ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, April 15, 2013

''አቤት በሉን''...''ለምን ልጣት ለምን ትዘን፣ ሆናኝ ጎኔ ለኔ በዚች አለም።''

ከእዚህ በታች የምታገኙት ግጥም እና ዘፈን ከያንያኑ ለሴት ልጅ መብት የደረሱት እና ያቀነቀኑት ነው። ነገር ግን ሀገር በሴት(እናት)  ትመሰላለች እና ለእናት ሀገር ብለው ቢሰሙት የማይሆንበት ምን ምክንያት አለ? 

አቤት !አቤት በሉን አቤት ስሙን ፣
መልክት አለን እዚህ ቤት ፣
አቤት በሉኝ አቤት መልክት አለኝ እዚህ ቤት። 
አቤት በሉን አቤት መልክት አለን እኛ ስለኛ።
----------እንዳንለያይ እንዳንለያይ አደራ።

እንውጣ ነቃ ብለን፣

እናስብ እንችላለን።

የናቁት አንድቀን ያደርጋል እራቁት፣

ንገሩት ለእዛ ሰው ምከሩና አንቁት።

ያክብረኝ ላክብረው መናናቁም ይቅር፣

መቸም የትም ቢሆን ያሸንፋል ፍቅር።

ለምን ልጣት ለምን ትዘን፣

ሆናኝ ጎኔ ለኔ በዚች አለም፣

የኛ ፡ የሁላችንም ድምጽ (ኢትዮ ገርልስ ግሩፕ እና ሃይሌ ሩት)

አጥታ ሰው ከጎኗ አቅሟም አንሷት፣

ላያት አልፈልግም ከፍቷት ብሷት፣

እንግዲህ ቻልኝ እሷን ልደግፋት፣

እንዳላየሁ ሆኘ ስንቴ አለፍኳት፣

ግን አሁን ይብቃኝ ልቁም ጎኗ፣

አለም ካለርሷ ሙሉ አትሆንምና።

ለምን ልጣት ለምን ትዘን፣

ሆናኝ ጎኔ ለኔ በዚች አለም።

ተነስተናል ቆርጠናል፣

ይሄው መጥተናል ።

ይበቃናል የድሮ፣ 

ተነስተናል ዘንድሮ። 
ተነስተናል ድሮ ተንቀናል፣

ባሳለፍነው ሰዎች ከፍቶናል 

ተነስተናል ዛሬ ቆርጠናል፣

ፍቅር ጥበብ ተስፋን ይዘናል፣

ተደፍረናል ድሮ ተንቀናል፣

ባሳለፍነው ሰዎች ከፍቶናል


1 comment:

Anonymous said...

Gitum girum etsub etsub new wendimschin.

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።