ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, April 17, 2022

በኖርዌይ ኡስታዝ አቡበክር አሕመድ በተገኙበት ከኢድ እስከ ኢድ ጉዞ ወደ ሃገርቤት መርሃግብር ዙርያ ውይይት ተደረገ።አስተባባሪ ኮሚቴ ተዋቅሯል።ኢትዮጵያውያን የተጎዱትን ወገኖቻችንን ለመደገፍ በጉዞው እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል።

====================

ጉዳያችን ዜና/Gudayachn News

====================

የአገር ቤት ጉዞ ሁለተኛ ክፍል የሆነው ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጥሪ ከተደረገ በኋላ ዝግጅቱ መጠናቀቁ ከሰሞኑ ተሰምቷል።ይህንን ተከትሎም መርሃግብሩ ወጥቷል። በእዚህ መሰረት ዛሬ ሚያዝያ 9/2014 ዓም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ (ኮሚኒቲ) በኖርዌይ ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጉዞ ላይ ማብራርያ እንዲሰጡ ኡስታዝ አቡበክር አሕመድን በዙም ጋብዞ ከኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት አድርጎ ነበር።

ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ

በእዚህ መሰረት ኡስታዝ አቡበክር አሕመድ በማብራርያቸው ላይ ዝግጅቱ ትኩረት የተሰጠው እና ዝግጅቶችም እየተደረጉ መሆናቸውን አብራርተው፣ጥሪው ግን ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸዋል።በተጨማሪም እስልምና ወደ ኢትዮጵያ ከመጣ ጀምሮ ከሌሎች ወገኖቹ ጋር በሰላም የኖረበት ሁኔታ ላይ አጽንዖት በመስጠት ከሌሎች አጎራባች ሃገሮች ጋር አነጻጽረው ገለጻ አድርገዋል።በተጨማሪም ኢትዮጵያ በእስልማን ውስጥ ያላት ከፍተኛ ቦታ እና ስደተኞችንም በመቀበል ደረጃ ቀዳሚ ሃገር መሆንዋን አብራርተው በአሁኑ ጊዜ በሳውዲ የሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ስላለው ፈተናም ድምጻችንን ማሰማት እንደሚገባ ገልጸዋል።

በመጨረሻም ከኖርዌይ ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጥሪ የሚሄዱም ሆኑ በሃሳብ እና በተለያዩ መንገዶች የራሳቸውን ድርሻ ለመወጣት የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንን ለማስተባበር የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በኖርዌይ የስራ አስፈፃሚ አባላትን ያካተተ ጊዜያዊ ኮሚቴ ያቋቋመ ሲሆን በኖርዌይ የሚገኙ የሙስሊምን አደረጃጀቶችን እንዲያካትት ሃሳብ ተሰጥቶ ስብሰባው ተፈጽሟል።በጉዞ የማስተባበር ሥራ የተመረጡ ከኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በኖርዌይ ስራ አስፈፃሚ አባላት ውስጥ ወ/ሮ አስማ እና ወ/ሮ ለይላ ሲመረጡ፣ ከእነርሱ ጋር በተጨማሪ አብረው የሚሰሩ ወ/ሮ ኢትዮጵያ እና ወ/ሮ ሮዛ ተመርጠዋል።

ከእዚህ በታች ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሃገር ቤት ጥሪ መርሃግብር ያገኛሉ።

የሰንጠረዥ ምንጭ  = አዲስ ማለዳ ሚያዝያ 12/2014 ዓም

=============///================

No comments: