Saturday, August 21, 2021

በኦስሎ፣ኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ሽብርተኛው ህወሓት በኢትዮጵያ ላይ እየፈፀመው ያለውን ሀገር የመበተን ወንጀል፣ግድያ እና በኤርትራውያን ስደተኞች ላይ የፈፀመውን ጭፍጨፋ በማውገዝ ዛሬ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ያደረጉት ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ሙሉ ቪድዮ።

Dagens enorme antall etiopiere og eritreere demonstrerer i Oslo, Norge.21.august 2021.

በኦስሎ፣ኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሽብርተኛው ህወሓት በኢትዮጵያ ላይ እየፈፀመው ያለውን ሀገር የመበተን ወንጀል፣ግድያ እና በኤርትራውያን ስደተኞች ላይ የፈፀመውን ጭፍጨፋ በማውገዝ ዛሬ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ያደረጉት ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ሙሉ ቪድዮ።

ይህ ዛሬ ነሐሴ 15/2013 ዓም በኦስሎ ኖርዌይ የተደረገው ሰልፍ የተዘጋጀው በኢትዮጵያውያን እና በኤርትራውያን የሲቪክ ድርጅቶች ሲሆን ዝርዝር ፣መረጃ የሚያገኙበት በእዚህ ቪድዮ ውስጥ 
  • ህይወታቸውን በሽብርተኛው ህወሓት ላጡት የጥቂት ሰኮንዶች የህሊና ፀሎት ፣
  • ከኦስሎ ማዕከላዊ ክፍል ወደ ኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተደረገ ሰልፍ 
  • የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ሲቪክ ድርጅቶች ተወካዮች ንግገር፣
  • የኤርትራ ወጣቶች ተወካይ ንግግር፣
  • የኢትዮጵያ ሲቪክ ድርጅቶች ተወካይ ንግግር፣
  • የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ሲቪክ ድርጅቶች ግብረኃይል ለኖርዌይ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የተለያዩ ክፍሎች፣ለኖርዌይ ፓርላማ ውጭ ጉዳይ ንዑስ ክፍል፣ለኖርዌይ ልማት ትብብር ክፍል እና በኖርዌይ ለሚገኙ የተለያዩ የኖርዌይ የፖለቲካ ድርጅቶች የተዘጋጀው ደብዳቤ ይዘት እና 
  • ከሰልፉ ተሳታፊዎች አስተያየት ያገኛሉ።
የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ሲቪክ ድርጅቶች ግብረ ኃይል ከሰኞ ጀምሮ ከላይ ለተጠቀሱት የኖርዌይ መንግስት ሚኒስትር፣ፓርላማ እና ልዩ ልዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በአካል እየቀረበ ደብዳቤውን ለመስጠት እና ለማስረዳት ቀጠሮ ተይዟል።
ሙሉ የሰልፉን ቪድዮ ከስር ይከታተሉ።

I dag var et stort antall etiopiere og eritreere på fredelig demonstrasjon i Oslos gater mot terroristen TPLF som drepte etiopiere i Afar og Amhara og eritreiske flyktninger. Demonstrasjonen ble startet fra Oslo sentrum og endte foran det norske utenriksministerens hovedkontor.

Se hele videoen av demonstrasjonen ved å klikke på lenken.

ይህ የቀጥታ ስርጭት የተቀረፀው ከኦስሎ፣ኖርዌይ ጉዳያችን እና ከለንደን ሉሲ ራድዮ እና ዘውዱ ሚድያ ጋር በጥምረት በመሆን የቀረበ  ነው።





No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...