ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, March 31, 2016

አዲስ አበባ የሚገኘው የኖርዌይ ኤምባሲ ድረ-ገፅ ላይ የወጣ:- New Norwegian Initiative to Promote Freedom of Expression and Independent Media



Foto source:- Royal Norwegian Embassy in Addis Ababa, Ethiopia
http://www.norway.org.et/News_and_events/press_releases/New-Norwegian-
initiative-to-promote-freedom-of-expression-and-independent-media-/#.Vv19ncd1pg0 
The below article is found on the web site ofRoyal Norwegian Embassy in Addis Ababa, Ethiopia.
(ከእዚህ በላይ የሚታየው ፎቶም ሆነ ከስር ያለው ፅሁፍ የተወሰደው ከኖርዌይ ኤምባሲ አዲስ አበባ  ድረ-ገፅ ላይ ነው)
Last updated: 18.01.2016 // The Ministry of Foreign Affairs is launching a new strategy today for efforts to promote freedom of expression. ‘Freedom of expression and independent media are under growing pressure. Norway is therefore strengthening its international work in this field,’ said Minister of Foreign Affairs Børge Brende. 
The Foreign Minister is presenting the strategy at an event in Oslo today for representatives of civil society, academia and others who have provided input.
Freedom of expression is the foundation on which all other democratic freedoms rest. Freedom of expression must be safeguarded and promoted tirelessly, every day and in every single country. We want everyone to be able to express their opinions openly, and be able to receive and share information freely,’ said Mr Brende.
 As part of Norway’s foreign and development policy, the Government will step up its efforts to support independent media, provide protection for people who express their opinions publicly, and improve public access to information. These are three cornerstones of the effort to ensure real participation and influence on decision-making processes.
‘Access to information is a new focus area for Norway’s international efforts. Access to information is vital if people are to be able to make informed decisions about their own lives, and to make it possible for them to understand and exercise their rights,’ said the Foreign Minister.
The Ministry of Foreign Affairs will promote openness, a free flow of information and access to the internet, and will initiate further steps to develop international norms on the right of access to information. Active efforts are needed to ensure that freedom of expression is safeguarded as new forms of communication and new technology platforms are developed.
A wide range of media channels is needed to ensure that people have access to a variety of sources of information. They can shine a critical spotlight on the exercise of power and authority and promote openness and accountability. The Ministry will therefore support training for journalists, other media staff and heads of media organisations


Tuesday, March 29, 2016

በኢትዮጵያ የወደፊት አቅጣጫ ላይ የመከረው ስብሰባ ተጠናቀቀ The future of Ethiopia, discussions on the roadmap for post TPLF Ethiopia


 eNGLISH VERSION IS ATTACHED BELOW 

ኢሳት (መጋቢት 19 ፥ 2008)

በቪዥን ኢትዮጵያና ኢሳት በዋሽንግተን ዲሲ ጆርጅ ታውን መሪየት ሆቴል ከማርች 26-27 2016 የተዘጋጀውና በኢትዮጵያ የወደፊት ሁኔታ በለውጥ፥ ዲሞክራሲና፣ የብሄራዊ አንድነት ላይ የሚመክር ስብሰባ በስኬት መጠናቀቁን የስብሰባው አዘጋጆች ገለጹ። በስብሰባው የኢትዮጵያ የወደፊት አቅጣጫ የሚመለከቱ ጉዳዮች የተዳሰሱበት ሲሆን በርካታ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ምሁራን፣ የሲቢክ ድርጅቶች እና የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጥናታዊ ጽሁፎቻቸውን ያቀረቡበትና የተሳተፉበት እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
ፕሮፌሰር ጌታቸው በጋሻው የመግቢያ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ በኮንፈረንሱ አንኳር አንኳር አገራዊ ጉዳዮች እንደሚነሱ ሃሳባቸውን አንስተዋል። በኢሳትና በቪዥን ኢትዮጵያ ትብብር ተዘጋጅቶ በነበረው በዚሁ ኮንፈረንስ ከተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት የተወከሉ ምሁራን በኢትዮጵያ ወቅታዊና የወደፊት አቅጣጫ ዙሪያም ሰፊ ውይይትን አካሄደዋል።
ከተለያዩ የሲቪክና የሰብዓዊ መብቶች እንዲሁም የእምነት ተቋማት የተወከሉ ተጋባዥ እንግዶች በኢትዮጵያ ዴሞክራሲና የተረጋጋ ሰላምን ማምጣት በሚቻልበት ዙሪያ የመከሩ ሲሆን፣ ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመፍጠርም ብሄራዊ እርቅና ብሄራዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
የአፍሪካ ሃገራትን ተሞክሮ በዋቢነት በማንሳት ለታዳሚ ገለጻን ያደረጉት ፕሮፌሰር አቻምየለህ ደበላ፣ በአህጉሪቱ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ መንግስት አይነት ምርጫ አድርጎ መቶ በመቶ አሸንፌያለሁ ብሎ ያወጀ መንግስት እንደሌለ አውስተዋል።
በጋና በናይጀሪያና በሌሎች ሃገራት በትምህርት ቆይታቸው የታዘቧቸውን ፖለቲካዊ ጉዳዮች ለኮንፈርነሱ ያካፈሉት ፕሮፌሰር አቻምየለህ፣ በሌሎች የአህጉሪቱ ሃገራት ፖለቲካዊ ለውጦች መታየት ቢጀምሩም በኢትዮጵያ ያለውን አካሄድ ግን ገና ብዙ የሚቀረው እንደሆነም አስረድተዋል።
በኒው ዮርክ ሲቲ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር የሆኑት ፕሮፌሰር ጆን ሀርብሰን በበኩላቸው, በኢትዮጵያ ከ1960 የአብዮት ፍንዳታ ጀምሮ ሃገሪቱን ዴሞክራሲያዊ ሊያደርጉ የሚችሉ አራት እድሎች ሳይሳኩ መቅረታቸውን ገልጸዋል።
በግንቦት 1977 የተካሄደው ብሄራዊ ምርጫ ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ ትግሎችን ያወሱት ፕሮፌሰር ሀርብሰን፣ ከኢትዮጵያ ጋር በሽብርተኛ ዙሪያ ትብብር ያላት አሜሪካ በሃገሪቱ ዴሞክራሲ እንዲያብብ ትብብር ማድረግ እንዳለባት ባቀረቡት ገለጻ አመልክተዋል።
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ግንባት የስራ አስፈጻሚ አባል የሆኑት ሌንጮ ባቲ፣ በመንግስት የሚፈጸሙ የኢሰብዓዊ ድርጊቶች በዝርዝር ካስረዱ በኋላ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት በመሆን በስልጣን ላይ ያለውን ኢህአዴግ መስወገድ እንዳለበት ተናግረዋል።
በሃገሪቱ እየተፈጸሙ ስላሉ ኢሰብዓዊ ድርጊቶች ሰፊ ሪፖርትን ያቀረቡት አቶ ነዓምን የኢህአዴግ መንግስት ፌዴራላዊ፣ ዴሞራሲያዊ ወይም ሪፐብሊክ ተብሎ ሊፈረጅ እንደማይችል አክለው ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የወደፊት ጉዳይ የሚመክረው ስብሰባ እሁድ እለትም በዚሁ በማሪየት ሆቴል ቀጥሎ የዋለ ሲሆን፣ በትግሉና በግጭት አፈታት እና ለዲሞክራሲ፣ አንድነት ዙሪያ ሴቶች የሚጫወቱት ሚና በሚል መድረክ ውይይት ተካሄዶበታል።
በሃዋርድ ዩንቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ ተማሪ የሆነችው ወ/ሪት ኤልሳቤጥ ላቀው ወደአሜርካ የፈለሱ አፍሪካውያን ሴቶችን ጉዳይ ከኢትዮጵያውያን ትግል አንጻር ትንተና ሰጥታለች። በመቀጠልም በኖርዌይ ሃገር የሚኖሩት ወ/ሮ ሰዋሰስ ጆሃንሰን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲንና ነጻነትን በኢትዮጵያ ለማምጣት በአንድነት መታገል እንዳለባቸውና ካወሱ በኋላ፣ አዲሲቷን ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ በመጀመሪያ እርቅ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አስምረውበታል። በመቀጠል የተናገሩት በፍራንክፈርት የሚኖሩት የሰብዓዊ መብት አቀንቃኝ ወ/ሮ አሳየሽ ታምሩ ሲሆኑ፣ በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በአገር ውስጥ ለሚሰቃዩ ኢትዮጵያውያን ሴቶች አጋርነታቸውን ማሳየት እንዳለባቸው ተናግረዋል። ወ/ሮ አሳየሽ፣ “ለልጆቻችን ማውረስ ያለብን ነጻነትን ነው” ሲሉ ተደምጠዋል። በዚህ ፓነል መጨረሻ ላይ የተናገሩት በዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ሴቶች የሰብዓዊ መብት አቀንቃኝ ወ/ሮ ወሰን ደበላ ሲሆኑ፣ 51% የሚሆነውን የኢትዮጵያን የሚሸፍኑት ሴቶች ቢሆኑም፣ በአገራዊ ጉዳይ ተሳትፏቸው ግን እጅግ ዝቅተኛ ነው ብለዋል። ወ/ሮ ወሰን የኢትዮጵያ ሴቶች በአገራዊ ጉዳዮች ላይ እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል። ፓነሊስቶቹ የኢትዮጵያ ሴቶች ድምጽ እንዲሰማ ቪዥን ኢትዮጵያና መድረኩን በማመቻቸታቸው አመስግነዋቸዋል።
እሁድ ከሰዓት በኋላ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ለመዳሰስ ስብሰባ ተካሄዷል። ስብሰባውን የመሩት አቶ ግዛው ለገሰ ናቸው። በመጀመሪያ ጥናታዊ ጽሁፋቸውን ያቀረቡት አቶ ኤርሚያስ ለገሰ ሲሆኑ፣ በፓርቲዎችና በማህበረሰብ (ኮሚኒቲ) አባላት መካከል መተባበር አለመኖር ለለውጥ ከፍተኛ እንቅፋት እንደሆነ ተናግረዋል። ለአጭር ይሁንም ለረጅም ጊዜ የጋራ ግብ በእነዚህ የማህበረሰብ አባላትና ፓርቲዎች መካከል በመተማመን ላይ የተመሰረተ ትብብር እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል። ዶ/ር መስፍን አብዲ በመሬት ጉዳይ ዙሪያ ትንተና ሰጥተዋል። በህወሃት አገዛዝ መሬት የገበሬዎች ሆኖ እንደማያውቅና ከመሬት ይዞታ ጋር የተያያዙ አያሌ ያልተመለሱ ጥያቄዎች እንዳሉ ተናግረዋል።
አሁን ያለችዋን ኢትዮጵያ በማስመልከትም ያለፈው ታሪክ ሆኖ ያለፈ በመሆኑ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ሁሉም በእኩል አይን የሚታይባት አገር መሆን ይኖርባታል ብለዋል። ከዚህ ጋር በማያያዝም ኦሮምኛ የኢትዮጵያ የስራ ቋንቋ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል። የኦሮሞና የአማራ ልሂቃንም በሁለቱ ህዝቦች መካከል መተማመን እንዲኖር እንዲሰሩ እንዲሰሩ ጠይቀዋል።
በመሬይ ስቴት ዩንቨርስቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ሰይድ ሃሰን በመሬት ነጠቃና ሙስና ላይ ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል። ፕ/ር ሰይድ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሙስና በአለም ላይ ከታዩት ሙስናዎች ለየት ያለ ነው ብለዋል። መሬት የስልጣን ምንጭ በመሆኑ የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት መሬት ነጠቃውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተንብየዋል። ሁሉም የኢትዮጵያ ተደራሽ አካላት ይህ ዘርፈ-ብዙ ውስብስብ ችግር ለመፍታት ተቀራርበው መነጋገር እንዳለባቸው ተናግረዋል።
በኬተሪንግ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ምሁር የሆኑት ፕሮፌሰር እዝቅኤል ገቢሳ፣ የዲሞክራሲ፣ የእድገት፣ የሰብዓዊ መብት፣ የሰላም ማስፈን እሴቶችን ከውስጣችን መመልከት እንዳለብን የሚተነትን ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ ወደ ዲሞክራሲ የምትሻገርበትን ብዙ እድሎችን ያጣችበትን አጋጣሚ የተነተኑት ፕሮፌሰር እዝቅኤል፣ ኢትዮጵያውያን ህወሃት ኢህአዴግን ከማስወገድ ባለፈ የወደፊት እቅድ ሊኖራቸው እንደሚገባ አስረድተዋል። ፕሮፌሰር እዝቅኤል በገዳ ስርዓትና በኦሮሞ እሴቶች ላይ ትንተና ሰጥተዋል።
“ከዚህ በኋላ ወዴት? ያልተመለሱ ጥያቄዎች!” የሚለው የመጨረሻው ስብሰባ የተመራው በኮሎራዶ ሜትሮፖሊታን ስቴት ዩንቨርስቲ መምህር በሆኑት በፕሮፌሰር ሚንጋ ነጋሽ ነው። ለዲሞክራሲ፣ ለለውጥና ለአንድነት ምን መደረገ እንዳለበት የመከረው ይኸው ስብሰባ፣ ኢትዮጵያ በአስቸኳይ ለውጥ የሚያስፈልጋት አገር እንደሆነች ተናግረዋል። የኢትዮጵያውያንን ህይወት የዳሰሰ በምስል ያሳዩት ፕሮፌሰር ሚንጋ፣ ኢትዮጵያ የሰላም፣ የዲሞራሲና የብልጽግና አቅጣጫ (Roadmap) ያስፈልጋታል ብለዋል። በመሆኑንም ከኤርትራ ጋር ያንዣበባት የጦርነት አደጋ፣ በኦሮሚያ፣ ኮንሶ፣ አማራ፣ ሶማሌ እና ጋምቤላ አካባቢዎች የሚታየው ግጭት ኢትዮጵያን ከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደከተታት ተናግረዋል። ከህወሃት/ ኢህአዴግ መወገድ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚተገበር አቅጣጫ መቀመጥም እንዳለበት ፕሮፌሰር ሚንጋ ተናግረዋል።
ፕሮፌሰር ተሾመ ከበደ በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለው ብጥብጥ የመንግስት የስልጣን ምንጭ እንደሆነ ለተሰብሳቢው ተናግረዋል። ፕሮፌሰር ተሾመ ኢትዮጵያ የዲሞክራሲ እሴቶችን የምታከብር፣ በሉዓላዊነቷ የማትደራደር አገር እንድትሆን ማድረግ ሃላፊነት እንዳለብን ለታዳሚው ተናግረዋል። ሕወሃት/ኢህአዴግን በተመለከተ ሙሉ በሙሉ እንዲደመሰስ ማድረግ ሳይሆን ዲሞራሲያዊ እሴቶችን እንዲቀበል ማስገደድ እንዳለብን ተናግረዋል። “አገራችን ችግር ላይ ናት፣ የእኛን እርዳታ ትሻለች” ሲሉ ለተሰብሳቢው ተናግረዋል።
ከዚህ ቀጥሎ የተናግሩት  የህግ ባለሙያና የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባት አባል የሆኑት ዶ/ር በያን አሶባ ሲሆኑ፣ ያለፉትና የአሁኑ አምባገነን መንግስታት በህዝቦቻችን ላይ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውን ተናግረዋል። ሌሎች ኢትዮጵያውያን በኦሮምያ እየተከሰተ ያለውን ህዝባዊ እንቅስቃሴ በጥርጣሬ መመከታቸውን ትተው እንዲደግፉት ጥሪ አቅርበዋል።
በካሊፎርኒያ ግዛት ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማሪያም የአምባገነን መንግስታት ባህሪ ነገሮችን መደበቅ ነው ብለዋል። በመሆኑም ህወሃት ኢህአዴግ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳይታወቅበት ኢሳትን በብዙ ሚሊዮን ብር በመክፈል በተደጋጋሚ በሞገድ ለማገድ መሞከሩን ለተሰብሳቢው ተናግረዋል። ሆኖም ህወሃቶች ለሰሩት ጥፋት ሁሉ ተጠያቂ የሚሆኑበት ጊዜ ሩቅ እንዳልሆነ ለተሰብሳቢው ገልጸዋል። ለዲሞክራሲና ለእኩልነት የሚደረገው ትግልም ህወሃት/ወያኔ ኖረም አልኖርም መቀጠሉ አይቀሬ መሆኑን አስረድተዋል። አዲስ አቅጣጫ የሚያመላክት ህገ-መንገስትም መዘጋጀት እንዳለበት ተሰብሳቢውን መክረዋል።
በመጨረሻ የቀረቡት በዳይተን ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር መሳይ ከበደ ናቸው። የተሻለው አቅጣጫ አሁን ያለውን በዘውግ የተከለለውን አስተዳደር መከተል መሆኑን አስመረው፣ ኢህአዴግ ቢወገድም የዘውግ ጥያቄ በቀላሉ የሚጠፋ አለመሆኑን ገምተዋል።
ከቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፎች በሁላ በርካታ ጥያቄዎች ለተሰብሳቢዎች የቀረቡ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ከመድረክ መልስ ተሰጥቶባቸዋል። አንዳንድ ያልተመለሱ ጥያቄዎች ወደ ፊት በሚካሄዱ ስብሰባዎች እንደሚነሱ ለማወቅ ተችሏል።

Scholars, politicians, civil society representatives share views on the future of Ethiopia, discuss roadmap for post TPLF Ethiopia

ESAT News (March 28, 2016)
Ethiopian scholars, politicians and representatives of civil societies and women gathered in Washington, DC for a two day conference on the future of Ethiopia: transition, democracy and national unity organized by vision Ethiopia.
Representing Patriotic Ginbot 7 for Unity and Democracy, Neamin Zeleke, a member of the leadership said the TPLF Federal Democratic Republic is neither federal, nor democratic, nor republic.
He said the recent uprising by the people in the Oromia region was evidence that the Federal system by the TPLF was not designed to benefit the people. The popular uprising in different parts of Ethiopia show federalism, as designed by the TPLF, did not give rights to the people, Neamin said.
He spoke at length on the human rights abuses in Ethiopia perpetrated by the TPLF. Neamin said the minority government is not to be reformed but to be removed. He said he does not believe the tyrannical government would be removed through peaceful political struggle. Armed struggle, among other forms of struggle, is crucial to remove tyranny from Ethiopia, he stressed.
Lencho Bati, member of the executive committee, Oromo Democratic Front spoke on the need to create a national and common discourse that bring together all political organizations. Lencho said the regime cannot call itself developmental state as a state to be called developmental should be legitimate and accepted by the poeople, which the TPLF is not. The bureaucracy is not free from political pressure and appointment of administrative positions is not based on merit but political assignment. He said Ethiopians should politically, militarily and using all available means work to remove the tyrannical regime in Ethiopia.
Prof. John Harbeson, Professor Emeritus of political science at City University of New York said Ethiopia had missed at least four opportunities to establish a democratic state: 1974 revolution, the fall of the Dergue in 1991, the constitution assembly of 1994 and the historic election of 2005. Prof. Harbeson said in all the four case, Ethiopia’s opportunity to make a transition to democracy was squashed.
He also said the US, while fighting terrorism, should also help promote democracy.
Professor Minga Negash, Professor of Accounting, Metropolitan State University of Denver, Colorado and the University of the Witwatersrand, Johannesburg, South Africa said Ethiopia needs a transformation, which is not only changing the government, but also a roadmap after post-EPRDF Ethiopia.  The conflict with Eritrea, popular uprising in Konso, Oromia, Amhara, Somali, Gambella need to be dealt carefully, Minga said.
Another panelist, Professor Teshome Abebe Former Provost and Academic Vice President, Eastern Illinois University and Professor of Economics, Illinois said that chaos has become the source of power for the ruling party in Ethiopia. Prof. Teshome underscored that there should be a consensus that Ethiopia should have “unflinching respect for democratic values and its sovereignty should not be questioned.” Instead of completely annihilating TPLF, Prof. Teshome said, TPLF has to be reformed to unequivocally embrace democratic principles. Teshome said, “Our country is in distress and needs our attention.”
Dr. Beyan Asoba, Lawyer and Human Rights Advocate and Member of the Oromo Democratic Front, said the current and previous regimes have committed gross human rights violations in the country. He said Ethiopians should see the protest in the Oromia region as a struggle for democracy and good governance, not as a threat to the nation.
Alemayehu Gebremariam, Professor of Political Science, California State University, San Bernardino, Attorney at Law, and weekly blogger on Huffington Post spoke about the dictatorial regime in Ethiopia. He said one of the characteristics of dictators is their secrecy. Prof. Alemayehu elabotated on why the Ethiopian government is spending millions of dollars to jam ESAT.  Prof. Alemayehu said sooner or later time will tell when TPLF will be held responsible for atrocious actions it committed on the people of Ethiopia. He stressed that whether the TPLF regime exists or not, the quest for democracy and respect for human rights will continue. According to Prof. Alemayehu, the roadmap for new Ethiopia is a new constitution.
Messay Kebede, Professor of Philosophy, University of Dayton, Ohio elaborated on ethnicity and power. Prof. Mesay said the way forward is to recognize the current ethnic based regional administrations. He said ethnic politics will not fade away even if TPLF is removed from power.
Ermias Legesse, former minister d’état of government communications, author, and human rights advocate said there is lack of cooperation among Ethiopian political parties and civic groups. Ermias called on the different political and civic organizations to cooperate for common, long and short-term goals. He said the cooperation among these groups should be built on a solid foundation of trust.
Dr. Mesfin Abdi, former lecturer at Addis Ababa University and researcher, presented a paper on land tenure and language issues in Ethiopia. He said, currently, the land does not belong to the farmers; and there are several unresolved questions.
Dr. Mesfin elaborated on the need to make Oromiffa as one of the working languages in Ethiopia. He said Amhara and Oromo elites should devise a mechanism to build a solid pillar of trust for the benefit of all nations in the country.
Seid Hassan, Professor of Economics, Murray State University, Kentucky, presented a paper on land grabs and state capture in Ethiopia.  According to Prof. Seid, the worst corruption in the world is practiced in Ethiopia. The scholar said the TPLF/EPRDF government would continue the land grab, for the land is the only source of power and survival for the TPLF regime. The current problem in Ethiopia is multifaceted and all stakeholders should come together to devise mechanisms to mitigate it, he said.
Professor Ezekiel Gebissa:  Professor of History, Kettering University, Michigan, and President Elect, Oromo Studies Association presented a paper on the theme: “Time to Look Inward: Harnessing Indigenous Asset and Resources for Democracy, Development, Human Rights and Peace Building.” Prof. Ezekiel discussed on the chances Ethiopia missed for its transition to democracy. He said we should have a plan for the country beyond overthrowing the TPLF regime. Prof. Ezekiel gave an elaborated speech on Gada System and Oromo values in Oromo society.
Ms. Elsabet Lakew a Political Science Student at Howard University and Organizer at Montgomery County Civil Rights Coalition, spoke about diaspora women in relation to their root. Elisabet related the struggle for democracy and human rights in Ethiopia to the “Black Lives Matter” in the United States.
Ms. Sewasew S.Johannessen, Manager, The Ark of The New Covenant Healing Ministry, Norway, requested all Ethiopians to come together to bring democracy and freedom in Ethiopia. Sewasew urged all Ethiopians work for reconciliation if they wish to see democratic Ethiopia.
Mrs. Asayesh Tamiru, human rights advocate, Frankfurt, who said humanity knows no boundaries urged diaspora Ethiopians show solidarity with women in Ethiopia. She said, “We should feel the pain of our people in Oromia, Somalia, Gambella- allover Ethiopia.” She underscored, “If we must inherit anything to our children, it is freedom!”
Ms. Wessen Debela, Human Rights Advocate and member of Center for Rights of Ethiopian Women (CREW), Washington, DC said though Ethiopian women intellectuals participate less in the affairs of the country. Ms. Wessen urged all women to participate in every aspect of socio-political life if they need to see a vibrant, prosperous Ethiopia.
Ms. Sewasew S.Johannessen, Manager, The Ark of The New Covenant Healing Ministry, Norway, requested all Ethiopians come together to bring democracy and freedom in Ethiopia. Sewasew urged all Ethiopians work for reconciliation if they wish to see democratic Ethiopia.
Mrs Asayesh Tamiru, Human Rights advocate, Frankfurt, said humanity knows no boundaries. Ms Asayesh said the diaspora Ethiopians must show solidarity for women in Ethiopia. She said, “we should feel the pain our people are facing in Oromia, Somalia, Gambella- allover Ethiopia.” She reiterated, “If we must inherit anything to our children, it is freedom!”
Ms. Wessen Debela: Human Rights Advocate and member of Center for Rights of Ethiopian Women (CREW), Washington, DC said though Ethiopian women intellectuals are more than 51% of the population, they participated less in the affairs of the country. Ms Wessen urged all women to participate in every aspect of socio-political life if they need to see a vibrant, prosperous Ethiopia.

Friday, March 25, 2016

''አያያዙን አይቶ ጭብጦውን ቀማው'' የሃይማኖት ሰው ባርነትን እና ግፍን አይሸከምም ! ሃይማኖት ፈሪ አያደርግም ደፋር እንጂ! (የጉዳያችን ማስታወሻ)

በ1928 ዓም ሃይማኖት ሰንቀው ዕውነት ይዘው ለአገራቸው የዘመቱ ኢትዮጵያውያን 
Photo :-East Africa campaign 1940, Bisheshwar Prasad

እውነት የፍልስፍና ጉዳይ አይደለም።እውነት የህሊና ዳኝነት እና የሃይማኖት ፍሬ ነው።ሸፍጥ በአንፃሩ የአድር ባይነት እና እራስን ዝቅ አድርጎ የማየት የተንሸዋረረ አስተሳሰብ ውጤት ነው።ኢትዮጵያውያን ቀደም ባሉ ዘመናት የምንታወቅበት አንዱ መለያ ግፍ እና ባርነት ለመሸከም  ምንም አይነት የሽንገላ ቃላት የማይደልሉን መሆናችን ነበር።ለእዚህ ደግሞ አንዱ እና ዋነኛው ምክንያት የሕይወት መመርያ ፍልስፍናችን በሃይማኖት የታሸ እና ፍትህን ያስቀደመ በመሆኑ ነው።

ዓለም በሕግ ስርዓት ሳይዳኝ ኢትዮጵያውያን ''በላ ልበልሃ'' ብለው ሹሙ ፊት ቀርበው በአደባባይ ፍርዱን ሕዝብ እየተመለከተ ይሟገታሉ።ፍትህም ከሹሙ ይቀበላሉ።በፍትህ ያልተስማማ ይሞግታል።ፍርዱ አድሏዊ ነው ካለ ጠብመንዣውን (ጠበንጃውን) አልያም ጦሩን ሰብቆ ጋሻውን ወድሮ ይሸፍታል።ሸፍቶ ሳለ ሹም ቢቀየር ፍትህ ቢሻሻል ከአገሬው ታርቆ፣ ይቅር ተባብሎ ወደ ሰላማዊው ኑሮ ይመለሳል። ከእዚህ ውጭ ባርነት እና ግፍን አይሸከምም።ኢትዮጵያዊው የሃይማኖት ሰው እንዲህ ነው።ኢትዮጵያም ነፃነቷን ጠብቃ የኖረቸው ለእውነት የቆሙ የሃይማኖት ሰዎች መኖርያ በመሆኗ ነው።

የሃይማኖት ሰው ፍርሃት አያውቅም።እውነትን ይዤ የማልችለው የሚያቅተኝ ምድራዊ ነገር አለ ብሎ ፈፅሞ አያስብም።ፍርሃት፣ ሐሰትን እና ሸፍጥን በውስጣቸው ይዘው ለሚሄዱ እንጂ ለሃይማኖት ሰው ፈፅሞ ፍርሃት አያሰጋውም።የእውነት መግነጢሳዊ ኃይል በእራሱ እንደ እሳተ ገሞራ ፈንቅሎ ድል የማድረግ ኃይል ለሃይማኖት ሰው የተሰጠ ፀጋ ነው። 

ኢትዮጵያ ዛሬ የመንደራቸውን ሰው 'ቅዱስ' ከመንደራቸው ያልተወለደውን 'እርኩስ' የሚያደርጉ በዘረኝነት፣በሌብነት፣በሙስና፣ሰውን በመግደል እና በማሰር የሥልጣናቸውን መንበር ለመጠበቅ በሚውተረተረው ህወሓት እጅ ወድቃ እየማቀቀች ነው። የሃይማኖት ሰው ምኑንም ያህል ትሕትና ቢያሳይ፣ ፍቅር ቢመግብ እና ከአድልዎ ፀድቶ የሸፍጥ እና የባርነት ቀንበራቸውን  ለማሳለፍ ቢሞክር አሁን በስልጣን ላያ ያለው ቡድን እና  አቀንቃኞች ሁሉንም በጥላቻ አይን እየነደፉ ወደ ባሰ የመረረ ጥላቻ በጎ ህሊናን እንደሚቀይሩ የሚያውቀው የደረሰበት ብቻ ነው።ያልደረሰበት አይረዳውም።

ሃይማኖት ያስታግሳል።ሃይማኖት በጎ ህሊናን ስለሚያጎናፅፍ ነገሮችን በቀና ለማየት ጊዜ ይሰጣል።ሃይማኖት የሚሰራውን ግፍ እየተመለከቱ ግፍ ሰሪ ወደ ህሊናው እንዲመለስ መካሪ ዘካሪ ያደርጋል።ግፍ የሚሰራው ግን ምክርን የማይሰማ 'ደረቴ ይቅላ ሆዴ ይሙላ' ብሎ በጥጋቡ ከቀጠለ ሃይማኖት በሁለት ሰይፍ ስላ በታላቅ ኃይል  ለፍትህ  ሥራ ታስነሳለች።

ሃይማኖት ካለምንም ለውጥ አገርን ወደ ባሰ ማጥ እየከተተ እና ህዝብን እያስረገጠ ፈሪ አያደርግም።ከሁሉም ይልቅ ኢትዮጵያዊነት ደግሞ ፈፅሞ በእዚህ አይነቱ መንገድ አይገለጥም። በግፍ እና በዘረኝነት ስትገፋ ኖረህ ከመሞት የበለጠ ሌላ ሞት የለም።የሃይማኖት ሰው ከሆንክ ፍትሕን ጥራት! በግፍ እና በዘረኝነት እንዲሁም በሙስና እና ኢትዮጵያን በመክዳት ሕይወትህን ያጎሳቆሉትን፣ ይህም ሳያንሳቸው በንቀት ለተመለከቱህ እና አሁንም ይህም ሳያረካቸው ሊረግጡህ ተረከዛቸውን ላነሱብህ የማትቀመስ መሆንህን ማሳየት ኢትዮጵያዊ ግዴታህ ነው። የሃይማኖት ሰው ባርነትን እና ግፍን አይሸከምም! ከአባቶቻችንም ይህንን አልተማርንም።'አያያዙን አይቶ ጭብጦውን ቀማው' እንዲል ግፍን እና ድብቁን እና ግልፁን ዘረኝነት በግልፅ ተጋፍጠህ አገርህን ነፃ ካላወጣህ የአንተን ማንነት ጭብጦህን እሰከ ዘላለሙ አታገኘውም። በንቀት ለተመለከቱህ ሁሉ ከእዚህ በፊት በቃል እንዳስተማርካቸው አሁን ደግሞ በተግባር አስተማሪያቸው ሁን።ለዕውነት እና ለአገር በክብር መቆም ከውርደት ሞት ያድናልና።ሃይማኖት ፈሪ አያደርግም ደፋር እንጂ! አንተ በእራስህ ለእራስህ ወስን! ስራህን በቅደም ተከተል አስቀምጥ! በፍጥነት ወደ ተግባር ግባ!



ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

መጋቢት 16/2008 ዓም 

Tuesday, March 22, 2016

ሰበር ዜና: የወልቃይት ጠገዴ ውጥረት ተባብሷል።አማራ ነኝ ማለት ወንጀል ሆኗል።ዛሬ ከ2000 ሕዝብ በላይ ሰልፍ ወጥቷል።የ16 ዓመት ታዳጊ በጥይት ተገድሏል።የህወሓት ደህንነት የሱዳን ታርጋ በለጠፉ መኪናዎች ይንቀሳቀሳል (ጉዳያችን)


ዛሬ ወልቃይት ጠገዴ ወረዳ ቀራቅር የምትባል ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ ነበር።በዛሬው ዕለት ብቻ ከ2000 ሕዝብ በላይ ሰልፍ ወጥቷል።የ16 ዓመት ታዳጊ በጥየት ተገድሏል።የህወሓት ደህንነት የሱዳን ታርጋ በለጠፉ መኪናዎች ይንቀሳቀሳል።
===========================================

የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ የአማርኛው አገልግሎት ዛሬ መጋቢት 13/2008 ዓም ከወልቃይት ጠገዴ በቀጥታ በስልክ ያነጋገራቸው እና በሰልፉ የተሳተፉ ነዋሪ እንደተናገሩት:- ''ሰልፉ የተደረገው ዳንሻ ከተማ ላይ አማራ ነን ብለው በጠየቁ ወጣቶች ላይ የግድያ እና እስራት ማዋከብ ተግባር ስለነበር ይህንን በመቃወም መንገድ በመዝጋት እና በመሳሰለው ጉዳዩ ትኩረት እንዲያገኝ አድርገናል'' ብለዋል።

በዛሬው ሰልፍ ስንት ሕዝብ ተገኘ? ተብሎ ለእኚሁ ነዋሪ ለቀረበላቸው ጥያቄ  ሲመልሱ  ''በቀራቅር ከተማ ብቻ ዛሬ ተማሪዎች  ወደ 800 ተገኝተዋል። ከሕዝቡ ገበሬው ወደ 1200 ሕዝብ ባጠቃላይ በግምት ወደ 2000 ሕዝብ ተሳትፏል ብለን እንገምታለን'' ብለዋል።

ቀሪው ቃለ ምልልስ በቀጥታ እንዲህ ቀጥሏል:-

ቪኦኤ :- ተሰልፋችሁ ወዴት ሄዳችሁ?

''ተሰልፈን ከተማውን ሁለት ጊዜ ዞረነዋል።በኃላ ወደ አስተዳደሩ ቢሮ ነው የሄድነው እሳቸው የዳንሻ መንገድ ስለተዘጋ ከህዝብ ጋር ለመደራደር ሄደዋል ተባልን።ቢሮ ይወከል አይወከል አይታወቅም አንዱ ሰብስቦን ነበር። እኛ ግን እሱን ማዳመጥ አልፈለግንም።ይሄው ሰው ግን ሰልፍ መውጣታችሁ ትክክል አይደለም።የዳንሻን ሕዝብ መወከል አትችሉም፣አማራ ነኝ ለሚል ወገን ብላችሁ መደገፍ አትችሉም የሚል መልስ ነው የሰጠን። እኛም በመልሱ ስላልተደሰትን ሌላ ስሜት ውስጥ እንዳንገባ ብለን ጥለነው ነው  የሄድነው ሰውዬው እዚያው ብቻቸውን ነው የቀሩት ''

ቪኦኤ:- የታሰሩ እና የተገደሉ አሉ ብለው ነበር? የታሰሩ የሚያውቁት አለ? 

''የታሰሩ ብዙ ናቸው። ስማቸውን መዘርዘር አይቻልም ብዙ ናቸው።''

ቪኦኤ:- ስንት ይሆናሉ?

''አሁን ጧት ያለን መረጃ 70 አካባቢ ደርሰዋል ተብሎ ነበር አሁን ግን የቀሩት በረሃ ይብላን ብለው ወደ በረሃ ወርደዋል።አሁን የቀሩት ወደ 40 ይሆናሉ።ሌላው ግን በርካቶች ሰዎች ሚሊሻ ታጣቂ ሁሉ ወገናችንን አንጨፈጭፍም ብለው ወደ በረሃ መውረዳቸውን እየደወሉ እየነገሩን ነው ያሉት''

ቪኦኤ:- የተገደሉት ይታወቃሉ?

''የተገደሉት አይታወቁም ሁለት በረሃ ተገለው ተገኝተዋል።አንዱ አድራሻው ጠፍቶብናል።ሊላይ ብርሃኔ የሚባል ልጅ ታፍኖ ጠፍቶብናል። አድራሻው አይታወቅም።ሁለቱ ግን በእኛ አካባቢ ሞተው ተገኝተዋል።''

ቪኦኤ:- አስከሬናቸውን አይታችኃል?

''አዎን አይተናል ግን ከየት ይምጡ ከየት አይታወቅም ሞተው አይተናቸዋል። አንዱ ግን ሊላይ ብርሃኔ ይሆናል ብለን ገምተናል።''

ቪኦኤ:- እንዴ እናንተ አቶ የላይን አታውቁትም?

''እናውቀዋለን ግን አስከሬኑ መልኩን ቀይሯል''

በመቀጠል ሌላ ተጠያቂ ቀረቡ እና  ስለሁኔታው እንዲህ አሉ:-

''ከጎንደር ወደ ሁመራ የሚወስደው መንገድ ተዘግቷል።ከዳንሻ ወደ 30 ሰው አማራ ነን የሚሉ ታስረዋል።አንድ የ16 ዓመት ልጅ ትናንት ማታ በጥይት ገለውታል። ሌላይ ብርሃኔን ከጎንደር ይዘውት እስከ ሳንጃ ድረስ ይዘው ሲያመጡት ታይቷል ቡሬ የሚባል ቦታ ነው የያዙት ከእዛ አልታየም እሱንም ገድለውታል።''

ቪኦኤ:- የያዘው ማነው?

          ''የትግራይ ደህንነት''

ቪኦኤ:- እንዴት አወቃችሁ የትግራይ ደህንነት መሆናቸውን?

        ''እዚህ ሁለት ታርጋ የሌላቸው እና የሱዳን ታርጋ የለጠፈ መኪናዎች እዚህ ቆመው ሰንብተዋል።እነርሱ ናቸው የወሰዱት''

ቪኦኤ:- የመንግስት ደህንነት መሆናቸውን እንዴት አወቃችሁ?

         ''ይታወቃል እናውቃለን......ብዙ ሰው በረሃ ግብቷል።''

ቪኦኤ:- በረሃ ገብቶ ምን ያደርጋል? 

      ''በረሃ ገብቶ አማራጭ መፈለግ''

ቪኦኤ:- አማራጭ ምን ይደረጋል?

''በቦታው ሰላም ከሌለ በዱር ሆኖ መታገል ይቻላል ''

ቪኦኤ:- አሁን ሰሮቃ ከተማ በምን ሁኔታ ላይ ትገኛለች እርስዎ ያሉባት?

''ዝግ ነው መኪና አይንቀሳቀስም ''

ቪኦኤ :- ለምንድነው መኪና የቆመው?

''አድማ ነው አድማ''

ቪኦኤ:- መኪናዎቹ ናቸው አድማ የመቱት?

''ህዝቡ ነው የአማራ ጥያቄ ይመለስ በሚል ነው''

ቪኦኤ:- የመንግስት አካላት ናቸው መኪና እንዳይተላለፍ ያደረጉት?

      ''ህዝቡ ነው የመንግስት አካላት የሉም።ህዝቡ ነው መንገዱን እንጨት እና ድንጋይ ዘግቶ አማራ እየተደበደበ ነው መብታችንን ብሎ''

ቪኦኤ:- ታድያ እስካሁን መልስ የሰጣችሁ  የለም?

''መልስ ከፌድራልም ከዞንም የለም አራተኛ ቀናችን ነው''

ቪኦኤ:- የሊላይ ብርሃኔ ጉዳይስ እየተከታተላችሁ ነው?

''ወንድምዬው ጧት  መጥቷል  አይቼዋለሁ።ወንድሜ ሞቷል ገለውታል ብሎ ሲያለቅስ አይቼዋለሁ።''

በመጨረሻም ቪኦኤ ከህወሓት በኩል ምላሽ ለማግኘት ጥረት ማድረጉን ግን ምላሽ ማግኘት አለመቻሉን አክሎ ገልጧል።ከእዚህ በተጨማሪ የአዲስ አበባ ሕዝብ በውሃ እጦት መቸገሩን እና በርካታ የከተማዋ ክፍሎች እሰከ 20 ቀን ድረስ ውሃ እንደማያዩ ነዋሪዎች አማረው ሲናገሩ አሰምቷል።


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com 
መጋቢት 14/2008 ዓም 

በስድስት ደቂቃዎች ውስጥ የጎንደር አብያተ መንግሥታትን (ቪድዮ) The Palaces and Castles of Gondar, Ethiopia



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Emperor Fasilidas established Gondar as a capital of Ethiopia in 1636. The castles, palaces and churches from the period are now UNESCO World Heritage Site. In the video, the main Gondar historic sites: Fasil Ghebbi, Fasiladas Bath, Debre Berhan Selassie Church, Kuskuam (Empress Mentewab's Royal compound).


Monday, March 21, 2016

የአቶ አሰፋ ጫቦ ግልፅ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ መንግስት - ''ይህንን የኢህአዴግ የክልል መንግስት፣ የታሪክና የማህበራዊ ሳይንስ ሊቃውንት ነገ ሲተነትኑት፤ 'ዘመን መሳፍንት ዳግማዊ' የሚሉት ይመስለኛል'' አቶ አሰፋ ጫቦ

አቶ አሰፋ ጫቦ 

ግልፅ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርይም ደሳለኝ 

ከአቶ አሰፋ ጫቦ 

         ይህን ደብዳቤ እንድጽፍልዎ ያስገደደኝ፣ ዛሬ አገራችን የገባችበት ማጥ ነዉ። ከፖለቲካነትን ይልቅ የ“ኧረ ምን ይሻላል! ኧረ  ምን ይበጃል !” ደብዳቤ አድርገው ቢያዩልኝ ደስ ይለኛል። እንደ መፍትሔ አፈላላጊ የአገር ሽማግሌ ድምፅ ሆኖ እንዲታይልኝ/ቢታይልኝ እወዳለሁ። ነውም!! ”የጋራ ቤታችን” እንዲህ ማጥ ውስጥ ስትዘፈቅ የሚያይ አገር ወዳድ ሁሉ ድምጹን የመስማት ግዴታ ያለበት ወቅት ላይ ነን ብዬ አምናለሁ። ከፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ይልቅ የአገራችን የኢትዮጵያ መሰንበት፤ ከዚያም “በነጻነትዋ ለዘላለም ትኑር!” ማለት ይቅደም እንደማለት ነው። በደርግ ቋንቋ “ኢትዮጵያ ትቅደም!” እንደማለት!
ታዋቂዉና ዝነኛዉ የጥንቱ የቻይና ሊቅ ሱን ዡ (Sun Tzu) በ “የጦርነት ጥበብ “ (The Art of War) መጽሐፉ ከጻፈው ጠቅሼ ብጀምር የሚሻል መስለኝ፡- 
“..ጠላትህን (ይቃወመኛል የምትለውን) የምታውቅ ከሆነ ፤ደግሞም ራስክን የምታውቅ ከሆነ የግጥሚያ ወጤት ከቶም አያጠራጥርም:: ሆኖም፤ ራስክን ብቻ አውቀህ ጠላት ነው (ተቃዋሚ ነው) የምትለውን የማታውቅ ከሆነ  አሸነፍኩ ባልክ ቁጥር ሽንፈት ያጋጥመሀል። ከዚህ ውጭ ግን ራስክንም ጠላቴ (ተቃዋሚዬ የምትለውን) የማታዉቃቸው ከሆነ በገጠምክ ቁጥር ሽንፈት እጣህ ይሆናል” ይላል፡፡
ከነጉዳንጉዱ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊያን መንግስት ለማድረግ ሙከራ ያደረገ መንግስት ቢኖር ደርግ ብቻ ነበር  ለማለት የምንችል ይመስለለኛል። የስልጣን መሠረቱ ብሔረሰብ አልነበረም። ያም ሆኖ የብሔረሰብ ጭቆና መኖሩን ተቀብሏል። ተቀብሎም  በመላ- ምት ሳይሆን ጥናት ላይ በተመሠረት መፍትሔ ለመሻት ተንቀሳቅሷል። “የብሔረሰብ ጥናት ተቋም” (Institute)፤ በምርጥ የኢዮጵያ ምሁራን የሚመራ፣ አቋቁሟል። የዚያ ጥናት ውጤት ሰባት የመፍትሔ አማራጮች ያቀፈ ነበር። በጊዜያዊነትም ቢሆን ከነዚህ አማራጮች አንዱን  “የራስ ገዝ”  የሚለውን በስራ አውሎ ኢትዮጵያን በዚያ ለማስተዳደር ሞክሯል። 
ኢሕአዴግ ከዚህ የደርግ ጥናት ውስጥ ሰባተኛ የነበረውን አማራጭ ወስዶ አገሪቱን “ክልል” በሚል  መጠሪያ ክልል አዋቀረ። ክልል ማለት በዚህኛው አገባቡ፣ለኔ፣ “አጥር ታጠረ!” እንደማለት ነው” “ድርሽ ትልና!  ድርሽ ትይና!” እንደማለት። ደርግ ለኃይለሥላሴ  ሲል እንደነበረው፤ “ውስጥ ውስጡን ሲብላላ የነበረው” ይኸዉ ላለፉት አራት ወራት ቁርጡ ለይቶለት መፈረካከስ ጀመረ። መንግስትዎን ይህ ነገር “ወትሮ ነበር እንጅ መጥኖ መደቆስ፤ አሁን ምን ይባላል ድስትን ጥዶ ማልቀሰ!”ን አስታወሰኝ። በዚህ ላይ መንግስትዎ አሁንም ሐሳብ- ወለድ ጠላቶች ላይ ጣቱን መጠንቆሉን ቀጠለ። ያ የተለምደ ስለሆነ አይገርመኝም። ሆኖም አዲስ ኪዳን ውስጥ ያለ አንድ ነገር ያስታውስኛል።” ሌላው አይን ውስጥ ያለ ትቢያ ከመጠቆምህ በፊት አንተ አይን ውስጥ የተጋረጠውን ግንድ መጀመሪያ አስውግድ!” የሚለው ነው።
በምሳሌ ለማስረዳት ልሞክር- “ተከለለ” ማለት “ታጠረ” ማለት ነው። ጋሞ “ካሎ” ይለዋል። ማስቃላ ከመድረሱ ወራት በፊት የከብቶች ማስማሪያ  መሐሉ ላይ አንድ እንጨት ይተከላል። ያንን በምሳሌ ለማስረዳት ልሞክር። ያ ቦታ/መስክ “ካሎ” ሆነ ማለት ነው። ያንን እንጨት መጀመሪያ የተከለው ባለስልጣን  እስኪነቅለው ከብት ድርሽ አይልበትም። ጎሜ/ ኃጢአት ነው የሚሆነው። ወንጀል/ሽብርተኝነት እንድምትሉት! ጋሞ ውስጥ ካሎ አይጣስም። ምክንያቱም ቀላል ነው። ሕዝቡ  የተቀበለው፣ ለዘመናትም ተቀብሎት የኖረው፤ እምነቱ ፤ንብረቱ ስለሆነ ነው።
ዛሬ በአገሬ፤ በኢትዮጵያ፣ ያለው በግሪክ ተረታ-ተረት (Mythology) ያለውን የፓንዶራን ሙዳይ (Pandora Box) ያስታውሰኛል። አማልክት እንደ ምርቃት/ እርግማን ሙዳይዋን በአለም ላይ በሚገኙ ክፋቶችና ተስፋ ሞልቶ ይሀጣታል። ፓንዶራ ቸኩላ ስከፍተው ክፋቶቹ ሁሉ በረው ወጡና እቡይ ስራቸውን ተያያዙት። ወያኔ በዚህ አዲስ የመንግስት አዋቃቀሩንና ሕግ መንግስቱ ያደረገው የፓንዶርን ሙዳይ እንደመክፈት መስሎ ይታየኛል። አንድ የሚያጽናናኝ ነጥብ ቢኖር ሙዳዩ ውስጥ አሁንም ተስፋ አለ። ኢሕአዴግ ብርታትን፣ ቅንነትን፤ “ለጋራ ቤታችን” ዘላቂነትን የሚፈልግ ቢሆን፤ይህችን ሙዳይዋ ውስጥ የተረፈቸውን ተስፋ አውጥቶ ተግባር ላይ ማዋል ብቻ ነው። የዚያን እለት፤ በዚያ ወቅት ፤የኢትዮጵያ ሕዝብ በተቃውሞ ሳይሆን በድጋፍ ከአጽናፍ እስከ አጽናፍ ይውጣል ብዬ አምናለሁ።  እኔ  ደግሞ በመሠረቱ ተስፋ መቁረጥ አላውቅበትም። ተስፋ የምቆርጥ ብሆን ይህንን ደብዳቤ ባልጻፍኩም!!
ጠቅላይ ሚኒስቴር ለነበሩት ለአቶ መለስ ዜናዊ፤የዛሬ ስንትና ስንት አመት በጻፍኩት ግልጽ ደብዳቤ አገሪቱን “አያድሩበት ቤት አያመሻሹበት አያፈርጉት!” ብዬ ነበር። እርስዎን ደግሞ “ላለፈ ክረምት ቤት አይሰራም!” ለማለት እፈልጋለሁ። ያለፈው ክረምት ቤቱን ነካካው እንጅ አላፈራረሰውም፤ ወይም ወደማፈራረስ አላቃረበውም ብዬ አምኜ ነው ይህንን ተረት የጠቀስኩት። እዚህ ተረት ውስጥ በውስጠ ታዋቂነት ያለው፤ ወይም አንድምታው “ያለፈው ክረምት ያናጋውን አይነት ቤት ደግመህ አትስራ!” የሚል ይመስለኛል። ማለትም እዚያ፤ ያለፈው ክረምት ቤት አወቃቀር ላይ/ውስጥ የነበረውን ደካማ ጎን አትድግመው ነው። ማለትም  “ካለፈው የግንባታ ስህተት ተማር!” ነው።
ከሆነ ደግሞ የግንባታው ስህተት ምን ነበር? ዙሪያውን ላለመዞር ስህተቱ ሕገ መንግስቱ ነው ! ስህተቱ ኢትዮጵያን በክልል ማዋቀሩ፤በብሔረሰብ ማካለሉ ነው!! 
ኢትዮጵያን በብሔረሰብ ሲዋቅር ወያኔ የመጀመሪያ አልነበረም። በ1928 ኢትዮጵያን የወረረው የጣሊያን፤ የሙሶሉኒ አወቃቀር በብሔረሰብ ላይ የተመሠረተ ነበር። “የጣልያን የምስራቅ አፍሪካ ግዛት! (Africa Orientale Italiana” ይለዋል። ከ19ኛው ምእተ አመት ጀምሮ ብዙ የጣሊያን “ሊቃውንት” ያጠኑት ጥናት ውጤት መሆኑ ነበር። የጥናታቸው ውጤት ኢትዮጵያን በጎሳ በመከፋፈል እርስ በርሳቸው ማናቆርና እነሱ ሲባሉ እኛ አርፈን መግዛት ነው የሚል ነበር። ታሪክ እንደሚነግረን፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዛኛው ተባብሮ፤ ዱር-ገደል ገብቶ  ጣሊያንን አዋርዶ አባረረው። እንግሊዝም  በሰሜን በኩል የትግራይ- ትግሪኝን፣ በምስራቅ በኩል የታላቂትዋን ሶማሌ መርዝ ቀበረች/ረጨች። ባጭሩ ይህ በብሔረሰብ  መከፋፋል ከጠላቶቻችን የመጣ በመሆኑ ሞዴል አድርገን ልንቀበለው ከቶም አይገባም ለማለት ነው። ይህም ማለት   ለአዲሱ፤ መጭው ክርምት፣ የሚሰራው ቤት በጠላቶቻችን ንድፍ ላይ የተመሠረት ሳይሆን በኢትዮጵያ እሴት፤ በኢትዮጵያ እውነት ላይ መሆን አለበት ለማለት ነው። መሠረቱ፤ ጣሪያ፤ ግርግዳው፤ ታዛው የኛው ይሁን ነው። ዞር-ዞር ብሎ የማየት እንጅ ታሪካዊ እሴት ሞልቶ የተረፈን አገር ነን። ከልቤ ነው የምልዎት!!
ደርግን “ከነጉዳንጉዱ”ብዬ ነበር የገለጽኩት። ለጊዜው ለተነሳሁበት ጉዳይ ሲባል ጉዳንጉዱን ልተወውና በጎ ጎኖቹ ሊባሉ ከሚችሉት ጥቂቱን ልጥቀስ። ከሁሉ ሁሌ  ቁልጭ ብለው ከሚታዩኝ ውስጥ አብዮት አደባባይ ሰልፍ በተደረገ ቁጥር ከደርግ ሊቃናተ መንበሮች በስተቀኝ ፓትሪያርኩ አቡነ ተክለሐይማኖት፤ ከግራ ሐጂ ያሲን የክብር ቦታ ይዘው ተቀመጠው የማየው ነበር። በኢትዮጵያ ምድር የእምነት እኩልነት ለማየት ሲያልም ለነበረ እስልምና እንዲህ የክብር ቦታ አግኝቶ በአደባባይ ከማየት የተሻለ የሚያረካ ወቅት ይኖራል ብዬ አልገምትም። ከዚያም መስከርም 12ትን አረፋ፤ ታህሳስ 13ትን መውሊድ፣ ሰኔ 29ን ረመዳን ብሔራዊ በአል አድርጎ የደነገገዉ ደርግ ነበር።
የካቲቲ 25 ቀን 1967 የገጠር መሬት አዋጅና የትርፍ ቤቶችና የከተማ ቦታ አዋጅ ሌላው የሚጠቀስ ነበር። የነዚህ አዋጆች ትርጉም “መሬት ለአራሽ/ለባለቤቱ፣ የከተማ መኖሪያ ቤትን አናሳ ገቢ ያላቸው ጭምር ተከራይተው እንዲኖሩ ማድረግ ነበር።  ደርግ ወያኔን ጉድፉን አጥርቶ፤መንገዱን ጠራርጎና ዘርግቶ ጠበቀው ልንል የምንችል ይመስለኛል። ወያኔን ከጥቂት ማሻሻል/በስተቀር “ግፋ በለው!” ብቻ ነበር የሚጠበቀው። ታዲያ ምን ሆነ?
ከዚያ የሆነውን እርስዎ ደጋግመው ከተናገሩት አንዱን ብቻ ወስጄ ለመግለጽ እንድሞክር ይፈቀድልኝል። ቃል-በቃል ባልጠቅስዎትም “መንግስታችን የኪራይ ሰብሳቢ መንግስት ሆነ!” አሉ። እኔም ልሁን ማንኛውም ተቃዋሚ ወይም መንግስትዎ አሸባሪ የሚላቸዉም ቢሆኑ ይህንን መንግስት ከዚህ፣ እርስዎ ከገለጹት በተሻለ ሊገልጡት የሚቻላቸው አይመስለኝም።
ለመሆኑ እኒህ ኪራይ ሰብሳቢዎቹ እነማን ናቸዉ? የሚያከራዩት ምንን/ማንን ነው? ብሎ መጠየቅ ተገቢ ይመስለኛል። ብቻ የሚያከራዩት ቢኖር ነው አከራይተው ኪራይ የሚሰበስቡት። ይህ ደግሞ ራሱን በራሱ ገላጭ እውነት ነው። ከሆነ ደግሞ የሚያከራዩት ኢትዮጵያን ወይም የኢትዮጵያን መሬትና ቤት መሆኑ ነው። ተሳስቼም ከሆነ ልታረም ፈቃደኛ ነኝ። ልማት በሚባል ታላቅ አሳሳች ቃል ስር ዛሬ ብር ወይም ጉልበት ያለው የፈለገውን ያክል የገጠር መሬትና ቦታ ማግኘት እንደሚችል መንግስትዎ በአደባባይ የሚናገረውና አስፈጻሚ አዋጅም ያወጣለት ነው። በቅርቡ ያነበብኩት አንድ የአፍሪቃ የባለሚሊዮን ዶላር ሀብታሞች ዝርዝር ገርሞኝ ነበር። ባለሚሊዮን ዶላር ሀብታሞች ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያዊያን የአንደኝነት  ስፍራ ይዘዋል። አሁን አንደኝነታችን በረዥም ሩጫ ብቻ ሳይሆን በዶላር ጭምር መሆኑ ነዉ/ሆነ።  እንደ ኢትዮጵያዊነቴ በዚህ ልኩራበት ወይስ ልፈርበት? ይህ ሁሉ የተቻለውን ‘በሕጉ’ መሠረት ባለመሬቶቹ ከመሬትና ቤት ንብረታቸው ተነቅለው ተጥለው ነው።  የመሬት ላራሹ አዋጅ፣ መሬት ለኪራይ ሰብሳቢ በሚል አዋጅ የተተካ አይመስልዎትም? የእስልምና ተከታዮችም  ከብዛታቸው የተነሳ ስማቸውን ልጠራ የማልችለውን ወህኒ ቤት ሞልተውታል።
በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ዘመነ መሳፍንት ተብሎ የተሰየመ አነሰም በዛ የመቶ አመት ታሪክ አለ። ይህም ማእከላዊ መንግስት የላላበት፤ የአካባቢ መሳፍንት የነገሱበት ዘመን ማለት ነው። ግዛቱን ለማስፋት፤ ወይም ጉልብቱን ለማሳየት፤ ወይም እኔ ካንተ በናቴም ባባቴም እበልጣለሁ በሚል ሰበብ አስባብ ጦርነት የሚከፋፈቱበት፤ ሚስኪኑ ኢትዮጵያዊ የሚያልቅበት ዘመን ነበር። ያንን ዘመን በር-ቀዳጅ የአድዋው ስሑል ሚካኤል ነበሩ።
ከዚያ ያለው እንደገና የማእከላዊ መንግስት መመስረት፤ ወይም ግዛት ማስፋት ዘመን ነበር። የዚህ አይነት ብሔራዊ መንግስት የመመስረት ሂደት (The Formation of National State) የሰው ልጅ ታሪክ ወጥ አካል ነዉ። ከነክፋቱ!! የአሁንዋ/የዛሬይቱ ኢትዮጵያም የዚያ ወጤት ነች። አሁን ከ120 አመት በላይ ሆኖታል። በዚህም የተነሳ ዛሬ ኢትዮጵያ በሚባለው አገር  ታይቶ ተስምቶ የማይታውቅ የብሔረሰብ አነባበሮ ተፈጥሯል። በዚህም 120 አመታት ውስጥ መጋባት፤ መገባባት፣ መግባባትና መዋለድ ብቻ ሳይሆን  አብሮ የመኖርና የመቻቻል  ስነ ልቦና (Psychological make up) ተፈጥሯል። 
ይህንን የኢህአዴግ የክልል መንግስት፣ የታሪክና የማህበራዊ ሳይንስ ሊቃውንት ነገ ሲተነትኑት፤ ዘመን መሳፍንት ዳግማዊ የሚሉት ይመስለኛል። በአገር ደረጃ ወደፊት መራመድ ራሱ ከባድ መሆኑን ይሔው የምታዩት ነው። 200 አመት ወደ ኋላ ለመውሰድ መሞከር ግን የጤና አይመስለኝም። ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ህዝብ ዩጎዝላቪያ ይባል የነበረው አገር ህዝብ አይነት አይደለም። ያ ሕዝብና  መንግስት እንደዚያ የተፈረካከሰው የዛሬ 500 አመት በፊት የሆነ  የታሪክ በደል በማንዠጉና አላምጦ ባለመዋጡ ነበር። ቱርክም፤ ሊባኖስም፤ ሶሪያም፤ ኢራቅም አይደለም:: የኢትዮጵያ ሕዝብ ቂም በቀል ፤የነበረ ያልነበረ የሚያመንዥግ ህዝብ  አይደለም። አላምጦ ውጦ የታሪኩ አካል አድርጎ ወደፊት የሚራመድ ታላቅ “ይቅር ለግዜር!!” ተባባይ ህዝብ ነው።  የታላላቅ እምነቶቹም ሆነ የባሕላዊ እምነቶቹ መሠረቱ ይሔው ነው።
የእስልምና እምነት በአላት በደርግ ዘመን ወደ ብሔራዊው በአልነት መሸጋገራቸውን አንስቼ ነበር። አሁን በኢሕአዴግ ዘመን ደግሞ ምን እንደደረሰባቸውና በመድረስ ላይ እንዳሉ የሚያዉቁትና መላው አለምም የሚያዉቀው ስለሆነ ዝርዘሩ ውስጥ አለገባም። አንድ ነገር ብቻ ላስታውስዎት እወዳለሁ። ጠቅላይ ሚኒስቴር የነበሩት የመለስ ዜናውን “የመጨረሻ ኑዛዜ” ያንብቡ። ኑዛዜ ያልኩት ከማረፋቸው አንድ ይሁን ሁለት ወር በፊት ያደርጉት የሚኒስቴሮች ምክር ቤት ስብሰባ ቃለ ጉባዔ ነው። ይህንን ሚስጥራዊ ቃለ ጉባዔ ያነበብኩት ድሕረ ገጾች ላይ ተለጥፎ ነበር። ማመን ነበር ያቃተኝ!! ወይም አንድ ሰው “የመጨረሻው ደውል” እንደተደወለለት ሲያውቅ፤ “እውነቱን ተናግሬ ልሙት!” ያሰኘዋል ይሉናል። በዚያ ስበስባ ላይ የአቶ መለስ አስተያየት ከማውቃቸውና ከሚታውቁበት መለስ ለየት ያሉ ነበር። እውነት ብቻ ሳይሆን የሚስጥር እውነት ነበር። ይህ እውነት የመጀመሪያቸውም የመጨረሻቸውም ነበር ብዬ እገምታለሁ። 
አቶ መለስ ያሉት ቢጨመቅ “ይህንን የእስልምና እምነት ችግር የቀየስነውና የፈጠርነው እኛው (መንግስት) ስለሆንን ከዚህ በኋላ ይወገድ!” የሚል ይሆናል። የተቃወመ ሰው ቢኖር አንድ ዶክተር ሽፈራው ተክለ ማርያም  የሚባሉ ነበሩ። የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈርጌሳ  መደገፍ ብቻ ሳይሆን ድርጊቱን አውግዘውና ይህንን ወሳኔ አድምቀው፤ አክርረው ደግፈዋል። ያም ሆኖ የእስልምና እምነት ተከታዮች ዛሬም አክራሪ ይሁን አሸባሪ (ልዩነት አልገባኝም፤ የገባውም ሰውም አላገኘሁም) በሚል እንደታጎሩ፤ያልታጎሩትም “ማነህ ባለ ሳምንት!”ን በመጠባበቅ እንደተሳቀቁ ናቸውና እባክዎን የአቶ መለሰን ኑዛዜ ስራ ላይ ያዉሉት። ከዚያ የተሻለ መፍትሔ የለምም!!
ይህንን ደብዳቤ  ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት አቶ መለሰ ዜናዊ አንዴ ከተናገሩት ጠቅሼ ማጠቃለል ፈለግሁ። መለስ፤ በሆነ አጋጣሚ (ረስቸዋለሁ) “በሩም መስኮቱም ከተዘጋ ህዝቡ ግድግዳውን ሰብሮም ቢሆን ይወጣል” ነበር ያሉት። ቃለ በቃል መጥቀሴ ሳይሆን መንፈሱ ይሔው ነበር። ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ የሚታየው ቃል በቃል ይሔው መሆኑ የሚያከራክር አይመስለኝም። በምድር ላይ የሚታየው ማስረጃ ይሔው ነው። በሰነዶች ላይ የሚታየው ይሔው ነው። ተቃዋሚዎች፣ መንግስት ግን አክራሪ ወይም አሸባሪ የሚላቸውም፣ የሚናገሩት ይህንኑ ነው። አገርና አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች አካላትም የሚሉት ይህንኑ ነው። እርስዎም በተደጋጋሚ በሚያደርጉት ንግግር የሚሉት መንፈሱ ሲነጠር ይሕንኑ ይመስላል።
ይህ ሁሉ ሲሰባሰብ አንድ እውነት የሚያሳይ ይመስለኛል። ይህንን ኢሕአፈግ “ልማት፣ እድገት” ያለውን ሕዝቡ አልተቀበለውም። ይህንን ኢሕአዴግ መቶ-ከመቶ(100%) ድምጽ አግኝቼ ምርጫ አሸንፌያለሁ ያለው ውሸት መሆኑ ነው። ውሸትም ባይሆን ትላንት መቶ-ከመቶ (100%) የደገፈ በማግስቱ መቶ-ለመቶ ፈንቅሎ አይነሳበትም ነበራ! ወደ ህዝቡ መግቢያ ሽፋን እንዲሆኑ የተፈጠሩት ለምሳሌም እንደ ኦሮሞ  ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት  የተባለውን ሽፋን መስጠት ቀርቶ ራሳቸው የሚሸፈኑበት ያጡ መሆናቸውም እውነት ነው። “አባይ ማደሪያ የለው ግንድ ያገላብጣል”ን አስታወሰኝ። እዚህ ያላነሳሁትን ሌሎች ማስረጃዎች ሰብሰብ አድርገን ብናበራያቸው ይህ ኢሕአዴግ ያመጣው ስርአት አልሰራም ማለት ነው። “ለማንም አልበጀ!” ሆኗል እንደማለት ነው። አድሮ ከዋለ ደግሞ ካደረሰው በላይ ዘላቂና ጠላቂ ጉዳት ያመጣል የሚል ብርቱ ፍርሐት አለኝ።
እንደኔ እንደኔ መፍትሔው፤ መውጫው ችግሩን በድፍረት ፊት ለፊት መጋፈጥ ነው። አውቃለሁ! መጋፈጡ እንዲህ ቀላል አይመስለኝም! ድፍረቱም ብልሐቱም ላይኖር ይችላል። ያም ሆኖ ግን አማራጩ፤ ማለትም አድሮ ውሎ ጊዜ ይፈተዋል   በሚል የሚሰጥ የመተንፈሻ ጊዜ መግዣ ምክንያት መደርደር  የሚጸጽት አማራጭ ይፈጥራል።  
ትላንትና ያደመጥኩትን አንድ ነገር ልጨምር ፈለግሁ:- ከሶቪየት ህብረት ዘመን ጀምሮ ሩሲያን የሚያውቁ፤ አሁን ጡረታ ላይ የሚገኙ ጋዜጠኛ አን ጋረለስ (Anne Garreles) ሰሞኑን Public Broadcasting System (PBS)  በተባለ ራዲዮ ጣቢያ  Fresh Air በሚባል ፕሮግራም ላይ ረዘም ያለ ቃለ መጠይቅ አድርገው ነበር። ለቃለ መጠይቁ ዋንኛ ምክንያት የፑቲን አገር “Putin Country” የሚል መጽሐፍ ደርሰው ስለነበር ነው። 
ቭላድሚር ፑቲን የሩሲያ የአሁኑ ፕሬዚዳንት ናቸው። ጋረልስ በዚህ ምልልስ በዚያ አገር፣ በሩሲያ፣ ውስጥ የሚታየውን የፖለቲካና ሁሉ ዘርፍ አቀፍ ንቅዘት ይዘርዝራሉ። የፑቲንን ጨምሮ!   “ይህ ሁሉ ጉድ እያለ ሕዝቡ ፑቲንን እንዴት ያያል?” ለሚለው በሰጡት መልስ “ዛሬ በአለም ላይ ከሚገኙት መሪዎች ሁሉ በመላው የሀገሪቱ ህዝብ በጣም ተወዳጅነት ያለው መሪ ቢኖር ፑቲን ናቸዉ”አሉ። ምክንያቱን ሲጠይቁ “ከሳቸው በፊት የነበረው ፕሬዝዳንት፣ ቦሪስ የልሲን፣ ሰካራም ከመሆኑም ሌላዘራፊም ነበር። ዝርፊያው እንደቀጠለ ሆኑ ፑቲን በአገራችን፤ በሩሲያዊነታችን እንድንኮራ፣ እንድንኩራራ፣ አፋችንን ሞልተን ሩሲውያን ነን ለመለት አበቃን!” የሚል መልስ ሰጡ። ቃለ ምልልሱን ከጠቀስኩት ጣቢያ ማድመጥ የሚችሉ ይመስለኛል።
ለኛም የምንኮራባት፤ በጠፍ ጨረቃ ጥለን የማንፈጥጥባት፤ እንደወጣን የማምንቀረርባት፤ ለመመለስ የምንናፍቃት ኢትዮጵያን እንዲያስቡ፤ እንዲያልሙ፣ ወደዚያ የሚወስደውን መንገድ በሙሉ መስራት ባይችሉ እንኳን ጠረግ ጠረግ እንዲያደርጉ ከልብ እመኛለሁ። እመኝሎታለሁም!
ብርታት፤ ብልሐት እመኝላችኋለሁ! ለአገሬም የተሻለውን፤ የሚበጀውን፤ የሚያምረውን፣ የሚዘልቀውን የሚያዘልቀንን እመኝላታለሁ!

ኢትዮጵያ በሕዝቦችዋ ትብብር በነጻነትዋ ለዘለዓለም ትኑር!
ከአክብሮት ጋር 

ምንጭ - አዲስ አድማስ ጋዜጣ ቅዳሜ መጋቢት 10/2008 ዓም ዕትም 

Saturday, March 19, 2016

ኢትዮጵያዊ ማንነት! ሳራን ከጀርመን መቱ ድረስ የወሰደ ኢትዮጵያዊነት ለዘላለም ይኑር! (የሳራን ቪድዮ ንግግር ይመለከቱ)


Video Source: TED Ideas worth spreading*


ጉዳያችን GUDAYACHN 

በሳምንቱ ውስጥ የነበሩ አጫጭር ዜናዎች (ጉዳያችን)




አቶ ኃይለማርያም የዓለም ሕዝብ የምግብ ዕርዳታ እንዲለግስ በድጋሚ በይፋ ተማፀኑ 

 ኢትዮጵያ ትናንት ዓርብ ለዓለም ማኅበረሰብ የምግብ እርዳታ እንዲሰጣት በድጋሚ ተማፀነች። ተማፅኖውን ያቀርቡት አቶ ሃይለማርያም ሲሆኑ የምግብ እርዳታው በአፋጣኝ ካልደረሰ አደጋ እንደሚከተል ገልጠዋል። አቶ ኃይለማርያም በምግብ እራሳችንን ችለናል ባሉ በአንድ ዓመት ሳይሞላ ነው ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብን ለሁለተኛ ጊዜ የተማፀኑት።

በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በረሃብ ለተጎዱ ወገኖቻቸው መርዳት ቀጥለዋል 

በውጭ የሚኖሩ ኢትዮያውያን በረሃብ ለተጎዱ ወገኖች መርዳታቸውን ቀጥለዋል ባለፈው ሳምንት አሜሪካ የሚገኘው በአርቲስት ታማኝ እና የሚመራው ''ግሎባል አልያንስ'' (አለማቀፋዊ ህብረት ወይንም ቃል ኪዳን ለኢትዮጵያ) የተሰኘው ድርጅት ከአንድ ሚልዮን ብር በላይ አሰባስቦ ለ'ዎርልድ ቪዥን' አስረክቧል።በአውሮፓ እና ሌሎች አገሮች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም በማሰባሰብ ላይ ናቸው።

አቶ አርከበ 'ብሉምበርግ' ቀርበው ምን አሉ?

 አቶ አርከበ በእዚህ ሳምንት ለብሉምበርግ ''በምግብ እራሳችንን ችለናል የኦሮምያው ግጭት ምጣኔ ሃብቱን አልጎዳም'' ብለዋል።እዚህ ላይ የቡና አምራች አካባቢ አመፅ ተነስቶ የአገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ቡና ላይ የተመሰረተ ሆኖ ሳለ እንዴት ምጣኔ ሃብቱ አልተጎዳም? ብላ የብሉምበርግ ጋዜጠኛ መጠየቅ ነበረባት።አቶ አርከበ በቃለ ምልልሳቸው ላይ በኢትዮጵያ የሚነሱ ፀረ መንግስት እንቅስቃሴዎች በሙሉ ወጣቱ ሥራ ስላጣ ነው፣ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካ እንከፍታለን የመሳሰሉትን ይናገሩ እንጂ አገሪቱ ግልፅ የሆነ የምጣኔ ሀብት አቅጣጫ እንደሌላት ለጋዜጠኞቹ ግልፅ ሆኗል።ለእዚህም ነው የብሉምበርግ ጋዜጠኛ ''ወዴት እየሄዳችሁ ነው ምንድነው ቀዳሚ ትኩረታችሁ?''የሚል ጥያቄ የጠየቀው።አቶ አርከበ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር እየጨመረ እንደሚመጣ እና በቅርቡ ከዓለም 10ሩ በሕዝብ ብዛት ቀዳሚ አገራት ውስጥ እንደምትገባ ገልፀው ለመፍትሄነት ያስቀመጡት ግን ግልፅነት የሌለው የአገሪቱን አቅም ያላመላከተ እና ወደፊት ኢንቨስተር ይመጣል የሚል መልስ ነበር።በመሰረቱ አቶ አርከበ በቃለ መጠየቃቸው ላይ የምጣኔ ሀብት ቃላት (terminology) አጠቃቀም ላይ ከሌሎች ባለስልጣናት የተሻለ የእንግሊዝኛ አጠቃቀም ይታይባቸዋል።

''ጌታዋን የተማመነች በግ ላቷን ውጭ ታሳድራለች'' ግብፅ በድጋሚ 'የኢትዮጵያን የአየር ክልል በሳተላይት ኢትየጠቆጣጠርኩ ነው 'አለች ህወሓት በዝምታ አበረታቷል። 

- ግብፅ የኢትዮጵያን የአባይ ግድብ ላይ ለ24 ሰዓታት ለመከታተል የቀድሞውን ሳተላይት በሌላ ልመቀየሯን በግልፅ ተናግራለች።የእዚህ አይነት ግልፅ ንግግሮች በግብፅ ባለስልጣናት ሲነገር ኢትዮጵያ እንደ ሉዓላዊ አገር ምላሽ አልሰጠችም።ይህ አንዱ የህወሓት አሳፋሪ ተግባሩ አካል ነው።የእዚህ አይነት ተግባር በግልፅ መነገራቸው ለኢትዮጵያ ያላቸውን ንቀት ለማሳየት ካልሆነ በቀር የአንድ ሉዓላዊት አገርን መሬት ከሳተላይት አያለሁ የሚሉ ንግግሮች በሚንስትር ደረጃ ሲነገሩ የተለመዱ አይደለም።በድብቅ አገራት ቢያደርጉትም በአደባባይ መናገር ግን ንትርክ ስለሚያስከትል አያደርጉትም የህወሓት ኢትዮጵያ ግን  በእዚህ ጉዳይ ላይ የግብፁን አምባሳደር ጠርታ ማብራርያም አጠይቅም።የመንደር አስተሳሰብ ካለህ ስለ ትልቁ አገር ማሰብ ታቆማለህ።ህወሓት ከአገር ይልቅ ለመንደር የሚጨነቅ ድርጅት ስለሆነ የኢትዮጵያን ጉዳይ እንዲህ ያጎሳቁለዋል።

''የኢትዮጵያው ደግ ክርስቲያን ንጉስ  እስልምናን ባይከላከል ኖሮ እስልምና ዛሬ አይኖርም ነበር'' የግብፁ የእስልምና እምነት አባት 

- ''በመጀመርያ እስልምናን ከለላ የሰጠልን ክርስትና ነው።የኢትዮጵያው ደግ ክርስቲያን ንጉስ ባይኖር ኖሮ እስልምና በአሁኑ ሰዓት ላይኖር ይችል ነበር'' ይህንን የተናገሩት የግብፅ የሃይማኖት አባት ለጀርመን ምክርቤት በእዚህ ሳምንት ነው። የሃይማኖት አባቱ እንደገለፁት ደጉ የአብሲንያ ንጉስ የመሐመድ ቤተሰቦችን መንከባከቡ እና በሰላም ማቆየቱ ዛሬ እስልምና ሳይጠፋ እንዲኖር አድርጎታል በማለት በማስረጃ አብራርተዋል።የግብፅ አልሃራም ጋዜጣ ዘግቦታል።ይህ ታሪካዊ ንግግር ነው።በመጀመርያ ደረጃ ንጉሡ ክርስትናውን ጠብቆ መኖሩን እና ኢትዮያ በዓለም ታላላቅ ክስተቶች ላይ አሻራዋ መኖሩ የተገለፀበት ነው።

ኢማሙ ለጀርመን ምክርቤት ባለፈው ማክሰኞ መጋቢት 6/2008 ዓም ቀርበው ያሉት እንዲህ የሚል ነበር።''Christianity was the first to provide sanctuary for Islam; without Abyssinia and its Christian king who protected the first Muslims, Islam would have been destroyed in its cradle,” Grand al-Azhar Imam Sheikh Ahmed al-Tayeb

''እየሰመጠ ካለ መርከብ ራስን የማዳኛ ጊዜ አሁን ነው!'' የአርበኞች ግንቦት 7 ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ሲጠናቀቅ ያወጣው መግለጫ።

በእዚህ ሳምንት ሌላው በድረገፆች የወጣው ዜና የአርበኞች ግንቦት 7 ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን ሲያጠናቅቅ በመጪዎቹ ሶስት ወራት የሚሰሩት ሥራ ላይ መወያይቱን እና ማፅደቁን ''ዘ-ሐበሻ'' ድረ-ገፅ ገልጧል።ድረ-ገፁ እንዳስታወቀው ስብስባው የሚከተሉትን  መልዕክቶች ለአባላቱና ደጋፊዎች፣ለመከላከያ ሰራዊት፣ለለህወሓት፣ ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴግ እና የኢህአዴግ አጋር ድርጅቶች አባላት እና  ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አስተላልፏል። መልክቶቹም : -


1. ለአርበኞች ግንቦት 7 አባላትና ደጋፊዎች
ወሳኝ በሆነ የትግል ወቅት ላይ እንገኛለን፤ በዚህ ወቅት በትጥቅ ትግሉ በቀጥታ ተሰልፈው ያሉት አባሎቻችን፣ በአገር ውስጥ በሕዝባዊ እምቢተኝነት በመሳተፍ ላይ ያሉ አባሎቻችንና ደጋፊዎቻችን እና በውጭ አገራት የሚገኙ አባሎቻችንና ደጋፊዎቻችን ሁሉ በአንድ ልብና መንፈስ ህወሓትን ከስልጣን የማስወገድ ሥራ ላይ እንዲረባረቡ ሥራ አስፈፃሚው ጥሪ ያደርጋል።
2. ለአገር መከላከያ ሠራዊት፣ ለፓሊስና የደህንነት አባላት
ነገ ከሚወድቅ ሥርዓት ጎን ቆማችሁ ወገኖቻችሁን ማጥቃት ተው! የመሳሪያዎቻችሁ አፈሙዝ የሁላችንም ጠላት ወደሆነው አገዛዝ ይዙር! ከወያኔ በኋላ በሚመጣው ሥርዓት የመከላከያ ሠራዊትና ፓሊስ መበተን የለባቸውም ብለን እናምናለን፤ ይህ እንዲሆን ግን ዛሬ ከአምባገነን ሥርዓት ጎን ሳይሆን ከሕዝብ ጎን ቁሙ።
3. ለህወሓት፣ ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴግ እና የኢህአዴግ አጋር ድርጅቶች አባላት
እየሰመጠ ካለ መርከብ ራሳችሁን አውጡ! አባል የሆናችሁባቸው ድርጅቶች ለአገራችን ብቻ ሳይሆን ለእናንተም በግል የሚበጁ አይደሉም። ቢቻል በግልጽ፤ ካልተቻለም በስውር ድርጅቶቻችሁን በማዳከም የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግልን አግዙ።
4. በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲፈጠር ለሚታገሉ የፓለቲካና ሲቪክ ማኅበራት
በጋራ የምንቆምበት ወቅት አሁን ነው። ዛሬ የምናደርጋቸው ትብብሮች የረዥም ጊዜ ውጤት ያላቸው መሆኑን ተገንዝበን ኃይላችንን እንድናስተባብር ጥሪ እናደርጋለን።
5. ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ
ጥያቄዎቻችን አካባቢ ተኮር ሊሆኑ ይችላሉ፤ ግባችን ግን የጋራ ነው። ከህወሓት አምባገነን አገዛዝ ነፃ የወጣች ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እንድትኖረን ሁላችንም በአንድነት እንድንቆም የአርበኞች ግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጥሪ ያደርጋል። 

የሚሉ ነበሩ።

ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com 

መጋቢት 10/2008 ዓም  (March 19/2016) 

Tuesday, March 15, 2016

ኦኬሎ ይፈታ! ኖርዌይ ኢትዮጵያውያንን በግዳጅ መመለስ ታቁም! ኢትዮጵያውያንን መግደል ይቁም! በሚል በኖርዋይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሰልፍ አደረጉ።







ዛሬ መጋቢት 6/2008 ዓም በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ኢትዮጵያውያን የኖርዌይ ዜግነት ያላቸው ኢትዮጵያዊው  ኦከሎ አክዋይ ኦቻላ በወያኔ ደቡብ ሱዳን ላይ ተጠልፈው ለእስር መዳረጋቸውን፣ የኖርዌይ መንግስት በግዳጅ ኢትዮጵያውያንን ከአገሩ ለማስወጣት እና ወደ ኢትዮጵያ ለመውሰድ ማቀዱን በመቃወም እና በኦሮምያ እና ልዩ ልዩ የአገራችን ክፍሎች የተፈፀሙትን እና በመፈፀም ላይ ያሉትን ግድያዎች እና እስራቶች በመቃወም  ሰልፍ ወጥተዋል።ሰልፉ የአገሪቱ ፖለቲካ ፓርቲዎች ፅህፈት ቤት ከሚገኝበት እስከ ምክርቤቱ ድረስ የ20 ደቂቃ የእግር ጉዞ በማድረግ የተከናወነ ሲሆን በሰልፉ ወቅት የኖርዌይ ፖሊስ በፈረሰኛ እና በመኪና በመታገዝ ጥበቃ አድርገዋል።

በሰልፉ ላይ የተገኙ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጅ የሆኑ የኖርዌይ ዜጎች ከደቡብ ሱዳን በግዳጅ ታግቶ የተወሰደው የቀድሞ የጋምቤላ አስተዳደር ኦኬሎ በፍጥነት እንዲፈታ የሚጠይቅ መፈክር እና ፎቶ ግራፍ ይዘው ነበር። በሰልፉ ላይ የተለያዩ ኢትዮጵያውያን ድርጅቶች፣የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በኖርዌይ እና የኖርዌይ እና ዓለም አቀፍ ሰብአዊ እና ፀረ ዘረኝነት ድርጅቶች ተወካዮች የተገኙ እና ንግግር ያደረጉ  ሲሆን የሰልፈኛውን ጥያቄ የያዘ ደብዳቤም ለኖርዌይ ፓርላማ እንዲደርስ  መደረጉን ለማወቅ ተችሏል።

ከእዚህ በታች በጉዳያችን የተነሱ የሰልፉን ገፅታ የሚያሳዩ ፎቶዎች ይመልከቱ።













ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com
መጋቢት 7/2008 ዓም


Saturday, March 12, 2016

''ኩዳድ '' የአማርኛ ታሪክ ቀመስ ልብ ወለድ መፅሐፍ በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ተመረቀ

የኩዳድ የፊት ገፅ 

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አርአያነት ያለው ተግባር እየፈፀሙ ነው። በአራት ዓመታት ውስጥ ሁለት የአማርኛ መፃህፍት፣አንድ ዳጎስ ያለ የአማርኛ ኖርዌጅኛ መዝገበ ቃላት እና ሰዋሰው (grammar)  ታትመው ገበያ ላይ ውለዋል። ይህ በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ትልቅ አርአያነት ያለው ተግባር ነው።
ወ/ሮ ዙፋን የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በኖርዌይ ሰብሳቢ የመክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ 

ዛሬ መጋቢት 3/2008 ዓም ደግሞ በደራሲ አቶ ማተቤ  መለሰ የተፃፈ ''ኩዳድ'' የተሰኘ ታሪክ ቀመስ ልብ ወለድ መፅሐፍ የምረቃ ስነ-ስርዓት ተከናውኗል።

ይህ 433 ገፆች የያዘ ታሪክ ቀመስ ልብ ወለድ  መፅሐፍ ምረቃ መርሃ ግብር ላይ በርካታ በኦስሎ እና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የታደሙበት ሲሆን የመክፈቻ ስነ-ስርዓቱን የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ በኖርዌይ ሰብሳቢ ወ/ሮ ዙፋን ለምረቃ የተዘጋጀውን ሪባን በመቁረጥ መፅሐፉ መመረቁን አብስረዋል።በመቀጠልም መፅሐፉ በሶስት ምሁራን ተገምግሟል።በመፅሐፍ ግምገማው ላይ በኦስሎ ዩንቨርስቲ ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር ተክሉ አባተ፣ ዶ/ር ሙሉ ዓለም አዳም እና አቶ ይበልጣል ጋሹ የተሳተፉ ሲሆን ሶስቱም ጥልቅ የሆነ ዕይታቸውን ለታዳሚው  በየተራ አቅርበዋል።
ደራሲው አቶ ማተቤ መለሰ  ከልጆቻቸው ጋር የኬክ ቆረሳ ስነ-ስርዓት ላይ 


ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር ተክሉ አባተ ከመፅሐፉ የፊት ገፅ ጀምሮ እስከ መጨረሻው ድረስ የታሪኩን ፍሰት እና ተያያዥነት ከመፅሐፉ እያጣቀሱ እና የገፀ ባህርያቱን የገሃዱ ዓለም ነባራዊ ነፀብራቅ መሆን ላይ አፅንኦት ሰጥተው ያብራሩ ሲሆን ዶ/ር ሙሉ ዓለም በበኩላቸው ከደራሲው ጥረት እና ትጋት ተነስተው እስከ ቃላት አጠቃቀም ጥልቅ ግምገማቸውን አቅርበዋል።አቶ ይበልጣል ጋሹ በሌላ በኩል በመፅሐፉ ውስጥ የተጠቀሱት ታሪኮች ምን ያህል ከቦታው ባህላዊ መስተጋብር ጋር የተያያዘ መሆኑን እና የሚያካልላቸው ቦታዎች ከጎጃም እስከ ኤርትራ ከዝያም እስከ ሱማሌ ምድር ድረስ  መሆኑን አብራርተዋል።
የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በኖርዌይ ሰብሳቢ በማኅበረሰቡ ስም ለደራሲው ስጦታ ሲያበረክቱ 

ከመፅሐፉ ግምገማ በኃላ የሻይ እረፍት ተደርጎ ከታዳሚው ለገምጋሚዎች እና ለደራሲው አቶ ማተቤ መለሰ ጥያቄዎች፣አስተያየቶች እና የመልካም ምኞት መግለጫዎች ተሰምተዋል።ለቀረቡት ጥያቄዎች ደራሲው እና የመፅሐፉ ገምጋሚ ምሁራን በቂ መልስ የሰጡ ሲሆን በመጨረሻ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በኖርዌይ ለደራሲው ውድ ጊዜያቸውን ሰውተው በስደት አገር ለአገራቸው ይህንን በማበርከታቸው አርአያ ሆነውናል በሚል ልዩ ስጦታ አበርክቶላቸዋል።በመጨረሻም  ደራሲው ከአራት ልጆቻቸው ጋር በመሆን የኬክ መቁረስ ስነ-ስርዓት የተካሄደ ሲሆን የደራሲው አቶ ማተቤ መለሰ  ልጆች በጋር ይህንን የምረቃ ዝግጅት ላዘጋጁ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በኖርዌይ አባላት የምስጋና የአበባ ስጦታ አበርክተዋል።

በመፅሐፉ የፊት ገፅ ላይ እንደሚነበበው መፅሐፉን ለማዘዝም ሆነ ደራሲውን ለማግኘት የሚከተሉትን አድራሻዎች መጠቀም ይችላሉ።

ተንቀሳቃሽ ስልክ = (0047) 99850153
ኢ-ሜል = matebemelese@yahoo.com  


ጉዳያችን GUDAYACHN 
www.gudayachn.com
መጋቢት 3/2008 ዓም 

Wednesday, March 9, 2016

የኢትዮጵያ ጉዳይ ከመቼውም ጊዜ በባሰ ሁኔታ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ትከሻ ላይ ወድቋል።የችግሮቹ የመፍትሄ አካላት እነማን ናቸው? መፍትሄው ምን ይሁን? (የጉዳያችን ወቅታዊ ማስታወሻ)





ስለ አገራችን ፖለቲካ ብዙ ብዙ ተብሏል።ሁሉም ከቆመበት ጥግ እየተነሳ ዕይታውን አካፍሏል።ከእዚህ ሁሉ ጋር ግን ያለንበት ጊዜ ምን ያክል አጣዳፊ እና ኢትዮጵያን የማዳን ሥራ የአንድ ግለሰብ ወይንም መሪ ወይንም የፖለቲካ ድርጅት ጉዳይ አለመሆኑን በምን ያህል ደረጃ ተገንዝበነዋል? የሚለው ጥያቄ  ሁል ጊዜም ወሳኝ ነው።ይህ ጉዳይ የሚመለከተው በኢትዮጵያ ምድር ላይም ሆነ ውጭ  ያለ ማንኛውንም ግለሰብ፣የፖለቲካ ድርጅት፣የጦር ኃይሉን  እና የትኛውንም ማኅበረሰብን ነው።

ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት አጣብቂኝ ሁኔታ በስልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ/ህወሓት ስልጣን መንገዳገድ  እና መንገዳገዱን ተከትሎ የሚመጣው የፖለቲካ ትኩሳት ብቻ አይደለም።ወደድንም ጠላንም ኢትዮጵያን እንደ አገር እንዳትቀጥል ለዘመናት የዋተቱ ኃይሎች በከፍተኛ ከበባ ላይ ናቸው።ይህንን አላየንም አልሰማንም ብለን የምናልፈው ጉዳይ አይደለም።ይህንን ያክል የፖለቲካ ጅልነት የሚያጠቃው ኢትዮጵያዊም የለም።ችግሩ ግን እይታችን በየገባንበት ጎጥ እና ጉራጉር ጉዳይ ውስጥ ተከለለና  አጠቃላይ የሆነውን የአገሪቱን ስዕል ማየት ተስኖናል።ይህ ፅሁፍ ባጭሩ ግን አሁን ያለብን ችግር እና መፍትሄዎቹ ምን መሆን ይገባቸዋል የሚለው መሰረታዊ ነጥብ ላይ ብቻ ያተኩራል።ፅሁፉ እይታም ነውና የአንድ ዜጋ ወይንም የሕዝብ ዕይታ አካልም አድርጎ መውሰድ ይቻላል።

አሁን ኢትዮጵያ ያለችበት ችግር 

ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ወቅታዊ ግን ፈታኝ ችግር በአራት ነጥቦች መለየት ይቻላል። እነርሱም:
1/ በከፍተኛ ደረጃ በከፋፋይ ሥራ የተጠመደ መንግስት መኖር 

በውስጥ መንግስታዊ የጎጥ ፖለቲካ ሕዝቡን እና ማንኛውንም የኅብረተሰብ አካል በከፍተኛ ደረጃ በመከፋፈል ሥራ ተጠምዷል።ይህም ስልጣኔን ያስጠብቅልኛል ከሚል ስሌት ነው።በኦሮምያ እና በአማራ ክልል ያሉ ተቃውሞዎችን እንደ አደጋም እንደ በጎ አጋጣሚም  ስርዓቱ ይመለከተዋል።
አደጋው ለስልጣኑ ሲሆን መልካም አጋጣሚው ከመቼውም ጊዜ በባሰ በተዘዋዋሪ ሳይሆን በቀጥታ በህወሓት ዕዝ ስር ክልሎችን በሙሉ ለማስገባት በማሰብ ነው።የኦሮምያ በስምንት የጦር ቀጠናዎች ስር  መግባት የጋምቤላ አስተዳደር መፍረስ አሁን ደግሞ በአማራ ክልል የሚሰማው ሁሉ ይህንን ያገራግጣል።

2/ ለውጥ አለመኖሩ 

የኢትዮጵያ ሕዝብ ቀዳሚ ችግር በአሁኑ ጊዜ የለውጥ አለመኖር ነው።ባለፉት 24 ዓመታት ውስጥም ህወሓት ብዙ ጊዜ ሕዝቡን ሊያታልለው ሞክሯል።ስለሆነም በህወሓት ጥገናዊ ለውጥ ኢትዮጵያ ምንም አይነት መሻሻል እንደማታገኝ የሕዝቡ እምነት ነው።
ስርዓቱ የኢትዮጵያን ሕዝብ ገድሎታል፣አሰድዶታል፣ማንነቱን ተጋፍቷል፣አደህይቶታል፣ኑሮ አስወድዶበታል፣ሌላው ቀርቶ በከተሞች ውሃ እና መብራት መጥፋት አስመርሮት ከስርዓቱ መወገድ ጋር እንደሚፈታ የሚያምኑ ታዳጊ ሕፃናት ሁሉ ሆነዋል። ባጠቃላይ የስርዓቱ አለመቀየር የአገሪቱ ቀዳሚ ችግር ሆኖ ቀርቧል።

3/ ባዕዳን ኢትዮጵያን ከመቼውም ጊዜ የመከፋፈል አደጋ አለባት ብለው እየከበቧት ነው

ሱዳን በቀጥታ የደቡብ ሱዳን አጀንዳ ተወት አድርጋ የኢትዮጵያን ድንበር ለመውሰድ ከህወሓት ጋር ውል ጨርሳ ወደ ማካለሉ ላይ ነች።የመከላከያ ሚኒስትሩ ሲራጅ ፈርጌሳ ሱዳን ደርሰው የተመለሱት ትናንት ነው።የሱዳኑ ሱዳን ትሪቡን ጋዜጣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር  ካርቱም የመጡት መሬት ለሱዳን ስለሚሰጥበት ጉዳይ ለመነጋገር መሆኑን በድንበር ማካለል በሚል ስም በመስጠት ዘግቧል።በሌላ በኩል የአረብ መንግስታ ሳውዲ እና ዩናይትድ አረብ ኢምረት የጦር ጀት መንደርደርያ እና የጦር ካምፖችን በአሰብ እና ጂቡቲ ላይ እየገነቡ ነው።አንዳንዶቹን ጨርሰው ሰራዊት እያሰፈሩ ነው።በቅርቡ ሳውዲ አረብያ ለሱዳን ለጦር መሳርያ መግዣ የሰጠችው የገንዘብ መጠን 2 ቢልዮን ዶላር በላይ መሆኑ ከተዘገበ ገና ወራት ማስቆጠሩ ነው።(አል-ሞንተርን ይመልከቱ)

4/ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ የድሕነት ችግር ውስጥ ገብተናል 

አሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ በልቶ ማደር ትልቅ ፈተና ሆኖበታል።በዓለም ላይ እጅግ ድሃ ከሚባሉት አገራት ተርታ ነን።የተባበሩት መንግሥታት የድህነት ወለል ብሎ ያስቀመጠው አንድ ሰው በቀን 1 ዶላር 25 ሳንቲም (በቅርቡ 25 ወደ 90 ሳንቲም ጨምሯል) አንፃር ስንታይ ገና ብዙ ይቀረናል።
በእዚህ ሂሳብ ስናሰላው በወር አንድ ሰው በወር ኢትዮጵያ ውስጥ በአማካይ  1600 ብር ማግኘት ማለት ነው።ይህ በአማካይ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የወር ገቢ ሆነ ማለት በእራሱ የድህነት ወለል ነው።እኛ ግን የዓለም ባንክ ካስቀመጠው የድህነት ወለል እጅግ በጣም ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ነን። 

ይህ ሁኔታ ከሳሃራ በታች ካሉት የአፍሪካ አገራት ጋርም ሲወዳደር የኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝብ የኑሮ ሁኔታ አሁንም ብዙ ልዩነት እንዳለው ማየት እንችላለን።ይህ በእራሱ ትልቅ አደጋ አለው።የድህነት መስፋፋት የፀጥታ ችግር ያስከትላል።በሌላ በኩል ደግሞ ለነፃነቱ የሚነሳ የቆረጠ ሕዝብም ይበዛል የሚሉም አሉ።ምን ይህል ትክክለኛ መሆኑ ባይረጋገጥም።

ድህነት ሲበዛ መደማመጥ ይጠፋል፣የድህነቱ ምንጭ የማንነት ችግር ተደርጎ ይወሰድ እና ወደሌላ ምስቅልቅል ፖለቲካ ይመራል።በእኛ አገር ነባራዊ ሁኔታ ደግሞ በመንግሥትነት የተቀመጠው ስርዓት ይህንን ብሶት እንዲባባስ ከስልጣኑ መጠበቅያ መንገድ አንፃር ብቻ  ስለሚጠቀምበት በእሳት ላይ ነዳጅ የማርከፍከፍ ያክል ችግሩ ይሰፋል።

በእኛ አገር ያለው የድህነት መብዛት ብቻ አይደለም።በሀብት የናጠጡ ጥቂቶች መኖርም የሀብት ክፍፍሉን ጎድቶታል።በጎጥ፣በሙስና እና በሕገ ወጥ መንገድ ሃብታም መሆን የተለመደ የዋልጌ ባለስልጣናት መለያ ሆኗል። 

የችግሮቹ የመፍትሄ አካላት እነማን ናቸው? መፍትሄው ምን ይሁን

የችግሮቹ የመፍትሄ አካላት እነማን ናቸው?

ከላይ በዋናነት የተጠቀሱት ችግሮች ሊፈቱ የሚችሉት ችግሮቹ እና አደጋዎቹ የሁሉም መሆናቸውን ማመን ሲቻል ነው።ይህ ማለት አደጋው አንድን ሕብረተሰብ በተለየ የሚያጠቃ ሳይሆን እንደ አገር የመኖር እና አለመኖር ሁኔታዎች ላይ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው።በመሆኑም የመፍትሄ አካላት ሊሆኑ የሚችሉት የሚመረጡት እጅግ አግላይ በሆነ መንገድ ሊሆን አይችልም።በመሆኑም የመፍትሄ አካል መሆን የሚገባቸው የሚከተሉት ናቸው።
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሰራዊት ውስጥ ገብተው የሚያገለግሉ የሰራዊቱ አባላት በእየደረጃቸው፣
/ በአሁኑ ስርዓት ስር ሆነው ነገር ግን ሕዝብን እና አገርን ይቅርታ ለመጠየቅ የተዘጋጁ ባለስልጣናት፣የንግድ ሸሪኮች፣የማኅበረሰብ መሪዎች፣ምሁራን ወዘተ፣
/ ከሊቅ እስከ ደቂቅ (ከትንሽ እስከ ትልቅ) ያለ በየትኛውም የኢትዮጵያም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ ባለ ቦታ የሚኖር ኢትዮጵያዊ፣
/ በኢትዮጵያ ጉዳይ የጋራ እሳቤ ያላቸው በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ስብስቦች በሙሉ ናቸው።

መፍትሄው ምን ይሁን? 

ከላይ አሁንም ባጭሩ እንደተቀመጠው ችግሩ ሁሉንም የሚመለከት መፍትሄውም እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ የሚመለከት ነው።እዚህ ላይ የችግሩ መፍተሄ አካል አሁን ያለውን ስርዓት ሙሉ በሙሉ ማድረግ (እራሳቸውን ከህዝብ ወገን ያደረጉ በይቅርታ ወደ ሕዝብ የሚመለሱትን ሳይጨምር) በእራሱ ችግሩን የበለጠ የምያወሳስበው ነው።

ይህ የጨለመ ወይንም ተስፋ ያጣ  አስተሳሰብ ውጤት አይደለም።ባለፉት 24 ዓመታት ተሞክሮ ስንመለከት ህወሓት የመጀመርያ እና ቀዳሚ ተግባሩ በማናቸውም ወጪ እና የአገር ክስረት ቢሆን ስልጣኑን ማስጠበቅን የመጀመርያ ስራው እንጂ የአገር ጉዳይ ቀዳሚ ጉዳዩ ሆኖ አልታየም።ባህሪው አነሳሱ እና ሂደቱ ሁሉ ያሳየው ይህንኑ ነው።በመሆኑም የስርዓቱን አቀንቃኞች ትቶ ለኢትዮጵያ የሚቆመው እና የማይቆመው በቁርጥ መለየት ተገቢ ነው።ይህንን ከግንዛቤ አስገብተን መፍትሄው ሊሆን የሚችለው አንድ ብቻ ይመስለኛል። ይሄውም ለውጥ እና ለውጥ ብቻ ነው።

አንዳንዶች ለውጥ በእራሱ ይዞት የሚመጣው ምስቅልቅል ሁኔታ ስለሚኖር ወደባሰ ችግር ላይ አገሪቱ ትገባለች ብለው የሚያስቡ አሉ።በእርግጥ ለውጥ ሁሉ ካለምንም መንገጫገጭ አይመጣም።ቁምነገሩ ግን ተንገጫግጮ ቦታው ይገባል የሚለው እሳቤ ነው።አሁን ባለው ሁኔታ መፍትሄ ሲታሰብ ያሉት ሁለት አማራጮች ናቸው።እነኝህን አማራጮች ስናወዳድር ለውጥ መምጣቱ የበለጠ አማራጭ ብቻ መሆኑን እንረዳለን።

አንድኛው፣ ምርጫ ህወሓት በስልጣን ላይ የመቆየቱ አማራጭ ሲሆን ሁለተኛው፣ህወሓት በአዲስ ስርዓት የመለውጥ ሂደት ነው።

ህወሓት በስልጣን ላይ የመቆየቱ አማራጭ

የመጀመርያው አማራጭ ስናየው ለጊዜው ኢትዮጵያ ያለች ይመስለናል እንጂ ''ዱር አልባው ሽፍተኝነት'' ያጠቃው የኢትዮጵያ ሕዝብ በምንም አይነት አገርን የማዳን ሥራ ላይ ከህወሓት ጋር አይሰለፍም።ለእዚህ ብዙ ምክንያቶች ስላሉ መዘርዘሩ አያስፈልግም።ከእዚህ ይልቅ ህወሓት በስልጣን በቆየ ቁጥር ሕዝብ የችግሩ እና የድህነቱ ምክንያት  ከማንነት ጉዳይ ጋር እየያዘው ይሄድና በመጨረሻ አገሪቱ ወደ እርስ በርስ ጦርነት የመግባት አዝማምያ ያሰጋታል።

ሁሉም ለእርስ በርስ ግጭቱ የሚሰጠው ምክንያት ደግሞ ወያኔን ለማውረድ ነው ስለሚል ጉዳዩ በተለያዩ የባዕዳን እጅ የመግባት አደጋው ይሰፋል።በመጨረሻ ወያኔ እራሱ የጎጥ ፖለቲካውን ያጦዘውና (የትግራይ ሕዝብ ምን ያክል ይተባበረዋል የሚለው ጥያቄ እንዳለ ሆኖ)  ትግራይን ለመነጠል ሙከራ ያደርጋል።ይህ እንግዲህ የአገሪቱ ሀብት በሙሰኛ ባለስልጣናት እና ባዕዳን የመዘረፍ ጉዳይ ሁሉ እንደቀጠለ ማለት ነው።በመጨረሻ ኢትዮጵያን የከበቡት ኃይላት በማናቸውም ጊዜ አገሪቱን በቀላሉ ከፋፍለው የማዳከም  አመቺ ጊዜ እንዳገኙ ያስባሉ። ህወሓት በስልጣን ላይ መቆየት ከቻለ መጪው ጊዜ ከእዚህ ያነሰ አይሆንም።ስርዓቱ የገባበት ቅራኔ በሙሉ ሳይፈታ እና የቅራኔው መነሻ ከስልጣን ሳይወርድ የኢትዮጵያን ህልውና ማስጠበቅ ፈፅሞ አይታሰብም።ሕዝብ እንጂ ግለሰቦች አገር አያድኑም።የኢትዮጵያ ሕዝብ አገሩን በባለቤትነት እንዲያድን ይህ ስርዓት ከስልጣን መውረድ አለበት።ከእዛ መለስ ግን ህወሓት ብሔራዊ ሕብረት የሚያመጣበትም ሆነ ስልጣኑን ሕጋዊ መሰረት ለማስያዝ ምንም የቀረው ጥይት የለም።በሕዝብ ዘንድ የመንግስት ሕጋዊነት (legitimacy) በእዚህ ያህል ደረጃ ከወረደ በኃላ ለመጠገን መሞከር ትርፉ የሚፎረፎተው ፍርስራሽ አይን ውስጥ እየገባ አይን እንዲያጠፋ ከማድረግ በቀር ምንም ትርፍ የለውም።ይህንን ከስርዓቱ ጋር እየሰሩ ያሉ በሙሉ ሊረዱት የሚገባ ሀቅ ነው። 

ባጭሩ የህወሓት በስልጣን ላይ መቆየት በአማራጭነት የማይቀርብ ይልቁንም ኢትዮጵያ በዘመኗ አይታ ወደማታውቀው የእርስ በርስ ግጭት የሚመራት መሆኑ መታወቅ አለበት።ይህ ሁኔታ ደግሞ እንደ አገር ሉዓላዊነቷን ለማስጠበቅ የማትችል ወደ ማድረግ የሚመራት አሁንም በስልጣን ላይ ያለው ቡድን የታቀደ የመከፋፈል እና የማጋጨት ሥራ ነው።

ለውጥ 

ሁለተኛው እና እንደ እኔ ብቸኛው አማራጭ የምለው በኢትዮጵያ አፋጣኝ ግን የሁሉም ህብረት የታየበት ለውጥ ማምጣት ነው።ለውጥ ጊዝያዊ  የኃይል ክፍተት፣የህዝብ አለመረጋጋት፣ የአካባቢ እና ዓለም አቀፍ መድረኮች የመደመጥ አቅም መቀነስ ወዘተ ያጋጥሙታል።ለእዚህም ነው ከላይ የመፍትሄ አካላት መሆን የሚገባቸው ተብሎ የኢትዮጵያ ጦር ኃይል እና ሕዝብ ይቅርታ የጠየቁ የስርዓቱ አካላት የለውጡ አካል እና ኢትዮትጵያን የማዳን ድርሻ አላቸው የተባለው።ስለዚህ የኃይል ክፍተት የፖለቲካ ፓርቲዎች ሥራ ብቻ ሳይሆን የጦር ኃይሉም ተግባር ነው።

ሰራዊቱ ከየትም የመጣ ሳይሆን  አሁንም ከኢትዮጵያ ሕዝብ የወጣ እና በየቦታው የሚነሱ ግጭቶች ሰለባ ስለሆነ  ችግሩ  የአገሪቱ ችግር የሚመነጨው ከመሪዎቹ እንደሆነ ይገነዘባል።ለውጥ መምጣቱ የአገራችን ችግር በጋራ መነጋገር ይስችላል፣ከልዩነታችን ይልቅ ሕብረታችንን የሚያሳዩን የመገናኛ ብዙሃን ይኖሩናል፣ ከሁለት ሚልዮን በላይ የሚገመተው በውጭ የሚኖር ኢትዮጵያዊ ለአገሩ የጋራ ጉዳይ የመስራት ዕድል ይኖረዋል፣የአገሪቱ ምጣኔ ሀብት በበለጠ ይነቃቃል፣ በኢትዮጵያ ላይ ከባዕዳን ጋር በማበር የሚያሴሩት በግልፅ ለሕዝብ ይጋለጣሉ፣ ሕዝብ በእራሱ የመለያየት ፖለቲካ አራማጆችን ከአገራዊ ፖለቲካ አራማጆች የመለየት ዕድል ስለሚያገኝ የመወሰን አቅሙን ያሳያል።

ይህ ሁሉ ሁኔታ ህወሓት በስልጣን ላይ ሆኖ ህዝቡ በመታፈኑ ሳብያ የሚመጣው አደጋ ጋር ሲነፃፀር ለውጥ የሚያመጣው አንድነት እና ህብረት የበለጠ የአገሪቱን አንድነት የማምጣት አቅም ይኖረዋል። እዚህ ላይ ብዙዎች በሌላ አገር ያሉ ተሞክሮዎችን በማንሳት ከአምባገነን መሪዎች በኃላ መከፋፈል እንደሚኖር ሊሰብኩ ይሞክራሉ።ይህ ግን እንደ ኢትዮጵያ ላለ የእረጅም ጊዜ ማኅበራዊ መስተሳስር ላለው ሕዝብ አይሰራም።እርግጥ ነው ይህ ማለት ማኅበራዊ መስተሳሰር በእራሱ ተአምር አይፈጥርም። ትውልድም ተቀይሯል።ስለሆነም የምሁራን አስተዋፅኦ በጣም ይፈለጋል።በዝምታ የእራስን ኑሮ እየኖሩ ከንፈር መምጠጥ በእራሱ ኢትዮጵያን ከመግደል አይተናነስም።


ባጠቃላይ ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ እንደ ውሃ ጠብታ ቀስ እያለ እየሸረሸራት ነው። ችላ ብሎ ወይንም ዝም ብሎ የሚኖረው ሕዝብ እጣው እና ህይወቱ ከአገሩ ጋር መያያዙን ማመን አለበት።በተለይ ምሑራን ቢያንስ ለአገራቸው እና ለሕዝባቸው አዳዲስ ሃሳቦች ከማፍለቅ አንስቶ የኑሮ መደላድላቸውን ብቻ እየተመለከቱ ከመኖር ባለፈ ለኢትዮጵያ ምን ላድርግ ማለት አለባቸው።ምንም እንዳልተፈጠረ ዝም ማለት በእራሱ በገዛ አገር ላይ የሚፈፀም የፀጥታ አሰቃቂ ወንጀል ነው።ኢትዮጵያ ከሌላ አገር ትለያለች።አምባገነኖች መጥተዋል፣አምባገነኖች ሄደዋል። ኢትዮጵያ ግን በሕዝቧ አስተዋይነት እና በእግዚአብሔር መሪነት ከብዙ ፈተና ድናለች።ወደፊትም ትድናለች። ለአገር ብዙ ሃሳብ እና አቅም ያላችሁ ግን ከእየተደበቃችሁበት የምትወጡበት ጊዜ አሁን ነው። የኢትዮጵያ ጉዳይ ከመቼውም ጊዜ በባሰ ሁኔታ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ትከሻ ላይ  ወድቋል።እያንዳንዷ ቀን ለኢትዮጵያ ወሳኝ ነችና።

ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com
የካቲት 30/2008 ዓም 

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።