ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, March 29, 2016

በኢትዮጵያ የወደፊት አቅጣጫ ላይ የመከረው ስብሰባ ተጠናቀቀ The future of Ethiopia, discussions on the roadmap for post TPLF Ethiopia


 eNGLISH VERSION IS ATTACHED BELOW 

ኢሳት (መጋቢት 19 ፥ 2008)

በቪዥን ኢትዮጵያና ኢሳት በዋሽንግተን ዲሲ ጆርጅ ታውን መሪየት ሆቴል ከማርች 26-27 2016 የተዘጋጀውና በኢትዮጵያ የወደፊት ሁኔታ በለውጥ፥ ዲሞክራሲና፣ የብሄራዊ አንድነት ላይ የሚመክር ስብሰባ በስኬት መጠናቀቁን የስብሰባው አዘጋጆች ገለጹ። በስብሰባው የኢትዮጵያ የወደፊት አቅጣጫ የሚመለከቱ ጉዳዮች የተዳሰሱበት ሲሆን በርካታ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ምሁራን፣ የሲቢክ ድርጅቶች እና የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጥናታዊ ጽሁፎቻቸውን ያቀረቡበትና የተሳተፉበት እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
ፕሮፌሰር ጌታቸው በጋሻው የመግቢያ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ በኮንፈረንሱ አንኳር አንኳር አገራዊ ጉዳዮች እንደሚነሱ ሃሳባቸውን አንስተዋል። በኢሳትና በቪዥን ኢትዮጵያ ትብብር ተዘጋጅቶ በነበረው በዚሁ ኮንፈረንስ ከተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት የተወከሉ ምሁራን በኢትዮጵያ ወቅታዊና የወደፊት አቅጣጫ ዙሪያም ሰፊ ውይይትን አካሄደዋል።
ከተለያዩ የሲቪክና የሰብዓዊ መብቶች እንዲሁም የእምነት ተቋማት የተወከሉ ተጋባዥ እንግዶች በኢትዮጵያ ዴሞክራሲና የተረጋጋ ሰላምን ማምጣት በሚቻልበት ዙሪያ የመከሩ ሲሆን፣ ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመፍጠርም ብሄራዊ እርቅና ብሄራዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
የአፍሪካ ሃገራትን ተሞክሮ በዋቢነት በማንሳት ለታዳሚ ገለጻን ያደረጉት ፕሮፌሰር አቻምየለህ ደበላ፣ በአህጉሪቱ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ መንግስት አይነት ምርጫ አድርጎ መቶ በመቶ አሸንፌያለሁ ብሎ ያወጀ መንግስት እንደሌለ አውስተዋል።
በጋና በናይጀሪያና በሌሎች ሃገራት በትምህርት ቆይታቸው የታዘቧቸውን ፖለቲካዊ ጉዳዮች ለኮንፈርነሱ ያካፈሉት ፕሮፌሰር አቻምየለህ፣ በሌሎች የአህጉሪቱ ሃገራት ፖለቲካዊ ለውጦች መታየት ቢጀምሩም በኢትዮጵያ ያለውን አካሄድ ግን ገና ብዙ የሚቀረው እንደሆነም አስረድተዋል።
በኒው ዮርክ ሲቲ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር የሆኑት ፕሮፌሰር ጆን ሀርብሰን በበኩላቸው, በኢትዮጵያ ከ1960 የአብዮት ፍንዳታ ጀምሮ ሃገሪቱን ዴሞክራሲያዊ ሊያደርጉ የሚችሉ አራት እድሎች ሳይሳኩ መቅረታቸውን ገልጸዋል።
በግንቦት 1977 የተካሄደው ብሄራዊ ምርጫ ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ ትግሎችን ያወሱት ፕሮፌሰር ሀርብሰን፣ ከኢትዮጵያ ጋር በሽብርተኛ ዙሪያ ትብብር ያላት አሜሪካ በሃገሪቱ ዴሞክራሲ እንዲያብብ ትብብር ማድረግ እንዳለባት ባቀረቡት ገለጻ አመልክተዋል።
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ግንባት የስራ አስፈጻሚ አባል የሆኑት ሌንጮ ባቲ፣ በመንግስት የሚፈጸሙ የኢሰብዓዊ ድርጊቶች በዝርዝር ካስረዱ በኋላ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት በመሆን በስልጣን ላይ ያለውን ኢህአዴግ መስወገድ እንዳለበት ተናግረዋል።
በሃገሪቱ እየተፈጸሙ ስላሉ ኢሰብዓዊ ድርጊቶች ሰፊ ሪፖርትን ያቀረቡት አቶ ነዓምን የኢህአዴግ መንግስት ፌዴራላዊ፣ ዴሞራሲያዊ ወይም ሪፐብሊክ ተብሎ ሊፈረጅ እንደማይችል አክለው ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የወደፊት ጉዳይ የሚመክረው ስብሰባ እሁድ እለትም በዚሁ በማሪየት ሆቴል ቀጥሎ የዋለ ሲሆን፣ በትግሉና በግጭት አፈታት እና ለዲሞክራሲ፣ አንድነት ዙሪያ ሴቶች የሚጫወቱት ሚና በሚል መድረክ ውይይት ተካሄዶበታል።
በሃዋርድ ዩንቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ ተማሪ የሆነችው ወ/ሪት ኤልሳቤጥ ላቀው ወደአሜርካ የፈለሱ አፍሪካውያን ሴቶችን ጉዳይ ከኢትዮጵያውያን ትግል አንጻር ትንተና ሰጥታለች። በመቀጠልም በኖርዌይ ሃገር የሚኖሩት ወ/ሮ ሰዋሰስ ጆሃንሰን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲንና ነጻነትን በኢትዮጵያ ለማምጣት በአንድነት መታገል እንዳለባቸውና ካወሱ በኋላ፣ አዲሲቷን ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ በመጀመሪያ እርቅ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አስምረውበታል። በመቀጠል የተናገሩት በፍራንክፈርት የሚኖሩት የሰብዓዊ መብት አቀንቃኝ ወ/ሮ አሳየሽ ታምሩ ሲሆኑ፣ በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በአገር ውስጥ ለሚሰቃዩ ኢትዮጵያውያን ሴቶች አጋርነታቸውን ማሳየት እንዳለባቸው ተናግረዋል። ወ/ሮ አሳየሽ፣ “ለልጆቻችን ማውረስ ያለብን ነጻነትን ነው” ሲሉ ተደምጠዋል። በዚህ ፓነል መጨረሻ ላይ የተናገሩት በዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ሴቶች የሰብዓዊ መብት አቀንቃኝ ወ/ሮ ወሰን ደበላ ሲሆኑ፣ 51% የሚሆነውን የኢትዮጵያን የሚሸፍኑት ሴቶች ቢሆኑም፣ በአገራዊ ጉዳይ ተሳትፏቸው ግን እጅግ ዝቅተኛ ነው ብለዋል። ወ/ሮ ወሰን የኢትዮጵያ ሴቶች በአገራዊ ጉዳዮች ላይ እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል። ፓነሊስቶቹ የኢትዮጵያ ሴቶች ድምጽ እንዲሰማ ቪዥን ኢትዮጵያና መድረኩን በማመቻቸታቸው አመስግነዋቸዋል።
እሁድ ከሰዓት በኋላ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ለመዳሰስ ስብሰባ ተካሄዷል። ስብሰባውን የመሩት አቶ ግዛው ለገሰ ናቸው። በመጀመሪያ ጥናታዊ ጽሁፋቸውን ያቀረቡት አቶ ኤርሚያስ ለገሰ ሲሆኑ፣ በፓርቲዎችና በማህበረሰብ (ኮሚኒቲ) አባላት መካከል መተባበር አለመኖር ለለውጥ ከፍተኛ እንቅፋት እንደሆነ ተናግረዋል። ለአጭር ይሁንም ለረጅም ጊዜ የጋራ ግብ በእነዚህ የማህበረሰብ አባላትና ፓርቲዎች መካከል በመተማመን ላይ የተመሰረተ ትብብር እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል። ዶ/ር መስፍን አብዲ በመሬት ጉዳይ ዙሪያ ትንተና ሰጥተዋል። በህወሃት አገዛዝ መሬት የገበሬዎች ሆኖ እንደማያውቅና ከመሬት ይዞታ ጋር የተያያዙ አያሌ ያልተመለሱ ጥያቄዎች እንዳሉ ተናግረዋል።
አሁን ያለችዋን ኢትዮጵያ በማስመልከትም ያለፈው ታሪክ ሆኖ ያለፈ በመሆኑ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ሁሉም በእኩል አይን የሚታይባት አገር መሆን ይኖርባታል ብለዋል። ከዚህ ጋር በማያያዝም ኦሮምኛ የኢትዮጵያ የስራ ቋንቋ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል። የኦሮሞና የአማራ ልሂቃንም በሁለቱ ህዝቦች መካከል መተማመን እንዲኖር እንዲሰሩ እንዲሰሩ ጠይቀዋል።
በመሬይ ስቴት ዩንቨርስቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ሰይድ ሃሰን በመሬት ነጠቃና ሙስና ላይ ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል። ፕ/ር ሰይድ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሙስና በአለም ላይ ከታዩት ሙስናዎች ለየት ያለ ነው ብለዋል። መሬት የስልጣን ምንጭ በመሆኑ የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት መሬት ነጠቃውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተንብየዋል። ሁሉም የኢትዮጵያ ተደራሽ አካላት ይህ ዘርፈ-ብዙ ውስብስብ ችግር ለመፍታት ተቀራርበው መነጋገር እንዳለባቸው ተናግረዋል።
በኬተሪንግ ዩኒቨርስቲ የታሪክ ምሁር የሆኑት ፕሮፌሰር እዝቅኤል ገቢሳ፣ የዲሞክራሲ፣ የእድገት፣ የሰብዓዊ መብት፣ የሰላም ማስፈን እሴቶችን ከውስጣችን መመልከት እንዳለብን የሚተነትን ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ ወደ ዲሞክራሲ የምትሻገርበትን ብዙ እድሎችን ያጣችበትን አጋጣሚ የተነተኑት ፕሮፌሰር እዝቅኤል፣ ኢትዮጵያውያን ህወሃት ኢህአዴግን ከማስወገድ ባለፈ የወደፊት እቅድ ሊኖራቸው እንደሚገባ አስረድተዋል። ፕሮፌሰር እዝቅኤል በገዳ ስርዓትና በኦሮሞ እሴቶች ላይ ትንተና ሰጥተዋል።
“ከዚህ በኋላ ወዴት? ያልተመለሱ ጥያቄዎች!” የሚለው የመጨረሻው ስብሰባ የተመራው በኮሎራዶ ሜትሮፖሊታን ስቴት ዩንቨርስቲ መምህር በሆኑት በፕሮፌሰር ሚንጋ ነጋሽ ነው። ለዲሞክራሲ፣ ለለውጥና ለአንድነት ምን መደረገ እንዳለበት የመከረው ይኸው ስብሰባ፣ ኢትዮጵያ በአስቸኳይ ለውጥ የሚያስፈልጋት አገር እንደሆነች ተናግረዋል። የኢትዮጵያውያንን ህይወት የዳሰሰ በምስል ያሳዩት ፕሮፌሰር ሚንጋ፣ ኢትዮጵያ የሰላም፣ የዲሞራሲና የብልጽግና አቅጣጫ (Roadmap) ያስፈልጋታል ብለዋል። በመሆኑንም ከኤርትራ ጋር ያንዣበባት የጦርነት አደጋ፣ በኦሮሚያ፣ ኮንሶ፣ አማራ፣ ሶማሌ እና ጋምቤላ አካባቢዎች የሚታየው ግጭት ኢትዮጵያን ከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደከተታት ተናግረዋል። ከህወሃት/ ኢህአዴግ መወገድ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚተገበር አቅጣጫ መቀመጥም እንዳለበት ፕሮፌሰር ሚንጋ ተናግረዋል።
ፕሮፌሰር ተሾመ ከበደ በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለው ብጥብጥ የመንግስት የስልጣን ምንጭ እንደሆነ ለተሰብሳቢው ተናግረዋል። ፕሮፌሰር ተሾመ ኢትዮጵያ የዲሞክራሲ እሴቶችን የምታከብር፣ በሉዓላዊነቷ የማትደራደር አገር እንድትሆን ማድረግ ሃላፊነት እንዳለብን ለታዳሚው ተናግረዋል። ሕወሃት/ኢህአዴግን በተመለከተ ሙሉ በሙሉ እንዲደመሰስ ማድረግ ሳይሆን ዲሞራሲያዊ እሴቶችን እንዲቀበል ማስገደድ እንዳለብን ተናግረዋል። “አገራችን ችግር ላይ ናት፣ የእኛን እርዳታ ትሻለች” ሲሉ ለተሰብሳቢው ተናግረዋል።
ከዚህ ቀጥሎ የተናግሩት  የህግ ባለሙያና የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባት አባል የሆኑት ዶ/ር በያን አሶባ ሲሆኑ፣ ያለፉትና የአሁኑ አምባገነን መንግስታት በህዝቦቻችን ላይ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውን ተናግረዋል። ሌሎች ኢትዮጵያውያን በኦሮምያ እየተከሰተ ያለውን ህዝባዊ እንቅስቃሴ በጥርጣሬ መመከታቸውን ትተው እንዲደግፉት ጥሪ አቅርበዋል።
በካሊፎርኒያ ግዛት ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማሪያም የአምባገነን መንግስታት ባህሪ ነገሮችን መደበቅ ነው ብለዋል። በመሆኑም ህወሃት ኢህአዴግ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳይታወቅበት ኢሳትን በብዙ ሚሊዮን ብር በመክፈል በተደጋጋሚ በሞገድ ለማገድ መሞከሩን ለተሰብሳቢው ተናግረዋል። ሆኖም ህወሃቶች ለሰሩት ጥፋት ሁሉ ተጠያቂ የሚሆኑበት ጊዜ ሩቅ እንዳልሆነ ለተሰብሳቢው ገልጸዋል። ለዲሞክራሲና ለእኩልነት የሚደረገው ትግልም ህወሃት/ወያኔ ኖረም አልኖርም መቀጠሉ አይቀሬ መሆኑን አስረድተዋል። አዲስ አቅጣጫ የሚያመላክት ህገ-መንገስትም መዘጋጀት እንዳለበት ተሰብሳቢውን መክረዋል።
በመጨረሻ የቀረቡት በዳይተን ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር መሳይ ከበደ ናቸው። የተሻለው አቅጣጫ አሁን ያለውን በዘውግ የተከለለውን አስተዳደር መከተል መሆኑን አስመረው፣ ኢህአዴግ ቢወገድም የዘውግ ጥያቄ በቀላሉ የሚጠፋ አለመሆኑን ገምተዋል።
ከቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፎች በሁላ በርካታ ጥያቄዎች ለተሰብሳቢዎች የቀረቡ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ከመድረክ መልስ ተሰጥቶባቸዋል። አንዳንድ ያልተመለሱ ጥያቄዎች ወደ ፊት በሚካሄዱ ስብሰባዎች እንደሚነሱ ለማወቅ ተችሏል።

Scholars, politicians, civil society representatives share views on the future of Ethiopia, discuss roadmap for post TPLF Ethiopia

ESAT News (March 28, 2016)
Ethiopian scholars, politicians and representatives of civil societies and women gathered in Washington, DC for a two day conference on the future of Ethiopia: transition, democracy and national unity organized by vision Ethiopia.
Representing Patriotic Ginbot 7 for Unity and Democracy, Neamin Zeleke, a member of the leadership said the TPLF Federal Democratic Republic is neither federal, nor democratic, nor republic.
He said the recent uprising by the people in the Oromia region was evidence that the Federal system by the TPLF was not designed to benefit the people. The popular uprising in different parts of Ethiopia show federalism, as designed by the TPLF, did not give rights to the people, Neamin said.
He spoke at length on the human rights abuses in Ethiopia perpetrated by the TPLF. Neamin said the minority government is not to be reformed but to be removed. He said he does not believe the tyrannical government would be removed through peaceful political struggle. Armed struggle, among other forms of struggle, is crucial to remove tyranny from Ethiopia, he stressed.
Lencho Bati, member of the executive committee, Oromo Democratic Front spoke on the need to create a national and common discourse that bring together all political organizations. Lencho said the regime cannot call itself developmental state as a state to be called developmental should be legitimate and accepted by the poeople, which the TPLF is not. The bureaucracy is not free from political pressure and appointment of administrative positions is not based on merit but political assignment. He said Ethiopians should politically, militarily and using all available means work to remove the tyrannical regime in Ethiopia.
Prof. John Harbeson, Professor Emeritus of political science at City University of New York said Ethiopia had missed at least four opportunities to establish a democratic state: 1974 revolution, the fall of the Dergue in 1991, the constitution assembly of 1994 and the historic election of 2005. Prof. Harbeson said in all the four case, Ethiopia’s opportunity to make a transition to democracy was squashed.
He also said the US, while fighting terrorism, should also help promote democracy.
Professor Minga Negash, Professor of Accounting, Metropolitan State University of Denver, Colorado and the University of the Witwatersrand, Johannesburg, South Africa said Ethiopia needs a transformation, which is not only changing the government, but also a roadmap after post-EPRDF Ethiopia.  The conflict with Eritrea, popular uprising in Konso, Oromia, Amhara, Somali, Gambella need to be dealt carefully, Minga said.
Another panelist, Professor Teshome Abebe Former Provost and Academic Vice President, Eastern Illinois University and Professor of Economics, Illinois said that chaos has become the source of power for the ruling party in Ethiopia. Prof. Teshome underscored that there should be a consensus that Ethiopia should have “unflinching respect for democratic values and its sovereignty should not be questioned.” Instead of completely annihilating TPLF, Prof. Teshome said, TPLF has to be reformed to unequivocally embrace democratic principles. Teshome said, “Our country is in distress and needs our attention.”
Dr. Beyan Asoba, Lawyer and Human Rights Advocate and Member of the Oromo Democratic Front, said the current and previous regimes have committed gross human rights violations in the country. He said Ethiopians should see the protest in the Oromia region as a struggle for democracy and good governance, not as a threat to the nation.
Alemayehu Gebremariam, Professor of Political Science, California State University, San Bernardino, Attorney at Law, and weekly blogger on Huffington Post spoke about the dictatorial regime in Ethiopia. He said one of the characteristics of dictators is their secrecy. Prof. Alemayehu elabotated on why the Ethiopian government is spending millions of dollars to jam ESAT.  Prof. Alemayehu said sooner or later time will tell when TPLF will be held responsible for atrocious actions it committed on the people of Ethiopia. He stressed that whether the TPLF regime exists or not, the quest for democracy and respect for human rights will continue. According to Prof. Alemayehu, the roadmap for new Ethiopia is a new constitution.
Messay Kebede, Professor of Philosophy, University of Dayton, Ohio elaborated on ethnicity and power. Prof. Mesay said the way forward is to recognize the current ethnic based regional administrations. He said ethnic politics will not fade away even if TPLF is removed from power.
Ermias Legesse, former minister d’état of government communications, author, and human rights advocate said there is lack of cooperation among Ethiopian political parties and civic groups. Ermias called on the different political and civic organizations to cooperate for common, long and short-term goals. He said the cooperation among these groups should be built on a solid foundation of trust.
Dr. Mesfin Abdi, former lecturer at Addis Ababa University and researcher, presented a paper on land tenure and language issues in Ethiopia. He said, currently, the land does not belong to the farmers; and there are several unresolved questions.
Dr. Mesfin elaborated on the need to make Oromiffa as one of the working languages in Ethiopia. He said Amhara and Oromo elites should devise a mechanism to build a solid pillar of trust for the benefit of all nations in the country.
Seid Hassan, Professor of Economics, Murray State University, Kentucky, presented a paper on land grabs and state capture in Ethiopia.  According to Prof. Seid, the worst corruption in the world is practiced in Ethiopia. The scholar said the TPLF/EPRDF government would continue the land grab, for the land is the only source of power and survival for the TPLF regime. The current problem in Ethiopia is multifaceted and all stakeholders should come together to devise mechanisms to mitigate it, he said.
Professor Ezekiel Gebissa:  Professor of History, Kettering University, Michigan, and President Elect, Oromo Studies Association presented a paper on the theme: “Time to Look Inward: Harnessing Indigenous Asset and Resources for Democracy, Development, Human Rights and Peace Building.” Prof. Ezekiel discussed on the chances Ethiopia missed for its transition to democracy. He said we should have a plan for the country beyond overthrowing the TPLF regime. Prof. Ezekiel gave an elaborated speech on Gada System and Oromo values in Oromo society.
Ms. Elsabet Lakew a Political Science Student at Howard University and Organizer at Montgomery County Civil Rights Coalition, spoke about diaspora women in relation to their root. Elisabet related the struggle for democracy and human rights in Ethiopia to the “Black Lives Matter” in the United States.
Ms. Sewasew S.Johannessen, Manager, The Ark of The New Covenant Healing Ministry, Norway, requested all Ethiopians to come together to bring democracy and freedom in Ethiopia. Sewasew urged all Ethiopians work for reconciliation if they wish to see democratic Ethiopia.
Mrs. Asayesh Tamiru, human rights advocate, Frankfurt, who said humanity knows no boundaries urged diaspora Ethiopians show solidarity with women in Ethiopia. She said, “We should feel the pain of our people in Oromia, Somalia, Gambella- allover Ethiopia.” She underscored, “If we must inherit anything to our children, it is freedom!”
Ms. Wessen Debela, Human Rights Advocate and member of Center for Rights of Ethiopian Women (CREW), Washington, DC said though Ethiopian women intellectuals participate less in the affairs of the country. Ms. Wessen urged all women to participate in every aspect of socio-political life if they need to see a vibrant, prosperous Ethiopia.
Ms. Sewasew S.Johannessen, Manager, The Ark of The New Covenant Healing Ministry, Norway, requested all Ethiopians come together to bring democracy and freedom in Ethiopia. Sewasew urged all Ethiopians work for reconciliation if they wish to see democratic Ethiopia.
Mrs Asayesh Tamiru, Human Rights advocate, Frankfurt, said humanity knows no boundaries. Ms Asayesh said the diaspora Ethiopians must show solidarity for women in Ethiopia. She said, “we should feel the pain our people are facing in Oromia, Somalia, Gambella- allover Ethiopia.” She reiterated, “If we must inherit anything to our children, it is freedom!”
Ms. Wessen Debela: Human Rights Advocate and member of Center for Rights of Ethiopian Women (CREW), Washington, DC said though Ethiopian women intellectuals are more than 51% of the population, they participated less in the affairs of the country. Ms Wessen urged all women to participate in every aspect of socio-political life if they need to see a vibrant, prosperous Ethiopia.

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...