- በጉባዔው ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤ/ክርስቲያን በአቡነ ሕርያቆስ የጣልያን እና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተወክላለች።
- ስብሰባው በዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክርቤት (World Council of Churches -WCC) ተደግፏል።
- በጉባዔው ላይ ከ20 የኦርቶዶክስ አብያተክርስቲያናት የተውጣጡ 52 ልዑካን ቡድን አባላት ተሳትፈዋል።
- በነሃሴ ወር ለሚደረገው የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክርቤት የኦርቶዶክሱ ዓለም ይዞ የሚቀርበው ምክረሃሳብ ላይ በጉባዔው ውይይት ተደርጓል።
- The meeting agreed to prepare themselves to the 11th WCC meeting in Karlsruhe, Germany From 31 August to September 8,2022.
- Fifty-two delegates representing 20 Eastern and Oriental Orthodox WCC member churches attended the meeting.

ጉዳያችን - በጉዳያችን ሚድያ፣ኮምኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት የሚዘጋጅ ሲሆን ከ2003 ዓም ጀምሮ በድረ-ገፅ ላይ የነበረ በአሁኑ ጊዜ ከአንድ ሚልዮን በላይ ጎብኚዎች ያሉት ገፅ ነው። Gudayachn is prepared by Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant Organization. It has been online since 2011. Currently, Gudayachn is being visited by over One-million readers from all over the world.
ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages
Tuesday, May 17, 2022
ትናንት በግሪክ ሳይፕረስ የተጠናቀቀው የዓለም ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ጉባዔ ልዩ ሪፖርት።Inter-Orthodox Churches, assembled from all over the world, attended the Pre-Assembly consultation meeting held in Cyprus, Greece.
Monday, May 16, 2022
የክረምቱ ወራት ሳይመጣ በሽብርተኛው ህወሃት እና ሸኔ የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያንን ከበለጠ ፈተና እናድናቸው።
Wednesday, May 4, 2022
በሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ እናቶች ልጆቻቸውን ከሕወሃት ጎን አሰልፈን አንዋጋም በማለታቸው እየታሰሩ መሆኑን ቢቢሲ በዛሬ ዜናው አስታውቋል።
Photo= Mitchellkphotos
Thousands of parents in the Tigray region in Ethiopia are arrested by TPLF for refusing to allow their children to fight against the Federal Government.
BBC Amharic report on May 4,2022
(Read English translation under Amharic here below)
ቢቢሲ አማርኛ ሚያዝያ 26/2014 ዓም
ከእዚህ በታች ያለው ዘገባ ሙሉው ከቢቢሲ አማርኛ ሚያዝያ 26፣2014 ዓም ከጻፈው ዜና እንዳለ የተወሰደ ነው።
ቢቢሲ ያነጋገረው አንድ የትግራይ ተወላጅ፤ ልጆች ለመዝመት ፍቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረታቸው ወላጅ አባቱ እና አጎቱ እንደታሰሩ ገልጿል።ለራሱና ለቤተሰቡ ደኅንነት ሲል ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀው ወጣት፤ "ቢያንስ ከቤተሰብ አንድ ሰው ውድትርና መላክ አለበት። መዋጣት አለበት የሚል ሕግ አለ" ይላል።
ይህ በአሁኑ ወቅት ከትግራይ ክልል ውጪ የሚገኘው ወጣት፤ "አባቴን ልጅህን አምጣህ አሉት። ማምጣት ስላልቻለ ለአንድ ወር አሰሩት። ከዚያ ደግሞ ወንድሜን እንዲያመጣ ብለው ለቀውት ነበር። አሁን ያለበትን ሁኔታ ባላውቅም ለመጨረሻ ጊዜ በስልክ ሳገኛቸው አባቴን አስረውት ነበር" በማለት ይናገራል።
ይህ ወጣት እንደሚለው አዋቂ የሆነው ወንድሙ በዚህ ጦርነት ተሳታፊ የመሆን ፍላጎት የለውም። "ወንድሜ እኮ ትልቅ ነው። ከፈለገ የአባቴን ፍቃድ ሳይጠይቅ ይሄድ ነበር። የያዙት ግን አባቴን ነው" በማለት ይናገራል።ልጆቻቸውን ወደ ጦር ሜዳ ባለመላካቸው አጎቱም ጨምር ለእስር መዳረጋቸውን ይህ ወጣት ይናገራል። "ከሁለት ወር በፊት አጎቴንም ሴት ልጁን አምጣ ብለው አስረውት ነበር። 18 ዓመት እንኳን አይሆናትም" ይላል።
"የደረሱ ልጆች የሉትም። በቤቱ ውስጥ ከትንንሾቹ መካከል ተለቅ ያለችው እሷ ነች። ስልክ ስለሌለ አሁን ያሉበትን ሁኔታ አላውቅም" ይላል።ይህ ወጣት እንደሚለው ከሆነ በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የትግራይ ክፍል እያስተዳደረ ያለው ህወሓት ለመዝመት ፍቃደኛ ያልሆኑ ልጆች ወላጆችን ማሰር ከመጀመሩ በፊት ሰዎችን አስገድዶ ወደ ጦር ሜዳ ይልክ ነበር ይላል።
"ከዚህ በፊት በኃይል አስገድዶ የመወስደ ተግባር ነበር። ይሄ ብዙ አላስኬድ አላቸው። ከዚያ 'ወላጆችን ብንይዝ ይገባሉ [ወደ ትግል]' የሚል አካሄደ መጥቷል። ይሄ በትግራይ በጣም ችግር እየሆነ ነው። እንደ ሕግ ነው የወረደው" በማለት ያብራራል። ከዚህ ወጣት በተጨማሪ በጦርነቱ ለመዋጋት ፍላጎት ስለሌላቸው ወላጆቻቸው እንደተሳሩባቸው ከሚናገሩት መካከል በክልሉ የሚንቀሳቀሰው የተቃዋሚ ፓርቲ አባል የሆኑት አቶ ክብሮም በርሀ ይገኙበታል።
የባይቶና ዓባይ ትግራይ የውጭ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ክብሮም በርሀ ታናሽ እህታቸው ለመዝመት ፍላጎት ስለሌላት ወላጅ እናታቸው በህወሓት መታሰራቸውን ለቢቢሲ ገልጸዋል።
"እኛ ቤት ሁሉም ስደት ላይ ናቸው። ከ18 ዓመት በታች የሆነች እህቴ ብቻ አለች [በትግራይ]። እህቴ 'ለምን ትግል አልሄደችም' ብለው ነው እናቴ ያሰሯት" ሲሉ ተናግረዋል።አቶ ክብሮም በርሀ ግን "ትግል መሄድ አለመሄድ የግል ምርጫ ነው፤ ወደ ትግል አልወጣህም ተብሎ ወላጅን ማሰር ግን በዓለም ታይቶ የሚታወቅ ነገር አይደለም" ይላሉ።
"ወላጅ እናቴ እዚጊእምን ተኽለሃይማኖት ትባላለች። በጣም ያሳዝናል። ያልጠበቅኩት ነገር ነው። የእኔ እናት ስለሆነች ሳይሆን የትግራይ ሕዝብ በሙሉ ረሀቡ፣ ችግሩ ሳያንሰው፣ መደፈር ሳያንሰው አሁን ደግሞ የኔ በሚላቸው ካድሬዎች መንገላታቱ ያሳዝናል" ብለዋል።
የባይቶና ዓባይ ትግራይ የውጭ ጉዳይ ኃላፊው የትግራይ ተወላጆች በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ፍትሕ ሳያገኙ መታሰራቸውን አውስተው "አሁንም ይህ በትግራይ ሲደገም ያሳዝናል" ሲሉ ተናግረዋል።አቶ ክብሮም ልጅ አልዘምትም ካለ የታመሙ ወላጆች ሳይቀሩ ለእስር እንደሚዳረጉ የገለጹ ሲሆን ፍርድ ቤት የሚቀርቡበት ሁኔታ ሳይኖር በርካታ ሰዎችም ትምህር ቤቶች ውስጥ ታስረው እንደሚገኙ ይናገራሉ።
ሌላኛው ቢቢሲ ያነጋገረው የትግራይ ክልል ነዋሪ በአሁኑ ወቅት በክልሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮች እንዳሉ ገልጾ ከእነዚህም መካከል አንዱ ወላጆች ልጆቻቸውን ለትግል እንዲልኩ መገደዳቸው አንዱ መሆኑን ይገልጻል።ለደኅንነቱ ሲባል ስሙን የማንጠቅሰው የትግራይ ክልል ነዋሪ፤ "ልጆቻችሁን አዋጡ እየተባልን ነው። መስተዳድር የለንም" ሲል ለቢቢሲ ተናግሯል።
=================
Thousands of parents in the Tigray region in Ethiopia are arrested by TPLF for refusing to allow their children to fight against the Federal Government.
============================
BBC Amharic report on May 4,2022
A native Tigray region resident interviewed by the BBC: said his parents and uncle were arrested for refusing to allow children for TPLF. The young man who asked not to be named for the safety of himself and his family; "There is a law that says at least one person in the family must send and safety receive."
According to this young man, his older brother did not want to take part in this war. "My brother is big. If he wanted to, he could go without my father's permission. But they arrested my father," he said.
He says that because he (his father) did not send his children to the battlefield, he and his uncle were imprisoned. "Two months ago, my uncle was arrested and told to bring his daughter. She is not even 18 years old," he said.
"He has no grown-up children. She's the biggest one in the house. I don't know where they are now because there is no telephone."
According to the young man, the TPLF, which currently controls most of Tigray, used to send people to the battlefield before they could arrest the parents of children who refused to march.
"In the past, there was rape. This has a lot to do with it. Then came the 'if we take parents, they will [fight].In addition to the young man, Kibrom Berha, a member of the regional opposition party, said his parents had been arrested for refusing to fight in the war against the Federal Government.
The head of foreign affairs of Baito and Abay Tigray, Kibrom Berha, told the BBC that his younger sister had been arrested by the TPLF for refusing to participate in the civil war.
"Everyone in our house is in exile. There is only my sister under the age of 18 [in Tigray]. My sister was arrested for saying, 'Why didn't she go to war?' The TPLF, for its part, says there have been signs of arresting parents in the past, but now it has stopped. "Such things were signs at the cadre level, but there is no way to arrest parents in this way. "Whether or not to go to war is a personal choice; arresting a parent for not going to war is not uncommon in the world," said Kibrom Berha.
"My mother is still called Tehlehaimanot. It is very sad. It is something I did not expect. It is unfortunate that this is being repeated in Tigray," he said. Kibrom said that even if the child is not a child, sick parents will be arrested and many people will be detained in schools without trial. Another resident of Tigray told the BBC that there are currently many problems in the region, one of which is forcing parents to send their children to fight. An unnamed resident of the Tigray region for security reasons; "We are being told to donate your children. We have no government," he told the BBC.
Source = BBC Amharic May 4,2022
Link = https://www.bbc.com/amharic/news-61316845
===============
Thursday, April 28, 2022
ድብቅ የፖለቲካ ዓላማ ያላቸው ቡድኖች የየዋህ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞችን የእምነት ስሜት ቆስቁሰው ወደ ግጭት ሊመሩን ሲሞክሩ ልንታለል አይገባም።
- በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ወደ ውጭ የፈረጠጠው ''የሸኔ የውስጥ አርበኛ'' ከሽብርተኛው የህወሃት ቡድን ጋር ከፈረጠጠባቸው አንዳንድ የመካከለኛው ምስራቅ ሃገሮች ውስጥ ሆኖ የሰሞኑን በኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች እና ሙስሊም ወገኖቻችን መሃከል ግጭት እንዲፈጠር ሲያስተባብር ነበር።
Tuesday, April 26, 2022
በዩክሬን ግጭት ሳቢያ ዘንድሮ የዓለም ምጣኔ 3.6 በመቶ ብቻ ያድጋል።የኢትዮጵያ ግን ዘንድሮ 3.8 በመቶ ሲያድግ በመጪው ዓመት ደግሞ በ 5.7 በመቶ ያድጋል ሲል አይኤምኤፍ አስታወቀ።
The Ethiopian economy will grow by 3.6% in 2022. By next year it will go up to 5.7% - IMF
አይኤምኤፍ የሩሲያና የዩክሬይን ጦርነት የዓለምን ኢኮኖሚያዊ ማገገም ወደኋላ እንደሚመልሰው ባብራራበት አዲሱ ሪፖርት፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እ.ኤ.አ በ2022 በ3.8 በመቶ ያድጋል ሲል ተንብዮ፣ በመጪው ዓመት ደግሞ ይህ ቁጥር ወደ 5.7 በመቶ ከፍ ይላል ብሏል፡፡
በጥቅምት ወር ይፋ ተድርጎ በነበረው የድርጅቱ ትንበያ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍጋኒስታን፣ ሊባኖስ፣ ሊቢያና ሶሪያ የተያዘውን የአውሮፓውያን ዓመት ጨምሮ ለቀጣይ አምስት ዓመታት ባለው ጊዜ ውስጥ የሚኖራቸውን አጠቃላይ አገራዊ ምርት ዕድገት መተንበይ አለመቻሉን አስታውቆ ነበር።
ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ አገሮች ኢኮኖሚ በዋናነት የኮሮና ወረርሽኝ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከመከሰቱ ጋር ተያይዞ በተፈጠረው የኢኮኖሚ ቀውስ ሳቢያ፣ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ማሽቆልቆል እንደሚገጥማቸው መተንበዩ አይዘነጋም፡፡ ኢትዮጵያ በትንበያው ያልተካተተችው በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሳቢያ አገራዊ የምርት ዕድገት ሒደቱን ማመላከት አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ እንደሆነ መግለጹ ይታወሳል፡፡
ባለፈው ሳምንት ይፋ በተደረገው ሪፖርት መሰረት በኢትዮጵያ ያለው የዋጋ ንረት እኤአ በ2021 ከነበረበት 26.8% ወደ 34.5% እንደሚያድግ የተተነበየ ሲሆን፣ነገር ግን ይህ አኃዝ እ.ኤ.አ በ2023 ወደ 30.5 በመቶ ዝቅ የማለት ዕድል አለው ተብሏል፡፡
የሩሲያና የዩክሬይን ጦርነት የዓለም ምጣኔ ሀብትንእኤአ በ2021 ከነበረው 6.1% ዕድገት በ2022 ወደ 3.6% ሊያወርደው እንደሚችል በሪፖርቱ ተመላክቷል። ይህ ደግሞ ጦርነቱ የውጪ ንግድ እንቅስቃሴዎችን በማስተጓጎል፣ የነዳጅና የምግብ ዋጋ ንረት በማስከተሉ እንደሆነ ሪፖርቱ ያሳያል፡፡
ከሰሃራ በታች የሚገኙት ነዳጅ አቅራቢ አገሮች በአማካይ 3.4 በመቶ እንደሚያድጉ የተተነበየ ሲሆን፣ መካከለኛ ገቢ እንዳለቸው የሚነገርላቸው የአፍሪካ አገሮች ደግሞ በአማካይ 3.3 በመቶ እንደሚያድጉ ይጠበቃል፡፡
ዝቅተኛ ኢኮኖሚ አላቸው የተባሉት አገሮች በአማካይ ሊያድጉ ይችላሉ የተባለበት አኃዝ 4.8 በመቶ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 6.4 በመቶ፣ ኬንያ 5.7 በመቶ፣ ቡርኪናፋሶ፣ ታንዛኒያና ኡጋንዳ እንደ ቅደም ተከተላቸው ከ4.7 አስከ 4.9 በመቶ የሚመዘገብ ዕድገት እንደሚስመዘግቡ ሲጠበቅ፣ ኢትዮጵያ ደግሞ 3.8 በመቶ እንደምታድግ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ዕድገት የዝቅተኛ ገቢ አላቸው ተብሎ ከተቀመጡት የአፍሪካ አገሮች ዝቅ ብሎ ቢገኝም፣ የነዳጅ ላኪ አገሮች ዝርዝር ውስጥ ከሚገኙት ናይጄሪያ፣ አንጎላና ጋቦን፣ እንዲሁም መካከለኛ ገቢ ካላቸው እንደ ደቡብ አፍሪካና ዛምቢያ ከመሳሰሉ አገሮች ብልጫ እንዳለው የአይኤምኤፍ ሪፖርት ትንበያ ያሳያል፡፡
የተራዘመ ጦርነት፣ ድርቅና ሰፊ የፀጥታ ችግር ውስጥ እንደምትገኝ በሚገለጸው ኢትዮጵያ ትንበያው ተስፋ የሚያሰንቅ ቢሆንም፣ አገሪቱ ብዙ ሥራዎች ማከናወን እንደሚገባት አመላካች እንደሆነ ሪፖርቱን የተመለከቱ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች አስታውቀዋል፡፡
የኢኮኖሚ ባለሙያው አቶ ዋሲሁን በላይ በሪፖርቱ ላይ ባቀረቡት አጭር ጽሑፍ እንዳመለከቱት፣ዓለም በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ተዳክሞ የነበረውን ኢኮኖሚ እንዲያገግም የማድረግ ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር፡፡ነገር ግን የሩስያና የዩክሬይን ጦርነት ነገሮችን ለውጦታል ብለዋል፡፡
አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ የዕድገት ትንበያ የሠራው የተጀመሩ ሥራዎችን፣ እንዲሁም ሪፖርቶችን መሠረት አደርጎ ነው የሚለውን ከግንዛቤ እንደወሰደ ይታመናል ያሉት የኢኮኖሚ ባለሙያው፣ በተጨማሪም በአገሪቱ ውስጥ የግብርና ምርታማነት እንደሚያድግ፣ የውጪ ንግድ አማራጮች እንደሚሰፉ፣ ለዓለም ገበያ ክፍት መሆን የጀመሩት ሥራዎችና የህዳሴ ግድብ የኃይል ምንጭ ጅማሮ ከግምት ውስጥ የገቡ ጉዳዮች ይሆናሉ የሚል እምነት እንዳለቸው አቶ ዋሲሁን ጠቁመዋል፡፡
የዜናው ምንጭ ሪፖርተር ጋዜጣ ሚያዝያ 24፣2022 ዓም እኤአ ዕትም ነው።
https://ethiopianreporter.com/article/25300
====================/////=========
Monday, April 25, 2022
መስቀል ስር ያለች መስቀል - የገጣሚት ሕሊና ደሳለኝ ግጥም (ቪድዮ)
Tuesday, April 19, 2022
ኦነግ ሸኔ ከኦሮምያ ክልል በቶሎ ካልተወገደ ፋኖ መላው የአማራ ክልልን ሊቆጣጠር ይችላል።ሸኔ በኦሮምያ ፋኖ በአማራ ተሰማርተው ኢትዮጵያ የጦር አበጋዞች አገር እንዳያደርጓት ጥንቃቄ ያስፈልጋል።
- አሁን ያለንበት ከስጋቱ ሁሉ በጣም ጧት ላይ ነን።ሆኖም ግን አስፈላጊው ስራ በመንግስትም ሆነ በህዝብ በትብብር ካልተሰራ ቀትርም ምሽትም ይመጣል።
Monday, April 18, 2022
በአማራ ክልል የጽንፍ እንቅስቃሴ? በአማራ ክልል ታዳጊዎችን ለጽንፍ ተግባር ለማሰማራት ስልጠና ተጀምሯል።ኦፌኮ ከሸኔ የጸዳ አይደለም የሚሉ ድምጾች ተበራክተዋል።ሽብርተኛው ህወሓት ሱዳን ውስጥ ስደተኛ ህጻናትን ለመመልመል እየተንቀሳቀሰ ነው።
በእነዚህ ሃይሎች የሚዘወረው ሱዳንን ማዕከል በማድረግ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው የህወሓት ሽብር ቡድን በተደጋጋሚ በአልፋሽጋ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ለመግባት ሙከራ አድርጓል፡፡ በድንበር አካባቢ ሰርጎ ለመግባት በሚደረገው ሙከራ በርካታ የትግራይ ወጣቶችን ህይወት እንደዋዛ እየቀጨ የአካል ጉዳተኛ እያደረገ ከንቱ ምኞት ሆኖ ቢቀርም፤ ቡድኑ ለትውሉዱ ደንታ ቢስ መሆኑን በሚያሳይ መልኩ ትንኮሳውን ቀጥሏል፡፡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በመጋቢት ወር 2014 ዓ.ም መጨረሻ በአልፋሽጋ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ ከነበሩ የቡድኑ ታጣቂዎች ውስጥ በርካቶች በኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት በወተሰደ እርምጃ ተገድለዋል፡፡ ብዛታቸው ያልታወቀ የቡድኑ ታጣቂዎች ቆስለው በሱዳን ጦር ወታደራዊ ካምፕ ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።
ቡድኑ በሱዳን የሚገኘውን የህወሃት ክንፍ ለማጠናከር የተለያዩ ስራዎች እያከናወነ መሆኑንም ምንጮች ይገልጻሉ፡፡ በዚህ መሰረት የሰው ሃይል ከመመልመል አንፃር ዶክተር መኮነን፣ ብ/ጄኔራል ግደይ ሃይሉ (ወዲ ፊውዳል)፣ ኮሎኔል ዕኮት፣ ኮሎኔል ሃይለ፣ ኮሎኔል ወዲ አማረ የተባሉ እና በየደረጃው የሚገኙ የቡድኑ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች በተለያዩ የስደተኛ መጠለያ ካምፖች በመዘዋወር የትግራይ ተወላጆችና ታጣቂዎችን ለመቀስቀስ ኮሚቴ በማዋቀር እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
በዚህ መሰረት የሰው ሃይል ከመመልመል አንፃር ዶክተር መኮነን፣ ብ/ጄኔራል ግደይ ሃይሉ (ወዲ ፊውዳል)፣ ኮሎኔል ዕኮት፣ ኮሎኔል ሃይለ፣ ኮሎኔል ወዲ አማረ የተባሉ እና በየደረጃው የሚገኙ የቡድኑ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች በተለያዩ የስደተኛ መጠለያ ካምፖች በመዘዋወር የትግራይ ተወላጆችና ታጣቂዎችን ለመቀስቀስ ኮሚቴ በማዋቀር እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ። የምልመላ ስራውን ለማሳካትም በጄኔራል ወዲ ፊውዳል የሚመራ ኮሚቴ ገዳሪፍ በሚገኘው የስደተኛ መጠለያ ካምፕ የሚገኙ ወጣቶችን ለመመልመል እንደተሰማራ ተጠቁሟል። በተመሳሳይ ኮሎኔል አጽረጋ እና ዶክተር መኮነን በተባሉ ግሰለቦች የሚመራ ኮሚቴ በካርቱምና አካባቢው የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ቡድኑን በመቀላቀል ወደ ስልጠና እንዲገቡ የመመልመል ስራዎችን እየሰሩ ነው። ሱዳንን ማዕከል በማድረግ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው የህወሓት ሽብር ቡድን የሰው ሃይል አቅሙን ለማጠናከር የሚያደርገውን የቅስቀሳና ታጣቂዎችን የመመልመል ስራ አጠናክሮ ከመቀጠሉ ባሻገር ወታደራዊ ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ታውቋል።አሸባሪው ቡድን በዚህ መልኩ የትግራይ ወጣቶችን ከመቀሌ እስከ ሱዳን እግር በግር እየተከታተለ መከራቸውን ለማራዘም እየሰራ ሲሆን፤ ይህ የማያባራ ሰቆቃ የሚጋብዝ እኩይ ሴራ አንድ ቦታ ሊቆም ይገባል፡፡ ቡድኑ በቃህ ሊባል ይገባል፡፡
Sunday, April 17, 2022
በኖርዌይ ኡስታዝ አቡበክር አሕመድ በተገኙበት ከኢድ እስከ ኢድ ጉዞ ወደ ሃገርቤት መርሃግብር ዙርያ ውይይት ተደረገ።አስተባባሪ ኮሚቴ ተዋቅሯል።ኢትዮጵያውያን የተጎዱትን ወገኖቻችንን ለመደገፍ በጉዞው እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል።
====================
ጉዳያችን ዜና/Gudayachn News
====================
የአገር ቤት ጉዞ ሁለተኛ ክፍል የሆነው ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጥሪ ከተደረገ በኋላ ዝግጅቱ መጠናቀቁ ከሰሞኑ ተሰምቷል።ይህንን ተከትሎም መርሃግብሩ ወጥቷል። በእዚህ መሰረት ዛሬ ሚያዝያ 9/2014 ዓም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ (ኮሚኒቲ) በኖርዌይ ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጉዞ ላይ ማብራርያ እንዲሰጡ ኡስታዝ አቡበክር አሕመድን በዙም ጋብዞ ከኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት አድርጎ ነበር።
በእዚህ መሰረት ኡስታዝ አቡበክር አሕመድ በማብራርያቸው ላይ ዝግጅቱ ትኩረት የተሰጠው እና ዝግጅቶችም እየተደረጉ መሆናቸውን አብራርተው፣ጥሪው ግን ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸዋል።በተጨማሪም እስልምና ወደ ኢትዮጵያ ከመጣ ጀምሮ ከሌሎች ወገኖቹ ጋር በሰላም የኖረበት ሁኔታ ላይ አጽንዖት በመስጠት ከሌሎች አጎራባች ሃገሮች ጋር አነጻጽረው ገለጻ አድርገዋል።በተጨማሪም ኢትዮጵያ በእስልማን ውስጥ ያላት ከፍተኛ ቦታ እና ስደተኞችንም በመቀበል ደረጃ ቀዳሚ ሃገር መሆንዋን አብራርተው በአሁኑ ጊዜ በሳውዲ የሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ስላለው ፈተናም ድምጻችንን ማሰማት እንደሚገባ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ከኖርዌይ ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጥሪ የሚሄዱም ሆኑ በሃሳብ እና በተለያዩ መንገዶች የራሳቸውን ድርሻ ለመወጣት የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንን ለማስተባበር የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በኖርዌይ የስራ አስፈፃሚ አባላትን ያካተተ ጊዜያዊ ኮሚቴ ያቋቋመ ሲሆን በኖርዌይ የሚገኙ የሙስሊምን አደረጃጀቶችን እንዲያካትት ሃሳብ ተሰጥቶ ስብሰባው ተፈጽሟል።በጉዞ የማስተባበር ሥራ የተመረጡ ከኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በኖርዌይ ስራ አስፈፃሚ አባላት ውስጥ ወ/ሮ አስማ እና ወ/ሮ ለይላ ሲመረጡ፣ ከእነርሱ ጋር በተጨማሪ አብረው የሚሰሩ ወ/ሮ ኢትዮጵያ እና ወ/ሮ ሮዛ ተመርጠዋል።
ከእዚህ በታች ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጥሪ መርሃግብር ያገኛሉ።
Friday, April 15, 2022
የኢትዮጵያን ወቅታዊ ችግሮች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የፈጠሯቸው ችግሮች አይደሉም።
Tuesday, April 12, 2022
በኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ዙርያ የአሁኑ ቅዳሜ ዓለም አቀፍ ውይይት ተዘጋጅቷል።ውይይቱን ሲቲዝን አስፓየር-ኖርዌይ፣ኢትዮጵያን ስኮላርስ በኖርዲክ ሃገሮች-ኖርዌይ፣ኢኦቲሲ ግሎባል ፎረም እና የኢትዮጵያውያን ሰላም እና እርቅ በዩኬ በጥምረት አዘጋጅተውታል።
- ሲቲዝን አስፓየር-ኖርዌይ፣
- ኢትዮጵያን ስኮላርስ በኖርዲክ ሃገሮች-ኖርዌይ፣
- ኢኦቲሲ ግሎባል ፎረም እና
- የኢትዮጵያውያን ሰላም እና እርቅ በዩኬ በጥምረት አዘጋጅተውታል።
ትናንት በግሪክ ሳይፕረስ የተጠናቀቀው የዓለም ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ጉባዔ ልዩ ሪፖርት።Inter-Orthodox Churches, assembled from all over the world, attended the Pre-Assembly consultation meeting held in Cyprus, Greece.
በጉባዔው ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤ/ክርስቲያን በአቡነ ሕርያቆስ የጣልያን እና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተወክላለች። ስብሰባው በዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክርቤት (World Council of Churc...
-
በ ካርታ ጫወጣ ጎበዝ አደለሁም። ግን ጆከር የተባለች ካርታ መኖሯን አውቃለሁ።ጆከር ካርታ በ ሁሉም ቦታ ስለምትገባ በ ካርታ ጫወታ ጆከር የደረሰው ሰው የማሸነፍ እድል ስላለው ፊቱ በ ፈገግታ ይሞላል። የ አትዮጵ...
-
••••••••••••••• ================= ጉዳያችን / Gudayachn News ================= አሜሪካኖች ኢትዮጵያ ውስጥ ገብተን ኢትዮጵያን ካልወጋን ብለዋል። ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሆኑ ወታደሮች...
-
Gudayachn / ጉዳያችን October 8,2021 CNN fake News may cost over 100 thousand Americans. The recent CNN allegation against Ethiopian Airlines h...