ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, May 29, 2021

ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ እያደረገች ያለውን ጣልቃ ገብነት በመቃወም በኦስሎ የአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ።

Ethiopians and Eritreans demonstration against US interference on Ethiopia's internal affairs was held  in front of US Embassy Oslo,Norway
የሰልፉ ሙሉ ቪድዮ፣ ለአሜሪካ ኤምባሲ የገባው ሙሉ ጽሁፍ እና በሰልፉ የተሳተፉ የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ሲቪክ ድርጅቶች ከቪድዮ ስር ያገኛሉ።

ጉዳያችን ሪፖርት /Gudayachn Report

በኦስሎ እና አካባቢዋ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ሰሞኑን አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ እያደረሰች ያለውን በውስጥ ጉዳይ መግባት በመቃወም  ሰላማዊ ሰልፍ  ያደረጉት ዓርብ ግንቦት 20/2013 ዓም ነበር።በሰልፉ ላይ የተገኙት ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ብቻ ሳይሆን በኤርትራም ሆነ በአፍሪካ ቀንድ ላይ ያላትን ጣልቃ ገብነት አውግዘዋል።በሰልፉ ዝግጅት ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ኮሚንቲ ጨምሮ፣ሌሎች የሲቪክ ድርጅቶችም ተሳትፈዋል።በሰልፉ መሃከልም የሲቪክ ድርጅቶቹ ተወካዮች ወደ አሜሪካ ኤምባሲ በመዝለቅ ደብዳቤያቸውን ሰጥተዋል።በተመሳሳይ በሌሎች ሀገሮች የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም የተቃውሞ ሰልፍ በሚገኙባቸው ሀገሮች ባሉ የአሜሪካ ኤምባሲዎች እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

የሰልፉን ሙሉ ቪድዮ እና ለአሜሪካ ኤምባሲ የተላከውን ደብዳቤ ከስር ይመልከቱ።




በኦስሎ፣ኖርዌይ ለሚገኘው ለአሜሪካ ኤምባሲ የገባው ደብዳቤ ሙሉ ይዘት


28. May 2021



Richard H Riley

The charge d'affaires ad interim

The embassy of the United states in Norway

Morgedalsvegen 36

0378 Oslo

Subject: Protesting ill-informed and ill-intended US senate Resolution (S.Res 97) on Ethiopia and

Eritrea

We, the undersigned Ethiopian and Eritrean organizations in Norway in conjunction with similar initiatives in many other European countries and US states, are writing this letter to the US embassy and representation in Norway protesting the US senate resolution 97 on Ethiopia and Eritrea. We write to express our disappointment over the recent and drastic US policy shift towards the region of Horn of Africa. We warn the shift may endanger damaging more than a century old fraternity and friendship between our countries and peoples. We would also like to remind the shift pause enormous humanitarian and political impact to our countries with consequences for the US interest in the region and beyond. Furthermore, the US induced economic and political crisis in the Horn of Africa will eventually lead to major security threats and destabilization for the larger regions of Africa, the Middle East and Europe.

Ethiopia and Eritrea are confronted with a multi-pronged covert and overt campaign by some of its partners exerting undue pressure on the government by levelling prejudiced and gratuitous accusations against it. We are deeply troubled by the continuous unfounded allegations and unwarranted pressure by members of the international community spearheaded by the EU and the USA. It is becoming questionable whether some have a genuine interest to understand the situation and assist our countries in dealing with the challenges. All of the public pronouncements of the State department and US representative at the UN, for example, indicates that it is working relentlessly to frustrate the reform agenda and undermine confidence in the coming elections in Ethiopia.

For several years, there has been and continues to be, relentless and unsubstantiated accusations against Eritrea, for acts of destabilisation and discord in the Horn of Africa. One of the clearly deceptive accusations, was the concocted allegation levelled against Eritrea, by TPLF backed by the US administration and western media. This put the country under unjust and illegal sanctions in 2009. Now it seems the same actors are aiming for history to repeat itself with similar accusations, which is now driving a dangerously misguided international response towards Eritrea, Ethiopia, and the broader Horn of Africa region.

We  would like to draw your attention to the following points:

  1. The government of Ethiopia was forced into a law enforcement operation in Tigray region in response to a large-scale treasonous military attack by the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) on the largest military division based in that region. It is a measure that any sovereign nation would have taken against such a heinous domestic threat. The government is currently providing the majority of humanitarian assistance to support those affected by the conflict. It is also working constructively with international humanitarian aid agencies by providing unhindered access to all parts of the region. However, the USA has been consistently undermining the efforts of Ethiopian government by repeatedly demanding access irrespective of the improved situation on the ground. It is simply not the real problem of the aid agencies in the region. The civilians affected by this conflict would rather benefit from increased capacity and resources to improve the relief efforts.

  2. Ethiopia is also taking all the necessary steps to investigate alleged human rights abuses and associated crimes and bring the perpetrators to justice. The recent announcement by the Federal Attorney General on the matter is part of this commitment. The Ethiopian Human Rights Commission and the UN Office of the High Commissioner for Human Rights are also working on the process of joint investigation. Therefore, the government is fully committed to applying the full force of the law and serve justice.

  3. Ethiopians are determined to build an inclusive and fair system of governance. One of the pillars of democracy is the holding of regular national elections. The country is working to organize the 6th national elections in such uncertain and difficult circumstances. The elections will no doubt fall short of democratic expectations in some respects but they will mark a decisive turn in the process of democratization. It is hoped that they will allow the people to freely exercise their democratic rights and contribute to building a strong, representative government with a more inclusive power structure. Thus, we believe that the decision by the EU not to observe the upcoming elections is unreasonable and completely misguided. It is in the EU's interest to support the reform efforts by the Government of Ethiopia including institutional capacity building for the sustainable process of democratization.

  4. The Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) is a non-consumptive hydroelectric dam being built on the river Nile inside Ethiopian territory with 100 percent local financing. GERD, once completed, provides much needed electric power to more than 60% of Ethiopians, who are currently off grid, to extricate themselves from poverty, accelerate the country’s sustainable development and mitigate environmental degradation. The electric power generated at GERD has tangible economic benefits for neighbouring nations as well, thereby fostering regional integration. Because the Nile is a transboundary water resource, Ethiopia strongly believes that its use shall be based on the principles of equitable and reasonable utilization and causing no significant harm to downstream riparian countries. As such Ethiopia, Egypt and Sudan have already agreed that the GERD will be filled in stages that last for 4-7 years. And the second stage filling of the dam is scheduled for the upcoming rainy season and the downstream countries have already indicated that it will not impact their interests. Therefore, it is difficult to understand why the filling of the GERD suddenly becomes a source of coercion that is being deployed by some in the international community.

We believe that Ethiopia is momentarily distressed but the citizens remain confident that elections will be held in due time, the GERD will soon be filled and the law and order will be restored in Tigray and other parts of the country. Moreover, all those who have committed human rights abuses in the country will be held accountable and be brought to justice.

The Eritrean and Ethiopian communities in Norway are dismayed by the content and language of the US senate resolution and the announcement of Visa restrictions and other punitive measures by the Secretary of state . The crisis in Tigray Region of Ethiopia unfolded solely due to the dangerous acts of military insurrection that the now defunct TPLF group launched on 4th November 2020. The TPLF’s military plot was not confined to Ethiopia but also included Eritrea as a target, by launching several missiles to Asmara and other populated areas. TPLF’s reckless act had endangered the lives of innocent people both in Ethiopia and Eritrea. To gloss over these facts and point an accusing finger on Eritrea defies logic and is unwarranted by any standards. Furthermore, the timing of the announcement – made on the eve of Eritrea’s Independence Day – exceeds minimal bounds of civility and decency. And irrespective of their actual implications, the announced measures cannot promote legality as well as regional peace and security.

In conclusion, as citizens of two independent nations, there is no dearer term for Ethiopians and Eritreans than independence. Freedom from dictation by a foreign power, respect for their sovereignty and non-interference in domestic affairs remain our creed. While all international support based on mutual respect is highly valued, they need to be based on principles of fairness and the utmost regards for the sovereignty of nations.

Therefore, we request the USA senate and government to revise the ill-informed and ill-intended policy shift we are witnessing. Besides we call on all peace-loving nations and international organizations to:

  1. Refrain from putting undue pressure on the government of Ethiopia, via irresponsible pronouncements and to desist from providing any dictates on and interference with its internal affairs

  2. Act on changing facts on the ground rather than operating on arbitrary demands and on the basis of misinformation.

Sincerely

Ethiopian Community and Civic organizations in Norway:

  1. The Defend Ethiopia EU/Norway. Kassahun G. Degena,; Kassuahun@gmail.com

  2. Sammen for Etiopia, Tesfaye Korfil, Tlf +4791516954, tesfaye_korfil@yahoo.com

  3. Den Etiopisk forening i Norge.  Email ethionor1@gmail.com Tlf   970 02 935

  4. Ethiopian Norwegian Professional Organization (ENPO), Email: ethionorway@e-npn.org

  5. Ethiopian Common Forum in Norway.  Email ethiopiancommonforum@gmil.com

  6. Mother of the Generation for peace and reconciliation. sewajoha@gmail.com

  7. Ethiopian Advocacy Norway. ethiopianadvocacynorway21@gmail.com

Eritrean Communities in Norway:

  1. Den eritreiske forening i Oslo

  2. Den eritreiske kvinneforening i Norge

  3. Den eritreiske forening i Rogaland

  4. Den eritreiske forening i Hordaland/Vestland

  5. Den eritreiske forening i Midt Norge

Represented by:

  • Samson Yared, samson.yared24@gmail.com

  • Elias Elefe, elias_elefe@outlook.com

  • Samson Gebreamlak, samsongebreamlak@gmail.com

Friday, May 28, 2021

The current US Government’s attempt to interrupt the democratic process of Ethiopia is the typical indicator of the failure of President Joe Biden and his team's foreign policy on Africa.

Prime Minister Abiy Ahmed (PhD)


  • US foreign policy on Africa is in a huge crise


By Getachew Bekele Damtew

Gudayachn Editor

======================

The Paradox


It is the paradox that to see Ethiopian National Army is fighting terrorism in Somalia to save the Horn from an immediate security danger and on the contrary, the current US Government is working to interrupt the democratic process of Ethiopia.Ethiopia is one of the most ancient lands in the whole world. It is the oldest independent country which has never been colonized by any foreign power. For the past century and even before the country was a proud land not only for the black world but for the South American and even far east people. In the history of fighting with colonialism, Ethiopian patriots' golden victory over colonialists at the battle of Adwa was a great bell ring to millions of people who had been under miserable operation by colonialists.For the liberation of many African countries including for the faildown of Apartheid in South Africa, Ethiopians continuous struggle against colonialism was special power.


For the last three decades, Ethiopia was ruled by ethnocentric ideology of Tigray People Liberation Front (TPLF).TPLF came from the minority (6%) region of Tigray. Its ethnic policy had never been accepted by Ethiopians for the last three decades. There were a number of crimes committed by TPLF. Thousands were killed,torched and became refugees all over the world. The Gambella Massacre, Hawassa Massacre and the recent Maykadra genocides are among many crimes on humanity committed by TPLF. In all these three decades, the US Government was supporting TPLF both Financially  and militarily. However, the US has never been seen to impose TPLF for its crimes made on humanity. 


The Reform and Democratic process


On February 15,2018 Ethiopian Prime Minister, Hailemariam Desalegn resigned due to consecutive popular protest against TPLF and its annex, Ethiopian Peoples Revolutionary Democratic Front (EPRDF). Hailemariam's plan was to end the political crisis through bringing the necessary Political, Economical and Social changes. As the result, the current dynamic and well educated Prime Minister of Ethiopia, Abiy Ahmed could be his successor after being elected by the Ethiopian Parlama. 


After Abiy Ahmed (PhD) inauguration,April 2018, a dramatic change has been seen in Ethiopia. All political prisoners were released,including Andargachew Tsige who had been hijacked by TPLF from Yemen, policy shifts,freedom of expression, and improving relations with Eritrea were some measures that Abiy took as soon as he started the highest job in the country. However, in all these reforms, TPLF was preparing itself for new fighting against the Federal Government.The Federal Government and a number of civic and religious organizations were also on reputative attempt to cool down the TPLF leaders. These attempts were open to the public even the National Television station was transmitting when elders demanded the former TPLF chairperson, Debretsion. Infact, Debretsion was officially undermining the civic organizations and religious leaders by not giving the necessary attention.


The first week of November,2020 was a black week for Ethiopia. TPLF leaders ordered their militia to attack Ethiopian National Army in over 10 fronts. On the same night Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed ordered the army to protect and confirm law and order in Tigray region in Ethiopia. The two years' preparation of TPLF to attack the Federal army was fully destroyed by the National army within almost three weeks. Almost over 95% of TPLF leadership and army has been bitten and became out of service. That means there is no more TPLF at this time.



President Joe Biden's failed Foreign Policy on Africa 


The suicide of TPLF, which was initiated by its attack Ethiopian National Army, opens a new democratic way to Ethiopia. Infact before TPLF was destroyed, Ethiopia was taking the necessary measures to implement key democratic processes. Election was one of the main plans that the Federal Government runs and postponed to the coming June,2021 due to Covid-19.


The current US Government paradox is here. United State main face is well known by talking a lot about the necessity of democracy and anti-terrorism. These are the two main pillars of the US Government's Foreign policy and strategic relationships. Ethiopia, particularly after the 2018 reforms, could fulfill the two important pillars of the US foreign Policy. Regarding democratic process, the country is preparing the best election in the whole history of Ethiopia. The Independent Election Board is on duty, different opposition political parties are introducing their programs and plans on over 20 Televisions throughout the country and Millions of Ethiopians have already registered and are waiting for the election day which is remaining less than four weeks.


On the other hand, Ethiopia is fighting terrorism both in land and abroad. Ethiopian army is the backbone of African Union Mission to Somalia (AMISOM). Recently, in this very week of May,2021 Ethiopian army was the sole performer to push Al shabab from four key towns in Somalia. The AMISOM leaders were so proud of the Ethiopian army's recent effective offensive work. Because these key towns were occupied for a long period of time by Al Shabab. Even Though, Ethiopia is performing at higher level to fight terrorism, the current US Government is threatening her to impose sanctions. President Joe Biden’s speech this week was nothing but threatening Ethiopia in the name of humanity in the Tigray region. In the Tigray region, humanitarian crises were there even when TPLF was administering the region. Over 2.5 million people were under the food saftinet program for the last two decades. This was due to the TPLF corruption and mismanagement. Because the role of the Federal Government in Tigray regions administration,particularly for the last three years, was almost nil.


In general, US foreign policy on Africa is in a huge crise. The main actor and formulator, Susan Elizabeth Rice and the team of President Joe Biden are losing their orbit towards Africa. Their policy formulation is hijacked by lobbyists and fake news producers of the Pro-TPLF institutions. These institutions are fueled financially with the looted money from Ethiopian people. It is a matter of time that everything will be exposed. However President Joe Biden and his team’s standing to affect Ethiopian democratic process and fighting against terrorism must not be taken as a simple issue. Because they are spoiling over 125 years of diplomatic and strategic relationships with the ancient land of Africa, that is Ethiopia.

==================///==============

Wednesday, May 26, 2021

በዘመናችን አባቶቻችንን ከስደት መልሰህ በአንድ ጉባኤ ሲቀመጡ እንድናይ ያደረክ አምላክ ተመስገን!የኃላውን ስለምንረሳ ባለማመስገናችንም ይቅር በለን!

ግነዩ ለእግዚአብሔር (መዝሙር ቪድዮ)  

ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Saturday, May 22, 2021

ከትግራይ፣መተከል፣ሰሜን ሸዋ እና ምዕራብ ወለጋ ለተፈናቀለው ሕዝብ ለመድረስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስቲያን በፍጥነት ልትሰራቸው የምትችላቸው አምስት ስራዎች አሉ

ጉዳያችን/Gudayachn

የትግራይ ሕዝብ ህወሓት ለአርባ ዓመታት ካሰቃየው በኃላም ዛሬም የተረፈው ቡድን እየተሹለከለከ ገበሬውን እየገደለ።ንብረቱን እየቀማው ነው።በመሆኑም ጥቂት ቅምጥሎች በስሙ የኖሩትን ሕይወት እየሰማ ዛሬም መልሶ ችግር ላይ መውደቁ ከተሰማ ሰንብቷል።በእርግጥ ከሕግ ማስከበሩ ሥራ ተከትሎ የፌድራል መንግስት ከ40 ቢልዮን ብር በላይ ወጪ አድርጎ የሰብአዊ ድጋፍ እና መልሶ ለማቆም ጥረት ማድረጉን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ዛሬ ግንቦት 14/2013 ዓም በቦሌ ክፍለ ከተማ ከሚኖሩ የክልሉ ነዋሪዎች ጋር ባደረገው ውይይት ላይ መገለጡን የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በዜና ሰዓት ላይ አቅርቧል። ከእዚሁ ባለፈ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ፣ የክልል አመራሮች፣የአማራ እና የትግራይ ክልል አመራሮች እና ባለሀብቶች  በተገኙበት ሕዝቡን መልሶ ወደ ቀዬው ለመመለስ እና በአማራ እና የትግራይ ክልል መሃል የህዝብ ለሕዝብ ማቀራረብ ስራዎችን የሚሰሩ የሀገር ሽማግሌዎች ያሉበት 14 አባላት ያሉት ሀገር አቀፍ ኮሚቴ ተመስርቷል።

በሌላ በኩል በትግራይ የሲቪሎች መገደል በተመለከተ የአቃቢ ሕግ የራሱን ማጣራት አድርጎ 110 ሲቪሎች መገደላቸውን ማጣራቱን ገልጧል።ግድያው በኤርትራ ወታደሮች መፈፀሙን ይገልጣል።ይህ በእንዲህ እያለ በትግራይ የተፈፀሙት የመደፈር ወንጀሎችም መፈፀማቸውን በሰብዓዊ መብት ድርጅቶችም ሆነ በራሱ በመንግስት ማጣራት ተገልጧል።በእዚህ መሰረት ከኢትዮጵያ ወታደሮች በእዚህ ተግባር ተሰማርተው ነበር የተባሉትን መንግስት አጣርቶ ክስ የመሰረተባቸው እንዳሉ ተገልጧል።

ከመተከል፣ሰሜን ሸዋ እና ከምዕራብ ወለጋ የተፈናቀሉ የአማራ ተወላጆችም ችግር ቀላል የሚባል አይደለም።በቅርቡ የአማራ ክልል እንደገለጠው ከግማሽ ሚልዮን በላይ ሕዝብ መፈናቀሉን ማስታወቁ ይታወቃል።ይህ ሁሉ ሕዝብም በቶሎ ወደ ተፈናቀለበት ቦታ መመለስ አለበት።ምክንያቱም አንገብጋቢው ጉዳይ ህዝቡ ዕለታዊ እርዳታ በቶሎ አግኝቶ ከመጪው ሰኔ አጋማሽ በፊት የእርሻ ስራውን እንዲጀምር የማድረጉ ሥራ ነው።ለእዚህ የተቀደሰ ተግባር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከሁሉ ቀድማ ልትሰራው የሚገቡ አምስት ተግባራት አሉ። ከሁሉም ቦታ የተፈናቀለው  ሕዝብ ወደ ቀዬው እንዳይመለስ ደባ እየሰሩ ካሉት ውስጥ የህወሓት ደጋፊዎች በዋሻ እና በውጭ ያሉት ሁሉ ናቸው።ምክንያቱም ህዝቡ ከቤቱ ከተበተነ ለነገ ግጭት ሊጠቀሙበት ይፈልጋሉና ነው።

አሁን የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ልትሰራቸው የሚገቡ አምስት ተግባራት አሉ። እነርሱም -

1)  በኢትዮጵያም ሆነ በውጪ ሀገር የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አጥብያዎች እና ገዳማት በሙሉ በሁለት ሰንበት የሚሰበሰበው ገንዘብ በሙሉ ለተፈናቀሉት ወገኖች እንዲሆን መወሰን እና ወደ ተግባር መግባት፣

2) በሁለት ሰንበታት ከሁሉም አጥብያዎች እና ገዳማት የሚሰበሰብ ቁሳቁስ እና አልባሳት ማሰባሰብ 

3) ይህንን የሚያስተባብሩ ከብክነት የሚጠብቁ እና እርዳታው ወደተፈናቃዮች እስከሚደርስ የሚያስተባብሩ በብሔራዊ ደረጃ መምረጥ እና ማስተዋወቅ፣

4) የእርዳታው አሰባሰብ እና አሰጣጥ ሪፖርት በሚገባ ለሕዝብ ግልጥ ማድረግ እና 

5) በውጭ የሚኖሩ ምእመናኖቿ የሚሳተፉበት በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የሚተላለፍ  የአንድ ምሽት የቀጥታ ጎፈንድሚ እና የገንዘብ ማሰባሰብያ ዝግጅት ማድረግ እና በዝግጅቱ ላይ ሊቃነ ጳጳሳት፣ሰባክያን እና መዘምራን  እንዲሳተፉ በማድረግ ከሚልንየም አዳራሽ ማስተላለፍ የሚሉት ናቸው።

እነኝህን የዕርዳታ ስራዎች ቤተክርስቲያን በቶሎ እንድትሰራቸው ግፊት ማድረግ የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ግዴታ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን ከብዙ አቅጣጫ እጅግ መፍጠን አለባት።
 ********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Thursday, May 20, 2021

ይህ ትውልድ ከአባቶቹ የተረከበውን የኢትዮጵያን ነፃነት ዳግም የሚያረጋግጥበት ተራው ደርሷል።ለኢትዮጵያ ነፃነት የቆመ ሁሉ ጠ/ሚ/ር ዓቢይን ከጎንህ ነን ማለት አለበት!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

>> ያለንበት ዘመን የዛሬ አንድ መቶ ዓመት የነበርንበት የንግሥት ዘውዲቱ ዘመንን ይመስላል።

ጉዳያችን/Gudayachn

ባለፈው የጉዳያችን ፅሁፍ ላይ የሩስያ ባሕር ኃይል ከሱዳን ጋር ያደረገው ውል በአሜሪካ ከፈረሰ በኃላ ጉዳዩ በኢትዮጵያ አንፃር የአሜሪካንን በትግራይ አሳባ የምታደርገው ተፅኖ ችግር ላይ እንደሚወድቅ አብራርታ ነበር።ኢትዮጵያ በዓለማችን ላይ ካሉት በከርሰ ምድሯ ውስጥ በያዘችው የተፈጥሮ ሀብትም ሆነ በምትገኝበት ስልታዊ አቀማመጥ ለዘመናት ሀገሪቱን ለመቆጣጠር በየዘመኑ የተነሱት ኃያላን ያልሞከሩበት ጊዜ የለም።ባለፉት ሁለት ወራትም በኢትዮጵያ ላይ ዓለም አቀፍ የመሸበቢያ ገመድ ለመሸምቀቅ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤትን ለመጠምዘዝ በአሜሪካ፣እንግሊዝ እና ፈረንሳይ የተደረገው ሙከራ በሩስያ እና ቻይና አለመስማማት ሳብያ ከከሸፈ በኃላ አሜሪካ ዛሬ በሴኔቷ አማካይነት ውሳኔ አሳልፋለች።ውሳኔው በትግራይ የተደረገውን የሕግ ማስከበር ሂደት አስታኮ ይወስን እንጂ የአሜሪካ ዋና ምክንያት የአፍሪካ ቀንድ ላይ በህወሓት እጅ በኩል የነበራት ተፅኖ ሽባ እየሆነ በመምጣቱ ነው።በተለይ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መሃል የተፈጠረው ድንገተኛ እርቅ የአፍሪካ ቀንድን ፖለቲካዊ፣ምጣኔ ሃብታዊ እና ወታደራዊ ቅርፅ በእጅጉ እንደሚቀይረው ግልጥ ሆኗል።

አሜሪካ እና ግብረ አበሮቿ አፍሪካን ካልከፋፈሉ ወይንም በዓይናቸው ስር በሚገኝ ህብረት ውስጥ ካልሆኑ ለጥቅማቸው አደጋ እንደተጋረጠበት ያምናሉ።በመሆኑም በቀላሉ በአቶ መለስ በኩል ይዘውሩት የነበረው የኢጋድ (የምስራቅ አፍሪካ በየነ መንግሥታት ድርጅት) ችላ ብለው የኢትዮጵያ፣ኤርትራ እና ሱማልያ አዲስ የትብብር እና የምጣኔ ሀብት ትብብር ሃሳብ ማንቀሳቀሳቸው እና በተለይ ከኤርትራ ጋር ያለው ትብብር ህወሓትን የማስወገድ የጋራ ወታደራዊ ትብብር ድረስ ተሻግሮ መሄዱ ጉዳዩ የሁለቱ ሀገሮች ግንባር መፍጠር ብቻ የአንድ ሺህ ኪሎሜትር ድንበር ከአፍሪካ ቀንድ ጋር የምዋሰነው እና መካከለኛ እና ሩቅ ምሥራቅን ከአውሮፓ ጋር የሚያገናኘው የቀይባህር በኢትዮጵያ እና ኤርትራ የጋራ ትብብር የማንም የውጭ ኃይል ወፍ ዝር እንዳይል የሚያደርግ ስለሆነ አሜሪካ እና አጋሮቿ ብርክ ይዟቸዋል።ስለሆነም ይህ ከሚሆን ኢትዮጵያ ብትበታተን የሚመርጡ መሆናቸውን በሰሞኑ ድርጊታቸው መረዳት ይቻላል። 

አሁን ምክንያት የምንደረደርበት ወይንም ቅሌን ጨርቄን የሚባልበት ጊዜ አይደለም።ኢትዮጵያ በየዘመኑ የተነሱ ኃያላን ሊያንበረክኩ ሞክረዋል።አሁንም ምንም ዓይነት ቅርፅ ብንሰጠው የባዕዳኑ ፍላጎት አንድ እና አንድ ነው።የተንበረከከች፣እንደፈለጉ ተነሽ እና ተቀመጭ የሚሏት ኢትዮጵያን ማየት ነው።በእዚህም በዋናነት አሁን ኢትዮጵያን ያለውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይን ማገዝ ይጠበቅበታል።አሁን ያለንበት ጊዜ የንግሥት ዘውዲቱ ዘመንን ይመስላል።ከሰገሌ ጦርነት በኃላ የካቲት 4፣1909 ዓም በዕለተ እሁድ አባታቸው ዳግማዊ አፄ ምንሊክ ባሰሩት በአዲስ አበባ በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በአቡነ ማቴዎስ እጅ ተቀብተው ነገሱ።በንግሳቸው ላይ የኢትዮጵያ አዋሳኝ የሆኑት የያኔዎቹ ቅኝ ገዢዎች የእንግሊዝ ሱዳንና የእንግሊዝ ሱማሌ ገዢዎች እንዲሁም የፈረንሳይ የያኔዋ አፋርና ኢሣ ገዢ እንዲሁም በኢትዮያ የሚገኙ ራሶች እና የየአውራጃ ገዢዎች ሁሉ በተገኙበት ነበር።በመቀጠለም በንግስ ስርዓቱ መሰረት በወቅቱ የደጃዝማችነት ማዕረግ የነበራቸው ተፈሪ (በኃላ አፄ ኃይለስላሴ) ራስ ተብለው አልጋወራሽና ባለሙሉ ስልጣን እንደራሴ መሆናቸው በአዋጅ ተነገረ።

ወቅቱ የአንደኛው ዓለም ጦርነት በዓለም የተፋፋመበት፣የባዕዳን ኃይሎች የኢትዮጵያን መሬት በተለይ ከአፄ ምንሊክ እረፍት በኃላ ኢትዮጵያ ትከፋፈላለች ብለው የሚጠብቁበት እና በውስጥ ለመከፋፈል ከፍተኛ ሙከራ የሚያደርጉበት ወቅት ነበር።ይህ በእንዲህ እያለ ዘመናዊ ትምህርት በመጠኑ የቀመሱ ወጣት ኢትዮጵያውያን በንግሥት ዘውዲቱ እና በዙርያቸው ባሉ የአፄ ምንሊክ ያህል በተፈጥሮ ያልሆኑ እና የወቅቱን የዓለም አቀፍ ሁኔታ የማይረዱ ቤተመንግስት መግባታቸው ስጋት ፈጥሮባቸዋል።ይህንን ሁኔታ ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ወቅቱን አስመልክተው ራሳቸው በፃፉት ''ሕይወቴ እና የኢትዮጵያ ርምጃ'' በተሰኘው መፅሐፋቸው ገልጠውታል።የያኔው ራስ ተፈሪ የኃላው አፄ ኃይለስላሴ ግን አርፈው አልተቀመጡም።ይልቁንም አውሮፓ ድረስ ሄደው የውጭው ዓለም ፖለቲካ ተገነዘቡ።ኢትዮጵያ በዓለም ማኅበር (ሊግ ኦፍ ኔሽን) አባል መሆኗ ላይ በወቅቱ ከነበሩት ከነቁት ጋር አብረው ሰሩ። ከንግስት ዘውዲቱ ንግሥ በኃላ የተነሳው ውስጣዊ ሹክቻ በሁለት የተከፈለ እንደነበር ይሄው የቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ  መፅሐፍ ያብራራል።አከፋፈሉ የንግሥት ዘውዲቱ እና የፊውዳል ወግ አጥባቂው እና ትምህርት ቀመስ የሆነው ኢትዮጵያን ወደ ዘመናዊ መንገድ ማስገባት ይገባል ለእዚህም ዓይነተኛ ሰው ራስ ተፈሪ ናቸው የሚሉት ነበሩ።
 
ዛሬም ኢትዮጵያ በአማራ፣በትግራይ፣በኦሮሞ በሚል የጎሳ ፖለቲካ ለስልጣን መወጣጫ ያልተሳካ ሙከራ የሚያደርጉ የመኖራቸውን ያህል በጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ፣በእዜማ እና በአቶ ኢሳያስም ወገን ጭምር የኢትዮጵያ አንድነት ከጎሳ ፖለቲካ የፀዳ እንዲሆን የሚፍልጉ ናቸው።አንዳንዶች አቶ ኢሳያስን ከእዚህ አስተሳሰብ ሊያወጡ ይሞክራሉ።ለእዚህም ምክንያት የሚያደርጉት የአቶ ኢሳያስን የሴራ ፖለቲካ አድርገው ስለሚያዩት ነው።ሆኖም ግን የአቶ ኢሳያስ ስጋት የጎሳ ፖለቲካ በኢትዮጵያ በቅሎ ኤርትራም እንደማትተርፍ አውቀዋል።ሌላው ዘግይተውም ቢሆን የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ዕድል አንድ መሆኑን በሠላሳ ዓመታት ተሞክሮ ስለገባቸው መሆኑን መረዳቱ ተገቢ ነው።

ኩሩው ጠቅላይ ሚኒስትር 

ኢትዮጵያ በአሁኑ የአሜሪካም ሆነ ግብረአበሮቿ ተግባር አንፃር መቆም ያለባት ከአንድነቱ ጎራ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ጎን ነው።በችግር ጊዜ ያውም ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይን የመሰለ ኩሩ መሪ ተገኝቶ የባሰ መጥፎ መሪም ቢሆን በኅብረት አብሮ መቆም የግድ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ወደ ስልጣን ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያዊነት ኩሩ የነፃነት መንፈስን በሚገባ አንፀባርቀዋል።ሌ/ኮ/ል ዶ/ር ዓቢይ ወደ አሜሪካ ባደረጉት የመጀመርያ ጉዞ ላይ ዋይት ሃውስ ጎራ ብዬ  ፕሬዝዳንት ትራምፕን ላናግር ብለው ደጅ አልጠኑም።ሕዝባቸውን አናግረው የተሰደዱትን ቅዱስ ፓትርያሪክ አቡነ መርቆርዮስን ይዘው ወደሀገራቸው ገቡ።ይህ ብቻ አይደለም የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ውሃ በቀጠነ እያለች ስትነጫነጭ ልዩ ልዑክ እየላኩ አሜሪካኖች ያስረዱናል ብለው ሲጠብቁ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስራቸውን ብቻ ይሰሩ ነበር።በኃላ ቢቸግራቸው ራሳቸው ፕሬዝዳንት ባይደን ልዩ ልዑክ ወደ አዲስ አበባ ሁለት ጊዜ ልከው የኢትዮጵያን አስተሳሰብ ሊያስቀይሩ ሞከሩ።ይህም አልተቻለም።በመሆኑም ግራ የተጋቡት አሜሪካኖች ወደ ምክር ቤታቸው ሄደው በሐሰት የሚድያ ዘመቻ ወደ ሰከረው ምክር ቤት ሄደው ውሳኔ አሳለፉ።ይህ ሁሉ ግርግር ማዕከላዊ መንግስትን አዳክሞ ደካማ ኢትዮጵያን መፍጠር እና ለአሜሪካ መንግስት የሚታዘዝ የኢትዮጵያን ጥቅም አሳልፎ የሚሰጥ አሻንጉሊት መንግስት ኢትዮጵያ ላይ መመስረት ይህ  ካልሆነ ሀገሪቱን መከፋፈል ነው።ስለሆነም ኢትዮጵያን የሚወድ እና ከማናቸው የባንዳ አስተሳሰብ የጠራ ሁሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይን ከጎናቸው መሆኑን የሚገልጥበት እና ለኢትዮጵያ ነፃነት እና አንድነት በኅብረት የሚቆምበት ወሳኝ ጊዜ ነው።


 ********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Friday, May 14, 2021

ማኅበረ ቅዱሳንንም ኢሳትንም ለሚያውቅ ለእኔ የኢሳትን፣የጋዜጠኛ ሲሳይን አስተያይተም ሆነ የማኅበረ ቅዱሳን መግለጫ የምረዳበት ዓውድ።

>> የአቡነ ማትያስን አባትነንትን ማክበር የቤተ ክህነትን የአስተዳደር ብልሹነት እና ወደፊት የሚወሰደውን የማስተካከልን ሥራ ፈፅሞ ሊጋርደው አይገባም።   

(የጉዳያችን ልዩ ጥንቅር) 

በክፉ ጊዜ ለማኅበረ ቅዱሳን የተሟገተው ኢሳት እና  ጋዜጠኛ ሲሳይም ሆነ ማኅበረ ቅዱሳን ሁሉም  የኢትዮጵያ ሕዝብ የተከበሩ ሐብቶች ናቸው። ሁሉም ለሀገራቸው እና ለወገናቸው መልካም ባደረጉ፣የእድሜ ግማሽ ዘመናቸውን ለኢትዮጵያ በወጡ በወረዱ ማንም እንደፈለገ የስም ማጥፋት ዘመቻ ሊያደረግባቸው አይገባም።ሰሞኑን በማኅበራዊ ሚድያ ሶስቱም ላይ የሚፈፀሙት የስም ማጥፋት ዘመቻዎቹ በትክክል ነጥብ በነጥብ ጉዳዩን እያነሱ ከሚሞግቱት ውጪ አጋጣሚውን ተጠቅመው ብስለት የሌላቸው፣ነገር ግን በአጋጣሚው የማኅበረ ቅዱሳንንም፣የኢሳትንም ሆነ የጋዜጠኛ ሲሳይ አጌናን ስም ተገቢ ባልሆነ እና ጨዋነት በጎደለው መልክ በማኅበራዊ ሚድያ የሚያጥላሉ እየተመለከትን እየታዘብን ነው። አንዳንዶቹበሶስቱም ላይ በአመለካከታቸው፣በአሰራራቸው እና በእምነት ጭምር ቀድሞም ሲያጥላሉ የነበሩ ዛሬ በተፈጠሩ ጉዳዮች አስታከው ወደ የለየለት የማጥላላት ዘመቻ ሲገቡ እያየን ነው።ይህ ሊቆም ይገባዋል።በመሃል ነገር የሚያካርሩ እና በአጋጣሚው የግለሰብንም ሆነ የድርጅትን ስም ለማጠልሸት ለሚሯሯጡ ዕድል ሊሰጥ አይገባም።

የሆነው ምንድን ነው? 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምርያ ስር የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን በያዝነው ሳምንት መጀመርያ ላይ መግለጫ አወጣ።መግለጫው ከእዚህ በፊት ማኅበሩ ካወጣቸው መግለጫዎች ጠንከር ያለ መግለጫ ነው።መግለጫው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ስደት ላይ ነች በሚል ርዕስ ሆኖ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ  የደረሰው እና ወደፊት የተጋረጠባት አደጋ የከፋ ነው የሚል ሃሳብ ይዟል።በመግለጫው ይዘት ላይ በእዚሁ ሳምንት አጋማሽ ላይ ለአደባባይ ሚድያ ማብራርያ የሰጡት የማኅበሩ አመራሮች በእዚህ ዓመት የተመረጡ እና ወደ አመራር የመጡ ቢሆኑም ከእዚህ በፊት በማኅበሩ አገልግሎት ላይ ግን ረዘም ያለ ጊዜ እንዳላቸው እና የወጣው መግለጫ ግን በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ካለው ፈተና አንፃር እንድያውም ያነሰ መሆኑን ገልጠው መንግስት በተደጋጋሚ ለደረሱት ጥፋቶች ተገቢውን ምላሽ ክብር ባለው መልክ ለቤተ ክርስቲያኒቱ አለመስጠቱ በራሱ ብዙ ነገር እንደሚያመላክት ገለጡ።

ይህንን መግለጫ ተከትሎ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን በሳምንቱ አጋማሽ ላይ በዕለታዊ ዝግጅቱ ላይ መግለጫው ላይ ትችት አቀረበ። ትችቱ በተለይ ከእዚህ በፊት ቤተ ክርስቲያን በተለይ በዘመነ ህወሓት የነበረችበት የፈተና ዘመንን በሚገባ አያብራራም፣ይልቁንም ይህንን ጉዳይ መንግስት በትኩረት ሊመለከተው የሚገባ ነው የሚል ሃሳብ ጨምሮ በተለይ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና በቅርብ ወደ ማኅበሩ የመጡ አመራሮች የወቅቱን አመራር የማይደግፉ መሆናቸው ነው የሚል ከሆነ ሰው እንደሰማ የሚገልጠውን ሃሳብ ጨምሮ በውይይቱ ላይ አቀረበ።

 የማኅበረ ቅዱሳንን መግለጫ የምረዳበት ዓውድ።

ማኅበረ ቅዱሳንን ከምስረታው ጊዜ ጀምሮ ብቻ ሳይሆን የዩንቨርስቲ ተማሪዎች በብላቴ በዘመቱበት ጊዜ ከዘማቾቹ አንዱ ስለነበርኩ እና ለማኅበሩ መመስረት እንደ አንድ ጥንስስ የሚቆጠረው በብላቴ አየር ወለድ ማሰልጠኛ ኬስፓን ውስጥ ከዘማቾቹ አንዱ ከሆነው ከሙሐዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት እና ሌሎች ወንድሞች የምሽት ትምሕርት ጀምሮ የማኅበሩን ሂደት አውቀዋለሁ።የማኅበሩም አገልግሎት  ከምንም አድርባይነት የፀዳ መሆኑን ፣እዚህ ላይ መጥቀስ የማያስፈልጉ ብዙ ፈተናዎች አባላቱ የተቀበሉበት ከሁሉም በላይ ከብሄር እና ጎሳዊ አስተሳሰብ ፈፅሞ የፀዳ ለመሆኑ ምስክር ነኝ።ሌብነት እና ሙስና በተንሰራፋባት ሀገር በመልካም ዜግነት የታነፁ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አባላት ያፈራ እና ለኢትዮጵያ ዘመናዊ የሲቪልም ሆነ ወታደራዊ ኃይል መልካም እና ታማኝ  ዜጋ በማፍራት ሂደት የራሱን አስተዋፅኦ ያደረገ ማኅበር ነው።

ማኅበረ ቅዱሳን በሩቅ የሚያዩት አንዳንዶች ከቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውጪ አድርገው የሚያስቡ አሉ።ሆኖም ማኅበሩ በቅዱስ ሲኖዶስ መተዳደርያ ደንቡ ተለክቶ እና ተወስኖ የተሰጠው እንዲሁም በቤተ ክርስያንቱ መዋቅር ስር የሚገኝ ከመሆኑም በላይ እያንዳንዱ የአገልግሎቱን ሪፖርት ለቅዱስ ሲኖዶስ  እና በሚገኝበት መዋቅር ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሚያቀርብ የአገልግሎት ማኅበር ነው።

በቅርቡ ማኅበሩ ያወጣው መግለጫ የቤተ ክርስቲያንን ስደት ብሎ የተነሳበት ነጥብ ላለፉት ሃምሳ ዓመታት የግራው ፖለቲካ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ከተቆጣጠረበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑን ነው የገለጠው።ስደት የሚለውን ብዙዎች ከፓትርያሪክ ስደት ጋር ብቻ አያይዘው ቤተክርስቲያን ተሰደደች የሚባለው ከአባቶች ስደት ጋር አያይዘው ግራ የተጋቡ አሉ።ይህ ግን ቤተ ክርስቲያን የሚለውን ትርጉም ከክርስቲያኖች ስብስብ፣ከሕንፃ ቤተ ክርስቲያን እና ከአንድ ክርስቲያን በአምሳለ እግዚአብሔር መፈጠሩን በሶስት ከፍሎ የሚሰጠውን የቤተክርስቲያን ትርጉም ካለመረዳት የሚመጣ ነው።ስለሆነም ስደት ሲባል የክርስቲያኖች ከወለጋ እስከ ባሌ፣ከሻሸመኔ እስከ ሐረር በክርስቲያኖች ላይ የደረሰውን ስደት፣ግድያ እና መከራ ሁሉ ቤተክርስቲያን እያንዳንዱ ሰውነትም ናትና የክርስቲያኖች መሰደድ የቤተ ክርስቲያን ስደት ተብሎ ይጠራል። ይህ ብቻ አይደለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በአደባባይ ከሚያከብሯቸው በዓላት ውስጥ እንደ መስቀል እና ጥምቀት ያሉት በዓላት ባሳለፍነው ሶስት ዓመታት ውስጥ በቢሸፍቱ እና ሆሳዕና ጨምሮ በአንዳንድ ቦታዎች ምዕመናን ማክበር አልቻሉም።

ቅዱስ ፓትርያሪክ አቡነ ማትያስ ማኅበረ ቅዱሳንን ምክንያት በሌላው መንገድ ከመውቀስ አልፈው ፈተና ያመጡበት ጊዜም ነበር።ለእዚህም ማኅበሩ የሰጠውን ምላሽ እንደ አንድ ማሳያ መመልከት ይቻላል።ማኅበሩ በፓትርያሪኩ ተወቅሶ የሰጠውን የጽሁፍ  ምላሽ ይህንን   በመጫን ማንበብ ይችላሉ።ይህም ሆኖ ግን ማኅበሩ ፓትርያሪኩን በመንበራቸው ክብር መከበር እንዳለበት ደጋግሞ ሲናገር ቤተክርስቲያኒቱ ከእዚህ በፊት የቤተ መንግስቱ ፖለቲካ ሲቀያየር ቤተክህነቱ ፓትርያሪክ እንዲቀይር የሚደረገው ሴራ ዛሬ ሊደገም እንደማይገባ በአፅንኦት ከማሳሰብ አንፃር የሚታይ ነው።ይህ ማለት ግን የቤተ ክህነት አስተዳደራዊ አሰራርም ሆነ የሙስና ተግባራት ሁሉ አይስተካከል የሚል እንደማይሆን ነው የሚገባኝ።

በአጠቃላይ ማኅበረ ቅዱሳን በእየለቱ ከመላዋ ኢትዮጵያ ካሉት የአገልግሎት መዋቅሮች ከአዲስ አበባ እስከ ታች ወረዳ ያለው የቤተ ክርስቲያን ፈተና ሪፖርቶች በእየሰዓቱ ለዋናው ማዕከል ይደርሱታል።እነኝህ ሁሉ ሪፖርቶች ብዙዎች አያውቁትም።ዛሬ ባሌ፣ከፋ፣አርሲ እና ሐረር በሚገኙ ወረዳዎች ውስጥ ካህናት ጠምጥመው ገበያ ቢወጡ በድንጋይ የመወገር አደጋ ስላለባቸው ጥምጣማቸውን አውልቀው ከቤታቸው እንደሚወጡ የሚያውቅ ጥቂት ናቸው።ይህ አንዱ የቤተ ክርስቲያን ስደት ማሳያ ነው።ሁኔታው በአፋጣኝ ካልተሻሻለ የሀገሪቱ የፀጥታ ችግር እንዳይሆን ከምርጫው በኃላ የሚመጣው መንግስት ብዙ ሥራ ይጠብቀዋል።

በክፉ ጊዜ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንም ሆነ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ስር ለሚገኘው ለማኅበረ ቅዱሳን የሞገተው ኢሳትንም ሆነ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌናን በተመለከተ የተረዳሁበት አውድ 

የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን ዛሬ አንዳንዶች ከፖለቲካ አስተሳሰብ እና ከገቡበት የዘውግ ፖለቲካ አንፃር በተለይ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ ሊያጥላሉት ቢሞክሩም፣ኢሳት ላለፉት አስር ዓመታት በኢትዮጵያ ላይ ተንሰራፍቶ የነበረውን የህወሓት/ኢህአዴግ የጭቆና ስርዓት በግንባር ቀደምትነት በመዋጋት ስሙ ከሚጠሩት ውስጥ ነው።እሳትንም ቀረብ ብዬ እንደመመልከቴ  ሰሞኑን አንዳንዶች ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር እያያዙ እንደሚነቅፉት ፈፅሞ አይደለም።ባለፉት አስር ዓመታት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በስሯ የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን ላይ በስርዓቱ እና በቤተ ክህነት ውስጥ በተሰገሰጉ የህወሓት አቀንቃኞች የሚነሱ አቧራዎች ሁሉ ኢሳት ለሕዝብ በማጋለጥ ግንባር ቀደም እንደነበር ምስክር ነኝ።የኢሳት ጋዜጠኞች ሲሳይ አጌናም ሆነ መሣይ መኮንን በማኅበረ ቅዱሳን ላይ እየደረሱ የነበሩትን ቅሰጣዎች ሁሉ እራሱን የቻለ መርሃግብር እያዘጋጁ ለሕዝብ በራድዮ እና በቴሌቭዥን እንዲተላለፍ አድርገዋል።መሳይ መኮንን ማኅበረ ቅዱሳንን አስመልክቶ ባደረጋቸው ወደ ሶስት ጊዜ የሚሆኑ የዜና ዝግጅቶች ላይ እራሴንም ጋብዞኝ በማኅበሩ ላይ እየደረሱ የነበሩ ፈተናዎች በተመለከተ እንድናገር ዕድል ሰጥቶኝ በወቅቱ በራድዮ እና ቴሌቭዥን ፕሮግራሞች ላይ ቀርበዋል (ከእዚህ ፅሁፍ በታች የኢሳትን ማኅበሩ ላይ እየደረሰ ያለውን ፈተና ለሕዝብ ያሰማበት  ልዩ ዝግጅት በቪድዮ ያገኛሉ)።

ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌናም በተለያዩ የዕለታዊ ዝግጅቶች ላይ በማኅበሩ ላይ እየደረሱ የነበሩትን ፈተናዎች ከማቅረቡም በላይ በአንድ ወቅት ራሱን የቻለ ልዩ ዝግጅት አቅርቦ ነበር።አንዳንዶች በወቅቱ ምናልባት ኢሳትን በሚገባ ሳይከታተሉ ዛሬ በአንድ ፕሮግራም በኢሳት ላይም ሆነ በጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ላይ እጅግ ነውረኛ የሆነ የስም ማጥፋት ቃላት ሲጠቀሙ ስመለከት በጣም ያሳዝነኛል። ይህ የሚመለከተው በአግባቡ ሃሳባቸውን የገለጡትን ሳይሆን በማኅበራዊ ሚድያ በወረደ መልኩ ስም ለማጥፋት የሚሞክሩትን ነውረኞች ነው። 

 ሰሞኑን በተደረገው የኢሳት ዕለታዊ ላይ በተለይ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና በማኅበረ ቅዱሳን መግለጫ ላይ የሰጠው አስተያየት በእርግጥ መታረም ያለባቸው ቃላት ቢኖሩበትም መነሻው ብዬ የምረዳው ግን ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት እጅግ ወሳኝ ጊዜ እና   በተለያየ አካላት በተከታታይ ከሚታዩት ሃገራዊ ሴራዎች አንፃር በማኅበሩ መግለጫም ለሀገር ከመጨነቅ አንፃር እረብሾታል።እርሱ የተሰማው ስሜት ደግሞ ማንም ሃገሩን የሚወድ ሰው የሚሰማው ስሜት ነው።ስለሆነም ስሜቱን በነካው መጠን ከሚገባው በላይ ድምፀቱን አክብዶታል።ይህ ማለት በማብራርያው ላይ መታረም ያሉባቸው አንዳንድ  አገላለጦች እንዳሉ ሆነው አንዳንዶች በነውረኛ አቀራረብ በጋዜጠኛው ላይ እና በኢሳት ላይ እንደሚሉት ግን ፈፅሞ አይደለም። 

ባጠቃላይ ግን ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ከእድሜው ከ1/4ኛ በላይ በኢትዮጵያ ጉዳይ የፃፈ፣የታሰረ፣የኢትዮጵያ ጉዳይ የሚያስጨንቀው እና ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሁሉም ዕምነቶች እኩል አክብሮት ያለው ወደፊትም የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያከብረው ጋዜጠኛ ነው። በመሆኑም አንዳንዶች ሰሞኑን በወረደ መልኩ ሊገልጡት እንደሚሞክሩት ያለ ግለሰብ አይደለም። አንድ በእኛ ማኅበረሰብ ውስጥ የተለመደ ክፉ ልማድ፣ አንድ ሰው አንድ ቀን የተሳሳተ ነገር የተናገረ ጊዜ የምናወርድበት ውርጅብኝ እና ለሀገር ስንት አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የተከበሩ የሀገር ሃብቶችን አጥላልተን የምንጥልበት መጠን የከፋ ነው።ይህ ኢትዮጵያን ሰው እንዳይወጣላት ያደረገ አጨንጋፊ ክፉ ልማድ ነው።በተለይ ማኅበራዊ ሚድያ ከመጣ በኃላ ስም እየቀየሩ መፃፍ እና ግለሰቦችንም ሆነ ድርጅቶችን ማብጠልጠል የተለመደ እኩይ ሥራ ነው። 


የመጨረሻው መጨረሻ ግን አንድ ነገር ሳልል ማጠቃለል የለብኝም።ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ማክበር የነቀዘውን የቤተ ክህነት የሙስና አሰራሮችን ማስተካከል እና ሙሰኞችን ከመንቀል ጋር ሊጋጭብን አይገባም።ቤተክህነት አሰራሩን ዘመናዊ ማድረግ አለበት። ሙሰኞች እና በቤተክህነቱ ውስጥ ተጠልለው ለዓመታት ወንጀል የሰሩ ገለል ማለት አለባቸው።
 ይህንን ብንስማማም ባንስማማም እግዚአብሔር የቆረጠበት ቀንን ማንም አይቀይረውም።ክርስቶስ በቤተ መቅደሱ ውስጥ ሲሸጡ ሲለውጡ የነበሩትን መንጥሮ ለማውጣት ጅራፉን ይዞ የሚመጣበትን ቀን ከፈሪሳውያን እና ፃሕፍት ጋር ተመካክሮ አልወሰነም።ስለሆነም ይህንን ቀን ማንም አያቆመውም።

አዎን! ቤተክርስቲያን ከውጪ እየደረሱባት ያሉት ፈተናዎች ቀላል አይደሉም።ነገር ግን ፈተናዎቹን የውስጥ ችግሯን ቀድማ ከመፍታት ውጪ የውጭ ፈተናዎችን መከላከል ከባድ ነው።ቤተክርስቲያኒቱን የመንግስት ሙሉ አካል ተፃራሪዋ ነው የሚለው የአንዳንዶች አስተያየትም ትክክል አይደለም።ከመንግስት መዋቅሮች ውስጥ በጠላትነት የሚያይዋት አሉ የሚለው የተሻለ አገላለጥ ነው።መንግስት ግን እንደ መንግስት የሀገሪቱ ግማሽ በላይ አካል ከሆነች ቤተክርስቲያን ጋር አለመስራት ብቻ ሳይሆን የተሻለች እና  የቀለጠፈ እንዲሁም የጠለቀ መንፈሳዊ አገልግሎት በመስጠት ሕዝቡ መርካቱ ለራሱ ለመንግስት ቢያንስ በፖለቲካዊ የሰመረ  አስተዳደር አንፃርም ብናየው የሚፈልገው መሆኑን አለመረዳት በራሱ የአስተሳሰብ መዛነፍ ችግር ነው።ስለሆነም አንዳንዴ አላስፈላጊ መጠራጠር አስፈላጊ ነው ብዬ አላምንም። ትልቁ ጉዳይ ቤተ ክርስቲያኒቱ የውስጥ የሙስና እና አስተዳደራዊ ጉዳዮች አስተካክላ እና መንፈሳዊ አገልግሎቷን በትሕትና፣በፍቅር እና በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ማስፋፋት፣ተግዳሮቶቹን ከምዕመኑ ጋር በብልሃት እና በእግዚአብሔር ዕርዳታ እየተጋፈጠች መሄዱ ላይ ነው ቁም ነገሩ።ከእዚህ በተጨማሪ የአገልግሎት ማኅበራት በዋናነት ሊያተኩሩበት የሚገባው ማኅበራዊ  አገልግሎት ማስፋፋት እና መላ ሀገሪቱን በሚሸፍን ደረጃ የማጠናከር ሥራ ላይ ነው።ይህ እጅግ የበዙ ጥቅሞች አሉት።በእዚህም የሀገሪቱን ችግር በመጠኑ ይቀርፉበታል፣ከመንግስት መዋቅሮች ጋር በልማት አጋርነት ይተጋገዙበታል፣ተደማጭነታቸው በሕዝቡም ሆነ በመንግስት ዘንድ ያጎሉበታል።ስለሆነም የትኩረት አቅጣጫዎች በአግባቡ መምረጥ እና የበጎ ተፅኖ  መፍጠርያ ቦታዎችን ለይቶ የቤተ ክርስቲያንን ታሪካዊ ቦታ የማስያዝ አንዱ እና ዓይነተኛ መንገድ እንደሆነ ማወቅ ብልሕነት ነው። ከእዚህ በተረፈ ግን ትሕትናን ገንዘብ እናድርግ! መሰደብ መነቀፍ አያስቆጣን።በክርስትና ሕይወት የምንከተለው የተነቀፈ እና የተሰደበ ብቻ ሳይሆን የተገረፈ እና የተሰቀለ አምላክ እና አንገታቸውን የተቆረጡ ሰማዕታት ናቸው።ለተተቸው እና ለተነቀፈ ጉዳይ ሌላው ቢረዳውም ባይረዳውም በጨዋነት እና በትሕትና ምላሽ እንስጥ።አካሄድን መምረጥ ግብን ለመለየት ይረዳል።አንዳንዶች አካልበው ከሁሉ ጋር እያጋጩ ወደ አልሰከነ አቅጣጫ በመውሰድ እንዳያታክቱን መጠንቀቅ ተገቢ ነው።ያለፉት ችግሮች እንዴት በማስተዋል እና ከሁሉም በላይ በጸሎት እንደተፈቱ ዛሬ ላይ ቆሞ ማስታወስ ተገቢ ነው። 

 በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ከቤተክህነት ጦር ሲወረወርበት የተሟላ ሪፖርት ያቀረበ ኢሳት ብቻ ነበር 
ከእዚህ በታች እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2014 ዓም በኢሳት የቀረበ ሪፖርት ነበር። 
(ቪድዮውን እስከመጨረሻው ይከታተሉ በርካታ ከአሁኑ ክስተት ጋር የተገናኙ ነጥቦች ያገኛሉ)






==============///=============

Thursday, May 13, 2021

''ኢትዮጵያን ለረጅም ጊዜ እናውቃታለን እንደ ደራጎን ለረጅም ጊዜ ተኝታ ድንገት የምትነሳ ሃገር ነች ብለው የግብፁ ፕሬዝዳንት ሳዳት ሲናገሩ ሰምቻለሁ'' ኮለኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የሰጡት መግለጫ (ኦድዮ) ሁሉም ሰው ሊያዳምጠው የሚገባ

 የኢትዮጵያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማርያም ከኢትዮጵያ ከወጡ ግንቦት 13/2013 ዓም ሠላሳ ዓመት ይሞላቸዋል።ከእዚህ በታች ካለው ሊንክ ላይ የኮ/ል መንግስቱ ቃለ መጠይቅ ያድምጡ።በርካታ አሁንም ያለው የኢትዮጵያ አመራርም ሆነ ሕዝብ ሊማርበት የሚገባ ነጥቦች ይዟል።
  
በቃለ መጠይቁ  
>> ደህንነት ሚንስትሩ ተስፋዬ ወ/ስላሴ መጨረሻ ላይ የሰሩትን ክህደት አንስተዋል፣ 
>> አሜሪካ እንዴት ባለሥልጣናቱን እንዳታለለች፣
>> ወደ ኬንያ የሄዱበት ምክንያት ያወሳሉ፣
>> የስነ ልቦና ጦርነት ምን ያህል አሁንም አደገኛ እንደሆነ ያስረዳሉ።
>> ቅድመ አያቶቻችንን አባቶቻችንንም እኛንም ዛሬ የሚፈትነው አንድ ጉዳይ ምን እንደሆነ ያስረዳሉ።
>> ኢትዮጵያ እንደ ሀገር እንድትቀጥል የሚያስፈልገው አንድ እና አንድ ጉዳይ ያስረዳሉ። 
>> የኢትዮጵያ ሕዝብ የተማረ፣በተፈጥሮ በቀላሉ ሊማር የሚችል ጥሩ መሪ ካገኘ ባጭር ጊዜ ያሰበበት የሚደርስ ነው።
>> የኢትዮፖያ ሀብት ከ400 ሚልዮን ሕዝብ በላይ የሚያስተዳድር ሀብት ያላት ሀገር ነች።
ሌሎች እጅግ ድንቅ የሆኑ መልዕክቶች ይዘዋል።ዛሬ ላለንበት ሁኔታ ምላሽ የሚሰጡ ብዙ ሃሳቦች ይዘዋል።እስከመጨረሻ ይከታተሉ።


Wednesday, May 12, 2021

ሱዳን ለሩስያ የባህር ኃይል ወደብ ለመስጠት የተስማማችውን ውል መሰረዝ ለአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ ምን ዓይነት በረከት እና እርግማን ያመጣል?

የሩስያ መርከብ (ፎቶ ታስ ዜና አገልግሎት)

>> የአሜሪካ ኢትዮጵያን በትግራይ ጉዳይ የመጎንተል ሥራ በቅርቡ ወደ መቃብር ይወርዳል።

ጉዳያችን/Gudayachn 


ሱዳን እና ሩስያ የሩስያ ባህር ኃይል ጣብያ በሱዳን ወደብ ላይ የጦር ሰፈር እንዲያገኝ ለመጪዎቹ 25 ዓመታት የሚቆይ ውል መዋዋላቸው የተሰማው ባለፈው ታህሳስ ወር መጀመርያ ሳምንት ላይ ነበር።ስምምነቱ ሩስያ የጦር መርከቦቿን በወደቡ ላይ ከማስፈር ባለፈ የመርከብ ጥገና ስራም የምትሰራበት እንደሚሆን ተጠቅሶ፣የኒኩለር ተሸካሚ መርከቦችን ማሳረፍ የጨመረ ዕድል ለሩስያ ሲሰጣት፣ሱዳን በምላሹ ነፃ የጦር መሳርያዎችን ከሩስያ የማግኘት ዕድል እንደሚከፍት ነው የተነገረው።የሩስያ በሱዳን የባህር ዳር ላይ ቦታ ማግኘት የአፍሪካ መግቢያ በር እንደሚሆናት ታስቦ ነበር።በሌላ በኩል የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ሀገሮች (ናቶ) ወደ ደቡብ የሚያደርገውን መስፋፋት ለመግታት የታሰበ የሩስያ አካሄድ ነው በማለት የተነተኑም ነበሩ።

የሩስያ በሱዳን ወደብ ላይ ቦታ ማግኘቷ በዋናነት የቆጠቆጣት አሜሪካ ነበረች።አሜሪካ ከሱዳን ጋር ያላትን ግንኙነት በቶሎ ከማሻሻል አንስቶ ሱዳንን ከአሸባሪ መዝገብ እንድትሰረዝ እና የዓለም ባንክ ገንዘብም ለወቅታዊ ችግሮቿ እንዲሸፍኑ ተሰጥቷታል። አሜሪካ ሩስያ በሶርያ ያላትን መሰረት ማጠናከሯ እንደትልቅ ስጋት የምታየው ሲሆን ወደ ሱዳን ያደረገችውን ግስጋሴ በሱዳን የውስጥ ጉዳይ በመግባት እና በማባበል ውሉ እንዲሰረዝ ያደረገችው አሜሪካ ነች እየተባለች ትታማለች።

የሩስያ ዜና አገልግሎት ''ታስ'' ከሳምንት በፊት እንደዘገበው ስምምነቱ አንድ ዓመት ሳይሆነው ለማቆም መሞከር ሁለቱም ወገኖች አንዳንዳቸው ለአንዳቸው በማሳወቅ ሳይስማሙበት ሊሆን እንደማይችል ከፍተኛ የሩስያ ባለስልጣን እንደገለጡለት ነው ያስታወቀው።ባለሥልጣኑ ይህንን ይበሉ እንጂ ውሉ መሰረዙን ግን የመካከለኛ ምስራቅ መገናኛ አውታሮች እና የሩስያ ዜና አገልግሎትም ገልጧል።

ጉድዩ ለአፍሪካ ቀንድ ይዞት የሚመጣው በረከት እና እርግማን ምንድነው? የሚለው መሰረታዊ ጥያቄ ነው። ሩስያ ፊቷን ወደ አፍሪካ እንደ ቻይና እና ምዕራባውያን ማዙሯ የአደባባይ ምስጢር ነው።ለእዚህም የሩስያ አፍሪካ ግንኙነት ላይ ያተኮረ ጉባኤ ከአንድ ዓመት በፊት በሩስያ ከተደረገ በኃላ ቀጣይ ከፍተኛ ዋጋ የሚሰጠው ጉባኤ በአፍሪካ እንደሚደረግ መነገሩ ያታወቃል።ጉባኤውን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ ፈቃደኛ መሆኗን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር  እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አቶ ደመቀ መኮንን አማካይነት መግለጧ ይታወሳል።አማርኛ አቀላጥፈው የሚናገሩት በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኤቭገኒ ተረኪን ሩስያ የኢትዮጵያ አጋር ሀገር መሆኗን ባገኙት አጋጣሚ ሲገልጡ ተሰምተዋል።ሩስያ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት የኢትዮጵያን ወቅታዊ ጉዳይ አስታኮ የጠራቸውን ስብሰባዎች በሙሉ በመቃወም ማክሸፍ ከቻሉት ሀገሮች ውስጥ ግንባር ቀደሟ ነች።ከእዚህ በኃላ ነው የተባበሩት መንግሥታት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚያከብር እና በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ላይ መግባት ተገቢ አለመሆኑን አፅንኦት የሚሰጥ መግለጫ ያወጣው። 

የአፍሪካ ቀንድ በሁሉም የዓለም ኃያላን ዘንድ መጪው ቁልፍ የበለጠ ስልታዊ ብቻ ሳይሆን ግዙፍ ምጣኔ ሀብት ይዞ ይወጣል ተብሎ የሚታሰበው እና ለአንዳንዶች ''የሚፈራው'' ጠቅላይ ዓቢይ ወደ ስልጣን እንደመጡ ያቀነቀኑት የኤርትራ፣ኢትዮጵያ እና ሱማሌ የምጣኔ ሀብት ጥምረት ሃሳብ ነው።ይህ ሃሳብ ግዙፍ የገበያ ማዕከል ብቻ ሳይሆን ይዞ የሚመጣው የቀይ ባህርን በተሻለ ጉልበት የመቆጣጠር ኃይል ለሶስቱ ሀገሮች ይሰጣል።ስለሆነም የሩስያ ቀጣይ መንገድ በኤርትራ የባህር ኃይል መሰረት የማግኘት ዕድል ከገጠማት እና ኢትዮጵያ የባህር ኃይሏን እንደጀመረችው ማደራጀት ከቻለች በአካባቢው ላይ ተፅኖ መፍጠር የሚፈልጉ ኃያላን ጥቅማቸው የሚነካ አድርገው ያዩታል።ስለሆነም ሩስያ እና ቻይና ከሚጠቀሙ የአፍሪካ ቀንድ ቢበታተን የሚመርጡ የሉም ማለት አይቻልም።የሶስቱ ሀገሮች የምጣኔ ሐብት ጥምረት ግን ለሦስቱም ሀገሮች ከፍተኛ ጥቅም ይዞ መምጣቱ አያጠራጥርም።በተለይ  በአንፃሩ የተሻለ የሰው ኃይልም ሆነ የምጣኔ አደረጃጀት ያላት ኢትዮጵያ ከፍተኛ ጥላ የምታጠላበት ጥምረት እንደሚሆን ነው የሚታመነው። ስለሆነም ሶስቱ ሀገሮች በሩስያ እና በአሜሪካ አንፃር የሚጫወቱት ጫወታ ከሀገሮቹ ዘላቂ ጥቅም አንፃር በደንብ አጥንተው የሚገቡበት መሆን አለበት ማለት ነው።

የሩስያ ከሱዳን የባህር ኃይል ማረፍያ አለማግኘት ማለት አማራጭ ቦታ የላትም ማለት አይደለም።በኢትዮጵያ አግባቢነት በኤርትራ የማግኘት ዕድል አሁንም አላት።ይህ እንዳይሆን አሜሪካ ኢትዮጵያን የማትለምንበት መንገድ አይኖርም።በእርግጥ ከመለመን በፊት አሜሪካ በትግራይ ጉዳይ አሳባ ብዙ የማወክ ሙከራ በኢትዮጵያ ላይ ላለፉት ስድስት ወራት ስታስኬድ ሰንብታለች።በውጤቱ ግን የተሳካ ሆኖ አላገኘችውም።የግብፅ የደህንነት ባለስልጣናት ለአሜሪካ 'የኢትዮጵያን ነገር ተይው ከውስጥ የጀመርነው ፕሮጀክት አለ' እያለች ስታማልል ብትከርምም በቅርቡ ግን ከቤንሻንጉል እስከ መቀሌ ያለው የተንኮል ድር በሙሉ በመበጣጠሱ አሜሪካ ከሰሞኑ የመለሳለስ መልክ ብታሳይም አይገርምም።

አሁን የአሜሪካ ስጋት ሩስያ ከኢትዮጵያ ጋር ከገጠመች በተለይ በኤርትራ ወደብ የባህር ኃይል ከመሰረተች ከሶርያ ቀጥሎ ሩስያ ቁልፍ ማረፍያ እንዳገኘች ትቆትረዋለች ብቻ ሳይሆን ከመካከለኛው ምስራቅ ወደ አፍሪካ የምታደርገው እመርታ ወሳኝ ምዕራፍ እንደሆነ ተረድታዋለች። ይህም ከቀዝቃዛው ጦርነት በኃላ ሩስያ እንደገና ወደ አፍሪካ አንፃር አንሰራራች ማለት ነው።ስለሆነም የሱዳን ውል ማፍረስ ለኢትዮጵያ ይዞ የሚመጣው አንዱ በረከት አሜሪካ ኢትዮጵያን በትግራይ ጉዳይ መጎንተሏን ታቆማለች ወይንም ታቀዘቅዛለች።በመቀጠልም ሰሞኑን እያሳየች እንዳለው የዓባይ ግድብ አንፃር ኢትዮጵያ የራሷን የተፈጥሮ ሀብት የማልማት መብት አላት የሚለውን አረፍተነገር በመደጋገም ታፈገፍጋለች።ኢትዮጵያ ይህንን የሩስያን ጉዳይ ከኤርትራ ጋር ተመካክራ እንደ ታላቅ ወንድም እያስፈራራች ምርጫውን እና የውሃ ሙሌቷን ከጨረሰች ቀሪውን ውሳኔዋን ከመስከረም አደይ አበባ መፈንዳት ጋር ቀስ ብላ ቡና ፉት እያለች መወሰን ትችላለች።

ለማጠቃለል የአሜሪካ በትግራይ ጉዳይ ኢትዮጵያን የመጎንተል ሂደት በቅርቡ ወደ መቃብር በእዚሁ በሩስያ ጉዳይ እንደሚያበቃ ግን ከወዲሁ መገመት ይቻላል።ይህ ማለት አንዳንድ በሎቢ የቀወሱ ሴናተሮች እና ጋዜጠኞች ዝም ይላሉ ማለት አይደለም። ዋናዎቹ የውጭ ፖሊሲ አውጪዎች ግን አንዳች እርምጃ ሊወስዱ አይችሉም ቢያንስ ለመጪዎቹ አራት ወራት።ሌላው ቀርቶ የአውሮፓ ህብረት አዲስ የሳተላይት መሳርያ ካላስገባሁ፣የምርጫ ውጤቱን እኔ ቀድሜ የመናገር መብት ካላገኘሁ እያለ ትንሽ  ጠገብ ብሎ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ሃሳቡ ተቀይሮ ባላችሁት መሰረት ለምርጫው ታዛቢ እልካለሁ ማለቱ ሁሉ የኢትዮጵያ ቦታ መልሶ መሬት እየቆነጠጠ መሆኑን ብቻ ሳይሆን የሚያሳየው አፍሪካ ቀንድ ላይ ያለው መራኮት ኢትዮጵያን ከሁሉ በላይ አስፈላጊ መሆኗንም ጭምር ነው።ይህ እንግዲህ በመላው አፍሪካ ላይ ያላትን ተፅኖ የመፍጠር አቅም ሳናነሳ ነው።ኢትዮጵያውያን ግን አሁን ማተኮር የሚገባው ግዙፍ እርዳታ በተለይ በቤተ እምነቶች አንፃር ለትግራይ እና በልዩ ልዩ ስፍራ አደጋ እና ጥቃት ለደረሰባቸው ኢትዮጵያውያን የእርዳታ ሀብት ማሰባሰብ እና መርዳት ነው።የኢትዮጵያ ቁስል ይሽራል።ከትግራት እስከ መተከል፣ከአጣዬ እስከ ወለጋ የተጎዱትን የመርዳቱ ተግባር ግን መቀጠል አለበት።
=======================////=============

Tuesday, May 11, 2021

የክርስትና እና የሙስሊም የእምነት አደረጃጀቶች የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎች እንዳይጎትቷቸው መጠንቀቅ አለባቸው።


ጉዳያችን/Gudayachn


ኢትዮጵያ የእምነት ሀገር ነች።ህዝቧ ከሊቅ እስከ ደቂቅ በፈጠረው አምላክ ያምናል።በችግሩ እና በደስታው ጊዜ ብቻ ሳይሆን በሰላምታው ጊዜም ሳይቀር አምላኩን የሚጠራ ሕዝብ ነው።ይህ ሕዝብ ካለምንም ማጋነን ከየትኛውም የዓለማችን ክፍል በተለየ እና በፀና ደረጃ በብዙ ፈተና ውስጥም ቢሆን ከፈጣሪው ጋር ግንኙነት አለው።በሌላው ሀገር የማናገኘው የሞራል ልዕልና በኢትዮጵያውያን ላይ የሚታየው ሌላ ሳይሆን የሕዝቡ በፈጣሪው ላይ ያለው ዕምነት ነው።በቅርቡ በአዲስ አበባ አስተዳደር ከፍተኛ ባለስልጣን እንደተገለጠው በአዲስ አበባ ብቻ በቀን አንዴ በልተው ለማደር የሚቸገሩ ከአንድ መቶ ሺህ በላይ ሕዝብ አለ።በእዚህ ደረጃ ችግር ላይ ያለ ሕዝብ ግን የእምነት ሕዝብ ስለሆነ አንዱ አንዱን እየረዳ የሚኖር የተቸገረውም በትሕትና እንጂ በነጠቃ የማይኖርባት ሀገር መሆኗን ይህ በራሱ ምስክር ነው።

ይህ በእንዲህ እያለ ይህ ወቅት የኢትዮጵያ የክርስትናም ሆነ የሙስሊም አደረጃጀቶች ከመቼውም ጊዜ በላይ ነቅተው እና ተግተው የሚቆሙበት ጊዜ ነው።በሁለቱም ዕምነቶች ውስጥ አደረጃጀቶቻቸውን ለመክፈል እና የፀብ መድረክ ለማድረግ በተለያዩ የፖለቲካ አካላት ጉተታ ይታያል።ጉተታዎቹ ሦስት ዓላማዎችን ይዟል። እነርሱም -  የእምነት ድርጅቶቹን እርስ በርስ በውስጣቸው ሰላም እንዳያገኙ ማበጣበጥ፣ከመንግስት ጋር ማጋጨት እና አንዱን እምነት ሌላውን እንዲጠራጠር ወሬ መንዛት ናቸው። 

በእስልምናም ሆነ በክርስትና ውስጥ ያሉ የውስጥ ቁርሾዎችን ማባባስ እና አደረጃጀቶቹ ሰላም እንዳይሆኑ በማድረግ ተከታዩ ምዕመንን ሰላም መንሳት እና በውጤቱ ሀገር እንዳይረጋጋ እና ሰላም እንዲጠፋ በማድረግ ርካሽ የፖለቲካ ግብ መምታት ነው።
በእዚህ መሰረት በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ውስጥ የበላይ አመራር መጅሊሱን ሕዝብ እንዳይቀበል የሚቀሰቅስ ቅስቀሳ በማካሄድ የፅንፍ ኃይሉ የበላይ እንዲሆን የማድረግ ሙከራ ነው።

በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንም ውስጥ ተመሳሳይ ድርጊቶች ይታያሉ።በተለይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሰሞኑን ቅዱስ ፓትርያሪኩ ከአንድ ወር በፊት የተቀዳው እና ወቅታዊ የኢትዮጵያን ሁኔታ የተመለከተ ቪድዮ ሰሞኑን መለቀቁን  የቤተክርስቲያኒቱን መዋቅር እና ድምፅ በትክክል የማይወክሉ የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች እዚህም እዝያም በሚድያ እየቀረቡ በቤተክርስቲያኒቱ ስም ሲናገሩ እየታየ ነው።በተለይ የኢትዮጵያ ሚድያዎች የቤተክርስቲያኒቱን ተዋረድ ሳይጠብቁ ያገኙትን ካህን በቤተክርስቲያኒቱ ስም ማናዘዝ እጅግ አደገኛ አካሄድ ነው።ቤተክርስቲያኒቱም የህዝብ ግንኙነት በተመለከተ በማዕከላዊነት የምትመራበት አንድ ድምፅ እንዲኖራት እና ማንም ከእዚህ ማዕከላዊ የህዝብ ግንኙነት ውጪ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም የሚናገር አገልጋይ እንዳይኖር ጥብቅ መመርያ ያስፈልጋታል። 

ሌላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንም ሆነ የእልምና ተከታዮች በተለያየ ጥግ ሆነው ከመንግስት ጋር እንዲጋጩ የሚሰሩ አሉ። እነኝህ የተለያየ ዓላማ የያዙ ናቸው።በእስልምና ውስጥ እጅግ ፅንፍ የያዘ እና የራሱን መጅሊስ ቆርጥሞ በልቶ እና እውነተኛ አማኙን ከመስጊድ አስወጥቶ በሌሎች ሀገሮች የሚታየው የፅንፍ አስተዳደር በእምነት ስም መለጠፍ የምፈልገው ቡድን በቅድምያ ሙስሊሙ ከመንግስት ጋር እንዲጋጭ ማድረግን እንደዋና ግቡ ወስዶታል።ለእዚህም ያገኘውን  እያሰፋ ነገር ስጎነጉን የሚያድር ነው።ይህንን አብዛኛው ሙስሊም ስላወቀበት አንዳንዴ ተመሳስሎ ሲቆም ይታያል።

በተመሳሳይ መንገድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንም ውስጥ በተለይ ላለፉት 27 ዓመታት በሌሎቹ የእምነት አደረጃጀቶች ውስጥ የታየው  ፀሐይ የሞቀው የአንድ ብሔር የበላይነት ባለፉት ሦስት ዓመታት በኢትዮጵያ በመጣው ለውጥም ሆነ በቀድሞው ሥርዓት ላይ በቅርቡ የተወሰደው የሕግ ማስከበር እርምጃ ሳይቀር ስላስከፋው ቤተክርስቲያኒቱን ለመከፋፈል በተለይ በውጭ ሀገር አንዳንድ እንቅስቃሴዎችን ሲያደርግ እየታየ ነበር።ይሄውም የትግራይ ካሕናትን ከቅዱስ ሲኖዶስ ስር ለመለየት አንዳንድ እንቅስቃሴዎች ሲያደርጉ ታይተው በትግራይ ካህናት ሳይቀር ከፍተኛ ተቃውሞ ስለገጠመው አድፍጦ መቀመጡ እየታየ ነው። በተለይ የእዚህ ዓይነቱ ቡድን በትግራይ በሚኖሩ አባቶች ቢሰማ የሚደርስበትን ውግዘት የተረዳው ቡድን ቤተክርስቲያኒቱን ለመረበሽ አንዳንድ ያልተሳኩ እና የማይሳኩ ሙከራዎች እያደረገ ነው።

የመጨረሻው በኢትዮጵያ የክርስትና እና የእስልምና አደረጃጀቶች ውስጥ እየታዩ ያሉ ተግዳሮቶች አንዱ ሌላውን በጥርጣሬ እንዲመለከት ማድረግ ነው።ይህ ደግሞ የሐሰት ወሬዎች በመንዛት ሲሆን በፅንፍ አካሄድ የሚታወቁ የፖለቲካ ድርጅቶች ዋና አቀጣጣዮች ናቸው።ይህ አለመተማመን የመፍጠር ሂደት በተለይ የእምነቶቹን ሊቃውንት ያገለለ በመሆኑ ''መደዴ'' የሆኑ የእምነቱ ተከታዮች ቀድመው በመናገራቸው ወይንም በመሳደባቸው ''እንደመሪ'' እየሆኑ የሚወጡበት ስለሆነ አደገኛ አካሄድ ይታይበታል።

ባጠቃላይ  የክርስትና እና የሙስሊም የእምነት አደረጃጀቶች የተለያዩ የፖለቲካ እና የፅንፍ ኃይሎች ጉተታ ውስጥ እንዳይገቡ  ከመቼውም ጊዜ በላይ የእስልምናም ሆነ የክርስትና አደረጃጀቶች የውስጣዊ ጥንካሪያቸውን፣በልቃውንቶቻቸው እና በሕጎቻቸው ላይ ብቻ በተመሰረተ መንገድ መመራታቸውን በደንብ መፈተሽ አለባቸው። 99% የሚሆን ሕዝብ በፈጣሪው የሚያምን ሕዝብ  ሀገር የእምነት አደረጃጀቷ ጤነኛ ብቻ ሳይሆን ለሀገር እድገትም አዎንታዊ አስተዋፅኦ ያለው እንዲሆን ያለምንም ወገንተኝነት የማገዝ ግዴታ ደግሞ መንግስት አለበት።መንግስት የኢትዮጵያ የእምነት አደረጃጀቶች መጠናከር እና ምእመናኖቻቸውን በሚገባ ማገልገል ማለት ሃገራዊ ሰላም ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን በሰላም የማሸጋገር አንዱ እና ወቅታዊው ወሳኝ ተግባር ነው።ከሁሉም በላይ ወሳኞቹ ግን የክርስትናም ሆነ የእስልምና የውስጥ ጤነኛ፣በፖለቲካ ኃይሎች ያልተዘወረ ግን የእምነት ነፃነቱን የጠበቀ የእምነት አደረጃጀት እንዲኖራቸው ጠንክረው ሲሰሩ ነው። ''እውነት አርነት ያወጣችኋል'' ዮሐንስ 8፣32 እንዲል ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያን ነፃ የሚያወጣት፣ እምነቷን ጠብቆ የሚያቆይም እውነት እንጂ የተለያዩ አመለካከቶች ጉተታ እና የእነርሱ ሰለባ መሆን አይደለም።

========================///=============

እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው።"
(ዮሐንስ 8:32)
እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው።"
(ዮሐንስ 8:32)

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።