ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, May 30, 2017

የኢትዮጵያ ሀገር አድን የጋራ ንቅናቄ ከኢትዮጵያ ወቅታዊ እና መጪ የፖለቲካ ጉዳይ አንፃር (የጉዳያችን ዕይታ )


ጉዳያችን/ Gudayachn
ግንቦት 23፣2009 ዓም / May 31,2017 

መንደርደርያ ኢትዮጵያ በታሪካዊው ምርጫ ዋዜማ 

ወቅቱ ኢትዮጵያ አዲሱን ምዕመት ልትቀበል ሽር ጉድ እያለች የነበረበት ወቅት ነበር።በኢትዮጵያ በ1997 ዓም የተደረገው ምርጫ ውጤት በሕወሓት/ኢህአዴግ (የዚያን ጊዜው ኢህአዴግ) የኢትዮጵያ ሕዝብ በአደባባይ በግልፅ ከተካደ በኃላ የኢትዮጵያውያን ምሁራን ደት በአዲስ መልክ የተንቀሳቀሰበት ጊዜም ነበር።ከእዛን ጊዜ በፊት ለትምህርት ወደውጭ የሚሄዱ ወጣቶች ሁሉም ባይሆኑም የሀገሪቱ መንፈስ የምርጫ ንፋስ እየሸተተው እና ትውልዱም ከአሁን በኃላ በኢትዮጵያ ምድር ስልጣን በደም መፋሰስ ሳይሆን በሰላማዊ ምርጫ ሆን ነው የሚል ከፍ ያለ ሕልም ሁሉም ሰንቆ የነበረበትም ወቅት ሆኖ አልፏል።በተለይ በምርጫው ክርክር ወቅት ሁለት ነገሮች ገሃድ ሆኑ።አንድኛው ኢትዮጵያ ከሕወሓት/ ኢህአዴግ ውጭ እጅግ አቅም ያላቸው እና ሀገሪቱን በአጭር ጊዜ ወደተሻለ ደረጃ የማድረስ ርዕዩም ሆነ ልምዱ ያላቸው ምሁራን እንዳሉ በግልጥ ታየ። ሁለተኛው ሀገሪቱን የመራ ያለው ስርዓት ቀድሞ ሕዝብ ከሚያውቀው እና ከምገምተው በላይ ከአቅም በታች በሆኑ እንደ ወቅቱ አጠራር (ከአፍንጫ እንሰ ከንፈር ብቻ የሚያስቡ) ሰዎች የሞሉበት እንደሆነ ታወቀ።ብዙ ሰው አቶ በረከትን፣አቶ ስዩም መስፍንን እና ሌሎች የሕወሓት ባለስልጣኖች ቀድሞ ከሚያውቃቸው በታች እጅግ ዝቅ ያለ አቅም እንዳላቸው አወቀ። ማወቅ ዕዳ ነው እንደሚባለው ይህንን ማወቁ ቀድሞ ከነበረው የለውጥ ስሜት የበለጠ በናረ መልኩ ምርጫው ሃገርን የማዳን ራ አካል መሆኑን ሕዝብ አመነበት።ሃገርን የማዳን ሥራ የሚለው አስተሳሰብ በሕዝብ ዘንድ መስረፅ የጀመረው በቅርብ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ በሁሉም ሕዝብ ዘንድ የተናኘው በእዚሁ በከሸፈው ምርጫ ወቅት ነበር። ይህ ትክክል አስተሳሰብ ነው።የተሳፈርክበት መኪና ሹፌር ከአቅም በታች መሆኑን ስትረዳ መክናውንም አንተንም ሲቀጥል እራሱ ሹፈሩንም ለማዳን መነሳት ተገቢ ነው።የኢትዮጵያ ህዝብም ያደረገው ይህንኑ ነው።የበለጠ ሲያውቅ የበለጠ ሃገሩን ለማዳን በሰላማዊ መንገድ ቆረጠ

ከ1997 ዓም ምርጫ ክሽፈት በኃላ የኢትዮጵያውያን ስደት 

አመታት በነጎዱ ቁጥር የኅብረተሰብ አስተሳሰብ፣አኗኗር እና የትግል መንገድ ሁሉ ይቀየራል።ከ1997 ዓም ወዲህ ኢትዮጵያ በበርካታ አሰቃቂ የፖለቲካ ምች ተመታለች። ከአዲሱ ሚሊንየም ማለትም ከ2000 አመተ ምህረት ወዲህ ብቻ  የዓለም ምሁራንን ፍልሰት ስታትስቲክስ ጠቅሶ የሱዳን ትሪቡን ጋዜጣ እንደዘገበው በምሁራን ፍልሰት በአፍሪካ ቀዳሚ ኢትዮጵያ መሆኗን እና በዓለም አቀፍ ደረጃም ቀላል ታ እንደሌላት መዘገቡን የእዚህ ፅሁፍ ፀሐፊ ያስታውሳል።ባጭሩ በአሜሪካ፣አውሮፓ እንዲሁም አፍሪካ ሳይቀር ለትምህርት የተላኩ ወጣቶች ሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ሳይመለሱ የቀሩት በተለየ መልኩ ከ1997ዓም ወዲህ ነው። ይህ ሁኔታ በደርግ የስልጣን ዘመን የነበረ ቢሆንም ደርግ በወደቀባቸው የመጀመርያ ዓመታት የመሻሻል አዝማምያ ታይቶ ነበር። 

በንጉሡ ዘመን የምሁራን ስደት ችግር ተብሎ የማይታሰብ እንደነበር እና ለትምህርት የሄዱ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ይልቁንም የምረቃ ጊዜ ሳይደርስ ወደ ሀገር ት እየመጡ የዲግሪ ሰርተፍኬታቸው ይላክላቸው እንደነበር ወቅቱን የሚያስታውሱ የሚናገሩት ጉዳይ ነው። በእንግሊዝኛ የሚታተመው "ኢትዮጵያን ሄራልድ" እኤአ 2015 ህዳር 10 ቀን " The Menace of Brain Drain On Ethiopia's Development" በሚል ርዕስ ሥር ባውጣው ዘገባ ላይ እንዲህ የሚል ፅሁፍ ይገኛል።
 " Prior to 1974 revolution virtually all Ethiopians who attended university in the country remained at home and the vast majority of those who studied overseas returned to Ethiopia. According to one study, only one Ethiopian physician was working outside the country as recently as 1972. The brain drain has not always been a problem in Ethiopia.

" ከ1966 አብዮት በፊት በውጭ ሀገር ዩንቨርስቲዎች ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ከነበሩ ኢትዮጵያውያን ውስጥ ብዙዎቹ ወደ ሀገራቸው ይመለሱ ነበር።አንድ ጥናት እንደሚያሳየው በ1964 ዓም ከኢትዮጵያ ውጭ ቀርቶ ለሌላ ሀገር ይሰራ የነበረ ኢትዮጵያዊ አንድ ሀኪም ብቻ ነበር።የምሁራን ፍልሰት በእራሱ ለኢትዮጵያ ችግር ተብሎ የሚወራ አልነበረም"

የኢትዮጵያውያን ስደት  በሕወሓት ዘመን እጅግ የከፋ እና ኢትዮጵያውያን በየትኛውም ዘመን ደርሶባቸው የማያውቅ መከራ ነው።ድንበር የለሽ ሀኪሞች ድርጅት (MSF) የኢትዮጵያውያን ስደት ርነት ወደሚደረግባት የመን ጭምር መሆኑ ምን ያህል አሰቃቂ ጉዳይ በሀገራቸው እንደገጠማቸው የሚያመላክት መሆኑን በገለጠበት እኤአ 2008 ዓም  ላይ ያቀረበው አመታዊ ሪፖርት ላይ በአንድ ወቅት ከደረሱት ስደተኞች ላይ በተወሰደ መረጃ ከስደተኞቹ ውስጥ 30% ቶች ሲሆኑ የቀሩት 70% ወንዶችን ምሮ ከሁለቱም ታዎች ውስጥ 54% የሚሆኑት በትዳር ይኖሮ የነበሩ እና ትዳራቸውን ትተው የተሰደዱ መሆናቸውን ይገልጣል። ይህ በገሃዱ አለምም የምናውቀው እውነታ ነው።በአረብ ሃገራት ተሰደው ከሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን እናቶች በትዳር ላይ እንደነበሩ እና ልጆቻቸውን እና ባለቤቶቻቸውን ትተው የተሰደዱበት ጉዳይ የከፋ የምጣኔ ሀብት መገለል ይህም የፖለቲካ ተፅኖ ውጤት እንደሆነ የታወቀ ነው።ባጭሩ ግን ስደት የሀገር መፍረስ ዳርዳርታ ነው።እዚህ ላይ ሀገር ማዳን የሚለው ፅንሰ ሃሳብ ምን ያህል ጋ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን መረዳት አያስቸግርም።ጥያቄው ማን ነው ሃገርን የማዳን ኃላፊነት መውሰድ የሚገባው? የሚለው ነው።

የኢትዮጵያ አደገች ሮፓጋንዳ እና የስልጣን መጠበቅያ መሣርያነቱ 

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከአዲሱ ሚሊንየም (2000ዓም) ወዲህ በሀገር ቤትም ሆነ በውጭ ብዙ ጉዳዮች እየተቀያየሩበት መጥተዋል።በሀገር ውስጥ በምርጫ ማጭበርበር እፍረት ያልተሰማው ሕወሓት አቶ መለስን ከፊት አስቀድሞ ኢትዮጵያ እያደገች ነው የሚል አዲስ ትርክት ይዞ ብቅ አለ።አቶ መለስ ልማታዊ መንግስት መርሆዎች የሚል ፅሁፍ ሲበትኑ አጫፋሪ ካድሬዎች በሚገባ እንዲያዳንቁ ከተላለፈ ሚስጥራዊ ትእዛዝ ጋር ነበር።የአቶ መለስ ዜናዊ ልማታዊ መንግስት አገላለፅ ግን ውስጠ ወይራ መሆኗን ይልቁንም የአንድ ጎሳ የበላይነትን ለማውጣት ውስጣዊ አጀንዳ የያዘ ነው የሚሉ ብዙዎች ናቸው።ከላይ በሚታየው ገፅታው ግን የአቶ መለስ ዜናዊ ፅሁፍ የመንግስትን ሚና ሲገልፅ 
" Role of the government should be limited to the protection of individual and property rights, enforcement of contracts, and safeguarding competition among economic actors" 
" የመንግስት ሚና መሆን የሚገባው የግለሰብ መብትን  እና የንብረት መብትን ማስከበር እንዲሁም በምጣኔ ሃብቱ ውስጥ ለሚኖሩ የእርስ በርስ ውድድሮች ዋስትና መስጠት ነው" ይላል።ይህ አባባል ግን ከእውነታው እና በገሃዱ ዓለም አቶ መለስ እና አስተዳደራቸው ሲያደርግ ከነበረው ጋር ፈፅሞ የተቃረነ ነበር።በሕወሓት ዘመን መንግስት ለግለሰቦች ነፃነት እና ንብረት ዋስትና ሲሰጥም ሆነ ለጤናማ ውድድሮች ዋስትና  የሰጠው መቼ ነው? ሌላው ቀርቶ በከተማ ቦታ ይዞታ ላይም ሆነ በገጠር መሬት ላይ ኢትዮጵያውያን ካለምንም ዋስትና ከቦታቸው የተነቀሉት በሕወሓት ዘመን ነው።የአቶ መለስ ፅሁፍ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ባሉ ምሁራን ይህንን ያህል የከበደ ብቻ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ከልማት ጥናቶች የተገለበጠ መሆኑ ስለታወቀ ትኩረትን ከካድሬዎች ባለፈ አልሳበም። አቶ መለስ ግን በዙርያቸው ያሉትን የእራሳቸውን ተቀናቃኞች ለማጥቃት አዲስ ሃሳብ ይዘው የመጡ መስለው ታይተውበታል። 

ከእዚሁ ጋር ተያይዞ ሕወሓት እንደ ጊዜያዊ የአመፅ ማስታገሻ ክኒን የተጠቀመበት ኢትዮጵያ በሁለት ዲጅት እያደገች ነው የሚለውን አባባል ነው።ለእዚህም ከሙሰኛ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ኃላፊዎች ጋር በመሞዳሞድ ኢትዮጵያ አደገች የሚል ሪፖርት መዥጎድጎድ ጀመረ።ሆኖም ግን የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ባለሙያዎችም ሆኑ አቶ መለስ እና ስርዓታቸው አንዲት ሀገር በጠቅላላ ምርት ድምር በማስላት አደገች የሚለው መርህ በተባበሩት መንግሥታት የልማት ድርጅት (UNDP) ሳይቀር ከተተወ እና ሀገሮች ማደጋቸው የሚለካው በተለያዩ መስፈርቶች ማለትም እያንዳንዱ ግለሰብ ካለው የትምህርት፣የጤና፣የገበያ፣የዲሞክራሲ እና ነፃነት ዕድል አንፃር መሆኑን ያውቃሉ።ሆኖም ግን በዓለም አቀፍ መድረክም እድገትን አስር የማይሞሉ የስርዓቱ ሰዎች በጠቀራመጡት  ሀብት አንፃር ሪፖርት እያቀረቡ ህዝቡ አደገ እያሉ ሲናገሩ ምንም አይነት እፍረት አላሳዩም። በእዚህ በቁጥር ማምታታት የአፍሪካ ሀገሮች "ከእጅ አይሻል ዶማ" እንዲሉ በእየቤታቸው እሳት ስላለ የኢትዮጵያ እድገት እያሉ መለፈፋቸው አልቀረም። እዚህ ላይ ኢትዮጵያ እድገት ፈፅሞ የላትም በ1983 ዓም በነበረችበት ቦታ ነች እያልኩ አይደለም።የከተሞች ማደግ፣የግንባታ መስፋፋት እና የመንገዶች መገንባት አዎንታዊ ነገር ግን በብዙ ብድር እንደተሰሩ ይታወቃል።ጥያቄው ግን ይህ ልማት ነው ወይንስ የቁጥር እድገት ነው? የሚለው ነው። ልማት እያንዳንዱ ሰው ሕይወትን የማሻሻል ኃይል አለው።የእድገት ቁጥር ግን የጥቂቶች ሀብታምነትን እና የብዙሃኑን የምጣኔ ሀብት ባርያ መሆንን ያሳያል። 

ኪኒን ጨምርልኝ    

የሕወሓት የራስ ምታት ክኒን ማለትም አድገናል የሚለው ፕሮፓጋንዳ ለጥቂት ጊዜ ጎማውን ለማሽከርከር ጠቀመው እንጂ ብዙም  አላራመደውም ይልቁንም 11% የምትለዋ ትርክት በእየሻይ ቤቱ መቀለጃ ሆነች።ከ1997 ዓም የምርጫ ክህደት በኃላ ሕወሓት ሕዝቡንም ሆነ ሚድያውን በሥራ የወጠረባቸው ጉዳዮች የመጀመርያው የሚሊንየም አከባበር ግርግር በመቀጠል የልማታዊ መንግስት ሃሳቦች ፕሮፓጋንዳ እና ኢትዮጵያ በሁለት ዲጅት አደገች የሚሉት ሁሉም ብዙ እርቀት አላስኬድ አሉ። የእዚህን ጊዜ አዲስ ሕዝብ የሚወጥር ጉዳይ ይዞ መምጣት ተፈለገ።የአባይ ግድብ፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ግድብ ካርድ ተመዘዘ። ይህ የግድብ ሥራ ለኢትዮጵያ ያለው ጥቅም ምንም የለም ከሚል እሳቤ መነሳት አይቻልም።ጉዳዩ ከቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ ዘመን ጀምሮ ብዙ ተብሎበታል።በንጉሱም ዘመን የተያዙ እቅዶች እንደነበሩ እና የግብፅ ደህንነቶች በብርቱ ጉዳዩን ሲከታተሉ እንደነበር ይታወቃል። ስለሆነም ግድቡን በጭፍን ማጥላላት በጎ ሃሳብ አይደለም።እስካሁንም በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ የሚኖር ኢትዮጵያዊ የእዚህ አይነት ሃሳብ ሲያንፀባርቅ አልታየም።የስርዓቱ ደጋፊዎች ግን ለፕሮፓጋንዳ በውጭ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ያላለውን ሲናገሩ ግን ተሰምተዋል። የኢትዮጵያ ሌቭዥንም አስተጋብቶላቸዋል። የአባይ ግድብ ጉዳይ በሕወሓት በኩል ሲቀርብ ግን ታስቦበት እና ታልሞ ሳይሆን የመቆያ ክኒን ጨምርልኝ መልክ ነው።ሕዝብ የሚወጥር፣በተስፋ የሚያስፈነድቅ እና ሕወሓትን ጀግና የሚያስብል ሃሳብ ተደርጎ ተወሰደ።ለእዚህም ማስረጃው እቅዱ በአምስት ዓመቱ የልማት እቅድ ላይ የሌለ እና የበጀት ምንጩም የድሀውን ኢትዮጵያዊ ጎጆ የበለጠ የሚያሟጥጥ መሆኑ ነበር።በሌላ በኩል ሕወሓት የመጀመርያ የአባይ ቦንድ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ዋሽንግተን ላይ ሲያዘጋጅ ጀምሮ ኢትዮጵያውያንን አርቲስት እና አክቲቪስት ታማኝ በየነን ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን በስብሰባው ለመሳተፍ ሲሄዱ ከበር ላይ እየመረጠ አስቀራቸው።በእዚህም የአባይ ጉዳይ የኢትዮጵያውያን ሁሉ ጉዳይ ሳይሆን የፖለቲካ መሳርያ መሆኑን በይፋ አወጀ።

በአባይ ግድብ ጉዳይ ላይ ኢትዮጵያውያን ምሁራንም ሆኑ የውጭ ባለሙያዎች የሚሰጡት ሁለት መሰረታዊ ሃሳቦች አሉ። በቅድምያ ግን ኢትዮጵያ ከፍተኛ የውሃ ማመንጨት አቅም እንዳላት እና ይህንን መጠቀም እንዳለባት የሁሉም ስምምነት ነው።ምሁራኑ ግን የሚያነሱት ሁለት ነጥብ።አንደኛ ኢትዮጵያ በእርሻ ምርት እራሷን ሳትችል ይህንን ያህል ግዙፍ የሀገር ሀብት የሚበላ ፕሮጀክት ላይ ሙሉ ኃይሏን ማሳረፍ ሃገሩን ሊያፈርስ የሚችል አደገኛ ውሳኔ ነው የሚል ነው።ለእዚህም ማስረጃው ፕሮጀክቱ የመንግስትን ለልዩ ልዩ ወጪ መዋል የሚገባው ሀብት ከመውሰዱ በላይ እያንዳንዱ ምስኪን ኢትዮጵያዊም ከጉሮሮው እየነጠቀ እንዲያዋጣ ማድረጉ በእራሱ ድህነትን ማስፋፋት ነው የሚል ሲሆን። ሁለተኛው ደግሞ በአሁኑ ዘመን ግዙፍ ግድብ መገንባት በጥቂት አመታት ውስጥ ግድቡ በደለል ሲሞላ ግድቡን ለማፅዳት የሚጠይቀው ወጪ በእራሱ የግድቡን መስርያ ለማከል ይቃጣዋል የሚል ነው።ለእዚህም አማራጭ የሚያቀርቡት በአውሮፓም ሆነ ሌሎች ሃገራት እንደሚደረገው በርካታ አነስተኛ ግድቦችን ማብዛት እና ኤሌክትሪክ ማመንጨት ይቻላል።ይህም ከፀጥታ ጥበቃም ሆነ የመስኖ ስራን ከማስፋፋት አንፃር ብዙ ጥቅም አለው የሚለው ይጠቀሳል።

ከእዚህ በተለየ ግን የሕወሓት መንግስት በግድቡ ግንባታ ላይም ካለጨረታ የሰጠው የጣልያኑ ኩባንያ እና የሕወሓት የንግድ ድርጅቶች በስራው ላይ ካለምንም ተቀናቃኝ መግባት የግንባታውን አላማ ከላይ ከተጠቀሱት ችግሮች በላይ አላማ እንዳለው የሚናገሩ ብዙዎች ናቸው።ይህም ሆኖ ግን አሁን አሁን ስለ ግድቡ ጉዳይ መሰረት የተጣለበትን ዓመት ከማክበር ባለፈ ወሬው እየራቀ መምጣቱ የብዙ ኢትዮጵያውያን የሹክሹክታ ወሬ ሆኗል።  

ከሶስተኛው ክኒን በኃላ የአቶ መለስን ሞት ተከትሎ ህወሓት ለማስታገሻነት የተጠቀመበት ነገር ግን ምንም ፍሬ ያልያዘለት የጥልቅ ተሃድሶ ጉዳይ ነበር።አቶ ኃይለማርያም ትልቅ ተሃድሶ፣ሙስና እያሉ ጫፍ መናገር ስጀምሩ በደረሰባቸው ከባድ የአንድ ወገን ምት አሁን ሙስና የምትል ቃል ከንግግራቸው አውጥተው እና ለገሃር ላይ የሚገኘው የፀረ ሙስና ሚሽን መስርያ ቤት ሲፈርስ እና በአርብቶ አደር መስርያ ቤት ሲገባ የመክሰስ መብቱም በፖሊስ ኮሚሽን ስር ሲወድቅ እያዩ ድምፃቸውን አጥፍተዋል።

የኪኒን ጋጋታ ያላስቆመው ሕዝብ ሆ! ብሎ ተነሳ 

ሕወሓት በእየዘመኑ ያወጣቻቸው የማስታገሻ ኪኖች አለምስራታቸው ብቻ ሳይሆን ህዝብን ዘላለም ማታለል አይቻልም እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ከእየአቅጣቸው በስርዓቱ ላይ ተነሳ።በባዮሎጂ ትምህርት አንድ ባክተርያ ለማጥፋት በተደጋጋሚ የምትሰጠው መድሃኒት ከእረጅም ጊዜ በኃላ ባክቴርያም ሊለምደው እና የመገዳደር አቅሙን ሊያጎለብትበት እንደሚችል ይገለጣል። የኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግር ማለትም የነፃነት፣የዲሞክራሲ፣የፍትህ እና የእኩል ተጠቃሚነት ችግሮች ሳይፈቱ ሕወሓት  እራሷን እና ደጋፊዎቿን ለመደለል ያቀረበችው ክኒን ሁሉ አልሰራ አለ። ሕዝብ በቃኝ ብሎ ተነሳ።በኦሮምያ፣በዐማራ፣ጋምቤላ፣አፋር፣ቤንሻንጉል ወዘተ አመፆች ተቀጣጠሉ። 

በመጀመርያ ደረጃ ሕወሓት አመፆቹን የአካባቢው የአስተዳደር ችግሮች እንጂ የብሔራዊ ጉዳይ አይደሉም በሚል ዝቅ ለማድረግ ብዙ ጥረት አደረገ።እውነታው ግን ይህ አልነበረም።አመፆቹ እያየሉ በአስር ዎች ወደ እስር ቤት እየተጋዙ ብዙ ሺዎች እንደወጡ የቀሩበት ሕወሓት ላለፉት 26 ዓመታት ገጥሞት የማያውቀው የህዝብ የቆረጡ ድምፆች ነበሩ። በመጨረሻ ግን አመፁ እንደማይቻል ሲታወቅ አስቸይ ጊዜ አዋጅ በያዝነው 2009 ዓም መጀመርያ ላይ ታወጀ።ሕወሓት አዲስ የሞት ድግስ የያዘ ክኒን ይዛ ብቅ አለች።የኮማንድ ፖስት የሚባል  ክኒን። የኮማንድ ፖስት የተሰኘው ክኒን ግን እራሷን ህወሓትን ይዞ ወደ ሞት የሚያወርድ መሆኑን በደንብ አላወቀችውም ማለት አይቻልም።አማራጭ ስታጣ የተገኘውን ሁሉ መድሃኒት ነው ብሎ መውሰድ ተስፋ የቆረጠ ሰው ተግባር ነው።ሕወሓትም ተስፋ ቆረጠች።አዋጅ አወጀች።አዋጁ ስድስት ወር ላይ ያበቃል ተብሎ ህወሀትን ሊያሽላት ስላልቻለ አላዋቂ ሀኪሞች የሕውሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ተሰበሰቡ እና እንደገና አራዘሙት።
  
የቅርቡ የኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ፖለቲካ ለውጦች  

የሕወሓት የሞት ድግስ የያዘው አዋጅ በእዚህ ዓመት ከመታወጁ ቀድም ባሉት ወራትም ሆነ ወዲህ በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ላይ አዳዲስ የሚባሉ የቅርፅ እና የይዘት ለውጦች መታየት ጀምረዋል። በሀገር ውስጥ የሕወሓት ተጣማሪ እንደሆኑ የሚናገሩት ብአዴን እና ኦህዴድ ተፈረካክሰው የቀራቸው አንዳንድ ምልክቶች ናቸው።ሕወሓት ግን አሁንም እንደሚመቹ አድርጎ እንደገና ለመጠገን ሙከራ እያደረገ ነው።ያለፉት አይነት አሻንጉሊት አድርጎ ለመቅረፅ ግን ፈፅሞ የማይቻል ሆኗል።ምክንያቱም አመፆቹ የተነሱት ከታች ካለው ሕዝብ እስከ ማዕከላዊ አመራር ደረጃ ባሉት ሁሉ ስለሆነ ይህንን ሁሉ መጠገን በእራሱ ሕልም ሆኖ ቀርቷል። እዚህም ላይ ሕወሓት አንዳንድ መጠቀም የፈለጋቸው  አዳዲስ እና አስቂኝ ኪንኖች ብልጭ ብለዋል። ለምሳሌ የኦሮምያ የኢኮኖሚ አብዮት እና የዳሸን ቢራ ጉዳይ ይጠቀሳሉ።የኦሮምያ የኢኮኖሚ አብዮት ምንም አይነት የፖለቲካ ስልጣን የሌለውን ኦህዴድ በተስፋ ዳቦ መሬቱ እና በመሬቱ ላይ ያሉ መዋለ ንዋይ ሁሉ ያንተ ነው የሚል ቃላት እየተጠቀሙ የነበረውን ጥቂት ስራዎች ማወክ ከተያዘ ሰነባብቷል።በእዚህም ክልሉን የበለጠ ወደ ኃላ የመውሰድ እና በመጨረሻ ሕወሓት ሲረጋጋ ከአዲስ እቅድ ጋር ለመዋጥ መሆኑን የማይረዳ ሰው የፖለቲካ ሀሁ ገና ያልተገለጠለት ሰው ብቻ መሆን አለበት።

ሌላው በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ላይ የታዩት አዳዲስ ክስተቶች ውስጥ በተለይ በውጭ ሃገራት መሰረታቸውን ያደረጉቱ ውስጥ የዐማራ የዘውግ ድርጅቶች መሰባሰብ እና የአርበኞች ግንቦት 7 ጥምረት ከሌሎች ድርጅቶች ጋር የሚሉት ዋነኞቹ ናቸው።የዐማራ የዘውግ ድርጅቶች በመጀመርያ መነሻ አመታት ላይ በርካታ ጥያቄዎችን አስነስተው ነበር።በመጀመርያ ደረጃ የነበረው በሶሻል ሚድያ ላይ ከመብዛታቸው የተነሳ የጥያቄዎቹ ቅርፅ ብዙ ክርክሮች አስነስተው ነበር።ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ በዋሽንገተን ከተደረገው ዓለም አቀፍ የአማራ ጉባኤ ወዲህ የድርጅቶቹ መሰባሰብ በተወሰነ መልኩ እየታየ ነው። በተለይ የዐማራ የዘውግ ፖለቲካ የፅንፈኛ የዘውግ ፖለቲካን የማስፋፋት ዕድል ይፈጥራል ለሚሉ ሃሳቦች በእዚሁ በዋሽንግተኑ ጉባኤ ላይ ወረቀት ካቀረቡት ውስጥ የዳግማዊ መዐሕድ የውጭ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ምስጋናው አንዱ ዓለም የዐማራው መደራጀት የፅንፈኛ ፖለቲካን የሚያከሽፍ መሆኑን ሲገልጡ : - 

የአማራው የአማራነት ጥያቄዎች ግን ይሄንን እንደልብ ሲፈነጭ የቆየ የአክራሪ ብሄረተኞች አደጋ ሚዛን በመስጠት ያረግበው ነበር። አማራው ራሱን ችሎ እንደ አንድ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሀይል ብቅ ማለት የእነዚህ አክራሪ ብሄረተኞች ህልውና መክሰም መንስኤ ነው። ለዛ ነው ብንዘገይም እንኳ አሁንም በቶሎ አማራዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ይሄንን ሁሉ ለአርባ አመት የተዛባ ሚዛን ማስተካከል ታሪካዊ ግዴታችን የሆነበት ጊዜ ላይ ነን የምንለው" ብለዋል። 

በእርግጥ ይህ አባባል በእራሱ በርካታ የተቃርኖም ሆነ የሚደግፍ ሃሳቦች ሊንሸራሸሩበት ይችላሉ።ጉዳዩ ፖለቲካም ነው እና አንዳንድ ሁኔታዎች የሚያመጡት በጎም ሆነ በጎ ያልሆነ ተፅኖ ለመፈተሽ የጊዜ እና የአካባቢያዊ ለውጦችን በሚገባ መፈተሽ ይጠይቃል። 

በሌላ በኩል በኢትዮጵያ አንድነት ጎራ ቀዳሚ ሚና የያዘው የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የእራሱ የሆነ ስልታዊ መንገዶች እየሄደ መሆኑን መመልከት ይቻላል።ድርጅቱ በመጀመርያ ከነበረበት ወደ ኤርትራ ለምን? የሚሉ ጥያቄዎች አልፎ አሁን ውጤቶችን የመለካት ደረጃ ላይ ደርሷል።በማኅበራዊ ሚድያ ላይ በጭፍን የሁሉንም የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶች በመተቸት የማጥላላት ዘመቻ ላይ የተጠመዱቱን ትተን ለሀገር በመቆርቆር የአርበኞች ግንቦት 7 ከሚነሳበት ወቀሳ አንዱ ጥምረት በዛ የሚል ነው።

"ድርጅቶች በዙ እና ጥምረት በዛ"  የቀድሞ እና የዘንድሮ ወጎ

በቀደሙት አመታት ይሰሙ የነበሩ ድርጅቶች በዙ የሚሉ ድምፆች በአሁኑ ጊዜ ጥምረት በዛ የሚሉ ሆነው ማግኘት በራሱ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ከማናቸውም አይነት ትችት እንደማይድን አንዱ ምስክር ነው።በተለይ የአንድነት ድርጅቶች ከብሄር ድርጅቶች ጋር መቀናጀት ለመፍጠራቸው መሰረቱ ምንድን ነው? የሚለው ጥያቄ በእራሱ የወቅቱ ጥያቄዎች ውስጥ አንዱ እና ጎልቶ እየወጣ ያለ ጥያቄ ነው።እዚህ ላይ ግን ድርጅቶች በዙ በተባለባት ሀገር ውስጥ ጥምረት መብዛቱ በእራሱ ችግር ሊሆን ይችላል ወይ? ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው።ስለሆነም ጥምረት መፈጠሩ በእራሱ በአደጋነት ሊፈረጅ አይገባም ማለት ነው። ከእዚህ ይልቅ የሚፈጠሩ ጥምረቶች ያላቸው በጎ እና በጎ ያልሆኑ ጎኖች ምንድናቸው? ብሎ መፈተሹ ተገቢ ነው።የኢትዮጵያ ሀገር አድን የጋራ ንቅናቄ ከኢትዮጵያ ወቅታዊ እና መጪ የፖለቲካ ጉዳይ አንፃር መፈተሹ አስፈላጊ የሚሆነውም እዚህ ላይ ነው።

ፖለቲካ ከግለሰቦች ስብዕና በላይ የዘለለ ተልዕኮ አለው 

 በአርበኞች ግንቦት 7 እና የብሔር ድርጅቶች መካከል የተደረጉት የጥምረት መግለጫ ለመጀመርያ ጊዜ የተሰማው በ ጉሜ 3፣ 2007ዓም ምሽት ነበር።

በእዚህ ዜና ላይ በኤርትራ የሚንቀሳቀሱ አራት በትጥቅ ትግል የተሰማሩ ኃይሎች  የጋራ ንቅናቄ መመስረታቸው ተነግሮ ነበር።በእዚህም መሰረት 

1ኛ/ የአፋር ድርጅቶች የጋራ ንቅናቄ

2ኛ/ የትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣

3ኛ/ የአማራ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ እ

4ኛ/ አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅና

 በጋራ ለመስራት በመስማማት የኢትዮጵያ ሀገር አድን በዲሞክራሲ የጋራ ንቅናቄን  መመስረታቸውን አስታውቀዋል። በእርግጥ የትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት እና የአማራ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ በጥምረቱ ላይ ለመቀናጀት የሚቀሩ ስራዎች እንዳሉ መጠቀሱ እና ደት ላይ ነው መባሉ ይታወሳል። 

በቅርቡ በጥቅምት ወር 2009 ዓም  ጥምረት የተፈጠረበት መድረክ ደግሞ በአቶ ሌንጮ ለታ እና በምክትላቸው ዲማ ነገዎ የሚመራው የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግምባር፣ በፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የሚመራው አርበኞች ግንቦት 7፣ በዶ/ር ኮንቴ ሙሳ የሚመራው የአፋር ህዝብ ፓርቲና አቶ በቀለ ዋዩ የሚመራው የሲዳማ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ የተመሰረተው ነው።ይህ ጥምረት በኢትዮጵያ የመልክዓ ምድር ሽፋን አንፃር የተሻለ መሠባጠር የታየበት ሲሆን የሚነሱበት ሁለት ጥያቄዎች ግን አሁንም አሉ። እነርሱም ጥምረት የፈጠሩት ድርጅቶች በተለይ የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር በአሁኑ ወቅት ያለው ተሰሚነት ምን ያህል ነው የሚል እና የድርጅቱ መሪዎችም በ1984 ዓም አካባቢ በዐማራ ላይ በተነሱ ጭፍጨፋዎች እጃቸው አለ የሚሉ ናቸው።ሆኖም ግን ግለሰቦችን ከድርጅቶች ነጥሎ ማየት እና ግለሰቦቹ አጠፉ የሚባለውን ጥፋት በውጭ ሃገራት የመክሰስ መብት ያለው ኢትዮጵያዊ የተባለው ማስረጃ አሰባስቦ ከመጠየቅ ይልቅ በፖለቲካ መድረኩ ላይ መታየታቸው ብቻ ጥፋት እንደሆነ መገለፁ አስቸጋሪው ጉዳይ ነው።ከእዚህ በተለየ ደግሞ አሁንም ጥምረቱ ለምን ዐማራዊ ድርጅቶችን አላቀፈም የሚለው ጥያቄ ነው።ሆኖም ግን ጥምረቱ ለእነኝህ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠቱ እንዳለ ሆኖ የድርጅቶች ጥምረት በእራሱ ለኢትዮጵያ መጪ የፖለቲካ ሁኔታ በእራሱ እንደ አደጋ ሊታይ ፈፅሞ አይችልም። ምክንያቱም ፖለቲካ ከግለሰቦች ስብዕና በላይ የሆነ ተልዕኮ ስላለው ነው።ግለሰቦች በግለሰቦች ይተካሉ። የፖለቲካ መስመሩ እና ዓላማው እንዲሁም ድርጅታዊ አቅም ግን የሚገነባው በአባላቱ እና በመላው ሕዝብ ፈቃደኝነት ነው።

ኢትዮጵያዊ ውል በአስተማማኝ መልኩ መልሶ ሳይታሰር ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ማውራት እንዴት ይቻላል?

በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያን ፖለቲካ ማንም በማኅበራዊ ሚድያ ውስጥ ገብቶ የሚተችበት አደገኛ ዕድል ፈጥሯል።አደገኛ ያልኩበት ምክንያት በሙያው በበሰሉ ሰዎች ሳይሆን በግብታዊነት እና ሻይ እና ቡና ሲጠጡ በሰሙት ውይይት ላይ ብቻ ተመርኩዘው ያንንም እንደ ትልቅ የእውቀት ምንጭ እየቆጠሩ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ድርጅቶች ሳይንሳዊ ባልሆነ መልክ የሚተቹ መብዛታቸው እና ሕዝብ ማሳሳታቸው እጅግ አደገኛ ክስተት ነው። በማናቸውም ጥምረት ላይም ሆነ አደረጃጀት ላይ ማንኛውም አይነት ጥይቄዎች፣አስተያየቶች እና ስጋቶች ሊገለጡ ይችላሉ። ጥምረት እና መተባበር ግን በእራሱ አደጋ ሊሆን ፈፅሞ አይችልም።

የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ በርካታ ተቺዎች የሚያነሱትን ያህል ለኢትዮጵያ አደጋ ነው ወይ? የአቅም፣የአፈፃፀም እና የታክቲክ ጉዳዮች ሊነሱ ይችላሉ።እነኝህ በሂደት እየጠሩ የሚሄዱ አበይት አስፈላጊ ጉዳዮች ናቸው።ጥምረት መፍጠር፣መወያየት፣በመጪው የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ በሰለጠነ መልክ መደራደር ግን ለነገ የማይባሉ ዛሬ መጀመር ያለባቸው ቁልፍ ተግባራት ናቸው።የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ከኦሮሞ፣አፋር እና ሲዳማ ጋር ብቻ ሳይሆን በቅርቡ በጀርመን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በተገኙበት ከኦጋዴን ተቃዋሚ ኃይል ጋር የጋራ መግባብያ ሰነድ ተፈርሟል።ውጤታቸው አመርቂ ይሁንም አይሁን እነኝህ ተግባራት ለነገዋ ኢትዮጵያ ወሳኝ ተግባራት ተደርገው መወሰድ አለባቸው። 

ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚደገሱ የባዕዳንም ሆኑ የስልጣን ጥመኛው ስርዓት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገም የሚሆን እልቂት ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንደሚያዘጋጁ የታመነ ነው። ብልህ ፖለቲከኛ ደግሞ በዛሬ ላይ ብቻ ሳይሆን በነገ አደጋዎች ላይ ከአሁኑ እያነጣጠረ እና ችግሮችን የመፍታት ሥራ እየጀመረ መሄድ ዋና ተግባሩ ነው።ሕወሓት ከስልጣን ቢወርድም የኦጋዴን ጉዳይ ሆነ የአፋር ሁኔታ በተወሰነ ደረጃ ለመጪው የኢትዮጵያ ፀጥታም ሆነ ልማት ቀላል የማይባል መንገጫገጮችን ማስከተሉ ሳይታለም የተፈታ ነው። ስለሆነም ዛሬ ላይ በጋራ ርዕይ ላይ የተመሰረተ የኢትዮጵያዊነት ውል ላይ መነጋገር፣መተማመን እና ቢያንስ መስማማት ባይቻል ተቀራርቦ መነጋገር በእራሱ ለነገዋ ኢትዮጵያ ላይ አንድ ብሩህ እርምጃ ነው። ኢትዮጵያዊ ውል በአስተማማኝ መልኩ መልሶ ሳይታሰር ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ማውራትስ እንዴት ይቻላል? ስለሆንም ሃገራዊ ንቅናቄውን በሚገባ መረዳት እና ዘግይተንም የምንመጣው ወደ እንደዚህ አይነቱ ንቅናቄ በመሆኑ ከአሁኑ መስተካከል የሚገባውን እያገዙ ጅምሩን ማበረታታት ከአንድ ንቁ ኢትዮጵያዊ የሚጠበቅ ተግባር ነው።ሃገራዊ ንቅናቄው በአሁኑም ሆነ በመጪው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ የሚከተሉት አዎንታዊ ተፅኖዎች መፍጠር ይቻላል። እነርሱም ; -

1/ ትልቅ ሃገራዊ ግንባር የመፍጠር አቅም ይኖረዋል፣

2/ በነገዋ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ በሂደት በሚመጣ ለውጥ ከብሄር አስተሳሰብ ወደ ሃገራዊ አጀንዳ ላይ የተመሰረተ አደረጃጀት እንዲዳብር ይረዳል፣

3/ በነገዋ ኢትዮጵያ ላይ አዲስ የግጭት አጀንዳ ለመፍጠር ለሚፈልጉ ባእዳን መንገዱን ይዘጋል፣

4/ በመጨረሻም የኢትዮጵያ ህገ መንግስታዊ ስርዓትም ሆነ የሀብት እኩል ተጠቃሚነት የተረጋጋ ያደርጋል።

ባጠቃላይ ስለ ኢትዮጵያ ስንናገር ስለመላዋ ኢትዮጵያ መሆኑን እርግጠኛ መሆን አለብን።መላዋ ኢትዮጵያ ደግሞ የተለያዩ አመለካከቶች፣የፖለቲካ ብስለቶች፣ ባህላዊ አመጣጦች እና ምጣኔ ሃብታዊ መሰረቶች አሏት። ይህንን ሁሉ አስተባብሮ ወደ አንድ ሀገር ጉዳይ ለማምጣት በእራሱ ጥበብ፣ትዕግስት እና ፅናት ይጠይቃሉ። 

ብዙዎቻችን የዘመኔ ሰዎች በፅሁፎች መካከል የአውሮፓውያን ምሁራን እና ታዋቂ ሰዎች የተናገሩት ንግግር የማድነቅ ሆኖም ግን የሀገራችን ሰዎች (ዓለም ያደነቃቸው) አባባሎች ብዙም ትኩረት አለመስጠት አባዜ ተጠናውቶናል።በመሆኑም ለእዚህ ፅሁፌ መደምደምያ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ ለሀገራቸው በሚሰሩት ሥራ ላይ ምን ያህል የአላዋቂዎች ወሬ ያውካቸው እንደነበር በገለፁበት አረፍተ ነገር  ላይ የተጠቀሰው አነጋገር  የኢትዮጵያን ሃገራዊ አንድነት ለማቆም እና ኢትዮጵያዊ ውል በአስተማማኝ መልኩ መልሶ ለማሰር መፅናት እንደሚገባ አመላካች ሆኖ ስላገኝሁት በእዚሁ ፅሁፌን ልደምድም። ንጉሡ በእራሳቸው እጅ በፃፉት "ሕይወቴ እና የኢትዮጵያ እርምጃ" በሚለው መፅሐፋቸው መግቢያ ላይ እንዲህ ነበር ይሉት : - 

      " የተበላሸውን ለማቅናት፣ያልተጀመረውም ሥራ እንዲጀመር ለማድረግና አዲሱን ስልጣኔ ለማግባት  እሳቤና ይልቁንም አሮጌውን ልማድ ለሚወደው ሕዝብ አጋዥ ስለነበረው በሁለት ብረት መካከል እንዳለ እንጨት አጣብቀውኝ የተቻለኝን እየሰራሁ ጊዜውን አሳለፍኩ።በመዝናናት ሰውነትን ደስ የሚያሰኝ ሥራ በመስራት የማሳልፈው ጊዜ ጥቂት ነበር።ከተጀመረው ከሀገሩ ውስጥ ሥራ ያቃናሁትና አዲስ የሰራሁት፣ከውጭ ሀገርም የስልጣኔ ሥራ በሀገር ውስጥ እንዲገባ ያደረግሁት በእየተራ ተፅፎ ይገኛል።በእዚህም ላይ የአዲሱ ስራችን መሰናክል የሚሆን በውስጥ ወይንም በውጭ ሰዎች የሚወራ አንዳንድ የውስጥ እና የውጭ ችግር በእየጊዜው ይደርስብን ነበር እና ሽብር እንዳይሆን እና የሰው ደም እንዳይፈስ በጎሳ መለያየትን እንዳይስከትል ስራውን ሁሉ በትግስት መስራት የሚያስፈልግ ሆነ
ሕይወቴ እና የኢትዮጵያ እርምጃ፣ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ፣1965።


ጉዳያችን GUDAYACHN 

 www.gudayachn.com


ዋቢ ማጣቀሻዎች 
===============

- Development state, Meles Zenawi, 2012

- Ethiopian Herald, Nov.102015

- MSF Report, 2008

- Zehabesha, 2016

- ሕይወቴ እና የኢትዮጵያ እርምጃ ፣ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ፣1965 

Wednesday, May 24, 2017

ምን ይሆን ችግራችን? መንፈሳዊ ግጥም በወ/ሮ አፎምያ ሚካኤል ኦስሎ፣ኖርዌይ (ኦድዮ)

ገጣሚት ወ/ሮ አፎምያ ሚካኤል




ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Wednesday, May 17, 2017

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ኢትዮጵያን የማዳን ኃላፊነት ከመቼውም ጊዜ በላይ እየገዘፈ መጥቷል። (የጉዳያችን ማስታወሻ)



 "ጆሮን የተከለው አይሰማምን? ዓይንን የሠራው አያይምን? አሕዛብንስ የሚገሥጸው፥ ለሰውም እውቀት የሚያስተምረው እርሱ አይዘልፍምን? የሰዎች አሳብ ከንቱ እንደ ሆነ እግዚአብሔር ያውቃል" መዝሙር 94፣ 9

ሁከት በዝቷል፣ጨዋነት ጠፍቷል፣ ኢትዮጵያውያን እርስ በርስ በጎሳ እንዲከፋፈሉ ሆነው በእራሷ በመገናኛ ብዙሃኗ እኩይ የክፍፍል ወሬ እየተነዛባት ነው።ትውልዱ በአራቱም አቅጣጫ እየተሰደደ ነው።ሰርቆ ህንፃ ያቆመ የሚደነቅባት፣ለፍቶ ሰርቶ የሚያድረው የሚናቅበት፣ሹማምንቷ የሀገሪቱን ገንዘብ በጠራራ ፀሐይ ይዘው ሲወጡ ከለንደን እስከ ታይላንድ አየር መንገዶች ላይ የሚያዙበት፣መሪ ተብሎ የተቀመጠው ሰው በቴሌቭዥን ሕፃናት ሳይቀሩ ሲያዩት ውሸት የሚያወራው የተባለበት፣ስታድዮም ውስጥ አብሮ ለመጫወት አንተ ከእዚህኛው ክልል አንተ ከእዝያ ማዶ ነህ እየታባባለ የሚቧቀስበት፣ ባለስልጣናቱ ሁሉ መድረክ ላይ ወጥተው ከኢትዮጵያውነታቸው ይልቅ ከእዚህ ዘር ነኝ የመጣሁት የሚባባሉበት፣ኢትዮጵያ ሴት ልጆቿ ከወላጆቻቸው ጋር ወግ ማዕረግ በማየቻቸው የአፍላ ወጣትነት ጊዜያቸው ለአረብ ሀገር የፈተና ሥራ ፍዳ የሚያዩበት፣ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ሆነች ሌሎች የእምነት አካላት ሁሉ በቀጥታ በፖለቲካ ጣልቃ ገብነት የተሾሙበት፣ ሕዝብ ሃዘን ላይ የሚገኝበት ወቅት ነው።

ይህ ብቻ አይደለም ወቅቱ ዓለም የኢትዮጵያን አካሄድ በጥንቃቄ እያየ እየተሳቀቀ እና ግራ እየተጋባ ያለበት ወቅት ነው። ወዲህ አዋጅ ያወጀበት ሕዝብ ላይ እልቂት የሚፈፅመው ስርዓት በእውር ድንብር አካሄድ ያገኘውን እያሰረ እና እየገደለ ልጆቿን እያሰቃየ በሌላ በኩል ኢትዮጵያን በባዕዳን ስትከበብ ሁሉ ምንም እንዳልሆነ ከማታለል በላይ የኢትዮጵያን ህልውና ከሚፈታተኑ ሁሉ ጋር ግንባር እየፈጠረ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ጦርነት ያወጀበት ነው።በሕወሓት እና ሱዳን መካከል የተደረገው ስምምነት ክርስቲያኑን ሕዝብ በመግደል እና በመጨረስ አላማ ላይ ያለመ ነው።ኢትዮጵያውያን ከውስጥ እሳት ከውጭ ረመጥ ሆኖባቸው መከራቸው እየባሰ ነው።

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ሆነች ሌሎች የእምነት አካላት ሁሉ ከላይ በተጠቀሰው ፈተና ውስጥ የተዋጡ መሆናቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው።በኢትየጵያ ቤተ ክርስቲያን አንፃርም እነኝህ ፈተናዎች እና የስርዓቱ ቤተ ክርስቲያኒቱን የማጎስቆል እና የማዳከም ተከታታይ ሥራ ላለፉት 25 ዓመታት ተሰርቷል።ባለፉት 25 ዓመታት የስርዓቱ ዕቅድ ቤተ ክርስቲያኒቱን አሁን ካለችበት ደረጃ በበለጠ መልኩ መቆጣጠር እና ማዳከም ቢሆንም የተሸረበውን እኩይ ዕቅድ ስርዓቱ በፈለገው ደረጃ ሙሉ በሙሉ ሄዶለታል ማለት አይቻልም። ለእዚህም ማስረጃው የምዕመኑ መጠንከር እና የበለጠ ቤተ ክርስቲያኑን በቅርብ ማወቁ ነው።ይህም ሆኖ ግን ከላይ ያለው መዋቅር ንቁ እንዳይሆን ብቻ ሳይሆን በሙስና እና ብልሹ ተግባራት ሲታመስ ሕግ አስከባሪ ነኝ የሚለው ስርዓት አንድም እገዛ ሳያደርግ ይልቁንም ለሕገ ወጦች የፖሊስ ኃይል ሁሉ እየመደበ ቤተ ክርስቲያኒቱ አሁን ላለችበት ደረጃ አድርሷታል። 

የሙስናውን ደረጃም በቅርቡ አቡነ ማቴዎስ ለሸገር ራድዮ እንደተናገሩት " ሁኔታው ከአቅም በላይ ሆኗል" ብለዋል። ከአቅም በላይ የሆነ ነገር በእግዚአብሔር በምታምን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ፈፅሞ ቦታ ባይኖረውም እርሳቸው ግን ብለውታል።በተለይ ይህ ፅሁፍ በሚፃፍበት ሰዓት በሀገር ውስጥ እና በውጭ የሚገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በአሜሪካ እና አዲስ አበባ የግንቦት ርክበ ካህናት የሲኖዶስ ስብሰባ ላይ ናቸው። በውጭ በአቡነ መርቆርዮስ በአገር ውስጥ በአቡነ ማትያስ ሰብሳቢነት። ይህ በእራሱ እንደ ሀገር አንዱ ስብራታችን ነው።የዘመናችን ቁስል ነው።ይህንን ቁስል ለልጆቻችን ሳይተላለፍ እንዴት ማጠገግ እና ማሻር ይቻላል? የሚለው በእያንዳንዱ ምእመን እና አባቶች ላይ የወደቀ ሸክም ነው።ይህ ሁሉ የሆነብን ይህ ስርዓት በጎሳ ላይ የተመሰረተ መከራ በላያችን ላይ ከጫነብን ጊዜ ጀምሮ ነው።እዳው ግን ይሄው እሳክሁን ቤተ ክርስቲያኒቱን እና ሀገሪቱን እያንገላታት ነው።የሚገርመው የቤተ ክርስቲያንን መከፋፈል በፅኑ ስርዓቱ እንደሚደግፈው ለመረዳት ላለፉት 25 ዓመታት ችግሩን እንደ ችግር አይቶ ለመፍታት ስንዝር ያህል የሄደበት ሂደት አለመኖሩን መመልከቱ በእራሱ በቂ ነው።ይልቁንም አባቶች በእራሳቸው ወደ ውይይት መድረክ ሲቀርቡ (የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ውይይትን ያስታውሷል) እነ አቦይ ስብሐት ተነስተው "መሰቀል አለባቸው" እና ሌሎችም አባባሎች በመናገር የቀድሞው ፕሬዝዳንት አቶ ግርማ ወ/ጊዮርጊስን የተናገሩትን እንዲያጥፉ በማስፈራራት ጭምር ኢትዮጵያ የቤተ ክርስቲያኗ አባቶች ለሁለት እንዲከፈሉ ከወትሮውም የሰሩ መሆናቸውን ዳግም አስመስክረዋል።

የኢትዮጵያ ጥሪ ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን 

አሁን ኢትዮጵያ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን እየተጣራች ነው።አንቺ ከሰማያዊ አምላክ ጋር ገፅ ለገፅ የተነጋገሩብሽ  ቤተ ክርስቲያን ልጆቼ በዘር እየከፋፈለ የሚያፋጅ መንግስት ሲያምሰኝ ዝም አትበይ። ልጆቼ በእየእሥር ቤቱ ተወርውረው እየማቀቁ እና በጎጥ እየተለዩ እየተሰደቡ ነው እና ከሕዝቡ ጋር አብረሽ አልቅሺ። ዋልድባን የሚያህል ለመላው ዓለም የሚፀልዩ የተሰወሩ አባቶች ፀጋ የሰፈነበት ገዳም ያሉ አባቶች ሲሰደዱ እና ሲገረፉ ካህናቶችሽ ማቅ ለብሰው ያልቅሱ።እንባቸው በሕዝብ ፊት ይታይ።የሃይማኖት ሰው ሃዘን እግዚአብሔርን ከዙፋኑ ይጠራዋል።የአዳም እንባ መድኃኔአለምን ከዙፋኑ እንደሳበው። የእኔ ነገር እንዲህ ሕፃን አዋቂውን አስጨንቆት ሕዝቤ ይህ መንግስት እንደ ሩዋንዳ ሊያባላን ነው እያለ በጭንቀት ላይ ሆኖ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሆይ!  ከጳጳሳቶችሽ  ከስር ባሉ ካህናቶችሽ እና ምእመናን ጋር በአደባባይ አልቅሺ።ማልቀስ ሲከለክሉሽ  ካህናቱ ቢታሰሩ ይሻላቸዋል።የኢትዮጵያ እንባ መሬቱን እያራሰው የሲቃ ድምፅ አለምን ሳይቀር እያስተከዘ በሕዝብ መሃል ከመኖር ከታሰሩት ጋር መታሰር ይሻላል። እርግጥ ነው የዕለቱም ሆነ የሳምንታቱ ፀሎት፣ቅዳሴ እና ምልጃ ሁሉ እንደሚያግዘኝ አውቃለሁ።የአሁኑ ወቅት ግን ከእዚህ የበዛ ድምፅ ወደሰማይ ማሰማት የሚሻበት ወቅት ነው። እስከዛሬ በለሆሳስ ከነበረ ፀሎቱ አሁን በእንባ እና የምድርን ዳር በሚንጥ እንዲሁም ወደ እግዚአብሔር በበለጠ በመጮህ መሆን አለበት። እስከዛሬ ትንሽ ትንሽ በመራብ ከነበረ አሁን የበለጠ በመጦም መሆን አለበት።እስከዛሬ ልጆቼ በጎሳ እየከፋፈለ የሚያባላቸውን ስርዓት በፍርሃትም ሆነ በአርምሞ ዝም በማለት ከነበረ አሁን በግልጥ አደባባይ ወጥቶ በመናገር እና ልጆቼን ከጥፋት በማዳን መሆን አለበት።

በእዚህ ሰዓት ምእመን ጳጳሱን የሚጠብቅበት፣ዲያቆኑ ቄሱን የሚጠብቅበት ወቅት አይደለም።ምዕመኑም ዲያቆኑን የሚጠብቅበት አይደለም።ኢትዮጵያን በዘር ፍጅት ውስጥ ለመክተት የመጨረሻ አማራጭ አድርጎ ስርዓቱ ወስኗል።ወንጀልን ለመሸፈን በእርስ በርስ የዘር ፍጅት አስነስቶ በሕዝብ ደም ታጥቦ አቅጣጫ ለማስቀየር።ለእዚህ ብዙ ምልክቶች ታይተዋል።በሱማሌ እና ኦሮሞ፣በአፋር እና ትግራይ፣በአፋር እና አማራ፣ወዘተ ግጭቶች የተነሱት በስርዓቱ አነሳሽነት መሆኑ ግልጥ ሆኗል።በቅርቡ በመቀሌ ስታድዮም የተነሳው የባህርዳር ከነማ እና የመቀሌ አቻው መሃል የተነሳውን ብንመለከት ችግሩ ስርዓቱን ያሳሰበው ሳይሆን ይልቁንም በትዕቢት  መመልከትን መርጧል። የትግራይ ፖሊስ አዛዥ ለጀርመን ድምፅ ራድዮ ሲመልሱ "ምን አገባችሁ" የሚል ምላሽ ነበር።ይህንን የሰሙ የስርዓቱ ደጋፊዎች እሰይ ደግ አደርጉ የሚል ምላሽ የሰጡ ሲኖሩ ሌሎች ጉዳዩ ያሳሰባቸው አሉ።ይህ ሁሉ የሚያሳየን መጪው ጊዜ ኢትዮጵያውያንን በመጪው ጊዜያት ህዝብን ሊያፋጅ የተዘጋጀ ሕዝብ እርስ በርስ እንዲታረቅ ምንም ጥረት የማያደርግ ይልቁንም እራሱ የፀብ ጫሪ መንግስት እንዳለን ካወቅን ሰንብተናል።በእዚህ ጊዜ የጎሳ ፖለቲካን አውግዘው ኢትይጵያውያንን የህብረት መንገድ የሚያሳዩ የሃይማኖት አርበኞች በመብራት ይፈለጋሉ።ይህንን የማያደርግ ሃይማኖተኛ ነኝ ብሎ ልናገር ከቶ አይችልም።ኢትዮጵያ የኢትዮያ ቤተ ክርስቲያንን ስትጣራ ከጳጳስ እስከ ተራ ምእመን ያለህ ሃይማኖት አለኝ የምትል ሁሉ ሕዝቤን ፍቅር እና አንድነትን እያስተማራችሁ ከተደገሰብኝ የእልቂት ድግስ አድኑኝ እያለች ነው።በሃይማኖት በኢትዮጵያ ላይ የተደገሰውን የእልቂት አዋጅ እንጋፈጥ።በሃይማኖት የተነሳን የሚችለው ምድራዊ ኃይል የለም።ሃይማኖት ብረቱን ያቀልጣል፣ተራራን ይንዳል፣ጨለማውን ይገፈዋልና።

አረሳት ኢትዮጵያን በዘማሪ ይልማ ኃይሉ 







ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Tuesday, May 16, 2017

Den 17. mai er Norges nasjonaldag. የኖርዌይ ብሔራዊ በዓል ቀን ግንቦት 17 እኤአ (ቪድዮ)

ጉዳያችን / Gudayachn (www.gudayachn.com)
=====================
Den 17. mai er Norges nasjonaldag. På denne dagen i 1814 ble Norges Grunnlov datert og undertegnet av presidentskapet i Riksforsamlingen på Eidsvoll. Forsamlingen valgte deretter enstemmig regenten, prins Christian Frederik, til konge av et uavhengig Norge. Senere samme dag mottok han en deputasjon av representanter, ledet av president Georg Sverdrup, som meddelte ham valget og overrakte ham et renskrevet eksemplar av Grunnloven.

በፈረንጆቹ አቆጣጠር ግንቦት 17  በእየዓመቱ ኖርዌይ ብሔራዊ በዓል ሆኖ ይከበራል። በ1814 ዓም በእዚሁ ግንቦት 17 ቀን የኖርዌይ ህገ መንግስት  የፀደቀበት እና የነፃነት ቀን የሚከበርበት ዕለት ነው።በኦስሎ በሺህ የሚቆጠሩ ከሁሉም ትምህርት ቤቶች የሚመጡ ተማሪዎች በማርሽ ሙዚቃ እያሰሙ በንጉሡ እና በንግስቲቱ እና ቤተሰባቸው በቁሙበት ሰገነት ስር ያልፋሉ።ሕዝቡም እንዲሁ ያደርጋል።ከእዚህ በታች ያለው ፊልም  የበዓሉን አከባበር ያሳያል።




ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Sunday, May 14, 2017

ቴዲ አፍሮ የእዚህ ትውልድን ምኞት፣ሕልም እና ሃሳብ ለዓለም ያሳወቀበት አዲስ ቃለ መጠይቅ።Teddy Afro reflects the vision and dream of the new generation of Ethiopia

"ኢትዮጵያዊነት ቀለሙ እንዲዘባረቅ ሆኖ እንደቀረበው አይደለም" ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)   ለአሶሼትድ ፕሬስ እና ኢትዮፍላሽ  በአማርኛ የሰጠው መግለጫ (ቪድዮ)። ቴዲ በእውነትም  የኪነጥበቡን ማኅበረሰብ ሚና አመላካች ብቻ ሳይሆን የትውልዱን እውነተኛ ድምፅ ሆኗል።ትውልዱ የቴዲ አድማጭ ብቻ ሳይሆን ቴዲ የሚለውን ከፍ አድርጎ ማስተጋባት እና ለተግባራዊነቱም መነሳት ይገባዋል።

ቪድዮ : ከቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ ዩትዩብ የተወሰደ)
Teddy Afro - interview with EthioFlash and Associated Press reporter Elias
Video : from Teddy Afro Youtube.



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Thursday, May 11, 2017

ሱማልያን የተመለከተ ወሳኝ የተባለ ጉባኤ ለንደን ላይ ዛሬ ሐሙስ ግንቦት 3፣2009 ዓም ተከፍቷል (ቪድዮውን ይመልከቱ)

በጉባኤው ላይ የኬንያ እና የኡጋንዳ ፕሬዝዳንቶች እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሃፊ  ጨምሮ የሀገራት መሪዎች ተገኝተዋል።
Video Source : Foreign & Commonwealth Office



ጉባኤው በከፊል በፎቶ
ፎቶ :  በጉዳያችን

ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Sunday, May 7, 2017

ሰሞኑን ባወጣው ኢትዮጵያ የተሰኘው ሲዲ ሳብያ ለድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ኢትዮጵያ መልሳ ልታዜምለት የምትችለው ዜማ (የጉዳያችን ምርጫ ለቴዲ አፍሮ)

ድምፃዊት የሺ ደመላሽ ከአምስት ዓመት በፊት ያዜመችው "አንተ ኮከብ ነህ የኮከብ አለቃ" የሚለው ዜማ ዛሬ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ለኢትዮጵያ ላዜመው ዜማ ኢትዮጵያ የመለሰችው ምላሽ አድርገን ብናስበው እንዲህ ይደመጣል።

"አዎ! አንተ ለእኔ ነው ቀድመህ ይተፈጠርከው፣ 
ያዜምክልኝ ዜማ ቀመር የቀመርክው"  ድምፃዊት የሺ ደመላሽ

በነገራችን ላይ ድምፃዊት የሺ ደመላሽ ያዘመችው ለድምፃዊ ቴዎድሮስ አለመሆኑ እንዲሁም  ሁለቱ ድምፃውያን የሚያገናኛቸው ጉዳይ እንደሌለ እና ጉዳያችን በእራሷ ያደረገችው ግጥምጥሞሽ መሆኑ ይታወቅ።


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Thursday, May 4, 2017

ከ26ሺህ በላይ ሰው አስሮ በምንም አይነት የሕግ የበላይነት ዋስትና አለው ማለት አይቻልም - የተባበሩት መንግሥታት ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር አዲስ አበባ ላይ የተናገሩት In Ethiopia - it is unlikely rule of law guarantees have been observed in every case-UN High Commissioner for Human Rights



High Commissioner for Human Rights Zeid Ra’ad Al Hussein (centre) addresses a press conference in Addis Ababa, the capital of Ethiopia. Photo: UN/Ahunna Eziakonwa

UN rights chief urges authorities for greater freedoms, especially space for critical voices

Source: - UN NEWS CENTER 
ምንጭ : - የተባበሩት መንግሥታት የዜና ማዕከል 


የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር ሰይድ ራድ አል ሁሴን (Zeid Ra’ad Al Hussein) ለሶስት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ካደረጉ በኃላ ዛሬ ከቀትር በኃላ አዲስ አበባ የተባበሩት መንግሥታት አፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ውስጥ መግለጫ ሰጥተዋል።ኮሚሽነሩ በአዋጅ ስር በምትማቅቅ ሀገር ጉዳይ ላይ መግለጫ ለመስጠት አንድም ጭላንጭል የሚባል በጎ ነገር እንዳላገኙ የተባበሩት መንግሥታት የዜና አገልግሎት ማምሻውን በለቀቀው የመግለጫቸው ይዘት መረዳት ይቻላል።

ኮሚሽነሩ በተጨማሪ "መንግስት ነፃ ሚድያን፣የሲቪሉን ማኅበረሰብ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን በአግባቡ ማዳመጡ እጅግ አስፈላጊ ነው። ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ማለትም ከ26ሺህ በላይ ሰው አስሮ በምንም አይነት የሕግ የበላይነት ዋስትና አለው ማለት አይቻልም። የድርጅቴ ሰራተኞች ችግሩ ወደተፈጠረባቸው ቦታዎች ገብተው ሁኔታዎችን እንዲመለከቱ ሊፈቀድላቸው ይገባል " ብለዋል።

የተባበሩት መንግሥታት የዜና ማዕከል ማምሻውን የለቀቀውን ሙሉ ዘገባ ከእዚህ በታች ያንብቡ።

4 May 2017 – Speaking to the press during his mission to Ethiopia, the United Nations High Commissioner for Human Rights today highlighted the need for greater and freer civic space, with “broader latitude for the contributions of critical or dissenting views” to decision-making in the country.

“All governments need to be held to the mark by independent media and the vital action of civil society and human rights defenders,” High Commissioner Zeid Ra’ad Al Hussein said at a press conference in the capital, Addis Ababa.

“I am convinced the Ethiopian Government will find its most important and productive investment will be in the rights of the people, which build strong and safe societies.”

In his remarks, the UN rights chief hailed the contributions of the Horn of Africa country ranging from its contributions to UN peacekeeping efforts as well as its commitment to protect the human rights of its people as illustrated by its accession to a number of human rights treaties and their reflection in the Ethiopian constitution.

He also expressed that the work of the Ethiopian Human Rights Commission was heartening and called on the Government to continue further steps to grant the body more independence.

However, speaking on the unrest in the country in November 2015 and August 2016, and the response of the security forces, Mr. Zeid urged the authorities to allow access to UN human rights officials to visit the affected region and establish the facts.

“The extremely large number of arrests – over 26,000 – suggests it is unlikely rule of law guarantees have been observed in every case. I believe my staff ought to be given access to the affected areas, and I renew my request,” he added, noting that he would continue to follow-up on the case.

The High Commissioner also spoke on the importance of economic, social and cultural rights and stressed that progress on these rights would translate into civil and political rights advances.

He also offered his support and that of his Office, OHCHR, to the Government and the people of Ethiopia in confronting the challenges posed by the drought plaguing large parts of the region.

SEE ALSO: As new drought hits Ethiopia, UN urges support for Government’s ‘remarkable’ efforts

During his visit, High Commissioner Zeid met with a number of senior Ethiopian officials, including the Prime Minister, Hailemariam Desalegn, Ministers, legislators, and human rights officials and defenders.

Also, while in Ethiopia, the UN top human rights official signed a Memorandum of Intent with the Government to strengthen OHCHR Regional Office in Addis Ababa programmes on capacity building for stakeholders across the region, including Ethiopia.

During his mission, Mr. Zeid also met with Chairperson of the African Union Commission, Moussa Faki Mahamat, and other senior African Union (AU) officials, with whom he discussed human rights priorities with the AU, as the regional bloc’s new leadership develops its vision and frameworks for impact across the continent.

Source: - UN NEWS CENTER 


Monday, May 1, 2017

ወያኔ የዘራብንም ሆነ ቀደም ብለው የነበሩ የጋራ ቁስሎቻችን የሚሽሩት እኛው ተመካክረን በምንመሰርተው መንግስት እንጂ ወያኔ ለክቶ እና ሰፍቶ በሚወረውርልን ድርጎ አይደለም። የኦሮምያ ልዩ መብት በአዲስ አበባ የሚለውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ ይመለከታል


========================
ጉዳያችን / Gudayacn
ሚያዝያ 23፣2009 ዓም (ሜይ 1፣2017)

ወያኔ የኢትዮያን ሕዝብ እርስ በርስ አባልቶ እድሜውን ለማራዘም ከእዚህ በፊት ያልጫረው መሬት ያልቧጠጠው ገደል የለም።አሁን ደግሞ  የኃይል ሚዛን ያገኘ መስሎት የኦሮምያ ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ ላይ የሚል አጀንዳ በማራገብ ህዝቡ እንዲገዛለት ለማድረግ እየሞከረ ነው።በሀገራችን ታሪክ ያወያኔን ያህል በሕዝብ ደም የተጫወተ እና ለመጪዋ ኢትዮጵያ ሳይቀር አረመኔያዊ ቢላዋ የሚስል መንግስት ኢትዮጵያ ገጥሟት አያውቅም።

አሁን ወሳኙ ሕዝብ ነው።ሕዝብ መምረጥ ያለበት የወያኔ እድሜ ማራዘምያ ክኒንን ሳይሆን ኢትዮጵያ በዘለቄታ ከወያኔ ከፋፋይ እና ዘረኛ ስርዓት የምትላቀቅበትን መንገድ ነው።የኦሮምያ ክልል ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ ላይ የተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅ የሚለውን ካርድ ወያኔ አሁን የመዘዘው በስርዓቱ ላይ የሚደረገው አጠቃላይ ተቃውሞ ውስጥ አዲስ አበባ እንዳትሳተፍ ለማስፈራራት ነው።ይህንኑ አጀንዳ የሚያራግቡ በውጭ ሀገር እና በሀገር ውስጥም ያሉ የኦሮምያ አክትቪስቶች አሉ።እነርሱ ግን ምክንያታዊ ከሆነ የሰው ልጁ ታሪክ  እና የከተሞች እድገት ሂደት ጋር የተቃረኑ፣ ተማርን የሚሉት የባህር ማዶ ትምህርት የድንቁርና ምንጭ ሆኖባቸው ጭንቅላታቸውን ቀስፎ የያዛቸው፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ የአኗኗር ዘይቤ፣ባህል፣እርስ በርስ ግንኙነት እና እምነት ሁሉ ደፍጥጠው ከወያኔ እኩል በተመረዘ ቂም በአጭር መንገድ ያውም በወያኔ ድርጎ አላማቸውን ያሳኩ የሚመስላቸው ናቸው።

በመጀመርያ ደረጃ አንድ የኦሮምኛ ተናጋሪ ጥቅሙ የሚከበረው ሃገራዊ፣የዜግነት፣የቡድን እና ግለሰባዊ መብቱ ሲከበርለት እንጂ ወያኔ በፈጠረው የኦሮምያ ክልል በሚል የተሰፋ ልብስ ውስጥ ነው ወይ? ይህ ጉዳይ ፈፅሞ ሊያምታታን አይገባም።ይህ ጥያቄ በእራሱ የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ ነው የሚለው አባባል የተሳሳተ ነው።ኦሮሞ ማለት የተለየ ፍጡር ሳይሆን ከአጠገባችሁ የምታውቁት በሪሳ፣ገመቹ፣እና ሌሎች ሁሉ ናቸው። የኦሮሞ ማኅበረሰብ  የወያኔን ከፋፍለህ ግዛ እና የኦሮምያ ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ በሚል መቀሌን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ የማድረግ እና አዲስ አበባን የማፍረስ ሥራ ይቀበላል ብሎ ማሰብ በእራሱ ስህተት ነው።

የእዚህ ረቂቅ አዋጅ ዓላማዎች የሚከተሉት ናቸው።

1/ ስልጣኑ ሁሉ በሕወሓት ስር መሆኑ እየታወቀ ጥቂት የኦሮሞ አክትቪስቶችን የመደለል ሥራ፣

2/ የአዲስ አበባ ሕዝብን እኔ ከስልጣን ከወረድኩ በዙርያህ ካለው የኦሮሞ ማኅበረሰብ ጋር ግጭት ትፈጥራለህ የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ፣

3/ የአዲስ አበባን እድገት ስልታዊ በሆነ መንገድ አዳክሞ የኢንዱስትሪ እና የዋና ከተማ ማዕከልነትን ወደ መቀሌ የመጎተት አላማ። ለምሳሌ በረቂቅ አዋጁ ጋር አዲስ አበባን እና የኦሮምያ ክልልን እንደ ሁለት ሀገር ድንበር አድርጎ ሲያስቀምጥ እንዲህ ይላል።

 "በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 
(1) በተደነገገው መሰረት የተቀመጠውን የወሰን ምልክት ከተደረገበት በኋላ በማናቸውም ምክንያት መስፋት የማይቻል ሲሆን ወሰኑንም ክልሉ እና አስተዳደሩ የማክበር ግዴታ አለባቸው፡፡ 
3) ይህ አዋጅ ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ በ6 ወራት ጊዜ ውስጥ ወሰን ተከልሎ ምልክት መደረግ ይኖርበታል፡፡"  ይላል።
4/  የአዲስ አበባ የተለያዩ ቦታዎችን ስያሜ ለምሳሌ አራት ኪሎ፣ ስድስት ኪሎ፣መርካቶ የሚሉት ስሞች ሁሉ እንዲቀየሩ በማድረግ የታሪክ ማዛባት መፍጠር በእዚህም ከ4 ሚልዮን የማያንሰውን የአዲስ አበባ ሕዝብ መብት ጨፍልቆ ታሪክ አልባ ማድረግ የሚሉት ይጠቀሳሉ።
ባጠቃላይ ወያኔ የህዝብ ማዕበል እየገፋው እንደሚሄድ ሲረዳ መጨረሻ ላይ ከሚወስዳቸው ርምጃዎች ውስጥ ኢትዮጵያውያንን እርስ በርስ የሚያፋጅ ሥራ ላይ ማተኮር እንደሚሆን የታወቀ ነው።ውጤቱ ግን ምን ይሆናል?
የእዚህ የነበረ ነገር ግን በ1997 ዓም በምርጫ ሲሸነፍ እንደመዘዘው ያለ ካርድ የመምዘዙ ጉዳይ የተበላ እቁብ ነው።የኢትዮጵያ ሕዝብ ኦሮምኛ ተናጋሪው ህዝብም ጭምር በትግሉ ሂደት በስሏል።ምናልባት ጥቂት የፖለቲካ ብስለቱ የጎደላቸው አክቲቪስቶች አሁንም ወያኔን አላወቁት ከሆነ በተዘጋጀላቸው ቦይ የመንጎድ መብታቸው እንደተጠበቀ ነው።የኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ከቀረው ማኅበረሰብ ጋር እንዴት እንደሚኖሩ የእራሳቸው የከበረ ባህል፣እምነት እና ወግ አላቸው።እነኝህ እሴቶቻችን ለሕብረታችን እና አብሮ መኖራችን ዋስትና ናቸው።በእርግጥ ወያኔ እነኝህንም እሴቶች ለመጉዳት በርካታ ጥረት ሲያደርግ ኖሯል።የተወሰኑትንም ለማቁሰል ሞክሯል። ፈፅሞ ማጥፋት ግን አልቻለም።

ስለሆነም ወያኔ ለሚመዘው ለእዚህ አይነቱ የቆየ ካርድ መፍትሄው እራሱ ወያኔ የሚያወጣው ሕግ ሕጋዊ አለመሆኑን እና ሕጋዊ መንግስት እስኪመሰረት ድረስ የሽግግር መንግስት አስፈላጊነት ላይ አበክሮ መግፋት ነው።አንድ መንግስት ውድቀቱ አፋፍ ላይ ሆኖ የሚያወጣው ሕግ በእራሱ የቁራ መጮህ ማለት ነው።ውድቀት አፋፍ ላይ ያለ መንግስት የአዋጅ ጋጋታ መደርደሩ የተለመደ የአምባገነን መንግስት የውድቀት ዋዜማ ደውል ነው።ይህ የታሪክ ሂደት ነው።አሁን ለችግሮቹ መፍትሄው ዘለቄታ የሆነ የግለሰብ እና የቡድን መብቶች የሚከበሩበት እውነተኛ የፌድራል መንግስት ኢትዮጵያ እንዲኖራት የወያኔ መንግስት በሽግግር መንግስት እንዲተካ መታገል ነው።ይህ ደግሞ የሁሉም ኢትዮያዊ ኦሮምኛ ተናገረ አማርኛ፣ትግርኛ ተናገረ አፋርኛ የእራሱ ህልውና ጉዳይ ነው።ይህ ባይሆን ወያኔ ለጥቂት በሙስና ለተጨማለቁ እና ፍርፋርያቸውን ለሚቃርሙ ግለሰቦች እና ቡድኖች ሲባል የማያልቅ ችግር ውስጥ መግባት ነው።በመሆኑም ወያኔ የሚመዘውን የእራስ ምታት ማስታገሻ ካርድ በሚገባ ይግባን።ነፋስ እንደሚወስደው ገለባ ሳንሆን ዋናው ሃገራዊ ጉዳይ ላይ እናተኩር። ወያኔ የዘራብንም ሆነ ቀደም ብለው የነበሩ የጋራ ቁስሎቻችን የሚሽሩት እኛው ተመካክረን በምንመሰርተው መንግስት እንጂ ወያኔ ለክቶ እና ሰፍቶ በሚወረውርልን ድርጎ አይደለም።  

ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።