ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, August 16, 2021

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን የአሁኑ ቅዳሜ እኤአ ኦገስት 21/2021 ዓም በኦስሎ ከተማ ግዙፍ ሰልፍ ጠርተዋል።ከወጣት እስከ ሽማግሌ ለሀገሩ ድምፁን እንዲያሰማ ሀገራዊ ጥሪ ቀርቧል።


  • በሽብርተኛው ህወሓት የሕፃናትን ለውትድርና መመልመል፣የንብረት ዘረፋ፣ወጣቶችን በመርዝ የመመረዝ ጭካኔ፣በአፋር የተፈጁት ሕፃናት፣በትግራይ በኤርትራውያን ስደተኞች ወንድሞቻችን ላይ የተፈፀመው ግድያ  እና ሌሎችም በሰልፉ የሚወገዙ ናቸው።ይህንን ሳያወግዝ በቤቱ የሚቀመጥ በኖርዌይ የሚኖር ኢትዮጵያዊ እና ኤርትራዊ ይኖራል ተብሎ አይታሰብም። 

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሰሞኑን በሌላ ሀገር ለሚኖረው የዲያስፖራ ማኅበረሰብ ምሳሌ የሚሆን ተግባር ፈፅመዋል።ከአንድ ሳምንት በፊት በኖርዌይ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ እና ሲቪክ ማኅበራት አስተባባሪነት በሀገር ቤት በሽብርተኛው ህወሓት የጥፋት ዘመቻ ለተፈናቀሉት ወገኖች የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ ተጀምሯል።የገንዘብ ማሰባሰቡ ዘመቻ አሁንም የቀጠለ ሲሆን  ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ እሁድ ነሐሴ 9/2013 ዓም በዙም በተደረገ የዙም ስብሰባ ላይም በኖርዲክ ሀገራት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልዕከተኛ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር የሆኑት ክቡር አምባሳደር ድሪባ ኩማ፣ የዲያስፖራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት እና የብሄራዊ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ አይድሩስ ሀሰን አማካይነት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል።

በእዚሁ መርሃግብር ላይም ቀደም ብሎ የተጀመረው የገንዘብ ማሰባሰብ ሥራ የቀጠለ ሲሆን እስከ ዛሬ ድረስ በኖርዌይ ክሮነር ከ280 ሺህ በላይ ክሮነር ማለትም ከ 1ነጥብ 3 ሚልዮን ብር በላይ ተሰብስቧል።የገንዘብ መሰብሰቡ አሁንም የቀጠለ ሲሆን አሁንም ለተፈናቀሉ ወገኖች እርዳታ ማድረግ የሚፈልጉ ሁሉ የባንክ አካውንት ቁጥር 1503 43 13420 (የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ኢመርጅንሲ አካውንት) ወይም በቪብስ ቁጥር 647675 በመጠቀም ድጋፋቸውን ማድረግ ይቻላሉ።

ይህ በእንዲህ እያለ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን የአሁኑ ቅዳሜ  እኤአ  ኦገስት 21/2021 ዓም በኦስሎ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 7 ሰዓት (13 ሰዓት) ጀምሮ መነሻውን መሃል ኦስሎ ያርንባርንቶርጌ በተለምዶ ''ነብሩ'' ተብሎ በሚጠራው ቦታ መነሻውን አድርገው ሰልፍ ለማድረግ ቀጠሮ ይዘዋል።በሰልፉ ላይ በሽብርተኛው ህወሓት የሕፃናትን ለውትድርና መመልመል፣የንብረት ዘረፋ፣ወጣቶችን በመርዝ የመመረዝ ጭካኔ፣በአፋር የተፈጁት ሕፃናት፣ በትግራይ በኤርትራውያን ስደተኞች ወንድሞቻችን ላይ የተፈፀመው ግድያ እና ሌሎችም በሰልፉ የሚወገዙ ናቸው።ይህንን ሳያወግዝ በቤቱ የሚቀመጥ በኖርዌይ የሚኖር ኢትዮጵያዊ እና ኤርትራዊ ይኖራል ተብሎ አይታሰብም።

ይህ በኖርዌይ በሚኖሩ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ሲቪክማኅበረሰብ ድርጅቶች የተዘጋጀው ሰልፍ ላይ ከኦስሎ ውጭ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ወደ ኦስሎ እንደሚመጡ የሚጠበቀው ሰልፍ በርካታ ሕዝብ እንደሚገኝበት ይጠበቃል።መልዕክቱንም ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ለሁሉም እንዲያደርሱ ተጠይቀዋል።

ሰልፉን በተመለከተ በኖርዌይኛ የተለቀቀው ፖስተር ላይ የወጣው መልዕክት እንደሚከተለው ነው። 

Demonstrasjon mot TPLF og støttemarkeringer for fred på Afrikas Horn 

Dato- 21. august 2021

Tid- Kl.13

 Karl Johan foran Østbanehallen, Oslo ( በተለምዶ ነብሩ ጋር)

 Etiopiske og Eritreiske sivilsamfunnsorganisasjoner



=============================

==========================
ማስታወቂያ /Advertisement 
===============================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...