ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, July 30, 2022

በእዚህ ሳምንት ውስጥ በውጭው ዓለም የተዘገቡ አገርቤት ትኩረት ያላገኙ ኢትዮጵያን የተመለከቱ 8 መልካም ዜናዎች

የለገዳዲ የመጠጥ ውሃ ግድብ ዕድሳት ስምምነት ሲፈረም 

ከ50 ዓመታት በላይ እድሳት ያልተደረገለት የአዲስ አበባ ለገዳዲ የመጠጥ ውሃ ግድብ በንጉሱ ጊዜ በሰራው የጣልያን ኩባንያ ለመጪዎቹ 50 ዓመታት እንዲያገለግል ተደርጎ ሊስፋፋ ነው።

የዓለም ባንክ በሰጠው 11 ሚልዮን ዶላር በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ጊዜ የተገነባው እና ለ50 ዓመታት እንዲያገለግል ተደርጎ የተሰራው የለገዳዴ የመጠጥ ውሃ ግድብ ቀድሞም በሰራው የጣሊያኑ ሳሊኒ ኩባንያ በሚደረግለት ዕድሳት ለቀጣይ 50 ዓመታት በተጨማሪ እንዲያገለግል ብቻ ሳይሆን ተጨማሪ ግድቡ አዳዲስ የማስተንፈሻ እና ዘመናዊ የማጣርያ መሳርያዎች የሚገቡለት ይሆናል።የግድቡ እድሳት በ18 ወራት የሚጠናቀቅ ሲሆን ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት የአዲስ አበባ አስተዳደር ከሳሊኒ (አዲሱ ስሙ እንገነባለን ''ዊ ብዩልድ'' ብሎ ቀይሯል) ጋር ስምምነቱን ሲፈራረም የአዲስ አበባ ውሃናፍሳሽ ባለስልጣን ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘሪሁን አባተ እንዳሉት ይህ እድሳት የግድቡ የውሃ የማቅረብ  አቅሙን በቀን በሠላሳ ሺህ ኩቢክ ሜትር ያሳድገዋል።

''ኢትዮጵያ ታሪክ እየሰራች ነው።አየርመንገዷ በአፍሪካ ያልገባ ኤር ባስ ኤ 350-1000  (Airbus’ A350-1000 aircraft) ገዝታለች '' ትራቭልራዳር
ኤር ባስ ኤ 350-1000

ሓሙስ ዕለት ትራቭል ራዳር ኢትዮጵያ ታሪክ እየሰራች ነው በሚል ርዕስ ያወጣው ዜና ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በእዚህ ግዢው የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከፈረንሳይ እና ከቻይና አየር መንገድ ጋር ከስድስቱ ግዙፍ አየርመንገዶች ተርታ ያሰልፈዋል ይላል።ዜናው አክሎም የኤርባስ የአፍሪካ እና የመካከለኛው ምስራቅ ዳይሬክተር ሚካኤል ሆአሪ  (Mikail Houari) ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ጠንካራ አጋርነት መፍጠራቸው እንዳስደሰታቸው መግለጻቸውን ጠቅሶ አየር መንገዱ በቴክኖሎጂ የተራቀቀውን ኤር ባስ ኤ 350 በመግዛት ከአፍሪካ ቀዳሚ አየርመንገድ ያደርገዋል ብለዋል ብሏል።

ኢትዮጵያ ሦስተኛውን የዓባይ ግድብ በያዝነው ክረምት እንደምትሞላ ለግብጽ መልዕክት ልካለች

ኢትዮጵያ በእየዓመቱ የዓባይን ግድብ ስትሞላ ኦፊሽያላዊ ደብዳቤ ለታችኞቹ ተፋሰስ አገሮች ማለትም ለግብጽ እና ለሱዳን በደብዳቤ እያሳወቀች ነበር። ዘንድሮም ሦስተኛውን የዓንባይ ግድብ እንደምትሞላ ግልጽ ደብዳቤ ከኢትዮጵያ እንደደረሳት ግብጽ መግለጿን  የዘገበው ''ኢጂፕት ኢንዲፐንዳንት '' የተሰኘው ጋዜጣ በያዝነው ሳምንት ውስጥ ነው።ይህንኑ የገለጹት የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሽኩሪን ኢትዮጵያን ለተባበሩት መንግስታት ለመክሰስ በጻፉት ደብዳቤ ላይ ኢትዮጵያ ውሃውን እንደምትሞላ በግልጽ ነግራናለች ብለዋል። ሚኒስትሩ የመንገሯን ጨዋነት ግን ማድነቅ አልፈለጉም።

የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ለኬንያ ሁለተኛው ግዙፍ የመብራት ኃይል አቅራቢ ሆነ



ይህንን የዘገበው የኬንያው ስታር ጋዜጣ በያዝነው ሳምንት ነው።ጋዜጣው ኬንያ ከኢትዮጵያ የመብራት ኃይል ለመግዛት ውል መፈራረሟን ገልጾ ባለፈው ሓሙስ በስቲማ ፕላዛ የተደረገው የኢትዮጵያ እና የኬንያ የመብራት ኃይል ውል መሰረት በኪሎዋት በአንድ ሰዓት ከስድስት እስከ ሰባት የኬንያ ሽልንግ እንደሚቆጥር ጋዜጣው ያብራራ ሲሆን የመስመር ዝርጋታው የተጠናቀቀው የመብራት ኃይል አገልግሎቱ ኬንያ ከኢትዮጵያ 600 ሜጋዋት ያህል የምታገኝ ሲሆን ኢትዮጵያ አገልግሎቱን ከመጪው ህዳር ወር ጀምሮ እንደምትሰጥ ዜናው ያትታል።በሓሙሱ የውል ስምምነት ላይ የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ እንደተገኙ የኬንያው ስታር ጋዜጣ ዘግቧል።


የኢትዮጵያ አየር ኃይል የአልሸባብን ይዞታ ዛሬ ቅዳሜ በድንገት አደባይቶታል

የቱርክ ዜና አገልግሎት አናዶሊ ዛሬ ቅዳሜ እንደዘገበው የኢትዮጵያ አየር ኃይል የአልሸባብ ይዞታዎችን ዛሬ ድንገት ደርሰው አደባይተውታል።አየር ኃይሉ ያጠቃበት ቦታ በደቡብ ምዕራብ ሱማልያ ጋራስዋይነ በተባለ ቦታ መሆኑም ገልጾ የአናዶል ዘጋቢ ከስፍራው በስልክ የነገረውን ገልጾ የቱርክ ዜና አገልግሎት እንደዘገበው አራት ሚሳኤሎች ከኢትዮጵያ አየር ኃይል ተወንጭፈው ኢላማቸውን መምታታቸውን ገልጿል።

ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የስበት ኃይልነቷ ከመቼውም ጊዜ በላይ ግልጽ እየሆነ ነው። 

ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ እና የመካከለኛው ምስራቅ የስበት ማዕከል እየሆነች እንደመጣች ከመቼውም ጊዜ በላይ ግልጽ ሆኗል።ይህንን ለማረጋገጥ የሃያላኑ መንግስታት የእዚህ ሳምንት አዲስ አበባ መክተም ብቻ በመመልከት መረዳት ይቻላል።
እያሳለፍነው ባለነው ሳምንት ብቻ 
  • ቻይና ከስድስት የምስራቅ አፍሪካ አገራት ጋር ጸጥታን በተመለከተ አዲስ አበባ ላይ ልዩ ስብሰባ አድርጋለች፣
  • አሜሪካ ልዩ ልዑክ ወደ አዲስ አበባ ዓርብ ዕለት ልካለች፣
  • የሩስያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም በእዚሁ ሳምንት አዲስ አበባ ከትመዋል።

አሜሪካ ለኢትዮጵያ 488 ሚልዮን ዶላር ለሰብዓዊ ዕርዳታ ለኢትዮጵያ ህዝብ መስጠቷን በዩኤስ ኤይድ ጋዜጣዊ መግለጫ የገለጠችው በእዚህ ሳምንት ነበር።

በጋዜጣዊ መግለጫው (ፕሬስ ሪሊዝ) ላይ የአሜሪካ ተራዶ ድርጅት እንደገለጸው ድጋፉ ወደ 8 ሚልዮን ለሚሆን ህዝብ የሚዳረስ ሲሆን ከምግብ ዕርዳታ በተጨማሪ ለገበሪዎች ለመጪ ዓመት ምርት ድጋፍ፣ለንጹህ መጠጥ ውሃ እና ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድጋፍ ጭምር እንደሚውል ያብራራል።

የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮጵያ የ4ነጥብ 3 ሚልዮን ዶላር ድጋፍ ማድረጉ የተገለጸው በእዚህ ሳምንት ነበር።

የአፍሪካ ልማት ባንክ በድረገጹ ላይ ከአቢጃን ረቡዕ እለት እንደገለጸው የባንኩ ቦርድ 4ነጥብ3 ሚልዮን ዶላር ለኢትዮጵያ ስጦታ የሰጠ ሲሆን ገንዘቡ ኢትዮጵያ በተለይ የገንዘብ ሚኒስትር ለሚያካሂደው የአቅም ግንባታ እንደሚውል ባንኩ በዘገባው ላይ አብራርቷል።
============///===========




Saturday, July 23, 2022

በግብጽ እና ሱዳን ጓዳ ሲቋጠሩና ሲፈቱ የከረሙት ጉዳዮች እና የኢትዮጵያ መከላከያ ያለፉት ሦስት ሳምንታት አክራሞት


===========
ጉዳያችን ልዩ ዘገባ
===========
በግብጽ እና ሱዳን ጓዳ ሲቋጠሩና ሲፈቱ የከረሙት ጉዳዮች

ኢትዮጵያና ሱዳንን ወደየለየለት ጦርነት ለመክተት በሱዳን ውስጥ በተሰገሰጉ የግብጽ ወኪሎች እና በግብጽ በራሷ ሲገፋ የነበረው ጥረት መጨረሻ ደረጃ ይሳካል ተብሎ የታሰበው በቅርቡ በሁለቱ አገሮች ድንበር አካባቢ በአልፋሻጋ አካባቢ የሱዳን ወታደሮች ተገደሉ የሚል ዜና በመንዛት ነበር። እነኝሁ በሱዳን የግብጽ ወኪሎች እና ግብጽ እራሷ ከፍተኛ የሚድያ ዘመቻ ከማድረግ አልፈው የግብጹ ፕሬዝዳንት አድርገው የማያውቁትን የሃዘን መግለጫ በኢትዮጵያ ለተገደሉት የሱዳን ወታደሮች ሃዘን በሚል አወጡ።በኢትዮጵያ በኩል ጉዳዩ ቀድሞ የታወቀ ስለሆነ እና ዓላማው በኢትዮጵያ እና ሱዳን መሃል ጦርነት ማስነሳት እና ግብጽ በመሃል የመግብያ ቀዳዳ እንድታገኝ በእዚህም በያዝነው ክረምት የሚሞላው ሦስተኛው ዙር የዓባይ ግድብ ማስተጓጎል ነበር። ከእዚህ ባለፈ የሱዳን መንግስት በውስጡ የተነሳው የህዝብ አመጽ ለመግታት እና አቅጣጫ ለማስቀየር የታሰበም ነበር።ሆኖም ግን የኢትዮጵያ አቋም ጉዳዩን በንግግር መፍታት ላይ ማትኮሯን የሚገልጽ መልዕክት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በአረብኛ በትዊተር ገጻቸው መለጠፋቸው ብቻ ሳይሆን የሱዳንን ባለስልጣናት ናይሮቢ በተደረገው የኢጋድ ስብሰባ ላይ አግኝተው ማስረዳታቸው ሱዳኖች ሳይወዱም በግድ በህዝባቸው ግፊትም ቢሆን ከግብጽ ግፊት ለማፈግፈግ ተገደው ነበር።

አሁን በቅርብ ያለው መረጃ እንደሚያሳየው ደግሞ የሱዳን ጦር በአልፋሻጋ እና አልሱቅራ በተባሉ ቦታዎች ገለዓሉባን ተራራ እና ሉግዲ በረከት በተባሉ ቦታዎች የሱዳን ኃይሎች በአካባቢው ያሉትን ሚሊሻዎች እየገፉ ቦታዎች እየያዙ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።

ሱዳን እና ግብጽ ጓዳ ምን እየተደረገ ነው?

በኢትዮጵያ አንጻር የሱዳን መንግስት በሚከተለው የግብጽን ፍላጎት የማሟላት ሂደት በሱዳን በራሷ በተለይ በባለስልጣናቱ መሃልም ጭምር ክፍፍል ፈጥሯል። የመጀመርያው ክፍፍል ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አማካይነት ናይሮቢ ላይ  ለሱዳኑ ሉዓላዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሌ/ጀነራል አብዱል ፋታህ በግልጽ ያስተላለፈችው መልዕክት ግልጽ ስለሆነ ሱዳን ለምን የራሷን ችግር በመፍታት ላይ አታተኩርም? የሚሉ የሱዳን ባለስልጣናት መንግስታቸውን ወጥረው መያዛቸው ነው። ይህንን ሃሳብ ከሚደግፉት ውስጥ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ውይይት ያደረጉት እራሳቸው ጀነራል አብዱል ፈታህ መሆናቸው እና ይህንንም አቋም ይዘው በመመለሳቸው ነበር በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር መከፈት ላይ እና የታጠቁ ኃይሎች በድንበር አካባቢ መንቀሳቀስ አይችሉም የሚል መግለጫ የሉዓላዊ ምክር ቤቱ እንዲያወጣ ያደረጉት።

ይህ በእንዲህ እያለ ግን ለሱዳን መንግስት ቅርበት ያላቸው የሱዳን መገናኛ ብዙኃን የሱዳን ጦር በኢትዮጵያ ሰራዊት ላይ እርምጃ እንደወሰደ እና የኢትዮጵያ ወታደሮች እንደተማረኩ እያስመሰሉ የበለጠ ብዥታ ለመፍጠር ሲሞክሩ የግብጽ ወኪል የሱዳን ባለስልጣናት በበኩላቸው ደግሞ የሱዳንን ህዝብ ስሜት ለመቀስቀስ የሱዳን ህዝብ በኢትዮጵያ እንደተዋረደ እያስመሰሉ ማቅረብ ጀመሩ።ይህ በእንዲህ እያለ ግን በኢትዮጵያ ድንበር ልዩ ቦታው ''በረከት ኑር በተባለ ቦታ የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው የገቡ የሱዳን ታጣቂዎች የኢትዮጵያ የእርሻ ካምፖችን፣መጋዘኖች እና 16 ትራክተሮችን እና በበርሜል የተከማቸ ነዳጅ ዘርፈዋል።እስካሁን ባለው መረጃም አስር የሚሆኑ የኢትዮጵያ ባለሃብቶች አፍነው ወስደው በረከት ኑር በተሰኘው አካባቢ ካምፕ ውስጥ መሸሸጋቸውን ለማወቅ ተችሏል። ይህ በእንዲህ እያለ ሱዳን አሁንም ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ከገፋ እስከ አየርኃይሏ ለመጠቀም በውስጥ መወሰናቸው ተሰምቷል። 


ይህ በእንዲህ እያለ ግብጽ በሱዳን ወታደራዊ መንግስት ላይ በኢትዮጵያ ላይ ወረራ እንዲያደርግ እስከ ማስራራት የደረሰ ጫና እያሳየች ነው። ወደእዚህ ዓይነት እርምጃ ግብጽን የመራት ደግሞ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እና የሱዳን ወታደራዊ መንግስት መሪ መሃል በናይሮቢ የተደረገው ውይይት ከግብጽ ቁጥጥር ውጪ የሆነ እና ምህዋሩን የሚያስታት በመሆኑ ከፍተኛ ድንጋጤ ፈጥሮባት ሰንብቷል። ይህንን ውይይት ተከትሎ ካይሮ ልዩ የደህንነት ልዑክ ወደ ካርቱም የላከች እና የጸረ ኢትዮጵያ እንቅስቃሴ እንዳይቆም የተቻላትን ለማድረግ  ሞክራለች።በተጨማሪም ግብጽ ቦይንግ 737 የመንገደኞች አይሮፕላን  የግብጽ አለስከንደርያ ኩባኛ ንብረት የሆነ አይሮፕላን በሱዳን የከሰላ አይሮፕላን ማረፍያ እንዳረፈ እና ሌሎችየካርጎ አውሮፕላኖች በገዳሪፍ አዘዛ በተባለው የሱዳን ወታደራዊ ካምፕ እና በገዳሪፍ አልፋው በተባለው የሱዳን 2ኛው ክፍለ ጦር ካምፕ የተለያዩ የህክምና መሳርያዎች እና መድሃኒቶች አራግፈው መሄዳቸውን የኢትዮጵያ መረጃ ቢሮ እጁ ገብቷል።

በሌላ በኩል ግብጽ በከፍተኛ ሁኔታ እየሮጠችበት ያለው ጉዳይ በኢትዮጵያ ፌድራል መንግስት እና በህወሃት መሃል ሊደረግ የታሰበው ውይይት በፍጥነት እንዲቀጭ የተቻላትን ሁሉ በማድረግ ላይ ነች።ለእዚህም እንዲረዳቸው ከህወሃት በኩል በድርድሩ የሚሳተፉትን አባላት እና ሌሎች የቡድኑ ወታደራዊ አመራሮች ወደ ካይሮ ለመውሰድ ወይንም በሱዳን የደህንነት ማሰልጠኛ ውስጥ ገብተው ስልጠና እንዲወስዱ ለማድረግ ዕቅድ እንዳላት የተገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ።


የኢትዮጵያ መከላከያ ባለፉት ሦስት ሳምንታት አክራሞት

በሸኔ፣ጋምቤላ፣ጉሙዝ እና በቅማንት ስም የሚንቀሳቀሱ የሽብር ቡድኖች በቅርብ እና የሩቅ የኢትዮጵያ ጠላቶች የተሰጣቸው ተልዕኮ ያሉበትን ክልል ከማተራመስ ባለፈ ወደ ሌሎች ክልሎች በፍጥነት እንዲሰርጉ ነበር። ሆኖም ግን መከላከያ ባሳለፍናቸው ሦስት ሳምንታት የወሰደው እርምጃ የሽብር ቡድኖቹ አከርካሪ ተመቷል።በእዚህም በአዝማቾቻቸው መንደር ከፍተኛ መበሳጨት ፈጥሯል።
በሸኔ ላይ የተወሰደው እርምጃ 
  • በመቶዎች የሚቆጠሩ የሸኔ ቡድን አባላት ተገድለዋል።
  • ከሁለት መቶ በላይ ቀላል እና መካከለኛ የጦር መሳርያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል
  • ከውጭ የነበረው የግንኙነት መረብ ከጠበቀው በላይ ተቋርጦበታል፣በእዚህም ከፍተኛ መደናበር በቀሩት አባላት ውስጥ ተፈጥሯል
  • ጥቃቱ በአራቱም የወለጋ እና የሸዋ ዞኖች እንዲሁም በጉጂ ዞን በተወሰደበት እርምጃ የተበታተነው የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች በአንዳንድ ቦታዎች የሚታየው ባልተደራጀ እና ሰንሰለቱ በተበጣጠሰ ደረጃ ሆኖ ነው
  • ይህም ሆኖ የተበታተነው ኃይል አልፎ አልፎ በጸጥታ ኃይሎች ላይ ጥቃት ለማድረስ መሞከሩ እንደማይቀር ይገመታል
በተመሳሳይ በጋምቤላ፣ጉሙዝ እና ቅማንት ስም የሚነግዱ የሽብር ቡድኖች ላይም በተወሰደው በተለይ በዓባይ ግድብ ላይ ለማድረስ የታቀደው ሁከት ከመከላከል ባለፈ የሽብር ቡድኖች ስጋት የመሆናቸውን አደጋ በእጅጉ ለመቀነስ መቻሉ ቢታወቅም አሁንም ከባዕዳን ጀምሮ እስከ የውስጥ አደራጆቻቸው እንደገና ለማወክ መሞከራቸው ስለማይቀር ዛሬም በንቃት የመጠበቅ ስራው ሊቀጥል ይገባል።

ባጠቃላይ አሁን የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያ የአባይን ግድብ ሦስተኛ ዙር ሳትሞላ አንዳች ዓይነት ሁከት ለመፍጠር እና የውስጡ ማወክ ካልተሳካ ቀጥታ ወረራ ለመፈጸም አያሰላስሉም ብሎ ማሰብ አይቻልም። በእርግጥ ማንም አገር በኢትዮጵያ ላይ ጥቃት ለመፈጸም ያሰበ አገር የሚያገኘው ምላሽ ምን እንደሆነ ያውቀዋል።በተለይ የሱዳን እና የግብጽ የጥቃት ሙከራ ከኢትዮጵያ ይልቅ ሁለቱን አገሮች የማፍረስ ደረጃ የማድረስ አደጋ አለው።ለእዚህም አንዱ ምክንያት ኢትዮጵያ ለሚሰነዘርባት ማናቸውም ጥቃት ከአየር ኃይል እስከ የእርቀት ሚሳኤሎች የአጸፋ ምላሽ መስጠቷ ስለማይቀር እና በሱዳንም ሆነ በካይሮ የህዝባቸው ከ70 በመቶ በላይ የሚሆነው ቁጥር ተከማችቶ የሚገኘው በተወሰኑ ከተሞች በመሆኑ የሁለቱ አገራት የተወሰነ መሰረተ ልማት ላይ ኢትዮጵያ ለምትወስደው እርምጃ በአስር ሚልዮኖች የሚቆጠር ህዝብ ይበተናል። ይህም ከፍተኛ ቀውስ ለመካከለኛውም ሆነ ለአውሮፓ ይዞ መምጣቱ አይቀርም። በመሆኑም ግብጽም ሆነች ሱዳን ኢትዮጵያን ከውስጥ በራሷ ከሃዲዎች ለማተራመስ ከፍተኛ ዋጋ እንደሚከፍሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ማወቅ አለበት።ከእዚህ በተረፈ ክውጭ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች አይኖሩም ብሎ ተዘናግቶ የሚቀመጡበት ጊዜ እንዳልሆነ ከመቼውም ጊዜ በላይ ግልጽ ነው።በቅርቡ በሳውዲ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባይደን ከግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ጨምሮ የአባይ ግድብ ጉዳይ በአጀንዳነት እንዲቀርብ ግብጽ ብዙ መጋጋጥ አድርጋ ሄዳበታለች።አሁን ጥያቄው በእዚህ ስብሰባ ላይ ምን ነበር ንግግሩ? የውስጥ የሴራ ንግግር ነበር ወይንስ ግልጽ ውይይት ነበር? ለሚሉት ጥያቄዎች ትክክለኛ ምላሾች ስናገኝ ብዙ ነገሮች ግልጽ ይሆኑልናል።ባጭሩ ግን ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያን ከውስጥም ከውጭም ነቅተው እና ተግተው የሚጠብቁበት ጊዜ አሁን ነው።
==============//////==================


Sunday, July 10, 2022

የ1966 ዓም የወሎ ረሃብን ጠላቶቻችን ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያውያንን እንደወጉበት ዛሬም ሊደግሙት ሲሰናዱ ህዝብ ለምን ትመቻችላቸዋለህ? ለምንድን ነው እንደህዝብ ያለፈ ስህተታችንን የምንደግመው?


ቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴ የክብር ዘብ ሲቀበላቸው 

======
ጉዳያችን
======

አንድን አገር እና ህዝብ ለማጥፋት፣ለመበተን እና ቢያንስ ስነልቦናው ተሰልቦ በአካል የሚጎማለል፣በስነልቦናው ግን ተሸናፊ እንዲሆን የጠላት አገር ጠበብት ተቀምጠው መክረው እንደህዝቡ ታሪክ እና ስስ ጎን እየታየ በርካታ የድርጊት ተግባሮች ተቀምመው ይላኩለታል። ይህ ደግሞ በእዚህ የማኅበራዊ ሚድያ ዘመን የተለያዩ አገር የማተራመሻ እና የህዝቡን ስነ ልቦና የሚነኩ አደገኛ ሥራዎች ይሰሩበታል። የእዚህ ዓይነቱ የተንኮል ሥራ የጠላይ አገሮች ከድህንነት ባለሙያ እስከ ሶሾሎጂስትና ታሪክ አጥኚ ድረስ ተሳትፎበት የሚዘጋጅ የተንኮል ድር ነው።በአባይ ወንዝ የምትቀናቀነን ግብፅ በእዚህ ተክናበታለች።ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያውያንን አንገት ለማስደፋት አይደለም ዛሬ ባንዳ እንደ አሸን ፈልቶ አግኝታ ቀርቶ ቀድሞም ዕድሜዋን የፈጀችው በእዚሁ የተንኮል ድር የማድራት ሥራ ላይ ተጠምዳ ነው።

የአፍሪካ አገሮች ከእዚህ የተቀናጀ የባለሙያዎች የምክክር ውጤት የሆነ ስነ ልቦናቸውን የመጉዳት እና የተሸናፊነት ስሜት እንዲያድርባቸው በእዚህ የረቀቀ እና የማናጋር ሥራ ይሰራባቸዋል።በእዚህም የአገሮቻቸው መሪዎች ሳይቀሩ እርባና ቢስ እስኪሆኑ ድረስ በብዙ የተንኮል መረቦች ተተብትበው አገራቸውን ለባዕዳን አስረክበው በስም ብቻ የአገር መሪ እየተባሉ ለመኖር የተገደዱ አሉ።የእዚህ ዓይነት ደካማ መሪዎች መኖር በድምር በአፍሪካ ኅብረት ላይ የራሱ የሆነ ጠንክሮ እንዳይወጣ የራሱ የሆነ ጥላ አጥልቶበታል።

ወደ አገራችን ጉዳይ ስንመለከት በ1966 ዓም የወሎ ረሃብ እና ፖለቲካዊ ተጽዕኖው በወቅቱ በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ የነበረውን የለውጥ ፍላጎት አስታከው የኢትዮጵያ ጠላቶች በአደገኛ መንገድ የኢትዮጵያን መሰረት ለማናጋት ተጠቅመውበታል። ረሃቡ ይዞት የነበረው የሞራላዊ ጥያቄን ኢትዮጵያ ከሥሯ እንድትናጋ ለማድረግ ረሃቡን ያመጡት ብቻ ሳይሆን ችላ ያሉት ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ናቸው የሚል ዘመቻ መጀመርያ በሰፊው እንዲከፈት ተደረገ።በርካታ ምሑራን አምባሳደር እና ደራሲ ሃዲስ ዓለማየው የንጉሱ ስልጣን ተገድቦ በጠቅላይ ሚኒስትር ባብዛኛው የሚዘወር መንግስት መመስረት እና ኢትዮጵያ የገነባቻቸው ተቋማት ሳይናጉ ዕድገቷን ማፋጠን አለባት የሚሉት ላይ የስነ ልቦና ውጊያው በውስጡ መርዝ የይዘ ነገር ግን ተራውን ኢትዮጵያዊ ሊያታልል የሚችል እጅግ አደገኛ አቀራረብ ነበረው። ይሄውም ረሃቡ አሳዛኝ ብቻ ሳይሆን አሰቃቂ ስለነበር አገር አስደንግጧል። የምዕራብ ሚድያም ሆነ በወቅቱ ያቆጠቆጠው የተማሪዎች እንቅስቃሴ ረሃቡን ከረሃብነት ባለፈ በንጉሱ ላይ እና በስርዓቱ ላይ ፖለቲካዊ ዘመቻ ለማድረግ እንደሚጠቅም ታምኖበት ስለነበር የረሃቡ ክርክር ከረሃብ ባለፈ የራሱ የሆነ የተሳሳተ ዕሳቤ ተስሎበት ቀረበ።

በወቅቱ በተለያዩ ሰዎች ተጽፈው ከነበሩት ጽሑፎች ለመረዳት እንደሚቻለው ረሃቡን ከአሳዛኝነቱ ባለፈ የፖለቲካዊ ቃናው ኢትዮጵያን ለማናጋት ጥቅም ላይ ሲውል አደጋው በወቅቱ ምን ያህል እንደሚተረተር የገባው ብዙ ሰው አይመስልም።በወቅቱ የነበረው የረሃቡ አቅራረብ በአጭር አነጋገር ይህንን ይመስላል። ይሄውም ''ረሃቡ የመጣው በዝናብ እጥረት ሳይሆን ንጉሱ እና ባላባቱ መሬቱን ስለተቀራመቱት ነው።ረሃቡ ሲመጣ ንጉሱ እንዳይነገር ደብቀዋል '' ካለ በኋላ '' ስለሆነም ንጉሱን ብቻ ሳይሆን መንግስት በሙሉ ይፍረስ '' የሚል ሃሳብ በህዝቡ ውስጥ ነዙ። ይህ ረሃብን ለፖለቲካ ጥቅም የተጠቀመው እና የኢትዮጵያ ጠላቶች ያቀበሉትን መንግስት የማፍረስ አጀንዳ ሲግፋበት ከመንግስት መፍረስ በኋላ ምን እንደሚመጣ አያውቅም ነበር።

ይህንን መንግስት ይፍረት ንጉሱ ናቸው ረሃቡን ያመጡት የሚለውን የሚሞግቱ በሁለት አደገኛ አቀራረብ ባላቸው የሰው ስሜት በሚነኩ ነገር ግን ግንኙነት በሌላቸው የመልስ ምት ሃሳቦች እንዲጣጣሉ ሆነው ተቀምመው ነበር።ለምሳሌ አንድ ሰው የወሎ ረሃብ አሳዛኝ ቢሆንም መንግስት ማፍረስ ግን መፍትሄ አይሆንም የሚሉ እንደ አረመኔ ህዝብ በረሃብ ሲያልቅ የማይሰማቸው፣ከሃዲዎች እና የስርዓቱ ተጠቃሚዎች ተደርገው ይሳሉ ነበር።ይህንን ለማስረዳት የሞከሩትን አብዛኛው የፖለቲካ ንቃቱ ደካማ ስለሆነ ጥቂቶች ደግሞ ሆን ብለው ለፖለቲካ ጥቅም ተጠቀሙበር። በመሆኑም ረሃቡን ከመንግስት መፍረስ ጋር አለማገናኘት በራሱ ያለማወቅ የመጨረሻ ደረጃ አድርገው የሚያዩ ብቻ ሳይሆን ስለረሃቡ አሳዛኝነት ካወሩ በኋላ መንግስት መፍረስ መፍትሄ እንደሆነ አብሮ ተሰበከ። ይህ የተሳሳተ አስተሳሰብ መሆኑን ለመረዳት ከወሎ ድርቅ በኋላ እና የንጉሱ አስተዳደር ከፈረሰ በኋላ 60 ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በታሪካችን ጥቁሩ ቅዳሜ ተብሎ በሚጠራው በኅዳር 14፣1967 ዓም ምሽት ሲረሸኑ የወሎ ረሃብ ያስራቡ ብለው ተፈረደ ያሉ የወቅቱ አብዮተኛ ተብዬዎች የሉም ማለት አይቻልም።

ከወሎ ረሃብ አርባ ዘጠኝ ዓመታት በኋላ በኢትዮጵያ ላለፉት አራት ዓመታት በታኝ እና ዘረኝነትን መሰረታቸውን ባደረጉ አሸባሪዎች አቀናባሪነት እና የባዕዳን የጀርባ ድጋፍ በርካታ ወገኖቻችን ተገድለዋል።እነኝህ ወገኖቻችን መገደላቸው እጅግ አሳዛኝ ቢሆንም የህዝብ የማዘንን ስሜት ተጠቅመው ፖለቲካዊ ዘመቻ ለማራመድ የሚጠቀሙበት እራሳቸው በታኝ ኃይሎች እና ባዕዳን የኢትዮጵያ ጠላቶች ሆነው እናገኛቸዋለን።ይህንን በንጽጽር ከአሁኑ ጋር እያስተያየን ማቅረብ እንችላለን።

በ1966 ዓም

በ2014 ዓም

ያኔም ሆነ አሁን ዕውነታው 

ለወሎ ረሃብ ምክንያቱ ንጉሱ እና መንግስት ነውነው

ሸኔን የፈጠረው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ነው።ነው።

ለረሃቡ ንጉሱ ምክንያት አልነበሩም።ይልቁንም በቀስታ ህዝቡን እንርዳ እንጂ ለባዕዳን ማሳጣት ጠባሳ ያመጣል የሚል ሃሳብ ያላቸው ንጉሱ ነበሩ። በወቅቱ ማን ሰምቷቸው። ዛሬም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን በመስቀል አደባባይ ለመግደል የሞከረውን፣ወለጋን ዐቢይ አይረግጥም ያለውን ሸኔ ዐቢይ አውቆ ነው እያሉ ህዝቡን የሚያታልሉ አሉ።አሉ።

የወሎ ረሃብ ከመሰረቱ ለማጥፋት መንግስት መፍረስ አለበትአለበት

የወለጋ እልቂት የሚቆመው ዐቢይ ሲወርድ ነው። የሚል ዘመቻ የኢትዮጵያ ጠላቶች አጀንዳ የሚያራግቡ አሉ።እነኝህ በውጭ ተቀምጠው ኢትዮጵያ ስትፈርስ አይስክሬም የሚልሱ ናቸው።ናቸው።

ዕውነታው በ1966ም ሆነ ዛሬ ለወሎ ረሃብም ሆነ ለሽብርተኞች ጥቃት መንግስት ማፍረስ ንጉሱንም ሆነ ዐቢይን ማውረድ ነው የሚለው አባባል የጠላት ወሬ ነው።ዓላማው ኢትዮጳያን የማተራመስ የባዕዳን አጀንዳ ነው።

ወሎ እየተራበ ንጉሱ ኬክ በሉ፣ፈገግ አሉ እየተባለ ይብጠለጠሉ ነበር።

ዛሬም ዐቢይ አገር ወክሎ በውጭ አገር ስብሰባ ሲገኝ ፈገግ ሲል፣ችግኝ ሲተክል ወዘተ ህዝብ እያለቀ ፈገግ ያለው፣ችግኝ የተከለው አውቆ እልቂቱን ስለሚደግፍ ነው እያሉ የኢትዮጵያ ጠላቶች ቀደም ብለው በቀመሩት ሥራ ኢትዮጵያውያንን ያውካሉ።ያውካሉ።

በንጉሱም ላይ ሆነ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ላይ የተደረገው የወሬ ዘመቻ ኢትዮጵያውያንን የማወክ እና እርስ በርስ እንዲከፋፈሉ ለማድረግ የታሰበ ሴራ ነው።በንጉሱ ጊዜ ረሃቡን ለመታደግ ከመዝመት ባለፈ በረሃቡ የሌሉበትን ንጉሱን መስደብ ይበዛ ነበር።በወቅቱ የቅድስት ማርያም የሴቶች ትምህርት ቤት ተማሪ የነበረች ዛሬ ላይ ስታስታውስ ወደ ትምህርት ቤት ስንሔድ እና ስንመጣ እነኝህ የስርዓቱ ልጆች እየተባልን መንገድ ላይ መንጓጠጥ ሁሉ ነበረብን ማለቷን የእዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ አድምጧል።


በጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ላይ የሚደረገው ዘመቻም እንዲሁ ተመሳሳይ ነው። ዋና ገዳዩን ኦነግ ሸኔን ከኮነኑበት ይልቅ ዐቢይ ዐቢይ እያሉ የሚሳደቡ እና ጠቅላይ ሚንስትሩ ህዝቡ ላይ የተኮሰ ቀረሽ ሃሳብ ሲያራግቡ የሚውሉ እና መንግስት ይፍረስ እያሉ በድፍረት ባዶ አስተሳሰባቸውን የሚለቁ አሉ።አሉ።

ለሕዝብ የተጨነቁ መስለው ነበር መንግስት ይፍረስ ያሉት                ዛሬም ለብሄር በማሰብ መንግስት መፍረስ እንዳለበት የሚሰብኩ አሉ።ሁሉም የኢትዮጵያ ጠላቶች አጀንዳ አስፈጻሚ ሆነው ቀረዋል።


ባጠቃላይ እንደ 1966 ዓም ዛሬም ደግመን ኢትዮጵያን ለሌላ 40 ዓመት መከራ ላይ እንዳንጥላት መጠንቀቅ አለብን።
የ1966 ዓም የወሎ ረሃብን ጠላቶቻችን ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያውያንን እንደወጉበት ዛሬም ሊደግሙት ሲሰናዱ ህዝብ ለምን  ትመቻችላቸዋለህ? ለምንድን ነው እንደህዝብ ያለፈ ስህተታችንን የምንደግመው? ኢትዮጵያ ቀና እንዳትል ለዘመናት ስንጋተው የነበረውን መርዝ ዛሬ ላይ እንድንግተው እና በምርጫ የተመረጠ መንግስት ይፍረስ እያሉ የሚለፍፉትን በጥብቅ ልንመረምራቸው እና አጀንዳቸው የእነማን እንደሆነ ማጋለጥ አለብን።
============///=============

Tuesday, July 5, 2022

የወለጋው የንፁሃን እልቂት የሚገታበት መንገድ አንድ እና አንድ ብቻ ነው።ቅሉን መስበር! ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ቅሉን ስበሩት ወይንም ኢትዮጵያንም እርስዎንም እስኪሰብርዎ ተቀምጠው ጠብቁት።

ጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ
===============
ጉዳያችን /Gudayachn
===============

የሁለት ወር ህጻን ተኩሶ የሚገድል፣እርጉዝ በስለት የሚወጋ፣አዛውንት እና ባልቴቶችን በዘራቸው እየለየ የሚገድለው ከኦሮምያ ምድር የበቀለው የዘመናችን የናዚ ቡድን በምን ያህል ደረጃ  በህዝብ ላይ ጥላቻ እንዳለው አሳይቷል። የገዳዩ መጋቢ አዳማም፣ነቀምትም አዲስ አበባም ተቀምጦ በንፁሃኑ ሞት እየሳቀ ነው።አቶ ታዬ ደንዳ የኦሮምያ ብልጽግና ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የሰላም ሚኒስቴር ዴታ ችግሩ የገዘፈ እንደሆነ እና ከራሱ ከኦሮምያ ክልል አስተዳደር ውስጥ ችግር እንዳለ በገለጸበት የማኅበራዊ ሚድያ ጽሑፉ ላይ ተጠያቂነት እንዲኖር አሳስቧል።የኦሮምያ ክልል ውስጥ እየተፈጸመ ያለው ጭፍጨፋን ''እሰይ!'' የሚሉ ከኦሮምያ ልዩ ኃይል እስከ የክልሉ አንዳንድ ባለስልጣናት ድረስ አሉ። በእነርሱ እሳቤ ይህ ጭፍጨፋ የስልት ማስፈጸምያ አድርገው ያዩታል።በሻገተ አዕምሮ ውስጥ ሆነው እራሳቸውን እንደ ታላቅ ሴረኛ እየቆጠሩ በህዝብ ደም የሚቀልዱ ናቸው።

የሱማልያ ክልል የፀጥታ ችግር ለሁሉ ምሣሌ በሚሆን ደረጃ የተረጋጋ ሲሆን የኦሮምያ ክልል በእዚህ ደረጃ የህዝብ ደም እንደ ጎርፍ እንዲፈስ የተተወው ብቻ ሳይሆን ክልሉ በመቶዎች በአንድ ጀንበር የሞቱበት የማይመስለው ለምንድን ነው? ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው።በኢትዮጵያ ምድር የሁለት ወር ህጻን ጨምሮ የመግደል ስነ ልቦና ከኦሮምያ ምድር መብቀሉ ስለሚያሳፍራቸው እና በተወለዱበት የኦሮምያ ክልል ቀድሞ ባልተጨበጠ ታሪክ ''ከመቶ ዓመታት በፊት ጡት ተቆርጧል'' ብለው የቂም ሃውልት ይሰራልን ብለው ያዙን ልቀቁን ያሉ ዛሬ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ከሁለት ወር ህጻን እስከ እርጉዝ የሚገድል አረመኔያዊ ድርጊት ፈፃሚ መነሳቱን ሊሸፋፍኑ የሚሞክሩ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ጭፍጨፋው የፈሪነት መገለጫ ብቻ ሳይሆን ለዓመታት የተተረከ ትርክት ውጤትም ነው።

አሁን ብዙ ፍልስፍና የሚደረደርበት ጊዜ አይደለም።ህዝብ የሚጨፈጭፈው የኦነግ ቡድን በኃይል እንደመጣ የሚመለሰው በኃይል ብቻ እንጂ ጀዋር አለስልሶ እንደሚናገረው በድርድር አይመለስም።በኃይል ለመመለስ ደግሞ የኦሮምያ ክልል በውስጡ የተቦካካ እና ለኦነግ ስስ ዓይን ባላቸው የልዩ ኃይል አባላት እና አንዳንድ ባለስልጣናት ቸልተኝነት የተሞላ ስለሆነ እስካሁን አመርቂ ውጤት አላስገኘም። ስለሆነም አሁን አዲስ አቅጣጫ መያዝ አለበት።

በቅርቡ በኢትዮጵያ የሚነሱ የጸጥታ ችግሮች የኋላ መነሻ እና የአሁኑ ተዋናዮችን ትተን ለምን መፍታት አልተቻለም? የሚለውን አንኳር ጥያቄ መመለስ እና በተለይ አሁን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆነ መንግስት በቆራጥነት ሊወስዱት የሚገባው እርምጃ ምንድነው? የሚለው ላይ ብቻ ለማትኮር እሞክራለሁ።የሱማሌ ክልል ግዙፍ የጸጥታ ችግር ያውም ከጎረቤት ሱማልያ ሽብርተኞች  የሚርመሰመሱበት ሆነው እያለ የሱማሌ ክልል ያለው አስተዳደር እንደ ኦሮምያ ብልጽግና በሴራ ስላልተተበተበ ከሁሉም የኢትዮጵያ ክልል በተሻለ የጸጥታውን ሁኔታ አስከብሯል።

አሁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሲያከብሩት ወይንም ሲጠነቀቁለት የኖሩት እና በሂደት ይፈታል ብለው የጠበቁት የክልሎች የጋራ የጥምረት የጸጥታ አጠባበቅ ሂደትን ወደፊት በማምጣት የጎሳ ቅሉን አሁን የመስበርያው ጊዜዎ ነው። የጎሳ ፖለቲካን እንደ እንቁላል ቢንከባከቡት የመጨረሻው ውጤቱ በገማ እንቁላል ሰውነትን ማበላሸት ነው። አሁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የጎሳ ቅሉን ከመስበር ሌላ አማራጭ የለም።ቅሉ እንዲሰበር የኢትዮጵያ ህዝብ በጉጉት እየጠበቀ ብቻ ሳይሆን ህይወቱንም ለመስጠት ዝግጁ ነው። ይህ የጎሳ የፖለቲካ  ቅል የመስበር ሥራ ዛሬ ባይሆን ነገ  በሁሉም በሰላም ወይንም በኃይል እንደሚሰበር በሁሉም ዘንድ ይታወቃል። ቅሉ እንዳይሰበር በሁሉም መልክ ካሉት የጎሳ ፖለቲካ አድናቂዎች በኩል ዘመቻ ለመክፈት ይሞክራሉ። ይህ ግን ከኢትዮጵያ ህዝብ አቅም አይበልጡም። ይህ ቅል እራስዎም ላይ በመስቀል አደባባይ የግድያ ሙከራ ከመፈጸም እስክ ብዙ ሴራዎች ሰርቶብዎታል።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር 

የዛሬዋ ኢትዮጵያ በአንዱ ቦታ የተነሳ የጸጥታ ችግር በሌላው ጫፍ ያለው ኢትዮጵያዊ ደርሶ እንዳያግዝ ተደርጋ የተሰራች የህወሃት ስሪት የሆነች ኢትዮጵያ እጅግ አደገኛ ሁኔታ ላይ ነች።ይህ አደጋ ግን ቅሉን በድፍረት በመስበር ይስተካከላል። ቅሉን መስበር የሚጀመረው በአንዱ ጫፍ ያለ ኢትዮጵያዊ በሌላ ጫፍ ያለ ኢትዮጵያዊ ደርሶ እንዳያድነው ተደርጋ የተሰራችበትን ስሪት አሁን መሰበር አለበት።ይህ እንዳይሆን እና ይህ የእርስ በርስ መተጋገዝ በተለይ በክልሎች መካከል ቢኖር ኢትዮጵያ ትፈርሳለች የሚሉን የኢትዮጵያን ህዝብ የማያውቁት የህወሃት ውላጆች እነ ጀዋር ናቸው። ኢትዮጵያውያን ልዩ ህዝብ ናቸው።በአክቲቪስቶች ስነ ልቦና የምትመራ አይደለችም። መሬት ላይ ያለው እውነታ ሌላ ነው።

አሁን ሃቅን እና እውነትን መጋፈጥ የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ ነን።ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፣ይህንን ቅል ሳይሰብሩ መሻገር ቢቻል ጥሩ ነበር። ቅሉን ከመስበር ትንሽ መዘግየት ቢቻልም ሸጋ ነበር። ነገር ግን አይቻልም። ዛሬ እነጀዋር እና ሌሎች የኢትዮጵያውያንን ተነጣጥሎ መመታት የሚያስደስታቸው ኃይሎች ሁሉ የሚነግሩን የኦሮሞ እና የአማራ ህዝብ በጸጥታ ጉዳይ ላይ ተጋግዘው ክልላቸው ሰላም እንዲሆን ማድረግ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ክልሎችም የሁለትዮሽ እና ከእዚያም በላይ እየሆኑ የጋራ ስምምነት እያደረጉ የጎሳ ፖለቲካ ሊግቱን የሚፈልጉትን ኃይሎች ሁሉ በጋራ የመቅጣት አቅም የሚዳብረው ክልሎች በጥምረት ህግ የማስከበር ሥራ እንዲጀመር ማድረግ ይህም ብቻ ኢትዮጵያን የሚያድን መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለኢትዮጵያ ህዝብ በቆረጠ መልኩ መግለጽ አለባቸው። በአማራ ክልል ሽብርተኛው ህወሃት ባደረገው ወረራ ላይ ከኦሮምያ እስከ ሱማሌ የነበረ የክልል ልዩ ኃይል እንደዘመተ ሁሉ ወለጋ ለገጠማት ፈተና ከአማራ ክልል ይሁን ከአፋር የሚዘምት ኢትዮጵያዊ ከጠፈር ላይ የመጣ ሳይሆን ወንድሙ መሆኑን ለህዝብ ማሳየት ቅሉን በድፍረት መስበር ማለት ነው።

ቅሉን በእዚህ ወቅት ማለትም ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር ውጥረት ላይ እያለች፣የአባይ ግድብ ሊሞላ በተቃረበበት ጊዜ እና ከህወሃት ጋር ያለው ጉዳይ ባልተቋጨበት ሁኔታ ቅሉን መስበር ይቻላል ወይ? የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል። ለጥያቄው ምላሽ የሚሆነው ግን ሌላ ጥያቄ በማንሳት ነው። ይሄውም የአክቲቪስቶችን ልፈፋ እየሰሙ የጎሳ ቅሉን ተሸክሞ በመሄድ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ተቃቅሮ መኖር እና አገር ወደ አደጋ መምራት ይሻላል? ወይንስ ድሮም ለውጡን ተስፋ ያደርገው ህዝብ የጎሳ ቅሉ ይሰበራል ብሎ የጠበቀውን ህዝብ ልቡን ቅሉን በመስበር መግዛት እና የህዝብ ኃይል ይዞ ኢትዮጵያን ወደፊት ማስፈንጠር? ከሁለቱ አማራጩ የጎሳ ፖለቲካውን ቅል በድፍረት መስበር ብቻ እና ብቻ ነው ያለው አማራጩ። ይህ ደግሞ በልምምጥ አይመራም።መራር እርምጃ ቆራጥ ውሳኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ይጠበቅብዎታል።ከእዚህ በላይ ቅሉን ተሸክማ የምትሄድ ኢትዮጵያ የለችም። ቅሉን እርስዎ ባይሰብሩት ሌላ ይሰብረዋል።ዕድሉ ባያመልጥዎ ግን ይመረጣል።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፣ወደ ስልጣን የመምጣትዎ ትሩፋት አድርጎ ህዝብ የጠበቀዎት የጎሳ ቅሉን ይሰብራሉ ብሎ በታላቅ ተስፋ እንደነበረ ያስታውሱ።ይህንንም በንግግርዎ እና በተግባርዎ ብቻ ሳይሆን በጻፉት የመደመር መጽሓፍም ሁሉ የጎሳ ቅሉን እንደሚሰብሩ በግልጽ ስለተናገሩ ነው። አሁን ከጎሳ ቅሉ ጋር የቆመ የኦሮሞ ብልጽግናም ሆነ የአማራ ብልጽግና፣ የአፋርም ሆነ የትግራይ በምንም ዓይነት በሳሳ ዓይን ሊመለከቱት አይገባም። የጎሳ ቅሉ እንዲሰበር ፊሽካውን ይንፉልን።ህዝብ ይነሳል።ወለጋን መታደግ የአማራውም፣የአፋሩም የሱማሌውም ኃላፊነት መሆኑን በተግባር እናሳይ።አንዳንድ ነገሮች ከታሰበቡበት ጊዜ በፊት የሚጀመሩበት ጊዜ አለ።አንዳንድ ነገሮች ደግሞ ከአሁን በኋላ መዘግየት የለባቸውም የሚባሉ ተግባራት አሉ።የጎሳ ፖለቲካ ቅሉን የመስበርያው ጊዜ ግን ነገ ሳይሆን አሁን ነው።ይህ የኢትዮጵያን ህዝብ የቅሉን ተንከባካቢዎች ለመፋለም እንዲነሳ ያደርገዋል።ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ቅሉን ስበሩት ወይንም ኢትዮጵያንም እርስዎንም እስኪሰብርዎ ተቀምጠው ጠብቁት።ሁለተኛውን ምርጫ እንደማይመርጡ እርግጠኛ ነኝ።
==================////===========






Sunday, July 3, 2022

ሽብርተኛው ህወሓት የአፄ ዮሐንስን ራስ ደግሞ ቆረጠው።


=====
ጉዳያችን 
=====
በአባታቸው ከተንቤን በእናታቸው ከእንደርታ የሚወለዱት አጼ ዮሐንስ 4ኛ የነገሱት በቀድሞ ስማቸው ደጃች በዝብዝ ካሣ ተብለው በሚጠሩት ዘመን  ነበር ከአፄ ተክለጊዮርጊስ ጋር አድዋ አካባቢ ተዋግተው ካሸነፉ ብኋላ ጥር 13/1864 ዓም  አፄ ዮሐንስ ተባሉ። አፄ ዮሐንስ የመጨረሻ የንግስና ዘመናቸው ያበቃው በወቅቱ ደርቡሾች ዛሬ ሱዳን የሚባለው አገር የመጣ ሰራዊት ጋር ባደረጉት ውጊያ ነበር።ውጊያው መተማ አካባቢሲሆን በመጨረሻም በእዚሁ ቦታ ህይወታቸው አልፏል።በጦርነቱ ወቅት መጀመርያ የኢትዮጵያ ሰራዊት የበላይነቱን ይዞ ነበር። በጦርነቱ መሃከል ግን የአፄ ዮሐንስ መቁሰል ተሰማ።ይህም ለሱዳን ጦር የልብ ልብ ስለተሰማው አፄ ዮሐንስ ከቆሰሉበት ቦታ ደርሶ አንገታቸውን ቆርጦ ወደ ሱዳን በመውሰድ ካርቱም ገበያ ለገበያ እያዞረ በንጉሱ አንገት ቀልደዋል።

ይህንኑ አስመልክቶ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ፣የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847 እስከ 1983 ዓም በሚለው መጽሓፋቸው ላይ የሚከተለውን 
ብለዋል 

ሽብርተኛው ህወሓት የአፄ ዮሐንስን ራስ ደግሞ ቆረጠው

የኢትዮጵያ ጠላት መሆኑን ኢትዮጵያን በትነን ሲዖል እግባለሁ በሚል መግለጫ የሰጠው የህወሃት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ ትናንት በሰጠው መግለጫ ላይ ደግሞ የአፄ ዮሐንስ አንገት ከተቆረጠባት ዛሬም ታሪካዊ ጠላት ለመሆን የሚጥር መንግስት ካላት ከሱዳን ጎን ሆኖ ኢትዮጵያን እንደሚወጋ በግልጽ ተናግሯል። በአንድ ወቅት ኢትዮጵያ በከፍተኛ የስልጣን ዕርከን ላይ አስቀምጣው የነበረው በኢትዮጵያ እንጀራ ፊቱ የወዛው ጌታቸው ረዳ የሱዳንን ጦር የኢትዮጵያ መከላከያ ሊያስፈራራው አይችልም፣ሱዳን እንድትነካ አንፈልግም፣ከሱዳን ጎን ነው የምንቆመው፣ውለታ ውለውልናል እና ሌላም ሌላም ብሏል። የህወሃት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ የተናገረው ሁሉ በህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ ተወስኖ እንዲነገር የተወሰነ በመሆኑ ህወሃት በግልጽ ከሱዳን ጎን መቆሟን በእዚህ መግለጫ አረጋግጣለች።

ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ ሌላው የህወሃት ጥቁር ታሪክ ብቻ ሳይሆን መጪው ትውልድ የህወሃትን ፍጹም ኢትዮጵያን መክዳት እና ከባዕዳን ጋር የመተባበር አሳፋሪ ታሪክ ተመዝግቧል። እዚህ ላይ ታሪካዊ ጥያቄ ለትግራይ ህዝብ ይቀርባል። ህወሃት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከአክሱም እስከ ሽሬ እና በሌላው ህወሃት በሚቆጣጠረው የትግራይ ክልል ሁሉ ወርዶ የህወሃት ዓርማ ሲሰቀል፣አሁን ደግሞ የአፄ ዮሐንስን አንገት የቆረጠው የደርቡሽ አገር ኢትዮጵያን ሲወር አብረን እንቆማለን፣ዛሬም ኢትዮጵያን እኛ መበተን ስላቃተን ኢትዮጵያን ለመበተን የሚመጣ ጠላት የትግራይን ህዝብ እናሰልፋለን ሲል ሁሉ የትግራይ ህዝብ ምላሽ ምን መሆን አለበት? የሚለው ጥያቄ ነው።ይህ ጥያቄ በኢትዮጵያ የታሪክ መዝገብ ላይ የሚጻፍበት መንገድ በጥቁር እና አሳፋሪ ታሪክ ነው ወይንስ ስህተትን በሚያርም መልኩ ነው የሚለው የሚመለሰው የትግራይ ህዝብ ለህወሃት አሳፋሪ ተግባር በሚሰጠው ምላሽ ይወሰናል።

አሁን ያለው አሳፋሪው እና መጪው ትውልድ በጥቁር ቀለም የሚጽፈው ታሪክ ሽብርተኛው ህወሓት ኢትዮጵያን ለማወክ ከንቱ ድካም ከሚደክመው ከደርቡሽ አገር ሱዳን ጋር አብሮ በመቆም  የአፄ ዮሐንስን ራስ ደግሞ መቁረጡን ነው።
===========////=========


ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።