ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, February 28, 2015

«እኔ ሴት ነኝ ጦርነት አልወድም። ሆኖም 
ይህን ኢትዮጵያን የኢጣሊያ ጥገኛ የሚያድርግ ውል ከመቀበል 
ጦርነትን እመርጣለሁ» እቴጌ ጣይቱ





 ቅድመ የዓድዋ ድል(1885 እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር)

እንደ  አውሮፓውያኑ አቆጣጠር የካቲት 16/1885 ጀርመን በርሊን ከተማ በሚገኘው ውብ በሆነው የ ሀገሪቱ ቻንስለር ቬን ቢስማርክ ባለስልጣን መኖርያ ህንፃ ሳሎን ፌሽታ በ ፌሽታ ሆኗል።ሶስት ወር ሙሉ አሰልቺ ውይይት የተደረገበት ዋና ዋናዎቹ የ አውሮፓ ቅኝ ገዢዎች ተሰብስበው '' አንተ ይሄን ያዝ አንተ በእዚህ ውረድ''ተባብለው የ አፍሪካ ካርታ  በመካከላቸው ተዘርግቶ ከወታደራዊ ዘመቻ በፊት አፍሪካን የተከፋፈሉባት ቀን ነበረች። በእዚህ ስብሰባ ከ80 በ መቶ በላይ የ አፍሪካ መሬት በ ሃሳብ መስመር እያሰመሩ ተከፋፈሉት። የበርልኑ''General act of Berlin conference''በ ታሪክ ባብዛኛው የሚታወቀው’'The division of Africa ''ወይንም ''scramble of Africa''(አፍሪካንየመቀራመትጉባኤ)ተብሎነው።በእዚህጉባኤላይጀርመን፣ኦስትሮሀንጋሪ፣ቤልጅየም፣ደንማርክ፣ፈረንሳይ፣ታላቅዋብሪታንያ፣ጣልያን ፣ኔዘርላንድ፣ፖርቱጋልን ጨምሮ የተገኙ ሲሆን ቅኝ ግዛትን ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት የተሞከረ ና በዚሁ መሰረት በ 1914 በ ፈረንጆቹ አቆጣጠር አብዛኛው የ አፍሪካ ግዛት በ ቅኝ ገዢዎች የወደቀበት ሁኔታ ነበር።

 ''ቀን እባብ ያየ   ምሽት ልጥ ይፈራል''

ጣልያን ከዚህ ስብሰባ ብዙ የተጠቀመች መሰላት።ቢያንስ ሀገራችንን ስትወር በ አፋርና ኢሳ (የአሁኑ ጅቡቲ) ከሰፈረው የ ፈረንሳይ ሰራዊትና ከ ግብፅ አስከ ሱዳን ከተዘረጋው ከ ብሪታንያ ቅኝ ግዛቶች ጋር አያተናኩልም ብላ አሰበች። የመስፋፋት ሕልሟንም ቀጠለች ።ዋናው  የጣሊያን የመስፋፋት ዘመቻ የመሰረት ድንጋይ የተጣለው አሰብ ላይ ነበር። ሩባቲኖ የተባለ የጣሊያን የመርከብ ድርጅት በወቅቱ የአሰብ ግዛት አስተዳደሪ ከነበሩት ሱልጣን ስፋት ያለው መሬት  በ9 ሺ ዶላር ገዛ። በሁዋላ ግን የጣሊያን መንግስት ወደ ተቀረው የኢትዮጵያ ክፍል ለመረማመጃነት እንደሚጠቀምበት በማመኑ፣ ከዚሁ ኩባንያ  መሬቱን በ43 ሺ ዶላር ገዛው(ይህ ግዢ ኢጣልያ በአድዋም ሆነ በ 1928 ዓም ኢትዮጵያን ለመውረር በርከፋች ከመሆኑም በላይ ለአካባቢው ችግር መዘዝ ደውል ተደርጎ ይጠቀሳል)።                                                                                                                        

ጣሊያንም አሰብን መያዝዋ እንደታወቀላት በቀጥታ አፍሪካን ለመቀራመት አላማ ካደረገው የበርሊን ጉባኤ እንድትሳተፍ ተደረገ።ይህ ብቻ አደለም ቅደም ብላ ጣልያን ምፅዋን ይዛ ስለነበር ከ ራስ አሉላ ጦር ጋር ተደጋጋሚ ውግያ ገጠማት።ለምሳሌ አንደፈረንጆቹ አቆጣጠር ጥር 26 /1887 ራስ አሉላ ''የ ኢትዮጵያ ድንበር ቀይ ባህር ነው ያለው'' በሚለው የፀና አምነታቸው ዶጋል ላይ ጣልያንን ሙሉ በሙሉ ድል አርገው መልሰውታል። የበርሊን ጉባኤ ተሳታፊ አገሮችም ጣሊያን ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት እንድትይዝ ፈቃድ የሰጡት ከዚህ ሁሉ ትንኮሳ በሁዋላ ነበር ።ዛሬ ብዙ ወገኖች በ ኢንቨስትመንት ስም ለ ባአዳን በሀገራችን ደቡባዊ ና ምራባዊ ክፍል የሚደረገውን ቅጥ ያጣ የ መሬት ሊዝ'' ኪራይ'' ይባል ''ውል'' በ ስጋት ቢያዩት አይፈረድባቸውም።በ ትክክልም ''በ ቀን እባብ ያየ በ ምሽት ልጥ ይፈራል'' እንዲሉ የ አሰብን ታሪክ ና ቀጥሎ የተከተለውን ያየ ተመሳሳይ ችግር ነገ አይመጣም ለማለት ዋስትና የለውም።                                         

''እግዚአብሄር ድንበር ይሁናችሁ ብሎ የሰጠንን ባህር እየተሻገረ እንደፍልፈል መሬት እየቆፈረ በመስፈር ላይ ነው''

የ ኢትዮጵያ ና ጣልያን ጦርነት ዋነኛ መነሻ የ ጣልያን የ ቅኝ ግዛት ጥማት ሲሆን እንደ ፈጣን ምክንያት  የሚጠቀሰው ግን የ ውጫሌ ውል አንቀፅ 17 ትርጉም ነው።የትርጉም ልዩነቱ ጉዳይ ሊታወቅ የቻለው እቴጌ ጣይቱ የውጫሌው ውል አንቀፅ 17 ላይ ዓለቃ ዓፅመ ጊዮርጊስ የተባሉት የጣልያንኛ ቋንቋ አዋቂ ዓፄ ምኒልክ በሰጧቸው ትዕዛዝ መሠረት የውሉን ሰነድ በመመርመር የውሉ አስራ ሰባተኛው አንቀፅ የያዘውን የትርጉም መዛባት በመግለፅ ጉዳዮ ኢትዮጵያ የምትጐዳበት ስለመለሆኑ ጭምር በማስረዳት በሰጡት ቃል ሲሆን እቴጌ በዚህ ወቅት ነገሮችን በጥንቃቄ የሚከታተሉ ስለነበር ዓፄ ምኒልክ በመጀመሪያ ሳይረዱ ዓለቃ ዓፅመ ጊዮርጊስ እንዲታሰሩ ቢያደርጉም እቴጌ ጣይቱ ግን እኒህ ሰው  ትክክለኛ የኢትዮጵያ ወዳጅ መሆናቸውን ለዓፄ ምኒልክ በማስረዳት ከሦስት ዓመታት እስራት በኋላ ማስፈታቸው ይታወቃል።

በዚህ በኩል ሲታይ እቴጌ ጣይቱ የምኒልክ የቅርብ አማካሪ በመሆን በፖለቲካ ተግባሮች ምን ያህል አስተዋፅኦ እንዳበረከቱ መገንዘብ ይቻላል። እቴጌ እንደተናገሩትም «ዓፅመ ጊዮርጊስ ቢታሰር ቢፈታም ለሀገሩ የሚገባውን ሠርቶ ነው። ኧረ ለመሆኑ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለውዮሴፍ፣ ጣሊያኖች በተንኮል ገብተው በማታለል ይህን የመሰለ ሥራ ሲሠሩ አነጋጋሪ ሆኖ ሳለ እንዴት ሳይስጠነቅቅዎ ቀረ?»በማለት የእቴጌ ጣይቱ የቁጣ መዓት ወደ ዮሴፍ ዞረ።ከዚያም ጨምረው «ከእንግዲህ ወዲህ የኢትዮጵያን ጥቅም የሚነካ፣ ሥር የሚነቅል፣ መሠረት የሚያፈርስ ጉዳዮን ሁሉ እኔ ሳላየው እንዳያልፍ ይፍቀዱልኝ» ብለው ለንጉሡ ባመለከቱት መሠረት ይኸው አንቺ ሳታይው ሳትመረምሪው አያልፍም በማለት ፈቀዱላቸው፣ይህ እንደሚያመለክተው እቴጌ ጣይቱ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የነበራቸውን ተገቢ ቦታ የሚያመለክት ነው። ውሉንም ለማስተካከል ዓፄ ምኒልክ ያደረጉት የዲፕሎማቲክ ጥረትው ጤታማ ሊሆን ባለመቻሉ ሚኒስትሮች የጦር አለቆችና መኳንንት የሚገኙበት ጉባዔ እንዲጠራ አደረጉ።

በአንቀጽ 17 ላይ የሰፈረው ስምምነት ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ በጣሊያን ቅኝ ግዛት ውስጥ የሚያስገባ ነበር። ይህ አንቀጽ በአማርኛው ቅጅ ላይ የሚከተለውን አሰፍሯል “ኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት በምታደርግበት ጊዜ የጣሊያንን መንግስት እገዛ ከፈለገች ጣሊያን የኢትዮጵያን ፈቃድ ለመፈጸም ፈቃደኛ ነች።” ይሁን እንጅ በጣሊያንኛ ቁዋንቁዋ በተፈረመው ቅጅ ላይ ያለው ስሜት ከዚህ በተለየ ቀርቦአል “ኢትዮጵያ ማንኛውንም አይነት የውጭ ግንኙነት በጣሊያን መንግስት በኩል ታደርጋለች'' የሚል ትርጉም ይዞ ነበር።ይህም ቆይቶ ዓፄምኒልክ ከ አንግሊዝ መንግስት ጋር ሊያደርጉ ላሰቡት ግንኙነት በ ጣልያን በኩል ይምጡ መባላቸው ሲሰማ የ ውሉ ትርጉም ምንነት ለየለት።ይህ ብቻ አደለም የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር የነበረው ክርስፒ ግን ጉራና ንቀት በተሞላበት ሁኔታ ኢትዮጵያ ከዛሬ ጀምሮ በጣሊያን ስር ነች እያለ ከማወጅ በስተቀር ውሉን ለማስተካካል የሚያስችል እርምጃ አልወሰደም ነበር። ይባስ ብሎም ኤርትራን በመውረር የመጀመሪያዋ የጣሊያን ቅኝ ግዛት አገር ተመሰረተች ብሎ 1890ዓም አዋጅ አስነገረ። እንግሊዝም ሳትውል ሳታድር ጣሊያን ላቀረበችው ሀሳብ ድገፉዋን ሰጠች

የጣሊያንና የሌሎች መንግስታት ተንኮል ያበሳጫቸው አጼ ሚኒሊክ፣ ወዲያውኑ ከጀርመን፣ ከሩስያና ከቱርክ መንግስታት ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማጠንከር፣ ጣሊያንን ለመፋለም ወስነው ዝግጅት ጀመሩ። እንዲህም ሲሉ ለህዝባቸው ተናገሩ “ እግዚአብሄር በቸርነቱ ጠላቶቼን ድባቅ መትቶልኝ፣ ግዛቴንም አስፍቶልኝ፤ እስከዛሬ ድረስ አቆየኝ። በእግዚአብሄር ጸጋም ነግሻለሁ። ጠላት አገራችንን ለመውረር ሀይማኖታችንንም ለማስለወጥ ደጃፋችን ድረስ መጥቷል። እግዚአብሄር ድንበር ይሁናችሁ ብሎ የሰጠንን ባህር እየተሻገረ እንደፍልፈል መሬት እየቆፈረ በመስፈር ላይ ነው። ጉልበት ያለህ በ ጉልበትህ ጉልበት የለለህ በ ፀሎትህ አግዘኝ። ከዚህ ሌላ ወስልተህ የማገኝህ ግን ማርያምን አልምርህም''

  «እኔ ሴት ነኝ ጦርነት አልወድም። ሆኖም ይህን ኢትዮጵያን የኢጣሊያ ጥገኛ የሚያድርግ ውል ከመቀበል ጦርነትን እመርጣለሁ» እቴጌ ጣይቱ

ዳግማዊ ምኒሊክ እና ንግስት ጣይቱ እውነተኛ ፎቶ (ፎቶ አዲስ ጆርናል) 

ጣሊያን ከባዱን የአድዋ ጦርነት ከማካሄዷ በፊት በርካታ መለስተኛ የሆኑ ጦርነቶችን ከኢትዮጵያውያን ጋር ስታደርግ ቆይታለች። እነዚህ ጦርነቶች ግን ሁሌም በጀግኖቹ የኢትዮጵያ መሪዎች አሸናፊነት ይጠናቀቁ ነበር። በተለይ የራስ አሉላ ብልህ የጦር አመራር ና ብቃት ያለው ሰራዊታቸው ለ ጣልያኖች የ ውስጥ አግር  ፍም ሆኖባቸው ቆየ።

የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በአፍሪካ ምድር ያልታየ አዲስ ታሪክ በኢትዮጵያ ምድር ተሰራ። እለቱ በኦሮቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ የቅዱስ ጊዮርጊስ ወርሀዊ በአል የሚከበርበት ቀን ነበር ። ሰማይ ከ መሬት ሳይለቅ ከ ለሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ንጉሡ ና የ ጦር ሹማምቶቻቸው ከ አዲስ አበባ ድረስ አብሮ በመጣው የ አራዳው ቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦተ-ሕግ ዙርያ ከበው ቆመው የ ኪዳን ፀሎት በማረግ ላይ   ነብሩ።  በ መካከል የሚኒሊክ የመረጃ ክፍል የሆነ አንድ ወጣት እየተንደረደረ መጥቶ ለንጉስ ሚኒልክ ''ጌታየ “ባራቴሪ” ተኩስ ከፍታብናለችና ቶሎ ብለው አንድ ነገር ያድርጉ'' በማለት ሹክ ያላቸው ፣ በመቀጠል ከ መቅደሱ ውስጥ ለ አፄ ሚኒሊክ ና ሹማምንቱ '' የቀረውን ፀሎት እኛ እንፈፅመዋለን ሂዱ አይዟችሁ የ ኢትዮጵያ አምላክ ይከተላችሁ'' የሚል ቃል ተቀብለው ፣ መስቀል ተሳልመው ዘመናዊ መሳሪያ እስካፍንጫው የታጠቀውን የጠቅላይ ሚኒስትር ክርስፒን ጦር ለመግጠም ቤተክርስቲያኑዋን ለቀው ወጡ።

ማታ ነው ድሌ


ጣሊያን ጂኔራል ባራቴሪ ለተባለው የጦር መሪዋ የቀይ ንስር የተባለውን ከፍተኛ ወታደራዊ ማእረግ ሸልማ ላከች። ጄኔራሉ ከ20 ሺ በላይ የሚሆነውን ጦሩን ይዞ፣ የኢትዮጵያን ጦር ለመግጠም ጦሩን በሶስት ማእዘን አንቀሳቀሰ። በጄኔራል ዳቦር ሜዳ የሚመራው ጦር የበለሀ ተራሮችን በቀኝ በኩል አጥሮ እንዲይዝ፣ የጄኔራል አርሞንዲ ጦር ደግሞ በመሀል ሰንጥቆ እንዲገባ ታዘዘ። ጄኔራል አልቤርቶኒ በበኩሉ የኪዳነምህረት ታራራን እንዲቆጣጠር ትእዛዝ ቢሰጠውም፣ እንዳ ኪዳነምህርትና ኪዳነምህረት የሚባሉት ሁለቱ ቦታዎች ስለተምታቱበት፣ ከኪዳንምህረት ተራራ ሳይደርስ በሌላ ቦታ ላይ ሰፈረ በጄኔራል ኢሊና የሚመራው ጦር ደግሞ ከጀኔራል ባራቴሪ ጦር ጋር በመሆን በተጠባባቂነት እንደቀመጥ ተደለደለ:: 

ከ አንድመቶ ሺ የሚበልጡት የ ኢትዮጵያ ሰራዊት   በየጦር አበጋዞቻቸው ና ''ፋኖ ተሰማራ '' ብሎ ልጁን ቤተሰቡን ተሰናብቶ ተነቃነቀ።ጦርነቱን የተቀላቀለው ከ ሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የተውጣጣው ጦር ውግያውን በየመጣበት ጠመደው።ድሉ ግን የማታ ማታ የ ኢትዮጵያ ሆነ። ጣልያኖች መሸሽ ጀመሩ። የንግሥት ጣይቱ በተመረጡ ወታደሮች ሥልታዊውን የ ጣልያኖች የ ውሃ ቦታ አስያዙ።ጣልያን ጀነራሏን በቁሙ አስማርካ በወቅቱ በ ምስራቅ አፍሪካ ከነበራት ከ ግማሽ በላይ የሚሆን ሰራዊቷን አጥታ ጦርነቱ ተጠናቀቀ።                                                                                                
ዶክተር ታደሰ ስለ ድሉ ሲገልፁ-
''በኢትዮጵያዊያን የጦር ሃይል ጥቅም ላይ የዋሉት ስትራቴጂዎች እና ታክቲኮች በንጉሰነገስቱ ዲፕሎማሲያዊ እና ወታደራዊ ክህሎት ላይ ብቻ የተመሰረቱ ሳይሆኑ በበርካታ ሺዎች በሚቆጠሩ አመታት በኢትዮጵያ የጎለበቱ ልዩ አስተሳሰቦች ላይም ጭምር የተመሰረቱ ነበሩ፡፡ እነዚህ አስተሳሰቦች በሌሎች የአለም ክፍሎች ትምህርት ከተወሰደባቸው ወታደራዊ ትምህርቶች ለየት ባሉ ሁኔታዎች የተፈጠሩ ነበሩ፡፡ ከዚህም ባሻገር እነዚህ የጦር ታክቲኮች እና ስትራቴጂዎች በሃገሪቱ ታሪክ እና መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ ተንፀባርቀው ነበር፡፡ በዚህ አካሄድ የኢትዮጵያ ሃይሎች ጣሊያኖች ይጠብቁት ከነበረው አኳኃን በተለየ ደረጃ ላይ ይገኙ ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት የአድዋ ጦርነት በቀጣይ ምእተ አመት በተለያዩ ወታደራዊ /ቤቶች የጥናት ርእስ ሆኗል፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን የአድዋ ጦርነት ከተካሄደበት ጊዜ ጀምሮ ለረጅም ጊዜ የትኩረት ምንጭ ሆኖ ቆይቷል፡፡'' ብለዋል።
የ ድሉ ዜና በመላ ዓለም ተናኘ ። ጥቁር አፍርካውያን አውሮፓውያንን አሸነፉ የሚለው ዜና ጣልያንን ብቻ ሳይሆን በተዋበው ህንፃ ውስጥ አፍሪካን ለመቀራመት ተሰብስበው የነበሩ   
መንግስታትን ሁሉ 'ክው !' ያደረገ መራር ዜና ነበር።በወቅቱ የ ኒውዮርክ ታይምስ  ጋዜጣ በ  ሽፋኑ ላይ በ ያወጣው ዜና ርአስ''ITALY's TERRIBLE DEFEAT'' የጣልያን አስፈሪው ሽንፈት''ማለቱ አስፈሪነቱ ለ በርሊኑ ጉባኤተኞች ሁሉ ማለቱ ሳይሆን ይቀራል?

አድዋ ጦርነት ድል ተከትለው የመጡ ክስተቶች


የ አድዋ ድል በ ኢትዮጵያ ድል አድራጊነት መጠናቀቅ የሚከተሉትን ሁኔታዎች በ ሀገርውስጥም ሆነ በ ዓለም አቀፍ የ ዲፕሎማሲ መድረክ ላይ ተከስቷል;-

    በ ጥቅምት ወር ላይ ጣልያን ከ ኢትዮጵያ ጋር ''አዲስ አበባ ውል '' የተባለ አዲስ ውል ለመፈረም ተገዳለች፣

    በ አሜሪካ፣አፍሪካ ና በመላው ዓለም ያሉ ጥቁሮች ለመብታቸው ተነሳስተዋል፣

    እ.ኤ.አ. በ1903 ዊሊያም ሄንሪ የተባሉት አፍሪካ አሜሪካዊ የንግድ ስራ ዋነኛ አንቀሳቃሽ የሄይቲ ዜግነት ካላቸው ገጣሚ እና ተጓዥ ከሆኑት ቤኒቶ ሲልቪያን ጋር በመሆን ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡አላማቸውም ንጉሰ ነገስት ሚኒሊክን ለመጎብኘት እና ከእርሳቸውም ጋር ለመተዋወቅ ነበር፣

    የኢትዮጵያን ነፃነት በአሜሪካ ለሚኖሩ ጥቁሮች እንደ ነፃነት ነፀብራቅ እና መሰረት በማየት ጋርቬይ በቂ ገንዘብ ለማሰባሰብ የሚያስችል የባህር ላይ የንግድ ስራ ለመመስረት አሰቡ፡፡ ከዚህም ሌላ ወደ አፍሪካ የሚመለሱ በርካታ አባላትን ለመመዝገብ አቀዱ፡፡ በጥቂት አመታት ውስጥ የጋርቬይ ማህበር ከሞላ ጎደል 10 ሚሊዮን ዶላር በማሰባሰብ እስከ ግማሽ ሚሊዮን የሚደርሱ አባላትን ለማቀፍ ችሏል፣

    ታዋቂ የሆነው የሲቪል መብቶች መሪ ማልኮም ኤክስ አባቱን ቄስ ኢያርል ሊትልን በመጥቀስ የሕይወት ታሪኩን መፃፍ ጀመረ፡፡ ለዚህም ምክንያት የሆነው አባቱ ከላይ የተጠቀሰው 'የዩናይትድ ኒግሮ ኢምፕሩቭመንት አሶሲየሽን' ከፍተኛ ደጋፊ ነበሩ፡፡ ማልኮም በዚህ ረገድ የሚከተለውን አስተያየት ሰጥቷል፡- ‘አባቴ ወደ ጋርቬይ ማህበር ስብሰባዎች የሚወስደው እኔን ብቻ ነበር፡፡ እነዚህ ስብሰባዎች በተለያዩ ሰዎች ቤቶችበሚስጥር ይካሄዱ ነበር፡፡ አባቴም እኔን አንዳንድ ጊዜ ወደ እነዚህ ስብሰባዎች ይወስደኝ ነበር፡፡ “አፍሪካ ለአፍሪካውያን የሚለውን አባባል አስታውሳለሁ፣ ኢትዮጵያዊያን ተነሱ’ ማልኮን ከጋርቤይ የፓን አፍሪካ መልእክት ጋር የነበረው ቁርኝት እና ይህም መልእክት በንባብ፣ በፅሑፍ እና በታሪክ ራሱን ሲያስተምር እንደ መነሻ ምክንያት የሚጠቀምበት ነበር፡፡ ‘በከፍተኛ ደረጃ ያስደሰቱኝን የመጀመሪያዎቹን መፅሐፍት በሚገባ ማስታወስ እችላለሁ፡፡ ጄኤ ፕሮዘርስ በፃፋቸው ሶስት መፅሐፍት ጥቁር የነበረው ኤዞፕ ስለ ታላቋ የ ክርስቲያን ግዛት ማለትም ስለ ኢትዮጵያ ገልጸል፡፡ ይህችም ሃገር የጥቁርን ቀጣይ እድገት ያስመሰከረች የምድርን ረጅም እድሜ ያስቆጠረች ሃገር ናት'' ብሎላታል።

    የናይጄሪያው ናሜንዲ አዚኪዊ፣ የጋናው ኩዋሜ ንክሩማ እና የኬንያው ጆሞ ኬኒያታ በመጀመሪዎቹ የአፍሪካ ነፃነት እንቅስቃሴዎች እንዲሁም በምእራብ ኢንዲንስ ያሉ መሪዎች ማለትም ጆርጅ ፓድሞሬ እና ማርከስ ጋርቬ (ጀማይካ) በድሉ ከፍተኛ የተነሳሽነት ስሜት እንዲያድርባቸው ሆኗል፡፡


ዳግማዊ ምኒልክ በ ኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የፈጠሩት በጎ ሁኔታዎች

ዳግማዊ ምኒልክ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የፈጠሩት በጎ ሁኔታዎች ሁሉ ሲወሱ የሚኖሩ ናቸው።ሀገራችን ለመጀመርያ ጊዜ የ ሚንስትሮች ካቢኔ፣ስልክ፣ባቡር፣ሆቴል፣መኪና፣ ያየችው በ ዳግማዊ ምኒልክ ዘመን ነበር። ከሁሉ የሚገርሙኝ ግን ሁለት ነገሮች ናቸው።የመጀመርያው ዛሬ ተማሩ በሚባሉ ሰዎች ዘንድ ስለ አካባቢ ጥበቃ ለማስረዳት ብዙ ጊዜ የመፍጀቱን ያህል የ ዛሬ መቶ ዓመት በፊት የነበሩት ዳግማዊ ምኒልክ ለ ወደፊቱ ትውልድ የ አካባቢ ጥበቅ ልማት አስበው በሃርዛፍ ከ አውስትራልያ ድረስ ማስመጣታቸው ና አጀንዳ ብለው መነጋገራቸው ሲሆን ሁለተኛው በ 1988 አዲስ ዓለም ማርያም ሙዜም ስጎበኝ የ ሙዝየሙ አስጎብኚ የነገሩን ነገር ነው። ጉዳዩ አንዲህ ነው-

ዳግማዊ ምኒልክ አንድ ቀን ጠባቂዎቼ በደንብ ይጠብቁኝ አንደሆነ ና አንዳልሆነ ላረጋግጥ ብለው ሌሊት ጋቢ  ለብሰው ይወጣሉ። ግቢውን ሲዞሩ  ጠባቅያቸው ከሩቅ ያየውን ሰው ስላላወቀ ''ቁም!ቁም!'' ብሎ መሣርያውን ያቀባብላል። ምኒልክ ቀልድ ያሉት ነገር ስህተት መሆኑን አውቀው ባለማወቅ አንዳይተኮስባቸው '' አይዞህ ምኒልክ ነኝ....ጌታህ ነኝ አይዞህ....''ይሉታል። ጠባቂውም ከሩቅ ሆኖ ''በምን አውቃለሁ ምኒልክ ተኝቷል'' ይላቸዋል። ወደአርሱ ቀርበው ''ምኒልክ ነኝ አይዞህ ስራህን በደንብ መስራትህን ላይ ነው'' ይሉታል። ተባቅያቸው ይደነግጣል። ''አሁን ተኩሼ ቢሆን ጌታዬን ገድዬ ነበር'' ብሎ ላብ አጠመቀው። ቀጥሎ ግን ተናደደ አሳስተውኝ ቢሆንስ ብሎ ዱላውን አውጥቶ ሁለት ጊዜ መታቸው። ምኒልክ አየፎከሩ አንዴት አንተ ሲሉ ግቢውን ለቆ ወጣ። ጧት ግብር ተበልቶ። ዳግማዊ ምኒልክ ያን ጠባቂ አስጠሩት። በሰራው ሥራ ግዞት አንደማይቀርለት ገምቶ ከፊታቸው ቆመ። ሌሊት የሆነውን ሁሉ አስረድተው ለ ሹማምንቱ ፍረዱ አሉ። ሁሉም ተነስቶ '' ግማሹ አርባ ይገረፍ....ሌላው ይገደል....'' ብሎ ፈረደ። ዳግማዊ ምኒልክ ግን '' ምን አረገ ካለበት የሄድኩበት ሳለሁ ስራውን በሚገባ በሰራ ሰው ላይ ለምን ትፈርዳላችሁ?'' ብለው መሬት ሸልመው ሾሙት።'' አሉን የ ሙዝየሙ አስተዋዋቂ። ቀጥለውም ''የናንተ ዲሞክራሲ  ዱላ አደለም ተናገራችሁኝ ብሎ ፍዳ የሚያሳይ ነው። ያኔ ይህም ተደርግዋል።ይህ ሲፈፀም የነበሩ የ 96 ዓመት የአድሜ  ባለፀጋመኖራቸውን ነገሩን ።የዚህ አይነት ዲሞክራሲ ነበረ!

ጉዳያችን

Saturday, February 21, 2015

ሰበር - እምነትን ከእምነት ጋር ማጋጨቱ ቀጥሏል፣በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ውስጥ 'የእሬቻ' በዓል እንደሚከበር ኢቢሲ መግለጡ ቁጣ ቀስቅሷል።



የአቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ንግሥገዳሙ የሚገኝበት ተራራ ላይ ያለው ሀይቅ ዙርያ ታቦተ ሕጉ ሲዞር 

ባለፈው መስከረም 15/2007 ዓም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (በቀድሞ ስሙ ኢቲቪ) በአማርኛ እና በኦሮምኛ እንደተለቀቀው ዜና ከሆነ ''በመጪው መጋቢት ወር መጨረሻ ላይ የእሬቻ በዓል በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ውስጥ ይከበራል ''ይላል።ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከተከበሩት እና ከታፈሩት ገዳማት ውስጥ አንዱ ነው።ገዳሙ ፃድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ከግብፅ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ለኢትዮጵያ እና ለመላው የሰው ዘር የፀለዩበት ቅዱስ ስፍራ ነው።

ይህንን ከ800 ዓመታት በላይ ፀንቶ የኖረ ገዳም ''እሬቻ'' እንዲከበርበት የተደረገበት ዋና ምክንያት እምነትን ከእምነት ለማጋጨት በስርዓቱ የተሸረበ ተንኮል ነው የሚሉ ብዙዎች ናቸው።ከእዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መሰረተ እምነትን የጣሱ ተግባራት ሲፈፀሙ እና ሙስና የሚፈፅሙ የስርዓቱ አጎብዳጆች (በቤተ ክህነቱ ዙርያ 'የጨለማው ቡድን አባላት' በመባል የሚታወቁቱ)  የቤተ ክርስቲያኒቱን ንብረት  እና ገንዘብ መተዳደርያቸው ሲያደርጉት አንዳች እርምጃ ሳይወሰድባቸው አመታት መቆጠራቸው ይታወሳል።

በቅርቡም በርዕሰ አድባራት እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሙዚየም የወርቅ መስቀልን ጨምሮ ሌሎች በቅርስነት የተመዘገቡ ንብረቶች መጥፋታቸው ይታወሳል።ከእዚሁ ጋር ተያይዞ የደብሩ አስተዳዳሪ ቀደም ብለው ሰራተኞችን ሰብስበው ''በሙዚየሙ የሚገኙ ቅርሶች ተሸጠው ለአባይ ቦንድ መግዣ ይዋሉ'' የሚል ሃሳብ አቅርበው በደብሩ አገልጋዮች እና ሰራተኞች ''ታሪክ አጥፍተን ታሪክ አንሰራም'' የሚል ምላሽ እንደሰጧቸው የገለፀው የሪፖርተር ጋዜጣ ባለፈው ሮብ የካቲት11/2007 ዓም በዘገባው  ''የቤተ ክርስቲያኗ ካህናት፣ ሠራተኞችና የአካባቢው ነዋሪዎች የደብሩን አስተዳዳሪና ሌሎች ኃላፊዎች ተባብረው ወርቆቹን ማጥፋታቸውን፣ በቤተ ክርስቲያኗ ሠራተኞች ላይ በደልና ብልሹ አሠራር እንዲደርስ ማድረጋቸውን በመግለጽ ተቃውሟቸውን በፊርማ በተደገፈ አቤቱታ ለሚመለከታቸው ሁሉ መላካቸውን'' ይገልጣል። 

ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ላይ የእሬቻ በዓል እንዲከበርበት መገለፁን የዘገበው የማኅበረ ቅዱሳንድረ-ገፅ  በበኩሉ ጉዳዩን አስመልክተው አቡነ ማትያስ ለኦሮምያ ፕሬዝዳንት አቶ ሙክታር ከድር ደብዳቤ መፃፋቸውን ይገልጣል።

ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ታሪክ እና አመሰራረት 

የዝቋላ አቡ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በ1168 ዓ.ም.ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዚህ ዓለም በሕይወተ ሥጋ በነበሩበት ጊዜ ከግብጽ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ቅዱሳት በሆኑ እግሮቻቸው በመርገጥና በመባረክ በተራራው አናት ላይ በሚገኘው ውብና ማራኪ በሆነው ባሕር ውስጥ ለ1ዐዐ ዓመታት በመጸለይ ከዘለዓለማዊው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማይታበል ሕያው ቃል ኪዳን የተቀበሉበት በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ በኋላ ጽላታቸው የተቀረጸበት ቤተክርስቲያናቸው የታነጸበት በክቡር ስማቸው ገዳም የተመሠረተበት አምላከ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ብርሃነ ረድኤቱን በየጊዜው የሚገልጥበት በሀገራችን ኢትዮጵያ አሉ ከሚባሉት ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳማት አንዱ ነው፡፡

የደብረ ዝቋላ ገዳም ከተመሠረተ ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርነው የ835 ዓመት እድሜን ያስቆጠረ ታላቅ ገዳም ነው፡፡ የመጀመሪያው መሥራች በውስጡ ልዩ ልዩ ጸዋትወ መከራዎችን በመቀበል ገድላቸውን የፈጸሙበት ታላቁ ጻድቅ አቡ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሲሆኑ እርሣቸው በ14ዐዐ ዓመት ውስጥ በነበረውና በኢትዮጵያው ንጉሥ በአጼ ዳዊት ልጅ በሕዝበናኝ (እንድርያስ) ዘመነ መንግሥት ካረፉ በኋላ ንጉሡ ሕዝበናኝ (ሁለተኛ ስሙ እንድርያስ) በዚህ አምሳለ ደብረ ታቦር በተሰኘ፣ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን የማይታበል ሕያው ቃል ኪዳን ከልዑል እግዚአብሔር በተቀበሉበት ተራራ ላይ በስማቸው ጽላት በማስቀረፅ ቤተክርስቲያን በማነጽ ገዳም እንዲመሠረት ካደረጉ በኋላ በሺህ የሚቆጠሩ መናንያን መነኮሳት በውስጡ ለዓለም ሰላም ለሕዝበ ክርስቲያን ይቅርታና ምሕረትን ከእግዚአብሔር እየለመኑ ትሩፋን እየሠሩ መንፈሳዊ አገልግሎትን እያገለገሉ እስከ ግራኝ ወረራ ድረስ ገዳሙን በማስፋፋት ቆይተዋል፡፡

ኋላም ግራኝ መሐመድ የኢትዮጵያን ገዳማትና አድባራት ባቃጠለና ባጠፋ ጊዜ ይህም ገዳም በግራኝ ወረራ መነኮሳቱ ተጨፍጭፈው አልቀዋል፣ ቤተክርስቲያኑም ተቃጥሏል፣ ገዳሙም ፈርሷል፡፡ ይሁን እንጂ ገዳሙ ዘወትር መንፈስ ቅዱስ የማይለየው እውነተኛ የቅዱሳን ቦታ በመሆኑ ሥራውን ባህታውያን ሳይለዩት እስከ ንጉሥ ማህለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ድረስ ለብዙ ዓመታት ያህል ጠፍ (ባዶ መሬት) ሆኖ ቆይቷል፡፡
የደብረ ዝቋላ ገዳምን መልክአ ምድር አቀማመጥ ከአየር ላይ ሲታይ  
በኋላም የንጉሥ ወሰን ሰገድ ልጅ የሆኑት ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ የታላቁ ጻድቅ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ መካነ ገድል የሆነውን የዝቋላን ገዳም እንደገና አሳድሰው እንደ ቀድሞው የመንፈሳውያንና የመናንያን መነኮሳት መሰብሰቢያ አድርገው አቋቁመውታል፡፡ ከዚያም በኋላ አጼ ምኒልክ ለገዳሙ መናንያን መነኮሳት መተዳደሪያ ሰፊ ርስት ጉልት ከመስጠታቸውም በላይ የመንፈሳዊ መተዳደሪያ ሕግና ሥርዓቱንም በወቅቱ ከነበሩት መንፈሳውያን አባቶች ጋር ሆነው በመወሰን ያወጡት ሕግ የሚሻሻለው በቅዱስ ሲኖዶስ ተሻሽሎ እነሆ እስከ አሁን ያለው የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያንም አጼ ምኒልክ ያሠሩት ነው፡፡ ይህ ብቻም ሳይሆን አጼ ምኒልክ ለደብረ ዝቋላ ገዳም ብዙ መጻሕፍትና ንዋየ ቅድሳትን የሰጡ ሲሆን አስከ አሁንም በቅርስነት ተጠብቀው ይገኛሉ፡፡

የዝቋላ አቡ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በታላቅ ተራራ ላይ የተመሠረተ ውብና ማራኪ የሆነ ምን ጊዜም ጸጋ እግዚአብሔር የማይለየውና ንጹህ ጤናማ አየር ያለው በአጠቃላይ ተፈጥሮ ያደለው እውነተኛ መካነ ቅዱሳን ነው፡፡ ወደዚህ ታላቅ ገዳም ለመድረስ ከአዲስ አበባ እስከ ዝቋላ ተራራ 82 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ሲሆን የተራራው ርዝመት በመኪና መንገድ 9 ኪ.ሜ. ነው፡፡ በእግር ተራራው ብቻ ከ2 ሰዓት ተኩል እስከ 3 ሰዓት ያስኬዳል፡፡ ይሁን እንጂ የዝቋላ ተራራ ዙሪያውን በደን የተሸፈነ በመሆኑ ተራራውን ለመውጣት ጉዞ ሲጀምሩ ውብና ማራኪ የሆነው የደን መዓዛ፣ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ፣ የቅዱሳን ረድኤት ልብን እየመሰጠ ያለምንም ድካም ከተራራው አናት ላይ ያደርሳል፡፡

ከዚያም ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቀዱስ ለዓለም ሰላም ለኢተዮጵያ ምሕረትን በመለመን )/1ዐዐ ዓመት ሙሉ በውስጡ የጸለዩበትን ባህር ዙሪያውን ጥቅጥቅ ባለ የተፈጥሮ ደንና የባሕር ዛፍ አጣና በሚያካክል ቀጤማ ተከቦ ሲታይ ሰማያዊ ገነትን የሚያስታውስ ምድራዊ ገነት እውነተኛ የጽድቅ ቦታ ለመንፈሳውያን መኖሪያ የተፈጠረ መሆኑንና ታላቅነቱን ያስመሰክራል፡፡ በዚህም የሐይቅ ጸበል ብዙ ሕሙማን ከልዩ ልዩ ደዌያቸው ይፈወሱበታል፡፡
የዚህ ሐይቅ አቀማመጥ ከተራራው አናት ላይ እንደ ገበታ ወይም ሣህን በጎድጓዳ ቦታ ላይ ያለ ሆኖ ዙሪያው በደንና በቀጤማ የተከበበ ነው፡፡ እጅግ በጣም የሚያስደንቀው ይህ ባህር ባልታሰበ ጊዜ እንደ አምፖል ያለ ብርሃን በግምት ርዝመቱ ከ2 እስከ 3 ሜትር የሚደርስ በባህሩ መካከል ሲበራ ማየት በዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ለሚኖሩ መነኮሳት የተለመደ ነው፡፡ 

የብርሃኑም ዓይነት ነጭ ሲሆን ይህ ከላይ የጠቀስነው ዓይነት ብርሃን በመካከሉ የሚቆም ሲሆን በቀጤማው ዙሪያ ደግሞ እንደ አምፖል ዓይነት ብርሃን ባህሩን ከቦት ለብዙ ሰዓት ይቆያል አንዳንድ ቀንም ሙሉ ሌሊቱን ሲያበራ የሚያድርበት ጊዜ አለ፤ ይህን ስንል ለአንባብያን ማመን ያስቸግር ይሆናል፡፡ ነገር ግን የሚጠራጠር ሁሉ በዝቋላ ገዳም ለጥቂት ቀን ከተቀመጠና እግዚአብሔር ከፈቀደለት አይቶ ማመን ይችላል፡፡


ከዚህ በላይ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስን አስደናቂ ተአምርና የገዳሙን ይዘት በመጠኑ አቅርበናል፡፡ በዝቋላ አቡ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገደም በየዋሻውና በየጫካው ወድቀው ለዓለም ሰላምን ለሕዝበ ክርስቲያን ይቅርታና ምሕረትን ከልዑል እግዚአብሔር እየለመኑ የሚኖሩ ባህታውያን ያሉበት በብዙ የሚቆጠሩ አረጋውያን አባቶችና እናቶች እንዲሁም አቅመ ደካሞች የሚጦሩበት አምላከ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ብርሃነ ረድኤቱን ሁል ጊዜ የሚገልጥበት ታላቅ ገዳም ስለሆነ ምዕመናን በዚህ ቅዱስ ቦታ በመገኘት የቅዱሳንን በረከት በመቀበል የታላቁ ጻድቅ የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የቃል ኪዳናቸው ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ እያመላከትን ጽሁፋችንን በዚሁ እናጠቃልላለን፡፡


ጉዳያችን GUDAYACHN

የካቲት 14/2007 ዓም (ፈብሯሪ 21/2015)

የገዳሙ ታሪክ ምንጭ - የአዲስ አበባ ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ድረ-ገፅ 

Wednesday, February 18, 2015

የየካቲት 12 አርበኞቻችን እና ሰማዕታቱ


ገነተ ልዑል ቤተ መንግስት 

በእዚህ ፅሁፍ ስር የሚከተሉትን ርዕሶች ያገኛሉ 
  • አብርሃም ደቦጭ፣ሞገስ አስገዶም እና ስምዖን አደፍርስ እነማን ናቸው?
  • 'እልል! በሉ' ልዕልት ተወለደች፣
  • የካቲት 12፣1929 ዓም ደም እንደ ጎርፍ፣
  • ሞግስ አስገዶም፣አብርሃም ደቦጭ እና ስምዖን አደፍርስ ፍቅር እስከ መቃብር፣
ጉዳያችን / Gudayachn
የካቲት 12/2008 ዓም (ፈብሯሪ 18/2015 ዓም)

ታሪክ ምን ያስተምረናል?


የካቲት 12 /1929 ዓም አዲስ አበባ ሰላሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎችዋ አንዲት ጀንበር ሰማአትነት የተቀበሉባት ቀን ነበረች። ይህ ታሪክ አስተማሪነቱ ዘርፈ ብዙ ነው።የሀገራችን ፖለቲካ የየካቲት 12 አይነት ታሪኮችን ትውልዱ በማስተማር በተለይ ከታሪክ አንፃር ብዙ ቁም ነገር ሊሰራበት ይገባል ለመሆኑ ዛሬ ስማንያ አራት ዓመት አዲስ አበባ ምን ሆነች? ብዙዎቻች ታሪኩን የምናውቀው የሚመስለን ግን አውቀነውም ቁምነገሩን እና አንደምታውን ችላ ያልነው ጥቂቶች አይደለንም። 
የዛሬ ሰማንያ አራት ዓመት አብርሃም፣ሞገስ እ ስምዖን በግራዝያን ላይ ባቀናበሩት ቦንብ አደጋ (ጣልያን አሸባሪ ብሏቸው የነበረ መሆኑን ሳንረሳ) የጣሉበት እና አዲስ አበባ ደም ጎርፍ የታጠበችበት መከራ ቀን፣የካቲት 12/1929

አብርሃም ደቦጭ፣ሞገስ አስገዶም እና ስምዖን አደፍርስ እነማን ናቸው?


 አውሮፓውያኑ አቆጣጠር 1936 (1929 ዓም )  ዓለም ፖለቲካ ብዙ አዳዲስ ክስተቶች የታዩበት ነበር።

- የጣልያኑ ፋሺሽት መሪ ሞሶሎኒ  ሮማ 'ኤምፓየር' አዲስ መሬት   አዲስ አበባን መያዙን  ያሳወቀበት፣ ቀደም    ብለው ተግባሩን  በስውር ሲደግፉ የነበሩ ሀገሮች ማንነታቸው የለየበት፣
 - ብሪታንያ ዜና አገልግሎት' ቢቢሲ' የመጀመርያ ቴሌቪዥን ፕሮግራሙን  የጀመረበት፣ 
 - አሜሪካው ፕሬዝዳንት  ሩዝቬልት ሁለተኛ ጊዜ የተመረጡበት
 - ጃፓን ባህር ኃይል ቻይናን ሻንጋይ ክፍለ ሀገር የወረረበት  እ ባጠቃላይ ጊዜው ዓለም ወደ ሁለተኛው ታላቁ ጦርነት ለመግባት አራት አመታት ብቻ ቀርቷት የምትታትርበት ጊዜ ነበር።

አብርሃም ደቦጭ እ ሞገስ አስገዶም ሐማሴን አና አካለጉዛይ (አሁኗ ኤርትራ)ተነስተው በፋሺሽት እጅ የወደቀችው የሀገራቸውን ኢትዮጵያ አርበኞች ሊቀላቀሉ መጡ።
ከለበሱት ልብስ ውስጥ ኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ አጥፈው ይዘዋል።ህልማቸው፣ሳጋቸውን እየተናነቀ የሚይዛቸው ሀገራቸው መከራ እረፍት ነሳቸው።


በወቅቱ ከነበሩት ትምህርት ቤቶች ጣልያንኛ ተምረው ስለነበር ቅኝ ግዛት ችግርን ሀገራቸው ኢትዮጵያ ላይ የሚያመጣውን አንደምታ ጊዜው ፖለቲካ ጋር አዛምደው መረዳታቸው ሌላው የእግር ውስጥ እሳት ነበርእዚህ ጊዜ ነበር እንደነሱ በሀገሩ ጉዳይ ውስጡ ይንተከተክ የነበረውን ስምዖን አደፍርስን  ያገኙት።

ስምዖን አደፍርስ ''በመናደድ ብቻ መቆም የለብንም  ወሳኝ የሆነ ሥራ መስራት አለብን ፋሽሽትን ደሞ ትጥቅ ትግል በቀር ምንም ሌላ መንገድ የሚዋጋው  የለም'' ይላቸው ነበር። ስምዖን አደፍርስ ገና የከተማ መልክ አየያዘች በነበረችው አዲስ አበባ ውስጥ ጅቡቲ ይኖር ከነበረው ወንድሙ በተላከለት ታክሲ  ሥራ ላይ ነበር። ስራው ላይ አያሌ ፋሺሽት ጣልያኖች ግፍ በደል እ  ሃገሩ የወደፊት እጣ ሲያስበው ንዴት ፣ውርደት አልገዛም ባይነት አንድ ላይ ተደባልቀው ውስጡን አናውጠውታል። ይህን ስሜት ይዞ ነበር ሌሎቹ ሀገራቸው  ኢትዮጵያ ፍቅር ያንገበገባቸውን ሁለቱን ወጣቶች አብርሃም ደቦጭ  ሞገስ አስገዶምን ያገኛቸው።

እልል! በሉ ልዕልት ተወለደች

አብርሃም፣ሞገስና ስምዖን አዚህ ሃሳብ ላይ ሳሉ ነበር ሞሶሎን ኢትዮጵያ ሹመኛ ግራዝያን'' ልእልት ተወለደች ተሰብሰቡቸርነቴን ተመልከቱ ላብላችሁ፣ላጠጣችሁ''ብሎ አሁኑ ስድስት ኪሎ ዩንቨርስቲ የያኔው አፄ ኃይለስላሴ ገነተ ልዑል ቤተመንግስት አዲስ አበባን ሕዝብ የጠራው። ይህ አጋጣሚ እነ አብርሃም ታላቅ አጋጣሚ ሆነ። ድግሱ ላይ ንግግር እንደሚያደርግ  የሚጠበቀው ግራዝያን ላይ የእጅ ቦንብ ወርውረው መግደል የሚል አቅድ አዘጋጁ።እዚህ ሃሳብ ደግሞ እጅ ቦንብ አጠቃቀም መማር ያስፈልጋል።ስምዖን ደጃዝማች አፈወርቅ ወታደሮች በድብቅ አንዲያስተምሯቸው ሁኔታውን አመቻቸ። በየቀኑ ወደ ስፍራው አዲስ አበባ ውጭ ከሁለት ሰዓት በላይ በታክሲው  እየወሰደ አስተማራቸው  ቀኑ ደረሰ።በአቅዳቸው መሰረት ሞገስ እ አብርሃም ግራዝያንን ቦንብ ገደሉ በሁዋላ አሁኑ ቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስትያን አጥር በኩል ይዘሉና ቆሞ  የሚጠብቃቸው ስምዖን ታክሲ ውስጥ ገብተው አዲስ አበባ መውጣት ቀጥለውም ሰሜን ሸዋ ላይ በውጊያ ላይ ካለው ራስ አበበ አረጋይ አርበኛ  ጦር ጋር መቀላቀል እ መዋጋት የሚል  ታላቁ አቅድ ብለው መከወን ተግባራቸው ሊሆን' ቃል ለምድር ለሰማይ 'መሀላቸው  ነበር።

የካቲት 12፣1929 ዓም ደም እንደ ጎርፍ

የካቲት ከገባ ገና አስራ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል።የ አዲስ አበባ አየር ደመናማ ነበር። የተለመደው በልግ ዝናብ ሊመጣ ዳር ዳር የሚል ይመስላል። አዲስ አበባ መንገዶች ጣልያን ወታደሮች ይታመሳል። ሰሜን ሸዋ ላይ የሚዋጋው አንዳንዴም አዲስ አበባ መግብያ በር ደረሰ እየተባለ የሚወራለት  አርበኛው ራስ አበበ አረጋይ ሰራዊት ጠጅ ቤቱ በ ቅኔ አዘል ግጥም ይሞገሳል። ቅኔው የገባቸው ባንዳዎችም አዝማሪውን እየጠቆሙ ፍዳውን ያሳዩታል። አዝማሪው ገና አለ ገና በሚል መልክ ውግያው ይቀጥላል የሚል ቃና ያለው ግጥም  ያንቆረቁራል-

 '' የወንድ ልጅ እናት ታጠቂ በገመድ፣
  ልጅሽን አሞራ እንጂ አይቀብረውም ዘመድ''

እየተባለ ሴት ወንዱ ውጊያ የተዘጋጀበት አርበኛ ሆኖ መሞት የተናፈቀበት  ጊዜ ነበር። ስድስት ኪሎ የያኔው ቤተመንግስት አሁኑ ዩንቨርስቲ አዲስ አበባ በግድም በውድም በተሰበሰቡ ባብዛኛው ሴቶች ሕፃናት ተሞላ። እብሪት የተሞላበት ግራዝያኒ ንግግር ተጀመረ። በንቀት ያየው ሕዝብ ላይ ስለ ''ታላቂቱ ጣልያን'' መደስኮር ጀመረ። ግን ብዙ አልቆየም አብርሃም እ ሞገስ ሕዝቡን ጥሰው ከፊቱ ደረሱ ሰባት ቦንቦችን አከታትለው ወረወሩበት፣ግራዝያን ቆሰለ፣ አየር ኃይሉ ኃላፊ ተገደለ። አብርሃም እ ሞገስ ቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስትያን በኩል ባለው ቤተመንግስቱ ጋራ  አጥር ዘለው ወጡ እ ታክሲ ይዞ ወደሚጠብቃቸው ስምዖን ገሰገሱ፣ ስምዖን በታክሲ ወጣቶቹን ይዞ ነጎደ፣ እንጦጦ ተራራ ላይ ውጥተው አዲስ አበባን ቁልቁል አይዋት፣ ግራዝያን በቆሰለበት ሆኖ አዋጅ አውጆ ለካ አዲስ አበባ ወንድ ሴት ሕፃን አዋቂ ሳይባል ጥይት፣በ አካፋ እ ዶማ በተገኘው ሁሉ መፈጀት ተጀምሯል።

ሶስቱ ወጣቶች ተቃቅፈው ተላቀሱ።ጊዜው እስኪመሽ ጠበቁ እ ስምዖን ወደ ደብረሊባኖስ ይዟቸው ነጎደ።ለ ሰሜን ሸዋ ራስ አበበ አረጋይ ቅርብ የሆነችው -ደብረሊባኖስ አመቺ መስመር እንደሆነች ሁሉም አምነውበታል። ስምዖን ተልኮውን ፈፅሞ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ። አብርሃም ሞገስ ራስ አበበ አረጋይ ጦር ጋር ተቀላቀሉ።

የካቲት አስራ ሁለት ቀን አዲስ አበባ ብቻ ሰላሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎችዋ ሰማአትነት ተቀብለዋል። ብዙ የሚቆጠሩ ቤቶች ተቃጥለዋል። ግድያው በመንገድ ላይ የተገኘ ማንኛውም ሰው ላይ ሲሆን ለመግደል  የሚፈለገው መስፈርት ኢትዮጵያው መሆኑ ብቻ ነበር።



አዲስ አበባ ስድስት ኪሎ የሚገኘው የካቲት 12 የሰማዕታት ሃውልት

ሞግስ አስገዶም፣አብርሃም ደቦጭ እና ስምዖን አደፍርስ ፍቅር እስከ መቃብር 

ስምዖን አብርሃም እ ሞገስን ደብረሊባኖስ ወደ ሰሜን ሸዋ መንገድ ከሚያውቃቸው አርበኞች ጋር አገናኝቶ ተመለሰ።ብዙም አልቆየ ፋሽስቱ ጥቁር ለባሾች ተይዞ ብዙ መከራ እና ስቃይ ተገደለ። የታሪክ ምሁራን እንዳስቀመጡት ስምዖን እጁም ሆነ እግሩ ጥፍር በጉጠት እየተነቀለ ጣቶቹን እየሰባበሩ አሰቃይተው ገደሉት።

አብርሃም ደቦጭ እ ሞገስ አስገዶም 

አብርሃም ደቦጭ ሞገስ አስገዶም ራስ አበበ አረጋይ አርበኞች ጦር ጋር ከተቀላቀሉ በኃላ ራስ አበበ አረጋይ ልዩ እንክብካቤ እንዲያገኙ አደረጉ።ቆይተው ግን የነበራቸውን ትምርት ደረጃ በመረዳት ሀገር ውጭ ወጥተው ሀገራቸው ቢሰሩ ይጠቅማሉ ብለው በማሰብ ስንቅ እ ገንዘብ ጋር ወደ ሱዳን እንዲሄዱ መከሯቸው። ሆኖም  ግን ጉዞአቸው ላይ ሱዳን ሊገቡ ትንሽ ሲቀራቸው  ፎቶዋቸው ገጠር ባሉ ፋሺሽት ወታደሮች ሁሉ ተናኝቶ ነበርና ፋሺሽቶች  ተይዘው በስቅላት ሰማዕት ሆኑ።በኃላ ግን አፄ ኃይለሰላሴ ሱዳን በኩል ጣልያንን እንግሊዝ ሰራዊት ጋር ሆነው ድል ሲያደርጉ አብርሃም እ  የሞገስ አስከሬን ተቆፍሮ ወጥቶ አሁን አዲስ አበባ በሚገኘው ቅድስት ስላሴ አርበኞች ሃውልት ስር እንዲያርፍ አድርገዋል።

ዘመኑን ዋጁት
'
ዛሬ ላይ ሆነን ዛሬ ሰማንያ አራት  ዓመታት የነበሩትን ወጣቶች ስናስብ እ ሐማሴን እ አካለጉዛይ እኛ ኢትዮጵያውያን የተለዩ አስመስለው ሊያወሩን ለሚፈልጉ መረብ ማዶም ሆነ ከመረብ ወዲህ ላሉት ባለ ጊዜዎች ትንሽ ጊዜ ወስደው እንዲያስቡ ማረግ ተገቢ ነው።መረብ ማዶውን መረብ ወዲሁ የተለያየው ታሪክ፣በዘር፣ ሃይማኖት አይደለም።ከእዚህ ይልቅ '' ውሸት ሲደጋገም እውነት የመሆን እድል ይኖረዋል'' የሚለውን ብሂል ሁል ጊዜ የሚሰራ የሚመስላቸው ወገኖች በሚነዙት ፕሮፓጋንዳ ብቻ ነው።

ፅሁፌን ከመጠቅለሌ በፊት አንዲት ሃሳቤን የምታሳርግልኝ ታዋቂው አሜሪካዊውን  ሀገራችን ታሪክ አዋቂ እ ስለ ኢትዮጵያ በመፃፍ የሚታወቁት አማርኛም አቀላጥፈው የሚናገሩት ፕሮፌሰር ዶናልድ ለቪን ከስምንት ዓመታት በፊት ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ በተናገሩት ንግግር ልደምድም።እንዲህ ነበር ያሉት :-''ኢትዮጵያን በአሁኑ ሰዓት የሚያስተዳድሯት የሀገሪቱን  ታሪክ በሚገባ የማያውቁ ናቸው።ስለዚህ የምመክረው ታሪክን በደንብ ይረዱ .......እናንት ኢትዮጵያውያን የችግሮቻችሁ ሁሉ መፍቻ ታሪካችሁ ላይ አለ በደንብ ተረዱት'' ፕሮፌሰር ዶናልድ ለቪን ።



ጉዳያችን Gudayachn

www.gudayachn.com  



ማሳሰብያ - ይህ ፅሁፍ ከአራት ዓመታት በፊት ለመጀመርያ ጊዜ በእዚሁ ገፅ  ላይ ወጥቶ ነበር።በሌሎች ድረ-ገፆችም ከእዚህ ገፅ ተወስዶ ተለጥፎ ነበር።


የፅሁፉ መርጃዎች

፩/ ዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ  http://www.ethioobserver.net/forgoten_heroes.ሕትም

፪/ኢሳት ራድዮ የካቲት 11/2004 ዓም ዝግጅት

፫/ ግሎባል አልያንስ ኢትዮጵያ  http://www.globalallianceforethiopia.org























ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።