ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, April 28, 2022

ድብቅ የፖለቲካ ዓላማ ያላቸው ቡድኖች የየዋህ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞችን የእምነት ስሜት ቆስቁሰው ወደ ግጭት ሊመሩን ሲሞክሩ ልንታለል አይገባም።

ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ሙስሊም እና ክርስቲያን አዲስ አበባ ሙዚየም በር ላይ 
Photo = Adam Jones
  • በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ወደ ውጭ የፈረጠጠው ''የሸኔ የውስጥ አርበኛ'' ከሽብርተኛው የህወሃት ቡድን ጋር ከፈረጠጠባቸው አንዳንድ የመካከለኛው ምስራቅ ሃገሮች ውስጥ ሆኖ የሰሞኑን በኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች እና ሙስሊም ወገኖቻችን መሃከል ግጭት እንዲፈጠር ሲያስተባብር ነበር።
===============
ጉዳያችን / Gudayachn
===============

በኢትዮጵያ ሃይማኖትን ከሃይማኖት ለማጋጨት ሙከራ ሲደረግ ዛሬ አዲስ አይደለም።ለ27 ዓመታት ህወሃት ኢትዮጵያን ሲመራ ሆን ብሎ የሃይማኖት ግጭቶች እንዲነሱ ሰርቷል። ክርስቲያኖች የጥምቀት በዓል ሊያከብሩ አንድ ቀን ሲቀራቸው ሙስሊሞችን የደገፈ የመሰለ መግለጫ ሲወጣ፣ የሙስሊም ወገኖቻችን ድምጻችን ይሰማ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የሙስሊም መንግስት ይመስረት እያሉ ነው የሚል የሃሰት ወሬ በክርስቲያኖች መሃከል ይዘራ ነበር።ህዝብ ከህዝብ ጋር የሚነጋገርበት የራሱ ልዩ ቋንቋ ስላለው ይህ ሁሉ ከንቱ ሙከራ ሆኖ አልፏል።

ሰሞኑን መንግስት በሸኔ ላይ የጀመረው በድሮን የታገዘ መጠነ ሰፊ ዘመቻ በራሱ በመንግስት ውስጥ ሆነው የሸኔን እና የሸኔ መመታት የህወሃት አንዱ ክንፍ መመታት መሆኑ ያስበረገጋቸው ሁሉ አንድ ዓይነት ግርግር ካልፈጠሩ በቀር የውድቀታቸው መጨረሻ እንደሆነ ገባቸው። በእዚህ ደግሞ ከውጭ ያሉ የባዕዳን አዝማቾቻቸው ጭምር የውስጥ ተላላኪዎቻቸው ላይ የሚወሰደው እርምጃ አስደንግጧቸው ከርሟል።ባዕዳኑ በከፍተኛ ደረጃ ኢትዮጵያን ከማወክ ባለፈ ይበትንልናል ብለው በቅደም ተከተል ያስቀመጡት ቀዳሚው ሽብርተኛው ህወሃት ሲሆን በማስከተል የቤንሻንጉል እና የኦነግ ሸኔ እንቅስቃሴዎች ናቸው። ህወሃት በህዝብ ክንድ ተመትቶ ወደ ጎሬው ሲገባ በሎጀስቲክ እና በምክርም ጭምር ከተረፈው የህወሃት ቡድን ጋር አቀናጅተው ኢትዮጵያን ለማወክ ተስፋ ያደረጉበት ሽኔ ከበርካታ ቦታዎች ሰሞኑን በመከላከያ ሰራዊት እየተመታ ሲጠራረግ አንዳንድ የቡድኑ ደጋፊዎች ወደ ውጭ ሃገር መፈርጠጣቸው የአጋጣሚ ጉዳይ አይደለም።

ይህ በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ወደ ውጭ የፈረጠጠው የሸኔ የውስጥ አርበኛ ከሽብርተኛው የህወሃት ቡድን ጋር ከፈረጠጠባቸው አንዳንድ የመካከለኛው ምስራቅ ሃገሮች ውስጥ ሆኖ የሰሞኑን በኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች እና ሙስሊም ወገኖቻችን መሃከል ግጭት እንዲፈጠር ሲያስተባብር ነበር።ለግጭቱ የገንዘብ ድጋፍ የተገኘውም ሆነ በየዋሃን እምነታቸውን በሚያከብሩ ክርስቲያን እና ሙስሊም ወገኖቻችን መሃከል የተደራጁ በወገናቸው ደም የሚነግዱ ተከፋዮች መዋቅራቸውን አንዳንድ የክልል ባለስልጣናት ቢሮ ውስጥ ሁሉ በገንዘብ ኃይል ለመዘርጋት የሞከሩ ሲሆን የሰሞኑ የጎንደርም ሆነ የዛሬው በወራቢ የደረሱት ጥቃቶች የእነኝህ ተከፋዮች ስውር እንቅስቃሴ ውጤቶች ናቸው።በጎንደር ባብዛኛው ሙስሊም ወገኖቻችን ሲጠቁ፣በወራቢ ደግሞ ክርስቲያን ወገኖቻችን ተጠቅተዋል። በሁለቱም ቦታዎች ቤተክርስቲያን እና መስጊድ ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። የጥቃቱ አነሳሾችም ሆኑ ጥቃት አድራሾቹ ላይ መንግስት ግልጽ በሆነ መንገድ ለፍርድ ማቅረብ እና ቅጣታቸውም ህዝብ አስተማሪ መሆን ይገባዋል።

በሙስሊም ወገኖቻችን መሃከል ሆነው ክርስቲያኖችን የሚያስቆጡ ድርጊቶች መፈጸም፣ በክርስቲያን ወገኖቻችን መሃከል ሆነው ሙስሊም ወገኖቻችንን የሚያበሰጭ እና የሚያጋጭ ተግባር እንዲፈጸም ማድረግ እና በሚያስገኙት የደም ማስፈሰስ ስፋት እና ጥልቀት እየታየ በልዩ ልዩ መንገዶች የሚከፈላቸው የራሳችን ወገኖች ተልዕኮ የሰሞኑ ክስተት ውጤት ነው። ድርጊቱን ደግሞ የኢትዮጵያ ባላንጣ የሆኑ የቅርብ ሃገሮች በስለላ መዋቅሮቻቸው ከጀርባ የሚደግፉት እና ያገኙትን ቀዳዳዎች ሁሉ በመጠቀም የማባባስ ስራዎች ላይ ተጠምደው ከርመዋል። ተከፋይ አጋጮች መሬት ላይ የሚሰሩት ብቻ ሳይሆን በማኅበራዊ ሚድያ የሚያጣሉ እና አንዳንዶቹ በክርስቲያንም ሆነ በሙስሊም ስም ዩቱበር እና ፌስቡክ ከፍተው ሁለቱም ላይ የሚያጋጩ ጽሑፎች እየለጠፉ ሕዝቡን ለማባላት የሚጥሩ ናቸው። ለእዚህ ነው ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ዝም ብለው የነበሩ በክርስቲያንም ሆነ በሙስሊም ወገኖቻችን የሚታወቁ ተከፋይ የሃይማኖቱ አስተማሪ ተብዬዎች ቁስል እየፈለጉ እና ያሉ መለስተኛ አለመግባባቶችን እያሳበጡ ለመቀስቀስ ከየጠፉበት ብቅ እያሉ መሆናቸውን መመልከቱ በቂ ማስረጃ ነው።እነኝህ ተከፋዮች መምሕራን ተብዬዎች በመገናኛ ብዙኃን የተሰሙ መለስተኛ ግጭቶች የሕዝቡን ስሜት እንዲነኩ አድርገው እየጮሁ እና ስሜት እንዲኮረኩር አድርገው በመንገር አንዱ በአንዱ ላይ እንዲነሳ ስልታዊ በሆነ መንገድ ይቀሰቅሳሉ።

የኢትዮጵያ ሕዝብ የተንኮል ዓይነቶቹን መለየት አለበት። መሬት ላይ ያለው እውነታ የጽንፍ አስተሳሰቦች አሉ።ሆኖም ግን ብዙኃኑ ክርስቲያንም ሆነ ሙስሊም ወገናችን በየራሱ ውስጥ ያሉትን የጽንፍ አስተሳሰብ አራማጆች ፈጽሞ አይቀበላቸውም።ይልቁንም ከሁሉም የመንፈሳዊ አገልግሎቶች ከጽንፍ ባለፈ የፖለቲካ አስተሳሰብ አራማጆችን በቻለው አያቀርብም፣ይከላከላል።ሆኖም ግን እነኝህ ተከፋይ አጋጮች ትንሽ የመግቢያ ቀዳዳ የሚያገኙት መለስተኛ ግጭቶች ታይተው የህዝብ ስሜታዊነት በሚያይልበት እና እነርሱም የጥላቻ ቅስቀሳቸውን በሚያቀጣጥሉበት ጊዜ ነው።ባጭሩ ድብቅ የፖለቲካ ዓላማ ያላቸው ቡድኖች የየዋህ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞችን የእምነት ስሜት ቆስቁሰው ወደ ግጭት ለመምራት ሲሞክሩ ልንታለል አይገባም።ከአንደኛው ክ/ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ የኖረው ክርስትናም ሆነ ከ6ኛው ክ/ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ ያለው የእስልምና እምነቶች ዛሬ በተከፋይ የፖለቲካ ከሳሪዎች እንደእንግዳ አይተያዩም።እንንቃ!
=================////==============

Tuesday, April 26, 2022

በዩክሬን ግጭት ሳቢያ ዘንድሮ የዓለም ምጣኔ 3.6 በመቶ ብቻ ያድጋል።የኢትዮጵያ ግን ዘንድሮ 3.8 በመቶ ሲያድግ በመጪው ዓመት ደግሞ በ 5.7 በመቶ ያድጋል ሲል አይኤምኤፍ አስታወቀ።

The Ethiopian economy will grow by 3.6% in 2022. By next year it will go up to 5.7% - IMF

በየሁለት ዓመቱ በሚያወጣው የዓለም ኢኮኖሚ ምልከታ ሪፖርት የኢትዮጵያን የአገር ውስጥ ምርት ዕድገት (ጂዲፒ) ትንበያ ሳያካትት ያለፈው የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ)፣ በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የሚያንሰራራበት ዕድል መኖሩን አስታወቀ፡፡

አይኤምኤፍ የሩሲያና የዩክሬይን ጦርነት የዓለምን ኢኮኖሚያዊ ማገገም ወደኋላ እንደሚመልሰው ባብራራበት አዲሱ ሪፖርት፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እ.ኤ.አ በ2022 3.8 በመቶ ያድጋል ሲል ተንብዮ፣ በመጪው ዓመት ደግሞ ይህ ቁጥር ወደ 5.7 በመቶ ከፍ ይላል ብሏል፡፡ 

በጥቅምት ወር ይፋ ተድርጎ በነበረው የድርጅቱ ትንበያ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍጋኒስታን፣ ሊባኖስ፣ ሊቢያና ሶሪያ የተያዘውን የአውሮፓውያን ዓመት ጨምሮ ለቀጣይ አምስት ዓመታት ባለው ጊዜ ውስጥ የሚኖራቸውን አጠቃላይ አገራዊ ምርት ዕድገት መተንበይ አለመቻሉን አስታውቆ ነበር።

ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ አገሮች ኢኮኖሚ በዋናነት የኮሮና ወረርሽኝ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከመከሰቱ ጋር ተያይዞ በተፈጠረው የኢኮኖሚ ቀውስ ሳቢያ፣ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ማሽቆልቆል እንደሚገጥማቸው መተንበዩ አይዘነጋም፡፡ ኢትዮጵያ በትንበያው ያልተካተተችው በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሳቢያ አገራዊ የምርት ዕድገት ሒደቱን ማመላከት አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ እንደሆነ መግለጹ ይታወሳል፡፡

ባለፈው ሳምንት ይፋ በተደረገው ሪፖርት መሰረት በኢትዮጵያ ያለው የዋጋ ንረት እኤአ በ2021 ከነበረበት  26.8% ወደ 34.5% እንደሚያድግ የተተነበየ ሲሆን፣ነገር ግን ይህ አኃዝ እ.ኤ.አ በ2023 ወደ 30.5 በመቶ ዝቅ የማለት ዕድል አለው ተብሏል፡፡

የሩሲያና የዩክሬይን ጦርነት የዓለም ምጣኔ ሀብትንእኤአ 2021 ከነበረው 6.1%  ዕድገት 2022 ወደ 3.6% ሊያወርደው እንደሚችል በሪፖርቱ ተመላክቷል። ይህ ደግሞ ጦርነቱ የውጪ ንግድ እንቅስቃሴዎችን በማስተጓጎል፣ የነዳጅና የምግብ ዋጋ ንረት በማስከተሉ እንደሆነ ሪፖርቱ ያሳያል፡፡

ከሰሃራ በታች የሚገኙት ነዳጅ አቅራቢ አገሮች በአማካይ 3.4 በመቶ እንደሚያድጉ የተተነበየ ሲሆን፣ መካከለኛ ገቢ እንዳለቸው የሚነገርላቸው የአፍሪካ አገሮች ደግሞ በአማካይ 3.3 በመቶ እንደሚያድጉ ይጠበቃል፡፡

ዝቅተኛ ኢኮኖሚ አላቸው የተባሉት አገሮች በአማካይ ሊያድጉ ይችላሉ የተባለበት አኃዝ 4.8 በመቶ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 6.4 በመቶ፣ ኬንያ 5.7 በመቶ፣ ቡርኪናፋሶ፣ ታንዛኒያና ኡጋንዳ እንደ ቅደም ተከተላቸው ከ4.7 አስከ 4.9 በመቶ የሚመዘገብ ዕድገት እንደሚስመዘግቡ ሲጠበቅ፣ ኢትዮጵያ ደግሞ 3.8 በመቶ እንደምታድግ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ዕድገት የዝቅተኛ ገቢ አላቸው ተብሎ ከተቀመጡት የአፍሪካ አገሮች ዝቅ ብሎ ቢገኝም፣ የነዳጅ ላኪ አገሮች ዝርዝር ውስጥ ከሚገኙት ናይጄሪያ፣ አንጎላና ጋቦን፣ እንዲሁም መካከለኛ ገቢ ካላቸው እንደ ደቡብ አፍሪካና ዛምቢያ ከመሳሰሉ አገሮች ብልጫ እንዳለው የአይኤምኤፍ ሪፖርት ትንበያ ያሳያል፡፡

የተራዘመ ጦርነት፣ ድርቅና ሰፊ የፀጥታ ችግር ውስጥ እንደምትገኝ በሚገለጸው ኢትዮጵያ ትንበያው ተስፋ የሚያሰንቅ ቢሆንም፣ አገሪቱ ብዙ ሥራዎች ማከናወን እንደሚገባት አመላካች እንደሆነ ሪፖርቱን የተመለከቱ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች አስታውቀዋል፡፡

የኢኮኖሚ ባለሙያው አቶ ዋሲሁን በላይ በሪፖርቱ ላይ ባቀረቡት አጭር ጽሑፍ እንዳመለከቱት፣ዓለም በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ተዳክሞ የነበረውን ኢኮኖሚ እንዲያገግም የማድረግ ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር፡፡ነገር ግን የሩስያና የዩክሬይን ጦርነት ነገሮችን ለውጦታል ብለዋል፡፡

አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ የዕድገት ትንበያ የሠራው የተጀመሩ ሥራዎችን፣ እንዲሁም ሪፖርቶችን መሠረት አደርጎ ነው የሚለውን ከግንዛቤ እንደወሰደ ይታመናል ያሉት የኢኮኖሚ ባለሙያው፣ በተጨማሪም በአገሪቱ ውስጥ የግብርና ምርታማነት እንደሚያድግ፣ የውጪ ንግድ አማራጮች እንደሚሰፉ፣ ለዓለም ገበያ ክፍት መሆን  የጀመሩት ሥራዎችና የህዳሴ ግድብ የኃይል ምንጭ ጅማሮ ከግምት ውስጥ የገቡ ጉዳዮች ይሆናሉ የሚል እምነት እንዳለቸው አቶ ዋሲሁን ጠቁመዋል፡፡

የዜናው ምንጭ ሪፖርተር ጋዜጣ ሚያዝያ 24፣2022 ዓም እኤአ ዕትም ነው።

https://ethiopianreporter.com/article/25300

====================/////=========

Tuesday, April 19, 2022

ኦነግ ሸኔ ከኦሮምያ ክልል በቶሎ ካልተወገደ ፋኖ መላው የአማራ ክልልን ሊቆጣጠር ይችላል።ሸኔ በኦሮምያ ፋኖ በአማራ ተሰማርተው ኢትዮጵያ የጦር አበጋዞች አገር እንዳያደርጓት ጥንቃቄ ያስፈልጋል።

ፋኖ፣ፋኖን ከ50 ዓመታት በፊት ያዜመው ድምጻዊ  ካሣ ተሰማ 
  • አሁን ያለንበት ከስጋቱ ሁሉ በጣም ጧት ላይ ነን።ሆኖም ግን አስፈላጊው ስራ በመንግስትም ሆነ በህዝብ በትብብር ካልተሰራ ቀትርም ምሽትም ይመጣል።
===============
ጉዳያችን / Gudayachn
===============
አገር ከብሔራዊ የጦር ኃይሏ ውጭ ምንም ዓይነት አደረጃጀት ቢኖረው ሌላ በሺህ የሚቆጠር የጦር ኃይል እንዲንቀሳቀስ የማንም አገር ሕግ አይፈቅድም።የማንኛውም መንግስት አንዱና ዋናው ግዴታውም ሰላም እና ጸጥታ ማስከበር ነው።ጸጥታን ማስከበር ድህነት በተስፋፋበት፣የምጣኔ ሃብቱ በተጎሳቆለበት ሁኔታ በራሱ ከባድ ፈተና አለበት።ምክንያቱም በቀላል የጥቅማጥቅም ድለላ ወጣቶችን በቀላሉ ወደ ጥፋት መንገድ መምራት የሚችል ከባቢያዊ ሁኔታ ይፈጥራል።ኢትዮጵያ ደግሞ በአሁኑ ጊዜ ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሕዝቧ ወጣት ነው።ይህ ኃይል ደግሞ ከሥራ ማጣት ችግሩ ጋር ተዳምሮ ብቸኛ የሥራ መስክ ጠብመንጃ አንግቦ መንቀሳቀስ እንዳይሆን ያሰጋል።

ኦነግ ሸኔ መንግስት ባለበት ሃገር አንድ ጊዜ ከሱማሌ አዋሳኝ መንደሮች፣ካለፈው እሁድ ጀምሮ ደግሞ በሸዋ ሮቢት ዙርያ ጥቃት ከፍቷል። እዚህ ላይ የሰሜን ሸዋ የመንግስት ተጠሪዎች በተለይ በሸዋ ሮቢት ዙርያ ዳግም የተከፈተው ጥቃት በግለሰቦች ግጭት የተነሳ እንደነበር ቢገልጹም ሁኔታው ግን እንደዛ እንዳልሆነ ለማወቅ ብዙም ምርምር አይጠይቅም።የኢትዮጵያ ከተሞች በኦነግ ሸኔ በተፈናቀሉ ስዱዳን እየተጣበቡ ነው። ደብረብርሃን ለእዚህ ጥሩ ምሳሌ ነች። ደብረብርሃን በኦነግ ሸኔ በሰሜን ሸዋ ባደረሳቸው ጥቃቶች ብቻ ሳይሆን በወለጋ ባደረሰው ጥቃትም የተፈናቀሉ ደብረ ብርሃን ከተማ ከትመዋል። 

የኦነግ ሸኔ በቶሎ አለመጥፋት አሁን ባሉት አነስተኛ ከተሞች የሚደረግ ጥቃት ብቻ አይሆንም መዘዙ። በቀጥታ ወደ የለየለት የከተማ የሽብር ቡድን እራሱን አያደራጅም ማለት አይቻልም።ለእዚህ ደግሞ ዋና ምክንያቱ የሸኔ የገንዘብ፣የስንቅ እና ትጥቅ ምንጭ በስልጣን ላይ ያሉ የኦሮምያ ክልል ባለስልጣናት እና የጸጥታ ጉዳይ ኃላፊዎች ጭምር መሆኑ ነው። መንግስት ባሉት የጸጥታ መዋቅሩ በሚገባ የሕዝቡን የጸጥታ እና ደህንነት በሚገባ ካላስጠበቀ ሕዝብ ከውስጡ የወጡትን ፋኖ እንዲጠብቀው እና ኢመደበኛ በሆነ መልክ ሁሌም እንዲኖር ይፈልጋል።በእዚህ መሃል ደግሞ በቅንነት የቆመው የፋኖ አባል  ቀድሞ ባላሰበው መንገድ ሊገፋ ይችላል።

ጉዳዩ አደገኛ ነው። ፋኖ በተለይ በኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ያለው ታሪካዊ ዳራ እና በታሪክም ለኢትዮጵያ ነጻነት የፋሺሽት ጣልያንን ከኢትዮጵያ ማስወጣት ጀምሮ የተጻፈ ታሪክ አለው።በስሙ ሲዘፈንለት፣ግጥም ሲገጠምለት እና የራሱ ሕዝባዊ ቅርጽ ያለው ታሪክ አለው። በቅርቡ ከህወሃት ጋር በተደረገው ጦርነትም የአማራ ክልልን ከኢትዮጵያ መከላከያ ጋር በአንድነት አኩሪ ታሪክ ሰርቷል። ይህ በራሱ የጠለቀ ማኅበራዊ መሰረት እንዳለው በቀላሉ መረዳት ይቻላል።

በሌላ በኩል ኦነግ ሸኔ የኦነግ ጽንሰሃሳብ ውሉደ ውሉድ ወይንም ውላጅ ነው።ጽንሰ ሃሳቡ የጠራ የፖለቲካ ግብ አይኑረው እንጂ ጧት ማታ የሚያዜመው አማራውን፣ነፍጠኛውን ማጥፋት እና የኦሮምያ መንግስት መመስረት የሚሉት ሃሳቦች የት እንደሚያደርሱ ሳያውቅ የሚናውዝ እሳቤ ባለቤት ነው። የመናወዙ ዲግሪ ለመረዳት የኦሮምያ ክልልን ያሏትን የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች ሳይቀር የሚያወድመው ይሄው የኦነግ ውላጅ የሆነ ሃሳብ የተሸከመው ሸኔ ነው። 

ሸኔ በቀጥታ ፋሺዝም ነው። ፋኖ የቀደመ ታሪኩም ሆነ አሁን ያለበት ደረጃ ሕዝብ ተከላካይ ነው። ፋኖ በቀድሞ ታሪኩ ሂደቱ ግልጽ ነው። ይሄውም ጦርነት ሲመጣ ሴት ወንድ ሳይል ይዘምታል፣የሃገር ሰላም አስተካክሎ ተመልሶ ገበሬው ወደ ግብርና ሰራተኛው ወደ ስራው ይመለሳል።አበቃ! አሁን ባለንበት ጊዜ ሽብርተኛው ህወሃት ገና ከትግራይ ህዝብም ጫንቃ ላይ ገና አልተነቀለም፣ኦነግ ሸኔም በዘር ላይ በተመሰረተ የጥላቻ ወረራ ገና አልቆመም።ስለሆነም ፋኖ የቤቱ እና የልጆቹ ጉዳይ ካላስገደደው በግንባር ጥቂት ጊዜ መቆየቱ ጉዳት የለውም። ይህም ግን ያለው ውስጣዊ አመራር ወደ ሌላ አደገኛ መንገድ እንዳይመሩት ጥንቃቄ አያስፈልገውም ማለት አይደለም።ምክንያቱም የአገር ቀዳሚ መርሁ አንድ መከላከያ ሰራዊት ነውና።

በእዚህ ሁሉ መሃል ኦነግ ሸኔ ካልጠፋ ግን ፋኖ ወደ ቤቱ የመመለስ እድሉ ላይኖር ይችላል ብቻ ሳይሆን በሂደት የአማራ ክልልን በሙሉ የመቆጣጠር ሁኔታዎች አይፈጠርም ማለት አይቻልም።ለእዚህ ደግሞ ዋናው መሰረታዊ አመላካች ጉዳይ ህዝብ ከመደበኛ ሰራዊቱ ባላነሰ ባንዳንድ ቦታዎች ፋኖ በበለጠ ሁኔታ ይጠብቀኛል የሚል ሕዝብ እየተፈጠረ መሆኑ ነው። በእዚህ አስተሳሰብ ደግሞ በህዝቡ ላይ ልንፈርድበት ምንም ዓይነት ሞራላዊ ሁኔታ አይኖርም።ምክያቱም መንግስት የሰላም እና የጸጥታ መጠበቅ ስራውን በሚገባ መወጣቱን ማሳየት ብቸኛው አማራጭ ነውና።

ለማጠቃለል ኦነግ ሸኔ ከኦሮምያ ክልል በቶሎ ካልተወገደ ፋኖ መላው የአማራ ክልልን ሊቆጣጠር ይችላል።ሸኔ በኦሮምያ ፋኖ በአማራ ተሰማርተው ኢትዮጵያ የጦር አበጋዞች አገር እንዳትሆን ያሰጋል።አሁን ያለንበት ከስጋቱ ሁሉ በጣም ጧት ላይ ነን።ሆኖም ግን አስፈላጊው ስራ በመንግስትም ሆነ በህዝብ በትብብር ካልተሰራ ቀትርም ምሽትም ይመጣል።ለእዚህ ሁሉ መፍትሄው ችግሮቻችንን በሚገባ መረዳት ነው። የኦነግ ሸኔ አረመኔያዊ ተግባርን ከአማራ ክልል እና ከሱማሌ ክልል ባልተናነሰ በኦሮምያ ክልልም ይታወቃል። ይህ ሁኔታ ግን ወደፊት እንዳለ ላይቀጥል ይችላል። ለምሳሌ ኦነግ ሸኔ ፋታ ተሰጥቶት ከኖረ ፋኖ አገንግኖ ወጥቶ ከሸኔ የመከላከል ብቸኛ አውራ ሆኖ ለመውጣት ታሪክ በራሱ ይገፋዋል። ይህ ደግሞ ከላይ በርዕሱ እንደተገለጸው ኢትዮጵያ የጦር አበጋዞች አገር እንዳትሆን ያሰጋል።ለእዚህም ዛሬ የሚሰራው አገራዊ የጋራ ስራ ወሳኝ ነው። በእዚህ ስራ ደግሞ መተማመን የሚፈጥር አሰራሮች መንግስት በሁሉም መስክ ማስፈን፣ኦነግ ሸኔ ላይ የሚደረገው ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠሉ ፋይዳው ብዙ ነው።
============////============


Monday, April 18, 2022

በአማራ ክልል የጽንፍ እንቅስቃሴ? በአማራ ክልል ታዳጊዎችን ለጽንፍ ተግባር ለማሰማራት ስልጠና ተጀምሯል።ኦፌኮ ከሸኔ የጸዳ አይደለም የሚሉ ድምጾች ተበራክተዋል።ሽብርተኛው ህወሓት ሱዳን ውስጥ ስደተኛ ህጻናትን ለመመልመል እየተንቀሳቀሰ ነው።

በአማራ ክልል ታዳጊዎችን ለጽንፍ ተግባር የሚመለምሉ አሉ።

===============
ጉዳያችን / Gudayachn
===============

ጽንፈኝነት ዘር የለውም። የእገሌ ጎሳ ሲሰራው ስህተት እና ወንጀል፣የእንቶኔ ጎሳ ሲሰራው ትክክል ሊሆን አይችልም። ነጩን ነጭ፣ጥቁሩን ጥቁር ብሎ ኢትዮጵያዊነት ከሁሉም አቅጣጫ ገንኖ እንዲወጣ ማድረግ በምንም ዓይነት ድርድር ውስጥ የሚገባ ጉዳይ አይደለም።ኢትዮጵያ ዘመናትን ተሻግራ ዛሬ ላይ የደረሰችው በጎሳቸው እያሰሉ ፍትሕ የማይሰጡ እውነተኛ መሪዎች ስለነበሯት ነበር። ህዝብን ወደ እልቂት የሚመራ ማናቸውም ዓይነት ተግባር ከየትኛውም ጎሳ ቢመጣ ኢትዮጵያን የሚል በሙሉ ሊቃወመው የሚገባ ነው።

ይህ በእንዲህ እያለ በአማራ ክልል ዕድሜያቸው ከ15 እስከ 19 ዓመት የሆናቸው ታዳጊዎችን በተለያዩ ሰዋራ ቦታዎች ወታደራዊ ስልጠና እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን መረጃዎች ወጥተዋል።ስልጠና እንዲሰጡ የሚያደርጉት ደግሞ የጽንፈኝነት እንቅስቃሴ ለማራመድ ዕቅድ በያዙ አካላት መሆኑን መረጃው ያሳያል። እነዚህ በታዳጊዎች ህይወት ቁማር ለመጫወት የቆረጡ ሰዎች በተጠቀሰው የእድሜ ክልል ብቻ የሚገኙ  የአማራ ተተኪ ትውልዶች እንዲመለምሉና ጫካ ገብተው የትጥቅ ትግል እንዲጀምሩ በወሰኑት መሰረት በርካቶች እንደ እሳት እራት በከንቱ መስዋዕት ለመሆን እየተዘጋጁ ይገኛሉ፡፡ ይህ የአማራ ክልል ወደ እርስ በርስ ግጭት እንዲገባ ብቻ ሳይሆን ክልሉ ለኢትዮጵያ ካለው ጉልህ ሚና አንጻር የእዚህ ዓይነት የጽንፍ እንቅስቃሴዎች ለኢትዮጵያ ትልቅ አደጋ አለው።

የኢትዮጵያ የቅርብም ሆኑ የሩቅ ጠላቶቿ በአሁኑ ጊዜ ትልቁ ፍላጎታቸው በኢትዮጵያ የእርስበርስ ጦርነት እንዲነሳ በቻሉት መንገድ በተለያየ መንገድ ያኮረፉ ግለሰቦች በገንዘብ በመደገፍ ወደ ጽንፍ እንቅስቃሴ እንዲገቡ ማድረግ ነው። የሚገርመው ታዳጊዎችን የመመልመሉ ተግባር ከአልሸባብ ጭምር መማር አለብን የሚል አቋም ማንጸባረቁ አስገራሚው ጉዳይ ነው።በእዚህ እኩይ ተግባር የተሰማሩ ነገ ክልሉን ማባርያ ወደ የሌለው እልቂት ከትተው ሕዝቡን ወደ የማይወጣው ማጥ ውስጥ ብቻ የሚከቱ ሳይሆኑ እርስ በርሱ ተከባሮ የሚኖረውን ኢትዮጵያዊ ወደ የባሰ ግጭት ከትተው መጪውን የኢትዮጵያውያንን ሕይወት የሚያጨልም አደገኛ አካሄድ በመሆኑ ከወዲሁ ህዝብ አውቆ ነቅቶ እና ተግቶ መቀመጥ አለበት።

ይህ በእንዲህ እያለ የትግራይ ወጣቶችን ያስጨረሰው ሽብርተኛው ህወሃት የትግራይ እናቶች ልጆቻችን የት አሉ? ብለው ሲጠይቁ ''የትግራይ ወጣቶችን ቆጥሮ ያስረከበኝ የለም '' የሚል የትዕቢት መልስ ከሰጠ በኋላ የትግራይ እናቶች በቤታቸው በድብቅ ከማልቀስ ሌላ አማራጭ አላገኙም።በኢትዮጵያ ያለውን የትግራይ ወጣት ያስጨረሰው ሽብርተኛው ሕወሃት ወደ ሱዳን ዘልቆ ታዳጊዎችን መመልመል ሥራ ላይ ተጠምዶ ሰንብቷል።ይህ በእንዲህ እያለ ግን በህወሓት ውስጥ የሁለቱ ቡድን ማለትም ድርድር እናድርግ የሚለው እና ጦርነቱን እያረዘምን እንዋጋ በሚሉት ቡድኖች መሃከል ውጥረቱ ከሯል።ጦርነቱን እንቀጥል የሚሉት የቡድኑ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች የሱዳኑን እንቅስቃሴ በዋናነት እንደሚመሩት  የሚነገር ሲሆን፤ ድርደር ይሻለናል የሚለው ጎራ የእነዚህን እንቅስቃሴ በጥርጣሬ ከማየት ባሻገር ውስጣዊ  ሽኩቻውን ከፍ እንዳደረገው በስፋት እየተሰራጨ ነው፡፡

በእነዚህ ሃይሎች የሚዘወረው ሱዳንን ማዕከል በማድረግ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው የህወሓት ሽብር ቡድን በተደጋጋሚ በአልፋሽጋ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ለመግባት ሙከራ አድርጓል፡፡ በድንበር አካባቢ ሰርጎ ለመግባት በሚደረገው ሙከራ በርካታ የትግራይ ወጣቶችን ህይወት እንደዋዛ እየቀጨ የአካል ጉዳተኛ እያደረገ ከንቱ ምኞት ሆኖ ቢቀርም፤ ቡድኑ ለትውሉዱ ደንታ ቢስ መሆኑን በሚያሳይ መልኩ ትንኮሳውን ቀጥሏል፡፡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በመጋቢት ወር 2014 ዓ.ም መጨረሻ በአልፋሽጋ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ ከነበሩ የቡድኑ ታጣቂዎች ውስጥ በርካቶች በኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት በወተሰደ እርምጃ ተገድለዋል፡፡ ብዛታቸው ያልታወቀ የቡድኑ ታጣቂዎች ቆስለው በሱዳን ጦር ወታደራዊ ካምፕ ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል። 

ቡድኑ በሱዳን የሚገኘውን የህወሃት ክንፍ ለማጠናከር የተለያዩ ስራዎች እያከናወነ መሆኑንም ምንጮች ይገልጻሉ፡፡ በዚህ መሰረት የሰው ሃይል ከመመልመል አንፃር ዶክተር መኮነን፣ ብ/ጄኔራል ግደይ ሃይሉ (ወዲ ፊውዳል)፣ ኮሎኔል ዕኮት፣ ኮሎኔል ሃይለ፣ ኮሎኔል ወዲ አማረ የተባሉ እና በየደረጃው የሚገኙ የቡድኑ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች በተለያዩ የስደተኛ መጠለያ ካምፖች በመዘዋወር የትግራይ ተወላጆችና ታጣቂዎችን ለመቀስቀስ ኮሚቴ በማዋቀር እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ። 

በዚህ መሰረት የሰው ሃይል ከመመልመል አንፃር ዶክተር መኮነን፣ ብ/ጄኔራል ግደይ ሃይሉ (ወዲ ፊውዳል)፣ ኮሎኔል ዕኮት፣ ኮሎኔል ሃይለ፣ ኮሎኔል ወዲ አማረ የተባሉ እና በየደረጃው የሚገኙ የቡድኑ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች በተለያዩ የስደተኛ መጠለያ ካምፖች በመዘዋወር የትግራይ ተወላጆችና ታጣቂዎችን ለመቀስቀስ ኮሚቴ በማዋቀር እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ። የምልመላ ስራውን ለማሳካትም በጄኔራል ወዲ ፊውዳል የሚመራ ኮሚቴ ገዳሪፍ በሚገኘው የስደተኛ መጠለያ ካምፕ የሚገኙ ወጣቶችን ለመመልመል እንደተሰማራ ተጠቁሟል። በተመሳሳይ ኮሎኔል አጽረጋ እና ዶክተር መኮነን በተባሉ ግሰለቦች የሚመራ ኮሚቴ በካርቱምና አካባቢው የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ቡድኑን በመቀላቀል ወደ ስልጠና እንዲገቡ የመመልመል ስራዎችን እየሰሩ ነው። ሱዳንን ማዕከል በማድረግ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው የህወሓት ሽብር ቡድን የሰው ሃይል አቅሙን ለማጠናከር የሚያደርገውን የቅስቀሳና ታጣቂዎችን የመመልመል ስራ አጠናክሮ ከመቀጠሉ ባሻገር ወታደራዊ ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ታውቋል።አሸባሪው ቡድን በዚህ መልኩ የትግራይ ወጣቶችን ከመቀሌ እስከ ሱዳን እግር በግር እየተከታተለ መከራቸውን ለማራዘም እየሰራ ሲሆን፤ ይህ የማያባራ ሰቆቃ የሚጋብዝ እኩይ ሴራ አንድ ቦታ ሊቆም ይገባል፡፡ ቡድኑ በቃህ ሊባል ይገባል፡፡


በሌላ በኩል የኦሮሞ ፌድራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ከሸኔ የጸዳ ነው ወይ? የሚለው ጥያቄ በህዝቡ መሃከል እየተወራ ነው። ለእዚህ መነሻነት በርካታ ጉዳዮች እየቀረቡ ነው።ከእዚህ ውስጥ አንዱ ድርጅቱ በቅርቡ ባደረገው ጠቅላላ ጉባዔ የአቋም መግለጫ ላይም ሆነ በኋላ ያወጣው መግለጫ ላይ አንድም ቦታ ሸኔ ያላወገዘ ብቻ ሳይሆን ከፓርቲው ጋር ቁርኝት ያላቸው አባላቱ በማኅበራዊ ሚድያ ሳይቀር ሽኔን ሲያሞካሹ ታይተዋል። ኦፌኮ ሸኔን በተመለከተ አለማውገዙ ብቻ ሳይሆን መንግስት እንዲደራደር የሚያግባባ መግለጫ ከማውጣቱ በላይ አመራሮቹ የሚሰጧቸው የተለያዩ መግለጫዎች የሚያሳዩት ይህንኑ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል።

ባጠቃላይ የጽንፍ እንቅስቃሴዎች በአዲስ መልክ በአማራ ክልል፣በመሃል ሃገር በኦሮምያ ብልጽግና ውስጥ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሸኔ አሁን በኦፌኮ ውስጥ አለ ተብሏል።በሌላ በኩል ሽብርተኛው ህወሓት ውስጡ እንደገና ከመከፋፈሉ በላይ ወደ ሱዳን ተሻግሮ ለአቅመ አዳም እና ሔዋን ያልደረሱ ልጆች እየመለመለ ነው። ይህ ሁሉ እንቅስቃሴ ኢትዮጵያን ወደ እርስ በርስ ጦርነት ለመክተት የሚደረግ የሃገር ውስጥም ሆነ የባዕዳን ሴራ ሁሉ ውጤት እንደሆነ ለማወቅ ሊቅነት አይጠይቅም። ኢትዮጵያውያን ጸንተው በመቆም ኢትዮጵያን ወደ የትኛውም የጽንፍ እንቅስቃሴ የሚገፉ ኃይሎች ከየትኛውም ክልል ቢነሱ ህዝብ እንደ ህዝብ ሊቃወመው ይገባል።ይህ የአሁኑ ትውልድን ማዳን ብቻ ሳይሆን መጪውን ትውልድም የማዳን ስራ ነው።
===============////============

Sunday, April 17, 2022

በኖርዌይ ኡስታዝ አቡበክር አሕመድ በተገኙበት ከኢድ እስከ ኢድ ጉዞ ወደ ሃገርቤት መርሃግብር ዙርያ ውይይት ተደረገ።አስተባባሪ ኮሚቴ ተዋቅሯል።ኢትዮጵያውያን የተጎዱትን ወገኖቻችንን ለመደገፍ በጉዞው እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል።

====================

ጉዳያችን ዜና/Gudayachn News

====================

የአገር ቤት ጉዞ ሁለተኛ ክፍል የሆነው ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጥሪ ከተደረገ በኋላ ዝግጅቱ መጠናቀቁ ከሰሞኑ ተሰምቷል።ይህንን ተከትሎም መርሃግብሩ ወጥቷል። በእዚህ መሰረት ዛሬ ሚያዝያ 9/2014 ዓም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ (ኮሚኒቲ) በኖርዌይ ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጉዞ ላይ ማብራርያ እንዲሰጡ ኡስታዝ አቡበክር አሕመድን በዙም ጋብዞ ከኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት አድርጎ ነበር።

ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ

በእዚህ መሰረት ኡስታዝ አቡበክር አሕመድ በማብራርያቸው ላይ ዝግጅቱ ትኩረት የተሰጠው እና ዝግጅቶችም እየተደረጉ መሆናቸውን አብራርተው፣ጥሪው ግን ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸዋል።በተጨማሪም እስልምና ወደ ኢትዮጵያ ከመጣ ጀምሮ ከሌሎች ወገኖቹ ጋር በሰላም የኖረበት ሁኔታ ላይ አጽንዖት በመስጠት ከሌሎች አጎራባች ሃገሮች ጋር አነጻጽረው ገለጻ አድርገዋል።በተጨማሪም ኢትዮጵያ በእስልማን ውስጥ ያላት ከፍተኛ ቦታ እና ስደተኞችንም በመቀበል ደረጃ ቀዳሚ ሃገር መሆንዋን አብራርተው በአሁኑ ጊዜ በሳውዲ የሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ስላለው ፈተናም ድምጻችንን ማሰማት እንደሚገባ ገልጸዋል።

በመጨረሻም ከኖርዌይ ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጥሪ የሚሄዱም ሆኑ በሃሳብ እና በተለያዩ መንገዶች የራሳቸውን ድርሻ ለመወጣት የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንን ለማስተባበር የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በኖርዌይ የስራ አስፈፃሚ አባላትን ያካተተ ጊዜያዊ ኮሚቴ ያቋቋመ ሲሆን በኖርዌይ የሚገኙ የሙስሊምን አደረጃጀቶችን እንዲያካትት ሃሳብ ተሰጥቶ ስብሰባው ተፈጽሟል።በጉዞ የማስተባበር ሥራ የተመረጡ ከኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በኖርዌይ ስራ አስፈፃሚ አባላት ውስጥ ወ/ሮ አስማ እና ወ/ሮ ለይላ ሲመረጡ፣ ከእነርሱ ጋር በተጨማሪ አብረው የሚሰሩ ወ/ሮ ኢትዮጵያ እና ወ/ሮ ሮዛ ተመርጠዋል።

ከእዚህ በታች ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጥሪ መርሃግብር ያገኛሉ።

የሰንጠረዥ ምንጭ  = አዲስ ማለዳ ሚያዝያ 12/2014 ዓም

=============///================

Friday, April 15, 2022

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ችግሮች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የፈጠሯቸው ችግሮች አይደሉም።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሰሜን ሸዋ ጉብኝት ላይ 
ሚያዝያ 7/2014 ዓም

===============
ጉዳያችን / Gudayachn
===============

ከችግር የፀዳ አገር የለም።የችግር ዓይነቱ መለያየቱ እርግጥ ነው። የኢትዮጵያ ወቅታዊውም ሆነ የከረሙት ፖለቲካዊ፣ምጣኔሃብታዊ እና ማኅበራዊ ችግሮች ስረ መሰረታቸው ከኋላ የሚጀምር እንጂ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የፈጠሩት በሚመስል መልክ አንዳንድ ዩቱበሮችም ሆኑ ግለሰቦች ለህዝብ እንደሚያስተላልፉት የተሳሳተ መረጃ አይደለም። ችግሮቻችንን መረዳት እና የሚፈቱበት መንገድ ላይ ከመምከር ይልቅ በመንጋ አስተሳሰብ በመዋጥ ብቻ ማኅበራዊ ሚድያ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ በተልዕኮ የማጥላላት ዘመቻ ከከፈቱ የአገር ውስጥ እና የባዕዳን የኢትዮጵያ ጠላቶች የሚወረወርላቸውን መርዘኛ ቃላት በማወቅም ካለማወቅ ወደ ውስጣቸው እያስገቡ መልሰው የወሬያቸው ማሟሻ ሲያደርጉ መመልከት አሳዛኝ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደ ስልጣን ሲመጡ የጠበቀቻቸው ኢትዮጵያ በጎሳ ላይ የተመሰረተ ህገመንግስት ብቻ ሳይሆን ታች ወረዳ ድረስ በጥላቻ የጎሳ ፖለቲካ የተወታተበ አሰራር እና አመራር ብቻ ሳይሆን የጸጥታ አስጠባቂም ጭምር ነው። አንዳንዶች ይህንን አሰራር እና አመራር ለምን አልቀየሩትም? የሚል ጥያቄ ይጠይቃሉ። ይህ ጥያቄ ተገቢ ጥያቄ ነው።ነገር ግን ጥያቄው የለውጡን አካሄድ ካለመረዳት የሚመነጭ ችግር ነው።ይህ ለውጥ በኢትዮጵያ በ1966 ዓም እና የ1983 ዓም ለውጥ የሚለይበት በተለይ የጸጥታ አጠባበቅ ታች በወረዳ ደረጃ የተለየ ባህሪ አለው። 

በ1966 ዓም የንጉሱ ሥርዓት በወታደራዊ መንግስት ከተቀየረ በኋላ ከመደበኛ ወታደሩ ውጭ ያለው ታች ያለውን የቀበሌ እና የወረዳ የጸጥታ አጠባበቅ በአብዮት ጠባቂ እና የገበሬ ማኅበር ታጣቂዎች የጸጥታ የማስጠበቅ ኃላፊነቱን ወሰዱ። ወቅቱ በፖለቲካ የስልጣን ግጭት ከፍተኛ የደም መፋሰስ ቢያስከትልም የቀበሌና ገበሬ ማኅበር ታጣቂ ከስር ያለውን የጸጥታ አጠባበቅ እስከ የግለሰብ ቤት ድረስ እንዲወርድ አድርጓል።

በሌላ በኩል በ1983 ዓም የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት ወደ ስልጣን ሲመጣ ብሔራዊ ጦር ሰራዊቱን ከማፍረስ ባለፈ አሁንም በከተሞች በቀበሌ እና በገጠር ደግሞ በገበሬው ደረጃ ልክ ወታደራዊ መንግስት በአብዮት ጠባቂ እና የገበሬ ማኅበር ታጣቂ እንዳደረገው ሁሉ ህወሃት/ኢህአዴግ በከተሞች 'ሰላምና መረጋጋት' የተሰኙ ታጣቂዎች በገበሬው ዘንድም በወታደራዊው መንግስት ዘመን የታጠቁ ታጣቂዎች በአዲስ ታጣቂዎች በመቀየር ከታች ያለውን የጸጥታ አጠባበቅ በማገዝ በቶሎ ጸጥታውን ማረጋጋት ተሞክሯል። የጸጥታው አካል ግን በራሱ የቆመ ሳይሆን የፖለቲካ አካሉ በታች ወረዳ ደረጃ ስለተቀየረ በ1966 ዓም ሆነ በ1983 ዓም የተፈጠሩት የጸጥታ አካላት ከፖለቲካ አመራሩ ጋር አብረው የተፈጠሩ ስለሆኑ እንደ እጅ እና ጓንት ለመያያዝ እና ለመናበብ ችለዋል።

አሁን ያለው ለውጥ ግን በትልልቅ የኢትዮጵያ የጸጥታ አካሎችን ለምሳሌ የመከላከያ እና የደህንነት መዋቅር ለማስተካከል የደከመውን ያህል ታች ወረዳ ላይ ያለው የጸጥታ መዋቅር እና የፖለቲካ አስተዳደሩን ግን እንደ 1966 ዓም እና እንደ 1983 ዓም አልቀየረም።በመሆኑም በክልል ደረጃ እና ከዋና ከተማዋ በራቁ ቦታዎች ላይ ያለው የጸጥታ መረጃዎች በስርዓት እንዳይፈሱ ቀድሞም የነበሩ የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች በከተሞችም ሆነ በገጠር የመንግስት የአስተዳደር መዋቅር ላይ ብቻ ሳይሆን በህወሃት/ኢሃዴግ ዘመን የነበሩ ለውጡ የደከመ ሲመስላቸው ከህወሃት ጋር የሚጻጻፉ ሌላ ጊዜ ደግሞ የለውጥ ሃዋርያ እየሆኑ በዘረፋ ሲጠመዱ ከርመዋል።በመሆኑም ይህ ለውጥ በጸጥታ አደረጃጀትም ሆነ ከታች ያለውን የፖለቲካ አመራር ሳይቀየር የተገባበት ስለሆነ ብዙ ነገሮች ተደባልቀው መሄዳቸው ያስከተሉት ችግር አንዱ እና ዋናው የለውጡ ችግር ነው።ይህ ሁኔታ ወደ ኦሮምያ ክልል ሲመጣ ቀድሞ ከነበረው የኦህዴድ አክራሪ ቡድን ላይ ከውጭ የመጣው የኦነግ የተለያዩ አደረጃጀቶች በክልሉ አስተዳደራዊም ሆነ የክልል ኃይል ውስጥ በቀጥታ ገቡ።ከእዚህ ሁሉ በላይ ግን ህወሃት በኢትዮጵያ ላይ አጥምዶት የሄደው ከፋፋይ የጎሳ ፖለቲካ አራማጅ ሕገ መንግስት የችግሮቹ ዋና አንቀሳቃሽ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ለአክራሪ የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች እንደ ጋሻ ሆኖ ለወንጀል መፈጸምያ መጠቀምያ መሆኑ የታወቀ ነው። 

ይህ ለውጥ የጎሳ ፖለቲካን ተንጠላጥለው የስልጣን ጥማቸውን ለማርካት በሚራወጡ ኃይሎች እና ኢትዮጵያን የሁሉም እኩል ጠቃሚ ትሁን በሚሉ ኃይሎች መሃከል የሚደረግ ፍትግያ ውስጥ ለመሆኑ የሚጠራጠር የለም።ይህም ሆኖ ግን በብሔራዊ ውይይት ኮሚሽን ሃሳቦችን በሰላማዊ መንገድ ቀርበው ውይይት ሲደረግባቸው ብዙዎቹ ሃሳቦች መፍትሄ ያገኛሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን።መፍትሄ የማያገኙ ሃሳቦች ቢኖሩ ቢያንስ ሕዝብ የበታኝ ኃይሎች ሃሳብ ምን ያህል ትውልድ እና አገር በታኝ እንደሆነ በውይይቱ ሂደት ለህዝብ መጋለጡ አይቀርም።

ለማጠቃለል የኢትዮጵያ ወቅታዊ ችግርን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የፈጠሩት አይደለም። የችግሩ ስሮች ወደ ኋላ የሚወስደን ነው።ይህ ማለት ግን አሁን ላሉት ችግሮች የመፍትሔ አካል አይደሉም ማለት አይደለም።የህወሃት ደጋፊዎችም ሆኑ የጽንፍ የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች አሁን ዋና ዒላማቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ናቸው። ከዩቱብ እስከ ትዊተር፣ከመንደር ጠጅ ቤቶች እስከ የገጠር ጠላ ቤት ድረስ ሁለቱም ኃይሎች ያሰማሯቸው እና ተከፋዮችን አሰማርተው የኢትዮጵያ ችግር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የሆኑ አስመስሎ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ በመንዛት ላይ ተጠምደዋል። ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ይልቅ ኃይለስላሴ የበለጡ ኦሮሞ ናቸው የሚል ትርክት ይዘው ብቅ ካሉት ከዶ/ር መራራ ጀምሮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አማራ ጠል ናቸው እስከሚለው ውሸት ድረስ የምዕራባውያን ሚድያዎች ሁሉ ዋና የጥላቻ ዘመቻቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ላይ የዘመቱ ናቸው። አንዳንዶች ከወሬው ብዛት ሳያውቁት እንዲጠራጠሩ የራሳቸውን የማገናዘብ እና ምክንያታዊ አስተሳሰብ ሲቃረኑ፣ ሌሎች ዐቢይ አማራ ጠል ሆነ ማለት ልጆቹ እና ባለቤቱን ጠላ ማለት እንደሆነ አዙረው ለማሰብ አለመቻላቸውን ለመገንዘብ ሲያቅታቸው መመልከት ያሳዝናል። ኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግል አገር አይደለችም።ሁላችንም እንደሚያገባን እና እንደምንወዳት እርሱም ይወዳታል።ምናልባት የእርሱ የመምራት ዕድሉን አግኝቷል። ኢትዮጵያውያን በወሬ ማዕበል ከመወሰድ ኢትዮጵያን ብሎ የቆመን መሪን በማገዝ ኢትዮጵያን ወደየተሻለ ደረጃ እናድርስ። የዩቱብ አሻሻጮች እየተከትልን የወሬ አዳማቂ መሆን አገር አይጠቅምም።
===============///============

Tuesday, April 12, 2022

በኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ዙርያ የአሁኑ ቅዳሜ ዓለም አቀፍ ውይይት ተዘጋጅቷል።ውይይቱን ሲቲዝን አስፓየር-ኖርዌይ፣ኢትዮጵያን ስኮላርስ በኖርዲክ ሃገሮች-ኖርዌይ፣ኢኦቲሲ ግሎባል ፎረም እና የኢትዮጵያውያን ሰላም እና እርቅ በዩኬ በጥምረት አዘጋጅተውታል።

ሲቲዝን አስፓየር ኖርዌይ 

=====================
ጉዳያችን ዜና / Gudayachn News
=====================

ታኅሳስ 20/2014 ዓም የኢትዮጵያ ተወካዮች ምክር ቤት በሁለተኛው ልዩ ስብሰባው አንድ ወሳኝ ውሳኔ አሳልፎ ነበር። ይሄውም የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለማቋቋም የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በአብላጫ ድምፅ በማሳለፍ ያቋቋመበት ቀን ነበር። ኮሚሽኑ ኢትዮጵያውያን በጋራ አጀንዳዎች ላይ እንዲመክሩ እና ብሔራዊ መግባባት እንዲፈጠር እንደሚሰራ የኮሚሽኑ ምስረታ ላይም ሆነ በኋላ የኮሚሽኑ አባላት ምርጫ ከተደረገ በኋላም ጭምር በሚገባ ተብራርቷል።

ይህ ለኢትዮጵያ የቀረበ የሰለጠነ የጋራ ችግር መፍቻ ዓይነተኛ መንገድ ብቻ ሳይሆን ዕድልም ጭምር ነው። አሁን ኢትዮጵያውያን በውይይቱ ዙርያ መወያየት፣የኮሚሽኑን ሥራዎች የተሳለጡ እንዲሆኑ በሃሳብ ማዳበር እና ልምዳቸውን ማካፈል በእጅጉ ይጠበቅባቸዋል። 

በእዚህ መሰረት የአሁኑ ቅዳሜ ሚያዝያ 8/2014 ዓም (አፕሪል 16/2022 ዓም) አራት የኢትዮጵያውያን ዓለም አቀፍ አደረጃጀቶች በኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ዙርያ አራት ምሑራን ማለትም ፕሮፌሰር ብርሓኑ መንግስቱ፣ዶ/ር ደሳለኝ ጫላ፣አርክቴክ ዮሓንስ  መኮንን እና ዶ/ር ልዑልሰገድ አበበ በዋናነት እና ሌሎች ምሑራን ሃሳብ የሚያካፍሉበት የውይይት መርሓግብር ተዘጋጅቷል።በዝግጅቱ ላይ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
ውይይቱን 
  • ሲቲዝን አስፓየር-ኖርዌይ፣
  • ኢትዮጵያን ስኮላርስ በኖርዲክ ሃገሮች-ኖርዌይ፣
  • ኢኦቲሲ ግሎባል ፎረም እና 
  • የኢትዮጵያውያን ሰላም እና እርቅ በዩኬ በጥምረት አዘጋጅተውታል።
ውይይቱ በዙም የሚደረግ ሲሆን ዝርዝር የመግቢያው ማስፈንጠርያ፣ኮድ እና ሰዓቱ እንደየከተሞቹ ከእዚህ በታች ካለው ፖስተር ላይ ያገኛሉ።ላልሰሙ በማካፈል አገራዊ ግዴታዎን ይወጡ።የአገር ጉዳይ ለተወሰኑ ሰዎች የሚሰጥ ሥራ ሳይሆን የሁላችንም የጋራ ተግባር መሆኑን ለሁሉም ማሳወቅ የእያንዳንዱ ሰው ኃላፊነት ነው።








The term Western Tigray is one-sided terminology that was introduced by the TPLF regime


Sustainable Solution for the Problem of Welkait and the surrounding

By Dejen Ras

Sustainable Solutions for global problems
We, humans, are keen to solve problems. Our intelligence, instinct, and intuition have helped us to be creative and make life better as time goes by. In fact, our collective problem-solving competence has increased through time. Our ancestors created fire and tamed fire for cooking food, surviving in harsh climates, defending themselves from harmful animals, and so on.  We invented machinery and robots that help us to automate and produce many things that are vital for life. The technology-based solutions to communication problems have brought the world together as if you live in the same village, they call it a global village. Problems like poverty, health, clean water, race discrimination, gender equality, and so on are being dealt with collectively and individually across nations, of course at a different pace. In all these, we are aspiring for solutions that are sustainable. 
Think about the race problem in America. The struggle for equality has never stopped. Just this week, the US Senate confirms Jackson as a first Black woman on U.S. Supreme Court.  She remarked the following in her historic confirmation with a moving speech: 'We've made it. All of us.'  We would like to give emphasis on the phrase, “All of Us.” She also quoted Maya Angelou and said, "I do so now while bringing the gifts my ancestors gave. I am the dream and the hope of the slave." She understood that she was the future of her ancestors. This is remarkable history for all humanity.  It will resonate all over the world.
We humans, in our endeavor, to solve the problems we face; create new problems as well. The growth of our needs has created global warming, for example. The 21st-century humans are aspiring to solve this environmental problem in every part of the globe. We are looking for environmentally friendly solutions that are sustainable. The solution that is being proposed should be sustainable, which means a solution that will be able to stay over a period of time.  We are not there but we are pursuing such a solution. Kudos!
The term sustainability is used in many global matters and affairs. For example, the UN has set up 17 interlinked global goals, called Sustainable Development Goals (SDGs), just to achieve a better and more sustainable future for all. Many global actors use these standards when designing projects that have the intention to solve problems related to the environment, agriculture, technology, health, education, and so on. Sustainability is embedded in all sectors.
Sustainable Solutions for local problems
We started to present the term sustainable solution in a broader global perspective for our audience so as to remind our readers that such global wisdom should be applied when trying to solve local problems as well,  like the Wolkait and its surrounding problem. We will define the Wolkait problem in its correct context soon. One has to involve the historical, cultural, and social context that has transpired in the past 50 years, even more, if we are keen to solve this problem sustainably. Without that, if you just try to cheat and make some kind of drama and manipulation like designed demography change, using Demographic Engineering,  and claim that it is yours, then you are only listening to your own selfish and barbaric interest. At the end, your solution becomes temporal.  At one time you feel you are strong, and you decided to occupy it by force, then another time when you are weak, others will come and take it by force. That means you did not solve the problem in a sustainable way at the outset. For example, if you aspire to solve global warming, and If you try to cheat and continue to produce more CO2, then you know, and know, that you will not solve the global warming problem at all. Facts matter when solving such real problems.   
Any global power and institution meddling in this local matter without knowing the local context in-depth, by only listening to one side of the story, is making a grave error as well. For example, the recent Amnesty International and Human Rights Watch report is one example: Crimes against Humanity and Ethnic Cleansing in Ethiopia’s Western Tigray Zone. We should not Condon any crime against humans. If done it should be investigated by the authorities, and justice should be made. 
This piece just deals with the main root problem: the problem of Wolkait and its surrounding. In this regard, in the report, they claim that this region belongs to Western Tigray. Right now, the term Western Tigray is one-sided terminology that was introduced by the TPLF regime. And it is in the constitution. But the constitution is not accepted document by all. It is only forced.  At present, the name western Tigray does not exist. So, when those who prepared the report use the term, they are meddling in an instant. Especially, for those people who have endured the injustice created by TPLF for the past 30 years in that area, it is not acceptable.   That means the people at Amnesty International and Human Rights Watch are ill-advised or ill-informed, or even they are doing it deliberately knowing the facts and siding with one. Therefore, even your approach to the problem matters, that means, if you are contributing to a sustainable solution or not. Let us define the problem in its deeper context, first.
How and when was this problem created?
Remember, the very reason, we are still in this problem is because this problem was deliberately created in the past 45-50 years when the Marxist-Leninist political party, TPLF, took the land by force using the Darwinian principle of “the survival of the fittest.” Even the pioneers of this party know that very well. It is in the public media what these former members of the TPLF witnessed about it.  Actually, that area was a hiding place for many rebel groups even before the formation of TPLF. The forces like the youth movement called EPRP,  EDU, and other small and large rebel groups used to control the area before and during the Derg regime.  TPLF forces took that area by force from all these rebel forces who were struggling with Derg, and even sometimes with each other. Prior to controlling this area, TPLF was confined in a very small area on the other side of Tekeze river. The remnants of these different rebel forces still exist today. If they are asked about it, they could provide a deeper clarity on the matter.  
Note that we did not define the problem by asking whose inheritance is that place? Which people group lived there and what kind of administration was there at that time prior to that period. The correct contextual definition of the existing problem comes out from the struggle to dominate the politics of the country. Historical evidence provides us that TPLF aligned with their northern neighbors, Shabiya, and assisted by western forces and Arab nations like Egypt managed to overthrow the Soviet-aligned central government. This provides a huge opportunity for TPLF forces to do whatever they want in the country. Especially, in this part of the country which helped them to hide and gain momentum almost for two decades of struggle. It is a highly a romantic place in connection to their struggle to power. So Welkait and the surrounding problem is created prior to TPLF assumed power. The problem was created prior to the existing constitution. This constitution was developed without the real representation of many pf the ethnic groups, especially the Amhara people. The constitution was not inclusive in that sense. 
If needed, the people who lived all their lives in that part of the country are there. They are able to give evidence of their inheritance.  All the rebels who used to hide there have eaten, drunk, and got shelter from these people.  There is no confusion on this matter. The only confusion arises when one comes and claims the land of others by force. And when the international body believe in and accept it as a fact by listening to the narrative of one side of the story. 
Make no mistake here, we are not arguing that Ethiopians from other parts of the country cannot live in Welkait and its surrounding. No way! Even the present constitution states that every Ethiopian has the right to live, work and make properties anywhere in the country, read Article 15. But administrative-wise, Welkait, and its surrounding got problems when the TPLF led government decided to include it in the Tigray region. This problem has been propagated from its inception until now. TPLF has created the problem. So, it is part of the problem. It cannot act as an innocent entity. It should not be treated as if so.   
The people have been formally asking the existing and previous governments for years in a democratic way. But the previous TPLF led government gave a deaf ear. There are many reasons for that. Its geostrategic importance is significant for everyone, especially for them. 
Why is the Welkait Problem so complicated?
1. Political power. Anyone who controls Welkait can control Ethiopia. This statement seems a bold one. But it is fact. Without controlling Welkait and its surroundings, TPLF and its former partner Shabiya could not have made it so far. Help from historical enemies of Ethiopia, like Egypt, comes this way. You can train and hide all your forces in these areas. Its proximity to the semen mountains and Tekeze river further will allow you to mobilize your forces easily and fight the central government for decades until you win.
Without Welkait, TPLF is back to its infant stage when it started its struggle on the other side of Tekeze. It is weaker without it. No clear weapon, logistics, and even food supply root.  Without direct communication with Sudan and without monopolizing the border with Eritrea, it cannot be a significant power force in the region. Welkait and its surrounding hold by its enemies means, TPLF is choking to death. The people of Tigray can  destroy it by themselves even.  Right now, TPLF is like a tiger whose spinal cord is crushed, it cannot move in a meaningful way. Only the head is left for the Tigray people to crash it themselves.
2. Economical Reason. Welkait and its surroundings have a huge agricultural potential. As stated by Tedla & Moges, “Economically, Welkait is rich in fertile land, where mechanized agriculture can produce surplus consumables and export items, including sesame seeds, incense, cotton, and valuable minerals. ” These are mostly export goods. One who has control over the local area has definitely an economical advantage over the adjacent areas.
3. Security and Stability Reason. Anyone who secures Welkait, and its surrounding region controls the security and stability of the country. It controls the area that has a direct border with Sudan as well as Eritrea. It means you control the tripoint or tri-border area.  Remember, the Fasil castle in Gondar was partly destroyed by forces who came this way; Emperor Yohannes was killed by Mahdist forces who came from that direction. Derg regime could not manage peace all the 17 years in Welkait area, and finally its downfall came from this surrounding.   
Now if TPLF forces control this area, they can enjoy direct access to Sudan, and Port Sudan and strengthen with historical enemies of Ethiopia, like Egypt,  to unsettle the country. At the same time, they also control the influence of Eritrea in the region. That is why they have tried to break through that area more than 3 dozen times in the last almost two years of war, but without success.
Sustainable solution to Welkait Problem
The way forward or the sustainable solution to this problem is to be truthful and allow the people in the country to decide by themselves so that they live in peace and develop (or prosper) together. We propose three solutions in order of their degree of sustainability. The former is our best suggestion.  
Sustainable solution 1.
The ultimate best solution is to eradicate ethnic-based regional and local administration from the constitution. Amending the constitution provides a sustainable solution to this critical problem.   That will allow citizens to live anywhere in the country, including Welkait and its surrounding. This is the most sustainable solution.  Even it is the most viable sustainable solution for most of the conflicts in the country right now. Many African countries have implemented such rules. They have avoided ethnic-based systems - the root of all evils. It starts sweet like honey when you start to fight for the right of your own ethnic group and ended up bitter like death when you kill other ethnic groups brutally whom you lived side by side for centuries. So, stop ethnic-based politics, regions, and local administrations. But of course, it does not mean ethnic cultures, languages, and rights should not be respected. Every ethnic Identity should be celebrated, and every ethnicity should co-exist with other ethnicities.
Sustainable solution 2.
If not, if people should adhere to this ethnic-based regional and local administration, then the way this problem, Welkait, and its surrounding problem, was handled in the past was wrong. It was first controlled by force as described above, and later demographic engineering was done systematically for more than two decades. Hence this reality should be considered when solving it if our solution has to be somehow sustainable.  Maybe go deep into the history. We recommend an article by, Achamyeleh Tamiru. Remember, the solution that considers such past history will face resistance from one side or the other.  However, the more you are closer to the truth, the more it is sustainable it will be. Why is the reason that two neighbor people, Amhara and Tigray, are not solving this problem in truth? The land is enough if it is handled rightly and respecting human life.   
Sustainable Solution 3.
Take out TPLF from the equation for example, by force or it decays by itself, or it becomes crushed by the Tigray people. Then there is no one who tries to get power in the country in a crooked way like it does, and the people of Tigray will live where ever they like to live in the country, including Welkait and the surrounding. The people can live where ever they want with their fellow citizens in the country without the burden of helping TPLF to get power or without the burden of helping the hidden agenda of Egypt and the West as they did so far.  We know that the youth of Tigray are dying every day for the main agenda of Egyptians and others, not just for the cause of Tigray people. They are the dream forces of the Egyptians to destabilize Ethiopia. Of course, this is not told to them directly. They said that they are fighting for the people of Tigray. But that is a pure lie. The fact of the matter is, the people of Tigray, as is evidenced in the recent development,  have benefited nothing in the past 47 years of struggle except a few ones who made fortunes out of it. But now they are in limbo, they are under the fierce control of TPLF, and they need to be free from this strong hold. So set them free from TPLF bondage. 
Of course, TPLF has come so long due to its enablers like Egypt, and some western powers. That is why the world was under one narrative, one propaganda when it comes to the northern conflict in Ethiopia. TPLF has many people at the top of the western echelon: WHO, Amnesty International, Human Rights Watch, USAID, and so on. The very strength of TPLF lies only with these global powers. That is why it has been difficult to apply this solution by Ethiopian government so far. 
Advice for global forces meddling in Ethiopia
The global forces who are meddling in other countries' internal affairs should align themselves to one of the sustainable solutions proposed above if they intend not to make the problem worsen. If they really care for the Tigray people, let them just leave the problem to be solved by Ethiopian people and the government so that those Tigray people who are now living in Welkait and the surrounding continue to live in peace and harmony like the rest of their fellow citizens. Hence, we remind you to preach and teach yourselves about sustainable solutions, which you claim to apply in your guiding documents. 
Right now, you are not helping! You are meddling! So #NoMore Meddling in other countries in the name of human rights and so on!  

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።