ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, March 2, 2016

ገጣሚና ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) ዛሬ ምሽት በማኅበራዊ ድረ-ገፁ የለቀቀው ግጥም አስተማሪ ነው።

ገጣሚና ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ)  

እንደምን አመሻችሁ ውዱ ወዳጆቼ ፥ቆየት ካሉ ግጥሞቼ አንዱን እነሆ ፦

ጎራው ያለ እደሆን ባራምባራስ ደስታ
ዛራፍ ያለ እንደሆን ባራምባራስ ደስታ
ጠላት ይጠፋዋል መደበቂያ ቦታ።
ፊት አውራሪ ፍላቴ
ግራ አዝማች በሃፍቴ
አዛዥ ለጥ ይበሉ
ቀኝ አዝማች በአካሉ
ዣንጥራር ባያለው
ደጃዝማች እንዳለው
እንዲህ ነው ካልቀረ አንጀት አርስ ሹመት
ለድል የሚያበቃ ጦር ይዞ ቢዘመት።
የጣልያን ጄኔራል ኮኮቡን ደርድሮ
በሊጋባሞ ዜር ስንት አሳሩን ቆጥሮ
ድል አድርጎት የኛ ሰው ፎክረን በኩራት እንደተመለስን
ስልጣኔ መስሎን የሱን ስም ወረስን።
ማቹ ጄኔራል ነው ገዳይ ፊት አውራሪ
ስም እንዴት ይዋሳል ደፋር ሰው ከፈሪ
በጠላት ሬሳ ላይ ቆመን እያቅራራን
በድላችን ማግስት የኛን ሹመት ንቀን ከ ሆንን ኔተራል
ባናውቀው ነው እንጂ የዛን ቀን ሙተናል።
ኮኔሬል አይበሉን ያገሩን አርበኛ
ጄኔራል አይበሉን ያገሩን አርበኛ
ፈረንጅ አደለንም ሀበሻ ነን እኛ።
የሞች ስም አደለም የገዳይ ሰው ምሱ
በደም ተበላሽተዋል ባለ ኮከብ ልብሱ
ገድየው ሳበቃ ባስታጠቁኝ ወኔ
በሱ ስም አይጥሩኝ ቆሞ እንዲሄድ በኔ
ጄኔራል ድል ሆኖ ስላለፈች ነፍሱ
ይበሉ ጃንሆይ ሹመቴን መልሱ።
ፊት አውራሪ ካታካምቦ
ሊጋባ ዴሊቦ
አዛዥ ለጥ ይበሉ
ቀኝ አዝማች አካሉ
ዣንጥራር አበጋዝ
እንዲህ ነው አንጀት አርስ ሹመት
ለድል የሚያበቃ ጦር ይዞ ቢዘመት
ፍቃድዎ ከሆነ ግርማዊ ተፈሪ
እንዳገሬ ሹመት በሉኝ ፊት አውራሪ
በሞች ከመጠራት ስለ ሚሻል እሱ
ይበሉ ጃንሆይ ሹመቴን መልሱ።




ጉዳያችን GUDAYACHN 

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...