ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, February 18, 2015

የየካቲት 12 አርበኞቻችን እና ሰማዕታቱ


ገነተ ልዑል ቤተ መንግስት 

በእዚህ ፅሁፍ ስር የሚከተሉትን ርዕሶች ያገኛሉ 
  • አብርሃም ደቦጭ፣ሞገስ አስገዶም እና ስምዖን አደፍርስ እነማን ናቸው?
  • 'እልል! በሉ' ልዕልት ተወለደች፣
  • የካቲት 12፣1929 ዓም ደም እንደ ጎርፍ፣
  • ሞግስ አስገዶም፣አብርሃም ደቦጭ እና ስምዖን አደፍርስ ፍቅር እስከ መቃብር፣
ጉዳያችን / Gudayachn
የካቲት 12/2008 ዓም (ፈብሯሪ 18/2015 ዓም)

ታሪክ ምን ያስተምረናል?


የካቲት 12 /1929 ዓም አዲስ አበባ ሰላሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎችዋ አንዲት ጀንበር ሰማአትነት የተቀበሉባት ቀን ነበረች። ይህ ታሪክ አስተማሪነቱ ዘርፈ ብዙ ነው።የሀገራችን ፖለቲካ የየካቲት 12 አይነት ታሪኮችን ትውልዱ በማስተማር በተለይ ከታሪክ አንፃር ብዙ ቁም ነገር ሊሰራበት ይገባል ለመሆኑ ዛሬ ስማንያ አራት ዓመት አዲስ አበባ ምን ሆነች? ብዙዎቻች ታሪኩን የምናውቀው የሚመስለን ግን አውቀነውም ቁምነገሩን እና አንደምታውን ችላ ያልነው ጥቂቶች አይደለንም። 
የዛሬ ሰማንያ አራት ዓመት አብርሃም፣ሞገስ እ ስምዖን በግራዝያን ላይ ባቀናበሩት ቦንብ አደጋ (ጣልያን አሸባሪ ብሏቸው የነበረ መሆኑን ሳንረሳ) የጣሉበት እና አዲስ አበባ ደም ጎርፍ የታጠበችበት መከራ ቀን፣የካቲት 12/1929

አብርሃም ደቦጭ፣ሞገስ አስገዶም እና ስምዖን አደፍርስ እነማን ናቸው?


 አውሮፓውያኑ አቆጣጠር 1936 (1929 ዓም )  ዓለም ፖለቲካ ብዙ አዳዲስ ክስተቶች የታዩበት ነበር።

- የጣልያኑ ፋሺሽት መሪ ሞሶሎኒ  ሮማ 'ኤምፓየር' አዲስ መሬት   አዲስ አበባን መያዙን  ያሳወቀበት፣ ቀደም    ብለው ተግባሩን  በስውር ሲደግፉ የነበሩ ሀገሮች ማንነታቸው የለየበት፣
 - ብሪታንያ ዜና አገልግሎት' ቢቢሲ' የመጀመርያ ቴሌቪዥን ፕሮግራሙን  የጀመረበት፣ 
 - አሜሪካው ፕሬዝዳንት  ሩዝቬልት ሁለተኛ ጊዜ የተመረጡበት
 - ጃፓን ባህር ኃይል ቻይናን ሻንጋይ ክፍለ ሀገር የወረረበት  እ ባጠቃላይ ጊዜው ዓለም ወደ ሁለተኛው ታላቁ ጦርነት ለመግባት አራት አመታት ብቻ ቀርቷት የምትታትርበት ጊዜ ነበር።

አብርሃም ደቦጭ እ ሞገስ አስገዶም ሐማሴን አና አካለጉዛይ (አሁኗ ኤርትራ)ተነስተው በፋሺሽት እጅ የወደቀችው የሀገራቸውን ኢትዮጵያ አርበኞች ሊቀላቀሉ መጡ።
ከለበሱት ልብስ ውስጥ ኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ አጥፈው ይዘዋል።ህልማቸው፣ሳጋቸውን እየተናነቀ የሚይዛቸው ሀገራቸው መከራ እረፍት ነሳቸው።


በወቅቱ ከነበሩት ትምህርት ቤቶች ጣልያንኛ ተምረው ስለነበር ቅኝ ግዛት ችግርን ሀገራቸው ኢትዮጵያ ላይ የሚያመጣውን አንደምታ ጊዜው ፖለቲካ ጋር አዛምደው መረዳታቸው ሌላው የእግር ውስጥ እሳት ነበርእዚህ ጊዜ ነበር እንደነሱ በሀገሩ ጉዳይ ውስጡ ይንተከተክ የነበረውን ስምዖን አደፍርስን  ያገኙት።

ስምዖን አደፍርስ ''በመናደድ ብቻ መቆም የለብንም  ወሳኝ የሆነ ሥራ መስራት አለብን ፋሽሽትን ደሞ ትጥቅ ትግል በቀር ምንም ሌላ መንገድ የሚዋጋው  የለም'' ይላቸው ነበር። ስምዖን አደፍርስ ገና የከተማ መልክ አየያዘች በነበረችው አዲስ አበባ ውስጥ ጅቡቲ ይኖር ከነበረው ወንድሙ በተላከለት ታክሲ  ሥራ ላይ ነበር። ስራው ላይ አያሌ ፋሺሽት ጣልያኖች ግፍ በደል እ  ሃገሩ የወደፊት እጣ ሲያስበው ንዴት ፣ውርደት አልገዛም ባይነት አንድ ላይ ተደባልቀው ውስጡን አናውጠውታል። ይህን ስሜት ይዞ ነበር ሌሎቹ ሀገራቸው  ኢትዮጵያ ፍቅር ያንገበገባቸውን ሁለቱን ወጣቶች አብርሃም ደቦጭ  ሞገስ አስገዶምን ያገኛቸው።

እልል! በሉ ልዕልት ተወለደች

አብርሃም፣ሞገስና ስምዖን አዚህ ሃሳብ ላይ ሳሉ ነበር ሞሶሎን ኢትዮጵያ ሹመኛ ግራዝያን'' ልእልት ተወለደች ተሰብሰቡቸርነቴን ተመልከቱ ላብላችሁ፣ላጠጣችሁ''ብሎ አሁኑ ስድስት ኪሎ ዩንቨርስቲ የያኔው አፄ ኃይለስላሴ ገነተ ልዑል ቤተመንግስት አዲስ አበባን ሕዝብ የጠራው። ይህ አጋጣሚ እነ አብርሃም ታላቅ አጋጣሚ ሆነ። ድግሱ ላይ ንግግር እንደሚያደርግ  የሚጠበቀው ግራዝያን ላይ የእጅ ቦንብ ወርውረው መግደል የሚል አቅድ አዘጋጁ።እዚህ ሃሳብ ደግሞ እጅ ቦንብ አጠቃቀም መማር ያስፈልጋል።ስምዖን ደጃዝማች አፈወርቅ ወታደሮች በድብቅ አንዲያስተምሯቸው ሁኔታውን አመቻቸ። በየቀኑ ወደ ስፍራው አዲስ አበባ ውጭ ከሁለት ሰዓት በላይ በታክሲው  እየወሰደ አስተማራቸው  ቀኑ ደረሰ።በአቅዳቸው መሰረት ሞገስ እ አብርሃም ግራዝያንን ቦንብ ገደሉ በሁዋላ አሁኑ ቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስትያን አጥር በኩል ይዘሉና ቆሞ  የሚጠብቃቸው ስምዖን ታክሲ ውስጥ ገብተው አዲስ አበባ መውጣት ቀጥለውም ሰሜን ሸዋ ላይ በውጊያ ላይ ካለው ራስ አበበ አረጋይ አርበኛ  ጦር ጋር መቀላቀል እ መዋጋት የሚል  ታላቁ አቅድ ብለው መከወን ተግባራቸው ሊሆን' ቃል ለምድር ለሰማይ 'መሀላቸው  ነበር።

የካቲት 12፣1929 ዓም ደም እንደ ጎርፍ

የካቲት ከገባ ገና አስራ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል።የ አዲስ አበባ አየር ደመናማ ነበር። የተለመደው በልግ ዝናብ ሊመጣ ዳር ዳር የሚል ይመስላል። አዲስ አበባ መንገዶች ጣልያን ወታደሮች ይታመሳል። ሰሜን ሸዋ ላይ የሚዋጋው አንዳንዴም አዲስ አበባ መግብያ በር ደረሰ እየተባለ የሚወራለት  አርበኛው ራስ አበበ አረጋይ ሰራዊት ጠጅ ቤቱ በ ቅኔ አዘል ግጥም ይሞገሳል። ቅኔው የገባቸው ባንዳዎችም አዝማሪውን እየጠቆሙ ፍዳውን ያሳዩታል። አዝማሪው ገና አለ ገና በሚል መልክ ውግያው ይቀጥላል የሚል ቃና ያለው ግጥም  ያንቆረቁራል-

 '' የወንድ ልጅ እናት ታጠቂ በገመድ፣
  ልጅሽን አሞራ እንጂ አይቀብረውም ዘመድ''

እየተባለ ሴት ወንዱ ውጊያ የተዘጋጀበት አርበኛ ሆኖ መሞት የተናፈቀበት  ጊዜ ነበር። ስድስት ኪሎ የያኔው ቤተመንግስት አሁኑ ዩንቨርስቲ አዲስ አበባ በግድም በውድም በተሰበሰቡ ባብዛኛው ሴቶች ሕፃናት ተሞላ። እብሪት የተሞላበት ግራዝያኒ ንግግር ተጀመረ። በንቀት ያየው ሕዝብ ላይ ስለ ''ታላቂቱ ጣልያን'' መደስኮር ጀመረ። ግን ብዙ አልቆየም አብርሃም እ ሞገስ ሕዝቡን ጥሰው ከፊቱ ደረሱ ሰባት ቦንቦችን አከታትለው ወረወሩበት፣ግራዝያን ቆሰለ፣ አየር ኃይሉ ኃላፊ ተገደለ። አብርሃም እ ሞገስ ቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስትያን በኩል ባለው ቤተመንግስቱ ጋራ  አጥር ዘለው ወጡ እ ታክሲ ይዞ ወደሚጠብቃቸው ስምዖን ገሰገሱ፣ ስምዖን በታክሲ ወጣቶቹን ይዞ ነጎደ፣ እንጦጦ ተራራ ላይ ውጥተው አዲስ አበባን ቁልቁል አይዋት፣ ግራዝያን በቆሰለበት ሆኖ አዋጅ አውጆ ለካ አዲስ አበባ ወንድ ሴት ሕፃን አዋቂ ሳይባል ጥይት፣በ አካፋ እ ዶማ በተገኘው ሁሉ መፈጀት ተጀምሯል።

ሶስቱ ወጣቶች ተቃቅፈው ተላቀሱ።ጊዜው እስኪመሽ ጠበቁ እ ስምዖን ወደ ደብረሊባኖስ ይዟቸው ነጎደ።ለ ሰሜን ሸዋ ራስ አበበ አረጋይ ቅርብ የሆነችው -ደብረሊባኖስ አመቺ መስመር እንደሆነች ሁሉም አምነውበታል። ስምዖን ተልኮውን ፈፅሞ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ። አብርሃም ሞገስ ራስ አበበ አረጋይ ጦር ጋር ተቀላቀሉ።

የካቲት አስራ ሁለት ቀን አዲስ አበባ ብቻ ሰላሳ ሺህ በላይ ነዋሪዎችዋ ሰማአትነት ተቀብለዋል። ብዙ የሚቆጠሩ ቤቶች ተቃጥለዋል። ግድያው በመንገድ ላይ የተገኘ ማንኛውም ሰው ላይ ሲሆን ለመግደል  የሚፈለገው መስፈርት ኢትዮጵያው መሆኑ ብቻ ነበር።



አዲስ አበባ ስድስት ኪሎ የሚገኘው የካቲት 12 የሰማዕታት ሃውልት

ሞግስ አስገዶም፣አብርሃም ደቦጭ እና ስምዖን አደፍርስ ፍቅር እስከ መቃብር 

ስምዖን አብርሃም እ ሞገስን ደብረሊባኖስ ወደ ሰሜን ሸዋ መንገድ ከሚያውቃቸው አርበኞች ጋር አገናኝቶ ተመለሰ።ብዙም አልቆየ ፋሽስቱ ጥቁር ለባሾች ተይዞ ብዙ መከራ እና ስቃይ ተገደለ። የታሪክ ምሁራን እንዳስቀመጡት ስምዖን እጁም ሆነ እግሩ ጥፍር በጉጠት እየተነቀለ ጣቶቹን እየሰባበሩ አሰቃይተው ገደሉት።

አብርሃም ደቦጭ እ ሞገስ አስገዶም 

አብርሃም ደቦጭ ሞገስ አስገዶም ራስ አበበ አረጋይ አርበኞች ጦር ጋር ከተቀላቀሉ በኃላ ራስ አበበ አረጋይ ልዩ እንክብካቤ እንዲያገኙ አደረጉ።ቆይተው ግን የነበራቸውን ትምርት ደረጃ በመረዳት ሀገር ውጭ ወጥተው ሀገራቸው ቢሰሩ ይጠቅማሉ ብለው በማሰብ ስንቅ እ ገንዘብ ጋር ወደ ሱዳን እንዲሄዱ መከሯቸው። ሆኖም  ግን ጉዞአቸው ላይ ሱዳን ሊገቡ ትንሽ ሲቀራቸው  ፎቶዋቸው ገጠር ባሉ ፋሺሽት ወታደሮች ሁሉ ተናኝቶ ነበርና ፋሺሽቶች  ተይዘው በስቅላት ሰማዕት ሆኑ።በኃላ ግን አፄ ኃይለሰላሴ ሱዳን በኩል ጣልያንን እንግሊዝ ሰራዊት ጋር ሆነው ድል ሲያደርጉ አብርሃም እ  የሞገስ አስከሬን ተቆፍሮ ወጥቶ አሁን አዲስ አበባ በሚገኘው ቅድስት ስላሴ አርበኞች ሃውልት ስር እንዲያርፍ አድርገዋል።

ዘመኑን ዋጁት
'
ዛሬ ላይ ሆነን ዛሬ ሰማንያ አራት  ዓመታት የነበሩትን ወጣቶች ስናስብ እ ሐማሴን እ አካለጉዛይ እኛ ኢትዮጵያውያን የተለዩ አስመስለው ሊያወሩን ለሚፈልጉ መረብ ማዶም ሆነ ከመረብ ወዲህ ላሉት ባለ ጊዜዎች ትንሽ ጊዜ ወስደው እንዲያስቡ ማረግ ተገቢ ነው።መረብ ማዶውን መረብ ወዲሁ የተለያየው ታሪክ፣በዘር፣ ሃይማኖት አይደለም።ከእዚህ ይልቅ '' ውሸት ሲደጋገም እውነት የመሆን እድል ይኖረዋል'' የሚለውን ብሂል ሁል ጊዜ የሚሰራ የሚመስላቸው ወገኖች በሚነዙት ፕሮፓጋንዳ ብቻ ነው።

ፅሁፌን ከመጠቅለሌ በፊት አንዲት ሃሳቤን የምታሳርግልኝ ታዋቂው አሜሪካዊውን  ሀገራችን ታሪክ አዋቂ እ ስለ ኢትዮጵያ በመፃፍ የሚታወቁት አማርኛም አቀላጥፈው የሚናገሩት ፕሮፌሰር ዶናልድ ለቪን ከስምንት ዓመታት በፊት ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ በተናገሩት ንግግር ልደምድም።እንዲህ ነበር ያሉት :-''ኢትዮጵያን በአሁኑ ሰዓት የሚያስተዳድሯት የሀገሪቱን  ታሪክ በሚገባ የማያውቁ ናቸው።ስለዚህ የምመክረው ታሪክን በደንብ ይረዱ .......እናንት ኢትዮጵያውያን የችግሮቻችሁ ሁሉ መፍቻ ታሪካችሁ ላይ አለ በደንብ ተረዱት'' ፕሮፌሰር ዶናልድ ለቪን ።



ጉዳያችን Gudayachn

www.gudayachn.com  



ማሳሰብያ - ይህ ፅሁፍ ከአራት ዓመታት በፊት ለመጀመርያ ጊዜ በእዚሁ ገፅ  ላይ ወጥቶ ነበር።በሌሎች ድረ-ገፆችም ከእዚህ ገፅ ተወስዶ ተለጥፎ ነበር።


የፅሁፉ መርጃዎች

፩/ ዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ  http://www.ethioobserver.net/forgoten_heroes.ሕትም

፪/ኢሳት ራድዮ የካቲት 11/2004 ዓም ዝግጅት

፫/ ግሎባል አልያንስ ኢትዮጵያ  http://www.globalallianceforethiopia.org























ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።