ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, January 31, 2013

''ሃገሬ ስንት ነች?'' (ከ ጉርዳፈርዳ ወረዳ ለተባረሩ በ ሺህ ለሚቆጠሩ ስዱዳን መታሰቢያ )

ማሳሰቢያ:- ይህ ፅሁፍ አምና ድርጊቱ(በ ደቡብ ክልል ማጂ ዞን በጉርዳፈርዳ ወረዳ ለ ዘመናት የኖሩ ኢትዮጵያውያን በግድ ማፈናቀል) እንደተፈፀመ(መጋቢት 30/2004 ዓ.ም.)  የተፃፈ ፅሁፍ ነበር። ብዙዎች በ ዜናነት ከማተት ባለፈ በተገቢው ያህል አልተናገሩለትም።ጉዳዩ ግን የመላው ኢትዮጵያውን በ አንድቦታ የመኖር እና ንብረት የማፍራት መብቱን ስለሚንድ ከ እርሱ ጋር ተያያዥ የሆኖ ሕጎችን በሙሉ ስለሚያፈርሳቸው ከ ሕግ እና ከ ፖለቲካ ጥያቄ በዘለለ ለመመልከት የሚያስገድድ ነው።በትናንትናው እለት ጥር 23/2005 ዓም ጉዳዩ እንደገና አለም አቀፍ ዜና ሆኖ ቀርቧል።የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ አንድ ወቅት በ ምክርቤት ስለጉዳዩ ተጠይቀው ሲናገሩ ''ማንም ኢትዮጵያዊ በፈለገበት ቦታ የመኖር እና ንብረት የማፍራት መብት አለው'' የሚለውን የ ህገመንግስቱን አንቀፅ ከመጥቀስ ይልቅ በደምሳሳው ''መሬቱን የ ደቡብ ክልል ነው የጠየቀው ፣ጉዳዩን ማራገቡ ማናችንንም አይጠቅምም'' የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። ይህን በሚናገሩበት ሰዓት ግን በ ሺ የሚቆጠሩ ከ አካባቢው ለዘመናት የኖሩ ነዋሪዎች ''የተሰራብንን ግፍ መንግስት ይመልከትልን'' ብለው ለ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቤት እያሉ ነበር። 

''ሃገሬ ስንት ነች?'' አቤል ጥያቄ 
አቤል ይባላል ደቡብ ኢትዮጵያ ከ ማጂ ዞን ጉርዳፋርዳ ወረዳ ተወልዶ ያደገ ከወረዳዋ በተለየ ሌላ ሀገር ያለ የማይመስለው የ አስራ ሁለት ዓመት ልጅ ነው።ደስተኛ ህይወቱን የመንደሩ ነዋሪ ሁሉ ይመሰክርለታል። ዛሬ ግን የደስታ ድባቡ ጠፍቶ በ ሃዘን የተዋጠ ልጅ ለመሆኑ በቂ ምክንያት ነበረው።
አቤልን የ መንደሩ ነዋሪ በጋራ ያወጣለት ስም አለ። ' ሮጦ የማይደክመው ' የሚል።ቀኑ ሙሉ ይሮጥበት የነበረው ሜዳ ዛሬ ወፍ ዝር አይልበትም ህዝቡ ንብረቱን ትቶ መሄድ ከጀመረ ወር ሊሞላው ነው። አቤል
ከ አራት የእድሜ አቻዎቹ ጋር ስለ ሰሞኑ ጉድ በ ልጅነት እግሩ ለ አምስት ሰዓት ያህል ቆሞ ካወራ በኋላ እንኳን ለ አንድ ደቂቃ ያወራ አልመስልህ ብሎት ስለመሸበት ብቻ ወደ ቤቱ ሄደ እንጂ ቤቱ አስጠልቶታል ። አሁን ግን መሸበት እናም እንዳቀረቀረ ወደ ቤቱ አመራ።

ማታ አባቱ የነገረው ነገር አሁንም እውነትነቱ አልገባ አለው። አባቱ ብቻ አደለም በ አስር ሺ የሚቆጠር ህዝብ ''በቶሎ ሃገሩን ለቃችሁ ውጡ!'' ተብለው ሰማይ ምድሩ ተደፍቶባቸው አይቷል።
አባት የ መንግስት ትዛዝ ገርሞታል ፣ደንቆታል፣ከ ሁሉ ያስለቀሰው ለ ብዙ ዓመት ያስቀደስበት ልጆቹን ሁሉ ክርስትና ያስነሳባት የ ቤተክርስትያኑ ጉዳይ ነው።'' ከ መድሃኔ ዓለም ታቦተ-ሕግ ርቀን ከ ክርስቶስም ሳንሆን ከ ለፋንበትም ንብረት ሳንሆን ሁለት ወር 'ሁዳዴ ' ፆመን ሳንገድፍ ስደተኛ ሆን ማለት ነው ?''ይልና ቀጥሎ ''ምን አይነት ሰዎች ምን አይነት ስብሰባ አርገው ከቀዬአችን ሊያስወጡን ወሰኑ አንተ? ምን አጠፋን? ሕግ ይሄን ያክል ተናቀ?መንግስት ምንም ግፍ ያልተፈፀመ ይመስል በ ራድዮና ቴሌቪዥኑ አለመናገሩ ምን ማለት ነው? '' ይላል።ለ አቤል ግን ''ምን አይነት ሰዎች ምን አይነት ስብሰባ አርገው ከቀዬአችን ሊያስወጡን ወሰኑ? ምን አጠፋን? ሕግ ይሄን ያክል ተናቀ? መንግስት ምንም ግፍ ያልተፈፀመ ይመስል በ ራድዮና ቴሌቪዥኑ አለመናገሩ ምን ማለት ነው? '' ሲል አባቱ ማታ የተናገረው ንግግር ጆሮው ላይ ይደውልበታል ።አባቱ ድሮ ' መንግስት' የሚለው ቃል በጣም ያከብር የነበረ መሆኑን ያስታውሳል። አባቱ ብቻ አደለም።የ ስነ -ዜጋ ትምህርት መምህሩ ስለ አንድ መንግስት 'ኃላፊነትና ግዴታ' ብዙ አስረድተውታል።።የ መንግስትን ብቻ አደለም የ አንድ ዜጋን ግዴታና መብትም ነግረውታል። በ ስነ-ዜጋ ትምርት ፈተናም ላይ ሁል ጊዜ ከ ዘጠና በላይ በማግኘቱ ሁለት ጊዜ በመምህሩ መሸለሙን አይዘነጋውም።

ሰሞኑን ጎረቤቱ ሁሉ ተሰብስቦ የ ሚነጋገርበት ጉዳይ አንድ ብቻ ነው :-
''ውጡ ተባልን'' የሚል። አቤል ጎረቤቱ ስነጋገር ቀድም ብሎ ማውራት ልማዱ ነው ጎረቤቱ ቡና ላይ ''ሀገር ልቀቁ'' ስለተባለው ወሬ ሲሰማ ነጠቅ ያረግ ና ''ሊሆን አይችልም ......የ አንድ መንግስት ግዴታ .....ነው ። ህገ መንግስቱ አንቀጽ ....ላይ .....የሚል አለ'' ብሎ ከ ስነ ዜጋ ትምርት የተማረውን ሊያስረዳ ይሞክር ነበር። በ ልበ ሙሉነት። ጎረቤቱም ሆነ ወላጆቹ በመጀመርያ እሱ የነገራቸውን የ ህገ መንግስት አንቀፅ ከ ወረዳው ሹሞች ጋር ሲነጋገሩ ይጠቅሷት ነበር።ቆይቶ ግን ጥቅስ እና ተግባር መለያየቱ ገባቸው።
ዛሬ ግን ከ ቤተሰቡ አልፎ አቤልም ያ! የ ስነ- ዜጋ መምህሩ የነገሩት ሁሉ ውሸት መሆኑን የተረዳው የ መንግስት ወታደር አጎቱን ና አባቱን ቤተሰባቸውን ይዘው ከ ሌሎች በ ሺህ ከሚቆጠሩ ነዋሪዎች ጋር ለቀው እንዲወጡ የሚገልፅ ደብዳቤ ለመላው የ ጉርዳፈርዳ ሰፋሪ ሕብረተሰብ ከታደለ በኋላ ነበር።
ታላቅ ወንድሙ የዛሬ ሰባት ዓመት የ ስምንት ዓመት ልጅ ሳለ-በ 1997 ዓም በነበረው የ 'ቅንጅት' ምርጫ ተብሎ በሚጠራው ጊዜ '' ስነ-ዜጋ ትምህርትና የ ገሃዱ ዓለም አልጣጣም አለኝ'' ብሎ ሲናገር ና አባቱን በጥያቄ ሲያጣድፍ የነበረ መሆኑ ዛሬ ይበልጥ ትዝ አለው። አቤል ተገረመ በ ልጅነት አናቱ ላይ ጉዳዩ ሁሉ ፈላበት።
ድንገት ተነሳና ወደ አባቱ ሄደ ቤተሰቡ የሚይዘው ግራ ገብቶታል።
አባት ያሉትን በሬዎች በተገኘው ዋጋ ለመሸጥ ይጣደፋል። ልጆች ፍራሽ ያስራሉ።
እናት በርጩማ ላይ ራሷን በ ሁለት መዳፍዋ ደግፋ ተንሰቅስቃ ታለቅሳለች። አቤል አባቱን ሊጠይቅ የነበረውን ጥያቄ ተወው። እንባው አቀረረ በ እንብርኩ ሆነና እናቴን ባፅናናት ብሎ ያሰበውን ቃላት መደርደር ጀመረ። ወድያው እንባውን ማቆም አቃተው። ቀጠለና :-


''እማ በቃሽ ስንት ቀን ታለቅሻለሽ? እኛ ልጆችሽ እስካለን ሁሉ ይተካል።ደግሞ ሌላ ምትክ ቦታ መንግስት ይሰጠን ይሆናል'' ብሎ ከመናገሩ
እናቱ 'እሳት ጎርሳ' ተነሳችና በቁጣ አየችው ልጅ መሆኑን የረሳች ይመላል ቀጠለችና
'' ካሁን በሁዋላ መንግስት መንግስት አትበል ከፊቴ.......
ከ አባትህ ጋር ከእዚህ ቦታ ስንመጣ አንድ ወፍ ዝር አይልም ነበር።
አባትህ ወደ እርሻ ሲሄድ ስንት ጊዜ ነብር የበላው ይሆን? እያልኩ ነፍስ እና ሥጋዬ ስትላቀቅ ከረምኩ?እመብርሃን ባማላጅነቷ ከለለችልኝ እንጂ......ተምርያለሁ ከምትሉት ከናንተ እኔው ደንቆሮዋ እሻላለሁ። መንግስት ለምንድነው ነፍስና ሥጋዬ እየተላቀቀ ካቀናሁት መሬት ና በፍቅር ከምኖርበት ሕዝብ የሚነጥለኝ? በል አስረዳኝ? የ እንጀራ ልጅ ነን እኛ ? ንገረኝ ያንተ ትምርት ለ እዚህ መልስ ካለው አሁን ንገረኝ? በላ? .......የዛሬ ሳምንት ለቀው የሄዱት እነ እማዋይሽ የት እንዳሉ ታውቃለህ? ከ መንግስት አድርሱን አቤት የምንለው በደል አለ ብለው ቢሄዱ የሚያናግራቸው ጠፍቶ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ግቢውን ከፍቶላቸው ሰርቶ የሚበላ እጃቸው ያዲሳባ ሕዝብ ለማኝ መሆናቸውን አሁን አባትህ ነገረኝ። እረፈው ! እናትህ ለማኝ ልትሆንልህ ነው!'' ለቅሶው ባሰባት።
ቤተሰቡ ንብረቱን እየሰበሰበ ሁሉም ጆሮውን ጣል አርጎ ይሰማ ነበርና ሁሉም ይህን አዲስ ግን ደግሞ ሌላ መከራ ሲሰማ ስራውን አቁሞ ማልቀስ ጀመረ። መንደሩ ሰሞኑን ለቅሶና 'ኡኡታ!' ለምዷል የለቅሶው ምክንያት ስለሚታወቅ ማንም አዲስ ነገር ተፈጠረ ብሎ አይመጣም። ወደ ምሽቱ ላይ ሁሉም ተሰብስቦ ለወጉ ያህል ቡና ተፈልቶ ''የናንተ መቼ ነው ውጡ የተባላችሁት? የናንተስ መቼ ነው?'' መባባል ልማድ ከሆነ ሰነበተ።

ECADF Ethiopian News
በሽፈራው ሽጉጤ ትዕዛዝ ከተፈናቀሉት የአማራ ብሄር ተወላጆች መካከል ጥቂቶቹ(ፎቶ ከ ECADF)


አቤል ግራ ገባው እናቱ ማፅናኛ የሚለው ቃላት ሁሉ ማለቃቸውን ሙሉ በሙሉ አወቀ። እናቱ ብዙ የምትበልጠው ነገር መኖሩ ዛሬ ገባው። ዛሬ በፊት ዳዊት መድገም ብቻ የምትችል ይመስለው ነበር። የእርሱ ስነ-ዜጋ ትምህርት ቢያንስ ዛሬ የሚፈይደው ነገር አለመኖሩን ተረዳ።
''መንግስትና ሕዝብ......መንግስት ለ ዜጎቹ ያለበት ግዴታ......ዜግነት......የ ዜግነት መብቶች......ወዘተ'' የሚሉት የ ስነ-ዜጋ ትምርት ላይ ያሉ ቃላት በ አይኑ ላይ ተርመሰመሱበት።
ቀና ሲል አባቱ በፍቅር ሲመለከተው አየ። ለመጠየቅ ድፍረት አገኘ። የ አባቱ አይኖች እንደዚህ የሚያዩት ከሆነ የጠየቀው ሁሉ እንደምደረግለት ያውቀዋል። እና ጠየቀ

'' አባ'' አለ አቤል።
''ወየ ልጄ'' አለ አባት ተስፋ የቆረጠ ፊቱን ወደ ልጁ አዙሮ።
'' ስነ-ዜጋ ትምርት ላይ ትቸር መንግስት ለ ህዝቡ ያስባል፣ህዝብን ይንከባከባል ያሉን ውሸት ነው ማለት ነው?ማነው የ ስነ-ዜጋ ትምርት ደብተሬ ላይ የተፃፈውን ከ ደረሰብን ጋር የምያስታርቅልኝ ?'' አለው ሲፈራ ሲቸር።
አባት ለመልሱ ጊዜ አልወሰደበትም '' አንተው ነህ ልጄ አንተው ነህ! ስነ-ዜጋ ደብተርህ ላይ የተፃፈውን የሚያጣምሙትን የምታስተምር አንተው ነህ ልጄ ዓለም ይሄው ነች በ ዘረኞች፣በ ጥቅመኞች ፣ ህዝብን ከ ሕዝብ ጋር በ ማላተም ትርፍ ያገኙ በሚመስላቸው ሰዎች ተሞልታለች። ሆኖም ግን ፀረ-ዘረኞች፣ፀረ-ጥቅመኞች ና ህዝብን ከ ሕዝብ ጋር በሚያስማሙ ሃሳብ አፍላቂዎችና ፖለቲከኞች ብዙ ጊዜ ከ አደጋ ድናለች በ እያንዳንዱ የ ህዝቦች አደጋ ውስጥ አንዳንድ የ አደጋ አምካኞችን እግዝያብሔር ፈጥሮላታል።ለምሳሌ በ አሜሪካ የ ባርያ ፍንገላ ውስጥ አብርሃም ሊንከንን፣ በ ናዚና ፋሺዝም ክፉ ተግባር ውስጥ እነ ዊንስተን ቸርችልን እየፈጠረ ሰዎችን አድኗል። ማን ያውቃል ደብተርህ ላይ የተፃፈውን ከ ገሃዱ ዓለም ጋር የምታስታርቀው አንተ የማትሆንበት ምን ምክንያት አለ? ንገረኝ ምን ምክንያት አለ? ከ ቂም በቀል ነፃ ልቦና ብቻ ይዘህ እደግልኝ ልጄ አይዞህ !'' አለ አባት ።


አቤል እንባውን አቅርሮ ዝም አለ።

አባት ቁጢጥ ብሎ ቁመቱን ከ ልጁ ቁመት ጋር አስተካከለና '' ልክ አደለም? ተሳሳትኩ ?'' አለ።
አቤል ራሱን ግራና ቀኝ በማወዛወዝ አለመሳሳቱን ገለፀ አሁን ግን እንባው መውረድ ጀምሮ ነበር። አባት ወደደረቱ አስጠጋውና ''ታድያ ለምን ታለቅሳለህ? እኔ አባትህ እያለሁ ክንዴን ሳልንተራስ አይርብህም፣ አይጠማህም ሁሉን ሰርቼ ነው ያገኛሁት የሰው ላብ አልወሰድኩ ሁሉን መልሼ አገኘዋለሁ!'' አለ።
አቤል '' ለ እዛ አደለም የማለቅሰው''
''ታድያ ሌላ ምን አዲስ ነገር መጣ የማላውቀው?''
አቤል ወደመሬት አቀርቅሮ ዝም አለ።
''ንገረኝ አይዞህ የኔ ጌታ ንገረኝ'' አባት ግራ ተጋባ።
'' ነገ ትምርት ቤት አልሄድም እነ ሰጠሄኝ፣እነ ግርማቸው ሁላችንም ባንድቀን መለያየታችን ነው ....ጓደኞቼን .....አስተማሪዬ ቲቸር አልማዝ.....ቲቸር አልማዝ አንድም ቀን ሲያለቅሱ አይቼ አልቅውቅም ነበር ትናንት ግን ውጡ ተብለናል ብለው መሬት አቀርቅረውሲያለቅሱ ነው የዋሉት......እህህህ '' አቤል ጧ ብሎ አለቀሰ።

አባት ለዚህ አይነቱ ነገር መልስ የለውም።ልጁን አቅፎ አብሮ ማልቀስ ጀመረ።በ ልጅነቱ ባንዲት ጀንበር ቀየውን ለቆ ብሄድ ለ አንድ ሕፃን ልጅ የሚፈጥረውን ስሜት አሁን ልብ ]አለው።አባትና ልጅ ተላቀሱ። በ መሃል አባትና ልጅን የለያያቸው የ መንግስት ታጣቂ ከ ቤት ገብቶ በጁ የያዘውን የ ስም ዝርዝር እያነበበ ''የናንተ ወረዳውን ለቃችሁ የምትወጡበት ቀን ነገ መሆኑን አውቃችኋል? '' ብሎ ሲደነፋና በ ቁጣ አይን ቤተሰቡን ስገላምጥ ነበር። ታጣቂው ቶሎ ከቤት መውጣቱ ነው አንጂ ትልቅ ፀብ ሊፈጠር የነበረ መሆኑ የ ቤቱ የ ዝምታ እና ሊገነፍል ያኮበኮበ የ ቁጣ መንፈስ ያስታውቃል።
////////////////--------------/////////////////////-----------------//////////////////////////----------------///////////
ይህ ከ ሆነ ከ ሳምንት በኋላ አቤል ና ቤተሰቡ የተገኙት አዲስ አበባ በ አንድ መጋዘን ውስጥ ከ ብዙ ከነርሱ መሰል ስዱዳን ጋር ነበር። አቤል አሁንም የ ስነ-ዜጋው ደብተር ላይ የተማራት ስነ-መንግስት ምራፍ ሶስት ላይ ያሉት ፅሁፎች ትዝ ብለውት እረፍት ነሱት። ቢቸግረው ያገኘውን ሰው ሁሉ መጠየቅ ጀመረ። ቆይቶ ግን አጎቱ ''ልጄ ደብተርህን በጉያህ አርገው! እንዳታስፈጄን '' ያለው ንግግር ዝም አንዲል አረጉት።
አቤልን አጎቱ ''ደብተርህን በጉያህ!እንዳታስፈጄን'' ያሉት ቀን አይረሳውም።ቀኑ የ አዲስ አበባ የ መጋቢት ወር ዝናብ መሬቷን ማራስ የጀመረበት ቀን ነበር።ድንገት ''ከ መንግስት የመጣን ነን መንግስት የወሰነውን ልናሳውቃችሁ ነው '' ያሉ ሰዎች ስደተኞቹ ወዳረፉበት መጋዘን መጥተው መንግስት ወደየ ክልላችሁ ግቡ በሏቸው ብሎናል'' ብለው ሲናገሩ ።

አቤል በንዴት ተነስቶ

'' ሃገሬ ስንት ነች? ኢትዮጵያ አንድ አይደለችም? እስከ ዛሬ የኖርኩባት የኔ ሀገር አደለችም ? የተወለድኩት ጉርዳፋርዳ ነው። ሌላ ሀገር አላውቅ?'' አቤል በንባ የተሞሉ አይኖቹን ይዞ ፊቱን ከ ካድሬው ወደ አባቱ አዞረና ጥያቄውን ደገመው። በ አዳራሹ ውስጥ ያሉት ሁሉ ትንፋሻቸውን ውጠው ማዳመጥ ጀመሩ።አቤል ቀጠለ '' አባዬ ሃገረ ስንት ነች? ሀገራችሁ ግቡ የሚለን?''ብሎ ሲናገር አዳራሹ ለቅሶ በለቅሶ ሆነ።
ከለቅሶው ቀጥሎ ግን ጥያቄው ጎረፈ በተለይ በትምህርት ገፋ ያሉት ጥያቄ ሊያባራ አልቻለም።
''በ ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ መኖርያውን ትቶ መሰደድ የ ሀገር አደጋ አደለም? ቀይመስቀል የት ነው? የ አደጋ ጊዜና ዝግጁነት ኮሚሽን የሚባል መስርያበት በ 'ብአዴን ' ተተካ? ይህ ሰው ሰራሽ አደጋ አይደለም?'' ወዘተ ጥያቄ።

የ አቤልን የምታህል ከባድ ጥያቄ ግን አልተገኘችም የ ትውልዱ ጥያቄ ሆና ትኖራለችና።

'' ሃገሬ ስንት ነች? ኢትዮጵያ አንድ አይደለችም? እስከ ዛሬ የኖርኩባት የኔ ሀገር አደለችም ?'' የምትለዋ ጥያቄ።

አዎን ሀገራችሁ ግቡ ባዮች ከ አቤል የከበደ ጥያቄ ይገኝላችሁ ይሆን ? ሀገራችን ኢትዮጵያ በናንተ አቆጣጠር ስንት ነች? አሁን የምንኖርባት ሀገራችን አደለችም? ምንጭ 
በ ጌታቸው በቀለ

ኦስሎ
የታሪኩ መነሻ የ አሜሪካ ድምፅ ራድዮን የ አማርኛው አገልግሎት በ መጋቢት / 2004 ዓም የዘገበውንና ከዚህ በታች የተያያዘውን ከፍተው ያዳምጡ።
http://www.voanews.com/templates/mediaDisplay.html?mediaPath=http://media.voanews.com/audio/AMH_aa_Farmers_dislocated_in_Southern_Ethiopia_Part_1-04April2012.Mp3&mediaContentID=፩፬፮፫፮፲፩፭


   

Sunday, January 27, 2013

የ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ቅዱሳን ገዳማት ማንነት፣ ለ ኢትዮጵያ ያደረጉት አስተዋፅኦ፣የገጠሟቸው ችግሮች እና የ ምዕመናን ድርሻ

የ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ቅዱሳን ገዳማት ማንነት፣ ለ ኢትዮጵያ ያደረጉት አስተዋፅኦ፣የገጠሟቸው ችግሮች እና የ ምዕመናን ድርሻ
በ  ''ሳዝ ፕሮሞሺን ኢትዮ-ኖርዌይ ካናል'' (ቪድዮ)  http://www.sazpromotion.com/

Saturday, January 26, 2013

ጀግንነት ፈፅሞ አለመሸነፍ አይደለም። ተሸንፎ መነሳት ነው-ለ ብሔራዊ ቡድናችን ፣ለ አሰልጣኞች እና ለደጋፊዎች ሁሉ

ፎቶ ከ ድሬ ዩቱብ (ለ ናይጀርያው ግጥምያ ዝግጅት ላይ)
 
 
ትናንት አርብ ጥር 17/ 2005 ዓም ኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ምሽቱ ሶስት ሰዓት ጀምሮ ደቡብ አፍሪካ የተላለፈው ኢትዮጵያ እና ቡኪናፋሶ እግር ኳስ ውድድር ኳስን መሰረታዊ ባህሪ በያዘ መልኩ ማለትም ማሸነፍ ወይንም መሸነፍ አንዱን መርጦ አብቅቷል። አዎን ኢትዮጵያ በኩል አራት ጎሎች ተቆጥረዋል። ጫወታው እንዳበቃ በመጀመርያ በጣም ተናደድኩ ትንሽ ቆይቼ ነገሩ አለመሞቱ ግን ቡድኑ ሞራል ምን ያህል ይሆን? የሚለው ብቻ አሳሰበኝ።ዛሬ ቅዳሜ ጫወታውን ደግሜ አየሁት።በ እውነት ትናንት ያልታዩኝ የተጫዋቾቻችን ድንቅ ጥበብ ታየኝ።ሰው አንድን ነገር ለመመልከት የረጋ ልቦና ይሻል የሚባለው ልክ ነው።ዛሬ ከስሜት ውጭ ሆኘ ስመከት ቡድናችንን የሚያስደንቁ ጥበቦቹ ታዩኝ።እናም የሚከበር ቡድን ግን አኛ ተመልካቾች ልናከብረው እና ልናደንቀው የሚገባ ነው ብዬ አሰብኩ።
አንድ ወቅት አስራዎች አመታት በፊት ግብፅ ውስጥ ብሔራዊ ቡድናችን (ለማጣርያ ይመስለኛል)ሲጫወት ቡድኑን ለማዋከብ የነበረው ተመልካች ዘዴ በጣም መጮህ እና እዚህ በፊት ሰማንያ አና ዘጠና ሕዝብ የተሞላ ስታድዮም ውስጥ ተጫውቶ የማያውቀውን ተጫዋች ማዋከብ ነበር። በወቅቱ ቡድናችን አለም አቀፍ ጫወታ ተሞክሮ ስሌለው እና ሰላሳ ሕዝብ የሚይዝ አዲስ አበባውን ስታድዮም ብቻ ስለሚያውቅ ትልቅ ችግር ፈጥሮ ነበር። አሁን አቅም ተፈጥሮ ጫወታው ቴክኒክ ሁሉ ጥሮ መስመር ላይ ነው ያለው። የተሞከሩት ጎል ሙከራዎች ዕድል ጉዳይ እንጂ ምርጥ ተጫዋቾች እንዳሉን ለመረዳት አይናችንን የሚከፍቱ ናቸው።አሁን የቀረን አንዲት ነገር ነች። ጀግንነት፣እራስን ማወቅ፣ካለምንም ጉራ ታላቅ ተጫዋቾች እንዳሉን ማወቅ፣ይህንንም ለቡድኑ መንገር።ሽንፈት የሚጀምረው እራስን ዝቅ አድርጎ ማየት ሲጀመር ነው።ቡክናፋሶች ጎል ዕድል ቢያገኙም፣በ ጫወታ ቢገዳደሩንም፣ አሁንም የማሸነፍ እድላችን እጃችን ውስጥ መሆኗን ማወቅ አለብን። መሸነፍ፣ፈተና፣ተስፋ መቁረጥ አንዳንዴ ተደጋግመው የተጫኑ የሚመስሉበት ጊዜ አለ። እዚህ ላይ ነው ጀግና የሚያስፈልገው። ''ቁርጥ ቀን ባይመጣ ሁሉም ጀግና ነበር'' የሚባለው እዚህ ቀን ነው። ቡድናችን አሰልጣኞቻችን ሁሉ በአንድ መንፈስ ቀጣዩን ጫወታ እንደሚያሸንፉ ሙሉ ልብ እራሳቸውን ከማወቅ እና ከማክበር ጋር ይጫወቱ ይመኑ ታምር ይሰራሉ።

እዚህ ላይ በቡድናችን የሞራል መጠበቅ ላይ እክል ፈጥረዋል የተባሉ ወደፊት ጥብቅ ምርመራ የሚፈልጉ እና በቀላሉ የማይታዩ ጉዳዮች እንደነበሩ ይወራሉ። ይህንን በተለይ አስልጣኝ ሰውነትም ሆኑ ምክትላቸው ተመሳሳይ ስህተት እንዳይሰሩ ለ ፖለቲካው አካላት ም ሆነ ለሕዝቡ በድፍረት እንዲነግሩልን እንጠብቃለን። በ እዚህ ዘመን ''የተሰወረ የማይታይ ያልታወቅ የማይገልጥ'' የለምና። ለሁሉም ግን አሁን መደረግ ያለበት  ቢያንስ ቀጣዩ ጫወታዎች እስከሚጠናቀቁ በ ትዕግስት የ ቡድኑንም ሆነ የደጋፊውን ህብረት እንዲጠበቅ ማድረግ ይመስለኛል።

ጀግንነት ፈፅሞ አለመሸነፍ አይደለም። ተሸንፎ መነሳት ነው። ጀግናን ጀግና የሚያሰኘው ፈፅሞ የማይሸነፍ ምትሃታዊ ፍጥረት ስለሆነ አይደለም ዕድል ወይንም ትንሽ ስህተት አልያም ችላ ብሎት ጀግና የመጀመርያ ሽንፈት ይሸነፋል። ሁለተኛ እና ሶስተኛ ላይ ግን የሚያስደነግጥ ብቻ ሳይሆን የሚያርበደብድ ይሆናል።የዓለማችን ጀግኖች ተሸነፉ ሲባሉ እንደገና ተነስተው ስለሚያሸንፉ ያለፈውን ሽንፈታቸው ከቶ ማን ሊያስበው ይቻላል? እንግሊዝን እስኪ አለም ዋንጫ ላይ የሚደርስባትን እንመልከት።እንዲያ ድንቅ ክለቦች ያላት ሀገር በዓለም ዋንጫ ላይ ግማሽ መድረስ ሲያቅታት እንግሊዝ ሕዝብ እና መንግስት ሰቀቀን የማይሆን ይመስለናል ? ግን እንግሊዞች ኳስ ስለማይችሉ ነው የተሸነፉት? አይደለም። ኳስ እንዲህ ስለሆነች ነው። ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ጫወታ ዛሬ አለፍ አለፍ እያልኩ ቡክናፋሶ ጋር ያደረገውን ጫወታ ስመለከት እጅግ ድንቅ ተጫዋቾች እንዳሉን ግን እኛ ልናከብራቸው፣ልናደንቃቸው፣ ታላቅ ችሎታ እንዳላቸው አንዳንድ ቴክኒካዊ ስራዎችን እያስተካከሉ እንዲሄዱ እራሳቸውን ዝቅ እንዳያደርጉ መንገር ባለዑያዎች ብቻ እንደሚገባ አመንኩ። ይህ ደግሞ ለሽንገላ ሳይሆን ቀድሞ የነበረው ''እኛ ኳስ አይሆንልንም'' የሚባልበት ጊዜ ላይ ላለመሆናችን ችሎታቸውን ልዩ አቀራረብ ያሳዩን ተጫዋቾች ምስክር ናቸው። ዛሬ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ደረጃዋ አለም አይደለም እኛ ኢትዮጵያውያንም ያስደነቀን ጉዳይ ነው። ወደ ኋላ ፈፅሞ መመለስ የለም!

በመጪው ማክሰኞ ናይጄርያ ጋር በሚኖረው ውድድር ተአምር የመስራት ብቃቱም ሆነ አቅሙ አላችሁ።በ አንድ በኩል ናይጀርያ በትናንትናው ቡክናፋሶ ጋር በተደረገው ጫወታ ቡድናችንን ዝቅ አድርጎ የማየት ሁኔታ ሊኖር እንድሚችል ይገመታል።ይህ ጥሩ ዕድል ነው።

እርግጥም ቡክናፋሶ ጋር የሆነ አምላክ እኛ ጋርም አለ። ናይጄርያ ጋር ያለ አምላክ እኛ ጋርም አለ። ቀጣዩን ናይጄርያ ጋርም ሆነ ቀጥለው በሚከፈቱት ዕድሎች ቡድናችን እንዲያሸንፍ እኛ ተመልካቾች የምናደርገው ሁለት ነገር ነው። አንድ ስታድዮም ተገኝቶ መደገፍ ሁለተኛው እና ዋናው ማንም ችላ ሊለው ወይንም ሊረሳው የማይገባው ከልብ የሆነ ቢያንስ ጥቂት ደቂቃዎች ልመና ወደ እግዚአብሔር ማቅረብን ነው። ያኔ ሁሉም ግዴታውን ተወጣ ማለት ይቻላል።የ ኢትዮጵያን ቡድን ያወደሱ ብእሮች እንደገና ይቀረፃሉ።ዋልያዎች በርቱ!

ጀግንነት ፈፅሞ አለመሸነፍ አይደለም። ተሸንፎ መነሳት ነው። ጀግናን ጀግና የሚያሰኘው ፈፅሞ የማይሸነፍ ምትሃታዊ ፍጥረት ስለሆነ አይደለም ዕድል ወይንም ትንሽ ስህተት አልያም ችላ ብሎት ጀግና የመጀመርያ ሽንፈት ይሸነፋል። ሁለተኛ እና ሶስተኛ ላይ ግን የሚያስደነግጥ ብቻ ሳይሆን የሚያርበደብድ ይሆናል።

ኢትዮጵያ ዘላለም ትኑር!

ጌታቸው  

ኦስሎ

Thursday, January 24, 2013

ለንደን የሚገኘው የ ኤርትራ ኤምባሲ ታግቶ ዋለ። የ አቶ ኢሳያስ ፎቶ ወርዶ በ ወጣቶቹ ተረጋገጠ (ቪድዮ)

ለንደን እንግሊዝየሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲበ ኤርትራውያንወጣቶች መታገቱንየተለያዩ የዜና ዘገባዎችበ ዛሬውእለት ዘግበዋል።የ 'ኢትዮጵያሪቪውን' ጨምሮበተለያዩ ብሎጎችሙሉ ፊልሙንአስደግፈው ዘግበውታል።'ጉዳያችን' የጡመራ መድረክባለፈው አመትመጋቢት ወርላይ የኤርትራን የፖለቲካ አቅጣጫእና በግብፅ አዲሱ' እስላምወንድማማቾች ህብረት'ስልጣን ከመያዙጋር እናበ ኢትዮጵያበወቅቱ ከነበሩትጠቅላይ ሚኒስትርአስተሳሰብ አንፃር'' ኤርትራ ጉዳይ ሃያ አንደኛው /ዘመን ልጆች አስተሳሰብ'' በሚልአርዕስት ስርአንድ ዘገባአቅርባ ነበር።ዘገባውን ይህንበመጫን ያንብቡ-(http://gudayachn.blogspot.no/2012/03/blog-post.html)

በኤርትራ የፖለቲካትኩሳቱ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረለመሄዱ የሚያሳዩሁለት ክስተቶችበያዝነው ሳምንትታይቷል። የመጀመርያውባለፈው ጥር14/2005 የተሞከረው የማስታወቅያ ሚኒስትርመስርያቤትን በታንክየታገዙ ወታደሮች
ለመቆጣጠር ያደረጉትጥረት(የቪድዮዘገባዎችንይህንበመጫንይመልከቱ)(http://gudayachn.blogspot.no/2013/01/142005.html)ሲሆን ዛሬደግሞ ለንደንየሚገኘውን ኤምባሲ ከሃያ በላይ ወጣቶች ተቆጣጥረው መዋላቸውነው። ከእዚህ በታች ቪድዮው ላይ እንደምትመለከቱት ወጣቶቹ አቶ ኢሳያስን ፎቶ ሰብረው በእግራቸው ሲረግጡት ከመታየቱም በላይ ኢምባሲው ግድግዳ ላይ ቀይ ኤክስ የተሰረዘ አቶኢሳያስን ምስል መልሰው ሰቅለዋል።ሙሉ ቪድዮውን እዚህ በታች ይመልከቱ።



 
 
 
 

Tuesday, January 22, 2013

በ አስመራ ኤርትራ በ ጥር 14/2005 ዓም የተከሰተው የ ወታደሩ አመፅ በተለያዩ የ አለም የ ቴሌቭዥን ጣብያዎች ሲዘገብ (ቪድዮ)

በ ኤርትራ አስመራ ትናንት ጥር 14/2005 ዓም ከ ሁለትመቶ የማያንሱ ወታደሮች የ ቴሌቭዥን እና ራድዮ ጣቢያውን ተቆጣጥረው የታሰሩ እስረኞች እንዲፈቱ እና የ 1990 ዓም  ህገ መንግስት እንዲከበር ጠይቀዋል። ይህንኑ  ዜና ሮይተር፣ኤ ኤፍ ፒ እና ኤሮ ኒውስን  ጨምሮ በ አጭሩ ዘግበውታል።
 ከምሽቱ 4 ሰዓት አልፎ የተላለፈው የ ኤርትራየ እንግሊዝኛው የ ቴሌቭዥን ፕሮግራም ምንም ነገር እንዳልሆነ ቀጥታ ሌሎች ዜናዎችን  ማስተላለፉ እና አለም ስለሚያወራው ጉዳይ ምንም አለማውራቱ አስገራሚ ትዕይንት ነበር። 
ጉዳዩ ግን ተለያዩ የ ዜና ዘገባዎች እንዲህ ቀርቧል።

1/ ኤሮ  ኒውስ 

 
 
 
 

2/ አልጀዝራ 
 
3/ ቴክ ኔትዎርክ ኒውስ 
 
 
 

Wednesday, January 16, 2013

ቤተክርስቲያንን ለሚሰቅሏት እና ለሚያሰቅሏት ወዮላቸው!

አዲስ አበባ ስብሰባ የተቀመጠው ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 6 እስከ ጥር 8/2005 ዓም ያደረገው ስብሰባ ዝርዝር ጉዳዩ ባይገለፅም ኢትዮጵያ ቴሌቭዥን አቡነ አብርሃም የተነበበው የውሳኔ መግለጫ ሕዝበ ክርስቲያንን ያሳዘነ ቤተክርስቲያንን ሌላ የመከራ እና የመከፋፈል ዘመን ፊቷ የደቀነ ሆኗል  ዛሬው ጥር 8/2005 ዓም 'ኢሳት ' አጭር ሞገድ ራድዮ ስርጭቱ ላይ 'ዘግይቶ የደረሰን ዜና' ብሎ ባቀረበው ዜና '' አቡነ አብርሃም የተነበበውም ሆነ ለጋዜጠኞች የተበተነው ወረቀት የደብዳቤ ቁጥር እና ማህተም የሌለው መሆኑ ታወቀ '' ካለ በኋላ ቀጠለና ''አቡነ ሕዝቅኤል አብዛኛው አባቶች ባላመኑበት ሁኔታ ማህተም አላሳርፍም ማለታቸው እና ስብሰባውን እረግጠው መውጣታቸውም ተስምቷል '' በማለት ዘግቧል

ቤተክርስቲያን ሕይወቷ መስቀል ላይ ነው። ለሚሰቅሏት እና ለሚያሰቅሏት ወዮላቸው።

ቤተክርስቲያንን ለሚሰቅሏት

ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እጅግ የሚያሳዝን ወቅት ላይ ነች። አስተዳደራዊ ጉዳይዋን ሳትፈታው፣የ ፓትርያርክ ጉዳይ፣ይህን ፓትሪያርክ ጉዳይ ሳትፈታው የዋልድባው እያለ ይሄው ዛሬ ደግሞ ሁለት አስርተ አመታት የተለያዩባት አባቶቿ በአለፈው ወር ዳላስ አሜሪካ እንደተመለከትነው አባቶች አንድ ላይ ኪዳን ሲያደርሱ ደስ ያለንን ያህል ዛሬ ዳግም አዘንን።መንግስት እርቀ ሰላሙ ሂደት ጀመሮ እስከ ዛሬዋ እለት ድረስ በግልፅ ያሳያቸው ጣልቃ ገብነት ስራዎች ነበሩ። እነዚህም ውስጥ ፕሬዝዳንት ግርማ 'ብፁዕ አቡነ መርቆርዮስን ወደመንበራቸው እንዲመለሱ ቢደረግ'' በሚል የፃፉትን ደብዳቤ 'መንግስት በቤተክርስቲያን ጉዳይ አይገባም' በሚል እንዲነሳ ማድረጉ፣ አስታራቂ ኮሚቴ አባላት በፀጥታ ኃይላት እንዲዋከቡ እና ተገፍተው ሀገር እንዲወጡ መደረጉ፣እርቀ ሰላሙ እየተካሂያደ ' ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ' እንዲዋቀር በመግፋት፣በመጨረሻም ጥር 6 እስከ 8 በተደረገው ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ አባቶችን በማስፈራራት አዲስ ፓትርያርክ ምርጫው እንዲከወን በመጣደፍ ላይ መሆኑ ሁሉ ጉልህ ማስረጃዎች ነበሩ እናም ቤተክርስቲያንን እየሰቀላት ያለው መንግስት ቤተክርስቲያንን ቁስል ከማድረቅ ይልቅ ሌላ መለያየት እነሆ አዲስ ምዕራፍ ከፈተባት።

ቤተክርስቲያንን ለሚያሰቅሏት

''እናንተንጳጳሳት አድርጎ ለሾመበት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ እኔ በኋላ ለመንጋይቱ የማይራሩ ነጣቂዎች ተኩላዎች እንደሚመጡ እኔ አውቃለሁ '' ሐዋርያት ሥራ 2028-30

ቤተክርስቲያን ጉዳይ አባቶች የመምራት፣የማስተማር እና እስከ መስዋዕትነት የሚጠይቅ ጉዳይ ቢኖር ግንባር ቀደምትነት እንዲቆሙ ለአባቶቻችን አደራ መሰጠቱን መፅሐፍ ቅዱስ የሚያረጋግጥልን እውነታ ነው።ዛሬ ግን ቤተክርስቲያንን መስቀል ባይችሉ በመከራ መስቀል ላይ ሊሰቅላት ከሚታትሩ ጋር ጮማ እየቆረጡ የሚያሰቅሏት አንዳንድ አባቶች አልጠፉም። ''በአንድ ገበታ ተቀምጠው ሐሰት ይናገራሉ'' የተባለለት ዘመንን ደረስንበት ማለት ይሆን? ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ታላቁ ገዳም ዋልድባ እየታመሰ ምንድነው የሆነው? ብለው ችግሩን ማዳመጥም ሆነ መፍትሄው ላይ ታች ማለት ያለባቸው አባቶች አዲስ አበባ ላይ ሲንሸራሸሩ መታየታቸው  ሌላው ቀርቶ የገዳሙን ችግር እንወያይ ብለው ምእመናንን ለማናገር መንግስት ሹመኞችን ግልምጫ እና እስር የፈሩ መሆናቸው፣ ይህ ሁሉ ባይሆንላቸው ባለፈው ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ አጀንዳ አስይዞ ለመወያየት ቅምጥል መንግስት ሹማምንትን ፊት የሚመለከቱ አንዳንድ አባቶች  ቤተክርስቲያንን ከሚያሳቅሏት ወገን ናቸው።

ዛሬ ከወደ አዲስ አበባ የተሰማው ወሬ ቤተክርስቲያንን የሰቀሏት እና የሚያሰቅሏት ተባብረው ላለፉት ሁለት አስርተ-አመታት የነበረባትን ሲኖዶስ ክፍፍል ሌላ አዲስ ምዕራፍ ሊያራዝሙባት ሽር ጉድ ማለታቸውን ነው።

ጥያቄው እኛ ከየት ወገን ነን? ከሚሰቅሉት ወይስ ከሚያሰቅሉት?

ቤተክርስቲያን ችግር ውስጣችን የደማ ሁሉ እና በሚሰራው ማባርያ የሌለው ጥፋት ያዘንን ሁሉ ዝምታችን ከከንፈር መምጠጥ ባላለፈ ተግባር ላይ መሆናችን ከሚሰቅሏት ወይንም ከሚያሰቅሏት ወገን ላለመሆናችን ከቶ ምን አይነት መረጃ ይኖረን ይሆን? ኑሮዬ፣ጨርቄን፣ ወዘተ እያልን በመስቀል አልያም በማሰቀል ላይ መሆናችንን ልብ ብለነው ይሆን?ጌታችን ቀራንዮ ሲሰቀል ሰፍነግ ያቀበሉም ሆኑ ከመስቀሉ ስር ገበጣ የሚጫወቱ- ሁለቱም በሰቃይነትም ሆነ አሰቃይነት ተፈርጀዋል።ቤተክርስቲያንን ለሚሰቅሏት እና ለሚያሰቅሏት ወዮላቸው! ዝምታ የሚሰበርበት ''የቤተክርስትያኔ ጉዳይ ያገባኛል'' የምንልበት እውነተኛው ጊዜ ነው እና 


ይቆየን

ጌታቸው
ኦስሎ 

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።