ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, September 29, 2022

ኢትዮጵያ ፬ ቁልፍ ጉዳዮችን የቅድምያ ቅድምያ ካልሰጠች ያሰጋኛል።

 
==========
ጉዳያችን
=========

ዓለም እየገባችበት ስላለው ማጥ በሚገባ አልተነገረንም

ዓለማችን አሁን ያለችበት ሁኔታ የትኛውም ሚድያም ምሑርም ሆነ ተንታኝ በሚገባ እየነገሩን አይደለም።ምሑራዊ ብልግና፣ጋዜጠኛዊ አድርባይነት እና ተንታኛዊ አሽቃባጭነት በዝቷል። የምዕራቡ መገናኛዎች በቀዝቃዛው ጦርነት ጊዜ ከነበሩበት ወርደዋል።የዩንቨርስቲ ምሑራን ለሰው ልጅ እና ለትውልድ ቀጣይነት የሚያስቡ እና እውነቱን የሚያወጡ ሳይሆኑ የጥናት ጽሑፎቻቸው ሁሉ በአዋጪ የገንዘብ ጥቅም ላይ ተመስርተው ማሰብ አናውዟቸዋል። ስለሆነም ዓለም ወደ ከባዱ እና የማይቀረው ታላቅ ጦርነት ለመግባት ዳር ዳር እያለች ነው። የዩክሬኑ ጉዳይ ጧት እና ማታ ይነገራል እንጂ የግሪክ እና የቱርክ መገናኛ ብዙኃን ጧት ማታ የሚያወሩት የቱርክ ድሮኖች የግሪክን ድንበር ጥሰው መግባታቸው፣ግሪክ ቱርክ ለወረራ እየተዘጋጀች እንደሆነ ነው። የሰርብና የክሮሽያ፣የአዘርባጃንና አርመን በየቀኑ ያሉ ውጥረቶች የት እንደደረሱ ገና አልሰማንም።መጪው የሚፈራው የባልካን አገሮች በተለይ ሰርብያ በሩስያ ድጋፍ የቀድሞ የዩጎዝላቭያ ግዛት ግጭት እንደ አዲስ ተወጥሯል።አውሮፓ እና ሩስያ የገቡበት የጋዝ እቀባ ሁሉ የዋናው ግጭት ዳር ዳርታ ናቸው።ይህ ሁሉ በያዝነው እና ባለፈው ሳምንት ያሉ እና እያደጉ የመጡ ውጥረቶች ናቸው እንጄ የቆዩ አይደለም።በዓለም ዜና ላይ ግን የሉም።

አገር መሆን ያቃታቸው እና እንደአገርነት አሉም እንዳል በዓለም መድረክ የማይታዩ መንግስታት ፈልገን ያላገኘንላቸው፣የሉም እንዳንል ለጊዜው የጦርነቱ ቋያ የበረደ የመሰለላቸው፣ውሏቸው እና አዳራቸውን የማናውቅላቸው ሊብያ፣ኢራቅ፣የመን፣ሶርያ እና ሱማሊያ የዓለም ''ፖሊስ'' አገሮች ባደረሱባቸው ግፍ ቂም አርግዘው ኖረው በደረሰበት ሲብከነከን ያደገው አዲስ ትውልድ ለአቅመ ትውልድ ደርሶ የደረሰበትን ከእነማን ጋር ተሰልፎ ምን እንደሚያደርግ ማወቅ አይቻልም።

ሩስያ ከዩክሬን ጦርነት የምዕራቡ የመረረ ምላሽ ተምራ መጪው ጊዜ ከኔቶ ጋር የሚኖራት ግጥምያ ከሚገባው በላይ እያሰበችበት እንደሆነ ግልጽ ነው። ቻይና በታይዋን ጉዳይ ብቻ አይደለም የምጣኔ ሃብት ጦርነቱ በንግድ ሥራ ብቻ ሳይሆን በጦር ሜዳ የበላይነትም እንደሚፈታ አልገባትም ማለት ጅልነት ነው።ኔቶም ሆነ የምዕራቡ ዓለም ምጣኔ ሃብቱ ብቻ ሳይሆን ሁሉም መንገዶች ወደ ጦርነት እየተጓዘ እንደሆነ ገብቶታል።ነገር ግን ሚድያዎቹ እውነቱን አፍረጥርጠው እንዲያወሩ አይፈቅድላቸውም።ከእዚህ ይልቅ ህዝቡን የንግስት ቀብር ወይንም ሌላ ጉዳዮች ካሉ በእዚያ ህዝቡን ወጥሮ ከጭንቀቱ ማስታገስ ነው የተመረጠው።  አሁን ያለው ዓለም ኃያላኑ በአንድ ጊዜ ወደ አጠቃላይ ጦርነት የሚገቡበት አይደለም።ነገር ግን በየቦታው ቀደም ብለው በለኮሷቸው ጦርነቶች እነርሱ ከጀርባ ሆነው ይዋጋሉ።በመቀጠል ወደ አጠቃላዩ ግጭት ይገባሉ።አንዳንዴ ማርክስ ''ኢምፔራሊዝም ከፍተኛ የእድገት ደረጃ ሲደርስ የጥሬ ዕቃ እና የገበያ ሽምያው ዓለምን ወደ ጦርነት ይመራታል'' ያለውን ደግሞ ማየት ያስፈልግ ይሆን? ያስብላል። 

ኢትዮጵያ!

ኢትዮጵያ አሁን ያለውን የዓለም አካሄድ በደንም መረዳት ያለባት ጊዜ ነው።መሪዎቿም ሆኑ ህዝቧ እውነታውን ጥርት አድርገው ማወቅ አለባቸው።ዓለም ወደጦርነት የመግባቱ አደጋ ግልጽ ነው።ይህንን ሲኤንኤን በማየት አይገመትም። ምክንያቱም ሚድያዎቹ እንደዘመኑ 'የፊት ሜክአፕ' ብዙ ነገሮች ተቀባብተው ጓዳቸውን ሸሽገው ነው የሚቀርቡት።በሩስያ ላይ የተደረገው የእቀባ መጠን እና ስፋት ብቻ ሳይሆን አሁን ላለው የየትኛውም የዓለም ጦርነቶች የሚዳኛ አንድም አቅም ያለው ተቋም የተባበሩት መንግስታትን ጨምሮ የለም።ይህ ብቻ አይደለም ጦርነቶች እንዳይደረጉ የሚያደርግ ዓለም አቀፍ የሰላም እንቅስቃሴ ብቻ ሳይሆን ከአርባ እና ሃምሳ ዓመታት እንደነበሩት ዓይነት የተራው ህዝብ ንቅናቄዎች የሉም።ስለሆነም በማንኛውም ሰዓት የሚሆነውን የምናየው ከሆነ በኋላ ነው።

ይህ የዓለም መጪው ሁኔታ እና ኢትዮጵያ በውስጧ ያለውን ችግሮች ለመፍታት፣የውጭው ማዕበል እንዳይመታት የውስጥ ሞገድ እንዳያናውጣት መንግስቷም ህዝቧም ተስማምተው መስራት የሚገቧቸው ፬ ቁልፍ ጉዳዮች አሉ።

፩/ የብቁ ዜጋ ስልጠና (የቀድሞው ብሔራዊ ውትድርና) መጀመር
  • ኢትዮጵያ የመቶ አስር ሚልዮን ሕዝብ ነች።አስፈሪነቷ በህዝቧ ቁጥር ብቻ አይደለም።የስድስት ወርም የውትድርና ስልጠና የወሰደ ወጣት መኖሩ ብቻ የኃይል ሚዛኗን በቀጠናውም በዓለምም የሚያስደምጣት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ውትድርና ወስዶ ቢያንስ ለስድስት ወራት የሰለጠነ ወጣት ሲኖራት ነው። የአገሮች የኃይል ሚዛን በበኛ ሰራዊቱ ብቻ አይለካም በሰለጠነው ወጣት እና ተጠባባቂ ኃይልም ጭምር ነው። ስለሆነም የሰለጠነ የሰው ኃይል በሰላም ጊዜ ብቁ ዜጋ ማፍርያ፣በቀውጢ ጊዜ ጉልበተኛ ማስታገሻ ነው። ኢትዮጵያውያን በቀድሞ ዘመን ልጁን ተኩስ እና ጉግስ ሳያስተምር የማያልፍባት ኢትዮጵያ ዛሬ በዘመናዊ መልክ ልጆቿን የብቁ ዜጋ ስልጠና መስጠት አለመጀመሯ አደጋ አለው።
  • ስልጠናው በግድ ከሚሆን ይልቅ በፈቃደኝነት የስልጠና ግዴታቸውን የተወጡ የተሻለ የሥራ እና የትምህር ዕድል እንዲያገኙ ብቻ ሳይሆን ልዩ የመጠርያ የክብር ተቀጥላ ስም መስጠቱ እና በሕብረተሰቡ ውስጥ ልዩ ክብር እንዲያገኙ በማድረግ እና ስሙን ጥሩ ያልሆነ ሥም ከተለጠፈበት ብሔራዊ ውትድርና ወደ የብቁ ዜጋ ስልጠና መቀየሩ የራሱ የሆነ በጎ ተጽዕኖ ይኖረዋል።
  • የብቁ ዜጋ ስልጠና ወይንም ብሔራዊ ውትድርና ግዴታ ያልሆነበት የአውሮፓ አገር ማን ነው? ኖርዌይ፣ስዊድን፣ጀርመን እና ሌሎች የአውሮፓ አገሮች ወጣቶች የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ ለወታደራዊ ስልጠና መግባት ቅድመ ሁኔታ ነው።ወደ ስልጠናው የገባ የዩንቨርስቲ መግብያ ነጥብ ብቻ ሳይሆን ሥራ ለማግኘት ቅድምያ አለው።
  • እነኝህ የአውሮፓ አገሮች አሁን ያላቸው ሰላም እያለ ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት ማብቃት በኋላም ወጣቶቻቸውን የሚያሰለጥኑት ከውትድርና ክህሎቱ ጋር ስልጠናው በራሱ ብቁ የሆነ ዜጋ ማፍርያ እንደሆነ ስለሚያምኑበት ነው።
፪/ የሥራ ባሕል እንደ የባሕል አብዮት መጀመር አለበት።
  • ማንም እጅ እና እግር ያለው በቀን አንድ ሥራ ሳይሰራ የማይውልበት የባሕል አብዮት ያስፈልጋል።
  • ኢትዮጵያ ከጎረቤት የአፍሪካ አገሮች ጋርም ሲነጻጸር የከተሜው ወጣት የሥራ ባሕል መቀየር አለበት።
  • ትምሕርት ቤት፣የሃይማኖት ተቋማት፣ሚድያውና ወላጆች በልዩ መልኩ ሊመክሩበት ይገባል።
  • ሥራ ሲባል ከቤት ያለው የቤተሰቡ የቀን ከቀን ሥራዎች እስከ ማንኛውም ድረስ ለሥራ ያለው ክብር ብቻ ሳይሆን ባሕል መሆን አለበት። ይህ ደግሞ ከስነ ልቦና ዝግጅት እና ማነቃቃት ጀምሮ የሚሰራ ሥራ ነው።
  • አገር በወታደር አይወረርም የሥራ ባሕል እንዳይኖረው ጫት እና ሕልመኛ ብቻ እንዲሆን ግን ባዕዳኑም በረቀቀ መልኩ ሰርተውብናል፣እኛም ችላ ብለነዋል።ጉዳዩ ግን አገር ይሰራል፣አገር ያፈርሳል።
፫/ ቤተ ዕመንቶች ያለባቸው የአስተዳደር ብልሹነት እና ንቅዘት እጅግ በቶሎ መስተካከል አለበት 
  • ይህ ካልሆነ እንደ ኢትዮጵያ ላለ አማኝ ህዝብ ላላት አገር የብዙ ምጣኔ ሃብታዊ፣ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ እንዲሁም የጸጥታው የተለየ መታወክ ሁሉ የቤተ ዕምነቱ ንቅዘት ውስጥ ተሸሽጓል።
  • ይህንን በቶሎ አለማድረግ ኪሳራው ቀላል አይደለም።አዲስ የሚመጣው ትውልድ ግዙፍ እና ስሜታዊ ግብግብ ከዕመነት ተቋማቱ ጋር ገብቶ ለማስተካከል ሊነሳ ይችላል።ይህ ደግሞ በራሱ ይዞ የሚመጣው ጥፋት አለ።
  • ስለሆነም ቀድሞ ማስተካከል ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ 
፬/ የተረሳው የአነስተኛ እና ጥቃቅን ንግድ ማስፋፍያ ልዩ ድጋፍ 
  • ነስተኛ እና ጥቃቅን በምጣኔ ሃብት ኢመደበኛ ምጣኔ ሃብት የሚለው ይተካከለዋል።አነስተኛ እና ጥቃቅን የሚለውም አሉታዊ ዕሳቤ ጥሎ ስላለፈ ወደፊት ስሙ ተቀይሮ መቅረብ ሊያስፈልገው ይችላል።
  • የአነስተኛና ጥቃቅን ንግድ ዘርፍ የህወሃት/ኢሃዴግ መንግስት አበላሽቶት ከማለት ይልቅ አተረማምሶት ሄዷል።
  • ዘርፉ ግን ያደጉ አደጎችም ኢመደበኛ ዘርፍ በሚል በቢልዮን የሚቆጠር ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ የሥራ ዕድል የፈጠረ ዘርፍ ነው።
  • በኢትዮጵያ ደግሞ በከፍተኛ ትምሕርት ገብቶ ከተማረው ውጭ ከፍተኛ የሥራ ዕድል መፍጠርያ ብቻ ሳይሆን በልምድ እና በሚሰራው አነስተኛ ንግድ ክህሎት ከፍተኛ ዕውቀት ያለው ህዝብ ያለበት ነው።ነገር ግን የካፒታል፣የሂሳብ አያያዝ፣የፈጠራ ክህሎት ማዳበርያ እና የመሬት ድጋፍ ከመንግስት እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ይፈልጋሉ።
  • የኢትዮጵያ የምጣኔ ሃብት ጉዳይ ሲነሳ የኢኮኖሚ አማካሪዎችም እየረሱት የመጡት እና ሚናውን ማሳየት የተዉት እንዲሁም መንግስት በዘርፉ ዙርያ አለመስራቱ የአገር ውድቀት መሆኑን የሚያሳይ የምጣኔ ሃብት አማካሪ ብዙም አይሰማም።
  • ህወሃት/ኢህአዴግ ዘርፉን የፖለቲካ መጠቀምያ ብቻ ሳይሆን ዘርፉ ላለፉት ሰላሳ ዓመታት የኢትዮጵያን አነስተኛ ንግድ ወደ መካከለኛ እና ከፍተኛ ደረጃ አሳደገው ወይ? ብለን ብንጠይቅ የሚጨበጥ ነገር የለም።ሁሉም ከፕሮፓጋንዳ ያላለፈ እንደ ሳሙና አረፋ ኩፍ ብሎ ታይቶ የጠፋ ጉዳይ ሆኗል።
  • አሁን መንግስት የተቸገሩትን በበዓል ሲደጉም በቴሌቭዥን ከሚያሳየው የበጎ አድራጎት ሥራ በተለየ ወጣቱን ከፖለቲካ ተጽዕኖ በተለየ እና ህወሃት/ኢህአዴግ ከሄደበት ስህተት የታረመ የአነስተኛ እና የጥቃቅን ንግዶች እና ማምረቻዎች እንዲስፋፉ ፖሊሲውን በሚገባ መከለስ እና የገንዘብ ተቋማትም ሆኑ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመጋጋቢ ሥራ እንዲሰሩ ማድረግ ያዋጣል።
  • የእዚህ ጽሑፍ አቅራቢ በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ እና በአዲስ አበባ ከተማ ንግድ እና ኢንዱስትሪ ውስጥ እንደመስራቱ የዘርፉ ወሳኝነትና የህወሃት/ኢሃዴግ ስህተት ምን እንደነበር የመረዳት ዕድሉ ገጥሞታል። በመሆኑም ዘርፉ ክብር ተሰጥቶት እና ከፍተኛ ባለሙያዎች ዘርፉን እንዲደግፉ ቢመደቡ የኢትዮጵያን ምጣኔ ሃብት ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ የሥራ ዕድል የመፍጠር አቅሙ  ከፍተኛ እንደሆነ ያምናል።ዘርፉ ከኢትዮጵያ ባሕል እና አኗኗር አንጻር የተለየ ጥናት ማድረግም የሚፈልግ ነው እንጂ የዓለም ባንክ ባለሙያዎች ባስቀመጡት አሰራር ብቻ መሔድ ለሁሉም በሽታ አንድ አይነት ኪኒን የመስጠት ያህል የቀደመው አካሄድ አያዋጣም።
  • በኢትዮጵያ የከተማ ከንቲባዎች ለተወሰኑ ምስኪኖች የሚበላ እና መጠለያ ሲሰጡ መታየታቸው በጎ እና ሊበረታታ የሚገባው ነው።ነገር ግን ከእዚሁ ጋር የአነስተኛ እና ጥቃቅን ንግድ ማስፋፍያ ሥራዎች አብዛኛውን ወጣት አቅፎ መንቀሳቀስ አለበት።
  • ዘርፉን ባለሃብቶች እንዲደግፉት ማድረግ እና ልዩ የሃገር ውስጥ ፈንድ ከተሞች እንዲሰበስቡ እና ለወጣቶች ሥራ ማስጀመርያ እንዲያግዙ ማድረግ ያስፈልጋል።
  • ዘርፉ ከፍተኛ ዕውቀት፣ልምድ እና አቅም ያለው የሰው ኃይል የሚመራው እንጂ እንደ ህወሃት/ኢሃዴግ በካድሬ መቀለጃ ሆኖ እንዲያልፍ ማድረግ አገርን ደግሞ መግደል ነው። 
ኢትዮጵያ ከላይ የተጠቀሱት ፬ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ በፍጥነት ካልሰራች የብዙ ችግሮቿ መተብተብያ ክር ለመፍታት እንዳትቸገር ያሰጋኛል።

================///===========



  


Saturday, September 24, 2022

“I Have Seen With My Own Eyes Young People Being Killed By The Leaders Of The TPLF Because They Retreated.” TPLF journalist Fitsum Tsegaye

ጋዜጠኛ ፍጹም ጸጋዬ Journalist Fitsum Tsegaye 
===============
''በጦርነት አንሳተፍም ብለው የተመለሱ የትግራይ ወጣቶችን የህወሃት መሪዎችሲገድሉ እኔ እራሴ 'በዓይኔ በብረቱ' አይቻለሁ።የትግራይ እናቶች ልጆቻቸውን ከሽብርተኛው ቡድን የሚደብቁበት ስፍራ አላገኙም።'' በእዚህ ሳምንት በመከላከያ የተማረከው የህወሃት ጋዜጠኛ ፍጹም ጸጋዬ።
-========
Mothers in Tigray have no place to hide their children from the terrorist group that is snatching them away.
=========
SCOOP Independent News
Saturday, 24 September 2022, 10:35 pm
==========

The terrorist TPLF started the recent war on Kobo front to exacerbate the sufferings of the people of Tigray who endured miseries by the offensives of the group for two rounds, Fistum Tsegaye, a journalist of the terrorist group TPLF who has surrendered to the National Defense Force revealed.

Mothers in Tigray “have no place to hide their children from the terrorist group that is snatching them away.”

During its 27 years rule of the country, the terrorist group has committed many atrocities and crimes against Ethiopians.

In those years of reign of terror, people were tied up together with hyena; others were kept in dungeons with their hands and feet tied for years. Some persons suffered from injuries as a result of burns inflicted by pouring burning plastics on their bodies.

After the terrorist group was removed from power by a popular protest, it committed treasonous attack on the Northern Command of the National Defense Force, in cooperation with Ethiopia’s historical enemies, and carried out invasions that threatened the country’s existence.

By denying the people of Tigray from receiving humanitarian assistance, the terrorist group has shown its cruelty to the people by forcing children to war as it cares little for the people.

Speaking to ENA, the journalist who surrendered to the NDF said the terrorist TPLF snatched children from mothers of Tigray, abandoning the elderly without support.

The journalist noted that the terrorist group, which has been extending its existence by inciting conflict, has proved that it is against peace by launching a third round of attack on the people of Ethiopia.

Fistum stated that even if the people of Tigray have been pleading with the group to end the war and solved the problems through peaceful means, the terrorist group launched the war.

The terrorist TPLF launched the war on Kobo front, disregarding the sufferings of the people of Tigray who endured miseries by the previous offensives.

For the third time, it launched attack and tries to deceive the people of Tigray by lying that the Ethiopian government started the war, he elaborated, adding that this confrontation has exacerbated the problems of the people of Tigray.

According to Fistum, neither the international community nor the people of Tigray should be confused by the false information and propaganda of the terrorist group.

The journalist revealed that there is no youth in Tigray who wants to go to the war front. However, the children and youth who flee to other zones and kebeles to escape from the terrorist group’s network would be seized and taken to war.

“The children and youth of Tigray are being hunted and forced to go to war. And the terrorist group shoots those who retreat with its killing squads,” he added.

The journalist said the youth lacked options as they were killed from behind when they fled and death became their only option.

“I have seen with my own eyes young people being killed by the leaders of the TPLF because they retreated,” he said.

Moreover, the journalist stated that the terrorist group’s army is in disarray due to the defiance of the youth who rebelled against the repression and abuses of TPLF on the people of Tigray.

However, through their established networks, the terrorists are taking the youth to war fronts and many who defied have been arrested, according to the journalist.

The people of Tigray are taken hostage by TPLF which deprived them of their rights to express grievances and opposition to the difficult situation in Tigray.

“The terrorist TPLF has made the people of Tigray suffer from starvation and death. It didn’t do anything to save the people.”

The journalist further revealed that what is being reported by the Tigray media about the situation in the region and the reality on the ground are completely different.
=========
The original article is ENA

You can read also on SCOOP Independent News

Sunday, September 18, 2022

አዲሱ የኢትዮጵያ የትምህርት ፖሊሲ የኢትዮጵያ ትንሳዔ አብሳሪ ልጆች ማፍርያ ፖሊሲ ነው። ፖሊሲውን በተመለከተ የማያውቋቸውን ጥቂት ነጥቦች ጉዳያችን ምጥን ለመዘርዘር ሞክራለች።


========
ጉዳያችን ምጥን
=========
''አንድ ዛፍ ተ ተጣሞ ካደገ በኃላ ፈፅሞ አታቃናውም።የተጣመመ የትምህርት ፖሊሲ ውስጥ የተማረ ተማሪም ካደገ በኃላ አታቃናውም'' ይህ ብዙ ጊዜ ተደጋግሞ የተነገረ ነው። ሀገር በተለያየ መንገድ ሄዶ ከሚፈርስበት ወይንም አንድነቱን ከሚጠበቅበት መንገድ አንዱ ወጥ የሆነ አፍራሽ ወይንም ገንቢ  የትምህር ፖሊስ በአንድ አገር ላይ መኖር እና አለመኖር ላይ የተመሰረተ ነው።ይህ ለውጥ አንደመጣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ከምክር ቤት ስብሰባ በኃላ መጀመርያ የታዩበት መድረክ የትምህር ፖሊሲ አንዲቀየር የሚያጠና ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ነበር።በስብሰባው ላይ ያደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ የትምህርት ፖሊሲ ምን ያህል ኢትዮጵያን ለመከፋፈል አስተዋጽኦ እንዳደረገ በሚገባ አሳይተዋል።ያለፈዐው የትምህርት ፖሊሲ ኢትዮጵያን ቀውስ ውስጥ ከቷት አልፏል።ገና መዘዙም ለቀጣይ ዓመታት የሚለቀን አይደለም።ከዛሬ ሰኞ ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆነው አዲስ የትምህርት ፖሊሲ ምን ምን ይዟል? ከብዙ በጥቂቱ እንደሚከተለው ለመዘርዘር እሞክራለሁ።
  • የመማርያ መፃህፍት ዝግጅቱ ሦስት ዓመታት ፈጅቷል።
  • በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከነገ መስከረም 9/2015 ዓም ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል።
  •  ከአንደኛ አስከ ስድስተኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች የግብረገብ ትምህርት ይማራሉ።
  • የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት አዲሱ ፖሊሲ በ80 ትምህርትቤቶች የሙከራ ሥራ ዘንድሮ ተሰርቶ በመጪው ዓመት ሙሉ በሙሉ ሥራ ላይ ይውላል።
  •  የሰባተኛና የስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች ‹‹ኬሪየር ኤንድ ቴክኒካል ኤጁኬሽን›› የተባለ የትምህርት ዓይነት ይሰጣቸዋል።
  • ይህ የትምህርት ዓይነት] መጠነኛ የሆነ የአካውንቲንግ፣ ቢዝነስ፣ እርሻና ሌሎች የሙያ ትምህርቶችን ዕውቀት የሚያስጨብጥ ነው።
  • ተማሪዎቹ 11ኛ እና 12ኛ ክፍል ሲደርሱ ይኼ ትምህርት ራሳቸውን የቻሉ እንደ ማኑፋክቸሪንግ፣ ኮንስትራክሽን፣ ጤና፣ ግብርና፣ ቢዝነስና አካውንቲንግ ባሉ የሙያ ትምህርት መስኮች ተበትኖ ይሰጣቸዋል።
  •  ስለሆነም አንድ ተማሪ 12ኛ ክፍል ሲጨርስ አንደ ድሮው ጨረሰ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ሙያዎች ይዞ ስለሚወጣ ምረቃ ይኖረዋል።ይህ በሌሎች አገሮች የተለመደ ነው።
  • 12ኛ ክፍል የጨረሰ ተማሪ በመለስተኛ ሥራዎች ተቀጥሮም ሆነ የራሱን ሥራ ለመስራት የሚያስችል አውቀት ይዞ ይወጣል።
  • የእንግሊዝ ኬምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ከሥርዓተ ትምህርት ጥናት እስከ መጻሕፍት ዝግጅት በገምጋሚነት ተሳትፎበታል።
  •  ለአንደኛ ደረጃ የተዘጋጁት መጻሕፍት በሙሉ በትምህርት ሚኒስቴር ድረ-ገፅ ላይ ይለቀቃሉ።መፃሕፍ የለኝም ማለት የለም ኮምፕዩተር ከፍቶ መፅሐፉን ማንበብይ ይቻላል።ወላጆችም ልጆቻቸውን ለማስጠናት ቀድመው መዘጋጀት ይችላሉ።
  •  የኬምብርጅ ዩንቨርስቲ አንዱ ያገዘው ያለፉ መፃህፍት ብዙ ነገር ያጨቁ አና ተግባራዊ አሰራሮች የማያሳዩ አና የ21ኛውን ክ/ዘመን የቴክኖሎጂ ለውጥ ያላገናዘበ መሆኑ ላይ ጠቃሚ ሃሳብ ሰጥቷል።
  •  አንደኛ ደረጃ›› ትምህርት የሚባለው ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ክፍል ያለው ሲሆን፣ ሰባተኛና ስምንተኛ ክፍል ‹‹መካከለኛ›› ደረጃ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ከዚህ ቀደም ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ በሚል ተከፍሎ የነበረው ከዘጠነኛ እስከ 12ተኛ ክፍል ያለው የአራት ዓመት ቆይታ አሁን ሁለተኛ ደረጃ በሚል ተጠቃሏል።
  •  የአሁኑ የትምህርት ፖሊሲ አንዱ አና ልዩ የሚያደርገው የአገር በቀል አውቀቶች ቦታ ተሰጥቷቸው ተጠቃልለውበታል።
  •  ሌላው ሕፃናት አንደኛ ክፍል ሳይገቡ የሚሰጠው ትምህርት 0 ክፍል ተብሎ የትምህርት ካሪኩለም የሌለው፣በቂ ባለሙያ ያልነበረው ሲሆን አሁን በሁሉም የመንግስት ትምህርት ቤቶች ከአምስት ዓመት አስከ 7 ዓመት ያሉ ሕፃናት የሚማሩበት ሥርዓት አና ባለሙያ ተቁአማዊ በሆነ መልኩ ተደራጅቷል።
  • የሁሉም የትምህርት ውድቀት የሚጀምረው ከሰባት ዓመት በፊት ያሉ ልጆች ወጥ የሆነ መሰረት ይዘው ስለማይሄዱ አና ድንገት 7 ዓመት ሆኗቸው አንደኛ ክፍል ሲጀምሩ የአአምሮ ዝግጅት ሳይኖር ብቻ ሳይሆን ትምህርት አንዲወዱ ከስር ሳይሰራ የተሄደበት ሂደት አንዱ ውድቀት እንደነበር አዲሱ ፖሊሲ ተገንዝቦ አሁን አርሞታል።

    =========////=============

Saturday, September 17, 2022

ሰበር ዜና - የሽብርተኛው ህወሃት ቡድን ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሃብቶች ወደ ጂቡቲ እና ናይሮቢ ለመሸሽ ሙከራ አደረጉ።


===============
ጉዳያችን/ Gudayachn
===============

ከዘንድሮው የአዲስ ዓመት በፊት ተከታታይ ስብሰባዎች ከውጭ መንግስታት ደጋፊ ባዕዳን ጋር ተገናኝቷል። በእነኝህ ስብሰባዎች ላይ በሽብር ቡድኑ የፖለቲካ እና የኃይል አመራሮች ጋር የነበራቸው ስብሰባ ላይ የነብሩትን ንትርኮች ለባዕዳኑ ጠቁሟል።ባዕዳኑም ከኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል ጥንካሬ አንጻር እና እራሱ የትግራይ ህዝብም በህወሃት ላይ ካለው መማረር አንጻር ወዴትም እንደማያስኬዳቸው መነጋገራቸው ተደርሶበታል።በእዚህ ንግግር ውስጥ የህወሃት አመራሮች አሁን ከቀድሞው የተለየ አካሄድ እንደሚሄዱ ለባዕዳኑ ጠቁመዋል። 

ይህ ከበፊቱ የተለየ የተባለው አካሄድ ደግሞ ግልጽ የሆነው መስከረም 1፣2015 ዓም ምሽት ላይ ህወሃት ታዛዥነቱ ለባዕዳን ነውና በኢትዮጵያ ፊደል ሳይሆን በእንግሊዝኛ ካለምንም ቅድመ ሁኔታ እንደሚደራደር እና የአፍሪካ ሕብረትንም አደራዳሪነት እንደሚቀበል አስታወቀ።ይህ ድንገተኛ የድርድር ጥያቄ ግን ከጀርባው ይዞት የነበረው ምን እንደነበር ውይይቱ ውስጥ ከነበሩ ከፍተኛ የሽብር ቡድኑ ዘግይተው አውጥተውታል። እንደመረጃው ህወሃት ድንገት ምሽቱን በእውር ድንብር በእንግሊዝኛ የለቀቀው የእንደራደር መግለጫ ዋና ዓላማ ለመደራደር አይደለም።በመደራደር ስም ጥቂት ጊዜ ወስዶ ሰራዊቱን ለማደራጀትም አይደለም።ህወሃቶች ሁሉ ነገር እንዳበቃ እራሳቸውም ገምግመው አውቀውታል።ባዕዳኑም በግምገማቸው ነግረዋቸዋል። የእንቁጣጣሽ ምሽት የእንግሊዝኛ መግለጫ ዋና ዓላማ ህወሃት አመራሩን ይዞ በድርድር ስም ወደ ጂቡቲ እና ኬንያ ለማምለጥ ነበር። ቀደም ብሎ የህወሃት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ ከእኛ በኩል የሚደራደሩት ስም አንገልጽም ብሎ የነበረ ቢሆንም በእንቁጣጣሽ ምሽት ላይ ግን ጌታቸው ረዳ እና ጻድቃን መመረጣቸውን ተናገረ።ዓላማው ከፍተኛ አመራሩ ከትግራይ እንደሚወጣ ለትግራይ ህዝብም ሆነ ለመንግስት ገልጾ የመሹለክ ዓላማ ብቻ የያዘ መግለጫ ነበር።

ለመደራደር ጂቡቲ መጣን ያለው የህወሃት መግለጫ ተከትሎ ሊያመልጡ የነበሩት ጌታቸው እና ጻድቃንን ጨምሮ ከ13 በላይ ጄነራሎች፣ከ25 በላይ የሚሆኑ የሲቪል አመራሮች፣6 ጋዜጠኞች፣12 የትግራይ ዩንቨርስቲ አመራሮች እና ከ3 ቢልዮን ዶላር በላይ የሚቆጠር ገንዘብ ያላቸው ባለሃብቶችን ይዞ ወደ ጂቡቲ ወይንም ናይሮቢ ድርድሩ ሊደረግ ነው ወደተባለበት ሃገር በህጋዊ ከለላ ለመውጣት እና ለማመለጥ የታቀደ እንደነበር ተጋልጧል። ይህ በድርድር ስም የመውጣት ዕቅድ ለማምለጥ የታቀደ እንደነበር በእዚሁ ሳምንት ህወሃት ባደረገው ስብሰባ ላይ ለድርድር ሊሄዱ ነበር የተባለው ሰው መብዛት የተመለከቱ እና እነርሱ ከዝያ ዝርዝር ያልተጨመሩበት አሳማኝ ምክንያት እንዲነገራቸው የህወሃት አመራሮችን ጠይቀዋል። ''እኛን ሜዳ ላይ ዘርግታችሁ ልትሄዱ ነበር። ማምለጥ ካለባችሁም ለምን እንድንነጋገርበት አይደረግም ነበር? አሁን በኋላ ማንንም የህውሃት አመራር ልናምን አንችልም '' የሚል የፊት ለፊት ኢንኪያ ሰላምታ እንደነበር መረጃው ጨምሮ ያብራራል። ይህ ዜናም መቀሌ ህዝቡ መሃል በበታች ካድሬዎቹ ስለተሰማ አሁን የህወሃት አመራሮች ወደ ግንባር ዘመትን የሚል ቪድዮ እንስራ የሚል ሃሳብ ከቡድኑ ውስጥ ተሰምቷል።

አሁን የህወሃት አመራር ተመልሶ ከምቾት ሶፋ ላይ ተነስቶ ወደ ደደቢትም ሆነ ተንቤን የመሄድ አንዳች ሞራል የለውም።ላድርግ ቢልም የአሁኑ የመንግስት ስልት የረቀቀ በመሆኑ ከመቀሌ በፊት የሽብር ቡድኑ ሊያመልጥበት ይችላል የተባሉትን ደደቢት እና ተንቤን ስልታዊ ቦታዎች ቀድሞ ከቦ ይዟቸዋል።በመሆኑም ለህወሃት አመራር የቀረው ደደቢት እና ተንቤን ጂቡቲ እና ናይሮቢ ናቸው።

ይህ ሁኔታ ለመንግስትም ሆነ ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚያሳየው ጉዳይ ምንም ዓይነት መዘግየት ሳይሰጡ የሽብርተኛው ቡድኑ አመራሮችንም ሆነ ጀሌውን በቶሎ ወደ ሕግ አቅርቦ የትግራይን ህዝብ ከህወሃት መንጋጋ የማውጫው ጊዜ አሁን መሆኑን ነው።አንዳንድ የምዕራብ አገሮች የሽብር ቡድኑ ደጋፊዎች የኢትዮጵያን መንግስት የሚወቅሱበት አዲስ ርዕስ ስላጡ በመገናኛ ብዙሃኖቻቸው ዙርያ ጥምጥም ከማውራት ሌላ አሁን የሽብር ቡድኑን የሚረዱበት ርዕስ ፍለጋ እንዲረዳቸው የውሸት የሰብዓዊ መብት ሪፖርት የሚል ከሰሞኑ ይዘው ለመውጣት ላይ ታች እያሉ ነው።ሪፖርቱን ካወጡ በኋላ ያንን እየጠቀሱ በየሚድያው ላይ ለማለቅለቅ እንደሚመች አምነውበታል። ይህ ግን አሁንም መሬት ላይ ያለውን ሁኔታ አንዳች አይቀይረውም። 
========

Monday, September 12, 2022

''ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ'' ዓይነት ንግግር ከሽብርተኛው ህወሃት ጋር ማድረግ ሃገር ከመሸጥ እኩል ነው።አሁን ህወሃትን የትግራይ ህዝብ ደገፈው አልደገፈው ስሌት ውስጥ የሚገባበት ጊዜ አይደለም።ህወሃትን ትጥቅ የማስፈታት ጥብቅ አቋም ከመንግስት ያስፈልጋል!



==========
ጉዳያችን ምጥን
==========

በኢትዮጵያ ታሪክ እንደ ሽብርተኛው ህወሃት በኢትዮጵያውያን ላይ ግፍ ያደረሰም ሆነ ኢትዮጵዊነቱን ሙሉ በሙል ክዶ ከባዕዳን ጋር ከባዕዳን በላይ ሆኖ ኢትዮጵያን የሸጠ አንድም ኢትዮጵያዊ ኃይል በታሪካችን አልገጠመንም። ለ27 ዓመታት የኢትዮጵያን ሃብት አሟጦ ከግል የውጭ የመንደር ባንኮች ሳይቀር ኢትዮጵያን አስይዞ መበደር ደረጃ የደረሰ እና የተበደረውንም እንደ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ፍሰት አጥኚ ከ11 ቢልዮን ዶላር በላይ ከኢትዮጵያ ያሸሸ የኢትዮጵያ ጠላት ነው።

ሽብርተኛው ህወሃት በትግራይ የትኛውም ቦታ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ እንዳይሰቀል አድርጎ በራሱ እራፊ ቀይሮ ትግራይን ለባዕዳን አስማምቶ የትግራይ መንግስት እያለ እራሱን የሚጠራ ወንጀለኛ ቡድን ነው።ስለ ቡድኑ ብዙ ተብሏል።እዚህ ላይ ማንሳት የተፈለገው ግን አንድ ጊዜ በአፍሪካ ህብረት አልዳኝም ካለ በኋላ መልሶ ደግሞ በባዕዳኑ ምክር ተመርቶ ከፌድራል መንግስት ጋር እነጋገራለሁል በማለት ትናንት መግለጫ ልኳል።

'አሁን መንግስት በ ''ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ'' ዓይነት ንግግር ከሽብርተኛው ህወሃት ጋር ካደረገ ሃገር ከመሸጥ ጋር እኩል ሥራ ከመስራት ጋር አንድ ነው።አሁን ህወሃትን የትግራይ ህዝብ ደገፈው አልደገፈው ስሌት ውስጥ የሚገባበት ጊዜ አይደለም።በሽብርተኛው ህወሃት በር ከፋችነት ባዕዳን ከሚገባው በላይ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ እየፈተፈቱ ነው።ይህ ብሔራዊ አደጋ ነው።ማንም ሃገር የማይፈቅዳቸው እና ማንም መንግስት በግዛቱ ውስጥ እንዲሆን ማየት አይደለም መስማት የማይፈልጋቸው ጉዳዮች በሽብርተኛው ህወሃት በኩል በኢትዮጵያ ውስጥ እየተደረጉ ነው።እነርሱም 

1/ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማን አውርዶ በራሱ እራፊ የሚንቀሳቀስ ክልል በትግራይ ተፈጥሯል።

2/ በራሱ ክልል ውስጥ የራሱን ታጣቂ ይዞ የሚንቀሳቀስ ኃይል በትግራይ ተፈጥሯል።

3/ እራሱን እንደ አንድ መንግስት የሚጠራ ክልል በትግራይ ተፈጥሯል።

እነኝህ ሦስት ጉዳዮች እጅግ አደገኛ ብቻ ሳይሆኑ ማንም መንግስት በሚገዛው ክልል ውስጥ የሚፈቅደው አይደልም።ኢትዮጵያ መንግስት ጠንክሮ እነኝህን ጉዳዮች አንስቶ እና ሳይስተካከሉ ድርድር የሚባል ነገር እንደሌለ በግልጽ ለኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ ለውጭ የህወሃት አጫፋሪ መንግስታት ማስታወቅ አለበት። ይህንን የኢትዮጵያ መንግስት በማድረጉ ደግሞ ማንም መንግስት በስውር እንጂ በግልጽ ዲፕሎማሲ ሊቃወም አይችልም።አሜሪካንም በምታወራው እና በምታወጣቸው መግለጫዎች ደጋግማ ያለችው ጉዳይ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት እና ሉዓላዊነት እንደምታከብር ነው።በመሆኑም ቢያንስ በግልጹ ዲፕሎማሲ እንዲህ ዓይነት አቋም ካንጸባረቀች የኢትዮጵያ መንግስትም የጠነከረ አቋም ለመያዝ የሚያግደው ምን ጉዳይ አለ?

ከእዚህ በኋላ ከህወሃት ጋር ለንግግር እቀመጣለሁ የሚል መንግስት ከላይ የተጠቀሱትን ሦስት መሰረታዊ የአገር ምሰሶዎች የሚገዘግዝ ሥራ ከመስራት ያነሰ አይደለም።ኢትዮጵያን አላውቅም ካለ ሽፍታ ጋር ድርድር አይሰራም።ከእዚህ በተሻለ የትግራይን ክልል አስተዳድራለሁ የሚል አዲስ አደረጃጀት ካለ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ባከበረ እና ሰላማዊ በሆነ መልኩ ከመንግስት ጋር የሚደራደር አዲስ ቡድን ማገዝ እና የትግራይን ህዝብ ከመርዳት መለስ ከህወሃት ጋር የሚደረግ ማናቸውም ድርድር ኢትዮጵያን የማፍረስ የዳርዳርታው ጅማሮ ነው። ጆሮ ያለው ይስማ! ''ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ'' ዓይነት ንግግር ከሽብርተኛው ህወሃት ጋር ማድረግ ሃገር ከመሸጥ እኩል ነው።አሁን ህወሃትን የትግራይ ህዝብ ደገፈው አልደገፈው ስሌት ውስጥ የሚገባበት ጊዜ አይደለም።ህወሃትን ትጥቅ የማስፈታት ጥብቅ አቋም ከመንግስት ያስፈልጋል!

Monday, September 5, 2022

ጌታቸው ረዳ ''ክው'' ብሏል።በትግሪኛ የሰጠው መግለጫ።ምን ይዟል?

ጌታቸው ረዳ በከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ 

=========
ጉዳያችን ምጥን 
=========
ጌታቸው ረዳ በትግርኛ ማምሻውን መግለጫ ሰጥቷል። ጋዜጠኞቹ ይችን ምሽት ጌታቸው አጠገብ መቀመጥ እንዳስጨነቃቸው ከጠያቂዎቹ መርበትበት ለመረዳት የስነ ልቦና ጠቢብ መሆን አይጠይቅም። ቢጨነቁም ምክንያት አላቸው። የህወሃት ባለስልጣናት ባሉበት ሁሉ እያነፈነፈች ድንገት የምትመጣው ድሮን በእዚህ ምሽት አትመጣም ብለው እንዴት አይፈሩም? ቃለ መጠይቅ ለማድረግ ወደ ጌታቸው የተደበቀበት ኮንቴይነር የተላኩት ጋዜጠኞች አንተ ሂድ አንተ ሂድ ሳይባባሉ አይቀሩም። ጌታቸውም ተጨንቋል።ራሱን ሳይበላው የግራ እጅ ጣቶቹን ወደ ጸጉሩ ጋር ይልክና መልሶ ያወርደዋል። 

ወጣት ጋዜጠኞቹ መጀመርያ መግለጫ አለ ሲባል ህወሃት አዲስ ነገር ይናገራል።ህዝቡን አላስፈጅም ስልጣኔን እለቃለሁ። የትግራይ ህዝብ እራሱ በመረጠው ይተዳደር ይላል ብለው ጠብቀው ነበር።ጋዜጠኞቹ ወጣቶች ናቸው።ለእነርሱ የናፈቃቸው መከላከያ መቀሌ ገብቶ መብራት መጥቶ ወላጆቻቸው በሰላም እንጀራ ጋግረው እፎይ ብለው ማየት ነው። ወጣቶቹ የናፈቃቸው መከላከያ መቀሌ ገብቶ የመቀሌ ጎዳናዎች በታክሲ እና መኪና ተጣበው ከጓደኞቻቸው ጋር ሳባ ካፌ ቁጭ ብለው መሳቅ ነበር። ጌታቸው ግን ምንም አዲስ ነገር አልነገራቸውም። ያንኑ ኢሳያስ፣ አቢይ፣ እያለ ያደርቃቸው ያዘ። ፊታቸው ከመቼውም ጊዜ በባሰ ተስፋ ቆረጠ። አንዷ ጋዜጠኛ የጌታቸውን ፊት መመልከት ስላስጠላት የሚጻፍ ሳይኖር አቅርቅራ የሆነ ነገር መሞነጫጨር ላይ ብቻ አተኮረች።ወንዶቹ ጋዜጠኞች ዛሬ ህወሃት አዲስ ነገር ይናገራል ህዝቡን ከእልቂት ያድናል ብለው ሲጠብቁ ጌታቸው በእርዳታ እህል የተብለጨለጨ ፊቱን እያሳየ አደረቃቸው።በተለይ በቃለመጠይቁ መሃል ላይ የነበረው ሳል የድሮን ጥቃት እየመሰለው ጌታቸውም ሆነ ጋዜጠኞቹ ሲደነግጡ ቃለ መጠይቁ ላይ ይታይ ነበር።

ጌታቸው በዛሬው የትግሪኛ ቃለ መጠይቁ የኢሳያስ ጦር በሙሉ አቅሙ ወሮናል፣የትግራይን ህዝብ ከምድረ ገጽ ለማጥፋት ነው ወረራው ካለ በኋላ ህወሃት ለሰላም እየሰራ ነው በማለት የትግራይን ህዝብ ለመደለል ሞክሯል። ጌታቸው የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ለወራት ከምንዋጋ አስር ዓመት ብንደራደር ይሻላል ያለውን። ሦስት ሳምንት ከምንዋጋ ሦስት ወር ብንደራደር ይሻላል። በማለት አሁንም የትግራይን ህዝብ ለማታለል ሞክሯል።

ጌታቸው በዛሬው መግለጫ ምንም አዲስ ነገር የለውም።ከእዚህ ይልቅ የቃለ መጠይቁ ምክንያት ምንድን ነው? ብሎ መጠየቅ የተሻለ ነው። ከቃለ መጠይቁ የምንረዳው ሽንፈቱ ከእዚህ በፊት ከሚያውቀው ሽንፈት እጅግ ስልታዊ እና ከመቀሌ ወጥቶ ደደቢት ለመግባት የማያስሽል። የኢትዮጵያ መከላከያ የአሁኑ አመጣጥ ህወሃቶች ቀድመው የሚገቡበትን ዋሻ በመያዝ ወደ መቀሌ የሚያመራ መሆኑ ነው።ከእዚህ በላይ የትግራይ ህዝብ እንደተነሳባቸው ብቻ ሳይሆን አሁን የሚያሳምኑበት ቃል እንዳለቀ ነው። ድሮም እናንተ በአፋር እና በወሎ በኩል ጦርነት የከፈታችሁ ለትግራይ ህዝብ ብላችሁ ሳይሆን የተወሰደባችሁን ፎቅ ለማስመለስ ነው እንጂ ለህዝብ አይደለም የሚለው ድምጽ በመላዋ ትግራይ እያስተጋባ ነው።ስለሆነም የጣረ ሞት የጌታቸው መግለጫ በትግሪኛ የሆነ ነገር ማለት ስላለበት ማይክራፎኑ ፊት ተሰየመ።ከእዚህ መግለጫ በፊት ጌታቸውም ሆነ የጠየቁት ጋዜጠኞች ዛሬ ቀን በኢቲቪ የታዩት እና ለመከላከያ እጃቸውን የሰጡት ምናልባትም ጋዜጠኞቹ በሰፈራቸው የሚያውቋቸው ልጆች ሁሉ ተማርከው አይተው ወደ ቃለ መጠይቁ መጥተው ይሆናል። ጌታቸው ግን አሁንም ያንኑ ዘፈን ይዘፍናል ብለው አልጠበቁም።ቢያንስ በእዚህ ጊዜ ህዝቡን ለማዳን አንድ ነገር ይለናል ብለው ጠብቀው ነበር። ያው ''የሞኝ ዘፈን ሁሌ አበባዬ '' እንደሚባለው ጌታቸው ያንኑ ኢሳያስ፣ ዐቢይ የሚለውን ዘፈን ዘፍኖ አሰናበታቸው። የትግራይ ህዝብ ህወሃትን አሁንም ዛሬም ተነስቶ በቃህ ካላለው ህወሃት ለስልጣኑ ህዝቡን ይዞ ወደ የበለጠ እልቂት እንደሚወስደው ዛሬ ላይም ያልተረዳ ይኖር ይሆን? ጥያቄ ነው።
==============

Saturday, September 3, 2022

Renewed TPLF Terror War Against The Ethiopian People ህወሃት ዳግም በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የከፈተው የሽብር ጦርነት በሚል ግራሃም ፕብለስ ''ኤይሮአስያ ሪቪው'' ላይ ዛሬ ያወጣው ጽሑፍ።

Graham Peebles
=======================
Written by Graham Peebles
September 3,2022
Source = Euraesia review News and Analysis
=======================

After a fragile ceasefire lasting just five months, the TPLF (Tigray People’s Liberation Front) have once again initiated violent conflict with federal forces in Northern Ethiopia.

They started the war in November 2020, were forced to retreat just over a year later, but not content with the level of human suffering resulting from their initial barbarism, they are, it seems, determined to kill and kill again; to rape and beat their Ethiopian brethren; to once more destroy property, burn farmland, slaughter livestock, sending fear through communities, deepening the pain of a nation in their frenzied quest for power.

This latest offensive was launched on 24 August, violating the humanitarian truce agreed with the Ethiopian government, and shattering the temporary peace. A Government statement relayed that, “Ignoring all of the peace alternatives presented by the government, the terrorist group TPLF…. continued its recent provocations and launched an attack this morning at 5 am (0200 GMT)”

The TPLF used the months of peace, not to enter unto constructive dialogue with the government, to address the needs of people in Tigray impacted by the war and beg for forgiveness, but to actively re-arm and rebuild its forces. The Crisis Group relate that they have “solid evidence” of at least 10 Antonov planes making deliveries (of arms it is assumed) “to two airports in Tigray,” almost certainly from Sudan. One such aircraft, en route from Sudan and loaded with weapons, was recently shot down by the Ethiopian air force.

The government has known about these arial shipments for some time, but failed to clamp down on them. This lack of decisive action, particularly in relation to law and order issues has been a feature of the Abiy premiership, and is something that needs to change.

Whilst TPLF thugs lit the fuse of renewed conflict in Tigray’s southern border, other misguided fighters, many little more than children, raided a World Food Program (WFP) warehouse in Mekelle (capital of Tigray region). “12 full fuel tankers with 570,000 litres of fuel” were taken, and UN staff detained, reported, Stephane Dujarric, chief spokesman for UN Secretary-General Antonio Guterres. “These fuel stocks were to be used solely for humanitarian purposes, for the distribution of food, fertilizer and other emergency relief items. This loss of fuel will impact humanitarian operations supporting communities in all of northern Ethiopia.”

Stealing from the UN to enable war is nothing new for the TPLF; From July-September 2021 the WFP state that, “445 contracted non-WFP trucks entered Tigray, but only 38 ….returned,” – 407 were stolen by the TPLF. The lack of vehicles the agency said, was “the primary impediment to ramping up the humanitarian response” within Tigray. The inability of UN agencies to deliver humanitarian aid is of no concern whatsoever to the TPLF leadership, who care not a jot for the people of Tigray, and even less for other ethnic groups throughout Ethiopia.

Alongside the declaration of a humanitarian truce, the March 24 agreement initiated by the Government, allowed for unfettered humanitarian access to Tigray, and created a platform for peace talks. But the TPLF do not want peace, have never wanted peace and have no intention of working for it. They failed to engage with the Main Peace Committee – established to “peacefully resolve the conflict in the northern part of the country”, or the National Dialogue Commission, set up by the government on 29 December 2021, to “facilitate “inclusive dialogue on national issues for the creation of national consensus and establishment of common grounds.” From the beginning of the conflict the government has repeatedly looked for a peaceful resolution, but the TPLF have erected obstacle after excuse after condition to scupper any progress; for its part the government has consistently said it will talk to TPLF representatives anytime, “without precondition, at any venue.”

This accommodating approach however is wasted on the TPLF: their aim is clear, to fracture Ethiopia, inject discord, hopefully overthrow the government (with western nations’ support) – the first government to be democratically elected by the way – and regain power. They will fail totally; they are hated and despised throughout the country (including within Tigray) and by Ethiopians and friends of Ethiopia everywhere, and with every Ethiopian that they kill, rape and abuse that hate deepens a little further.

Western support: arms and credibility

The TPLF have been a malignant force in Ethiopia for decades. They dominated the previous EPRDF government (a coalition in name only) for 27 years (1991-2018), stealing election after election. Ruling through fear, enflaming division, agitating ethnic disagreements, violently crushing human rights and committing state terrorism in various parts of Ethiopia. Throughout their time in office and since their overthrow Western powers, to the bewilderment of many, have consistently supported them. Perhaps unsurprisingly, given their addiction to regional meddling, the main sponsor of TPLF terror is the US government. Successive administrations, together with the UK, and to a lesser degree the European Union, have backed the TPLF, empowering them financially, politically, and throughout their war on the Ethiopian State, it is widely believed, militarily.

With western political support and lasting TPLF influence in Washington, London, New York and Geneva, has come media collusion. CNN, BBC, Al Jazeera, The Guardian, New York Times etc, all have been guilty of mis/dis-information; biased or just poorly researched stories ranging from outright lies to nauseating bothsidesism as with Voice of America (VOA) reporting of the recent theft of WFP fuel by TPLF fighters, witnessed by UN staff. VOA state that Tigrayan forces are condemned for “allegedly stealing” the fuel: allegedly!

The extent to which western politicians were, and given the recent attacks, appear to remain, involved in the TPLF’s terror war was revealed by a video that was leaked in November 2021. The footage shows a Zoom meeting between Berhane Gebre-Christos, referred to as “a “chief representative of the TPLF,” and top US, UK and European Union diplomats with long-standing connections to Ethiopia, including US Ambassador to Somalia Donald Yamamoto. The group reportedly celebrated the TPLF’s advance on Addis Ababa (which never actually transpired) and discussed how the TPLF could form a post-Abiy government.

It is geopolitics at its most ugly and menacing; these ex-colonial/imperialist political powers have no interest in seeing Ethiopians or indeed anyone in Sub-Saharan Africa prosper and are still trying to install puppet regimes wherever possible. As long as the TPLF continue to receive support from ‘foreign powers’ the terrorists will continue to wage war on the Ethiopian people. The ‘international community’, which equates in this case primarily to the US, needs to stop feeding the dogs of war and start compelling the TPLF, a cancer within the nation and the wider region, to engage meaningfully in peace talks with the government.

============

Graham Peebles is an independent writer and charity worker. He set up The Create Trust in 2005 and has run education projects in India, Sri Lanka and Ethiopia where he lived for two years working with acutely disadvantaged children and conducting teacher training programmes. Website: https://grahampeebles.org/
To read the above article on Eurasia review click this link

Friday, September 2, 2022

WHO director, Teodros Adhanom, uses his UN post to lobby for his TPLF party. ዶ/ር ቴዎድሮስ የተባበሩት መንግስታትን የስልጣን ወንበር ለህወሃት ፕሮፓጋንዳነት እያዋሉት ነው።በሚል አን ጋሪሰን በምርመራ ዘገባዎቹ የሚታወቀውመሰረቱን ሳንፍራንሲስኮ ላደረገው ዘግራይዞን ገጽ ላይ የጻፈችው ሙሉ ጽሑፍ።

By Ann Garrison, September 1,2022
Source = The Grayzone
=================
UN World Health Organization chief Dr. Tedros Adhanom is also the world’s most prominent advocate of the Tigrayan People’s Liberation Front. He has said nothing about the TPLF’s recent theft of fuel intended for UN relief efforts in Ethiopia.


Hours ago, Tigrayan authorities stole 570,000 liters of fuel for operations in #Tigray! Millions will starve if we do not have fuel to deliver food. This is OUTRAGEOUS and DISGRACEFUL. We demand return of this fuel NOW.
Stéphane Dujarric, Spokesperson for United Nations Secretary-General António Guterres, had included more detail in his August 24, 2022 briefing. According to Dujarric, after the TPLF broke into World Food Programme facilities, it overwhelmed UN staffers and stole 12 fuel tanker trucks:
“I was asked what the impact of the renewed fighting was having. This morning, on August 24th, a World Food Programme warehouse in Mek’ele was forcibly entered by Tigrayan forces who took 12 fuel trucks/tankers with 570,000 liters of fuel. The team on the ground unsuccessfully tried to prevent this looting.  
These stocks of fuel were to be used solely for humanitarian purposes, with the distribution of food, fertilizer, and other emergency relief items. This loss of fuel will impact humanitarian operations in supporting communities in all of Northern Ethiopia.
We condemn any looting or confiscation of humanitarian goods or humanitarian premises, and we call on all parties to uphold their obligations under international humanitarian law and to respect humanitarian personnel, activities, assets, and goods.”
The TPLF, who control Tigray regional state, have always claimed to represent the people of Tigray, who are no doubt suffering as a consequence of the war. But the faction’s brazen heist of fuel needed for humanitarian relief operations makes it difficult to believe it actually cares about the conflict’s human toll.
US Special Envoy to the Horn of Africa Mike Hammer and EU Special Envoy to the Horn of Africa Annette Weber went to Tigray to talk and snap a selfie with TPLF leaders Debretsion Gebremichael and Getachaw Reda. This was several weeks before the resumption of the Ethiopian civil war and the TPLF fuel heist.

As Tedros’ party steals from UN’s largest humanitarian agency, he looks the other way

One hour after Dujarric’s August 24 briefing, UN World Health Organization Secretary-General Dr. Tedros Adhanom Ghebreyesus was busy tweeting about a conference in Togo. By early afternoon on August 25th, Tedros had returned to do more of the same before moving on to tweeting about Ebola vaccinations in the Democratic Republic of the Congo.

Yet Tedros – who also happens to have been a leader of the TPLF and the faction’s prominent advocate – had absolutely nothing to say about his political party’s theft of 600,000 liters of fuel from the UN’s most important humanitarian agency.

One week later, many of Tedros’s 1.8 million Twitter followers are still waiting for the WHO chief’s response to the TPLF fuel heist.

As The Grayzone revealed, UN staffers have previously accused Tedros of flagrantly violating UN code to further the objectives of his political allies in Ethiopia’s conflict.

Tedros uses his UN post to lobby for his TPLF party

Tedros served as the TPLF’s Health Minister from October 2005 to November 2012, and its Foreign Minister from November 2012 to November 2016, while it held power in Ethiopia’s capital Addis Ababa. Eight months after leaving the foreign ministry, in July 2017, he was appointed as the World Health Organization’s Director General and thus, beginning in 2020, the manager of the global coronavirus pandemic.
In 2018, a year after Tedros assumed his post at the WHO, a popular uprising ousted the TPLF from power, after which they retreated to Tigray. Ethiopia’s parliament then elected Abiy Ahmed as prime minister; he won a popular election two years later.
In November 2020, in a seeming bid to return to power, the TPLF attacked fellow soldiers at Ethiopia’s Northern Command Base, initiating the ongoing civil war. Prime Minister Abiy immediately dispatched national troops to Tigray to stop the insurrection but withdrew them in July 2021. The TPLF then invaded Amhara and Afar regional states, until the Ethiopian national army and regional forces drove them back into Tigray and the Ethiopian government declared the humanitarian truce that ended on August 24th.
Throughout this time, no one has been more vocal and visible than Tedros in accusing the Ethiopian government of deliberately fomenting a humanitarian crisis in Tigray, blockading food aid to Tigray, and even committing genocide in the region. He has never, however, acknowledged the pain and displacement that the TPLF has inflicted on Amharas and Afaris.
Throughout April and May of this year, I traveled through Amhara and Afar regional states and saw thousands huddled in IDP camps, all in dire need of food, water, medicine, and sanitation.
Around this time, the Internal Displacement Monitoring Center reported, “Conflict and violence triggered more than 5.1 million new displacements in Ethiopia in 2021, three times the number in 2020 and the highest annual figure ever recorded for a single country. The conflict in the northern region of Tigray deepened, spreading to neighboring regions and uprooting millions of people from their homes.”

US humanitarian interventionists cry genocide, ignore TPLF human rights abuses

Within hours of the unprovoked TPFL attack on Ethiopia’s national army in November 2020, the TPLF and its advocates took to Twitter to cry “Tigray genocide!” Meanwhile, the most vehement humanitarian interventionists in the US, from  USAID Chief Samantha Power to congress members Tom Malinowski, Brad Sherman, Ilhan Omar, and Gregory Meeks, to name a few, joined the calls to defend Tigray and destabilize the government in Addis Ababa.
Malinowski’s bill, House Resolution 6600, which has yet to reach a vote on the House floor, demands the Ethiopian government’s total capitulation. “Sanctions will be lifted,” it says, “only after: (1) The Government of Ethiopia has ceased all offensive military operations associated with the civil war and other conflicts in Ethiopia.”
The TPLF enjoyed wholehearted US support throughout its 27-year rule, from 1991 to 2018, in exchange for its compliance with the US agenda in Africa. As former CIA and State Department official Cameron Hudson commented to Foreign Policy, “This is a major strategic shift in the Horn of Africa, to go from an anchor state for US interests to become a potential adversary to US interests.”
In 2015, shortly after the TPLF announced that it had won a thoroughly implausible 100% of the seats in Ethiopia’s parliament, Susan Rice and Barack Obama traveled to Addis Ababa to congratulate the party on its democratic achievements.

How do the TPLF keep fighting?

If Tigray is suffering such terrible deprivation, as the WHO’s Tedros, the TPLF, and their humanitarian interventionist allies insist, where do the TPLF find the resources to keep fighting? War is expensive. It requires the constant resupply of weapons, munitions, vehicles, food, emergency trauma care, and intelligence technology.
We may have a partial answer to that question now that both WFP Chief David Beasley and the UN Secretary-General’s spokesperson Stéphane Dujarric report that the TPLF have broken into a WFP warehouse and stolen 12 fuel tankers containing 570,000 liters of fuel that is desperately needed for humanitarian relief operations.
Hundreds of WFP aid convoy trucks have also disappeared into Tigray, though without a trace of official outrage.
The TPLF’s  seizure of food aid and its use of food to force recruitment and otherwise exploit civilians has been widely reported by Tigrayan IDPs who have fled to the Amhara region, as well as by Tigrayan troops who were captured or who surrendered in Afar Region. Again, none of this malfeasance triggered protests at the very top of the UN hierarchy as the fuel heist has.
Will WHO Chief Tedros call WFP Chief David Beasley to explain this heinous crime by his political faction?


Ann Garrison is a Black Agenda Report Contributing Editor based in the San Francisco Bay Area. In 2014, she received the Victoire Ingabire Umuhoza Democracy and Peace Prize for promoting peace through her reporting on conflict in the African Great Lakes Region. She can be reached on Twitter @AnnGarrison and at ann(at) anngarrison(dot)com.

You can read the above article also by opening this link.

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።