ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, December 31, 2013

ስለ ዳግማዊ ምንሊክ የ'' ኒዎርክ ታይምስ '' ጋዜጣ (ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር) የዛሬ 96 አመት የፃፈው ፅሁፍ ለአሁኑ ትውልድ ታሪካዊ ማስረጃ ነው


ጉዳያችን ጡመራ ታህሳስ 22/2006 ዓም
ዳግማዊ አፄ ምንሊክ ፎቶ 

ኢትዮጵያ በየዘመኗ በሕልውናዋ ላይ የተቃጣባት የመበታተን አደጋን ያለፈችበት መንገድ የጦርነት መንገድ ብቻ አይደለም።ሆኖም ግን ከነበሩን የግጭት ታሪኮች በዘለለ በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ የነበሩ እና በሕዝብ ዘንድም የተወደዱ  መሪዎች ነበሩን።ከእነኝህ ውስጥ ዳግማዊ ምንሊክ አንዱ ነበሩ። አፄ ምንሊክ ሀገር የማስተዳደር ጥበብን የተማሩት በአፄ ቴዎድሮስ እጅ ሆነው እድገታቸውን በንጉሡ ቤተመንግስት ማድረግ ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑን ብዙዎች ይስማማሉ።ንጉሡ የቀደሙ አባቶቻቸው አፄ ቴዎድሮስ እና አፄ ዮሐንስ ኢትዮጵያን አንድ የማድረግ አላማቸው እውን እንዲሆን ያደረጉ እድለኛ ንጉስም ናቸው።

አፄ ምንሊክ ኢትዮጵያን አንድ ከማድረግ አልፈው እስከ ኬንያ፣ሱዳን እና ሱማልያ ግዛት ድረስ ዘልቀው ገብተው በቅኝ ግዛት ይማቅቁ የነበሩ ህዝቦችን ነፃ ያወጣሉ የሚል ስጋት የነበረባቸው  እና በወቅቱ በእነኚሁ የጎረቤት ሃገራት  ላይ የጥቅም ፍላጎት የነበራቸው የአውሮፓ ሃገራት በብርቱ ተፈታትነዋቸው ነበር።በመሆኑም አዲስ የድንበር ውል ከኢትዮጵያ ጋር የመፈራረም ፍላጎት ከእንግሊዝ፣ፈረንሳይ እና ኢጣልያ በኩል ጥያቄ መነጻቱን የወቅቱ የታሪክ ድርሳናት ያወሳሉ።

ዛሬ ዛሬ በምንሊክ ላይ ታሪካዊ መሰረት የሌላቸው ቀድሞ አፄ ምንሊክ የቅኝ ግዛት ጥማታቸውን በገቱባቸው እና ቂም በያዙ ፀሐፊዎች የተፃፉ ናቸው ብለው ከሚነግሩን አስገራሚ ''የታሪክ'' ፅሁፎች ውስጥ ''በምኒሊክ ዘመን እስከ አስር ሚልዮን ኦሮሞዎች አለቁ'' የሚል ፅሁፍ በአንዳንድ የማህበራዊ ድህረ ገፆች ተለቀው ሲነበቡ መመልከት  አስገራሚ የሰሞኑ ክስተት ነው።በፖለቲካው አለም በቂ ርዕዮተ አለምም ሆነ ፖለቲካዊ ፍልስፍና የጠፋባቸው አንዳንድ ወገኖች ''ትርፋማ'' ብለው ያሰቡት የዘር ፖለቲካ በኢትዮጵያውያን መካከል መዝራት እና ከመቶ አመት በፊት  የሆነውን የታሪክ ክስተት የአሁኑን ትውልድ በመውቀስ ትኩረት ለማግኘት ሲታትሩ መመልከት የዘመኑ አስቂኝ ተውኔት ነው።ዳግማዊ ምንሊክ ገና ብዙ የሚጠና ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ወታደራዊ ክህሎት ባለቤት ለመሆናቸው በወቅቱ ከወጡት የዓለማችን ድንቅ ጋዜጦች አንዱ የ ኒውዮርክ ታይምስን እትም መመልከት ይበቃል።

ከእዚህ በታች በሚገኘው የኒውዮርክ ታይምስ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ላይ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ሕዝብ ብዛትን 7,000,000 (ሰባት ሚልዮን) መሆኑን ያስቀምጣል። እዚህ ላይ አንዳንድ እራሳቸውን የታሪክ ምሁራን ነን በሚል ባልተጨበጠ ይልቁንም በምኒሊክ የቅኝ ግዛት ህልማቸው ከተደናቀፈባቸው ቂመኛ ፀሐፊዎች አነበብን የሚሉት እና የኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያንን ያማለሉ መስሏቸው  ''ምንሊክ 10 ሚልዮን ኦሮሞ ገደሉ'' እያሉ ኢትዮጵያ ከነበራት የህዝብ ብዛት (7 ሚልዮን) በላይ  ቁጥር ሲጠሩ እፍረት አልተሰማቸውም።

''ማን ያውራ የነበረ'' እንዲሉ የኒውዮርክ ታይምስ  ጋዜጣ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ላይ ጋዜጣው አዲስ አበባ በነበረ  በልዩ ዘጋቢው አማካይነት ስለንጉሡ እና ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ሁኔታ ፅፎ ነበር።ጋዜጣው  አፄ ምንሊክ እና አስተዳደራቸውን ከገለፀበት አረፍተ ነገር  ውስጥ እነኝህ ይጠቀሳሉ  -

 - ኢትዮጵያን ወደ ህገመንግስታዊ የንጉሥ አስተዳደር ለመቀየር ሂደት ላይ መሆኗን፣

 - የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት 7 ሚልዮን መሆኑን፣

 - አፄ ምንሊክ ንጉሰ ነገስት ሲሆኑ ጦርነት የነበረው የአፄ ዮሐንስ ተተኪ  እሳቸው መሆናቸውን ካልተቀበሉት ጋር ብቻ እንደ ነበር፣

 - የአውሮፓውያንን ስልጣኔ ወደሀገራቸው ለማምጣት የባርያ ንግድን ከመዋጋታቸውም በላይ ነፃ ትምህርት ዕድል ዜጎች እንዲያገኙ መሰረት መጣላቸውን፣

 - ምንሊክ እራሱ ልዩ ችሎታ ያላቸው ሰው መሆናቸውን። ከችሎታዎቻቸው መካከል  ዲፕሎማት፣የፋይናንስ ባለሙያ እና  ወታደር የሚሉት እንደሚጠቀሱ እና

 - እንደ ዲፕሎማት እና ወታደር የጣልያንን ወረራ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ያደረጉበት ጥበብ መሆኑን፣

 የሚሉ ይገኙበታል።የጋዜጣውን ሙሉ ፅሁፍ ከእዚህ በታች ያለውን ሊንክ ከፍተው ያንብቡ።

 የኒውዮርክ ታይምስ  ጋዜጣ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ለማንበብ ይህንን ሊንክ ይክፈቱ።

Published: November 7, 1909 Copyright © The New York Times

http://query.nytimes.com/mem/archive-free/pdf res=F50A12F63A5A15738DDDAE0894D9415B898CF1D3 



Friday, December 27, 2013

'' ሆድ ያባውን ንግግር ያወጣዋል''- የጀዋር መሐመድ እና መሰሎቹ ፅንፈኛ 'ሜጫዊ' አስተሳሰብ አላማው ህዝብን ማፋጀት ነው!

('ሜጫ' የሚለውን ቃል ከጀዋር ንግግር አገባብ መረዳት እንደሚቻለው ካራ፣ጎራዴ ለማለት ተጠቅሞበታል)
 በአሜሪካዋ ሚኒሶታ ግዛት ሁለቱ ''አክቲቪስት'' ጀዋር መሐመድ እና ሃጂ ነጂብ መሐመድ ያደረጉት ንግግር አስደንጋጭ እና አሳሳቢ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ በመጪው ግዚያት  የሚገጥሟትን ተግዳሮቶች የሚያመላክትም ጭምር ነው። የጀዋር መሐመድ ''ሙስሊም  ያልሆነውን'' እንደርሱ አገላለፅ እርሱ በተወለደበት አካባቢ ''በሜጫ አንገቱን እንደሚቀላ'' የተናገረበት እና ሃጅ ነጂብ መሐመድም በተራቸው ''ከኦሮሞ ተወላጅ ባብዛኛው (ከ80% በላይ) ሙስሊም ነው .....በኢትዮጵያም እንዲሁ ከ ሃምሳ ሚልዮን በላይ ነን.....'' ሲሉ ተደምጠዋል። ሁለቱም የሜኖሰታ ተናጋሪዎች ከእዚህ ቀደም በሙስሊም ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ላይ እየደረሰ ያሉትን መንግስታዊ የአስተዳደር በደሎች ለማስተጋባት ''ድምፃችን ይሰማ'' በሚሉ መድረኮችም ሆኑ ሌሎች መድረኮች በማስተጋባት መታወቃቸው ብዙ ግን አስፈላጊ ጥያቄዎች እንዲነሱ በር ከፍቷል።

በሀገራችን ካለው የፖለቲካ፣የሃይማኖት፣ወዘተ በደሎች አንፃር የእስልምና ወንድሞቻችን የሚያነሱዋቸው ጥያቄዎች በትክክለኛ በኢትዮጵያ አንድነት፣ነፃነት እና ዲሞክራሲ በሚያምኑ ወገኖች አማካይነት ሲነሳ እና ሲመራ ማየት የሁሉም ሀገር ወዳድ ወገን ፍላጎት ነው።ከእዚህ በዘለለ ግን ጉዳዩ የአክራሪነት እና የፅንፈኝነት ስሜት በያዙ ወገኖች እሳት ዳር እንደሚጫወት ሕፃን ያሻቸውን ሲያደርጉ መመልከት ደግሞ ተገቢ አይደለም።

ጉዳያችን ጡመራ ባለፈው አመት ጥቅምት 2004 ዓም ላይ ''የሙስሊሙ ጉዳይ'' በሚለው ርዕስ ስር እንቅስቃሴው ወዴት ሊያመራ ይችላል? በሚል ከእዚህ በታች ያለውን ሁለት ስጋቶች አስቀምጣ ነበር።

''ጉዳያችን ጡመራ'' ቀ 27 ወራት በፊት (ጥቅምት/2004 ዓም) የነበራት ስጋት

  • ''የ ሙስሊም ፅንፈኛ ቡድን'' የ ሙስሊሙን ጥያቄ  የመሪነት ሚና ለመያዝ ቀና ማለት 
አልፎ አልፎ ብቅ ሲል የነበረው በ ሙስሊሙ ሃይማኖት ስም የሚንቀሳቀሰው ''የ ሙስሊም ፅንፈኛ ቡድን'' ከ ቢጫ ቀጥሎ ይወሰዳል ለተባለው እርምጃ የመሪነት ሚናውን ለመያዝ ቀና ቀና ማለቱ አይቀርም።በ ኢትዮጵያ ከ ቅርብ አመታት ወዲህ በ ጅማ፣ሐረር፣እልባቦር እርሲ ወዘተ እነኝህ ፅንፈኛ ቡድኖች በ አብያተ ክርስትያናት እና ምእመናን ላይ ጥቃት ሲፈፅሙ እንደነበር ይታወሳል።በመሆኑም  የ ሙስሊም ወንድሞቻችን እና እህቶቻችንን የማይወክሉ ግን ለ እራሳቸውም እንግዳ ትምህርት ይዘው የመጡባቸው  ክፍሎች የ እዚህ አይነቱን  ቀይ ካርድ መምጣት ''ሰርግ እና ምላሽ '' አርገው እንደሚመለከቱት ሳይታለም የተፈታ ነው። እዚህ ላይ በ ነሐሴ ወር ላይ የ ''አልሸባብ'' ሰዎች ሳይሆኑ አይቀሩም የተባሉ በ ከፍተኛ ደረጃ የታጠቁ ቡድኖች  በሞያሌ ከተማ ላይ ያደረጉት ጥቃት አይዘነጋም።
  •  በ አፍሪካ ቀንድ ለዘመናት ችግር ሲፈጥር የነበረው አለም አቀፍ አክራሪ እስልምና መነቃቃት ይጀምራል።
  
 አፍሪካ ቀንድ ለዘመናት ችግር ሲፈጥር የነበረው አለም አቀፍ አክራሪ እስልምና በመነቃቃት  ኢትዮጵያውያን  ፅንፈኝነት አስተሳሰብ ያላቸውንሙስሊሞች  መንግስት ስልጣን ጥያቄ እንዲያነሱ እና ኢትዮጵያ ''እስላማዊ መንግስት'' እንዲኖራት ወደሚል ግብ እንዲሄዱ ይህን ካደረጉ ብቻ  ጎናቸውእንደሚቆም ግፊቱን ሊያደርግ ይችላል። ይህንን ደግሞ ብዙ ሙስሊም ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን አይደግፉትም።  እዚህም ነው ጥያቂያቸውን ጥንቃቄ እና  ሰላማዊ መንገድ ብቻ  ማቅረብ ብዙውን ሕዝብ ያስደመሙት።  እዚህ በተጨማሪ  አለም አቀፍ ፅንፈኛ  እስልምና እንቅስቃሴ ኢትዮጵያ ቦታ ካገኘ ሁለት መሰረታዊ ክስተቶች  ሀገራችን ላይ ሊያመጣ ይችላል። እነርሱም አንድ  ሃያላኑ መንግሥታት ጣልቃ ገብነት ቢያንስ  ቁሳቁስእና  ቴክኒክ እርዳታ ነገሩን ማወሳሰብ እና ሁለተኛው  እስልምና ውጭ በሆነው ኢትዮጵያዊ ጋር ከፍተኛ ፍጥጫ ውስጥ መክተቱ የሚሉት ይጠቀሳሉ።'' (ጉዳያችን ጡመራ ጥቅምት/2004 ዓም http://gudayachn.blogspot.no/2012/10/blog-post_5.html ) 

ዛሬ ጀዋርም ሆነ ሃጅ ነጂብ መሐመድ እያመላከቱን ያሉት ይህንኑ ነው።የዲሞክራሲ ጥያቄን በድምር የመመለስ አባዜ ማለትም ችግሩ የብሔር እገሌን ችግር መፍታት፣የሃይማኖት እገሌን ችግር መፍታታ፣ ወዘተ የሚሉ የአምባገነንነትን መጫኛ ፈረስ ማዘጋጀት የተበላ ዕቁብ ከመሆን አያልፍም።ጀዋርም ሆኑ ሃጅ ነጂብ መሐመድ በመኖሶታው መድረክ ሊነግሩን የፈለጉት ''ውሃ ቢወቅጡት እምቦጭ'' መሰል ላለፉት ሃያ አንድ አመት ስንሰማው የነበረውን ''ኢትዮጵያን በብሄር ከፋፍሎ አላማን ማሳካት'' የሚለውን ያፈጀ መዝሙር መሰል ማላዘን ነው።እነርሱ የጨመሩበት ነገር ቢኖር ''በኦሮሞ ስም የታሸ አዲስ እስልምና'' ያለ መሆኑን ለመናገር ደፋርነት ማሳየታቸው ነው። ይህ ሂደት በእራሱ በወንድማማችነት የኖረውን የእስልምናውን ሃይማኖት የሚጣረስ እና በሃይማኖቱ ብሔር ብቻ ሳይሆን የሀገር ድንበር የማይገድበውን በአለማችን ካሉት ታላልቅ አምነቶች አንዱ -እስልምናን እንደነርሱ አገላለፅ ''በኦሮሞነት'' ስር መሸበብ ነው።

በመሰረቱ የኢትዮጵያ የእውነተኛ ዲሞክራሲ ጥያቄ በግለሰቦች ''ሜጫዊ'' ''ቁረጠው!ፍለጠው!'' ንግግር እና ጣልያን ኢትዮጵያን ሲወር በተጠቀበት መርዛማ ንግግር ብሄርን ከብሄር አልያም የሃይማኖት ተከታይን ከሃይማኖት ተከታይ በማበላለጥ አይሰናከልም። በብሄር እና በሃይማኖት ለመከፋፈል የቆሙ የመኖራቸውን ያህል ለኢትዮጵያ አንድነት እና ለእምነቶች መከባበር የቆሙ ሚሊዮኖች ኢትዮጵያ እንዳላት መዘንጋት አይገባም።የጀዋር መሐመድ እና የሃጅ ነጂብ መሐመድ ንግግር ግን የመብት፣የዲሞክራሲ እና የአንድነት ትግሉን ጠልፎ ወደ አለተፈለገ አቅጣጫ የመግፋት የግል ስሜታቸውን ከመግለፅ ባለፈ የሚያመጣው አዲስ ነገር አይኖርም። ይልቁን ''ሆድ ያባውን ንግግር ያወጣዋል'' የሚል ስያሜ መስጠት ግን የሁለቱን ንግግሮች በበቂም ባይሆን በመጠኑ የሚገልፀው ይመለኛል።
 በመጨረሻም የጀዋር መሐመድ እና የሀጂ ነጂብ መሐመድን ንግግር ይመልከቱ።




ጉዳያችን GUDAYACHNgetachewb221@gmail.com

Thursday, December 26, 2013

ድንበር የማይቀዘቅዝ ትኩስ ደም ነው። የኢትዮጵያ እና የሱዳን የድንበር ውል ዝርዝር ጉዳይ ከሕዝብ ሊደበቅ አይገባም።

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከሁለት ሳምንት በፊት በሱዳን ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል።በእዚህ ጉብኝት ላይ አቶ ኃይለማርያም ''እጅግ ለም የሆነ  የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን ለመስጠት ተስማምተዋል አሁን የቀረው ችካል ማስቀመጥ ነው'' የሚል ዜና በኢሳት ሲዘገብ ቀናት ነጉደዋል።ትናንት ታህሳስ 16/2006 ኢሳት በአለም አቀፍ ራድዮ ስርጭቱ ላይ የኢትዮጵያ የድንበር ጉዳይ የሚከታተሉ  'የኢትዮጵያ ድንበር ኮሚቴ' የተሰኘ ኮሚቴ አባላትን በቃለ መጠይቅ አቅርቦ ነበር።እንደ ኮሚቴው ገለፃ ከሆነ አሁን ''የኢትዮጵያ መንግስት ለሱዳን  ለመስጠት መስማማቱ የሚነገረው መሬት ከቀድሞ ጀምሮ በኢትዮጵያ ይዞታ ላይ ያለ አሁንም  ገበሬዎች የሚገኙበት እና ባዶው ቦታን ጨምሮ በትንሹ ካለምንም ማጋነን 15 ሚልዮን ሕዝብ አስፍሮ መመገብ የሚችል ቦታ ነው።15 ሚልዮን ልብ በሉ! 

በሕዝብ ስም የሚደረግ ማንኛውም ውል ከህዝብ ሊደበቅ አይገባውም።ድንበር የማይቀዘቅዝ ትኩስ ደም ነው።ይህ ደም ደግሞ ለዘመናት የኢትዮጵያ አባቶች እና እናቶች ያፈሰሱት ደም ነው።ማንም መንግስት በሕዝብ ደም ሊደራደርም ሆነ ድንበር ሊሰጥ አይችልም።ለአንድ 'ኩርማ' መሬት 'ለባድሜ' በሺዎች ላረገፈ ጦርነት ክተት ያወጀ  መንግስት 15 ሚልዮን ሕዝብ የሚያሰፍር መሬት ለሱዳን ለመስጠት መነሳቱ በቁም እየተሸጥን ለመሆኑ ማሳያ ነው። በትዊተር በብዛት የሚታዩት ባለስልጣናት ከሌላው ዜና ይልቅ የእዚህ አይነቱን ቅድምያ ሊሰጡት በተገባ ነበር።ድንበር የማይቀዘቅዝ ትኩስ ደም ነው።
ፊልሙ  መጨረሻ ላይ ሲናገር የምትመለከቱት የስርዓቱ አቀንቃኝ ይመስላል።በጋራ ''አሸባሪዎችን ይዋጋሉ'' የሚለው ጌቶቹ መሬቱን ሸጠው እንደጨረሱ በገደምዳሜ እየነገረን ነው።በመጀመርያ እንደዚህ አይነት አካባቢ አገር ጎብኚ ሲመጣ  እንዲያስተናግድ የሚፈቀድለት የስርዓቱ  ሹም ነው።በመሆኑም በጋራ ድንበር እየጠበቁ ነው ይለናል።አገር ጎብኝዋ ግን ''እህ!'' በማለት ውሸቱን ማወቅ መቻሏን ትገልፃለች። 



ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

Wednesday, December 25, 2013

ከትዝታዬ


ከትዝታዬ የሚሉ በጣም አጫጭር ጽሁፎች አልፎ አልፎ ጣል ለማድረግ ማሰቤን ልግለጽና ለዛሬ ይህችን ላካፍላችሁ። በደርግ መውደቅያ ዘመን አካባቢ አዲስ አበባን የምናውቃት በታክሲ ውስጥ፣በትምህርት ቤት፡ መምህራን፣ ካፌ ቤት፣ሰራተኞች ከስራ ባልደረቦቻቸው ጋር  በነጻነት (ሌላውን ነጻነት ትተን) በትግርኛ፣ኦሮምኛ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ይናገሩ ነበር።

ከሚኒባሱ ጋቢና የተቀመጠ ሰው ከኋላ ለተቀመጠ ወዳጁ በትግርኛ ድምጹን ከፍ አድርጎ ያወራ ነበር።በአውቶቡስ ውስጥም ኦሮምኛ ሆነ ጉራጊኛ ህዝቡ ካለ አንዳች መሳቀቅ ይናገር ነበር። ሁሉም ተከባብሮ ይኖር ነበር።ሌላ ቋንቋ ለመናገሩ አንዳች መሳቀቅ አይሰማውም።

ዘመኑ በደንብ ትዝ ይለኛል 'ጋሽ ተስፋ ጽዮን' የሚባሉ የሳይንስ መምህር ትምህርት ቤታችን ውስጥ ቮሊቮል መጫወት ይወዱ ነበር።ሲጫወቱ በትግሪኛ እያውሩ ነበር ኳሱን የሚሰርቡት... ጋሽ መገርሳ የእስፖርት አስተማሪያችንን አልረሳቸውም ኦሮምኛ የሚችሉ ልጆች ጋር በኦሮምኛ ይቆጧቸው ነበር፣ ኮሜርስ ስገባ ጎይቶም የሚባል በጣም የማዝንለት ጓደኛ ነበረኝ።ጎይቶም የአክሱም ልጅ ነው።አባቱ በህወሃት እስር ቤት መሆኑን ከእናቱ ጋር ወደ አዲስ አበባ መምጣቱን ይነግረን ነበር።ጎይቶም ትግሪኛ ሲናገር ባይገባንም ጓደግኞቹ የተለየ ንግግ ር የተናገረ ያክል አይሰማንም።እርሱም ደስ ብሎት አውርቶ ቀጥሎ ወደ እኛ ዞሮ አማርኛ ያወራናል... አዲስ አበባ ንግድ ስራ ኮሌጅ ሬጅስትራር ክፍል ስንሄድ ኦሮምኛ የሚናገሩ ሰራተኞች ብዙ ነበሩ።ይህ ቢሮ ውስጥ ነው የማወራው። ማንም ቅር አይለውም።ልዩነትም የለውም።

... መከላከያ ፊት ለፊት ያለው ትልቁ ኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ለስራ ልምምድ ስላክ ብዙ አለቆች የእረጅም ጊዜ የስራ ልምድ ያላቸው የተከበሩ አባቶች የሚባሉ የትግራይና የኤርትራ ተወላጆች ነበሩ።በሻይ ሰኣት ሁሉም ዘና ብለው በትግሪኛ ያወራሉ ይጫወታሉ።ሁላችንም 'ጋሼ እትዬ' ብለን የታዘዝነውን እንሰራ ነበር... ብላቴ ስንሄድ ብዙ የተለያዩ ቋንቋ ተናጋሪዎች በየቋንቋቸው ይናገሩ ነበር።
ይህ ውበት ዛሬ ኢትዮዽያ የራቃት ይመስለኛል። ህዝቡን ጎሰኞች ስለ ጎሳ ብዙ በማውራት አሳቀቁት። ዛሬ ስለ ጎሳ አብዝቶ የሚያወራው መንግስት ከመጣ ወዲህ ወገኔ ተሳቀቀ።ነቀምት ሲገባ አማርኛ መናገር፣ጉራጊኛ ማውራት ተሳቀቀ።አዲስ አበባ ሲገባ ከ አራዳ ቋንቋ ሌላ ማውራት የሚያሳቅቀው ሆነ። የጎሳን ነገር  መንግስት ቤተ መንግስት አስገብቶ እንደፈለገው አብኩቶ ህዝቡን አሳቀቀው።ህዝቡ የእራሱ የሆነ የመከባበር ዘይቤው ጠፋው።ዘረኞች ፋታ አገኙ።ህዝቡን ናኙበት።ዛሬ በነጻነት ድምጹን ከፍ አድርጎ የሚያወራው አዲስ አበባ ላይ  በስደት ላይ የሚገኙ ሱማሌዎች ብቻ ሆኑ።እነርሱ ታክሲ ውስጥም ጮክ ብለው ያወራሉ።ሌላው አፈረ።ይህች ነች የብሔር ብሄረሰብ መብት? ሕዝብ መከፋፈል ለስልጣን ጥበቃ።

ታህሳስ 16/2013 ዓም 


Sunday, December 22, 2013

የኢትዮዽያ መጪው ትውልድ ሳይንቲስቶች እና አላማዎቻቸው (ቪድዮ)




ከሰይፉ ፋንታሁን ኢቢኤስ ዝግጅት የተገኘ

ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

Thursday, December 19, 2013

ሰበር ዜና-በደቡብ ሱዳን የሪክ ማቸር ኃይሎች ውግያ ጀመሩ። ትናንት ምሽት ቁልፏን ከተማ ቦርን ተቆጣጠሩ።ኢትዮጵያና ዑጋንዳ በደቡብ ሱዳን አንፃር (ጉዳያችን አጭር ዘገባ ታህሳስ 10/2006 ዓም)


ደቡብ ሱዳን ቦር ከተማ (photo Reuters)

በደቡብ ሱዳን የተቃዋሚ ኃይሎች ከሀገሪቱ ዋና ከተማ ጁባ በ 200 ኪሎሜትር  እርቀት ላይ የምትገኘውን 'ቦር' የተሰኘችውን ቁልፍ የደቡብ ሱዳን ከተማ ተቃዋሚ ኃይሎች መቆጣጠራቸውን የከተማዋ ከንቲባ ንሂሃል ማጃክ ለቢቢሲ ረቡዕ ታህሳስ 9/2006 ዓም አስታውቀዋል።
ፊሊፕ አጐር የተሰኙ የመንግስት የጦር ኃይሉ ቃል አቀባይ በሌላ በኩል ''ወታደሮቻችን በከተማዋ የነበራቸውን የበላይነት ለሪክ ማቸር ኃይሎች አስረክበዋል'' ብለዋል።ሪክ ማቸር የቀድሞ የደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝዳንት እና በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተሳትፈዋል ተብለው በሱዳን መንግስት እየተፈለጉ መሆናቸው ይታወቃል።

በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ከትናንት በስትያ በተሞከረ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ እንደ ተባበሩት መንግሥታት ዘገባ 500 ሰዎች ሲገደሉ ከ 20 ሺህ የማያንሱት ከመኖርያ ስፍራቸው ተፈናቅለው በተባበሩት መንግሥታት ግቢ ውስጥ እንዲጠለሉ ያደረገ ሲሆን ቁጥሩ ከእዚህም እንደሚልቅ ይገመታል።

በደቡብ ሱዳን ካሉት ትልልቅ ጎሳዎች ውስጥ የኑዌር እና ዲንቃ ጎሳዎች ሲጠቀሱ። የመፈንቅል ሙከራውን ያደረጉት ሪክ ማቸር የኑዌር ጎሳ ሲሆኑ ከመንግስት በኩል የተሰለፉት አብዛኞቹ የዲንቃ ጎሳ መሆናቸው ይነገራል።ጎሳዎቹ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ሰሜን ምዕራብ ኬንያ እና ሰሜናዊ ዑጋንዳ ጋር ድንበር ከመጋራት አልፎ ተመሳሳይ ጎሳዎች ከመኖራቸው አንፃር ሲታይ ጉዳዩ የአካባቢው ፖለቲካ ላይ የሚኖረው አንደምታ ቀላል ላይሆን ይችላል።

 በዑጋንዳ ካምፓላ የሚታተመው ትልቁ የዑጋንዳ ጋዜጣ ''ዘ ኒው ቪዥን'' በዛሬ ማለዳ እትሙ ላይ የዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሰቬኒ የደቡብ ሱዳንን ግጭት እንዲሸመግሉ የተባበሩት መንግሥታት መጠይቁን ዘግቧል።በደቡብ ሱዳን ጉዳይ ከሁሉ በተሻለ ተፅኖ የመፍጠር አቅም የሚኖራት ምናልባትም በጉዳዩ ላይ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ እጇ ሊኖር ይችላል ተብሎ የሚገመተው ዑጋንዳ ነች።የዑጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ አሁን ውግያ ለጀመረው የርክ ማቸር ኃይል መጠለያ ለመስጠትም ሆነ ስንቅ እና ትጥቅ ለማቀበል ብቸኛ አማራጭ የመሆናቸው ዕድል ትልቅ ነው።

የኢትዮጵያን ሚና ስንመለከት ግን መንግስት በሁለት አጣብቂኝ ውስጥ የገባ ይመስላል። በአንድ በኩል የሰሜን ሱዳን ወዳጅነት እንዳይደፈረስ በሌላ በኩል በደቡብ ሱዳን ያለው ጥቅም እንዳያመልጥ።የኢትዮጵያ አየርመንገድ በረራን ጨምሮ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጁባ ቅርንጫፍ እስከ መክፈት ድረስ የደረሰ የንግድ ግንኙነት ያላት ኢትዮጵያ የአሁኑን ሁኔታ በጥንቃቄ የምታየው ብቻ ሳይሆን ኢህአዲግ በሌለው ብቁ የአካባቢያዊ ፖለቲካ ትንተና ሁኔታ አንፃር  በነገሮች ላይ ውሳኔ የመስጠት ዘገምተኝነት እና የተንዛዛ የውሳኔ አሰጣጥ ሰንሰለት መርዘም ሊኖር እንደሚችል መገመት ይቻላል።

በአቶ መለስ ጊዜ ውሳኔዎችን እራሳቸው ስለሚሰጡ እና ግልፅ መስመር በማሳየት  በኩል የተሻለ ሁኔታ በአካባቢያዊ ዲፕሎማሲ ላይ ይታይ የነበረ ለመሆኑ የማይታበል ሀቅ ነው።የሱማሌው ጉዳይ ላይ አቶ መለስ የአሜሪካንን ፍላጎት የሚያረካ አቅጣጫ  የ1997 ዓም ምርጫ ማጭበርበር አንፃር ለተነሳው ሕዝባዊ አመፅ የአሜሪካንን ድጋፍ ያገኙበት መሆኑ የሚታወቅ ነው።

በደቡብ ሱዳን ጉዳይ ላይ የብዙ ጥቅም ተጋሪ የሆኑት የኢህአዲግ የጦር ሹማምንት እና አንዳንድ ባለስልጣናት ውሳኔውን ከንግድ ጥቅማቸው አንፃር ብቻ እንዳይመዝኑ እና ሃገርን ለባሰ ጉዳት እንዳይዳርጉ የብዙዎች ስጋት ነው።ከሰሜን ሱዳን ጋር ያለውን ወዳጅነት ለማቆየት ብዙ ለም መሬት በመስጠት የሚታወቀው ኢህአዲግ ደቡብ ሱዳን ላይ የሚይዘው አቅጣጫ በቅርቡ የሚታወቅ ይሆናል።

እዚህ ላይ ሊሰመርበት የሚገባው ጉዳይ ግን ምንም አይነት የመንግስት ለውጥ በደቡብ ሱዳን ውስጥ ቢፈጠር ወይንም ያለው መንግስት ለተወሰነ ጊዜ እየተንገዳገደም መቆየት ቢችል ኢትዮጵያ ከሰሜን ሱዳን ወይንም ከደቡብ ሱዳን አንዳቸውን የመደገፍ አዝማምያ ለማሳየት ባትፈልግም የምትገደድበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል።አሜሪካ አንዳንድ ጊዜ ብዙም ሀብት እና ስትራተጅያዊ ጥቅም የላቸውም ላለቻቸው ለትልልቅ የህዝብ ስደት እና ግጭቶች ጆሮዋን የማትሰጠው ን ያክል ለደቡብ ሱዳን በከፍተኛ ባለሥልጣኗ አማካይነት በጉዳዩ ላይ ሃሳቧን ሰጥታለች።

አሜሪካ ለጊዜው ጉዳዩ ላይ በቀጥታ መግባት ባትችልም የአካባቢው ሃገራትን '' 'ቀኝ እጄን ሰጥቻለሁ'  እንደእኔ ሆነህ ይህንን አድርግ'' የምትለው ሀገር የሚታዩዋት ምናልባት ኢትዮጵያ እና ዑጋንዳ ብቻ ናቸው።ኢትዮጵያ ደግሞ በአሜሪካ ፍቃድ ብቻ ላለመሄድ የሚያደርጋት የሱዳን ፊት አለ።ሱዳን ተፅኖ ለመፍጠር በኤርትራ የሚገኙ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎችን መሸጋገርያ እንዳትሰጥ ያሰጋል።በመሆኑም ኢትዮጵያ በደቡብ ሱዳን ጉዳይ እንደ ሱማሌው ችግር ሙሉ በሙሉ የመግባቷ አዝማምያ እምብዛም አይታይም።ለዑጋንዳው ዩዌሪ ሙሰቨኒ ግን ሰርግ እና ምላሻቸው ነው።

ጉዳያችን ታህሳስ 10/2006 ዓም
የጉዳያችንን ዘገባ በድህረ ገፅዎ ላይ ሲያወጡ ያገኙበትን ምንጭ  መግለፅ ጨዋነት ነው።

Wednesday, December 18, 2013

የኢትዮጵያ ኢንተርኔት አገልግሎት የዘመኑን ሉላዊነት (globalization) የመወዳደር አቅሙ በአሳዛኝ ደረጃ ወርዷል።



በአንድ ወቅት ላይ ያለ መንግስት የሚሰራው ስህተት ወይንም ብቃት በሌለው አሰራር ሳብያ የሚያስከትለው ችግር አሁን ካለው ትውልድ ተሻግሮ ለመጪው ዘመናትም የማይለቅ ተከታታይ ችግሮችን ይዞ መምጣቱ አይቀርም።ባለፈው ወር ላይ አዲስ አበባ ላይ በተደረገ የአፍሪካ  የኃይል አጠቃቀም ላይ አንድ ምሁር ባቀረቡት የጥናት ፅሁፍ ላይ የተናገሩት በአንድ ትውልድ ዘመን ያለ መንግስት ደካማ አሰራር ምን ያህል ተከታታይ ትውልዶች ላይ ጠባሳ እንደሚያስከትል የሚያመላክት ነው።ምሁሩ ''አፍሪካ'' ይላሉ ''አፍሪካ የኢንዱስትሪው አብዮት ተሳታፊ ሳትሆን አለፋት፣ቀጥሎም የመረጃ ቴክኖሎጂ (information technology-IT) በአግባቡ ሳይደርሳት አለፈ አሁን ደግሞ አረንጓዴ ኃይል ዘርፍ ተጠቃሚ ሳትሆን እንዳያልፋት ያሰጋል'' ብለዋል። ይህ ጉዳይ ኢትዮጵያንም ይመለከታል።

የኢንተርኔት አገልግሎት ቁልፍ እና የሁሉም የምጣኔ ሀብት ዘርፎችን የማንቀሳቀስ አቅሙ ቀላል አይደለም።የኢንተርኔት ዘርፉ ቢያንስ በውጭ የሚኖሩ እና በሀገር ውስጥ ያለ የግል ዘርፉን የማሳተፍ እድሉ በእጅጉ ከመጥበብ አልፎ እጅግ አደገኛ በሆነ መንገድ እና  ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ለቻይና ኩባንያዎች ስራውን እያስተላለፈ መምጣቱ ሌላው አሳሳቢ ተግባር ነው።

ጂ-4 የተባለው የአራተኛው ትውልድ ቴክኖሎጂ ሥራ ጨምሮ ቻይና ሙሉ በሙሉ እጇን በኢትዮጵያ ውስጥ አስገብታለች።ሲሶው እጅ በቻይና መንግስት ሽርክና መያዙ የሚነገርለት የቻይና የቴሌኮምዩኒኬሽን  ዜድቲ ኢ (ZTE)  ለኔትዎርክ ሥራ ብቻ እስከ 1.3 ቢልዮን ዶላር የሚደርስ ውል እንዲፈርም መደረጉ የሚታወስ ነው።የእዚህ አይነት ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በአግባቡ ዓለም አቀፍ ጨረታ አውጥቶ ደረጃቸውን የጠበቁ ኩባንያዎችን ከማሳተፍ ይልቅ ግልፅነት የጎደላቸው ጨረታዎች ሥራ ላይ መዋላቸው ተለምዷል።ይህ አይነቱ ድርጊት እራሳቸውን የቻሉ ተያያዥ ችግሮችን ብቻ ሳይሆን ለተከፈለው ክፍያ ተገቢው እና ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመገኘቱ ዋስትና መጥፋቱ ሌላው ችግር ነው።ከእዚህ በተጨማሪ ቻይና የሀገራችንን የፖለቲካም ሆነ ምጣኔ ሃብታዊ ጉዳዮች ላይ እጅ የመጠምዘዝ አቅሟን የማሳደጉ ጉዳይ ሳይረሳ ነው።

ይህ ሁሉ ሆኖም ግን የ 2013 ዓም ''ፍሪደም ሃውስ'' ዓለም አቀፍ የመረጃ መረብ እና ዲጂታል መገናኛ ዳሰሳ ሪፖርቱ መሰረት ኢትዮጵያን ከመጨረሻዎቹ ተርታ ሃገራት መካከል ፈርጇታል። የመረጃ መረብ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ  የዘመኑን  የሉላዊነት ተግዳሮትን ለማሸነፍ ቁልፍ ከመሆኑ አንፃር ሪፖርቱ  ለሀገራችን ብዙ ማለት ለመሆኑ አያጠራጥርም።ከሰማንያ ሃገራት ውስጥ የመንን ብቻ እንደምንበልጥ መስማት ሌላው እራስ ምታት ነው።በሀገርቤት በኢህአዲግ እና በኢቲቪ የሚቀርበው ሪፖርት ግን ፈፅሞ እውነታውን አያመላክትም።በነገራችን ላይ ሪፖርቱ መረጃቸው ያልተገኘ ያላቸው ጥቂት ሃገራትን አላካተተም።ከእነዚህም ውስጥ ኤርትራ ትገኝበታለች።

ሙሉውን ሪፖርት ለማንበብ ይህንን ድህረ ገፅ ይክፈቱ።
http://freedomhouse.org/sites/default/files/resources/FOTN%202013_Full%20Report_0.pdf 

Tuesday, December 17, 2013

''ኢትዮጵያ ማንዴላን አዳነች'' የደቡብ አፍሪካ ኤስ ኤ ቢሲ ቲቪ ልዩ ቃለ መጠይቅ ከሻምበል ጉታ ዲንቃ ጋር (ቪድዮ) Ethiopia saved Mandela-SABC TV VIDIO

In 1962 Former President Nelson Mandela secretly travelled to Ethiopia for military political and spiritual training under the name of David Motsamai. Haile Selassie's Ethiopian army, on the orders of Haile Selassie himself first trained and armed Nelson Mandela in his struggle against apartheid South Africa.

On the personal orders of his Majesty, the Ethiopian Colonel in charge of Mandela's military training gave him a gun with which he was to bring down the ignoble and unhappy apartheid regime still thriving at that time in South Africa. Mandela went back to South Africa to continue his struggle. The rest is history.

One of the things that Madiba recently learned is that while he was in Ethiopia , the aparheid government knew where he was and had paid his menders to kill him.We are joined now by Captain Guta Dinka who not only looked after Madiba while he was in Ethiopia but was ordered to kill Madiba. He is with Prof Mamo Muchie who will do the translation for us.



ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

Sunday, December 15, 2013

''ፖለቲካ ሀጢአት ነው ወይ? '' የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሊቅ አጭር እና ግልፅ ምላሽ

በሳምንቱ መጨረሻ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን ወደ ደብረዘይት ደብረ መድሃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስያን  ባዘጋጀው የመንፈሳዊ ጉዞ ላይ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ምዕመናን ተሳትፈዋል።መርሃግብሩ ላይ ከምዕመናን እና በቀጥታ በማኅበራዊ ድህረገፆች ለአባቶች የጥያቄ እና መልስ መርሃግብር ተዘጋጅቶ ነበር። ለተነሱ ጥያቄዎች ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምላሽ መስጠታቸው ከማኅበሩ የፌስ ቡክ ገፅ ላይ የተገኘው መረጃ ይገልፃል።ምእመናን ከእንደዚህ አይነት መርሃግብሮች እና ከሊቃውንቱ ቀጥተኛ እና  ትክክለኛ መረጃ ማግኘታቸው  ትልቅ ዋጋ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው።

ከገፁ ላይ የተገኘውን ከእዚህ በታች እንዲህ ይነበባል-

''ቀጥሎ የሚኖረን መርሐ ግብር የጥያቄና መልስ መርሐ ግብር ሲሆን ሊቃውንቱ መልአከ ታቦር ተሸመ ዘሪሁን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ አባል፤ መጋቤ ሐዲስ ደጉ ዓለም ካሣ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲሳት ትርጓሜ መምህር፤ መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ በቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የብሉይና የሐዲስ ትርጓሜ መምህር፤ ሲሆኑ ከምዕመናን ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ደግሞ በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ አቅራቢነት ያስተናግዳሉ፡፡ በዚህ አጋጣሚ ይመለስልን የምትሉት ጥያቄ ካላችሁ በውስጥ መስመራችንም ሆነ በ ኢ-ሜላችን ብትሉክልን እናስተናግደዋለን፡፡
……………………

ጥያቄ 2 . ቅዱስ ጳውሎስ ሀገራችን በሰማይ ነው ስላለ እኛ ክርስቲያኖች በምድራዊት ሀገራችን ላይ እንዴት እንስራ?


እግዚአብሔር ሰማይ ዙፋኔ ምድርም የእግሬ መረገ ናት እንዳለ አሁን ዛሬ ተቀምጠን የምንዘምርበት፣ የምንማርበት፣ የምናመሰግንበት፣ ይሄ ምድርም የእግዚአብሔር ፍጥረት ስለሆነ ሰው ለሀገሩም ሊሰራ ሊሞት ይገባዋል፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በአድዋ ድል የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ሱታፌ ማስታወስ በቂ ነው፡፡ መልአከ ታቦር ተሸመ ዘሪሁን የሊቃውንት ጉባኤ አባል
……………………..

ጥያቄ 4 ፡ ፖለቲካ ሀጢአት ነው ወይ?

ሰው በዚህ አለም ሲኖር ከሀጢአት በቀር በአለም ያለው ሁሉ ይመለከተዋል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ እነ ዳዊት፣ እነሰሎሞን ፖለቲከኞች ነበሩ ስለዚህ ሀጢአት አይደለም ሀጢአት የሚሆነው አያያዙን ማወቅ ሲያቅት ነው፡፡ ወተት መጠጣት ሀጢአት አይደለም በረቡዕ ከተጠጣ ግን ሀጢአት ይሆናል፣ ቢላዎ ባለሞያ ሴት ካገኘችው ያገለግላል ባለጌ ካገኘው ሰው ይጎዳበታል ፖለቲካም አያያዙን ካወቅንበት ሀጢአት አይደለም፡፡ መጋቢ ሐዲስ እሸቱ ዓለምዓየሁ በቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የብሉይና የሐዲስ ትርጓሜ መምህር።''
በጉባኤው ላይ ከታደሙት ምዕመናን በከፊል 



ምንጭ - https://www.facebook.com/mkidusan



Saturday, December 14, 2013

የአኝዋክ ጎሳን እልቂት ችግር ጉዳይ ከባዕዳን እጅ እንዲወጣ የኢትዮጵያውያን ንቁ ተሳትፎ ያስፈልጋል፣ የአቶ ኦባንግ ሜቶ ክቡር ተግባርም ሊደገፍ ይገባል።ማስታወሻው የአቶ ኦባንግ ሜቶን ቪድዮ ቃለመጠይቅ ይዟል።

 አቶ ኦባንግ ሜቶ

በጋምቤላ አኝዋክ ጎሳ ላይ በጅምላ እልቂት የተፈፀመበት እና ከ 400 በላይ አኝዋኮች የተገደሉበት( ታህሳስ 13/2003 ዓም እ ኤ አቆጣጠር) አስረኛ ዓመቱን ደፍኗል።በተለያዩ ወገኖች ስለ እልቂቱ የሚዘገቡት ዘገባዎች የድርጊቱ እጅግ ዘግናኝነት ያወሳሉ።ጉዳዩን ነፃ የዲሞክራሲ ስርዓት በሀገራችን ቢኖር ኖሮ በግልፅ ውይይት ከእየጎሳው የተውጣጡ ሽማግሌዎችን በማደራጀት በካሳ እና በይቅርታ በጉዳዩ ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የተሳተፉ ወንጀለኛ ባለስልጣትና (በየትኛውም የስልጣን እርከን ላይ ቢሆኑ) ለፍርድ እንዲቀርቡ በማድረግ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ በደሉን ለመዝጋት መሞከር ከአስተዋይ መንግስት የሚጠበቅ ተግባር ነበር።ይህ ግን አልሆነም።ይልቁን በመንግስት በኩል ችግሩን የባሰ ማድበስበስ እንደአማራጭ ተወስዷል።

ይህ እልቂት ከኢትዮጵያውያን ይልቅ በባዕዳን ብዙ ሲባልለት ይሰማል።ሆኖም ግን የእራሳችንን ችግር እና የሰብአዊ መብት ጉዳይ በተገቢው መንገድ ማሰብ መዘከር የሚገባን እኛው ነን።ባዕዳን ጉዳዮችን የሚያነሱበት መንገድ እራሱን የቻለ ችግር ይዞ ይመጣል። ምክንያቱም ችግሮቻችንን፣ህመማችንን እና ቁስላችንን የሚነግሩን ከእራሳቸው ስልታዊ ጥቅም አንፃር ነው።በመሆኑም በተለይ በባህር ማዶ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የአኝዋክን እልቂት ሻማ በማብራት ከተጎዱት ጎን በመሆን ማፅናናት እና በመሳሰሉት መርሃግብሮች ማሰብ የወቅቱ  አንገብጋቢ ተግባራቸው መሆን ይገባዋል።

አቶ ኦባንግ ሜቶ በጋምቤላ አኝዋኮች ላይ የተፈፀመውን ግፍ ለዓለም ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ከሚያሰሙት መካከል ናቸው።አቶ ኦባንግ ጉዳዩን የሚያነሱበት ጥግ እራሱ ከጎሳ ጉዳይ አውጥተው ''ችግሩ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ነው።የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ችግር ሲፈታ የጋምቤላውም፣ የአፋሩም ወዘተ ችግር ይፈታል'' ብለው የሚያምኑ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ናቸው።አቶ ኦባንግ ሜቶ ይህንን ሃሳባቸውን ወደ ተግባር ለመቀየር ''የአዲሲቱ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ'' የተሰኘ ብሔራዊ አላማ ያለው ድርጅት መስርተው ይንቀሳቀሳሉ።

የአኝዋክ ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ ነው።ከዋሽግተን እስከ አውስትራልያ ያሉ ኢትዮጵያውያን ቢያንስ ይህንን እልቂት ሻማ በማብራት መዘከር ይገባቸዋል።በሀገርቤትም ያሉ  ችግሩ መነሻው ከጎሳ ግጭት ተነስቶ መንግስት ወገን የያዘበት ጉዳይ መሆኑ ከትውልድ ወደትውልድ  ሲቆይ ይዞ የሚመጣው የእራሱ የሆነ ቅርፅ በተለይ ባዕዳን በአካባቢው ካላቸው የሀብት ፍላጎት አንፃር ለማወሳሰብ መጣራቸው ስለማይቀር የሲቪል ማህበራት እና የሃይማኖት ተቅዋማት ችግሩን በሽምግልና ለመፍታት ቢያንስ ሂደቱን ዛሬ መጀመር ይገባቸዋል።

ከእዚህ በታች ባለ ቪድዮ ላይ የተከበሩ አቶ ኦባንግ ሜቶ ስለ ኢትዮጵያ  ይናገራሉ።ቃለ መጠይቁ  በኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን (ኢሳት) ''ምን አለሽ  መቲ'' ከተሰኘ መርሃ ግብር የተወሰደ ነው።



ጉዳያችን GUDAYACHNgetachewb221@gmail.com

Thursday, December 12, 2013

አንዳንድ አፍቃሪ ወያኔዎች በአፄ ምንሊክ ላይ በአድዋ ጦርነት ወቅት ወደ ኢትዮጵያ ከዘመቱት የኢጣልያ መኮንኖች እኩል ጥላቻ አላቸው የታህሳስ 3/2006ዓም (አጭር ማስታወሻ)


ዛሬው ታህሳስ 3/2006 ዓም የንጉሰ ነገስት ዳግማዊ አፄ ምንሊክ 100ኛ ዓመት እና የፊት አውራሪ ሃብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ 87ኛ ዓመት የእረፍት መታሰብያ እለት ነው።

-  በፌስ ቡክ እና በሌሎች የማህበራዊ መገናኛ መስመሮች መንግስት እና የመንግስት ደጋፊዎች በዳግማዊ ምንሊክ ላይ የስድብ ውርጅብኝ ሲያወርዱ ውለዋል።ለምሳሌ ዳንኤል ብርሃነ የተሰኘ የኢህአዲግ ካድሬ (በኢቲቪ ሚድያ ዳሰሳ ላይ ላይ በክብር ካድሬነት ይቀርባል) በፌስ ቡክ ገፁ ላይ  አሳፋሪ ቃላትን እየፈለገ የእርሱን የጨብሲ ውሎ በሚያሳብቅ መልክ ሲሳደብ ውሏል።

-  ይህ ብቻ አይደለም ዳንኤል ብርሃነ ሰሞኑን ቴዲ አፍሮ ስለ ምንሊክ በማቀንቀኑ ሰፊ የስም የማጥፋት ዘመቻ ከግብረ አበሮቹ ጋር አብሮ  ከፍቶበት ሰንብቷል።

- ዳንኤል የሚያስብባት ትንሽዬ ማሰብያ ጭንቅላት የመንግስት መሆኑን የምትረዱት የምሽቱ የ 2 ሰዓቱን ኢቲቪ አንዳች ነገር ስለ አፄ ምንሊክ 100ኛ ዓመት እረፍት በዓል አለመተንፈሱን ስትመለከቱ ነው።

- ይህ ብቻ አይደለም ከምንገምተው በላይ ኢህአዲግ/ወያኔ በሀገር ጥላቻ ባህር  ውስጥ እየዳከረ  መሆኑን ለመረዳት የዛሬውን ቀን የአንድ የመኪና አደጋ ዜና ያክል ቦታ ሳይሰጠው ማለፉ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን የወከሉ ባለስልጣናት ዛሬ በነፃነት በአዲስ አበባ እንዲፏልሉ ያደረጋቸው አፄ ምኒልክ የመሩትን የአድዋ ድል እረስተው አንዳች ትኩረት እንዳይሰጠው አድርገዋል።ምናልባት ባለስልጣናቱ ጊዜ ላይኖራቸው ይቻላል ምክንያት ዛሬ ጣልያን ኤምባሲ የራት ግብዣ ይኖርባቸው ይሆናላ!

- በአዲስ አበባ በዓታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ካህናት የዳግማዊ አፄ ምንሊክን እና የፊት-አውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ 87ኛ ዓመት  የእረፍት መታሰብያ በፀሎት አስበዋል።

- የሰማያዊ ፓርቲ ልዩ የፎቶግራፍ አውደ-ርዕይ በፅህፈት ቤቱ ከፍቶ ለሕዝብ አሳይቷል።

-  ሸገር ኤፍ ኤም  በዜና ሽፋኑ ላይ የባዕታውን የፀሎት መርሃግብር ቀንጭቦ ከማሰማቱም በላይ  ''ታሪክን የኃሊት'' በተሰኘ ማስታወሻው ላይ  እንዲህ ብሏል-''አፄ ምኒልክ የተለዩ ሰው የሚያደርጋቸው ለሀብት እና ንብረት የማይጨነቁ ይልቁን ከቤተመንግስት ውጭ አንዳችም እርስት እና ንብረት የሌላቸው እና ለልጆቻቸውም አለማውረሳቸው ነው።''

 ከዛሬ 100 ዓመት በፊት በአዲስ ዓለም ኦሮሞዎች 'እምዬ' የተባሉት ንጉስ ምንሊክ ዛሬ ቂም የሚይዝ፣ከንፈር የሚነክስ መንግስት ስልጣን ይዞ ዳግማዊ ምንሊክን ኢትዮጵያ በብሔራዊ ደረጃ መዘከር ባትችል በዜና መልክም ሳትናገር አለፈች።ምንሊክ የቅኝ ገዢዎች እና የባንዳዎች ጠላት ነበሩ።በእዚህ እንስማማለን።

ግን ማስታወሻዬን ከመደምደሜ በፊት አንድ ጥያቄ ልጠይቅ ኢህአዲግ/ወያኔ የእዚህን ያክል ተራ ቂም፣ዘረኝነት፣ሸር እና ተንኮል  አናቱ ላይ እየጨፈሩበት እንዴት ብሎ  ነው ኢትዮጵያን ያክል ሀገር እና ሕዝብ መምራት ይችላል?

ጉዳያችን ታህሳስ 3/2006 ዓም 

Wednesday, December 11, 2013

ዳግማዊ አፄ ምኒልክን ሳስብ የሚገርሙኝ ሶስት አስገራሚ ችሎታዎቻቸው፣የዳግማዊ ምኒልክ እውነተኛ ድምፅ (ኦድዮ) እና አፄ ምኒልክ የነዷት የመጀመርያዋ እውነተኛ መኪና(ቪድዮ)

 ዳግማዊ አፄ ምኒልክ የጥቁር ህዝቦችን የቅኝ ግዛት ታሪክ ተረት ያደረጉ ብቸኛ የዓለማችን መሪ ናቸው።ያረፉበት 100ኛ ዓመት ታህሳስ 3/2006 ዓም በሰማያዊ ፓርቲ እና በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ ይታሰባል።ዕለቱ የዳግማዊ አፄ ምኒልክ ብቻ ሳይሆን የፊት-አውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ 87ኛ እረፍት መታሰብያም ነው።ይህ በዓል ሊከበር የሚገባው በብሔራዊ ደረጃ ነበር።ሆኖም ግን ጉዳዩ የተገላቢጦሽ ሆኖ ኢትዮጵያ ጀግኖቿን እና ታሪክ የሰሩ እውነተኛ ልጆቿ የሚገፉበት ወቅት ሆነ።ይህንን በዓል ለማክበር ሰማያዊ ፓርቲ በጃን ሜዳ ለመሰብሰብ የጠየቀው ጥያቄ እንዳልተፈቀደ ገልጧል።ፓርቲው ግን ዝግጅቱን ቀጥሏል።

ኢትዮጵያውያን በሀገር ቤት የግራዝያኒን ሃውልት መሰራት ተቃውመው ሲወጡ በፖሊስ ተደበደቡ።በሳውዲ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ግፍ አስመልክተው በሳውዲ ኤምባሲ ለመቃወም ሲሰለፉ እንዲሁ ለፖሊስ ዱላ እና ለእስር  ተዳረጉ።ዘንድሮ ደግሞ የዳግማዊ አፄ ምኒልክ 100ኛ  እና የፊት-አውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ 87ኛ እረፍት መታሰብያ ለማዘጋጀት ጃን ሜዳ እንሰብሰብ ሲሉ አሁንም ተከለከሉ።

የእዚህ አይነቱ ታሪካችንን በአግባቡ እንዳንዘክር የማድረጉ ተግባር ባዕዳንን ሊያስፈነድቅ ይችላል።ለኢትዮጵያውያን ግን በመጪው ታሪካችን ሁሉ በጥቁር ቀለም ተፅፎ የምናነበው አሳዛኝ ታሪክ ነው።ካለፈው ታሪካችን ጋር በእዚህ አይነት ደረጃ የተቃረነ መንግስት ያጋጠመን አይመስለኝም።

እኔ ግን ሁል ጊዜ ዳግማዊ ምኒልክን ሳስብ  የሚገርሙኝ  ሶስት አስገራሚ ችሎታዎቻቸውን መጥቀስ እፈልጋለሁ።

1/ የዲፕሎማሲ ችሎታ

በወቅቱ የነበረው የአውሮፓውያን የቅኝ ግዛት የመስፋፋት ፖሊሲ ከእንግሊዝ ጋር በኬንያ አና ሱዳን በኩል ከኢጣልያን ጋር በሱማሌ እና በኤርትራ በኩል ከፈረንሳይ ጋር በጅቡቲ በኩል የነበሩትን ቁርሾዎች እናስብ።በወቅቱ የነበሩትን ንግግሮች፣ደብዳቤዎች፣ሉዓላዊነትን የማስከበር ሂደቶች ሁሉ ማሰብ ይቻላል።ድንቅ እና ለዘመናዊው ዓለም መማርያ የሚሆኑ ብዙ ትምህርቶች ይገኙበታል።

2/ ዘመናዊ አስተተሳሰብ የመቀበል አቅም 

ከአውሮፓውያን ጋር በነበሩ ግንኙነቶች ሉዓላዊነትን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ዘመናዊ አሰራርን የመቀበል ሂደት።የመጀመርያ ዘመናዊ መኪና፣ካቢኔ፣ባቡር፣ስልክ፣ፖስታ፣ሆቴል፣ሲኒማ ቤት ወዘተ የተጀመሩበትን ሂደት እናስብ።በወቅቱ ዘመናዊ አሰራርን ንጉሡ ባይቀበሉ ኖሮ አዲሱ መኪና ላይ እንዳይወጡ ያወገዙ እንደነበሩ አለመዘንጋት ነው።ምኒልክ ግን ዘመናዊ አሰራርን ተቀበሉ።

3/ የአካባቢ ጥበቃ ጠበቃ 

አፄ ምኒልክ ዛሬ የዓለማችን ትልቅ ችግር የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይ ያሳሰባቸው ገና በጧቱ ነበር።የደን መመናመን ጉዳይን በቤተመንግስታቸው በአጀንዳነት የተወያዩ እና መፍትሄ ያስገኙ ቆይቶም ባህር ዛፍ ከአውስትራሊያ በማስመጣት እንዲተከል ያደረጉ የአካባቢ ጥበቃ ተሟጋች ነበሩ።

ይህ ሁሉ የሆነው ከአንድ መቶ አመታት በፊት ነው።ይህ ሁሉ የሆነው ዓለም በመረጃ ባልተሳሰረበት እና ዘወትር ለመማር ዝግጁ በሆኑት እለት እለት እራሳቸውን በሚሰሙት፣በሚያነቡት እና በሚያማክሯቸው ሰዎች እራሳቸውን በእውቀት ባበለፀጉት ንጉስ ምኒልክ ነው።

አፄ ምኒልክ የነዷት መኪና(ቪድዮ)



የዳግማዊ ምኒልክ እውነተኛ ድምፅ (ኦድዮ) ድምፁን በሞባይ መስማት ያልቻላችሁ ሞባይላችሁ ላይ የፕሮግራም አለመጫን ስለሚሆን በቤት ኮምፕዩተር ይክፈቱት።


Monday, December 9, 2013

Mr Mandela's military training in Ethiopia-just before he arrest on 5 August 1962

General Tadesse Birru (Ethiopian army officer) gave a pistol to Nelson Mandela as he returned to South Africa(BBC photo)


By Penny Dale
BBC Africa, Addis Ababa
9 December 2013 Last updated at 09:52 GMT

….In July 1962, Col Fekadu Wakene taught South African political activist Nelson Mandela the tricks of guerrilla warfare - including how to plant explosives before slipping quietly away into the night.

Mr Mandela was in Ethiopia, learning how to be the commander-in-chief of Umkhonto we Sizwe - the armed wing of the African National Congress (ANC).

The group had announced its arrival at the end of 1961 by blowing-up electricity pylons in various places in South Africa.
Mr Mandela was in Ethiopia at the invitation of the emperor, an ardent supporter of Africa's decolonisation and African unity.

At the time, Ethiopia had one of the strongest armed forces on the continent.

Its troops were part of the UN peacekeeping operation during the Congo crisis in 1960 and a decade earlier Ethiopian soldiers had fought in the Korean war.

And the emperor had invited many other African liberation struggle fighters to be trained on Ethiopian soil….
Read more on BBC.co.uk link-  http://www.bbc.co.uk/news/world-africa-23515879 


Saturday, December 7, 2013

''የዓለም ማዕበል ጎርፍ ያላናወጣት ፍቅሯ ያልለወጠ በፈተና ብዛት'' (ኦድዮ)

የአባቶቻችን አምላክ ወዴት ነህ? ኢትዮጵያን ተመልከት!



Thursday, December 5, 2013

ኔልሰን ማንዴላ ከእስር ሲፈቱ እና ዓለም አቀፍ አቀባበል ሲደረግላቸው ለመላው የዓለም ሕዝብ ያደረጉት የመጀመርያው ታሪካዊ ንግግር (ቪድዮ) Nelson Mandela first speech as he released from prison (full speech)

እረጅሙ ጉዞ ወደ ነፃነት!
ኔልሰን ማንዴላ ነፍስህን በገነት ያኑርልን።
LONG WALK TO FREEDOM!
RIP NELSON MANDELA WE WILL NEVER FORGET YOU.



''ኢትዮጵያ ልዩ ስፍራ የምሰጣት እና የማልማት ሀገር ነች።ፈረንሳይን፣እንግሊዝን እና አሜሪካንን ጎብኝ ከምትሉኝ ኢትዮጵያን መጎብኘት እመርጣለሁ።ኢትዮጵያን መጎብኘት ማለት አፍሪካዊ ያደረገኝን ስረ-መጥነቴን የጎበኘሁ ያክል ይሰማኛል።ቀዳማዊ ሃይለስላሴን አግኝቼ እጃቸውን የጨበጥኩ ጊዜ ታሪክ እራሱን የጨበጥቁ ያክል ነበር''
ኔልሰን ማንዴላ ከፃፉት ''እረጅሙ ጉዞ ወደ ነፃነት'' ከተሰኘው መፅሐፋቸው የተወሰደ።

''Ethiopia has always held a special place in my own imagination and the prospect of visiting Ethiopia attracted me more strongly than a trip to France, England and America combined. I felt I would be visiting my own genesis, unearthing the roots of what made me an African. Meeting the Emperor( Emperor Haileselassie I of Ethiopia) himself would be like shaking hands with history.” Nelson Mandela on his Book -Long Walk to Freedom


 Photo-Haile Selassie Mediating between southern Sudanese insurgents (the Anya Nya) and the Sudan government in Addis Ababa, 72; His mediation efforts were responsible for 11 years of relative peace in the Sudan. This scene was later replicated by reggae singer Bob Marley on his “One Love Peace Concert” in April of 78, when he asked rival political leaders of 'the Jamaican Labor Party' and 'the People's National Party' on stage and managed to get them to shake hands. )
ጉዳያችን GUDAYACHN

Wednesday, December 4, 2013

ሰበር ዜና - የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስ እና የባህል ኮሚሽን(UNESCO) በኢትዮጵያ የሚከበረውን የመስቀል ደመራ በዓል ዓለም ዓቀፍ እንክብካቤ እና ጥበቃ እንዲደረግለት በዓለም ቅርስነት ዛሬ መዘገበ!!



የምዝገባ ሂደቱን በተመለከተ ከእዚህ በፊት በጉዳያችን ጡመራ ላይ የወጣውን ለመመልከት ይህንን ይጫኑ - http://gudayachn.blogspot.no/2013/09/blog-post_26.html 

የዩኔስኮ (UNESCO) በቅርስነት የመዘገበበትን ዜና ከድርጅቱ ድህረ-ገፅ ላይ ለማንበብ ይህንን ይጫኑ - http://www.unesco.org/culture/ich/en/RL/00858

Decision 8.COM 8.11
The Committee (…) decides that [this element] satisfies the criteria for inscription on the Representative List of the Intangible Cultural Heritage of Humanity, as follows:
R.1: Rooted in the religious and cultural traditions of Ethiopia and passed on from generation to generation, the festival of Maskel promotes social unity, integration and diversity across the nation;
R.2: Inscription of the festival of Maskel on the Representative List could enhance the visibility of intangible cultural heritage and promote inter-cultural dialogue among the multi-ethnic population of Ethiopia, as well as other communities internationally;

ኢህአዲግ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ሥራ እየሰራ ላለመሆኑ አይነተኛ ማስረጃ - በደርግ እና በኢህአዴግ መካከል ለብሄር ብሔረሰቦች የሚውል ገንዘብ አመዳደብ ልዩነት


ደርግ በብዙ አምባገነናዊ ድርጊቱ ይጠቀሳል።በብሄር ብሄርሰቦች ጉዳይ ግን ከኢህአዴግ ጋር ምን ይለያቸዋል? እስኪ በሃሳቤ የመጡልኝን ስር የያዙ የምላቸውን ነጥቦች ላንሳ

ደርግ 

1/ ''የብሔር ብሔርሰቦች ኢንስቲትዩት'' የተሰኘ ትልቅ የምርምር ኢንስቲትዩት መስርቶ የታወቁ የታሪክ ምሁራን እነ ፕሮፌሰር ላጵሶ ገልዴቦ እነ ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራትን እና ሌሎችም ታላላቅ ስራዎችን እንዲሰሩ አደረገ።ኢንስቲትዩቱ የብሔር ብሔረሰቦች ባህል፣ስር አመጣጥ፣በጋራ የሚያስተሳስራቸው ኢትዮጵያዊነት ወዘተ ላይ ጥናቶች አጥንቷል።የተለያዩ የምርምር ፅሁፎችን፣ዎርክሾፖችን ወዘተ አዘጋጅቷል።ኢንስቲትዩቱ ከሀገር ውስጥ አልፎ የውጭ ዓለም አቀፍ ምሁራንን እየጋበዘ የጥናት ወረቀቶችን ያሰራ ነበር።

2/ ለኢቲቪ ከ 40ሺህ ብር በላይ በጀት መድቦ ''ተጓዥ ካሜራችን'' የሚል በሳምንት አንድ ጊዜ በጋዜጠኛ ብዙ ወንድም አገኘሁ አዘጋጅነት የሚቀርብ  የሚናፈቅ ፕሮግራም ጀምሮ የተረሱ ብሄረሰቦችን  የአኗኗር  ባህላቸውን እና ታሪካቸውን ያስተምር ነበር።ብዙዎቻችን በልጅነት ጊዜ ይህንን ፕሮግራም እናስታውሳለን።

3/ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በ'ህብረት ትርኢት' ፕሮግራም ላይ የሁሉንም ብሔሮች ዘፈኖች ሕዝብ እንዲመለከት ያደርግ ነበር። ይህም በተለይ ለታዳጊው ወጣት የሁሉንም  ባህል እንዲረዳ እና እንዲያከብር ያደርግ ነበር።የቲያትር ቤቶች የሚኖራቸው የኪነት ቡድን የብዙዎቹን ብሔሮች ውዝዋዜ መለማመድ ግዴታቸው ነበር።

ኢህአዲግ 


1/ ስለ ብሔር ብሄረሰብ ብዙ ይናገራል፣በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 29 ከፈለጉ መገንጠል እንደሚችሉ ያትታል።

2/ የብሔር ብሄርሰቦች ቀን ብሎ ብዙ ዘፈን፣ምግብ፣መጠጥ፣ያዘጋጃል፣ከየብሄሩ ለመጡ አባላቱ ያበላል፣ያጠጣል በብዙ ሺህ የሚቆጠር ብር ያወጣል።


3/ የቴሌቭዥን ፕሮግራሞች አንዱ የአንዱን እንዳይቀላቅል የሚቀርቡትን  ዘፈኖችን ብንመለከት በአማርኛው ላይ የኦሮምኛ እንዳይቀርብ፣በትግርኛው ላይ የአማርኛው እንዳይቀርብ ወዘተ ሆኗል።ይህም ቀድሞ አማርኛ ፕሮግራም ላይ ኦሮምኛው፣ትግርኛው ይቀርብ ስለነበር ሕዝብ እርስ በርሱ አንዱ የአንዱን ባህል የማወቅ ዕድል ነበረው። የእነ ኪሮስን፣አሊብራን የመሰሉ ከያንያን ዝናን ያተረፉት አንድ ለእናቱ በነበረው ቲቪ ህዝቡ እየተመለከተ ነው እንጂ የትኛው ኤፍ ኤም ነው ያስተዋወቀው?

4/ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቁ የብሄሬ ድንበር፣ወሰን ተጣሰ ስሞታዎች እና ግጭቶች ተበራክተዋል።ለእዚህም መንግስት ጉዳዩን ለብቻው የሚመለከት አካል እስከመመደብ የደረሰው በእዚሁ ስለ ብሔር ብሔረሰቦች ብዙ በምዘፈንበት ጊዜ ነው።

ባጠቃላይ 

 ለኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ብዙ ሺህ ብር እያወጣ ምግብ የሚበላ መንግስት ነው ጥሩ አደረገ የሚባለው ወይንስ ገንዘብ መድቦ የብሔር ብሄርሰቦች ኢንስቲትዩት የመሰረተ? በእየ ዓመቱ የብሔር ብሄርሰቦች ቀን ተብሎ የሚባክነው ብር ስንት ሥራ ለብሄር ብሄርሰቦቻችን በሰራ ነበር። ኢህአዲግ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ሥራ እየሰራ ላለመሆኑ አይነተኛ ማስረጃ ይህም ነው።  እነሆ ዘንድሮም ጅጅጋ ላይ እንደጉድ ይዘፈናል። ያ የብሔር ብሔረሰቦች ኢንስቲትዩትን ያያችሁ? አሁን አለ? 

Monday, December 2, 2013

ኢትዮጵያ ''ብሔር ብሄረሰብ'' እያለች እንድትዘምር ሲፈረድባት ጎረቤቶቿ ግን በብሄር ስም የፖለቲካ ድርጅት መመስረትን በሕግ ከልክለው በአንድ ገንዘብ ለመጠቀም ስምምነት ላይ ደረሱ



ኢትዮጵያ ያረጀ ያፈጀውን የማርክሲስት አስተሳሰብ ''ብሔር ብሄረሰብ'' ርዕዮት እንድትዘምር ተፈርዶበታል።ህዳር 29 ቀን ጅጅጋ ላይ የቀለጠ ድግስ ተዘጋጅቷል።የእዚህ አይነት ዝግጅት በኢትዮጵያ ወጣቶች መካከል ለምሳሌ በትምህርት ቤቶች መካከል የሚደረግ ከፖለቲካዊ ይዘት የራቀ ግን ወጣቶች የሚቀራረቡበት መልክ ቢኖረው ብዙ ፍሬ ባፈራ ነበር።የኢህአዲግ ዝግጅት ግን ኢትዮጵያውያን አንድ የሚያደርጋቸው እልፍ ነገሮችን ማውሳት ትቶ  የሚለያዩበት ነገር እየተነቀሰ የሚነገርበት መርሃ ግበር መሆኑ ነው አሳዛኙ ነገር።

ኢትዮጵያ ውስጥ ይህ ይሁን እንጂ ጎረቤቶቻችን ግን በሀገራቸው በብሄር ስም የፖለቲካ ድርጅት መመስረትን በሕግ ከልክለው  በአንድ ገንዘብ ለመጠቀም ስምምነት ላይ ደረሱ ።ቅዳሜ ህዳር 21/2006 ዓም የኬንያ፣ዩጋንዳ፣ታንዛንያ፣ቡሩንዲ እና ሩዋንዳ መሪዎች በዩጋንዳ ዋና ከተማ ካምፓላ ተገናኝተው በአስር ዓመት ውስጥ የጋራ መገበያያ ገንዘብ እንዲኖራቸው የፕሮቶኮል ስምምነት ተፈራርመዋል። ይህ ማለት ኢትዮጵያን የሚቀናቀን ትልቅ ገበያ እንደሚፈጥሩ ይታመናል።ኢትዮጵያ በእዚህ ጊዜ ቢያንስ በታዛቢነት አለዝያም ከደቡብ ሱዳን፣ጅቡቲ፣ሱማልያ ወዘተ ጋር የጋራ ገበያ የምትፈጥርበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይገባት ነበር።ከእዚህ ይልቅ ''ምኑ ቀርቶብኝ በወጉ በኮነነኝ'' እንደሚባለው የጎረቤት የጋራ ገበያ ቀርቶ  ጠንካራ ሃገራዊ አንድነት እንዳትፈጥር  በብሄር እንድታስብ ተፈርዶባታል።ህዳር 29 በቴሌቭዥን እያዘፈነች እበላ ባይ አፈጮሌ ካድሬዎቿ ስሽሞነሞኑ ማየት የሰሞኑ አሳዛኝ ድርጊት ነው።

የአምስቱ የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት መሪዎች የቅዳሜ ስብሰባ ይዘትን ከእዚህ በታች ጉዳያችን ጡመራ ላይ ይመልከቱ።
Burundi, Kenya, Rwanda, Tanzania and Uganda will establish common currency

Nov 30, 2013
The presidents of Burundi, Kenya, Rwanda, Tanzania and Uganda met Saturday in the Ugandan capital, Kampala, to sign a protocol for the creation of a monetary union to be established in 10 years. This will be a major change and breakthrough for international trade and tourism alike.

The EAC began 13 years ago with the goal of creating a common customs union, market, monetary union and a political federation of East African states.

Progress has been slowed, however, due to concerns of the member countries about the impact of the bloc's decisions on their individual economies.

The five countries in the East African Community regional economic bloc agreed on the following:
5TH ORDINARY SUMMIT OF HEADS OF STATE OF THE EAST AFRICAN COMMUNITY
COMMUNIQUÉ

1.THE EAST AFRICAN COMMUNITY HEADS OF STATE, THEIR EXCELLENCIES PRESIDENT UHURU KENYATTA OF THE REPUBLIC OF KENYA, PRESIDENT JAKAYA MRISHO KIKWETE OF THE UNITED REPUBLIC OF TANZANIA, PRESIDENT YOWERI KAGUTA MUSEVENI OF THE REPUBLIC OF UGANDA, PRESIDENT PIERRE NKURUNZIZA OF THE REPUBLIC OF BURUNDI AND PRESIDENT PAUL KAGAME OF THE REPUBLIC OF RWANDA HELD THE 15TH ORDINARY SUMMIT OF THE EAST AFRICAN COMMUNITY HEADS OF STATE AT THE SPEKE RESORT AND CONFERENCE CENTRE IN KAMPALA, UGANDA ON 30TH NOVEMBER 2013. THE HEADS OF STATE AND GOVERNMENT MET IN A WARM AND CORDIAL ATMOSPHERE.
2. THEBUREAUOFTHESUMMITWASCHANGEDWHEREBYTHEREPUBLIC OF KENYA TOOK OVER FROM THE REPUBLIC OF UGANDA AS
2
CHAIRPERSON AND THE UNITED REPUBLIC OF TANZANIA TOOK OVER FROM THE REPUBLIC OF BURUNDI AS THE RAPPORTEUR. THE INCOMING CHAIRPERSON EXPRESSED HIS GRATITUDE TO THE OUTGOING CHAIRPERSON FOR HIS STEWARDSHIP OF THE INTEGRATION PROCESS DURING THE LAST ONE YEAR.
3. THE SUMMIT EXPRESSED ITS SOLIDARITY WITH THE PEOPLE OF THE REPUBLIC OF KENYA FOLLOWING THE BARBARIC ATTACK BY THE AL- SHABAAB TERRORISTS ON WESTGATE MALL, NAIROBI AS A RESULT OF WHICH PEOPLE LOST THEIR LIVES AND PROPERTY DESTROYED, AND BUSINESS DISRUPTED. THE SUMMIT REITERATED ITS COMMITMENT TO THE COLLECTIVE SAFEGUARD OF THE PEACE AND SECURITY FOR THE PEOPLE OF EAST AFRICA. THE SUMMIT ALSO EXPRESSED ITS SYMP ATHY WITH THE PEOPLE OF THE REPUBLIC OF KENY A FOLLOWING THE DISASTROUS FIRE AT THE JOMO KENYATTA INTERNATIONAL AIRPORT AND DIRECTED TO ESTABLISH RELIABLE MECHANISMS FOR DISASTER RESPONSE AND RISK MANAGEMENT FOR THE EAC REGION.
4. THE SUMMIT RECEIVED THE ANNUAL REPORT OF THE COUNCIL OF MINISTERS COVERING THE PERIOD NOVEMBER 2012 – NOVEMBER 2013 AND NOTED THE STEADY PROGRESS MADE IN THE COMMUNITY IN PARTICULAR ON PROGRESS ON REMOVAL OF NON-TARIFF BARRIERS. THE SUMMIT COMMENDED THE COUNCIL FOR THE PROGRESS MADE IN DIFFERENT PROGRAMMES OF THE COMMUNITY.
5. THESUMMITCONSIDEREDAMECHANISMFORTHEIMPLEMENTATIONOF OUTSTANDING SUMMIT DECISIONS AND:-
3
a) DIRECTED THE SECRETARY GENERAL IN CONSULTATION WITH THE RELEVANT HEADS OF STATE TO REPORT REGULARLY ON THE IMPLEMENTATION OF DECISIONS INCLUDING NON-COMPLIANCE AND DECIDED THAT THE STATUS OF IMPLEMENTATION REMAINS A STANDING ITEM ON THE AGENDA OF THE SUMMIT.
b)UNDERTOOK TO REPORT ON INDIVIDUAL PARTNER STATES’ IMPLEMENTATION OF DECISIONS INVOLVING THEIR RESPECTIVE COUNTRIES AT EVERY ORDINARY SUMMIT
c) DIRECTED THE SECRETARIAT TO PREPARE A COMPREHENSIVE LIST ON NON IMPLEMENTATION OF ALL DECISIONS FOR CONSIDERATION AT THE 12TH EXTRAORDINARY SUMMIT IN APRIL 2014.
d)DIRECTED THE COUNCIL TO PRESENT A REPORT ON ALTERNATIVE FINANCING MECHANISM INCLUDING THE OPTION OF 1% OF IMPORTS FROM OUTSIDE THE EAST AFRICAN COMMUNITY IN PRINCIPLE OF FINANCIAL SOLIDARITY AND EQUITY AND REPORT TO THE SUMMIT AT ITS 12TH EXTRA-ORDINARY MEETING IN APRIL 2014.
e) DIRECTED THE COUNCIL TO SUBMIT PROGRESS REPORTS IN IMPLEMENTATION OF MAJOR DECISIONS AND DIRECTIVES OF THE COUNCIL AND THE SUMMIT EVERY SIX MONTHS.
6. THE SUMMIT DIRECTED THE COUNCIL TO CONCLUDE THE EAC INSTITUTIONAL REVIEW AND REPORT TO THE SUMMIT AT THE 12TH EXTRA-ORDINARY MEETING IN APRIL 2014; AND
4
7. THE SUMMIT APPOINTED DR. EMMANUEL UGIRASHEBUJA FROM THE REPUBLIC OF RWANDA JUDGE OF THE EAST AFRICAN COURT OF JUSTICE (APPELLATE DIVISION) TO REPLACE HON. LADY JUSTICE EMILY RUSERA KAYITESI WHO RESIGNED. THIS APPOINTMENT TAKES EFFECT FROM 1ST DECEMBER 2013.
8. THE SUMMIT APPOINTED HON. LADY JUSTICE MONICA MUGENYI FROM THE REPUBLIC OF UGANDA JUDGE OF THE EAST AFRICAN COURT OF JUSTICE (FIRST INSTANCE DIVISION) TO REPLACE HON.LADY JUSTICE MARY STELLA ARACH AMOKO, DEPUTY PRINCIPAL JUDGE WHO IS RETIRING. THIS APPOINTMENT TAKES EFFECT FROM 1ST DECEMBER 2013.
9. THE SUMMIT DESIGNATED HON. MR. JUSTICE ISAAC LENAOLA AS DEPUTY PRINCIPAL JUDGE TO REPLACE HON. LADY JUSTICE MARY STELLA ARACH AMOKO. THIS DESIGNATION TAKES EFFECT FROM 1ST DECEMBER 2013.
10.THE SUMMIT RECEIVED THE REPORT ON THE ATTAINMENT OF THE SINGLE CUSTOMS TERRITORY. THE SUMMIT NOTED THAT THE FRAMEWORK FOR THE OPERATIONALISATION OF THE SINGLE CUSTOMS TERRITORY HAD BEEN FINALISED AND ADOPTED BY THE COUNCIL. THE SUMMIT DIRECTED THAT THE SINGLE CUSTOMS TERRITORY COMMENCES ON 1ST JANUARY 2014 AND THAT ALL OPERATIONAL REQUIREMENTS BE FINALISED BY JUNE 2014.
11.THE SUMMIT RECEIVED THE PROGRESS REPORT ON THE NEGOTIATIONS FOR THE ADMISSION OF THE REPUBLIC OF SOUTH
5
SUDAN INTO THE EAST AFRICAN COMMUNITY. THE SUMMIT OBSERVED THAT THE COUNCIL OF MINISTERS HAD ESTABLISHED A HIGH LEVEL NEGOTIATION TEAM TO CONDUCT THE NEGOTIATIONS AND ENABLE THE SUMMIT MAKE A DECISION ON THE MATTER AT THE 12TH EXTRA- ORDINARY SUMMIT IN APRIL 2014.
12.THE SUMMIT RECEIVED THE PROGRESS REPORT ON THE VERIFICATION OF THE APPLICATION OF THE REPUBLIC OF SOMALIA TO JOIN THE EAST AFRICAN COMMUNITY. THE SUMMIT NOTED THAT THE TERMS OF REFERENCE FOR THE VERIFICATION PROCESS HAD BEEN DEVELOPED AND A VERIFICATION COMMITTEE PUT IN PLACE. THE SUMMIT DIRECTED THE COUNCIL OF MINISTERS TO SUBMIT PROGRESS REPORT ON THE VERIFICATION EXERCISE AT THE 16TH ORDINARY SUMMIT IN NOVEMBER 2014.
13.THE SUMMIT RECEIVED THE PROGRESS REPORT ON THE ROADMAP FOR THE ESTABLISHMENT OF THE EAST AFRICAN FEDERATION. THE SUMMIT NOTED THAT THE REVISED MODEL STRUCTURE, ROAD MAP AND ACTION PLAN WILL BE CONSIDERED BY THE COUNCIL OF MINISTERS AND SUBMITTED TO THE 12TH EXTRA-ORDINARY SUMMIT MEETING IN APRIL 2014.
14.THE SUMMIT APPROVED AND SIGNED THE PROTOCOL ON THE ESTABLISHMENT OF THE EAST AFRICAN MONETARY UNION AND DIRECTED THAT:
a) ALL PARTNER STATES SHOULD CONCLUDE THE RATIFICATION PROCESS OF THE EAMU PROTOCOL BY JULY, 2014;
6
b) THE COUNCIL OF MINISTERS SHOULD IMPLEMENT THE ROADMAP TO SINGLE CURRENCY AS INDICATED IN THE SCHEDULE ON THE EAMU PROTOCOL;
c) THE FOLLOWING INSTITUTIONS NECESSARY FOR THE IMPLEMENTATION OF THE EAMU BE ESTABLISHED:-
i) THE EAST AFRICAN MONETARY INSTITUTE
ii) THE EAST AFRICAN STATISTICS BUREAU TO BE RESPONSIBLE
FOR STATISTICS
iii) THE EAST AFRICAN SURVEILLANCE, COMPLIANCE AND
ENFORCEMENT COMMISSION TO BE RESPONSIBLE FOR
SURVEILLANCE, COMPLIANCE AND ENFORCEMENT; AND
iv) THE EAST AFRICAN FINANCIAL SERVICES COMMISSION TO BE
RESPONSIBLE FOR FINANCIAL SERVICES.
d) THE COUNCIL OF MINISTERS DEVELOPS THE BILLS FOR THE ESTABLISHMENT OF THE INSTITUTIONS PROVIDED IN THE PROTOCOL FOR CONSIDERATION BY THE EAST AFRICAN LEGISLATIVE ASSEMBLY AS PROVIDED FOR IN THE ROAD MAP;
e) THE COUNCIL OF MINISTERS APPRISES THE SUMMIT ON THE PROGRESS MADE ON IMPLEMENTATION OF THE ROADMAP TO SINGLE CURRENCY AT EVERY ORDINARY SUMMIT.
15.THE SUMMIT NOTED THAT THE SECTORAL COUNCIL ON FINANCE AND ECONOMIC AFFAIRS WILL BE RESPONSIBLE FOR THE IMPLEMENTATION OF THE MONETARY UNION PROTOCOL.
16.THE SUMMIT APPROVED THE COUNCIL RECOMMENDATION TO EXTEND THE JURISDICTION OF THE EAST AFRICAN COURT OF JUSTICE TO
7
COVER TRADE AND INVESTMENT AS WELL AS MATTERS ASSOCIATED WITH THE EAST AFRICAN MONETARY UNION. ON HUMAN RIGHTS MATTERS AS WELL AS CRIMES AGAINST HUMANITY, THE SUMMIT DIRECTED THE COUNCIL OF MINISTERS TO WORK WITH THE AFRICAN UNION ON THIS MATTER.
17.THE SUMMIT DIRECTED THAT THE INTERNATIONALIZED NEW GENERATION EAST AFRICAN PASSPORT BE LAUNCHED BY NOVEMBER 2015.
18.THE SUMMIT DISCUSSED THE PREVAILING SECURITY SITUATION AND THE NEED FOR CONCERTED EFFORTS TOWARDS COMBATING TERRORISM AND NEGATIVE FORCES IN THE REGION AND REAFFIRMED ITS COMMITMENT TO THE PEACE AND SECURITY IN THE REGION.
19.THE SUMMIT NOTED WITH CONCERN THE RECENT POLITICAL AND SECURITY DEVELOPMENTS IN SOMALIA AND URGED ALL PARTIES TO EMBRACE DIALOGUE AND CREATE AN ENVIRONMENT CONDUCIVE FOR THE IMPLEMENTATION OF SOMALIA’S VISION 2016 AND FACILITATE THE ELECTIONS BY 2016.
20.THE SUMMIT TOOK NOTE OF THE UN SECURITY COUNCIL RESOLUTION 2124 ADOPTED ON 12TH NOVEMBER 2013 REGARDING ENHANCING THE MILITARY CAPACITY OF THE AMISOM AND THE SOMALI NATIONAL FORCES AND CALLED FOR THE REVIEW OF THE RESOURCE PACKAGE TO ASCERTAIN ITS ADEQUACY TO FACILITATE CONTINUITY AND STRENGTHENING OF THE MILITARY CAMPAIGN AGAINST AL-SHABAAB.
8
21.THE SUMMIT REITERATED ITS CONTINUED SUPPORT FOR THE GOVERNMENT OF SOMALIA AND CALLED UPON REGIONAL BODIES AND THE INTERNATIONAL COMMUNITY TO COME FORWARD AND SUPPORT ECONOMIC, SOCIAL AND POLITICAL INTERVENTIONS GEARED TOWARDS ENHANCING THE CAPACITY OF THE SOMALI GOVERNMENT AND ITS GOVERNANCE INSTITUTIONS TO FULFIL ITS MANDATE AND MEET THE EXPECTATIONS OF ITS CITIZENS.
22. THE SUMMIT REAFFIRMED THEIR SUPPORT FOR THE EFFORT OF THE ICGLR/SADC MEMBER STATES AND THE INTERNATIONAL COMMUNITY ON THE ONGOING PEACE INITIATIVES AIMED AT STABILIZING EASTERN DRC, AND IN THAT REGARD, ENCOURAGED THE EAC PARTNER STATES TO SUPPORT THE ONGOING POLITICAL PROCESS (KAMPALA DIALOGUE), WHICH SHOULD BE CONCLUDED AS SOON AS POSSIBLE.
23.THE SUMMIT NOTED THE JUSTIFIABLE CAUSE FOR THE NEED TO HARMONISE THE TERMS AND CONDITIONS OF SERVICE FOR THE ELECTED MEMBERS OF THE EAST AFRICAN LEGISLATIVE ASSEMBLY WITH THOSE OF ALMOST EQUAL STATUS WITHIN THE COMMUNITY. THE SUMMIT APPROVED A LUMPSUM INCREMENT OF USD 1,206 PER MEMBER WITH EFFECT FROM 1ST JULY 2014.
24.THE SUMMIT COMMENDED THE INITIATIVE BY THE MEDIA IN THE REGION TO FORM A BODY THAT WILL REPRESENT THEIR INTEREST AND PLAY A MORE ROBUST ROLE IN PROPAGATING THE INTEGRATION ISSUES.
9
25.THE SUMMIT DIRECTED THE COUNCIL OF MINISTERS TO STUDY THE MODALITIES OF INCLUDING FRENCH AS A LANGUAGE OF THE COMMUNITY IN ADDITION TO ENGLISH AND KISWAHILI.
26.THEIR EXCELLENCIES, PRESIDENT PAUL KAGAME OF THE REPUBLIC OF RWANDA, PRESIDENT, UHURU KENYATTA OF THE REPUBLIC OF KENYA, PRESIDENT JAKAYA MRISHO KIKWETE OF THE UNITED REPUBLIC OF TANZANIA, AND PRESIDENT PIERRE NKURUNZIZA OF THE REPUBLIC OF BURUNDI THANKED THEIR HOST, HIS EXCELLENCY PRESIDENT YOWERI KAGUTA MUSEVENI OF THE REPUBLIC OF UGANDA, FOR THE WARM AND CORDIAL HOSPITALITY EXTENDED TO THEM AND THEIR RESPECTIVE DELEGATIONS DURING THEIR STAY IN UGANDA.
DONE AT KAMPALA, THIS 30TH DAY OF NOVEMBER 2013

H.E. UHURU KENYATTA
PRESIDENT OF THE REPUBLIC OF KENYA
H.E. YOWERI KAGUTA MUSEVENI
PRESIDENT OF THE REPUBLIC OF UGANDA
H.E. JAKAYA MRISHO KIKWETE
PRESIDENT OF THE UNITED REPUBLIC OF TANZANIA
H.E. PIERRE NKURUNZIZA
PRESIDENT OF THE REPUBLIC OF BURUNDI
H.E. PAUL KAGAME
PRESIDENT OF THE REPUBLIC OF RWANDA

source - http://www.eturbonews.com/40192/burundi-kenya-rwanda-tanzania-and-uganda-will-establish-common-c  

ኢህአዲግ/ወያኔ ከግንቦት ሰባት የሰላም፣የፍትህ እና የነፃነት ንቅናቄ ጋር ድርድር ላድርግ ስላለው ግንቦት 7 ፈፅሞ እንዳይበርደው እንዳይሞቀው (vidio)

ኢህአዲግ/ወያኔ ግንቦት ሰባትን ዛሬ ልደራደር ስላለው እንዳይበርደው እንዳይሞቀው ያስፈልጋል።ምክንያት ግንቦት ሰባት ኢህአዲግ /ወያኔ ከእዚህ ቀደም ድርድር ካደረገባቸው ከኦጋዴን ወዘተ ድርጅቶች አያንስም።ብዙም ሳይገረሙ መራመዱ ብቻ ነው ለሀገር የሚበጀው።ለኢህአዲግ/ወያኔ መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ ከማለት ''ትንሽ ነው ያሉት እንዲህ ቁጭ ብድግ ያስደርጋል እና በአንክሮ ታስቦበት ከልብ የፖሊሲ ለውጥ ላይ አተኩሮ ፍፁም ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ላይ ማተኮሩ የሚበጅ ነው። በብረት ተማምኖ ስልጣን ላይ መቆየት እንደማይቻል ታሪክ አስተምሯል።ሃሳቤን የምትገልፀው ቪድዮ ይህች ነች።





ጉዳያችን GUDAYACHNgetachewb221@gmail.com

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።