ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, August 31, 2021

Breaking News - USAID Ethiopia director, Sean Jones confirmed as TPLF looted the USAID warehouses. That means TPLF is using aid food to war.

ሰበር ዜና - የዩኤስኤይድ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ሚስተር ሲአን ጆን ህወሓት የዕርዳታ እህል ለጦርነት እንደሚጠቀም ገለጡ።መጋዘናችንን እየሰበረ እህል ዘርፎናል ብለዋል።ለምን እስከዛሬ እንዳልተናገሩም ተጠይቀዋል።

USAID Ethiopia director Sean Jones

===================
ጉዳያችን/ Gudayachn News
===================

In the mid of August, Gudayachn reported TPLF used aid food to war.On the third day after Gudayachn news released  (the front page of the news was WFP logo), complain comes from the United Nations stating that UN was concerned about statements appearing on social and mainstream media claiming the UN agencies. The UN August 16,2021 press release under the the title ‘'UN statement on impartial engagement in support of Ethiopia’ stated -

''The United Nations in Ethiopia is very concerned about recent statements appearing on social and mainstream media claiming that UN agencies and humanitarian partners are operating in Ethiopia in support of partisan political agendas.’’ UN statement August 16,2021

No matter how, facts on TPLF uses aid food to war are coming to front now. The USAID Ethiopia director, Sean Jones, today confirmed that TPLF is using aid food to war. Mr. Jones' statement is released today as of August 31,2021 by Ethiopian Broadcasting Corporation (EBC) Amharic News hour. According to the director’s statement Sean Jones said to EBC -

 ‘’ Yes, TPLF is opportunist. We are very sure in all areas of TPLF insurgence, they loot all of our warehouses.This is the fact that we know well. We know also in every areas they invade the Amhara region, they looted aid organization’s warehouses, took any type of cars, looted the farmer’s properties and killed innocent people.’’

In this interview,  EBC journalist forwarded a question why USAID as an aid organization and the US Government as a responsible Government did not say anything when the Ethiopian Government complained on this issue. The USAID director said -

 ‘’We did not say anything does not mean that we did not agree with Ethiopian Government complaints. This is due to the US Government's experience of not giving press releases or responses for each and every issue. On the other hand, we were looking for concrete evidence on this issue. Now we are very confident that TPLF soldiers emptied our warehouses. That is why we are speaking openly.’’

Regarding the Ethio-US relation, the USAID Ethiopia director said 

‘’Ethiopia is one of our best partners from all over the world. We seriously care for our relationship with Ethiopia.As a true partner, when we think there is a problem, we share our concern clearly.This is just like any healthy marriage. For your easy information, frankly speaking, there is no honest conversation with Ethiopia leadership as of today.We have good communication. I can assure you my relationship with senior Ethiopian officials may be never been better’’

Watch the video of the director's interview with EBC 


=====================

ማስታወቂያ /Advertisement 
===============================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 


Friday, August 27, 2021

የአንድ ዓመት ከስድስት ወር ልጅን በመድፍ

በመድፍ የወደመው ቤት 

ከትግራይ መሬት የበቀሉት በንፁሃን ደም የሰከሩት የደብረፅዮን እና ጌታቸው ረዳ ጀሌዎች ከሰሞኑ በአማራ እና የአፋር ክልል በሚኖረው ኢትዮጵያዊ ላይ የፈፀሙት ግፍ ተፅፎ አያበቃም።ለአቅመ ሔዋን ያልደረሱ ሴቶች ተደፍረዋል፣ የገበሬዎች ንብረት ከተጋገረ እንጀራ እና ሊጥ እስከ የቁም ከብት ተዘርፏል።ከእዚህ ሁሉ በላይ አዛውንት እና አሮጊቶች መሬት ለመሬት እየተጎተቱ ተገድለዋል።እንደ መርሳ ባሉ ቦታዎች ደግሞ ሕዝቡን እየሰበሰቡ ያልታወቀ መርፌ ወግተውታል።ይህንን ሁሉ ሲያደርጉ ነገ የአፀፋ ምላሽ የሌለው መስሏቸዋል።

በአፋር የሽብርተኛው ህወሓት የጅምላ ግድያ የሚዘገንን ነበር።በመጠለያ ውስጥ ያሉ 107 ሕፃናት ጨምሮ ከ200 በላይ ሕዝብ በአንድ ላይ ነው የፈጇቸው።አንዲት የአፋር እናት ለኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ጋዜጠኛ ሲናገሩ -

 ''በአፋር ታሪክ በሙሉ እንዲህ ዓይነት ግፍ በማንም መንግስትም ሆነ ጠላት ተፈፅሞብን  አያውቅም።እስካሁን የተዋጉት ወንዶቻችን  ናቸው።አሁን ግን አንዲትም ሴት ከቤት አንቀመጥም  እርጉዝ አትቀርም ስንዋጋ'' በማለት ገልጠዋል።በአፋር የተፈፀመው ግፍ የሞቱትን ለመቅበር መቃብር የሚቆፍሩትን ሁሉ ላይ ነበር።

ቢቢሲ አማርኛ እኤአ ሐምሌ 23/2021 ዓም በአፋር ሽብርተኛው ህወሓት የፈፀመውን ግፍ አስመልክቶ በሰራው ዜና ላይ እንዲህ የሚል ይገኝበታል - 
''ከአፋር የደረሱን በርካታ ምንጮች እንደሚሉት የህወሓት አማጺ ኃይሎች በአፋር ክልል በርካታ ንጹሐንን ገድለዋል። ንብረቶችንም ዘርፈዋል። ቤቶችን በእሳት አቃጥለዋል። ይህም በያሎ እና በአውራ የተከሰተ ነው።ያሎ ከሚባለው የአፋር አካባቢ ሸሽቶ ያመለጠ አንድ ነዋሪ እንደተናገረው ሰዎች የተገደሉት የቀብር ሥነ ሥርዓት እየታደሙ በነበረበት ሰዓት ነውበማኅበራዊ ትስስር መድረክ እየተጋራ የሚገኝ አንድ ተንቀሳቃሽ ምስል ይህንኑ የሚያጠናክር ነው።አንድ የአፋር ነዋሪ አጠገቡ የአማርኛ አስተርጓሚ እየተናገረ የሚከተለውን ሲል በተንቀሳቃሽ ምሥሉ ላይ ይታያል፡- "ለ20 ሟቾች መቃብር በመቆፈር ላይ ነበርን። እየተጠጉን ሲመጡ ይህን ጨርቅ ከፍ አድርጌ አሳየኋቸው፤ ንጹሐን ነዋሪዎች እንደሆንን እንዲረዱ ነበር። ነገር ግን ከመሀላቸው አንዱ ተኩስ ከፈተብን።" ቢቢሲ አማርኛ እኤአ ሐምሌ 23/2021 ዓም

ፋሺሽታዊው የሽብርተኛው ህወሓት ጀሌ በአፋር ሕዝብ ላይ ከፈፀመው አውሬያዊ ተግባር ሌላ አጋምሳ ቆቦ የሚገኝ አንድ ሙሉ መንደር ሆን ተብሎ እንዲወድም መደረጉ ሌላው ዘግናኝ ተግባር ነው።

የአንድ ዓመት ከስድስት ወር ልጅን በመድፍ 

ጦርነት የራሱ ሕግ አለው።በጦር ሜዳ ከወታደር ጋር ልትዋጋ ትችላለህ።ቤታቸው ያሉ ገበሬዎች ቤት ገብቶ መረሸን ግን ከውስጥ የወጣ የጥላቻ ጥቀርሻ ነው።አማራ በመሆናቸው ብቻ መግደል አለብን የሚል ተልዕኮ ይዘው በንፁሃን ደም ታጥበው ተመልሰው ትግራይ ይገባሉ ወይ? ነው።በእዚህ ወንጀል ውስጥ ያሉ የጊዜ ጉዳይ እንጂ ለፍርድ መቅረብ ወይንም በገቡበት መውጫ አጥቶ መያዝ አይቀርም።

ባሳለፍነው ሳምንት ውስጥ የደብረታቦር ከተማ የደብረ ታቦርን ዓመታዊ በዓል ለማክበር ዝግጅት ላይ ነበረች። በክምር ድንጋት እና ጋይንት ላይ  ሾልኮ የገባው የሽብርተኛው የህወሓት ጀሌ ገበሬው ላይ እየተኮሰ እህሉን ብቻ ሳይሆን ከብቱን በጥይት አረር እየገደለ መሆኑ ተሰምቷል።በእዚህ መሃል የደብረ ታቦርን ከተማ ለመያዝ ጀሌው ጥረቱ አልተሳካም።ለእዚህም ዋናው ምክንያት ደግሞ የደብረ ታቦር ከተማ እና የአካባቢው ወጣት ከጎራደ እስከ የነፍስ ወከፍ ክላሽ ይዞ ወጥቶ ከደብረ ታቦር ከተማ ወጥቶ ሰርጎ የገባውን ከማሳደድ አልፎ አያሌዎችን ማርኮ ደብረታቦር ከተማ አሰልፎ ለሕዝብ አሳየ።ይህን ተከትሎ የደብረ ታቦር እለት ወደ ከተማው የሚገኙ ሁለት አብያተ ክርስትያናት እና ሆስፒታል ላይ ከባድ መሳርያ እና መድፍ ተተኮሰ።

ከተተኮሱት ውስጥ ሦስቱ የታለሙት አንዱ ለደብረ ታቦር መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን፣ሁለተኛው አሁንም በከተማው ለምትገኘው እናቲቱ ማርያም የታለመ እና ሦስተኛው ደግሞ ሆስፒታሉን ለማውደም የተተኮሱ ነበር።ሲተኮሱ ደግሞ ማንምም የአማራ ተወላጅ በመግደላቸው ብቻ እንደ ስኬት የተቆጠረ ነው።ይህ ደግሞ በድንገት የተፈፀመ አይደለም።ሆን ተብሎ ታቅዶ እና ከላይ የሽብርተኛው አመራሮች በተላለፈ ትዕዛዝ ጭምር ለመሆኑ መሪዎቹ ቀደም ብለው ሲናገሩት የነበረው ''ከአማራ ጋር ሂሳብ እናወራርዳለን'' የሚለው ንግግር ማስረጃ ነው። 

ወ/ሮ ታደላ ነጋ የደብረታቦር ነዋሪ ነች። ታደላ ኑሮዋ ከደብረታቦር መድሃኔ ዓለም ስር ነው።ቤቷ ውስጥ የደብረ ታቦር ዕለት ታደላ ቤት የአንድ ዓመት ከስድስት ወር ልጅ፣ወላጅ እናቷ፣ ሁለት እህቶቿ፣አንድ ወንድሟ እና ግቢው ውስጥ የተከራዩ እንደወንድም የምታያቸው ሁለት ተከራዮች ነበሩ።የህወሓት ከባድ መሳርያ የደብረ ታቦር መድኃኔዓለም ለበዓል የተሰበሰበውን ሕዝብ ለመፍጀት ታልሞ ያረፈው ወ/ሮ ታደላ ነጋ ቤት ላይ ነበር።ወ/ሮ ታደላ የአንድ ዓመት ከስድስት ወር ልጇን፣እናቷ፣ሁለት እህቶቿ እና አንድ ወንድሟ ወድያው ሕይወታቸው ተቀጠፈ። እንደወንድም የምታያቸው ተከራዮችም እንዲሁ ከቆሰሉ በኃላ ሕይወታቸው አለፈ።

ሁለተኛው ከባድ መሳርያ የደብረታቦር እናቲቱ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለፍልሰታ ጾም እና ለደብረ ታቦር በዓል የተሰበሰበውን ሕዝብ ለመፍጀት ያለመ ነበር።ሆኖም ግን ጥይቱ ያረፈው ከቤተ ክርስቲያኑ ጎን ይኖር የነበረ ነዋሪ ጣርያ ላይ ነበር።ግለሰቡ አጋጣሚ ወደ ቤተ ክርስቲያን ለመሄድ ከቤቱ ወጥቶ የቤቱን ቁልፍ ከውጭ እየቆለፈ እያለ መሳርያው ቤቱ ላይ ሲያርፍ ቆርቆሮው ተሰንጥቆ እግሩ ላይ አረፈ ቆስሎ ወደቀ።ወደ ሆስፒታል ተወሰደ።ሕይወቱ ግን ወደ ቤተ ክርስቲያን ለመሄድ በመውጣቱ ተረፈ እንጂ ከቤት ውስጥ ቢሆን  ሟች ነበር። ሶስተኛው ከባድ መሳርያ የተተኮሰው የደብረታቦር ሆስፒታልን ለማውደም ታቅዶ የተተኮሰ ነበር።ሆኖም ይሄኛውም ሆስፒታሉንም ሆነ የማንንም ቤት ሳይነካ ሜዳ ላይ ወደቀ። 

ለማጠቃለል ይህ የፋሺሽቶቹ የትግራይ ህወሓት አረመኔያዊ ታሪኮቹ ውስጥ የሚከተብ ነው።የአንድ ዓመት ከስድስት ወር ሕፃን በመድፍ የተገደለበት ታሪክ። ጀሌው የተኮሰው የአንድ ዓመት ከስድስት ወር ህፃንን ለመግደል ብቻ ሳይሆን እርጉዝም ከተገኘች እንደሚገድል የተኮሱት እና ያስተኮሱት ያውቃሉ።አበባ እንዳልበተኑ ይረዳሉ።ዓላማቸው ለደብረ ታቦር የተሰበሰበው ሕዝብ በጅምላ እንዲያልቅ እና የደብረታቦር ከተማ በአምቡላንስ ስትታመስ ማየት ነበር። ከአንድ ቤተሰብ እስከ ስድስት ሰዎች መሞታቸው አንዱ እና አሳዛኙ ሁኔታ ቢሆንም በጅምላ ሺዎች ንፁሃንን ለመግደል ያቀዱት ዕቅድ ግን አልተሳካም።ለእዚህም የእግዚአብሔር ጥበቃ ከሕዝቡ አልተለይም።ገዳዮች ግን በሕሊናቸው ንፁሃንን ገድለው ጨርሰዋል።የእዚህ ዓይነቱ የአውሬነት ተግባር ነገ ከተጠቃው ሕዝብ ምን ዓይነት ምላሽ እንደሚያሰጥ ሲታሰብ ግን ያስፈራል።የተዘረፈው ተዘርፎ ቁጭ ይላል ወይ? የግፍ አገዳደሉስ ለከት ማጣት በአማራው ላይ ያለው የጥላቻ ጥግ በሽብርተኛው ህወሓት አንፃር እንዲህ የአንድ ዓመት ከስድስት ወር ልጅን በመድፍ በመግደል ሲገለጥ በዘመናችን ሰማን። 
==============///=============== 
==========================
ማስታወቂያ /Advertisement 
===============================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Thursday, August 26, 2021

ሰበር ዜና - የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ሩስያ፣ሕንድ እና ቻይና ከኢትዮጵያ ጎን መቆማቸውን አረጋገጡ።ቻይና ጉዳዩ የፀጥታው ምክር ቤት በመወያየት መፍትሄ አይመጣም ስትል ሩስያ ዕርዳታን ፖለቲካዊ ማድረግ እና መርዛማ ሚድያዎች የችግሩ ምክንያቶች ናቸው ብላለች። (የሩስያ, የቻይና ሙሉ ንግግር ነጥቦች በአማርኛ ይንብቡ)

ሩስያ አሜሪካንን በትግራይ ጉዳይ በገደምዳሜ ወረፈቻት ''ኢትዮጵያ የሚደረገውን የሰብዓዊ እርዳታ ከፖለቲካዊ ጉዳይ ውስጥ መውጣት እንዳለበት የሩስያ እምነት ነው። በእዚህ በኩል መርዛማ ሚድያዎች በመጠኑ ዕድል ያገኙ ይመስላል።'' በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት የሩስያ አምባሳደር ነሐሴ 20፣2013 ዓም 

''We are convinced to address the situation in Northern Ethiopia (Tigray), it is necessary to depoliticize the North Ethiopian Humanitarian activities. In this regard the toxic media atmosphere seems gets a little chance.'' Russia Ambassador to UN Security Council, August 26,2021

 ''ይህንን ጉዳይ (የትግራይን ጉዳይ) በፀጥታው ምክር ቤት በመወያየት መፍትሄ አያመጣም።ከእዚህ ይልቅ እያንዳንዱ የፀጥታው ምክር ቤት አባል ችግሩን ለመፍታት የራሱን ጥረት ሲያደርግ ነው።'' በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት የቻይና  አምባሳደር ነሐሴ 20፣2013 ዓም 

''No one can solve the problem (Tigray conflict) by discussing in Security Counsel but the solution comes when each member of the security council made its contribution to solve the problem.'' Chaina Ambassador at UN Security Council August 26,2021

''የትግራይ ክልል ችግር መፍትሄ ኢትዮጵያዊ መር መሆን አለበት'' - በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት የህንድ አምባሳደር ነሐሴ 20፣2013 ዓም 
''The solution to the Tigray region must be Ethiopian led''.- Indian Ambassador at UN Security Council August 26,2021

====================
ጉዳያችን / Gudayachn
====================

''የአፍሪካ ሰላም እና ፀጥታ'' በሚል ርዕስ ስር የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት የኢትዮጵያ ትግራይ ክፍለሀገር የፀጥታ ጉዳይ ላይ መክሯል።ስብሰባው እንዲጠራ የጠየቁት ስቶንያ፣ፈረንሳይ፣ኖርዌይ፣አየርላንድ፣እንግሊዝ እና አሜሪካ ናቸው።

ስብሰባው የፀጥታው ምክር አባላት አምባሳደሮች የየሀገሮቻቸውን ሃሳቦች ያዳመጠ ሲሆን በመጨረሻም የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴን ንግግር አድምጧል።

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ በቅድምያ መነሻ ንግግር ካደረጉ በኃላ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት በየተራ ንግግራቸውን አቀረቡ።ካቀረቡት ውስጥ ከሞላ ጎደል ገዢ የሆኑ ሃሳቦች እንደሚከተለው ለአማርኛ አንባቢ ኅብረተሰባችን ለማቅረብ እሞክራለሁ።

አሜሪካ 

ከባለፈው ጊዜ ወዲህ ብዙ ለውጥ የለም በማለት የጀመሩት የአሜሪካው ተወካይ በመቀጠል የሚከተለውን ብለዋል።
- ለድርድር የቀረቡ ሃሳቦች መንግስት አልተቀበለም።ህወሓትም ጦሩን ወደ አጎራባች የአማራ እና የአፋር ክልል አስገብቷል።
- በእነዚህ ክልሎች እየተካሄደ ያለው የወያኔ ወታደራዊ እንቅስቃሴ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን እያፈናቀለ ነው እና ይህ  በቶሎ ማቆም አለበት።
- ዛሬ በእነዚህ ሶስት ስጋቶች ላይ ማተኮር እፈልጋለሁ - አስከፊው የሰብአዊ ሁኔታ ፣ ወደ ዘላቂ የተኩስ አቁም አስቸኳይ ድርድር አስፈላጊነት እና የኤርትራ ኃይሎች መውጣት።
- ባለፈው ሳምንት በአማራ ክልል አንድ የሰብዓዊ ሠራተኛ በሕወሓት ኃይሎች የተገደለ ሲሆን ሰብዓዊ ተሟጋቾች ዕቃዎቹ ወደ ትግራይ እየተወሰዱ የሕወሓት መንግሥታዊ ያልሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ መሥሪያ ቤቶችን እና መጋዘኖችን ሲዘረፉ ተመልክተዋል። ይህ ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም።
- ቀውሱን በማባባስ ደረጃ ኤርትራ ተጠያቂ ነች።
- አሜሪካ የኢትዮጵያን ሕዝብ ለመደገፍ ፍቃደኛ ነች።
እዚህ ላይ የአሜሪካው ወኪል ማንሳት ያልፈለጉት የኢትዮጵያ መንግስት የተናጥል ተኩስ አቁምን እንዳላየ አልፈዋል።በአማራ እና አፋር ላይ ህወሓት ያደረገችውን ወረራ በአረፍተ ነገር ጠቀስ አድርገው አለፉ እንጂ በሚገባ አላወገዙም።ይህ አሳፋሪ ነው።



ሩስያ 

- ሩስያ የአካባቢውን ሁኔታ በጥንቃቄ እየተከታተለች ነው።
- ሩስያ በሰኔ በተናጥል ተኩስ አቁም የኢትዮጵያ መንግስት ያወጀው በህወሓት እንደተጣሰ ታምናለች።
- ህወሓት ከእዝያ በኃላም ጦርነቱን ቀጠለ/
- የምግብ እርዳታው እንዲደናቀፍ ያደረጉ የህወሓት ተዋጊዎች ናቸው በጅቡቲ እና በአዲስ አበባ መሃል ያለውን መንገድ ለመቁረጥ ሞክረው ነበር።
- በእዚህ ወረራቸው የስደተኞች ቁጥር እና የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እንዲጨርም አድርገዋል።
- የኢትዮጵያ መንግስት የሰብዓዊ ቀውሱን ለመቀነስ የዓለም ምግብ ፕሮግራም እርዳታ መኪናዎች ወደ ትግራይ እንዲሄዱ ማድረጉ ይታወቃል።
- ኢትዮጵያ የሚደረገውን የሰብዓዊ እርዳታ ከፖለቲካዊ ጉዳይ ውስጥ መውጣት እንዳለበት የሩስያ እምነት ነው። በእዚህ በኩል መርዛማ ሚድያዎች በመጠኑ ዕድል ያገኙ ይመስላል።
''We are convinced to address the situation in Northern Ethiopia (Tigray), it is necessary to depoliticize the North Ethiopian Humanitarian activities. In this regard the toxic media atmosphere seems gets a little chance.'' Russia Ambassador to UN Security Council, August 26,2021

- የሰብዓዊ ዕርዳታ ከትግራይ ሌላ ለሌሎቹ ለምሳሌ አምሐራ፣ኦሮምያ እና ሱማሌም ያስፈልጋቸዋል 
- እነኝህ አካባቢዎች በድርቅ፣በጎርፍ እና በአንበጣም ጭምር የተጎዱ ናቸው።
- ይህ ደግሞ በተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ እርዳታ መርህም የሚያዘው ነው።
- የፖለቲካ ንግግር ከተባለም በራሳቸው በኢትዮጵያውያን አነሳሽነት እና መሪነት እንጂ በውጭ ኃይል ግፊት ሊሆን አይገባም።
- የሰኔው የኢትዮጵያ ምርጫ ያሳየን ነገር የተመረጠው የኢትዮጵያ ፈድራል መንግስት የኢትዮጵያን አንድነት የመጠበቅ አቅም እንዳለው ነው።
- እኛ ኢትዮጵያውያን አሁን ያለውን ችግር እንደሚፈቱት እና ወደ ሰላማዊ ሁኔታ ሀገሪቱን እንደሚመልሱ ሙሉ እምነት አለን።
- የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ እና የአፍሪካ ህብረት የሚጠበቅባቸው የኢትዮጵያ መንግስትን መልካም ጅምሮች በቀላሉ መደገፍ ብቻ ነው።
- ከእዚህ በተለየ በተናጥል በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የሚደረግ የተናጥል ዕቀባ ወደ የባሰ አለመግባባት የሚመራ ነው።
- ከእዚህ በተጨማሪ ማንም ይህንን ጉዳይ (የትግራይን ጉዳይ) በፀጥታው ምክር ቤት በመወያየት መፍትሄ አያመጣም።ከእዚህ ይልቅ እያንዳንዱ የፀጥታው ምክር ቤት አባል ችግሩን ለመፍታት የራሱን ጥረት ሲያደርግ ነው።
No one can solve the problem (Tigray conflict) by discussing in Security Counsel but the solution comes when each member of the security council made its contribution to solve the problem.
- የሚያስፈልገው የሁለትዮሽ ግንኙነት ከኢትዮጵያ ጋር በመፍጠር መፍታት ነው።
አመሰግናለሁ!




ቻይና 

- የሰብአዊ እርዳታ ለአማራ እና አፋር ክልልም የሚያስፈልግበት ሁኔታ አለ።
- ቻይና ለትግራይ ክልልም እርዳታ ልካለች።
- ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ሲሰሩ የተባበሩት መንግሥታት መመርያ እና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ሊያከብሩ ይገባል።
- ቻይና የኢትዮጵያ መንግስት እና ሕዝብ የሀገራቸውን አንድነት፣መረጋጋት እና ሰላም ለመደገፍ የሚያደርጉትን ጥረት ሁሉ ትደግፋለች።
- የዓለም አቀፍ ማኅበረስብም ይህንኑ ሊያደርግ ይገባል።
- ቻይና በሰብዓዊ መብት ሰበብ በኢትዮጵያ ላይ የሚደረግ ማናቸውንም ጣልቃ ገብነት አጥብቃ ታወግዛለች።
- እኛ የአፍሪካ ጉዳይ በአፍሪካውያን ይፈታ የሚለውን መርህ እንደግፋለን።
- ቻይና የኢትዮጵያ መንግስት አሁን ያለውን ችግር ለመፍታት አቅምም ሆነ ጥበብ እንዳለው እና የኢትዮጵያ ሕዝብም አሁን የገጠመውን ፈተና በአሸናፊነት እንደሚወጣ ታምናለች። 
- ቻይና ለኢትዮጵያ ሰላም እና አንድነት ከሚሰራ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ጎን ሁል ጊዜም ትቆማለች።

ሜክሲኮ 

- ስቶንያ፣ፈረንሳይ፣ኖርዌይ፣አየርላንድ፣እንግሊዝ እና አሜሪካ ይህንን ስብሰባ በመጥራታቸው አመስግናለች።
- ኢትዮጵያ የሜክሲኮ ታሪካዊ ግንኙነት ያላት ሀገር ነች።
- ኢትዮጵያ ለአፍሪካም ሆነ ለአፍሪካ ቀንድ መረጋጋት ቁልፍ ሀገር ነች።
- በተባበሩት መንግሥታት እና በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ኮሚሽኖች በጥምረት እየተደረገ ያለውን የሰብዓዊ ጥሰት ምርመራ ውጤት ሜክሲኮ ትጠብቃለች።
- የባንክ እና የመገናኛ መቆም የእርዳታ ሂደቱን ያደናቅፋል።
- ሁሉም ወገኖች የተባበሩት መንግስታትን እና የዓለም አቀፍ ሕግ ማክበር አለባቸው ብላ ሜክሲኮ ታምናለች።
- የቀድሞው የናይጀርያ ፕሬዝዳንት ኦቦሳንጆ የአፍሪካ ቀንድ ጉዳይ ተወካይ ሆነው በአፍሪካ ህብረት መሾማቸውን እንደግፋለን።




ሕንድ 

- አሁን ግጭቱ እየተስፋፋ ያለው በህወሓት ነው።ወደ አጎራባች ክልሎች አማራ እና አፋር በመግባቱ 
- በእዚህ ወረራውም ሕፃናት፣ልጆች እና አዛውንቶች ተገድለዋል።
- ህወሓት የሕፃናት ወታደሮች እየተተቀመችም ነው።ይህም ትልቅ የሰብዓዊ ጥሰት ነው።
- የኢትዮጵያ መንግስት በሰኔ ወር ላይ የወሰደው የተኩስ አቁም ትልቅ እርምጃ ነበር።
- ሆኖም ግን በህወሓት በኩል በተፈጠረው ወረራ የአንድ ወገን ጥረት ውጤታማ አልሆነም።
- የሰብዓዊ ዕርዳታው ቁጥር ጥሩ እንደሆነ እና እየደረሰ እንደሆነ የተባበሩት መንግሥታት ኦቻ ስታትስቲክስ ያሳያል።
- በኢትዮጵያ መንግስት እና በእርዳታ ድርጅቶች መሃል ያለው ግንኙነትም ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ በእጅጉ ተሻሽሏል።
- ለእዚህም ማሳያው በሰመራ የተመሰረተው የኢትዮጵያ መንግስት የዓለም ምግብ ድርጅት እና የእርዳታ ድርጅቶች በጥምረት የመሰረቱት ጣብያ በአፋር በኩል ምግብ ለማድረስ ጥሩ ድልድይ ፈጥሯል።
- ስለሆነም ኢትዮጵያ አሁን ከዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ሁሉንም ዓይነት ድጋፍ ያስፈልጋታል።
- የትግራይ ክልል ችግር መፍትሄ ኢትዮጵያዊ መር መሆን አለበት (The solution to the Tigray region must be Ethiopian led.)

ከእዚህ በተጨማሪ የኬንያ እና የእንግሊዝ አምባሳደሮች የተናገሩ ሲሆን በተባበሩት መንግሥታት  የኢትዮጵያ ባለሙሉ አምባሳደር ታዬ ሕፅቀሥላሴ  ንግግር አድርገዋል።አምባሳደር ታዬ ሕፅቀሥላሴ በንግግራቸው ኢትዮጵያ የሕግ ማስከበር ስርዓቱን ጨምሮ ሉአላዊት ሀገር በመሆኗ ሙሉ መብቷ መሆኑን እና ከእዚህ ውጭ የሚደረግ የውጭ ጣልቃ ገብነትን ኢትዮጵያን ፈፅሞ እንደማይቀበሉ በለሰለሰ የዲፕሎማሲ ቃል ተናግረዋል። 

==================///================

==========================
ማስታወቂያ /Advertisement 
===============================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 







Saturday, August 21, 2021

በኦስሎ፣ኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ሽብርተኛው ህወሓት በኢትዮጵያ ላይ እየፈፀመው ያለውን ሀገር የመበተን ወንጀል፣ግድያ እና በኤርትራውያን ስደተኞች ላይ የፈፀመውን ጭፍጨፋ በማውገዝ ዛሬ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ያደረጉት ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ሙሉ ቪድዮ።

Dagens enorme antall etiopiere og eritreere demonstrerer i Oslo, Norge.21.august 2021.

በኦስሎ፣ኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሽብርተኛው ህወሓት በኢትዮጵያ ላይ እየፈፀመው ያለውን ሀገር የመበተን ወንጀል፣ግድያ እና በኤርትራውያን ስደተኞች ላይ የፈፀመውን ጭፍጨፋ በማውገዝ ዛሬ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ያደረጉት ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ሙሉ ቪድዮ።

ይህ ዛሬ ነሐሴ 15/2013 ዓም በኦስሎ ኖርዌይ የተደረገው ሰልፍ የተዘጋጀው በኢትዮጵያውያን እና በኤርትራውያን የሲቪክ ድርጅቶች ሲሆን ዝርዝር ፣መረጃ የሚያገኙበት በእዚህ ቪድዮ ውስጥ 
  • ህይወታቸውን በሽብርተኛው ህወሓት ላጡት የጥቂት ሰኮንዶች የህሊና ፀሎት ፣
  • ከኦስሎ ማዕከላዊ ክፍል ወደ ኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተደረገ ሰልፍ 
  • የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ሲቪክ ድርጅቶች ተወካዮች ንግገር፣
  • የኤርትራ ወጣቶች ተወካይ ንግግር፣
  • የኢትዮጵያ ሲቪክ ድርጅቶች ተወካይ ንግግር፣
  • የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ሲቪክ ድርጅቶች ግብረኃይል ለኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የተለያዩ ክፍሎች፣ለኖርዌይ ፓርላማ ውጭ ጉዳይ ንዑስ ክፍል፣ለኖርዌይ ልማት ትብብር ክፍል እና በኖርዌይ ለሚገኙ የተለያዩ የኖርዌይ የፖለቲካ ድርጅቶች የተዘጋጀው ደብዳቤ ይዘት እና 
  • ከሰልፉ ተሳታፊዎች አስተያየት ያገኛሉ።
የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ሲቪክ ድርጅቶች ግብረ ኃይል ከሰኞ ጀምሮ ከላይ ለተጠቀሱት የኖርዌይ መንግስት ሚኒስትር፣ፓርላማ እና ልዩ ልዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በአካል እየቀረበ ደብዳቤውን ለመስጠት እና ለማስረዳት ቀጠሮ ተይዟል።
ሙሉ የሰልፉን ቪድዮ ከስር ይከታተሉ።

I dag var et stort antall etiopiere og eritreere på fredelig demonstrasjon i Oslos gater mot terroristen TPLF som drepte etiopiere i Afar og Amhara og eritreiske flyktninger. Demonstrasjonen ble startet fra Oslo sentrum og endte foran det norske utenriksministerens hovedkontor.

Se hele videoen av demonstrasjonen ved å klikke på lenken.

ይህ የቀጥታ ስርጭት የተቀረፀው ከኦስሎ፣ኖርዌይ ጉዳያችን እና ከለንደን ሉሲ ራድዮ እና ዘውዱ ሚድያ ጋር በጥምረት በመሆን የቀረበ  ነው።





Thursday, August 19, 2021

የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ - ትግራይ ክልል፣የአማራ ክልል፣ወቅታዊው የምጣኔ ሀብት እና የኢትዮጵያ ወቅታዊ ዲፕሎማሲ ሁኔታ

አዲስ አበባ Addis Ababa
Photo Getty images

  • ኢትዮጵያ በምንም ዓይነት ፈታኝ ሁኔታ ላይ ብትሆንም ይህ ፈታኝ ሁኔታ ይዞላት የመጣው ዕድል ደግሞ አለ።

ጉዳያችን ምጥን ዳሰሳ 

መነሻ 

የኢትዮጵያ ወቅታዊ  ሁኔታ በተመለከተ የተለያየ ሰው ካለው መረጃ እና የቀደመ የኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግር እንዲሁም ወደፊት እየሄደችበት ካለው ሁኔታ አንፃር የየራሱን ዕይታ ይሰጣል።በተለይ የእኛ ማኅበረሰብ የመረጃ ምንጩም ቡና ሲጠጣ በሚ ወያየው፣ወይንም ከሚኖርበት መንደር ውስጥ የተሻለ ግንዛቤ አለው ብሎ የሚያስበው ሰው የሚሰጠው አስተያየት፣ ከእዚህ ባለፈ የውጭ መገናኛ ብዙሃን ለምሳሌ እንደ የአሜሪካ ድምፅ እና የጀርመን ራድዮ በሃገርኛ መግባብያ የሚያዘጋጁት  የምዕራቡን ፍላጎት የሚያንፀባርቁ የፕሮፓጋንዳ ስራዎች ናቸው።ከእዚህ በተለየ ግን አሁን ባለው ሁኔታ የማኅበራዊ ሚድያ እንደፈለገ የሚነዛው የሐሰት ወሬ ሌላው የአብዛኛው ህዝባችን የመረጃ ምንጮች ናቸው።

እዚህ ላይ የመንግስት እና የግል መገናኛ ብዙሃን የመረጃ ምንጭነትን መዘንጋት አይገባም።ከእነኝህ የመረጃ ምንጮች በተለየ ግን በኢትዮጵያ እየሆነ ያለውን ሕዝብ እንዲረዳው ትክክለኛ የመግለጥ እና የማስረዳት ሥራ ያስፈልጋል።መረጃዎች በድፍን ለሁሉም ሕዝብ መረጃ አይሆኑም።ያልተቆረጠ ብርቱካን ብርቱካኑን ቆርጦ  እንዴት እንደሚበላ ለማያውቅ ልጅ መጫወቻ እንጂ የሚበላ መሆኑን አያውቅም።በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታም እንዲሁ ለሕዝቡ እንዴት ጉዳዮችን ማየት እንዳለበት በቅጡ ዕይታን ማቅረብ ያስፈልጋል እንጂ ድፍን መረጃዎች እና ዜናዎች ብዥጎደጎድ ዜናውን እና መረጃውን እንዴት እንደሚረዳው ለማያውቅ ሕዝብ የፈለገው በፈለገው መንገድ እየትነተነ የሚያሳስት እና ሽብር የሚነዛ ሞልቷል። በመሆኑም አሁን ያለው ወቅታዊ የኢትዮጵያ ሁኔታ በተመለከተ ጉዳያችን ምጥን ዳሰሳ እንደሚከተለው ታቀርባለች።

ትግራይ ክልል

ትግራይ ክልል አሁን ህዝቡ ያለበት ሁኔታ ከተለያዩ በእርዳታ ድርጅቶች ሰራተኝነት በክልሉ ከሚገኙ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ሰራተኞች የሚሰማው በጣም አሳዛኝ ነው።ክልሉ ትምህርት ቤቶችን ወደ የማሰልጠኛነት ቀይሮ የትምህርት ቤት መቀመጫ ሳይቀር እየተፈለጠ ለማገዶ መጠቀም ተጀምሯል።መብራት የለም፣የጤና ጣብያዎች ፕላስተር ብርቃቸው ሆኗል።የምግብ ዋጋ ይህን ያህል ነው ለማለት መጀመርያ ባንክ ኖሮ ገንዘቡ ሲገኝ ነው።ባጭሩ ክልሉ የሚገኙ ከተሞች ወደ ድንጋይ ዘመን እየተምዘገዘጉ ነው። ቀድሞ የነበሩ ፋብሪካዎች እነሞሰበ ሲብንቶ ፋብሪካ መኪናዎች ከአማራ ክልል ለመዝረፍ እንደወጡ ሲመለሱ የአስከሬን ክምር እየጫኑ ያውም እድለኛ የሆኑት ወደ ትግራይ ሲመለሱ የቀሩት በሰቆጣ፣አላማጣ የቆረጠው መከላከያ እና ልዩ ኃይል መመለሻ አጥተው እዚሁ ወሎ እና ደቡብ ጎንደር ቆላዎች እየታከኩ ከቦታ ቦታ እየተንከራተቱ ነው።

ሽብርተኛው ህወሓት ወደ አማራ ክልል እና አፋር ጀሌውን የላከው በሳምንት ውስጥ የጅቡቲ አዲስ አበባን መንገድ እዘጋለሁ፣ወደ ሱዳን የሚወስደውን መንገድ አስከፍታለሁ፣ የቆመውን የመብራት እና የበጀት ገንዘብ በእዚህ አስገድጄ አስለቅቃለሁ የሚሉ ነበሩ። ሆኖም ግን በአፋር ክልል ለቁጥር የሚያታክት ሰራዊቱ ከአፋር አሸዋ ጋር ተደባለቀ።አስከሬን ለመቅበር ሳምንታት አልበቃ አለ።ይህ በእንዲህ እያለ ትግራይ ልጆቻቸውን ፈልገውም ሳይፈልጉም የላኩት ልጆቻቸው ማለቃቸውን ህወሓት ባይነግራቸው የእናት ስድስተኛ የስሜት ህዋሳቷ ይነግራታል።ለእናቶች መልስት መስጠት ያልቻለው የጌ ታቸው ረዳ ቡድን ያለው አማራጭ ድል እያደረግን ነው እያለ መዋሸት ነው።የትግራይ ክልልን ሁኔታ የሚገልጠው አባባል ህወሓት ወደ የድንጋይ ዘመን እየቀየራት ነው።ይህ በእዚሁ ከቀጠለ ደግሞ ለመጪዎቹ 30 ዓመታትም ተመልሳ ለመነሳት የምትችልበት ሁኔታ አይሆንም።እውነታው ይሄው ነው።እነጌታቸው እና ደብረ ፅዮን አይናቸው እያየ አንድ ብርጭቆ ውሃ እና የአንዲት አንፖል መብራት አገልግሎት ለሕዝቡ የማያቀርቡ ከመቀሌ አድዋ የሚመላለሱ በጭንቀት የተወጠሩ ሆነው ነው የቀሩት።ይህንን ተመልክቶ ለለውጥ ህዝቡ እንዳይነሳባቸው ደግሞ በጦርነት መወጠር ስላለባቸው እየሰበሰቡ ወደ አማራ ክልል ዘርፈህ ብላ ብለው ይልኩታል። 

የአማራ ክልል

የአማራ ክልል በጎጠኛው ህወሓት ግልጥ እና ስውር ተግባሮች አማካይነት በርካታ የማዳከም እና ሕዝቡን እንደህዝብ የማደህየት ሥራ ሲሰራ ኖሯል። በአሁኑ ጊዜ ክልሉ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች በተለይ በህወሓት ዘረፋ እና ወረራ ምክንያት ይዟል።ይህ በራሱ የሚፈጥረው ጫና ቢኖርም ክልሉ ግን በአሁኑ ጊዜ ከሊቅ እስከ ደቂቅ በሚባል ደረጃ ሽብርተኛ ህወሓትን ለመመከት ተነስቷል።በእዚህም  ሺዎች ወደ ስልጠና ገብተዋል።ሌሎች ሺዎች ደግሞ ታጥቀው ፍልምያ ገብተዋል።አሁን በአማራ ክልል ሰርጎ የገባው የህወሓት ጀሌ  በተበታተነ መልኩ በዘረፋ እና አንዳንድ ቦታ ሸሽተው የተበተኑት እንደገና ለመሰባሰብ እየሞከሩ መንደሮች ላይ ጥቃት ይፈፅማሉ። በገጠር ነክ የወረዳ ከተሞች ቀድሞም ከወረዳው ያለፈ የፖሊስ ኃይል  ስለሌለ እየተደበቁ እየገቡ ፎቶ መነሳት እና ሽብር ፈፅሞ መውጣት ከእዚህ ባለፈ ደግሞ ሴቶችን መድፈር፣ንብረት መዝረፍ እና ከተሞች ላይ ለምሳሌ ወልድያ እና ደብረታቦር ከተማ ላይ ከባድ መሳርያ በመተኮስ አለን ለማለት ይሞክራሉ።እዚህ ላይ በአማራ ክልል አንዳንድ በወንጀል የተገለሉ እና ከወረዳ ስልጣን የወረዱ ከሽብርተኛው ቡድን ጋር እየተመሳጠሩ በሕዝቡ ላይ ደባ ለመስራት የሞከሩትን ህዝቡ በአደባባይ እርምጃ መውሰዱ ነው እየተሰማ ያለው። 

የአማራ ክልል ሕዝብ አሁን ምናልባትም በቅርብ ታሪኩ በእዚህ ደረጃ ታጥቆ አያውቅም።በርካታ ጀግኖች በየቀኑ እየወጡ ነው።ታንክ ላይ ዘለው ገብተው ተዋጊውን በስለት የሚያወርዱ፣ምግብ ቤት ገብተው ሊመገቡ ያሉትን አስራ አንዱ ላይ አንዱ ብቻውን እርምጃ የሚወስድበት እና መትረጌስ ከሚተኩሰው ሰው ጀርባ ድንገት ደርሰው በዱላ የሚማርኩ ብዙ ያልተነገረላቸው ጀግኖች ወጥተዋል።የህወሓት ጀሌ አሁን በየትም ከተሞች ታየ ቢባል እውነታው አንድ ነው። ይሄውም በገባበት የሰሜን ወሎ መስመር መውጣት እንደማይችል ግልጥ ሆኗል ስለሆነም ሰተት ብሎ የገባበት ወጥመድ ለመውጣት መንከራተቱ ሒደ ላይ ነው አሁን እዚህ ከተማ ታዩ እስህ ከተማ ከባድ መሳርያ ጣሉ እየተባለ የሚወራው።ብዙዎቹ ገባንባቸው የሚሉት ከተሞች ደግሞ የፎቶ ከተሞች ናቸው።የአማራ ክልል ይህንን የህወሓት ወረራ ከመቀልበስ አልፎ የትግራይን ሕዝብ ከህወሓት የማላቀቅ አቅም አለው።ይህንን አቅም ደግሞ በቁጭት እንዲሰራ የሚያደርገው የራሱ የህወሓት የጭካኔ ተግባር ነው።የአማራ ክልል ይህንን ወረራ በሕዝብ ደረጃ እንዲመቀት ያደረገው ዘግይቶ ነው።ህወሓት ግን ሕዝቡን በግድም በውድም ያለውን እንጥፍጣፊ የሰው ኃይል ሳይቀር ወደ አማራ ክልል የላከው ዘርፋችሁ ብሉ ብሎ ነው እንጂ እንደማያሸንፍ ያውቀዋል።ሌላው ቀርቶ ዛሬ በደብረ ታቦር ከተማ ላይ ሶስት የከባድ መሳርያ የተኮሱት ሶስቱ ጀሌዎች ውስጥ ሁለቱ ወዲያው እርምጃ ሲወሰድባቸው አንዱ መማረኩ ለማወቅ ተችሏል።የአማራ ክልል በተመለከተ ጠንካራ የደህንነት ሥራ፣የቁሳቁስ እና የገንዘብ እርዳታ እና በወረዳ እና ታች ቀበሌ ደረጃ ያሉ አመራሮች አቅም በጊዝያውነትም ቢሆን ህዝቡ ጣልቃ እየገባ የአስተዳደር ስራዎቹን ማገዝ አስፈላጊ ነው 

 ወቅታዊው የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት

ጦርነት የምጣኔ ሀብት ይበላል።በተለይ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በሽብርተኛው ህወሓት እጅ ዛሬም የሚ ዘወርበት መንገድ በመኖሩ በምጣኔ ሃብቱ ላይ ከባድ ሴራ እየተበተበ ነው።በመሆኑም የዋጋ ንረቱ ቀላል አይደለም።ይህ ብዙ ጊዜ የተባለ ነው።አሁን መንግስት እና የግሉ ዘርፍ ይህንን የምጣኔ ሀብት ችግር በተመለከተ መውሰድ የሚገባቸው ሶስት እርምጃዎች አሉ። እነርሱም -
1) በተመረጡ ትልልቅ ከተሞች መንግስት መሰረታዊ ፍጆታዎች ከገበያው በተሻለ ዋጋ መንግስት ማቅረብ አለበት።ይህ ከመንግስት ሰራተኞች ጀምሮ እስከ የከተማ ድሆች ድረስ ለመጪዎቹ ጥቂት ወራት መዝለቅ ይችላል።የቀድሞው ወታደራዊ መንግስት በጦርነት ውስጥ በነበረበት ጊዜ ለከተማ ነዋሪ በቀበሌ ኅብረት ሱቅ አማካይነት በማቅረቡ ሕዝቡ በቅናሽ የምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ፍጆታዎች ያገኝ ነበር።

2) በተወሰኑ የምግብ ሸቀጦች እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ሸቀጦች ላይ ቀረጥ በግዚያዊነት ማንሳት ወይንም በጣም መቀነስ የዋጋ ቁጥጥር ማጠናከር እና 

3) ከመስከረም ጀምሮ የሚሰበሰበው የእህል ምርት በቁጠባ መጠቀም እንዲቻል መንግስት በባንኮች ካለው ገንዘብ በብድርም ቢሆን በመውሰድ ወይንም እራሳቸው ባንኮቹ በስራው እንዲገቡበት እና በሚያገኙት መጠነኛ ትርፍ ዋናቸውን እንዲመልሱ በማድረግ ከገበሬው ላይ እህል መንግስት በብዛት መግዛት እና መልሶ በተመጣጣኝ ዋጋ የመሸጥ ሥራ ማከናወን።በእዚህ ከልክ የለሽ አትራፊ ምርቱን ከማዳን ጀምሮ ተጠቃሚውም በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ ይረዳዋል።


የኢትዮጵያ ወቅታዊ ዲፕሎማሲ ሁኔታ

ኢትዮጵያ የራሷን መብት ስታስከብር እና በምዕራባውያን ጫማ ልክ ማሰብ ማቆሟን የተረዱት ምዕራባውያን በኢትዮጵያ ላይ የቻሉትን ያህል ዘመቱባት።በሽብርተኛው ህወሓት ጎን ሆነው አዋከቧት።ከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣናት ወደ አዲስ አበባ ተመላለሱ።መመላለሳቸው ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዱ ጉዞ የኢትዮጵያ ባለስልጣናትን እነርሱ ባሉት መንገድ ለማስገደድ እና እጅ ለመጠምዘዝ ተነሱ። ይህ ሁኔታ ላለፉት ወራት ቀጥሎ ቆይቷል። የኢትዮጵያ ጉዳይ ዘንድሮ ከጂ 7 ስብሰባ እስከ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታ ምክር ቤት ስብሰባ ድረስ ተነሳ።ኢትዮጵያ በእዚህ ዓይነት ደረጃ ርዕስ የሆነችው ምናልባት በ1977 ዓም በደረሰው የድርቅ አደጋ ሊሆን ይችላል። 

ይህ የተበላሸ የዲፕሎማሲ ሂደት አንዱ ዓላማ ለምዕራቡ ፍላጎት የታዘዘ አመራር በአራት ኪሎ ለማስቀመጥ ብቻ ሳይሆን ይህ ካልሆነ ደግሞ ኢትዮጵያን መበተን እና እንደ ሶርያ፣የመን እና ሊብያ እርስ በርሷ የምትጋደል ሀገር መፍጠር ነው።ሆኖም ግን ይህ ሁኔታ በትናንትናው የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ የቱርክ ጉብኝት ነፋሱን ቀይሮታል። በእዚህም ኢትዮጵያ በይፋ የዲፕሎማቲክ ማጥቃት ጀምራለች። የምስራቅ አፍሪካ አራት ሀገሮች ማለትም ኢትዮጵያ፣ጅቡቲ፣ኤርትራ እና ሱማልያ ለማስተባበር ኢትዮጵያ በዶ/ር ዓብይ  አነሳሽነት የተጀመረው ሥራ ፍሬ የማግኘት እድሉ እያደገ ነው።በእዚህም ኢትዮጵያ ከቱርክ ጋር መልካም ግንኙነት በመፍጠር የዋይት ሃውስ ባለስልጣናትን አስደንግጧል።በእዚህም ኢትዮጵያ ለምዕራቡ ዓለም ምላሽ '' መፈንቅለ ዲፕሎማሲ  '' (Diplomatic coup d'etat  ) አድርጋለች ማለት ይቻላል።በእዚህም ኢትዮጵያ የነበረውን የዲፕሎማሲ ከባቢያዊ ሁኔታ ቀይሮታል።በቀጣይ የሚታዩት ውጤቶች የምናየው ነው።ሆኖም ግን ከግብፅ እና ሱዳን አንፃር ራሱን የቻለ ማስጠንቀቅያ ያዘለ ነው።አሜሪካም በቀጣይ የአካሄድ ለውጥ ማድረግ እንዳለባት ከማመን ውጭ በያዘችው የደረቀ አካሄድ ልሂድ ብትል የፖሊሲ መሰበር እንደሚገትማት ግልጥ በሆነ መልዕክት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ እንዳገኘች መረዳት ይቻላል።የቱርክ ወዳጅነት ከኢትዮጵያ ጋር ብቻ አይደለም ዛሬ ምሽት የሱማልያው ፕሬዝዳንት ፈርማጆ ጠቅላይ ሚንስትር ዓቢይ ከቱርክ ከተመለሱ በኃላ በትውተር ገፃቸው ላይ በቱርክ እና በሱማልያ መካከል ያለው ግንኙነት የጠነከረ መሆኑን በማመስገን ፅፈዋል።



ይህ ማለት ኢትዮጵያ እየሄደችበት ያለው የዲፕሎማሲ አፀፋዊ ምላሽ የአካባቢ ሃገራት ማለትም በሱማልያ እና ኤርትራ አንፃርም የተናበበ መሆኑ ለምዕራቡ ዓለም በቀላሉ ለመሰርሰር እንደሚያስቸግረው አመላካች ነው።ለእዚህ ነው ያላቸው አማራጭ በደረቀ ፖሊሲ ቀጥሎ ፖሊሲው ሲሰባበር ማየት ወይንም ነገሮችን አለሳልሶ መደራደር እና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አክብሮ በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ጥቅም ላይ መደራደር።በህደቱም የህወሓት ሽብርተኛ ጋር የሚኖር ግንኙነት እና ድጋፍ ማቆም ያላቸው አማራጭ ነው።

ባጠቅላይ ኢትዮጵያ በምንም ዓይነት ፈታኝ ሁኔታ ላይ ብትሆንም ይህ ፈታኝ ሁኔታ ይዞላት የመጣው ዕድል ደግሞ አለ። የመጀመርያው ከወራት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ወደ ውትድርና ብዙ ሕዝብ አይመለመልም የሚል ማሳሰብያ በተወካዮች ምክርቤት ስብሰባ ተናግረው ነበር።ን ይህ ተቀይሯል።የህወሓት ወረራ ኢትዮጵያ የብዙ መቶ ሺዎች ሰራዊት ባለቤት ያደርጋታል።ይህም በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በተሻለ ብቻ ሳይሆን በአሸናፊነት እንድትወጣ ብቻ ሳይሆን ለመካከለኛው ምስራቅ አንዳንድ ሀገሮች ዛቻም የማትቀመስ  አድርጎ ያወጣታል። በሌላ በኩል በምዕራብ ወጥ የትብተባ አዙሪት የምትወጣበት እና በራሷ የምትራመድበት ወርቃማ ጊዜ ይፈጥራል። ይህ ብዙ ማለት ነው።ኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ታሪክ፣ ባሕል እና ስልጣኔ ያላት ሀገር በመሆኗ ከተፈጠሩ ሁለት መቶ ዓመታት ገደማ የሆናቸው በቀላሉ የምያጠፏት አድርጎ የማየት አባዜ ይቀበራል ወይንም ሽባ ይሆናል።ስለሆነም የአሁኑ የኢትዮጵያ ሁኔታ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ተስፈንትራ ለመውጣት የምችልበት  እጅግ ወርቃማ ጊዜ ነው። ይህ ግን የሚሆነው ኢትዮጵያን ከሽብርተኛ ህወሓት እጅ አስጥሎ በመረጠችው መንገድ የመሄድ እና ከድህነት የመውጣት እድሏን ከፍ ያደርገዋል።ስለሆነም የኢትዮጵያ መንገድ አዋጭ ብቻ ሳይሆን አፍሪቃንም ይዛ እንድትነሳ የሚያደርግ ሂደት ነው። ይህንንም የሚያውቁት ምዕራባውያን  ኢትዮጵያ የህወሓት የጎሳ ፖለቲካ ተጭኖባት ስትራኮት እንድትኖር ሽብርተኛውን ቡድን ሲደግፉ ይታያሉ። ይህ ግን አዋጭ እንዳልሆነ እራሳቸውም ገምግመው አይረዱም ማለት አይቻልም።ግራ መጋባት እና የተሳሳተ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ጥቅማቸውን በእዚህ የሚያስጠብቁ መስሏቸው ይለፋሉ።

====================  
================
 ማስታወቂያ / Advertisment
====================
የጓደኞችዎን ወይም የቤተሰብዎን የሞባይል አየር ጊዜ ለማሳደግ ከዚህ በታች ያለውን አገናኝ ጠቅ ያድርጉ።
በአንድ ሁኔታ ውስጥ በሚመገብ ቤት የሚኖር የቤተሰብ እውነተኛ የወዳጅነት ስልክዎ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን የሚመለከት ከስር ሊ መረጃን ይጫኑ - 
Open the link to mobile top up at home


Tuesday, August 17, 2021

ሱዳን ልቧ አብጧል።የሚያስተነፍሳት ትፈልጋለች። በኢትዮጵያ ላይ ዳግም ወረራ በመፈፀም ተጨማሪ መሬት ለመውረር እንደምታስብ አዲስ ምልክት ሰጥታለች።ኢትዮጵያውያን ለሀገራችን ዘብ የምንቆምበት ወሳኝ ጊዜ ላይ ነን።



ጉዳያችን ዜና / Gudayachn News 

ሱዳን በአሜሪካ አይዞህ ባይነት ከአቅሟ በላይ እየተንጠራራች ነው። የውስጥ ውጥንቅጥ ፖለቲካዋን ሳታጠራ ኢትዮጵያ በውጥረት ላይ መሆኗን የገመተችው ሱዳን ከእዚህ በፊት ከወረረችው መሬት በተጨማሪ አዲስ መሬት ልትወር እንደምትችል በአደባባይ ትናንት ተናግራለች።ይህንን የተናገረችው ትናንትየሱዳን  የሽግግር ምክርቤቱ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አልቡርሃን እና ጠቅላይ ሚኒስትር ሃምዶክ 67ኛ ዓመት የጦር ሰራዊቱን በዓል በአልፋሻቅ የኢትዮጵያ ድንበር አቅራብያ ባከበሩበት ጊዜ ነው። ባለስልጣናቱ እንደተናገሩት የሰራዊቱን በዓል በአልፋሻቅ ያቀበሩበት ምክንያት ቦታው የሱዳን መሆኑን ለማስረገጥ እና ወደፊትም የሱዳን ሰራዊት በቦታው እንደሚቆይ ለማረጋገጥ ስለፈለግን ነው ብለዋል።

''ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም እንፈልጋለን።ነገር ግን የመሬታችን ኢንች እንዲነካ አንፈልግም'' ያሉት የሱዳኑ ሽግግር ምክርቤት ፕሬዝዳንት  በአልፋሻቅ አሁንም በኢትዮጵያ የተያዙብን ስድስት ቦታዎች አሉ።አሁንም ኢትዮጵያ ድምፃችንን ትስማን ሲሉ ተናግረዋል። በመቀጠልምእንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2017 ዓም የሱዳን ጦር ሰራዊት ቦታዎቹን ለማስመለስ ጥረት አድርጎ ነበር ካሉ በኃላ ሆኖም ግን በኃላ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብን ፈርቶ እና በወቅቱ የነበረው ስርዓት ቸልተኝነት እንዲሁ ቀረ ሲሉ ተደምጠዋል።

ይህ በእንዲህ እያለ ኢትዮጵያ በሁሉም የወታደራዊ ማሰልጠኛዋ ከፍተኛ ቁጥር ያለው አዲስ እና ወጣት ሰራዊት ሌት ከቀን እያሰለተነች ነው።በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩት አዲስ ምልምሎች በጣም ወጣት፣ እጅግ ንቃት እና ቅልጥፍና የሚታይባቸው ናቸው። የኢትዮጵያ ይቅርብም ሆነ የሩቅ ጠላቶች ኢትዮጵያ በእዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ይህንን ያህል ሰራዊት ታዘጋጃለች ብለው ፈፅመው አልገመቱም።ምክንያቱም በእነርሱ ግምት ዘረኛው ህወሓት በኢትዮጵያ ለ27 አመታት የዘራው የጎሳ ፖለቲካ ሀገሪቱን ለመከላከል በኢትዮጵያዊነት የሚነሳ ትውልድ አሳጥቷታል ብለው ያስቡ ነበር።የሆነው ግን በተቃራኒው ነው።ኢትዮጵያ በዘመናዊ ታሪክዋ ውስጥ በእዚህ ደረጃ ልጆቿን ለውትድርና ለማሰልጠን የከተተችበት ጊዜ የለውም።

በመጨረሻም አሁን ባለው የሱዳን የፀብ ጫሪነት አካሄድ በተለይ የሽብርተኛው ህወሓት ጀሌ የሆነው እና በማይካድራ ጭፍጨፋ የተሳተፈው ሳምሪ በመባል የሚታወቀውን ቡድን ሱዳን በማሰልጠን ለኢትዮጵያ ቀጥተኛ የፀጥታ ስጋት መሆኗ ኢትዮጵያ ይህንን ቡድን ሱዳን ውስጥ ገብታ በአየርም ሆነ በልዩ ኃይል የመደምሰስ ሙሉ መብት አላት። ኢትዮጵያ ህወሓት ጁንታ በልዩ ኃይል እና ሚሊሻ ከመመከቱ አንፃር ዋናው የውግያ ግንባሯ ሱዳን ሊሆን ይችላል። አንድ ወቅት የኢትዮጵያ የጦር ኃይሎች አታማዥር ሹም ሌ/ጀነራል ባጫ ደበሌ የምንዘጋጀው ለህወሓት ጁንታ እንዳይመስላችሁ እኛ የምንዘጋጀው ለዋና አዝማቾቻቸው ነው።ማለታቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ሁኔታ ሁሉም ዘብ ሊቆምላት የሚገባበት ጊዜ ነው።ለነፃነቷ ደግሞ ከልጅ እስከ አዋቂ ተሰልፏል።በሰሞኑ የኢትዮጵያ ጦር ኃይልን ለመደገፍ በአዲስ አበባ ሊስትሮዎች ገንዘብ አተራቅመው ገቢ ሲያደርጉ፣በትናንትናው ዕለት ደግሞ መንግስትን ይህንን አድርግ እያልን እንደምናስቸግረው ሁሉ ዛሬ እኛም ለሀገራችን እና ለመንግስት ይህንን እናድርግ ብለን ገንዘብ አሰባሰብን ያሉ የአካል ጉዳተኞች ማኅበር ፌዴሬሽን ከአካል ጉዳተኞች  በፈቃዳቸው ከ100 ሺህ ብር በላይ ማዋጣታቸው የተሰማው በእዚህ ሳምንት ነው። 

ኢትዮጵያ  በፈጣሪዋ እና በልጆቿ ተጋድሎ ፈፅማ  ተሸንፋ አታውቅም! አሁንም አትሸነፍም!


Monday, August 16, 2021

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን የአሁኑ ቅዳሜ እኤአ ኦገስት 21/2021 ዓም በኦስሎ ከተማ ግዙፍ ሰልፍ ጠርተዋል።ከወጣት እስከ ሽማግሌ ለሀገሩ ድምፁን እንዲያሰማ ሀገራዊ ጥሪ ቀርቧል።


  • በሽብርተኛው ህወሓት የሕፃናትን ለውትድርና መመልመል፣የንብረት ዘረፋ፣ወጣቶችን በመርዝ የመመረዝ ጭካኔ፣በአፋር የተፈጁት ሕፃናት፣በትግራይ በኤርትራውያን ስደተኞች ወንድሞቻችን ላይ የተፈፀመው ግድያ  እና ሌሎችም በሰልፉ የሚወገዙ ናቸው።ይህንን ሳያወግዝ በቤቱ የሚቀመጥ በኖርዌይ የሚኖር ኢትዮጵያዊ እና ኤርትራዊ ይኖራል ተብሎ አይታሰብም። 

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሰሞኑን በሌላ ሀገር ለሚኖረው የዲያስፖራ ማኅበረሰብ ምሳሌ የሚሆን ተግባር ፈፅመዋል።ከአንድ ሳምንት በፊት በኖርዌይ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ እና ሲቪክ ማኅበራት አስተባባሪነት በሀገር ቤት በሽብርተኛው ህወሓት የጥፋት ዘመቻ ለተፈናቀሉት ወገኖች የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ ተጀምሯል።የገንዘብ ማሰባሰቡ ዘመቻ አሁንም የቀጠለ ሲሆን  ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ እሁድ ነሐሴ 9/2013 ዓም በዙም በተደረገ የዙም ስብሰባ ላይም በኖርዲክ ሀገራት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልዕከተኛ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር የሆኑት ክቡር አምባሳደር ድሪባ ኩማ፣ የዲያስፖራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት እና የብሄራዊ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ አይድሩስ ሀሰን አማካይነት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል።

በእዚሁ መርሃግብር ላይም ቀደም ብሎ የተጀመረው የገንዘብ ማሰባሰብ ሥራ የቀጠለ ሲሆን እስከ ዛሬ ድረስ በኖርዌይ ክሮነር ከ280 ሺህ በላይ ክሮነር ማለትም ከ 1ነጥብ 3 ሚልዮን ብር በላይ ተሰብስቧል።የገንዘብ መሰብሰቡ አሁንም የቀጠለ ሲሆን አሁንም ለተፈናቀሉ ወገኖች እርዳታ ማድረግ የሚፈልጉ ሁሉ የባንክ አካውንት ቁጥር 1503 43 13420 (የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ኢመርጅንሲ አካውንት) ወይም በቪብስ ቁጥር 647675 በመጠቀም ድጋፋቸውን ማድረግ ይቻላሉ።

ይህ በእንዲህ እያለ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን የአሁኑ ቅዳሜ  እኤአ  ኦገስት 21/2021 ዓም በኦስሎ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 7 ሰዓት (13 ሰዓት) ጀምሮ መነሻውን መሃል ኦስሎ ያርንባርንቶርጌ በተለምዶ ''ነብሩ'' ተብሎ በሚጠራው ቦታ መነሻውን አድርገው ሰልፍ ለማድረግ ቀጠሮ ይዘዋል።በሰልፉ ላይ በሽብርተኛው ህወሓት የሕፃናትን ለውትድርና መመልመል፣የንብረት ዘረፋ፣ወጣቶችን በመርዝ የመመረዝ ጭካኔ፣በአፋር የተፈጁት ሕፃናት፣ በትግራይ በኤርትራውያን ስደተኞች ወንድሞቻችን ላይ የተፈፀመው ግድያ እና ሌሎችም በሰልፉ የሚወገዙ ናቸው።ይህንን ሳያወግዝ በቤቱ የሚቀመጥ በኖርዌይ የሚኖር ኢትዮጵያዊ እና ኤርትራዊ ይኖራል ተብሎ አይታሰብም።

ይህ በኖርዌይ በሚኖሩ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ሲቪክማኅበረሰብ ድርጅቶች የተዘጋጀው ሰልፍ ላይ ከኦስሎ ውጭ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ወደ ኦስሎ እንደሚመጡ የሚጠበቀው ሰልፍ በርካታ ሕዝብ እንደሚገኝበት ይጠበቃል።መልዕክቱንም ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ለሁሉም እንዲያደርሱ ተጠይቀዋል።

ሰልፉን በተመለከተ በኖርዌይኛ የተለቀቀው ፖስተር ላይ የወጣው መልዕክት እንደሚከተለው ነው። 

Demonstrasjon mot TPLF og støttemarkeringer for fred på Afrikas Horn 

Dato- 21. august 2021

Tid- Kl.13

 Karl Johan foran Østbanehallen, Oslo ( በተለምዶ ነብሩ ጋር)

 Etiopiske og Eritreiske sivilsamfunnsorganisasjoner



=============================

==========================
ማስታወቂያ /Advertisement 
===============================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Saturday, August 14, 2021

ማዋከብ እና ማቀዝቀዝ ሁለቱ የሽብርተኛው ህወሓት ወቅታዊ ዘዴዎች ናቸው።ከገጠር እስከ ወረዳ ከተሞች፣ከሀገር ቤት እስከ ዲያስፖራ ልናውቀው የሚገባ ነው።



  • ኢትዮጵያ የህልውና ትንቅንቅ ላይ ነች።ትንቅንቁ ከተወካዩ የሽብር ቡድኑ ጋር ብቻ ሳይሆን ከዋሽንግተን እስከ ካርቱም፣ ከካይሮ እስከ የአረብ ሊግ ሀገሮች ሴራ ትብተባ ድረስ ይዘቃል።


ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ በተጠና መልኩ ሲሴርባት  የነበረው ሀገሪቱን የማፍረስ ዕቅድ ለማስፈፀም ጠላቶቿ ተነስተውባታል።የኢትዮጵያ ጠላቶች የረጅም ጊዜ እቅድ ለማስፈፀም እጅግ የተመቸ ሆኖ የተገኘው ደግሞ  ሽብርተኛው ህወሓት ነው።ህወሓት የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ሙሉ ውክልና ወስዷል።ለውክልናው ምላሽ ደግሞ የጦር መሳርያ እና የሎጀስቲክ ድጋፍ ከኢትዮጵያ ጠላቶች ያገኛል።ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ሁኔታ በ19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ከገጠማት የባዕዳን ከበባ የከፋ ደረጃ ነው።በ19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ኢትዮጵያን አንድ ካልሆነች ዙርያዋን በከበቧት የአውሮፓ ቅኝ ገዢዎች የመወረሯን አደጋ የተረዱት አፄ ቴዎድሮስ በዘመነ መሳፍንት የተነሱትን የአካባቢ ገዢዎች ወደ አንድ ለማምጣት ደክመዋል ብቻ ሳይሆን መሰረትም ጥለዋል።


ኢትዮጵያ በ19ኛው ክ/ዘመን ከትግራይ የገጠማት ፈተና ለኤርትራ በጣልያን መወረር ምክንያት ነበር።


የአፄ ቴዎድሮስ ፍፃሜን ከወቅቱ የብሪታንያ ወራሪ ጋር አብረው  የእንግሊዝን ሰራዊት እየመሩ እስከ መቅደላ ድረስ ያስመጡ፣አፄ ቴዎድሮስ ራሳቸውን ከሰዉ (መስዋዕትነት ከተቀበሉ) በኃላ እንግሊዞች የአፄ ቴዎድሮስ ንብረቶች እና ልጃቸውን ይዘው እንዲሄዱ እያጫፈሩ  ኢትዮጵያን የከዱ የትግራይ ደጃች በዝብዝ ነበሩ።ደጃች በዝብዝ ከእዚህ በላይ መቅደላ ተሰብስበው የነበሩ የኢትዮጵያ የብራና መፃህፍት እና ቅርሶች በግመሎች እና በዝሆኖች ተጭነው እንዲሄዱ ያስደረጉ ቅርሶቹ ከሀገር ሲወጡ አጅበው እስከ ወደብ ያደረሱ የወቅቱ የትግራዩ ገዢ ደጃች በዝብዝ ነበሩ።

ደጃች በዝብዝ አሁንም ይህንን ሁሉ ያደረጉት ከእንግሊዝ አሮጌ መሳርያ ለማግኘት እና ንግስና ለመጫን ነበር።ደጃች በዝብዝ ከንግስናቸው በኃላ ደርቡሽ ሲመጣ ለኢትዮጵያ በመሞታቸው የኢትዮጵያ ሕዝብ ያለፈ ጥፋትን የመተው ባሕሉ መኖሩ ነው እንጂ በ19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ላይ ከትግራይ የተነሱት ደጃች በዝብዝ ኢትዮጵያን በእዚህ ደረጃ አደጋ እንዳደረሱባት መካድ አይቻልም።በደጃች በዝብዝ እየተመሩ መቅደላ የደረሱት እንግሊዞች የኢትዮጵያን መልክዐ ምድር አስቸጋሪነት እና የህዝቡን ተዋጊነት ተረድቶ በአፄ ቴዎድሮስ የታሰሩበትን ዜጎቹን ብቻ አስፈትቶ ባይመለስ ኖሮ እና በቅኝ ግዛት ኢትዮጵያን ለመያዝ ቢሞክር ኖሮ ደጃች በዝብዝ ኢትዮጵያን አሳልፈው ሰጥተዋት ነበር ማለት ነው።እዚህ ላይ ደጃች በዝብዝ የኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን ይዞታ ለማስጠበቅ ዋጋ የከፈሉት ራስ አሉላ ከዶጋሊ በኃላ ተመልሶ የመጣውን ጣልያንን እንዳይዋጉ በምን ያህል ደረጃ እንቅፋት እንደፈጠሩባቸው እና ኤርትራ በጣልያን እጅ እንድትወድቅ ከአድዋ በፊት ምን ዓይነት ስሕተት እንደሰሩም መዘንጋትም አይገባም።

ጣልያን ኤርትራን እንዲቆጣጠር የቀድሞው ደጃች በዝብዝ የኃላው አፄ ዮሐንስ ራስ አሉላን ከጦር ኃይል አዛዥነት አንስተው ስልጣኑን ለታላቅ ወንድማቸው ልጅ ራስ ኃይለማርያም በመስጠት የጣልያን እግር እሳት የነበሩትን ራስ አሉላን በሐማሴን ብቻ እንዲወሰኑ ማድረጋቸው ጣልያንን አስፈንድቆ፣ራስ አሉላን እና የኢትዮጵያ ወዳጆችን አሳዝነው በውጤቱም ኤርትራን ለጣልያን እንድትጋለጥ አድርገው አልፈዋል። ይህንን ታሪክ ማወቅ በተለይ በእዚህ ጊዜ አስፈላጊ ነው።በተለይ ይህንን እውነታ እየደበቀች ህወሓት አዲስ አበባ ስትገባ የኤርትራን በጣልያን መቆየት በአድዋ ጦርነት ተከትሎ የመጣ ለማስመሰል ሲተረክ ቆይቷል።እውነታው ግን የቀድሞው ደጃች በዝብዝ የኃላው አፄ ዮሐንስ ራስ አሉላን በሀማሴን ወስነው ለታላቅ ወንድማቸው ስልጣኑን መስጠታቸው መሆኑን እና ራስ አሉላንም በሚገባ አለማበረጣታቸው ነው። ራስ አሉላ ግን ይህ ሁሉ ደርሶባቸውም ለኢትዮጵያ የቆሙ ናቸው እና ጣልያን ተመልሶ በአድዋ ዘመቻ ሲመጣ አዲስ አበባ ድረስ መጥተው አፄ ምንሊክ ጋር ህብረት ፈጥረው ኢትዮጵያን ለመከላከል ተዋግተዋል።

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም  የራስ አሉላ መገፋት አዳፍኔ በተሰኘ መፃህፋቸው ላይ ሲገልጡ 

 ''ከዶጋሊው ጦርነት ወዲህ የጦር ጠቅላይ አዛዥነቱን ንጉሰ ነገስቱ ከራስ አሉላ አንስተው ለታላቅ ወንድማቸው ልጅ ለራስ ኃይለ ማርያም ሰጥተው አሉላን በሃማሴን ግዛት ስለወሰኗቸው (ራስ አሉላ) ቅሬታ ነበራቸው ይባላል።" (ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም አዳፍኔ፣ገፅ 13) 

ማዋከብ እና ማቀዝቀዝ  ሁለቱ የሽብርተኛው ህወሓት ወቅታዊ ዘዴዎች

''ኢትዮጵያን ለማፍረስ እስከ ሲዖልም ቢሆን እንወርዳለን'' እያለ የሚያቅራራው ሽብርተኛው ህወሓት አሁን ከገጠር እስከ ከተማ እና ዲያስፖራ ድረስ ሊጠቀምባቸው የሚሞክራቸው ሁለቱ መንገዶች ማዋከብ እና ማቀዝቀዝ ናቸው።

ማዋከብ 

ህወሓት ጀሌዎቹን ወደ አማራ እና አፋር ክልል ሲገቡ የተጠቀሙበት አንዱ መንገድ በከተሞች እና በገጠር የሚኖረው ሕዝብ መሃል  የሐሰት ወሬ በመንዛት ማዋከብ፣አዋክቦም ሕዝብ የሚኖርበትን ቀዬ ለቆ እንዲወጣ፣እንዲቅበዘበዝ እና  በቀላሉ የጠላቶቹ ዒላማ እንዲሆን ማድረግ ነው።የማዋከብ ተልዕኮ የሚወስዱት ደግሞ በተለያየ ደረጃ በማኅበረሰቡ ውስጥ የሚገኙ አካላት ናቸው።እነኝህ አካላት በቁጥር ጥቂት ሲሆኑ አብዛኛው ያልገባው ግን በማያውቀው ጉዳይ እየተዋከበ የሚገባ ነው።የማዋከብ ስራው በዋናነት ሕዝቡ ውስጥ የሚፈፅሙት የሽብርተኛው ቡድን ከተማ ወይንም የገጠር ወረዳ ሳይገባ እንደገባ በማስመሰል ቁጥሩ ከፍተኛ እንደሆነ በማውራት ሕዝብ ከተማ ወይንም ገጠር ይዞታውን ለቆ እንዲወጣ ያደርጉታል።

የማዋከብ ስራው ሌላው የሚከናወነው ሕዝቡን በሚመሩ የከተማ እና የገጠር የመንግስት አስተዳደር ኃላፊዎች ቢሮዎች ውስጥ ነው። በእነኝህ ቢሮዎች ውስጥ የሚሰሩ ለሽብር ቡድኑ በዘር ሐረግ ወይንም በገንዘብ ጥቅም የተያዙት የመንግስት የአስተዳደር ኃላፊዎችን ወሬ የሰሙ በማስመሰል ያዋክቧቸዋል።በውክብያውም ተረጋግተው ሕዝብ እንዳይመሩ እና ኃላፊነታቸውን እንዳይወጡ ብቻ ሳይሆን በሕዝብ እና በሃላፊዎቹ መሃል ክፍተት እንዲፈጠር ኃላፊዎቹ ቀድመው እንደሄዱ አድርገው ስብሰባ ላይ ያሉትን ኃላፊዎች ሁሉ ስም የማጥፋት ስራ በመስራት ለሽብር ቡድኑ በር የሚከፍቱ አሉ። እነኝህ የማዋከብ ስራዎች በሀገር ውስጥ የጦርነቱ ቀጠና ውስጥ ባሉ አካባቢዎች ብቻ የሚታይ አይደለም።በውጭ ሀገርም ስልክ እየደወሉ ወይንም በአካል ሲያገኙ ሁሉ ግለሰቦችን እየመረጡ የሚያዋክቡ እና የሐሰት ወሬ በመንዛት የሰውን ስነ ልቦና ለመስለብ የሚሞክሩ አሉ። እነኝህኞቹ በውጭ ያለውን ማኅበረሰብ በማወክ በቀላሉ የተሸናፊነት ስሜት ለማሳደር እና ይህንን ስሜት ሀገር ቤት ለሚያውቁት እንዲያጋቡላቸው የታለመ ነው።

ስለሆነም በሀገር ቤትም ሆነ በውጭ ያለው ማኅበረሰብ የሽብር ቡድኑ በዋናነት በማዋከብ ግርግር ፈጥሮ ከፍተኛ ጥፋት ለማድረስ እና ሕዝቡን ከመኖርያው አፈናቅሎ ማኅበራዊ ቀውስ መፍጠር እንዲሁም በመግደል እና በመዝረፍ ትርምስ ለመፍጠር የሚጠቀምበት ዋነኛ መንገድ መሆኑን በማወቅ ሕዝብ ቀየውን ሳይለቅ እራሱን ማደራጀት እና መጠበቅ እንዳለበት ሊገነዘብ ይገባል።

ማቀዝቀዝ 

ሌላው የሽብር ቡድኑ ተግባር ማቀዝቀዝ ነው።ይሄውም የሕዝብ በሽብር ቡድኑ ላይ ያለው የቁጣ እና የመደምሰስ ስሜት፣ወደ የጦር ማሰልጠኛ ካምፖች የመግባት ተነሳሽነት፣የእርስ በርስ ማኅበራዊ ትስስሩ መጠንከር ላይ ቀዝቃዛ ስሜት ማፍሰስ ነው። ይህንንም በተለያየ መንገዶች ይፈፅሙታል።ከእነኝህ ውስጥ ወጣቱ ወደ ፈንጠዝያ የሚሄድባቸው መርሃግብሮች በከተሞች እንዲበዙ ማድረግ፣ማኅበራዊ ሚድያዎች በዘፈን እና አልባሌ ጉዳዮች ትኩረት ማስቀየር፣ በሕዝቡ መሃል ወሬ በመንዛት በመንግስት እና በሕዝብ መሃል መተማመን እንዳይፈጠር በማድረግ የህዝብ ስሜት ማቀዝቀዝ እና ሕዝቡን ለማስተባበር የነቁትን እና የተጉትን እንዲሁም የአመራርነት ሚና የወሰዱትን ከወረዳ ጀምሮ ሕዝብ የመምራት እና የማስተባበር ስሜታቸው እንዲቀዘቅዝ የግል ማኅበራዊ ጉዳያቸውን ሁሉ በሚያውቁት ሰው እንዲረበሽ ከማድረግ ሙከራ እስከ የአካል ጥቃት በማድረስ የመምራት እና የማስተባበር ስሜታቸውን አቀዝቅዞ ለማስወጣት መሞከር የሚሉት ተጠቃሾች ናቸው።

ስለሆነም በእዚህ ወቅት ግለሰብ እንደ ግለሰብ፣ሕዝብ እንደ ሕዝብ እና አመራሮች እንደአመራሮች ኃላፊነት እንዳለባቸው መረዳት አለባቸው። ኢትዮጵያ አሁን የገጠማት ጠላት የሽብርተኛው ጁንታው ኃይሎች ብቻ አይደሉም።ከዋሽንግተን እስከ ካርቱም፣ ከካይሮ እስከ የአረብ ሊግ ሀገሮች ሴራ እየተጠነሰሰባት ነው።ይህ ሴራ ደግሞ ዋና ኢላማው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ላይ የሚመስለው ካለ ተታሏል።ጉዳዩ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር አንገቷን ቀና እንዳታደርግ ለማዳከም እና በተዳከመች ኢትዮጵያ ውስጥ እንደልባቸው ገብተው የተፈጥሮ ሃብቷል ለመቀራመት የሚፈልጉ ኃይሎች እሩጫ ነው።ይህ ግን ፈፅሞ እንደማይሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሰሞኑ ያሳየው እጅግ ፈጣን እና አስደማሚ  ሕብረት፣ውሳኔ እና ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛዎች እያደረገ ያለው መትመም ሁሉ ለወገን ደስታ ለቅርብም ሆኑ ለሩቅ የኢትዮጵያ ጠላቶች ታላቅ ድንጋጤ አትርፏል። አሁን የሽብር ኃይሉ ህወሓት ሙሉ በሙሉ እንደሚመታ ምንም የሚያጠራጥር አይደልም።ይህ ማለት ግን እየተበጣጠሰ ሾልኮ እየገባ ሕዝብ አያወናብድም ማለት አይደለም።ሕዝብ ግን ለመወናበድ እራሱን ሳያጋልጥ የማዋከብ እና የማቀዝቀዝ የሽብር ቡድኑን መንገዶች ከመንደሩ ጀምሮ እየመረመረ እና እራሱን አንቅቶ እስከ ቆመ ድረስ ብቻ ነው።ኢትዮጵያ ተሸንፋ አታውቅም። 

 ==========================
ማስታወቂያ /Advertisement 
===============================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 



Friday, August 13, 2021

TPLF is using aid food to inject its war in Amhara and Afar regions in Ethiopia. Some International Aid organizations staff are involved.



 ህወሓት የእርዳት እህል በአማራ እና አፋር ላይ ለከፈተው ጦርነት እየተጠቀመበት ነው።የአንዳንድ የእርዳታ ድርጅት ሰራተኞች እጅም አለበት።

======================

ጉዳያችን ዜና /Gudayachn News

======================

There is reliable information that Gudayachn gets from Tigray, stating that Tigray People's Liberation Front (TPLF), categorized as the terrorist group by Ethiopian Parliament, is using aid food to inject its war in Amhara and Afar regions in Ethiopia. The Ethiopian Government has not yet commented on the news. However, the information from Tigray region aid workers says, even though the aid organizations took responsibility to facilitate the aid operation in Tigray, TPLF is using aid food to inject its war in Ethiopia.

 

It was last June 24 that the first UN Humanitarian Air Service (UNHAS) aircraft arrived at Mekelle with 30 staff from different aid organizations. The leading responsible organization to supply food items is the UN annex organization, World Food Program (WFP). The WFP Regional Director for Eastern Africa, Michael Dunford, last June said that his staff's arrival at Mekelle would scale up the humanitarian response to reach 2.1 million people with food assistance. However, the recent information from Tigray is indicating the TPLF has hijacked the aid food and used it to inject its war against the Amhara and Afar regions in Ethiopia.

 

The information, on TPLF uses aid food to inject its war, underlines the two main ways that TPLF used illegally. The first way is directly taking aid food from the aid organizations stores. As a result thousands of sacks  of food  are loaded directly to the military camps and used for the TPLF militia's daily consumption.However, even around Mekelle there are Internally displaced people sheltered  within schools, churches and Mosques are in need of emergency food aid.

 

The second way that TPLF used the aid food to inject its war is through politicizing the aid program itself. That is the TPLF cadres involved directly on aid food distribution. There are pre-conditions cadres put on all Tigraian residences.The condition is painful for any ordinary individual. Because unless at least one person is serving in TPLF militia service, it is forbidden to get aid food. Therefore, many parents are starving for hiding their children not to be recruited to TPLF militia. It is quite known that any aid organization’s law and regulations did not put any  preconditions to provide aid. However, it is so difficult to say that the TPLF’s illegal action is not known by aid organizations operating in Tigray. Rather some staffs of the aid organizations are involved in this illegal activities. Others are annoyed with it but fear to stop the TPLF cadres.

 

TPLF has a history of using aid food to war. In 1985 the huge event organized by Bob Gedof raised over 136 million USD to support starving people. Dr.Aregawi Berhe, the founder of TPLF, is currently the director of the Great Ethiopian Renaissance Dam (GERD) fundraising committee under Prime Minister Abiy’s administration. Dr. Aregawi told Deutsche Welle (Voice of Germany) English service  how TPLF used aid food for war in the mid 1980s. He said  ‘‘the rebel movement, TPLF, had received the money under false pretences - through its development arm, the so-called 'Aid Association of Tigray' (MARET). But MARET belonged to the party. So after the aid from donors and aid charities was collected, it was made available through the budget of the party's central committee - for logistics and financing of the resistance." Deutsche Welle, March 11,2010.

 

History repeats itself. Today, after 35 years, the same organization categorized as terrorist, according to the Ethiopian Parliament, is using aid food for another vicious war. The International Community needs to act as soon as possible.

=====================

Getachew Bekele Damtew

=====================


ማስታወቂያ /Advertisement 
===============================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Wednesday, August 11, 2021

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በጦርነቱ ምክንያት ለደረሰው ሰብዓዊ ቀውስ ዕርዳት የሚውል ገንዘብ ማሰባሰብ ጀምረዋል።በሳምንቱ መጨረሻ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን ጋብዘው በሰብዓዊ ቀውሱ ዙርያ ማብራርያ ለማግኘት ቀጠሮ ይዘዋል።


በሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ከፍተኛ የሆነ ሰብአዊ ቀውስ እንደተፈጠረ ይታወቃል።በመቶ ሺዎች የሚሆኑ ተፈናቅለዋል።ጦርነት ከመፈናቀል በላይ ይዞ የሚመጣው ተያያዥ ችግሮች አሉ።ሕፃናት ካለወላጅ ይቀራሉ፣የአካል ጉዳተኞች ይኖራሉ።አሁን ግን በዋናነት የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን የዕለት ጉርስ እና ልብስ ያስፈልጋቸዋል። ይህንን ሰብዓዊ ቀውስ ለመቀነስና ለወገኖቻችን አለን! በማለት ተፈናቃዮችን ለማገዝ እንዲቻል በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የሰብዓዊ እርዳታ ማሰባሰብ ሥራ ጀምረዋል።በማስተባበር ሥራ ላይ የተሰማሩት በኖርዌይ የሚገኙ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰቦች፣የሃይማኖት ድርጅቶች እና የሲቪክ ማኅበራት በአንድነት በመሆን ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በሳምንቱ መጨረሻ በደረሰው የሰብዓዊ ቀውስ ዙርያ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሚና ዙርያ ለመወያየት እና ማብራርያ ለማግኘት በኖርዲክ ሀገሮች የኢትዮጵያ አምባሳደር ድሪባ ኩማ፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲያስፖራ ጉዳይ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት እና የብሔራዊ አደጋ እና ዝግጁነት ኮሚሽን ኮሚሽነር ምትኩ ካሳ በዙም ተገኝተው በኖርዌይ ለሚኖሩ ለኢትዮጵያውያን ማብራርያ ይሰጣሉ (ዝርዝሩን ከላይ ፖስተሩ ላይ ይመልከቱ)።

ድጋፍ የሚያደርጉበት ሁለት አማራጭ መንገዶች

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የዕርዳታ ማሰባሰብያ የሚገባበት የባንክ አካውንት ቁጥር 1503 43 13420 (የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ኢመርጅንሲ አካውንት)
ወይም በቪብስ ቁጥር 647675 በመጠቀም ድጋፍዎን ለወገንዎ ማድረግ ይቻላሉ።






Tuesday, August 10, 2021

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የክልል ልዩ ኃይሎችና ሚሊሻዎች ኢትዮጵያን ለማፈራረስ የተነሣ የክህደት ኃይልን ለመደምሰስ ብርቱና የማያዳግም ክንዳቸውን እንዲያሳርፉ መመሪያ ሰጠ፡፡



በቃን ብለን ከተነሣን ከፊታችን የሚቆም ምንም ዓይነት ኃይል እንደሌለ ታሪክ ምስክር ነው። ውጊያው የትግራይን ሕዝብ ምሽግ ካደረገው እኩይ ኃይል ጋር እንጂ ከትግራይ ጋር አይደለም፤ እናም ስንፋለም መጠቀሚያ የሆነውን የትግራይ ሕዝብ ብሎም መላዋ ኢትዮጵያን ከአሸባሪው ቡድን ነጻ ለማውጣትና የሀገራችንን ሰላምና አንድነት ለማስከበር ነው።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የክልል ልዩ ኃይሎችና ሚሊሻዎች ኢትዮጵያን ለማፈራረስ የተነሣ የክህደት ኃይልን ለመደምሰስ ብርቱና የማያዳግም ክንዳቸውን እንዲያሳርፉ መመሪያ ሰጠ፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መልዕክትና ሀገራዊ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-
ኢትዮጵያ ሀገራችን በዘመናት መካከል ያጋጠሟትን ፈተናዎች እና የተጋጠሟትን የክፋት ኃይላት ሁሉ ድል በመንሣት ታፍራና ተከብራ ነጻነቷን አስጠብቃ ኖራለች።
ጀግኖች እናቶቻችንና አባቶቻችን የውጭ ወራሪዎችን ብቻ ሳይሆን የውስጥ ባንዳዎችን በማንበርከክ የዛሬይቱን ኢትዮጵያ በነፍሳቸው ተወራረደው ለእኛ አቆይተውልናል። በታሪክ አጋጣሚ ዛሬም ኢትዮጵያ የአጠባ ጡቷን፣ የአጎረሰ እጇን የሚነክሱ ከሐዲዎች፣ ሊያዳክሟትና ሊበትኗት ከቅርብና ከሩቅ ከተነሡ ኃይላት ጋር በመመሳጠር አቆብቁበው ተነሥተዋል።
ሀገራችን የድህነትና የጭቆና ቡትቶዋን አሽቀንጥራ በመጣል ወደ አይቀሬው የብልጽግና ጎዳናዋ ለመግባት ታጥቃ በተነሣችበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ ትንሣኤችን የማያስደስታቸው ታሪካዊ ጠላቶች፣ ከጉዟችን ሊያስቆሙን እየተረባረቡ ይገኛሉ። ‘እኔ ረግጬ ያልገዛሁዋት ሀገር ትውደም’ የሚል የክህደት ቀረርቶ ሲያሰማ የከረመውም ሕወሐት፣ የጠላቶቻችን መጋለቢያ ፈረስ በመሆን፣ ሰላማችንን ለማደፍረስና ሀገራችንን ለማፍረስ የጥፋት ነጋሪቱን እየደለቀ ይገኛል።
እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ሕዝብ የወያኔ አሸባሪ ቡድን የነበረበትን ችግር እያወቀ እንኳን ብዙ ዕድሎችንና ሃያ ሰባት የመታረሚያ ዓመታትን ሰጥቶታል። አሸባሪ ቡድኑ ግን በሤራ ተጠንስሶ በጥፋት ያደገ ነውና፣ የሚብስበት እንጂ የሚታረም አልሆነም። ይህ የጥፋት ኃይል በሕዝብ ቁጣ ከሥልጣን ከተወገደ በኋላም ቢሆን፣ የተሰጠውን ተደጋጋሚ የመታረም ዕድል ለመጠቀም አልፈለገም። ይልቁንም መቀሌ ላይ መሽጎ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከውጭና ከውስጥ ጠላቶች ጋር በማሤር ጊዜውንና የዘረፈውን ገንዘብ ሲረጭ ከርሟል።
በዚህም የተነሣ ግጭት፣ መፈናቀልና አሰቃቂ ግድያን በመላ ሀገራችን መለኮስና ማስፋፋት የዕለት ተግባሮቹ አድርጎ ቆይቷል። የትግራይ ሕዝብ በዚህ ለጥፋት ተጸንሶ ለአፍራሽነት በተወለደ አሸባሪ ቡድን የተነሣ እንዳይጎዳ በማለት፣ መንግሥታችን ችግሩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያልሞከረው መንገድ አልነበረም። ስድብና መንጓጠጡ ሳያስቆጣው እስከ መጨረሻው ሰዓት መንግሥት ሁሉንም የሰላምና የሽምግልና መንገድ ተግባራዊ አድርጓል።
በተቃራኒው ይኽ የጥፋት ኃይል የፈጸማቸው ልዩ ልዩ ግፎች አልበቃ ብሎት፣ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሰሜን ዕዝ ላይ በፈጸመው በታሪካችን የማይረሳ አሰቃቂ ጥፋት ነገሩን ሁሉ ከቁጥጥር ውጭ አደረገው። ጀግናው የመከላከያ ኃይላችንም ከአማራ እና ከአፋር ሚሊሻና ልዩ ኃይል ጋር በመሆን ይሄንን የጥፋት ኃይል መትቶ አከርካሪውን በመስበር፣ የቡድኑ አባላት በተንቤን ጉድጓዶች እንዲወሸቁ ተገድደዋል። ከአመራሮቹ ብዙዎቹ ተደመሰሱ፤ ከፊሎቹ ተማረኩ፤ ጥቂቶቹም በየዋሻውና በሰላማዊ ሕዝቡ ጉያ ውስጥ ገብተው ተሸጎጡ።
ሕግን ከማስከበሩ ተግባር ጎን ለጎን፣ መንግሥት የትግራይ ክልልን ከዚህ የጥፋት ኃይል ነጻ ለማድረግ፣ ያፈረሱትን መሠረተ ልማቶች ለመገንባት፣ ሕዝቡ ራሱን በራሱ እንዲያስተዳድር ለማስቻል፣ ሰብአዊ ርዳታ ለሕዝቡ ለማድረስ፣ በሂደቱ የተፈጸሙ ጥፋቶችን ለማረምና፣ የጤናና የትምህርት አገልግሎቶች እንዲጀመሩ ለማድረግ ባለፉት ስምንት ወራት በሙሉ ጉልበቱ ተግቷል።በዚህ ሂደት ውስጥ የጁንታው ርዝራዦች በሕዝቡ ውስጥ ተሠግሥገው ሕዝቡን ለጥፋት እየቀሰቀሱ በሚፈጥሩት ቀውስ የትግራይሕዝብ የተረጋጋ ኑሮ ለመኖር አልቻለም።
የርዳታ ሥርጭትን በማስተጓጎል፣ መሠረተ ልማቶች እንደገና ሥራ እንዳይጀመሩ በማደናቀፍ፣የጤናና የትምህርት ተቋማትን በማውደም፣ የአካባቢ አመራሮችን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል፣ ገበሬው ተረጋግቶ እንዳያርስ የእርሻ ሥራውን በማስተጓጎል፣ የመልሶ ግንባታ ተግባራትን ማደናቀፉን የሙሉ ጊዜ ሥራቸው አደረጉት።
ችግሩን ለማባባስ በሚፈልጉ ኃይላት ጆሮውን የተጠመዘዘው ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም የሂደቱን ውስብስብ ጠባይና የአሸባሪውን የጥፋት ባሕርይ ለመገንዘብ ባለመፈለግ፣እውነትን ትቶ የአጥፊውን አካል ጩኸት አስተጋባ። ቡድኑ በረጅም የሥልጣን ዘመኑ የፈጸመውን አሰቃቂ የሰብአዊ መብት ጥሰትና የሚልዮኖችን ህልውና የማጥፋት ሥራ በዝምታ የተመለከቱ ዓለም አቀፍ አካላት፣ ዛሬ አጥፊውን ኃይል ለራሳቸው አጀንዳማስፈጸሚያነት ስለሚፈልጉት፣ እርሱን ለማዳን ሲሉ የመንግሥትን መልካም ጥረት እንዳላዩ ማለፍን መርጠዋል።
እንደሚታወቀው በሰላማዊው ጊዜ እንኳን በትግራይ ክልል አንድ ሦስተኛ የሚሆነው ሕዝብ በሴፍቲኔት ድጋፍ የሚደረግለት ነው።ባለፈው የምርት ወቅትም በአንበጣ መንጋና በኮሮና ምክንያት ሕዝቡ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጉዳት እንዳገኘው ይታወቃል። በዚህ መካከል በትግራይ ከተጀመረው ዘመቻ በኋላ ሌላ የክረምት ወቅት መጣ። ዘመቻው ከቀጠለና ሁለት ክረምቶችን ሳይረጋጋ ካሳለፈ በሕዝቡ ላይ የሚደርሰው ቀውስ ከፍተኛ ይሆናል በሚል እምነት፣ መንግሥት የተናጠል የተኩስ አቁም አድርጎ መከላከያ ከትግራይ አካባቢዎች እንዲወጣ ወሰነ። መንግሥት የተናጠል የተኩስ አቁሙን ያደረገው በዋናነት ለገበሬውና ለሕዝቡ ሲል ነበር።
ያም ሆኖ ሕዝቡ ከአሸባሪው ጁንታ እስከ ዘለዓለሙ ካልተለያየ በቀር፣ ገበሬው ተረጋግቶ ማረስ እንደማይችል ግልጽ ሆኗል። እንኳንስ የትግራይ ገበሬ ወደ እርሻው ሊመለስ ቀርቶ፣ አሸባሪው ጁንታ በአጎራባች አካባቢዎች የሚገኙ ገበሬዎች እንዳያርሱ ማወክ ከጀመረ ውሎ አድሯል።
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አስፈላጊ ርዳታ እንዳይደርስና ሰብአዊ መብቶች እንዳይከበሩ የሀገር መከላከያ ዕንቅፋት ሆኗል እያለ በክስ ጆሯችንን ሲያደነቁረን እንደከረመ ይታወሳል።
አሁን የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን የተኩስ አቁም አድርጎ ከወጣ በኋላ ግን ሕጻናት ለጦርነት ሲሰለፉ፤ ርዳታ የጦርነት መሣሪያ ሲሆን፣ እናቶችና ወጣት ሴቶች ሲደፈሩ፣ የእምነት ተቋማት የጦር መለማመጃዎችና የጦር መሣሪያ መጋዘን ሲደረጉ፣ የርዳታ እህል የጫኑ መኪናዎች ወደ ትግራይ ክልል እንዳይገቡ በጁንታው የጥፋት ተግባር ሲስተጓጎሉ፣
በአፋር ክልል በአንድ የሕክምና ተቋም የተጠለሉ ከ200 የሚበልጡ ሰዎችን ሲያርድ ፣ ከ300,000 በላይ ዜጋ ሲያፈናቅል፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጭምር እውነታው ምን እንደሆነ ለማወቅ ፍላጎት ያለው አካል ሁሉ ለመታዘብ ችሏል።
ከእውነት ይልቅ ሐሰቱን ማድመቅ የሚፈልጉም በዚያው ተግባራቸው ቀጥለዋል። ለመንግሥት ጥረት ተገቢውን ዋጋ መንፈጋቸው ሳያንስ፣ በርዳታ ሰበብ ጁንታውን የሚደግፍ ተግባር ሲፈጽሙም እጅ ከፍንጅ የተያዙ አሉ።
መንግሥት የተናጠል የተኩስ አቁሙን ከማድረጉ በፊት መቀሌ ውስጥ 400ሺ ኩንታል የርዳታ እህል፣ 2.5 ሚልዮን ሊትር የምግብ ዘይት፣ 14 ሚልዮን ሊትር ነዳጅ፣ 536,979 ኩንታል ማዳበሪያና፣ 37,599 ኩንታል ምርጥ ዘር በመንግሥት ገንዘብ ተገዝቶ ለሕዝቡ ደኅንነት ሲባል አስቀምጧል። መታረስ ከሚችለው መሬት 70 በመቶው እንዲታረስ ተደርጓል።
በተጨማሪ 1079 ሜትሪክ ቶን ምግብ፣ 664 ቶን ምግብ ነክ ያልሆነ ቁሳቁስ እና 47,740 ሊትር ነዳጅ በአጋር አካላት በኩል መቀሌ ገብቶ ነበር። ከዚያም በኋላ ቢሆን መንገዶችን በማመቻቸት የርዳታ አቅርቦት እንዳይቋረጥ ተሠርቷል። ለሰብአዊ ርዳታ የሚሆን የአውሮፕላን በረራ ተፈቅዷል።የዚህ ሁሉ ምክንያቱ በአሸባሪው ጁንታ ምክንያት በትግራይ ክልል ያለው ሕዝባችን እንዳይቸገር በማሰብ ነው።
ከሐዲው የጁንታ ቡድን ግን ኢትዮጵያን ለመበተን ከተነሳበት የአሸባሪነት ባህሪው ሊላቀቅ አልቻለም። የአማራንና የአፋር ክልሎችአጎራባች ሕዝቦችን መግደልና መዝረፍ ቀጥሏል። ገበሬዎችን እንዳያርሱ አስተጓጉሏል። ገዳማትን ሳይቀር ዘርፏል። የርዳታ መኪኖችንቸ ወደ ትግራይ ከመግባት አግዷል። መንግሥት መቀሌ ውስጥ ያከማቸውን እህልም ጁንታው አይዘምቱልኝም ላላቸው ሰዎች እንዳይታደል ከልክሏል።
የሀገር መከላከያ ሠራዊታችንና የክልል ልዩ ኃይሎች መንግሥት የወሰነውን የተኩስ አቁም በማክበር ርምጃ ከመውሰድ ቢቆጠቡም፣ አሸባሪው ጁንታ ግን የድፍረት ድፍረት ተሰምቶት የጥፋት ሥራውን ቀጥሎበታል። የሕወሐት ዓላማና ግብ ኢትዮጵያን ማፈራረስ እንደሆነ አመራሮቹ በእብሪት ተናግረዋል። ለዓላማው መሳካትም በብዙ የውጭ ኃይሎች በመታገዝ ለበለጠ ጥፋት ምላጭ መሳብን መርጧል።
ወጣቶችን በእኩይ ፕሮፓጋንዳ በመደለልና ሕጻናትን በሐሽሽ እንዲናውዙ በማድረግ ለጦርነት እየመለመለ፣ በአፈሙዝ የሚነዱ አዛውንቶችን ጭምር እያሰለፈ ይገኛል። የአሸባሪው ጁንታ አካሄድ ሕዝብ አስጨራሽ የሆነ የሽፍትነት አካሄድ መሆኑን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም ሆነ ለትግራይ ሕዝብ በተደጋጋሚ ተናግረናል፤ አስጠንቅቀናል።
ጁንታው እየከፈተ ያለው ጥቃት ሕዝባዊ መልክ እንዲይዝ በማድረግ ስለሆነ መመከት የሚገባውም በዚያ አግባብ ነው፤ የመላው ሕዝባችንን የማያዳግም ምላሽ ሊያገኝ ይገባል።
ባለፉት ጊዜያት ሕዝባችን በአራቱም አቅጣጫ አሸባሪውን የሕወሐት ኃይል ከታሪክ ገጽ ለመደምሰስ ቁርጠኝነቱን አሳይቷል። ሕዝባችን በቁርጠኝነቱ እንደሚገፋበት ምንም ጥርጥር የለውም።
የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን፣ የክልል ልዩ ኃይሎችና ሚሊሻዎች፣ ይህንን ኢትዮጵያን ለማፈራረስ የተነሣ የክህደት ኃይልና የውጭ እጆች ስውር ደባ ለመደምሰስ ብርቱና የማያዳግም ክንዳችሁን እንድታሳርፉ አቅጣጫ ተቀምጦላችኋል።
ሀገር በመከላከል ዘመቻው ለመሳተፍ እድሜያችሁና ዐቅማችሁ የሚፈቅድላችሁ ኢትዮጵያውያን ሁሉ የመከላከያ ሠራዊቱን፣ ልዩ ኃይሉንና ሚሊሻውን በመቀላቀል የሀገር ዘብነታችሁ የምታሳዩበት ትክክለኛው ጊዜ አሁን ነው።
የጸጥታ ኃይሎችን በቀጥታ ለመቀላቀል ያልተቻለው የኅብረተሰብ ክፍል ከመቼም ጊዜ በላይ ወገቡን አሥሮ በልማት ሥራዎች ላይ ተሳትፎውን ማጠናከር አለበት። የመንግሥት ሠራተኛውም በሙሉ ዐቅሙ ያለ ቢሮክራሲ ሥራውን ያከናውን።ሁሉም ዜጋ ነቅቶ አካባቢውን ይጠብቅ።
የጁንታው ተላላኪዎች የጥፋት ተልዕኳቸውን እንዳይፈጽሙ ሕዝባችን በዓይነ ቁራኛ ይከታተል። ከዚህ ባለፈ ለሠራዊቱ የሚሆን ስንቅ በማዘጋጀትና የሞራል ድጋፍ በማድረግ ብርቱ ደጀን ይሁን።ሚዲያዎች፣ የኪነ ጥበብ ባለሞያዎችና ማኅበራዊ አንቂዎች ሕዝቡ ከሀገሩ ጎን እንዲቆም የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታበረክቱ ይጠበቃል።
አሸባሪው ጁንታ ሰላማዊ ሰዎች አስመስሎ በየአካባቢው ያሠማራቸው ሰላዮችና የጥፋት ተላላኪዎችን ለመከታተልና ለማጋለጥ እንዲቻል፣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ለሀገሩ ዐይንና ጆሮ በመሆን ከጸጥታ አካላት ጋር በቅርበት ሊሠራ ይገባል። የሃይማኖት አባቶች በጸሎት፣ የሐገር ሽማግሌዎች በምክር፣ ሁሉም ዜጋ በችሎታው ኢትዮጵያን ብሎ ይቁም።
ቀደምቶቻችን እንዲህ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት ሲገጥማቸው ስንቃቸውን በአህያ፣ አመላቸውን በጉያ አድርገው ዘምተዋል። ሴቶችና ወንዶች፣ ወጣቶችና ጎልማሶች እንደ አንድ ሠራዊት ተምመዋል። መሥዋዕትነት ከፍለውም ሀገራቸውን አድነዋል። ዛሬ ያ ታሪካዊ አደራ በእኛ ጫንቃ ላይ ወድቋል። በሀገር ውስጥና በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ እናት ሀገራችሁ ጥሪ ታቀርብላችኋለች።
በቃን ብለን ከተነሣን ከፊታችን የሚቆም ምንም ዓይነት ኃይል እንደሌለ ታሪክ ምስክር ነው። ውጊያው የትግራይን ሕዝብ ምሽግ ካደረገው እኩይ ኃይል ጋር እንጂ ከትግራይ ጋር አይደለም፤ እናም ስንፋለም መጠቀሚያ የሆነውን የትግራይ ሕዝብ ብሎም መላዋ ኢትዮጵያን ከአሸባሪው ቡድን ነጻ ለማውጣትና የሀገራችንን ሰላምና አንድነት ለማስከበር ነው።ትግላችን ከአሸባሪው ጁንታ ጀርባ ላይ ተፈናጥጠው ሀገራችንን ለማፈራረስና የኢትዮጵያን ህልውና ለማጨለም ከተነሡ የቅርብና የሩቅ ኃይላትና ሀገራት ጋር ጭምር ነው።
ስለዚህ ሁሉም ሀገር ወዳድ ሉአላዊነቱን ለማስጠበቅ በሙሉ ልቡ ይሠለፍ፤ እንደ ጥንቱ ዛሬም የሀገሩን ክብር ላለማስደፈር ቆርጦ ይነሳ። የእውነትም ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኖራለች፤ የእኛም ስም በታሪክ መዝገብ በጀግንነት ተመዝግቦ ይኖራል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት
ነሐሴ 4፣ 2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።