ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, February 28, 2020

በፋሽሽት ጣልያን ወረራ ወቅት የሴት አያቷን የጦር ግንባር ታሪክ የፃፈችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አሜሪካዊት መዓዛ መንግሥቴ መፅሐፍ ''ዘ ሻዶው ኪንግ '' (The Shadow King) አድናቆት አትርፏል።

ጉዳያችን ሚድያ፣ኮሚኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት 
Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant

ደራሲ መዓዛ መንግሥቴ (Photo New York Times, Nina Subin)

መዓዛ መንግሥቴ ትባላለች።አያቷ ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት ያደረጉትን ተጋድሎ ኢትዮጵያ ድረስ መጥታ የጦርነቱን ቦታዎች ተመልክታለች።እናቷ ከአያቷ የሰሙትን እያንዳንዱን መራር ተጋድሎ ከትባዋለች።መትሽፉ የወጣው በእዚህ ዓመት መስከረም ወር ነው።

''ታሪኩ ለራሴ የመሰጠኝ፣ያስገረመኝ ነው።አያቴ ወደ አርበኝነት ስትሄድ የአባቷን ጠበንጃ ይዛ ነበር።'' ያለችው መዓዛ መፅሐፉ የአፍሪካውያን ሴቶች ተጋድሎ ኩራት ማሳያ መሆኑን ያስመሰከረ ተብሏል።መዓዛ ከእዚህ በፊት በጥር 2010 ዓም እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር  ''Beneath the Lion's Gaze'' የተሰኘ መፅሐፍ በ1966 ዓም በነበረው የኢትዮጵያ አብዮት ወቅት የሚተርክ መፅሐፍ ፅፋ ነበር።

''ዘሻዶው ክንግ'' የተሰኘው መፅሐፍ በአሁኑ ጊዜ በአማዞንም ጭምር እየተሸጠ ሲሆን አማዞን መፅሐፉን ሲያስተዋውቅ ስለመፅሐፉ የለጠፈው ፣ስለመፅሐፉ ይዘት በሚገባ ያስረዳል።

A gripping novel set during Mussolini’s 1935 invasion of Ethiopia, The Shadow King takes us back to the first real conflict of World War II, casting light on the women soldiers who were left out of the historical record.
With the threat of Mussolini’s army looming, recently orphaned Hirut struggles to adapt to her new life as a maid in Kidane and his wife Aster’s household. Kidane, an officer in Emperor Haile Selassie’s army, rushes to mobilize his strongest men before the Italians invade. His initial kindness to Hirut shifts into a flinty cruelty when she resists his advances, and Hirut finds herself tumbling into a new world of thefts and violations, of betrayals and overwhelming rage. Meanwhile, Mussolini’s technologically advanced army prepares for an easy victory. Hundreds of thousands of Italians―Jewish photographer Ettore among them―march on Ethiopia seeking adventure.
As the war begins in earnest, Hirut, Aster, and the other women long to do more than care for the wounded and bury the dead. When Emperor Haile Selassie goes into exile and Ethiopia quickly loses hope, it is Hirut who offers a plan to maintain morale. She helps disguise a gentle peasant as the emperor and soon becomes his guard, inspiring other women to take up arms against the Italians. But how could she have predicted her own personal war as a prisoner of one of Italy’s most vicious officers, who will force her to pose before Ettore’s camera?
What follows is a gorgeously crafted and unputdownable exploration of female power, with Hirut as the fierce, original, and brilliant voice at its heart. In incandescent, lyrical prose, Maaza Mengiste breathes life into complicated characters on both sides of the battle line, shaping a heartrending, indelible exploration of what it means to be a woman at war.



ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Wednesday, February 26, 2020

Gudayachn replied to David Pilling's opinion, issued in Financial Times, under the title of ''Why Abiy Ahmed is more popular in Norway than in Ethiopia'', Feb.26, 2020.



David Pilling (picture FT)

ጉዳያችን ሚድያ፣ኮሚኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት
Gudayachn Multimedia, 
Communication and Consultant 


To: David Pilling
david.pilling@ft.com
      Financial Times


Dear Sir, David, first of all, I would like to thank you for your opinion on Financial Times, under the title of Why Abiy Ahmed is more popular in Norway than in Ethiopia, posted two hours back as of today February 26,2020. 

Fortunately, my origin is from Ethiopia and follows the day to day political situation of the country. On the other hand, I am also living in Oslo and got the chance to attend the recent remarkable Nobel Prize ceremony of the Prime Minister Abiy  in Oslo city hall.

As far as I understand the situation in Ethiopia is quite different from your mentioned sources. In fact the nation is in a real change. But the change process is not so spontaneous like that had happened in 1974 of the  mass revolution and the rebel control of the capital Addis Ababa in 1991. The current political change is big reform but going so slow without dropping the vital political,economic and social values of the ancient and historical nation, Ethiopia. Africa has a good experience in losing valuable assets of social, peace and stability. That is through running a political change process that could abolish all human and capital resources, just through categorizing all former political actors  under the name of ''former regime''. As far as I understand the current political movement of Abiy is attempting a new path of political thinking called MEDEMER.

Abiy’s  introduction of MEDEMER is quite a new phenomena to Africa.In the last two years, since the reform was launched, all political parties could get into the country and move freely. In fact, before them,all political prisoners were released and all media who had been  exiled could be functional in Ethiopia’s territory which was unthinkable even three years ago.

Here I can realize that your source of information is from the extremist group like you mentioned, Jawar Mohamed as a commentator. I think you need to dig a little bit, at least, to visit google about such a person's negative contribution for the security and social cost of the current generation of Ethiopia both at home and abroad. I think also, it is quite a good indicator to know the reason why over One-Hundred fifty thousand people signed a petition against Jawar Mohamed, that is only for the past 18 months. I am not feeling comfortable, when a political commentator like you quote, Jawar, as a reference source of the peace and security of the nation with over one-hundred million people. That is Ethiopia. 

Ethiopia’s current immediate problem is ethnocentric politics running by individuals and activists like you have mentioned, Jawar Mohamed. This politics is not only dangerous to Ethiopia but also for the horn of Africa. It is not even a week since Jawar's idea of ethnocentric politics was seriously criticized by a senior political advisor of Eritrea, Yemane G.Meskel. Yemane, on his reply to Jawar’s tweeter, just three days back on February 22,2020 reads as -

"Our position is not ambivalent.  We strongly believe that the policy of institutionalized ethnicity is toxic & obsolete.  In our view, eradication of this malaise will serve the best interests of Ethiopia. Furthermore, Eritrea & the whole region will benefit from this."

That is why I am saying there is a big information gap between you and the real political situation in Ethiopia. In addition to that, I need to remind you that  your opinion has totally disregarded the recent three consecutive weeks Pro-Abiy demonstrations in over Eight major cities in Ethiopia. 

In general, your opinion needs a big update in the current political situation of Ethiopia. Rather it is based on one sided view of the country. I think you need to see the other side too.

With Best Regards

Getachew Bekele Damtew
E-mail = getachewb221@gmail.com

Editor ጉዳያችን ሚድያ፣ኮሚኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት
Gudayachn Multimedia, 
Communication and Consultant 

Tuesday, February 25, 2020

ሰበር ዜና - የጣልያን መከላከያ ሚኒስትር ሎረንዞ ጐርኒ፣ ፋሺሽት ጣልያን በደብረሊባኖስ መነኮሳት ላይ ለፈፀመችው ጭፍጨፋ አገራቸው ታሪካዊ ተጠያቂነቷን ማመን አለባት አሉ። ቦታውን ሄጄ ለማየት ወስኛለሁ ብለዋል።


====================
ጉዳያችን ሚድያ፣ኮሚኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት 
Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant
=====================


የጣልያን መከላከያ ሚኒስትር ሎረንዞ ጎርኒ  Lorenzo Guerini 

የጣልያን መከላከያ ሚኒስትር ሎረንዞ ጎርኒ  Lorenzo Guerini ዛሬ የካቲት 17/2012 ዓም ጣልያን ውስጥ በሰጡት መግለጫ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1937 ዓም ከግንቦት 21 እስከ 29 በኢትዮጵያ ደብረ ሊባኖስ ገዳም የፋሺሽት ወታደሮች የፈፀሙትን አሰቃቂ ጭፍጨፋ ጣልያን በታሪክ ተጠያቂ የሆነችበት መሆኑን ማመን እንዳለባት ገልጠዋል።


ሚኒስትሩ የጳውሎ ቦሩሶ Paolo Borruso ''ደብረ ሊባኖስ በ1937'' የተሰኘውን መፅሐፍ ጠቅሰው ጣልያን በዘመኑ ከሰራችው ከባዱ የጦር ወንጀል ውስጥ የደብረ ሊባኖሱ እልቂት መሆኑን አብራርተዋል።ዜናውን የዘገበው የጣልያን ዜና አገልግሎት አንሳ (ANSA) እንደገለጠው በደብረ ልባኖሱ እልቂት ሰማዕትነት የተቀበሉት የገዳሙ መነኮሳት 449 ናቸው ቢባልም እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1990 ዓም በተገኘ አዲስ ጥናት የተገደሉት ሰማዕታት መነኮሳት ቁጥር ከ1500 እስከ 2000 እንደሚደርስ ዛሬ ማምሻው ባወጣው ዘገባ ለመረዳት ተችሏል። 


ጉዳያችን GUDAYACHN 

 www.gudayachn.com

የድንግል ማርያምን ዘላለማዊ ድንግልና እና የስላሴን ምስጢር የሚነቅፍ አስተያየት በፌስ ቡክ ገፁ ከሶስት ዓመት በፊት የፃፈው ስፔናዊ አርቲስት በስፔን ክርስቲያን ጠበቆች ማኅበር በያዝነው ወር ፍርድ ቤት ተከሰሰ።

====================
ጉዳያችን ሚድያ፣ኮሚኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት 
Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant
=====================
ዊሊ  ታሌዶ (Willy Toledo)


ዊሊ  ታሌዶ (Willy Toledo) ይባላል።49 ዓመቱ ነው።ስፔን ውስጥ ታዋቂ አክተር እና አክቲቪስት ነው።በፌስ ቡክ ገፁ የፈለገውን ሲጥል ሲያነሳ አንድ ቀን የማይገባ ስድብ በድንግል ማርያም ላይ እና በሥላሴ ሶስትነት እና አንድነት ላይ  ይፅፋል። ከእዚህ በፊት የስፔን ፍርድ ቤት ተከሶ ሁለት ጊዜ ችላ ብሎት ሳይቀርብ ቀርቷል።ይህንንም ተከትሎ  ታዋቂ አክተር እና አክቲቪስት በመሆኑ ከፍርድ በላይ ሊሆን አይገባም፣የኅብረተሰባችንን ስነ ልቦና የሚቃረን እና እምነታችንን የሚያጥላላ ፅሁፍ ፅፏል፣በአንደበቱም ተናግሯል በማለት የስፔን ክርስቲያኖች ጠበቃ ማኅበር በያዝነው የካቲት/2012 ዓም መልሶ ፍርድ ቤት ከሶታል።

ተከሳሹ ''የመናገር እና ሃሳብን የመግለጥ መብቴን ተጠቅሜ ነው የፃፍኩት፣ልከሰስ አይገባም'' ቢልም በማድሪድ ከተማ በሚገኘው 26ኛው የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክሱ እየታየ ነው።እአአቆጣጠር ሐምሌ 5፣2017ዓም በፌስ ቡክ ገፁ በፃፈው አስተያየት በወቅቱ ክስ ተመስርቶበት አንዳንዶች ታዋቂ አክተር እና አክትቪስትነቱን ተጠቅሞ ፍርድ ቤት ለመቅረብ ያንገራገረው ዊሊ  ታሌዶ፣ የስፔን ክርስቲያን ጠበቆች ማኅበር እንደገና በያዝነው ወር ክሱን ስላንቀሳቀሰው ጭንቀት ላይ ነው።

''ወንጀል የሚባለው የወንጀል ተግባር ነው እንጂ እንዴት ቃላትን ወንጀል ብላችሁ ትከሱኛላችሁ?'' በማለት ለፍርድቤቱ ከጠበቃው  አንዲካ ዙሉታ (Endika Zulueta) ለተነሳለት ጥያቄ መልስ የሰጠው አክተር፣ ፅሁፉን መፃፉን አምኖ ጉዳዩን ከስፔን የዲሞክራሲ አገር መሆን አለመሆን ጋር ለማያይዝ ሞክሯል።ፍርድ ቤቱ ግን ስሞታውን አልተቀበለውም።በሕግ ጉዳይ የእዚህ ዓይነት የክስ ጉዳዮች እና ሂደታቸው አስተማሪ ብቻ ሳይሆኑ ተመሳሳይ ሕጎች መውጣት እንዳለባቸው አስተማሪ እንደሚሆኑ ይታመናል።

በነገራችን ላይ ፣አውሮፓ የሃይማኖት ዶግማ ነቅፈው የሚፅፉ እንዲህ ይከሰሳሉ።ገዳማትን እየነቀፉ የምርጫ ቅስቀሳ የሚያደርጉት ያልተከሰሱባት የኢትዮጵያ ጉዳይስ? በቅርቡ በሰሜን ሸዋ የኦሮሞ ፌድራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) የደብረ ሊባኖስን ገዳም አስመልክቶ የተነገሩት አገር ከፋፋይ ዘረኛ ንግግሮች እንዴት ታለፉ?በእርግጥ የኢትዮጵይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ የሐሰት ዜና የሚነዙ ሚድያዎች ላይ ክስ መስርቷል።ይህ እንዳለ ሆኖ ግለሰቦችም በተለይ በእምነት ጉዳይ እያስታከኩ የሌላውን እምነት የሚያጥላሉ ለሕግ መቅረብ እንዳለባቸው የአውሮፓው ተሞክሮ ያመላክተናል።

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Monday, February 24, 2020

በታላቁ የዓድዋ በዓል አከባበር ላይ በሰውኛ ፕሮዳክሽንና ኢንተርቴይንመንት ውስጥ ሕይወት የዘሩ አርቲስቶች - ሚካኤል ሚልዮን እና ባለቤቱ መዓዛ ታከለ

ጉዳያችን ሚድያ፣ኮሚኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት 
Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant

  • በእዚህ ፅሁፍ ስር የሳምንቱን የዝክረ ዓድዋ በዓል መርሐግብር ያገኛሉ 

ፎቶ -አርቲስት ሚካኤል ሚልዮን እና መዓዛ ታከለ በጣይቱ ሆቴል ስለ ዝክረ ዓድዋ መግለጫ ሲሰጡ።
(ከአርት ቲቪ የተወሰደ )

''የአድዋ ድል የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው ዓለም ድል ነው።ድሉ የሰውን ልክ ያገኝ፣ ቅኝ ገዢዎች ከአላስፈላጊ ትዕቢት ዝቅ ብለው በሰው መጠን እንዲኖሩ፣ለጥቁሮች ደግሞ ራስን ዝቅ አድርጎ ከመመልከት ወጥተው በሰው እኩል መሆናቸውን ያሳዩበት ታላቅ ድል ነው።ይህ ማለት ሁሉንም የሰው ማዕረግ ያስተካከለ ድል ነው''
ይህንን የተናገረችው የአርቲስት ሚካኤል ሚልዮን ባለቤት አርቲስት መዓዛ ታከለ ነች።አርቲስት መዓዛ፣ አርቲስት ሚካኤል ሚልዮን እና ሌሎች አጋሮች ጋር ሆነው ''ሰውኛ ኢንተርቴይመንት'' የተባለ ድርጅት መስርተዋል።ሰውኛ ከሚሰራቸው የኪነጥበብ ፈጠራዎች በተጨማሪ የዓድዋ በዓል መልክ ባለው እና ዘመኑን በሚዘክር ደረጃ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ማክበር ነው።ላለፉት አራት ዓመታት በተከታታይ የዓድዋ በዓልን ድምቀት በመስጠት ብቻ ሳይሆን ለትውልዱ ከአዕምሮ በማይጠፋ ደረጃ ለማስቀረት አርቲስቶቹ ትልቅ አስተዋፅኦ በማድረግ ላይ ናቸው።

ከወንዶች ጉዳይ አዝናኝ ፊልም ጀምሮ በልዩ ልዩ የፊልም እና የመድረክ ስራዎቻቸው  የምናውቃቸው አርቲስት  ሚካኤል ሚልዮን እና መዓዛ ታከለ በሰውኛ  ፕሮዳክሽንና ኢንተርቴይመንት ለአራተኛ ጊዜ በሚከበረው የዓድዋ በዓል ላይ ዛሬ በወመዘክር የመክፈቻ መርሃግብሩን በርካታ ታዳሚ በተገኘበት ያስጀመሩ ሲሆን በቀጣይ ቀናት እስከ በዓሉ ማለትም የካቲት 23/2012 ዓም ድረስ የተለያዩ መርሃግብሮች አሏቸው።ከመርሃግብሩ ውስጥ የአድዋ በዓል ዕለት ከምኒልክ አደባባይ እስከ አድዋ ድልድይ ድረስ የሚኖረው የባዶ እግር ጉዞ እና የአድዋ ዘማቾች የሚያስታውስ የጎዳና ትዕይንት እና በእዚሁ እለት ቀትር ላይ በእንጦጦ የዳግማዊ ምንሊክ ቤተ መንግስት የንጉሱን የግብር ማብላት ስነስርዓት በጠበቀ መልኩ የሚዘጋጅ የምሳ ፕሮግራም የብዙዎችን ትኩረት የሳበ እና በአዲስ ትውልድ ውስጥም የማይጠፋ አሻራ የሚያኖር ነው።

ሰውኛ ፕሮዳክሽንና ኢንተርቴይንመንት በእዚህ ሳምንት እና እስከ በዓሉ ድረስ በአዲስ አበባ ያዘጋጃቸውን መርሐግብሮች ከእዚህ በታች ይመልከቱ።
የአርት ቲቪ ዝግጅቶቹን አስመልክቶ ያወጣው ማስታወቂያ 
ምንጭ - አርት ቲቪ ቪድዮ 




ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Friday, February 21, 2020

Eastern part of Ethiopia, Harar christians need protection.


ጉዳያችን ሚድያ፣ኮሚኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት 
Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant

Abune Mekarios, Member of Ethiopian Orthodox Tewahedo church Holy Synod and Archbishop of Ethiopian-Somali region and East Hararge, Amharic press release on January 29,2020 explained the situation in Eastern Ethiopia, Hararge. Here under is the main content of the press release.


Abune Mekarios


Abune Mekarios Press release 
In the name of the Father, and of the Son, and of the Holy Spirit, Amen. 
Between January 19 and January 22, 2020,  Christians were physically attacked, properties of four Christians were destroyed, 17 Christians were unfairly arrested; 246 Christians are displaced from their homeland and fled to Debre Adhano St Gabriel Church in Harar after being physically attacked, robbed and received  death threats. We want all human beings to stand up for justice. Harrar is not a city that belongs to only a small group of people, but it is for all Ethiopians. 


For those who were attacked by the police that were supposed to serve everyone without prejudice, those who were arrested even after being attacked by people who are now walking free - we want you to remain strong for your sufferings shall be counted as good deeds in the eyes of the Lord. Like our forefathers passed through times of hardships by keeping their faith, we are certain that nothing will stop you from doing the same. Christianity is always about victory over challenges, not a guarantee to a temporary satisfaction. The latest attack on Christians is no different from what the wicked emperors had done against our forefathers. You undeniably have more to gain by enduring challenges like our forefathers did. 


Even though organized mobsters with irresponsible security police officers attempted to incite you to engage in violence and chaos, you remained patient and strong. By so doing, you have proved how strong Christians are, even during trying times. And be happy for what you did (for your patience and restraint).


It is not possible to live a peaceful life while publicly discriminating Christians. Bearing this in mind, we want the government to evaluate its system once again and stop these irresponsible government officials, who are attempting to advance their hate filled agenda and are attempting to impose their belief (on Christians), from committing such acts. 

The police must serve all citizens despite their background and religion and impartially, without prejudice. However, the latest attacks targeted against our church reveals that the reality on the ground is different. Since it is challenging to live a peaceful life while persecuting others (Christians), we want the government to ensure such acts (of terror) won’t happen again and to take the necessary preventive measures before it gets worse.

We request the government bring to justice the groups and individuals that are trying to incite violence between communities that are living in harmony and peace. The fact is that the perpetrators of these heinous attacks are being released, while Christians who were victims of these atrocities are still being arrested. We call for the end of such (blatant) acts.

Even though some commendable actions have been taken by the regional government which announced it has arrested the mobsters who were behind the recent attacks, such acts (arresting the innocent and releasing the perpetrators) however is nothing different from arresting Christ while releasing Barabbas. 

We were happy that the United Nations Educational Scientific and Cultural Organization (UNESCO) passed a resolution to add Ethiopian Epiphany to the list of World Intangible Cultural Heritages. On the other hand, the attempt to take over a place of religious festivals of Orthodox followers and replace it with another one is very depressing. We call for the end of such actions.  

Like other religions that celebrate their sacred festivals peacefully without being attacked, we want to urge the government to do the same to all Christians without prejudice. As long as followers of Christians are being victims to violence and attacks... we will continue demanding for the respect of our rights. We also want to make it clear that we will hold a demonstration to denounce the recent attacks soon. 

We once again denounce the acts of the regional government’s actions of arresting innocent Christians, while releasing mobsters. And, we call upon the Christian youth to be organized and defend their faith from anymore attack and collect the necessary evidence if any additional acts are committed by mobsters against churches to bring those perpetrators to justice. 


God Bless Ethiopia, God Bless the World.








Wednesday, February 12, 2020

የኢትዮጵያ ወቅታዊ ፖለቲካ ድምፅ የሚሰማባቸው ሰፈሮች ወቅታዊ ገፅታ

ጉዳያችን/ Gudayachn
የካቲት 5፣2012 ዓም (ፈብሯሪ 13/2020 ዓም)
================
በእዚህ ፅሁፍ ውስጥ በሚከተሉት ርዕሶች ስር ፅሁፎች ያገኛሉ። እነርሱም - 

- የካቲት ወር በ1909 ዓም ፣
-  የካቲት ወር በ2012 ዓም፣
- ኢትዮጵያና ዓለም አቀፍ ኮርፖሬሽኖች፣
ብልፅግና  ፓርቲ የጀዋርን ቡድን የማቅጠን ሂደቱን  አጠናክሮ በግልጥም በስውርም ቀጥሏል፣
የብልፅግና ፓርቲ የገጠመው ትልቁ ተግዳሮት ፣
-  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ለኢትዮጵያ ፀጥታ ወሳኝ ጉዳይ ነው፣
እግዚአብሔርን የማይፈሩ፣ሰውን የማያፍሩት የህወሓት አመራሮች ጉዳይ፣
ቴዲ አፍሮ በመጪው ሳምንት በመስቀል አደባባይ
 ===============================
የካቲት ወር በ1909 ዓም

በ1909 ዓም የዳግማዊ ምንሊክ ሴት ልጅ ንግስት ዘውዲቱ በየካቲት 4 ቀን ዘውድ ደፉ።በእዚሁ ዓመት ራስ ተፈሪ የንግስትቱ ሞግዚትና አልጋ ወራሽ እንዲሆኑ ተሾሙ።የንግሥት ዘውዲቱ ወደ ንግስና መምጣት በልጅ ኢያሱ ዘመን የነበረው ሹክቻ እና ብጥብጥ የሚቆምበት በመሆኑ ህዝቡ መደሰቱ ይነገራል።ከንግስት ዘውዲቱ ንግስና በኃላም የኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ በአንፃሩ የተረጋጋ መልክ ቢያሳይም በመሬት ባላባቱ የጦር አበጋዞች እና ትምህርት ቀመስ በሆኑ ወጣት የሹማምንቱ ልጆች መሃል ልዩነት ፈጥሮ ነበር።በወቅቱ በዘመናዊ ትምህርት የተሻሉ የነበሩት እና የውጪውን ዓለም በተለይ ስለ አውሮፓ ስልጣኔ የተሻለ ግንዛቤ የነበራቸው የቀድሞው ራስ ተፈሪ (የኃላው ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ) ይደገፉ የነበሩት በወቅቱ በነበሩ ጥቂት ዘመናዊ ትምህርት ቀመስ ወጣቶች  ሲሆኑ እነኝህ ወጣቶች ንግስት ዘውዲቱ ከነገሱም በኃላ የኢትዮጵያ ጉዳይ ያስጨንቃቸው ነበር።

በወቅቱ የሚጨነቁት ወጣቶች ዋና ምክንያታቸው 20ኛው ክፍለዘመን ከመግባቱ ጋር በአውሮፓ የነበረውን እንቅስቃሴ ከሌላው ባላባት በተሻለ ማወቃቸው ነበር።በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ያለው የአውሮፓ ቅኝ ገዢዎች አመጣጥ በአድዋ እንደነበረው ዓይነት አይደለም።በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ዓለም ተቀይሯል።ወቅቱን የመጠነ ዘመናዊ ዲፕሎማሲ የሚጠይቅ እና ለእዚህም የመሬት ባለቤት በመሆን እና አገሬን እወዳለሁ ብሎ በመፎከር ብቻ የሚገኝ ሳይሆን ዘመናዊ ትምህርት እንደሚያስፈልግ ያውቁ ስለነበር የንግሥት ዘውዲቱ መምጣት ብቻ ኢትዮጵያን የ20ኛውን ክ/ዘመንን እንደማያሻግራት ገብቷቸዋል።ስለሆነም ከንግስት ዘውዲቱ ንግስና ቀን ጀምሮ የራስ ተፈሪ ቡድን ራስ ተፈሪ ኢትዮጵያን እንዲመሩ ለማድረግ ጥረታቸውን ቀጠሉ።

የካቲት ወር በ2012 ዓም

የየካቲት ወር የኢትዮጵያ ፖለቲካ ድምፅ የሚሰማበት ወር ነው።2012 ዓም ከገባ ስድስተኛ ወር ሆነ።ከየካቲት ወር  ቀደም ብሎ በነበሩት ወራት ከሶስት ያላነሱ የአደባባይ የህዝብ በዓላት እና የአፍሪካ ሕብረት መሪዎች ስብሰባ የመንግስት የፀጥታ አካልንም ሆነ ሕዝብን በተወጠረ ስሜት የያዘ ጉዳይ ነበር።በተለይ በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ወቅት የውስጥ ወይንም የውጭ ያልታወቀ ኃይል አንዳች አደጋ እንዳይፈጥር ማስጨነቁ አልቀረም።ይህንንም ተከትሎ ነው የዘንድሮው የመሪዎች ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት ጥበቃው በሄሊኮፍተር በታገዙ ኮማንዶዎች ጭምር መሆኑን የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በዜና ላይ ሳይቀር ሁሉ ሲያሳይ ነበር።ትልቁ ቁምነገር ግን ስብሰባው በሰላም ተፈፅሟል።

በዘንድሮው የካቲት ላይ ሆነን ከመቶ ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ጉዳይ የተጨነቁት ወጣት ምሑራን ተመሳሳይ ስሜት ዛሬም ይታያል።ኢትዮጵያ በወሳኝ የ21ኛው ክ/ዘመን በብቃት የመሻገር እና ያለመሻገር ድልድይ ላይ ትገኛለች።ጊዜው ወሳኝ ለመሆኑ ከእኔ አባባል በላይ በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በፓርላማ ቀርበው እንደተናገሩት ''ጊዜው የሞትሽረት ወቅት'' መሆኑን ተናግረዋል።ይህ ማለት ከሩቅ ተመልካች ብቻ ሳይሆን እራሱ መንግስትም ያመነው ነው ማለት ነው።

ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፍ ኮርፖሬሽኖች 

ኢትዮጵያ ባሳለፍነው ክ/ዘመን በርዕዮተ ዓለም ስትንገላታ ነው የኖረችው።የኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ በአገር ውስጥ ፖለቲካ ብቻ የተያዘ አይደለም።የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ሂደት በጉጉት ከሚጠብቁት ውስጥ ዓለም ዓቀፍ ቱጃር ኩባንያዎች ናቸው።እነኝህ ኩባንያዎች ከቻይና ጋር በአፍሪካ ቅርምት የድርሻቸውን የገበያ ድርሻ ለመውሰድ በከፍተኛ ጉጉት ላይ ናቸው።የግሉን የኢኮኖሚ ዘርፍ ማሳደግ ላይ ከቻይና እስከ ኒውዮርክ ያሉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች የሚስማሙበት ነው።ነገር ግን መጠኑ በምን ያህል ይሁን?መንግስት እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች ውስጥ በምን ያህል ደረጃ ራሱን ከምጣኔ ሃብቱ ማርቅ አለበት? የግል ዘርፉንስ የውጭ ኩባንያዎች ናቸው ወይንስ የአገር ውስጥ ኩባንያዎች እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ቅድምይ ሊሰጣቸው የሚገባው? በሚሉት ዙርያ ጥያቄዎች መነሳታቸው  የሂደቱን ወሳኝ አፈፃፀም  ይወስነዋል።

የውጪ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ መጉረፍ በተለይ በቁልፉ የምጣኔ ሀብት ዘርፍ ለምሳሌ እንደ ባንክ፣ቴሌ እና የኃይል ማመንጫ ዘርፍ  መምጣት በራሱ መጥፎ ነው የሚል አመለካከት የመኖሩን ያህል መምጣታቸው ተገቢ ነው የሚሉ ምሁራን አሉ። ይህንን ክርክር ለጊዜው እናቆየው እና ጉዳዩ ግን በኢትዮጵያ መጪ ፖለቲካ ላይ የውጪው በተለይ የምዕራባውያን  የድጋፍ ዋና መሰረት ከጅኦ-ፖለቲካው በተጨማሪ ይሄው  የኢትዮጵያን የገበያ እና ጥሬ ዕቃ የማግኘት ጉጉት  የአገሪቱን መጪ ፖለቲካንም እንደሚወዘወዝ መገንዘብ ይገባል።

ብልፅግና  ፓርቲ የጀዋር ቡድንን የማቅጠን ሂደቱን  አጠናክሮ በግልጥም በስውርም ቀጥሏል።

ጀዋር በአንድ ቀጭን መንገድ መሄድ ጀምሮ መንገዱ መሃል ላይ ሲደርስ የኃላ በር በኃይል ሲዘጋ ዘወር ብሎ የተደናገጠ እና ያለው አማራጭ የፊቱ ምን እንደሚሆን ሳያውቅ የሚሄድ ሰው ይመስላል።ብዙ ስልት አውቃለሁ የሚል ብቻ ሳይሆን በአንድ ወቅት የዕድምያቸውን አብዛኛውን ጊዜ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ሲንገላቱ የኖሩት አቶ አንዳርጋቸውን ስልት አለዎት ወይ? እያለ መመፃደቅ ደረጃ የደረሰው ጀዋር አሁን የአሜሪካ ዜግነቱን ለመተው አመልክቶ አዲስ አበባ ላይ ያንን ስንቀው የነበረውን ኢትዮጵያዊነት ስጡኝ እያለ እየተማፀነ ነው።

የምርጫ ቦርድም የካቲት 2/2012 ዓም ለኢሚግሬሽን እና ዜግነት ጉዳይ በፃፈው ደብዳቤ ጀዋር ዜግነት በተመለከተ ማብራሪያ እንዲሰጠው መጠየቁ ለማወቅ ተችሏል።በሌላ በኩል የጀዋር ቡድን እና የብልፅግና ቡድን በኦሮምያ ውስጥ ከፍተኛ ፍጥጫ ላይ መሆናቸው ግልጥ ሆኗል።በእዚህም ምክንያት ብልፅግና የአመራር ሚናውን ቢይዝም በወረዳ እና በዞን ደረጃ እንዲሁም በሌላው ቢሮክራሲ ውስጥ የጀዋር ቡድን የሚደግፉ ፅንፈኞች  ላይ ርምጃ መውሰድ ተጀምሯል።ርምጃው በያዝነው ወር በበለጠ እንደሚጠናከር ይጠበቃል። በእዚህ ሂደት ብልፅግና ቀድሞ የሰራቸው ስራዎች የጀዋርን አከርካሪ ብቻ ሳይሆን ጥርሱን ያነቃነቀ ሥራ ሰርቷል።ይሄውም በታች ደረጃ ያሉትን የእርሱ አድናቂዎች በተለያየ የስራ እና የብድር ዕድል እየሰጡ ከጀዋር የመለየቱ ሂደት በብዙ ቦታ ተሳክቷል።ለምሳሌ በአምቦ ውጥረት ለመፍጠር የሚሞክሩ ወጣቶች ላይ መንግስት  በቀጥታ ማሰር መጀመሩ እና በትናንትናው እለትም በጅማ ጀዋር ሊያደርግ ያሰበው ስብሰባ ህዝቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይን ፎቶ ይዞ በመውጣቱ  ከፍተኛ መሸማቀቅ በጀዋር ላይ ደርሷል። ይህ ብቻ አይደለም።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ከጅማ በተጨማሪ የቦረና እና ባሌ የኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያንን ልብም በድማቅ ንግግራቸው እና በልማት ፕሮጀክቶች መግዛት ችሏል።በእዚህም ጀዋር ከፍተኛ ክስራት ደርሶባታል። በእዚህ አይነት ጊዜ ላይ ጀዋር የለመዳት አንድ አይነት አካሄድ አለ።እርሱም እየተነነበት ያለውን የደጋፊ ኃይል ለማንቃት አንድ የማንቂያ እና የመሞከርያ ጉዳይ አንስቶ አንድ አይነት ግጭት ለመፍጠር እንደሚያስብ  እና አለሁ ለማለት እንደሚፈልግ የታወቀ ነው።ባለፈው ተከበብኩ የሚለውን ጉዳይ ለግጭት የተጠቀመበት ለእንደዚህ ዓይነት የመሞከር ሥራ እንደሆነ ማወቅ ይቻላል።የጀዋርን መኖር እንደ መጠባበቂያ ኃይል የሚመለከቱት ሶስተኛ ረድፈኞች በሌላ በኩል የጀዋርን ደጋፊ መሳሳት ተከትለው ራሳቸውን ወደ መቅበር እያዘነበሉ እንደሆነ ይታያል።

የብልፅግና ፓርቲ የገጠመው ትልቁ ተግዳሮት

ኢህአዴግ በመፍረሱ (መፍረስ የሚለው በራሱ ፈርሷል ወይንስ? የሚል ጥያቄ እንዳለ ሆኖ) የማይደሰት የለም።አንዱ እና ዋናው ጥላቻ አደረጃጀቱ በጎሳ ላይ መሆኑ ሲሆን ብልፅግና ቢያንስ እንደ ሱማሌ፣አፋር እና ቤንሻንጉል ያሉ ክልሎችን ፖሊሲ አውጪው አካል ውስጥ መግባታቸው እንጂ አሁንም ብልፅግና አደረጃጀቱ ከኢህአዴግ የጎሳ አደረጃጀት ለመውጣት የሚውተረተር  ምንልባት ከምርጫው በኃላ የሚሳካለት ሊሆን ይችላል።

ይህ በእንዲህ እያለ ግን የብልፅግና ፓርቲ መሰረታዊ እና ትልቁ ተግዳሮት ከፍተኛ የአድርባይነት እና የአቅም ችግር ያለባቸውን የኢህአዴግ ካድሬ እና አመራር ይዞ ለመሄድ የሚያደርገው ደካማ አካሄድ ዋጋ እንዳያስከፍለው ያስፈራል።ብልፅግና በአዲስ አካሄድ ነው የምሄደው ካለ አቅም ያላቸው እና ከነበረው የአድርባይነት ባህል የለሉበት አዲስ የሰው ኃይል ማካተት እና ወደ አመራር ማምጣት እንጂ የነበረውን አድር ባይ ካድሬ አስራ ሰባት ቀን አይደለም ከዛ በላይ ቢሰለጥንም የተሻለ መንገድ ከማምጣት ይልቅ ወደ ኃላ እንዳይጎተት ያስፈራል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ለኢትዮጵያ ፀጥታ ወሳኝ ጉዳይ ነው።

በኢትዮጵያ ላይ የሚመጡ ለውጦች በሙሉ ማዕከል የሚያደርጉት የፖለቲካውን አውድ ብቻ ሳይሆን የማኅበራዊ በተለይ የሃይማንቱን አውድም ጭምር ነው።በተለይ ከኢትዮጵያ ሕዝብ አብዛኛው የምከተላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ዋናዋ የፖለቲካ ስሜት ማብረጃ ስትሆን ኖራለች።ይህ የደርግ መንግስትም ሆነ የህወሓት መራሹ መንግስት ሲመጣ  በስጋት የሚመለከታት  እና በሚፈልገው መልክ ለመቆጣጠር በቤተክርስቲያኒቱ ላይ ትልቅ ጉዳት አድርሰዋል።በአሁኑ ጊዜም የኦዴፓ እና የፅንፍ አካል ተጠግተው ከእዚህ በፊት በቤተክርስቲያኒቱ ላይ የማዳከም ሥራ ሲሰሩ የነበሩ እንደ እነ ቀሲስ በላይ ያሉትን በገንዘብ በማባበል ቤተክርስቲያንቱን ለመክፈል ከሁለት አካላት  ድጋፍ እየተደረገለት መሆኑ ይሰማል።እነርሱም የመጀመርያው ከፅንፈኛው የጀዋር ቡድን ሲሆን ሁለተኛው ከፅንፈኛ የተሃድሶ እንቅስቃሴ ነው።ሁለቱም አካላት የምታከኩት ሃይምኖትን ይምሰል እንጂ ግቡ ፖለቲካዊ እና ኢትዮጵያን ለመከፋፈል የሚደረግ ትልቁ አጀንዳ አካል ነው።

ይህ በእንዲህ እያለ በመንግስት በኩል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚፈፀመውን ጉዳይ በቀላሉ እየተመለከተው ነው።የደህንነት መስርያቤቱም ሆነ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ለመክፈል የሚደረገው ሙከራ ትልቁ እና ቀዳሚው የኢትዮጵያ የፀጥታ ጉዳይ እንደሆነ ያሰቡበት አይመስልም። አጀንዳው አገርን የመክፈል እንጂ ቤተክርስቲያኗን ብቻ አይደለም።ከጀርባ የሚንቀሳቀሰው የበጀት እና ሃይማኖቱ የማይመለከታቸው የሰው ኃይል ሁሉ የሚያሳየው ጉዳዩ ፖለቲካዊ ብቻ ሳይሆን አገራዊም መሆኑን ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ድንገተኛ ስብሰባ ለመጪው ሰኞ ጠርቷል።የስብሰባው ዋና አጀንዳ በወቅታዊው በቤተክርስቲያኗ ላይ እየደረሰ ባለው ጉዳት ላይ እና በተለይ በኦሮምያ ቤተ ክህነት በሚል በቀሲስ በላይ የሚመራው ቡድን ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ ተወያይቶ ቀኖናዊ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል።

እግዚአብሔርን የማይፈሩ፣ሰውን የማያፍሩት የህወሓት አመራሮች ጉዳይ  

በቅዱስ መፅሐፍ የሚገኝ አንድን ሰው ክርስቶስ እራሱ ሲጠቅሰው ''ሰውን የማያፍር፣እግዚአብሔርን የማይፈራ'' አንድ ሰው ነበር በማለት ነው።አንድ ሰው እግዚአብሔርን ባያፍር የሰፈሩን ሰዎች ያፍራል።ሰውን ባያፍር እግዚአብሔርን ይፈራል።ሲሆን ሁለቱም ቢሆን ጥሩ ነበር።የህወሓት አመራር ግን ሁለቱንም አጥተውታል። በከዘራ እና በሰው እየተደገፉ የሚሄዱት ፣አቶ ኃይለማርያም  በአንድ ወቅት ሲመራቸው ''እንደ ጆፌ አሞራ ቢሮዬ ቁጭ ብዬ ይዞረኛል'' ያሏቸው አቦይ ስብሐት ሲሆን አክሱም ፅዮን ተቀምጠው ካልሆነ ወደ አድዋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ጥግ ይዘው ዳዊት በመድገሚያቸው  እና የህወሃትን አመራር በመምከርያቸው ጊዜ በአገር አማን መቀሌ ላይ ዛሬም ክላሽ ወጣቱን እያስያዙ ሲፎክሩ ማየት ያስገርማል። ኢትዮጵያን ከባንክ እስከ ግድብ ፕሮጀክት፣ከስኩአር ፕሮጀክት እስከ የኮንትሮባንድ መዳኒት ማስመታት ድረስ ከዝያም በላይ ከ11 ቢልዮን ዶላር በላይ ግጠው ወስደውባት እና ራቁቷን ቆማ ዛሬም ሰውን ሳያፍሩ፣እግዚአብሔርን ሳይፈሩ የካቲት 11 በዓል ለመጨፈር የህወሓት አመራር እየተዘጋጀ ነው።መቸም ረስተነው ይሆናል እንጂ ህወሓት በዓሏን ዱባይ ላይ ሁሉ ድል አድርጋ በድሃው የኢትዮጵያ ሕዝብ ደግሳ እንደነበር መቸም አይረሳም መቀሌ ላይ የውሃ ፕሮጀክቱ ገንዘብ ተበልቶ ዱባይ ላይ ውስኪ ሲወራረድ ነበር። በ21ኛው ክ/ዘመን ሕዝቡን ለስራ ከማስነሳት ይልቅ ወንድምህን ግደል ብሎ ያውም አንድ እግራቸው መቃብር በገባ አዛውንት ሲቀሰቀስ መመልከት ምንኛ ያሳዝናል።ህወሓት የካቲት 11 ለማክበር ምን ዓይነት ሞራል አላት? ቢያንስ ራሱ  ተራው የህወሓት ታጋዮች የተነሱበት የመነሻ መፈክርን የአሁኖቹ የህወሓት አመራሮች አንግበውታል? የኤፈርትን ገንዘብ በማን እጅ ነው? የትግራይ ከተሞች ንፁህ ውሃ ማግኘት ተስኗቸው የኤፈርት ብር ኝን በማን እጅ ነው? የካቲት 11 ሲከበር በየትኛው የሞራል ልዕልና ነው?

ቴዲ አፍሮ በመጪው ሳምንት በመስቀል አደባባይ  

ኪነ ጥበብ ኢትዮጵያዊነትን በተለይ ላለፉት ሰላሳ ዓመታት ትውልዱን ለማስተማር ምን ያህል ሰርቷል? ቢባል ይህንን ያህል የጎላ ሥራ አልታየም ማለቱ ይቀላል። የኢትዮጵያን ነገር ትቶ ያልተወው ቴዎድሮስ ካሳሁን ግን በትውልዱ ውስጥ ኢትዮጵያን ለማጉላት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ቴዲ በያዝነው ሳምንት መጨረሻ በመስቀል አደባባይ ለሕዝብ ስራዎቹን ያቀርባል።በእዚህ ላይ ብዙ ባልልም፣ቴዲ የፍቅር ጉዞ ብሎ ገና በጧቱ ትውልዱን ለመምከር ሥራ ሲጀምር እነ ጀዋር በከፈቱበት የማኅበራዊ ሚድያ ዘመቻ ተሰናክሎ ነበር።ዛሬ ጀዋር የኢትዮጵያዊነት ዜግነት ስጡኝ እያለ በሚለምንበት ሰዓት ቴዲ ኢትዮጵያ የሚለውን ዜማ በመስቀል አደባባይ ጮክ ብሎ በመጪው ሳምንት መጨረሻ ያዜማል።ግሩም ነው። ኢትዮጵያ!

=====================//////================


የቴዲ አፍሮ ኢትዮጵያ! ቪድዮ 




ጉዳያችን / Gudayachn



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Sunday, February 9, 2020

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ሊቀመንበር አቶ የሸዋስ አሰፋ በኦስሎ ኖርዌይ ተገኝተው ከኢዜማ ድጋፍ ማኅበር አባላት ጋር ተወያዩ።

 አቶ የሸዋስ አሰፋ የኢዜማ ሊቀመንበር 
Please Note - Under Amharic version (here below) you can see the video of Ethiopian Prominent Opposition partyEthiopian Citizens for Social Justice Party latest brief for the Diplomatic Community in Addis Ababa.

ጉዳያችን ምጥን ዜና 
የካቲት 1/2012 ዓም (ፈብሯሪ 9/2020 ዓም)

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ሊቀመንበር አቶ የሸዋስ አሰፋ ዛሬ ዕሁድ የካቲት 1/2012 ዓም በኦስሎ፣ኖርዌይ ከኢዜማ ድጋፍ ማኅበር ጋር ስብሰባ ማድረጋቸውን ጉዳያችን በቦታው ተገኝታ ለመረዳት ችላለች።በስብሰባው ላይ አቶ የሸዋስ ኢዜማ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ እያደረገ ያለው የምርጫ ዝግጅት፣የአባላት ተሳትፎ እና በወቅታዊ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ማብራርያ ከሰጡ በኃላ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎች ተነስተው  ለተነሱት ጥያቄዎች አጥጋቢ ምላሾች ሰጥተዋል። 

በተለይ ኢዜማ በአንዳንድ ከተሞች ያደረጋቸው የስብሰባ ጥሪዎች በአንዳንድ ህገ ወጦች መሰረዙን አስመልክቶ ሲናገሩ። የማኅበራዊው ሚድያ ባብዛኛው የሚያወራው ኢዜማ  ኢትዮጵያ ውስጥ ካደረጋቸው በርካታ የተሳኩ ስብሰባዎች  ይልቅ በሕገወጦች ምክንያት ያልተደረጉት አራት የሚደርሱ ስብሰባዎች ላይ የሚያተኩር መሆኑን ጠቅሰው። እነኝህ ቦታዎችም ቢሆን ለመረበሽ የሞከሩት ቁጥር ከኢዜማ ደጋፊ ቁጥር ጋር ሲተያይ እጅግ ያነሰ ቢሆንም  ኃላፊነት በተሰማው መንገድ ሰዎች እንዳይጋጩ የፀጥታ ማስከበር ሰራውን መንግስት መስራት አለበት ከሚል ፅኑ ዓላማ አንፃር  የሰረዝናቸው ስብሰባዎች ነበሩ በማለት አብራርተዋል።

በእዚሁ ስብሰባ ላይ አቶ የሸዋስ የኢዜማ የፖሊሲ ጥናቶች ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ በከፍተኛ ባለሙያዎች የተዘጋጀ ሲሆን ባለሙያዎቹ የግድ የኢዜማ አባል መሆን አይጠበቅባቸውም ነበር ብለዋል።በሌላ በኩል በመላው ኢትዮጵያ በተመሰረቱት በ400 የምርጫ  ወረዳ ጣቢያዎች ላይ በእያንዳንዱ ጣቢያ ቢያንስ ከሶስትመቶ ሰው አባል እና አስራአምስት የስራ አስፈፃሚ እንዳለው ገልጠው።ከእዚህ በተጨማሪ በእነኝሁ ወረዳዎች ደረጃ የፖሊሲ ጥናት ቡድን እንዳለ አስታውቀዋል።በመጨረሻ ላይ ኢዜማ በኢትዮጵያ ከገዢው ፓርቲ የቀድሞው ኢህአዴግ የአሁኑ ብልፅግና ፓርቲ ጋር በሚወዳደርበት ጣብያ ብዛት በተገዳዳሪ ደረጃ  ከመቀሌ እስከ ሞያሌ፣ከወለጋ እስከ ከሚሴ ከ400 በላይ የምርጫ ጣቢያ መስርቶ ለመጪው ምርጫ በበቂ ደረጃ የተዘጋጀ መሆኑ በአቶ የሸዋስ ተብራርቷል።

Ethiopian Citizens for Social Justice Party latest brief for the Diplomatic Community. (video)









ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Wednesday, February 5, 2020

Observers in Ethiopia are in a great fear that the current Ethiopian Government officials and police force from Oromia region are full of anti-Semitic and anti-Ethiopian orthodox Tewahido church.

 Prime Minister Abiy must act on it. 

የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ መንግስት በፀረ-ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና ፀረ ሴማውያን ባለስልጣናት እና የፖሊስ ኃይል ተሞልቷል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፍጥነት ርምጃ መውሰድ አለባቸው። (ጉዳያችን ልዩ  የእንግሊዝኛ ዘገባ)

Gudayachn Special 

ጉዳያችን / Gudayachn 
February 5/2020 


This evening, just before two hours, Ethiopian Orthodox Tewahido Church Patriarch His Holiness Abune Mathias  condemned last night’s brutal act of the Government on Ethiopian Orthodox Tewahido Church followers. Following the police brutal action, two people were killed and many others were seriously wounded and taken to hospitals in Addis Ababa.

It was yesterday around midnight that Police in Addis Ababa in a place called ''22 SEFER'' surrounded  innocent Ethiopian Orthodox Tewahido Church  followers, opened tear gas and fired live bullets. During this black midnight, when the police acted on innocent citizens,  children, young, old fathers and mothers were sleeping around the newly built church's temporary house.

Many people are criticizing Abiy's government’s top officials and the members of police forces  (particularly those who came from Oromiya region) that they are anti-Semitic and anti-Ethiopian Orthodox Tewahido Church Christians. Since PM Abiy’s administration came to power two years ago, Ethiopians are increasingly criticizing his government not only for its inability to protect the Ethiopian Orthodox Tewahido Churches' followers and buildings but for the unwillingness of the police force to intervene when the church followers were attacked by extremists in eastern and southern part of the country. 

In 2019 only, over 15 Ethiopian Orthodox Tewahido churches were burnt down and over one hundred followers of the church were killed, just for their Christian faith and for being Semitic. Observers in Ethiopia are in a great fear that Abiy’s administration is full of officials and  members of the police force who are alarmingly anti-Semitic and anti-Ethiopian Orthodox Tewahido church.

 ''Abiy himself may not have such symptoms, but his officials and the police force need to be checked properly. This must be done by Abiy himself. He should check who is around him.'' one observer from Addis Ababa reflected his feeling on the current situation of Ethiopia to Gudayachn.

 ''If the situation continues like this the security of the nation may develop to a very dangerous and unexpected way.'' another Bank Officer said to Gudayachn via telephone from the  Ethiopian capital, Addis Ababa. 

According to Gudayachn’s observation, PM Abiy's administration’s ability to keep peace and security in the country is going from bad to worse. Most problems are due to unnecessary delay to act against illegal moves of extremists. In fact, the problem is not restricted to  Abiy's administration, but some opposition parties based in Oromiya region are also officially reflecting their anti-Semitic sentiments. It was just three weeks ago, that Oromo Federal Congress (OFECO) election campaign led by a controversial activist and the former managing director of the Oromia Media Network, Jawar Mohamed, delivered an anti-Ethiopian Orthodox Tewahido Church and anti-Semitic speech, which was widely condemned by Ethiopians worldwide and at home. Following this particular anti-Ethiopian Orthodox Tewahido church and anti-Semitic speech, an influential Ethiopian Orthodox Tewahido church association called PETROSAWYAN ''ጴጥሮሳውያን'' in Amharic accused the campaign and the media which transmitted the provoking election campaign. The association has written an open letter to Prime Minister Abiy Ahmed and other key government offices.

There is one word you can hear in Ethiopia, when I am writing this news and analysis. That is Prime minister Abiy must act on anti-Ethiopian Orthodox Tewahido church and anti-Semitic forces in all part of the country. Otherwise the Horn of Africa nation may jump into unexpected political turmoil.



His Hollyness Abune Matias and the Mayor of Addis Ababa, Takele Uma Press release on brutal action of police in Addis Ababa, February 5,2020


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Saturday, February 1, 2020

መጪው የኢትዮጵያ ምርጫ የተለያዩ ''ሴናርዮዎች'' በሚል ርዕስ በኖርዌይ የኢትዮጵያውያን መድረክ አዘጋጅነት በኦስሎ የተደረገው ስብሰባ ይዘት


     ዶ/ር ተክሉ አባተ  


       ዶ/ር ሙሉዓለም አዳም

ጉዳያችን/Gudayachn
ጥር 23/2012 ዓም (ፌብርዋሪ 1/2020 ዓም)

- ''በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ባብዛኛው የሚታየው የጥቅም አክራሪነት እንጂ የብሔር አክራሪነት ማለት አይቻልም'' በካይሮ፣ግብፅ የአሜሪካ ዩንቨርስቲ አሶሼት ፕሮፌሰር  ዶ/ር ተክሉ አባተ 

=======================
ዛሬ የካቲት 1/2012 ዓም በኦስሎ፣ኖርዌይ የሚገኘው የኢትዮጵያን የጋራ መድረክ በኦስሎ ''አንቲ ራሲስት'' የስብሰባ አዳራሽ መጪው የኢትዮጵያ ምርጫ ሴናርዮዎች በሚል ርዕስ ባዘጋጀው የውይይት መርሃግብር ላይ በስካይፕ ከካይሮ፣ግብፅ የአሜሪካ ዩንቨርስቲ አሶሸት ፕሮፌሰር ተክሉ አባተ እና ከኖርዌይ የኢዜማ ድጋፍ ሰጪ ማኅበር ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉዓለም አዳም ሃሳባቸውን አቅርበዋል።

በመጀመርያ መጪውን ምርጫ አስመልክተው ዘርዘር ባለ መልክ ሃሳባቸውን ያቀረቡት ዶ/ር ተክሉ አባተ ምርጫ ቦርድ ያወጣውን የጊዜ ሰሌዳ መሰረት  ሰኔ 4 ፓርቲዎች ለምርጫ ቅስቀሳ ስማቸው ቅደም ተከተል ዕጣ ያወጣሉ፣ነሐሴ 10 የምርጫ ማድረጊያ ቀን ይሆናል፣ነሐሴ 10 እና 11 ውጤት ይለጠፋል፣ነሐሴ 11-15 በክልል ደረጃ ውጤቱ ይፋ ይደረጋል፣ነሐሴ 11-20 አጠቃላይ የምርጫው ውጤት ይገለጣል ካሉ በኃላ አከራካሪ ጉዳዮች ያሏቸውን እንደሚከተለው ዘርዝረዋል።

አከራካሪ ጉዳዮች 

በአሁኑ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሁኔታ በማንሳት በኢትዮጵያ ምርጫ መደረግ አለበት ወይንስ የለበትም? ብለው የሚጠይቁ መኖራቸውን የጠቀሱት ዶ/ር ተክሉ በመቀጠል እርሳቸው የሚያነሷቸውን ተጨባጭ ማስረጃዎች እንደሚከተለው  ዘርዝረዋል። እነርሱም -

1) ሰላማዊ እና የተሳካ ምርጫ ለማድረግ የሚያስቸግሩ ነባራዊ ሆነታዎች አሉ።ዛሬም ሕፃናት በሰሜን ጎንደር ታፍነው ተወስደው  አደጋ ደርሶባቸዋል፣ምዕራብ ወለጋ ብንወስድ ጦርነት አለ፣አንዳንድ ቦታዎች ላይ ሰው ወጥቶ ለመመለስ ስጋት ላይ ነው።

2)የጥቅም አክራሪነት ሰፍኗል።እኔ የብሔር አክራሪነት አልለውም።የጥቅም አክራሪነት ነው የተስፋፋው።ሰዎች የጥቅም ፍላጎታቸውን በብሄር አክራሪነት ለመሸፈን እየሞከሩ ነው። በአማራም በኦሮሞም ብንመለከት ያለው የጥቅም አክራሪነት ነው። ይህ የጥቅም አክራሪነት ደግሞ ለሽምግልናም አስቸጋሪ ነው።ስለሆነም ለምርጫው አንዱ እንቅፋት ሊሆን ይችላል።

3) የፖለቲካ ፓርቲዎች አሁን ድረስ እንደፈለጉ ተዟዙረው ስብሰባ ማዘጋጀት አልቻሉም።ለምሳሌ በቅርቡ ኢዜማ በጎንደር እና በባሕርዳር ያደረጋቸው ስብሰባዎች ላይ የደረሱትን መመልከት ይቻላል። እነኝህን ስብሰባዎች የሚያውኩ ሰዎች ይህንን  የሚያደርጉ ሰዎች ለአማራ ሕዝብ አስበው  ነው ብዬ ማሰብ አልችልም የጥቅም ጉዳይ ነው።

4) በርግጥ የተወሰኑ በብሄር ስሜት የተነሱ አሉ።ሁሉም በጥቅም ብቻ ነው ማለት አይቻልም።እነኝህ ደግሞ ተጠቂ ነን የሚል ስሜት ያላቸው ግን የራሳቸውን ብሔር በሌላው ላይ ለመጫን የሚፈልጉ ናቸው።በተለይ በትምህርት ደረጃ ዝቅ ያለውን የህብረተሰብ ክፍል ብሔርህ ተነካ በሚል ይቀሰቅሱታል።

5)የፓርቲዎች መብዛት ሌላው ችግር ነው።በአሁኑ ጊዜ ከ110 በላይ ፓርቲዎች አሉ።አብዛኛው ብሔር ተኮር ነው። ጥቂት በኢትዮጵያ ላይ የሚሰሩ አሉ። ይህ ማለት የምርጫ ቅስቀሳውን ብቻ ስናስብ በራሱ ጉድዩን አስፈሪ (''ናይት ሜር'') ያደርገዋል። ካሉ በኃላ ዶ/ር ተክሉ ምርጫው እነኝህን ተግዳሮቶች አልፎ ምርጫው ጊዜ ላይ ቢደርስ የሚከተሉትን ''ሰነርዮዎች'' ማስቀመጥ እንደሚቻል ዘርዝረዋል።

ምርጫው ከላይ የተገለፁትን ተግዳሮቶች አልፎ መደረግ ደረጃ ቢደርስ

1) ታዛቢዎችን የማዋከብ እና የማስፈራራት ሥራ በብሄር ድርጅት ደጋፊዎች አይኖርም ማለት አይቻልም።በቅርቡ በሲዳማ የክልል ውሳኔ ድምፅ አሰጣጥ ላይ በታዛቢዎች ላይ የተደረገውን እንደምሳሌ ማስታወስ ይቻላል።

2) የክልል ፓርቲዎች ህዝቡ የክልሉን ፓርቲ ብቻ እንዲመርጥ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሕዝቡን ሊያስገድዱት ይችላሉ።

3) የምርጫው ቆጠራ በራሱ ደረጃውን በጠበቀ መልክ ላይደረግ የመቻል ዕድል ሊገጥመው ይችላል።

4) ከሁሉ የከፋው ደግሞ ምርጫው ውጤት ሲነገር ውጤቱን አንቀበልም የሚሉ ክፍሎች ሊነሱ ይችላሉ።

5) በምርጫው ውጤት ብሔር ተኮር ድርጅቶች ሊያሸንፉ ይችላሉ። ይህ በራሱ የሚፈጥረው የፖለቲካ ውጥረት ይኖራል።ምክንያቱም የክልል መንግሥታት  ከአሁኑ በባሰ የመጠንከር ዕድል ሊገጥማቸው ይችላል።ይህ ማለት የማዕከላዊ መንግስትን ስልጣን በባሰ መልኩ ይሸረሽራል። ምናልባት በአዲስ አበባ ደረጃ ካየን በቀዳሚነት ኢዜማ እና ባልደራስ በከፍተኛ ደረጃ  ፉክክር የሚያሳዩበት ቦታ ሊሆን ይቻላል።በሶስተኛ ደረጃ ብልፅግና ፓርቲ ሊከተል ይችላል።
እዚህ ላይ በክልል ደረጃ የብሔር ድርጅቶች አብላጫውን ያዙ ማለት አራት ኪሎ ሲመጡ የሚኖረውን የእርስ በርስ መገፋፋት አስቡት።ምክንያቱም አሁን የሚመጡት የህዝብ ድምፅ ይዘናል በሚል ስለሆነ ከፍተኛ መፈታተግ ይኖራል ይህ በራሱ ለአገር የሚፈጥረው ጉዳት አለ ያሉት ዶ/ር ተክሉ ምርጫው በርግጥ ቢደረግም ሆነ ባይደረግ የራሱ የሆነ አደጋ ''ሪስክ'' ሊኖረው ይችላል ካሉ በኃላ የምርጫው ሂደትም ሆነ እርሱን ተከትሎ የሚመጣው አሳሳቢ ጉዳይ መነሻ ያሏቸውን ጠቅሰዋል።

ከምርጫው ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ችግሮች መነሻ ምክንያቶች 

1) ፓርቲዎች ለሚናገሩት ንግግር ኃላፊነት መውሰድ አለመቻል እና ለተሳሳተ አነጋገራቸውም የሚጠይቃቸው አካል አለመኖሩ፣

2) የመንግስት ሕግ የማስከበር ፍላጎት እና አቅም (አንዳንዶች አቅም አለው የሚሉ አሉ ግን አቅሙን እስካሁን አላሳየንም) በበቂ ሁኔታ ብቻ ሳይሆን ፈፅሞ አለማሳየቱ፣

3)ፈታኝ የኑሮ ውድነት፣ሥራ አጥ ወጣት መብዛቱ፣ይህ በራሱ ጀብደኞች እንዲፈጠሩ ምክንያት ሆኗል።በቀላል ብር የሚደለሉ እና ለብጥብጥ  የሚገዙ ወጣቶች መብዛት አስከትሏል።

4) በአሁኑ ጊዜ ያለው ወጣት በዘመነ ህወሓት የኖረው ወጣት በራሱ በከፍተኛ ደረጃ የሞራል ድቀት ያደገ ወጣት መሆኑ፣

5) የህዝቡ የፖለቲካ ንቃት ደረጃ አለማደግ።አብዛኛው ሕዝብ ኢትዮጵያዊነቱን የሚፈልግ ቢሆንም 5% የማይሆኑ ጥቂቶች የሚፈጥሩት የነውጥ ሥራ ብዙሃኑ በቀላሉ እንዲጠቃ አድርጎታል ካሉ በኃላ ዶ/ር ተክሉ ምን አደረግ አለበት? የሚል ጥይቄ አንስተው የሚከተለውን የመፍትሄ ነጥቦች ዘርዝረዋል።

ምን ማድረግ ይገባል?

1) የኢትዮጵያ ሕዝብ የተቀነባበረ የስነ ልቦና ዘመቻ ተደርጎበታል።ስለሆነም አሁንም በቂ የፖለቲካ ንቃት ያስፈልገዋል።ስለሆነም ፖለቲካ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ለሕዝብ  አሁንም መንገር ይገባል።ፖለቲካ ማለት ከዳቦ ከውሃ ጋር የሚገናኝ እና ቀጥታ ተፅኖ የሚፈጥር ጉዳይ መሆኑን ለሕዝብ በሚገባ መንገር ያስፈልጋል።ይህንንም በሚድያ፣በብሎግ ሳይቀር ለሕዝብ መንገር ያስፈልጋል።በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ይህንን አጠናክረው መቀጠል አለባቸው።

2) የውይይት መድረኮችን ማብዛት ያስፈልጋል።ለምሳሌ ዛሬ የተሰበሰብንበት የኢትዮጵያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ የመሰሉ ድርጅቶች በሌሎች አገሮችም ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።

3) ኢትዮጵያውያን መድረኮችን ማብዛትና በዓለም አቀፍ ደረጃ ማጠናከር፣

4)መከባበር አስፈላጊ ነው።የብሔር ድርጅቶች የኢትዮጵያዊ ድርጅቶችን፣የኢትዮጵያዊ ድርጅቶች የብሔር ድርጅቶችን መነቃቀፍ ሳይሆን የተሻለ ፖሊሲ ላይ  መሆናቸውን የኢትዮጵያውያን ድርጅቶች ለብሄር ድርጅቶች ማሳየት እና በብልጫ ልቆ መገኘት እንጂ በመናቅ እና በመዘላለፍ መሆን የለበትም፣

5) በውጭ የሚኖረው ማኅበረሰብ በምርጫው ላይ የራሱ ሚና እንዳለ ማመን ያስፈልጋል።ለምሳሌ በውጭ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ የሚደግፈውን የፖለቲካ ፓርቲ የማስተዋወቅ ድርሻውን መወጣት አለበት።በማለት በካይሮ፣ግብፅ የአሜሪካ ዩንቨርስቲ አሶሸት ፕሮፌሰር ዶ/ር ተክሉ አባተ ገለጣቸውን አጠናቀዋል።

በመቀጠል ዶ/ር ሙሉ ዓለም አዳም በኖርዌይ የኢዜማ ድጋፍ ሰጪ ማኅበር ሥራ አስፈፃሚ አባል በዶክተር ተክሉ የቀረበውን ማብራርያ አወድሰው በኢትዮጵያ የግለሰቦች ሚናንም በደንብ ማሰብ እንዳለብን አሳስበዋል።በእዚህም መሰረት የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በአሁኑ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ያላቸውን ተፅኖ እንዳለ ሆኖ ምርጫውን በተመለከተ በእዚህ ሁኔታ እስከ ምርጫው  ድረስ በተለመደው አካሄድ ይሄዳል? ወይንስ እርሱ እንደሚለው ወደለመድነው የሥርዓት ማስከበር ሥራ ይገባል የሚለው ሁኔታዎችን ሊቀይራቸው እንደሚችል  ገልጠዋል። ከእዚህ በመቀጠል ዶ/ር ሙሉዓለም ኢትዮጵያዊነትን በተመለከተ ስብስቦች መጠናከር እንዳለባቸው ገልጠው፣ ባለፈው ሳምንት በኦስሎ የተደረገው የኢትዮጵያዊነት ስብሰባ አንዱ ማሳያ እንደሆነ እና ኢትዮጵያውያን የበለጠ የእዚህ አይነት ስብስቦች ላይ በመገኘት አገራዊ ግዴታቸውን መወጣት አስፈላጊ መሆኑ ላይ አፅንኦት ሰጥተዋል።

በስብሰባው መደምደምያ ላይ ከተሳታፊዎች የተነሳው ጥያቄ ኢትዮጵያ በእዚህ በብሄር ፖለቲካ በምትታመስበት ጊዜ የሃይማኖት አባቶች እና  መምህራን የት ናቸው? ለምን ሕዝብ የብሔር ፖለቲካ ውስጥ ሲገባ አይመክሩም? ካህናትም እስከ ማውገዝ የሚደርስ ርምጃ መውሰድ እንዳለባቸው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል። ይህንንም አስመልክቶ ዶ/ር ተክሉ ሲመልሱ ችግሩ መኖሩን ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት በአገርቤት ሕዝብ በብሄር መከፋፈል እንደሌለበት የሚመክሩ ለምሳሌ የ24 ሰዓት የቴሌቭዥን ስርጭት የጀመረው የማኅበረቅዱሳን ቴሌቭዥን በሰፊው የማስተማር ሥራ ላይ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

በእዚህ የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ ስብሰባ ላይ የተገኙት ኢትዮጵያውያን ቁጥር በቂ ባለመሆኑ የጋራ መድረኩ በዕለቱ የተያዘውን የጋራ መድረኩን ሪፖርት እና የአዳዲስ አስተባባሪዎች ምርጫ ለማድረግ አለመቻሉ ተገልጦ።ኢትዮጵያውያን ለወደፊቱም በጋራ ሻይ እና ቡና ሲጠጡ ለብቻቸው በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከመከራከር የእዚህ አይነቱን መድረክ ቢጠቀሙበት ጠቃሚ እንደሆነ ሃሳብ ተሰጥቶ የዕለቱ ስብሰባ ተፈፅሟል።



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።