮላ ዚንጋሬቲ  የአፊሌ ባለሥልጣናት የገንዘብ እርዳታ የጠየቁት ለመናፈሻ ግንባታና  ላልታወቀ ወታደር  ሐውልት መሥሪያ  እንጂ ለአወዛጋቢው ጀነራል ለግራዝያኒ ሐውልት መሥሪያ እንዳልነበር ተናግረዋል  ።  የላዝዮ ግዛት ለእርዳታ የመደበው 180 ሺህ ዩሮ ወይም 235 ሺህ ዶላር ለግራዝያኒ እስካሁን የተገነቡት መታሰቢያዎች ከአካባቢው እስኪነሱ ድረስ እንደማይሰጥ አስታውቋል ።  ጀነራል ግራዝያኒ በኢጣልያ ወረራ ወቅት በኢትዮጵያ የኬሚካል የጦር መሣሪያዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉና በርካታ ሠላማዊ ሰዎችም እንዲጨፈፈጨፉ  ትዕዛዝ ያስተላለፈ ፣ጨፍጫፊው የሚል ቅፅል የተሰጠው የጦር አዛዥ ነበር  ። የኢትዮጵያ አርበኞች ማህበርና በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን  ለፋሽሽቱ ግራዝያኒ ሐውልት መቆሙን በማውገዝ ጠንካራ ተቃውሞ ሲያስሙ ቆይተዋል ። ፋሺስት ኢጣልያ ከተሸነፈች በኋላ ግራዝያኒ ለፈፀማቸው የጦር ወንጀሎች በወታደራዊ ፍርድ ቤት 19 ዓመት ቢፈረድበትም 2 አመት ብቻ ታስሮ በነፃ ተለቋል ።''

Source-http://www.dw.de/ይዘት/ዜና/s-11648

Wednesday, April 24, 2013

''ህዝብ ለሕዝብ የኪነት ልዑክ'' በደርግ ዘመን ''የአባይ ግድብ ቦንድ ግዥ'' በዘመነ ኢህአዲግ -የሀገሬ አዙሪት(አጭር ማስታወሻ ለሀገሬ ልጅ)

በዘመነ ደርግ በ ፍ 1977 ዓም ኢትዮጵያ ገጥሟት የነበረው የድርቅ አደጋ መላው አለም ከጎኗ በመቆሙ  ኢትዮጵያ የኪነት ቡድኗን በመላው አለም እያዟዟረች ባህላዊ እና ዘመናዊ ሙዚቃዎቿን በማሳየት የምስጋና ቃሏን አሰማች።የኪነት ቡድኑም ሕዝብ ለሕዝብ የኪነጥበብ ልዑክ ተሰኘ።በእዚህ ሃሳቡን ከማመንጨት ጀምሮ ቡድኑን በመምራት በመላው አለም ይዘው የተዟዟሩት አምባሳደር ዶክተር ካሳ ከበደ የቀድሞው መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣን ነበሩ።

በልዑካን ቡድኑ ውስጥ አንጋፋ የኪነት ሰዎች  ጥላሁን ገሠሠ፣ብዙነሽ በቀለ፣መሐሙድ አህመድ እና ሌሎችም 
የተሳተፉ ሲሆን የዛሬው ተወዳጁ አክቲቪስት ታማኝ በየነም ተካቶበት ነበር።ቡድኑ በአሜሪካ፣አውሮፓ፣መካከለኛው ምስራቅ  ተገኝቶ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ከማሳየቱም በላይ በብዙ የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ የኢትዮጵያን ሌላውን ገፅታ በማሳየት አድናቆትን አትርፏል።ታድያ በወቅቱ ቡድኑ በሄደበት ቦታ ሁሉ እግር በእግር እየተከታተሉ ቡድኑን ይቃወሙ የነበሩ አንዳንድ ቦታ ለዱላ የትጋበዙ ከእዛ ባስ ሲል ደግሞ ግርግር በመፍጠር ዝግጅቱን ለማስቆም የሞከሩ የሻብያ፣የኢህአዲግ፣እና ሌሎች የደርግ ተቃዋሚዎች በእየዝግጅቱ አዳራሽ መግቢያ ላይ ነበሩ።አንዳንዶቹ ቦታዎች እንዲያውም ከያንያኑን አግቶ ለመውሰድ ሴራ ተጠንስሶ ነበር።አዎን በትክክል ለሚያስብ ሰው የሀገርን ገፅታ መቀየር መቃወም  አሳዛኝ ነው። የወቅቱ እሳቤ ግን ''ደርግ ሀገር ሰላም ነው ለማለት ነው----በመጀመርያ ሰብአዊ መብት ይከበር'' የሚል  ነበር።

መሃሙድ አህመድ (ሕዝብ ለሕዝብ ልዑክ አባል)
በዘመናችን ደግሞ ሌላ ሕዝብ ለሕዝብ ቡድን የአባይ ቦንድ ግዥ ሆኖ መጥቷል።አባይን መገደብ ሀገር ያለማል፣ወገን ያኮራል።የያነዎቹ የህዝብ ለሕዝብ ተቃዋሚዎች ሀገርቤት ገቡ እና የአባይ ግድብ ቦንድ ግዥ ይዘው እንደ ሕዝብ ለሕዝብ የኪነት ልዑክ በውጭ ለሚኖረው ኢትዮጵያዊ   ''የሀገር ገፅታ ይቀይራል ወገን ያኮራል ቦንድ ግዙ'' ብለው ጠየቁ።''ከአባይ ግድብ በፊት በመጀመርያ ሰብአዊ መብት ይከበር''ሆነ ጥያቄው።
የወጣው ቢገባም የገባው ቢወጣም ሀገሬ ከማይለቅ አዙሪት አልወጣችም።እውነትነት የሌላቸው ህዝብን ቀርቶ ቤተሰባቸውን በአግባቡ ማሳመን በማይችሉ ቃላት የሚሸነግሉ መሪዎች ተሸክማ ሀገሬ አሁንም አለችበት ቆማለች።
እንደዜጋ ማሰብ ''እሰይ አሳፈርኩት፣ኩም አድርጌ መለስኩ'' ሳይሆን ሃገሬ ከእዚህ አዙሪት የምትወጣው፣በዘረኝነት ላይ ከተመሰረተ አስተሳሰብ የምትላቀቀው ፣አባይንም በሕዝብ ፍቅር ላይ የምትመሰርተው፣''ሕዝብ ለሕዝብ የኪነጥበብ ልዑክ'' ካለአንዳች እረብሻ ለመላው አለም የምታሳየው  መቼ ነው? የሚለው ጥያቄ ነው ጥያቄው።ለእዚህስ የእኔ ድርሻ ምንድንነው? ነው ቀጣዩ ጥያቄ።

ጌታቸው በቀለ 
ኦስሎ 

Monday, April 22, 2013

ትኩረት- ኢትዮጵያ ''አይከን'' የሆኑ ሃገር በቀል መዋለ ንዋይ አፍሳሽ ባለ ሃብቶችዋን በተለያየ ምክንያት ማጣቷን ቀጥላለች።

 ቀደም ብለው እንደ አማልጋሜትድ ኩባንያ፣በያዝነው አመት ብቻ ደግሞ 
-የ አዋሽ ባንክ ስራ አስኪያጅ ሰው ገጭተዋል አልገጨሁም ንትርክ ፣

-የ ሆላንድ ካር ኩባንያ ተጨማሪ ብድር ድጋፍ በመፈለግ ብቻ ለኪሳራ ተዳርጎ ኩባንያው ከስራ ውጭ መሆኑን፣

-  የ አክሰስ ባንክ መስራች እና ኢንቨስተር አቶ አመልጋ ተመሳሳይ መሰል ችግር ገጥሟቸው ነገር ግን ተመልሰው የገጠማቸውን ችግር እንደሚቋቋሙ መግለጻቸው፣
ሚያዝያ 9 ቀን 2005 ዓ.ም. የ አያት አክስዮን ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ አያሌው እና ሌሎች ባልደረቦቻቸው ከቀረጥ ጋር በተያያዘ ፍርድ ቤት ቀርበው አቃቢ ህግ የሰባ አመቱን አዛውንት'' ከ ሰባ አመት በላይ እስር ይፈረድልኝ፣ያላቸው መኪናዎች ሁሉ ይወረሱ'' የሚል ጥያቄ አቅርቧል። በነገራችን ላይ አቶ አያሌው ለ አባይ ግድብ የ አንድ ነጥብ አምስት ሚልዮን ብር ቦንድ መግዛታቸው ከግንዛቤ ውስጥ መግባት እንደነበረበት ለፍርድ ቤቱ አሳስበዋል።ፍርድ ቤቱ ግን አልሰማም ፍርዱ ለ ሚያዝያ 29 ተቀጥሯል።
ከሪፖርተር ዕሁድ ሚያዝያ 13/2005 ዓም  ስለ ፍርድቤት ውሎው የተነበበው ዘገባ ውስጥ እንዲህ የሚል ይገኘበታል።
''አቶ አያሌው ዕድሜያቸው 70 ዓመት መሆኑን፣ ከ15 ዓመታት በላይ በተለያዩ ሕመሞች ማለትም የልብ ቀዶ ሕክምና እንደተደረገላቸው፣ የደም ግፊት፣ የጀርባ ሰረሰር ጉብጠትና የነርቭ ሕመምተኛ መሆናቸውንና ሌሎችንም በመጥቀስ ፍርድ ቤቱ ከግምት ውስጥ በማስገባት እንዲመለከትላቸው ጠይቀዋል፡፡ ፀባያቸው መልካም መሆኑን የሚኖሩበት ክፍለ ከተማ ወረዳ ጽሕፈት ቤት በደብዳቤ ማረጋገጡን፣ የ15 ቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆናቸውን፣ ባለቤታቸው የልብና የስኳር ሕመምተኛ መሆናቸውን፣ እህታቸው የዓይን ግርዶሽ ታማሚ መሆናቸውንና እርሳቸው እየረዷቸው እንደሚኖሩም አስረድተዋል፡፡

በትምህርት ዘርፍ ከ1974 ዓ.ም. ጀምሮ በግል ተልዕኮ (ርቀት) ትምህርት በመሰማራት ለበርካታ ወገኖች የላቀ ጠቀሜታ ማስገኘታቸውን፣ በሪል ስቴት ልማት ፋና ወጊ መሆናቸውንና የቤት እጥረትን ለማስወገድ የላቀ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን በመዘርዘር፣ ፍርድ ቤቱ እንዲመለከትላቸው በቅጣት ማቅለያ ሐሳባቸው ላይ አስፍረዋል፡፡ አያት አክሲዮን ማኅበር 2,468 ቋሚ ሠራተኞችና ጥቃቅን ድርጅቶች በሥሩ እንዳሉ፣ ማኅበሩ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ከ310 ሚሊዮን ብር በላይ ለመንግሥት ገቢ ማድረጉን፣ ለዚህም አስተዋጽኦ እሳቸው ሥራ አስኪያጅ ሆነው በሚሠሩበት ጊዜ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ይኼንንም በማቅለያነት እንዲመለከትላቸው ጠይቀዋል፡፡ 

የውጭ አገር ቤት ገዥዎችን በማፈላለግ በተለያዩ አገሮች የሚኖሩ ሰዎች በውጭ ምንዛሪ እንዲገዙ በማድረግ በድምሩ ከ145 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ እንዲገባ ማድረጋቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ትምህርት ቤቶችን በመሥራት አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን፣ የጤና ጣቢያዎችን ከሐኪሞች መኖሪያ ጋር ሠርተው ማስረከባቸውን፣ የገበሬ ማሠልጠኛ ገንብተው ማስረከባቸውን፣ የአትሌቲክስ ስፖርትን ለማጠናከር አሠልጣኝ መቅጠራቸውን በዝርዝር በመግለጽ ባደረጉት አስተዋጽኦ መሠረት ፍርድ ቤቱ በማቅለያነት እንዲወስድላቸው አመልክተዋል፡፡ 

በአዲስ አበባ የወጣቶች ማዕከል መገንባታቸውን፣ በትግራይ ‹‹ከዳስ ወደ ክላስ›› በተሰኘ መፈክር በመማር ማስተማሩ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን፣ በ1998 ዓ.ም. በድሬዳዋ ለደረሰው የጐርፍ አደጋ አንድ ባለአንድ ፎቅ ሕንፃ ገንብተው ማስረከባቸውን፣ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ ሲከበር ከፍተኛ ወጪና ቁሳቁስ በማቅረብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን፣ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ድርጅቱ የ340 ሺሕ ብር ስጦታና የ980 ሺሕ ብር ቦንድ ግዢ፣ አቶ አያሌው የ100 ሺሕ ብር ስጦታና የ200 ሺሕ ብር የቦንድ ግዢ መፈጸማቸውንና ለአገራቸው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን ማስረጃ በማያያዝ ለፍርድ ቤቱ አቅርበው፣ በማቅለያነት እንዲወስድላቸው ጠይቀዋል፡፡ እንዲሁም ለኢሕአዴግ በተለያዩ ጊዜያት ለተከናወኑ ፕሮግራሞች አቶ አያሌው አንድ ሚሊዮን ብር መስጠታቸውንና በማረሚያ ቤት ቆይታቸውም ባላቸው መልካም ፀባይ የተለያዩ የምሥጋና ደብዳቤዎች እንደደረሳቸው በማስረዳት፣ ፍርድ ቤቱ ሁሉንም የቅጣት ማቅለያ ጥያቄዎችንና ማስረጃዎቻቸውን በመመልከት ዝቅተኛ ቅጣት እንዲወስንላቸው ጠይቀዋል፡፡ ''
ኢትዮጵያ ''አይከን'' የሆኑ ሃገር በቀል መዋለ ንዋይ አፍሳሽ ባለ ሃብቶችዋን በተለያየ ምክንያት ማጣቷን ቀጥላለች። 

Saturday, April 20, 2013

ኢህአዲግ የአባይን ግድብ የቦንድ ሽያጭ በባህር ማዶ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን መተንኮሻ አድርጎታል።

ዛሬ እነሆ በኖርዌይ እንዲህ ሆነ

ከኖርዌይ ከተሞች ውስጥ በደቡባዊ ክፍል የምትገኘው ስታቫንገር ከተማ ዛሬ ሚያዝያ 12/2005 ዓም በስዊድን የኢትዮጵያ አምባሳደር / መብራት በተገኙበት ለአባይ ግድብ ቦንድ ሽያጭ የተዘጋጀው ዝግጅት ከኦስሎ ስምንት ሰዓታት በላይ በአውቶቡስ ተጉዘው በስብሰባው በተገኙ ኢትዮጵያውያን በገጠመው ከፍተኛ ተቃውሞ ሙሉ በሙሉ ዝግጅቱ ተሰርዞ አምባሳደሯ በፖሊስ ቦታውን ለቀው  እንዲሄዱ ተመክረው አዳራሹን ለቀው ወጥተዋል።

በመርሃግብሩ መክፈቻ ላይ በሥርዓት ተቀምጠው የተገኙት ኢትዮጵያውያን መርሃግብሩ ከመጀመሩ በፊት ''በዘመነ ኢህአዲግ የተገድሉትን ኢትዮጵያውያን በቅድሚያ በህሊና ፀሎት እናስብ ይህንንም ለማድረግ ሁላችንም ከተቀመጥንበት እንነሳ'' በማለት አምባሳደሯም እንዲነሱ እና አብረው በፀሎት እንዲያስቡ ይጠይቃሉ።አምባሳደሯም ሆኑ አብረዋቸው የመጡት ፈቃደኛ አልሆኑም። በመቀጠል ኢትዮጵያውያኑ እንግዲያው ስለ አባይግድብ አሁን ልንነጋገር አንችልም በማለት ያስታውቃሉ።በእዚህ መሃል ከፍተኛ የተቃውሞ ድምፅ መሰማት ይጀምራል። 
''ከአባይ በፊት ሰብአዊ መብት ጥሰት ይገደብ!''
''የሙስሊሙ ድምፅ ይሰማ!''
''የኢትዮጵያውያን ድምፅ ይሰማ!''
''የዘር መድሎ ይቁም!'' (stop apartheid in Ethiopia!'' ወዘተ የሚሉ መፈክሮችን በማሰማት ላይ ሳሉ የኖርዌይ ፖሊስ ሁኔታውን ለማረጋጋት ሁሉም እንዲቀመጡ ይነገራቸዋል። በእዚህን ጊዜ ግን ኢትዮጵያውያኑ የኮኮብ ምልክት ያለበትን ከአምባሳደሯ ጀርባ ባለው ግድግዳ ላይ የተለጠፈውን ባንዲራ የኢህአዲግ አርማ ኮኮብ በሌለበት ኢትዮጵያ ባንዲራ ሸፍነው ጨርሰው ነበር።
ፖሊሱ ኢትዮጵያውያንን ካስቀመጠ በኃላ ቀጥሎም ሁኔታው ደህና መሆኑን ለማስረዳት ይሞክራል።በእዚህ መሃል ኢትዮጵያውያኑ ይብሱን  ቁጣቸውን በዜማ ይቀጥላሉ።

''ተከብረሽ የኖርሽው ባባቶቻችን ደም 
 እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም የደፈረሽ ይውደም''

ይህን የተመለከቱት ፖሊሶች ኢትዮጵያውያኑን ከማስወጣት አምባሳደሯን ማስወጣት ትክክለኛ እርምጃ እንደሆነ ስለተረዱ አንዱ ፖሊስ ወደ አምባሳደሯ ቀርቦ አዳራሹን ለቀው እንዲወጡ በቃልም በእጁም መውጣት እንዴት እንደሆነ እያሳየ ይነገራቸውል። አምባሳደር መብራት ቦርሳቸውን አንስተው ወደ አዳራሹ ዘወር እያሉ እየተመለከቱ ወደ በሩ አዘገሙ። ኢትዮጵያውያኑ ቀጠሉ።

''ተከብረሽ የኖርሽው ባባቶቻችን ደም 
 እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም የደፈረሽ ይውደም'''
''ሌባ ሌባ አለ ገና አለ ገና!'' አምባሳደሯ ፈጠን ባለ እርምጃ በፖሊስ ታጅበው ወደ መኪናቸው ሄዱ።








ኢህአዲግ የአባይን ግድብ የቦንድ ሽያጭ በባህር ማዶ የሚኖሩ  ኢትዮጵያውያንን መተንኮሻ አድርጎታል።

ማንም ኢትዮጵያዊ አባይ ቢገደብ ኢትዮጵያ ከድህነት ብትወጣ አይጠላም።ዛሬም  ተቃውሟቸውን የገለፁት ኢትይጵያውያን ለኢትዮጵያ ሞት የሚመኙ ሆነው አይድለም።ኢህአዲግ ግን በውጭ የሚኖረውን ኢትዮጵያዊ ያሳጣ እየመሰለው ብዙ ተቃዋሚ አለ ብሎ የሚያስበበት ቦታ ሁሉ አባይ ግድብ ቦንድን ካርድ እየመዘዘ የልዩነት መስመር በኢትዮጵያውያን መሃከል ይፈጠራል ብሎ ያስባል። ለእዚህም አይነተኛ ማስረጃው የመጀመርያው የአባይ ቦንድ ሽያጭ ዝግጅት በዋሽግተን ዲሲ  ሲዘጋጅ ብዙ ኢትዮጵያውያን ካርድ ወስደው አክትቪስት ታማኝ በየነን ጨምሮ ወደ ስብሰባው ቦታ ሲሄዱ ''የእንጀራ ልጅ እና የቤት ልጅ'' በሚል መለያ አድርጎት ''አንተ አትገባም አንተ ግባ'' እያለ መለየት ጀመረ። 
''በሀገራችን ጉዳይ ያለንን ሃሳብ መስጠት እንፈልጋለን ካርድ ይዘናል'' ያሉ ታማኝንም ጨምሮ  እንዳይገቡ ተከለከሉ። 

በወቅቱ የሚገቡት ኢትዮጵያውያን ምንም አይነት ሃሳብ ቢኖራቸው ሃሳባቸውን መስማት እና ምላሽ መስጠት ያን ቀን መግባባት ባይቻል ለቀጣይ ሌላ ስብሰባ አድርጎ መመካከር የጤነኛ መንግስት ልዑክ አሰራር ነበር።ኢህአዲግ ግን ከመጀመርያው የአባይ ግድብን ሲያነሳ በባህርማዶ ያለው ሕዝብ ሲቃወም በሀገር በት ያለው መደገፉ ስለማይቀር ይለያያል። በውጭ ያለውም ብሔራዊ ስሜቱ አይሎ እርስ በርሱ ይከራከራርል የሚል ታሳቢ ያደርገ አቀራረብ ስለነበረው በዋሽግተኑ ስብስባ ላይ እራሱ ኤምባሲው በድብዳቤ የጠራቸውን ሁሉ ተምታተውበት አላስገባም አለ።ኢትዮጵያውያን በገዛ የሀገራቸው ጉዳይ ባይተዋር ሆኑ።


በእንደዚህ አይነት የተጀመረው አባይ ጉዳይ ይሄው ኢህአዲግ እስካሁን ድረስ እንደማስይሳካ እያወቀ በባህር ማዶ የሚኖሩ ተቃዋሚዎች እና የሀገራቸው ጉዳይ የእግር እሳት የሆነባቸውን ኢትዮጵያውይንን መተንኮሻ አድርጎ ይጠቀምበታል።በነገራችን ላይ ይሄው ተመሳሳይ መርሃግብር በኦስሎ አፕሪል 23/2013 መርሃግብር መያዙን ከአምባሲው ድህረገፅ ላይ የተለጠፈው ማስታወቂያ ያስነብባል። ሃገራዊ ህብረት ሳይፈጠር፣ዜጎች ከአንድ ክልል ወደ አንድክልል ካልፈቃድ ለምን ገባችሁ ተብለው እየታሰሩ(የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ቤንሻንጉል ክልል ለመታሰር ያበቃቸው) በሺዎች መሬት እና ንብረታቸውን ተነጥቀው ሲንከራተቱ አንዳች ያልተናገረው መንግስት ይህም ከፍተኛ ተቃውሞ በኢትዮጵያውያን ዘንድ በፈጠረበት በእዚህ ጊዜ ስለ አባይ ግድብ ቦንድ ግዙ ብሎ መጠየቅን ምን ስም እንስጠው?

ጉዳያችን Gudayachn


ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።