ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, June 22, 2022

በምዕራብ ወለጋ በሸኔ ፊታውራሪነት፣በህወሃት አቀናባሪነት እና ድጋፍ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ በንጹሃን ላይ የተፈጸመው ጭፍጨፋ ከሞቱት ውስጥ ከአንድ ቤተሰብ 12 ሰዎች የሞቱበት ሁኔታ አለ።የጭፍጨፋው ስልት ያልታየበት አቅጣጫ አለ።

ህወሃት በአቦይስብሃት ተወክላ አክራሪውን የሸኔ ቡድን ትግራይ ላይ ስትቀበል

========
ጉዳያችን
========

የጨፌው ስብሰባ 

ከወራት በፊት የኦሮምያ ክልል ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ከቦረና የመጡ ዕድሜ የጠገቡ አዛውንት እጃቸውን አወጡ።ሽማግሌው የክልሉ ፕሬዝዳንት ያቀረቡት ሪፖርት ላይ ዋናው እና አንገብጋቢው ጉዳይ በሚገባ አለመወሳቱ አናዷቸዋል። አዛውንቱ በቀረበው ሪፖርት ላይ የክልሉ ህዝብ ራስ ምታት የሆነው የፋሺሽቱ ሸኔ ጉዳይ በሚገባ አለመነሳቱን ተናገሩ። በመቀጠል የተናገሩ ተሳታፊዎችም ሸኔን ማጥፋት የሚለው አጀንዳ ዋና መሆን እንዳለበት ደጋግመው ተናገሩ።ይልቁንም እኛ ህዝቡን ወክለን እዚህ እንደመቀመጣችን ህዝብ የነገረን የጸጥታው ጉዳይ ቅድምያ ይሰጥ የሚል ነው በሚል ደጋግመው ተናገሩ። በመቀጠል የክልሉ ስብሰባ አቅጣጫ ወደ ሸኔ ጉዳይ ላይ ዞረ። አቶ ሽመልስም በጥቂት ወራት ሸኔን እናጠፋለን የሚል ዕቅድ መያዙን አስታወቁ።

የህወሃት የሽብር ጥቃት እና የወለጋ ጭፍጨፋ ፊትና ኋላ ናቸው።

አክራሪ እና አሸባሪው የኦነግ ክንፍ በህወሃት ዘመን በኦህዴድ ውስጥ ዘልቆ እንዲገባ ብቻ ሳይሆን ወደ ስልጣን እርከኑ እንዲወጣ የተደረገው በህወሃት ምስጢራዊ ስብሰባ ነው።ከጅማ በሸሻ ጭፍጨፋ ጀምሮ የቀድሞው የጅማ ከተማ በጽንፈኛ የተሞላው አስተዳደር ጨምሮ አክራሪዎቹ ወደ ኦህዴድ የስልጣን መሰላል ሲንጠላጠሉ ህወሃት ያውቃቸው ነበር።ይህንንም እያወቀ የለቀቃቸው ስለ ሁለት ዓላማ ነበር። አንዱ ምክንያት በኦሮምያ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆችን እንዲያሳድዱ ሲሆን ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በራሱ በኦሮምያ ክልል ውስጥ በለዘብተኛው እና አክራሪው መሃከል ግጭት እንዲፈጠር እና ህወሃት በመሃል የክልሉን ሃብት እንደፈለገ መጠቀም እና መዝረፍ ስለፈለገ ነበር።

የዛሬ ሦስት ዓመት በፊት የኦነግ አክራሪ አንጃ በኤርትራ በኩል ወደ ኢትዮጵያ የገባውን ቡድን አቦይ ስብሃት ዓርማውን ጉልበታቸው ላይ አስደግፈው ምሳ የጋበዟቸው ቀድመውም ውስጡን የሚያውቁትን ቡድን ተጨማሪ የሎጀስቲክ ድጋፍ ከደጎሙት ኢትዮጵያን ያተራምስልኛል የሚለውን የህወሃት የነበረ ዕቅድ እያሰላሰሉ ነበር።ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ሽብርተኛው ህወሃት በንጹሃን ላይ ጭፍጨፋ ከመፈጸሙ በፊት በምዕራብ ወለጋ የንጹሃን ህይወት ሲቀጠፍ በተከታታይ ታይቷል።በመሃል ከተፈጸሙት ጥቃቶች ውስጥ ለምሳሌ የጥቅምት 24ቱ የሽብርተኛው ህወሃት ጥቃት ከመፈጸሙ በፊት በምዕራብ ወለጋ በአንድ ምሽት ከሁለት መቶ በላይ ንጹሃን ተገደለው ነበር።ህወሃት እና ሸኔ የተለያዩ አድርጎ ማየት አይቻልም።እነርሱም የተለያየን ነን አላሉም።የዛሬ ዓመት ላይም በጋራ ግንባር ፈጥረናል ብለው እንደነገሩን ብቻ ሳይሆን በከሚሴ ከተማ ጭምር በጋራ ሲገድሉ እና ሲዘርፉ እንደነበር እናስታውሳለን።በቅርቡ የተደረገው ጭፍጨፋም ላይ ህወሃት በሎጀስቲክ ብቻ ሳይሆን በስልጠናም አልተሳተፈም ማለት ሞኝነት ነው። ህወሃት በወለጋው ጭፍጨፋ ውስጥ እጁ እንዳለበት ለመረዳት ብዙ የምትቸገሩ አንዳንድ የዋሆች የጀርባ ታሪኩን ባታምኑ በሰሞኑ የህወሃት የፕሮፓጋንዳ ማሽኖች ለወለጋው ጭፍጨፋ ኦነግ ሸኔ አይደለም በሚል ሲለፍፉ መመልከት ብቻ በቂ ማስረጃ ነው።

የጭፍጨፋው ስልት ያልታየበት አቅጣጫ አለ።

እንደ መቀሌው ሁሉ በካምፓላ፣ጁባእና ናይሮቢ የሚርመሰመሱት የሸኔን እና ህወሃትን የተናበበ ጭፍጨፋ አቀናባሪዎች እና የውስኪ ብርጭቆዎቻቸው

የወለጋው ጭፍጨፋ አፈጻጸም ስንመለከት በአፍሪካ በተለይ በኮንጎ፣ናይጀርያ እና ሴራልዮን ውስጥ ይፈጸሙ የነበሩት ዓይነት ጭፍጨፋዎች ናቸው።እነኝህ ጭፍጨፋዎች የጠነከረ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ክርክሮች አይደሉም። ይጭፍጨፋዎቹ ዋና መሰረቶች ገንዘብ፣ኢትዮጵያን በጎሳ ፖለቲካ ለማተራመስ እና መንግስትን ውጥረት ውስጥ መክተት የሚሉት ናቸው።የግድያው ድርድር የሚደረጉት እና በሟቾቹ የደም ፍሳሽ ልክ ከባዕዳን ገንዘብ የሚቀበሉት ሰው በላ ቡድን አስተባባሪዎች የሚተራመሱት እና በፈሰሰው ደም ልክ ውስኪ የሚራጩት የሚተራመሱት ኝ መቀሌ፣ካምፓላ እና ናይሮቢ ናቸው። ወለጋ የማዕድን ፍላጎት ያላቸው የውጭ ኩባንያዎች አሉ። በተመሳሳይ በናይጄርያ፣ሴራልዮን እና ኮንጎ ይፈጸሙ የነበሩ ጭፍጨፋዎች የሚመሩት በፈጻሚዎቹ ብቻ ሳይሆን በማዕድናት ላይ ፍላጎት ያላቸው አንዳንድ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ጭምር በጓሮ በር ይደገፉ ነበር።ኩባንያዎቹ የእዚህ ዓይነት የቆ ሸሸ ሥራ ላይ ይሰማራሉ ብሎ የሚያስብ ማን አለ?

ከላ።ይ በጥቂቱ የጭፍጨፋው ሂደት የምናይበት አቅጣጫ አንጻርየወለጋው ጭፍጨፋ በተመለከተ መደረግ ያለባቸው ሦስት ጉዳዮች አሉ። እነርሱም  

  1. የኦነግ ሸኔ ዋና ደጋፊ ህወሃት አሁንም ለፍርድ መቅረብ አለበት። የኦነግ ሸኔ አስተሳስብንም ሆነ ቡድኑን መግቦ ያሳደገው እራሱ ህወሃት ነው።
  2. ከመቀሌ በተጨማሪ በናይሮቢ፣ካምፓላ እና ጁባ የሚተራመሱት የሸኔ የውስኪ ቅምጥሎች አድኖ ለፍርድ ማቅረብ ያስፈልጋል።እነኝህ በህወሃት እና በኦነግ ሸኔ መሃል አገናኝ መኮንኖች እነኝህ ናቸው።
  3. ለኦነግ ሸኔ የሳሳ ልብ ያላቸው ቀድሞ ህወሃት ወደ ኦህዴድ አውቆ ያስጠጋቸው ጽንፈኞች ከኦሮምያ ክልል የአስተዳደር መዋቅር ውስጥ መንጥሮ ማውጣት ያስፈልጋል።
  4. ወለጋ ከአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እና ከአማራ''ማጽዳት'' ወለጋ የኦሮምያ ብቻ ትሆናለች ብለው እያሰቡ የሚጃጃሉ የኦሮምያ ክልል ባለስልጣናት ዛሬም አሉ። ሆኖም ግን ወለጋን ከአገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እና አማራ ማጽዳት የማዕድኑን ሃብት ለመቆጣጠር ብቻ ሳይሆን የተራዘመ ጦርነት በመክፈት ኢትዮጵያን እናዳክም ብለው የሚያስቡ መኖራቸው የሚሉት ተጠቃሾች ናቸው። 
 ባጠቃላይበምዕራብ ወለጋ በሸኔ ፊታውራሪነት፣በህወሃት አቀናባሪነት እና ድጋፍ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ በንጹሃን ላይ የተፈጸመው ጭፍጨፋ ከሞቱት ውስጥ ከአንድ ቤተሰብ 12 ሰዎች የሞቱበት ሁኔታ አለ።የጭፍጨፋው ስልት ያልታየበት አቅጣጫ አለ። የወለጋ የንጹሃን ኢትዮጵያውያን ግድያ ከዘር ጭፍጨፋ ባለፈ በአፍሪካ የማተራመሻ መንገድ ሆኖ በሌሎች የአፍሪካ አገሮች ላይ ተፈጽሟል።በኦሮምያ ክልል ያሉ ጽንፈኞች የአማራ ተወላጅ ወጥቶ ሰላም የሚያገኙ መስሏቸዋል።ይህ ግን ፈጽሞ አይሆንም።ድርጊቱን ባዕዳን የኢትዮጵያ ጠላቶች የሚደግፉት ቦታውን ካለተከላካይ አመናምኖ እና አተራምሶ በቀጣይ ለውጭ ኩባንያዎች ባርያ የሆኑ የመንደር ቡድኖች መመስረት እና መበዝበዝ ቀጣዩ ሥራ መሆኑ ካልገባቸው ሊገባቸው ይገባል።ባጭሩ በወለጋው እልቂት ከኦነግ ሸኔ በላይ ህወሃት በንጹሃን ደም ጨፍሯል።ባዕዳኑ የማተራመሻ አጀንዳ ለመፍጠር አቀጣጣይ ክብሪት ይሆናል ብለው ይጠብቃሉ። ከሁሉም ከሁሉም ግን መንግስት የጸጥታ አጠባበቅ መንገዱን መከለስ እንዳለበት ብቻ ሳይሆን የደህንነቱ መዋቅር ቀድሞ የመከላከል አቅሙን ማዳበር ይገባዋል።
==========////============

Saturday, June 18, 2022

ህወሓት በእንግሊዝኛ እደራደራለሁ፣በትግርኛ ደግሞ ለትግራይ ህዝብ ''እናንተ ሙቱልኝ እኔ ልኑር'' እያለ ነው።

  •  ''ከመሃል አገር የተወለዱትን የአህያ ልጆች አሉን፣ የመከላከያ አባላት በሲኖ ጨፍልቀው ሲገደሉ አይተናል።የ6ወር ህጻን ልጇን ይዛ ወደ ባሏ የሄደች የትግራይ ተወላጅም ተገድላለች።'' ከጽሑፉ መጨረሻ ላይ ህወሓት በመከላከያ ሰራዊት የፈጸመውን ግፍ የትግራይ ተወላጅ እናት እና ልጅ የዐይን ምስክርነት ቪድዮ ያገኛሉ።
  • የኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፍ ወቅታዊ ሁኔታ አጭር ዳሰሳ 
===============
ጉዳያችን / Gudayachn
===============

ጥቂት ወደ ኋላ ስንመለከት 

አዲሱ ምዕተ ዓመት ከተጀመረ በኢትዮጵያ አቆጣጠር አስራ አራት ዓመታት አለፉ። ያለፈው ምዕተ ዓመት ኢትዮጵያ እንዴት አሳለፈችው? ብለን እራሳችንን ብንጠይቅ በሚከተሉት ዐበይት ጉዳዮች ዙርያ መሆኑን መግለጽ ይቻላል። እነርሱም በባዕዳን ቀጥታ ወረራ እና በነጻነት ድል፣መልሰን በመጠኑ በማንሰራራት፣ መልሶ በተነሳ በእርስ በርስ ጦርነት፣ በጎሳ ፖለቲካ የጥፋት ሰደድ እና ከጎሳ ፖለቲካ ለመውጣት እና እራስን ለመመልከት የሚታትር ትውልድ መነሳት በሚሉት ማጠቃለል ይቻላል ብዬ አምናለሁ።

እያንዳንዳቸው ታሪካዊ ሁነቶች በኢትዮጵያ ላይ ባለፈውም ሆነ የአሁኑ ትውልድ ላይ የራሱ የሆነ አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ አሻራ ጥሏል።በምዕተ ዓመቱ የተደረጉብን ቀጥተኛ የባዕዳን ወረራ ብንመለከት ግብጽ፣ኢጣልያ እና ሱማልያ ያደረጉትን ወረራ ማስታወስ ይቻላል። የጣልያን ወረራ በአባቶቻችን ትውልድ ውስጥ ከፍተኛ የትምሕርት እና የመሰልጠን ጥያቄ ጭሮ ንጉሱ እና በወቅቱ የነበረው ትውልድ በትምሕርት ላይ እና ኢትዮጵያን ከቀረው ዓለም እኩል ለማድረግ ከፍተኛ ትንቅንቅ ውስጥ እንዲገቡ አድርጓቸዋል። በእዚህም ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለአፍሪካ ነጻነት ፋና ወጊ ከመሆን አልፋ አፍሪካን በራሷ ድርጅት (የአፍሪካ ሕብረት) እንድትሰባሰብ አሻራ ትተው አልፈዋል።

ከባዕዳን የቀጥታ ወረራዎች በተለየ በቀጣይ ጊዜዎች የተነሱት የኢትዮጵያ ታሪካዊ ክስተቶች ውስጥ የጎላው የእርስ በርስ ጦርነቶች በተለይ በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ እና ኤርትራ የተለኮሰው ጦርነት ነበር።ይህ ጦርነት ውስጣዊ ይምሰል እንጂ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የተርገበገበው እና የተደገፈው በኢትዮጵያ የቅርብ እና የውጭ ባዕዳን ነበር። የባዕዳኑ ዋና ፍላጎት ደግሞ ኢትዮጵያ የዓባይ ምንጭ እና የቀይባሕር ላይ ያላት የአንድ ሺህ ኪሎሜትር ቁጥጥር ነው። በተለይ በቀይባሕር ላይ በቀዝቃዛው ጦርነት ጊዜ የነበረው የሁለቱ የወቅቱ ኃያላን የአሜሪካ እና የሩስያ ሹክቻ ኤርትራን ከኢትዮጵያ ለመገንጠል የሚንቀሳቀሰው ሻብያ እንደ መልካም ዕድል ተጠቀመበት።ሻብያን ተከትሎ የተመሰረተው የህወሃት ቡድንም እንደፈጣሪው ሻብያ ከአሜሪካ ብቻ ሳይሆን ከመካከለኛው ምሥራቅ አንዳንድ አገሮች ጋር ሳይቀር ያሳደገቻቸውን ኢትዮጵያን ለመውጋት በገፍ የጦር መሳርያ ድጋፍ አግኝተዋል።በኋላ ህወሃት አዲስ አበባ ሲገባ የባዕዳኑን አጀንዳ የጎሳ ፖለቲካ በኢትዮጵያ ላይ ለመትከል ሲታትር ከኖረ በኋላ የራሱን የጥፋት ትውልድ ተክሎ ኢትዮጵያን ወደ የመጨረሻው ውድቀት ለመክተት ሲዘጋጅ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለለውጥ ተነስቶ ሃገሩን ከውድቀት አፋፍ ታድጎ ትንቅንቁን ቀጠለ።

ያለፈው ምዕተ ዓመት ኢትዮጵያ ብዙ መልካም የሚባሉ ጉዳዮች ቢኖሯትም አጠቃላይ ውጤቱ ግን ኢትዮጵያን እንደ አገር ከጠላቶቿ ተናንቃ ለመቀጠል የቻለችበት፣የማደግ እድሏ በከፍተኛ ደረጃ ላይ ያስቀመጠበት፣ ነገር ግን መድረስ ትችልበት ከነበረበት ደረጃ እንዳትደርስ ተጎትታ የተያዘችበት እና በጎሳ የሚያስብ ትውልድ የተፈጠረባት ጊዜ ሆኗል።

አሁን ያለንበት ዓለም አቀፋዊ እና አገራዊ ሁኔታ  

ይህ በተለይ እያገባደድነው ያለው 2014 ዓ ም  ሆነ መጪው ቅርብ ጊዜ ምን ዓይነት ጊዜ ላይ ነን ብሎ አጠቃላይ ስዕሉን በመጠኑ ማወቅ እጅግ ጠቃሚ ነው።ለእዚህ ደግሞ የአገር ውስጡ እና የዓለም አቀፉ ሁኔታ ብሎ ከፍሎ ማየት ያስፈልጋል።

የዓለም አቀፉ ሁኔታ 

የዓለም አቀፉ ሁኔታ ከኮቪድ 19 በኋላ ያለው ዓለም አንድ ዓይነት ፍትጊያ ውስጥ እንደሚገባ ግልጽ እንደነበር ከሦስት ወራት በፊት ጉዳያችን ላይ ዩክሬን፣ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ እና ወቅቱ የሚጠይቀው ኢትዮጵያን እና መንግስትን የማገዝ ሃገራዊ ፋይዳው በሚል ርዕስ በወጣው ጽሑፍ ላይ እንዲህ የሚል ዓረፍተነገር ተጽፎ ነበር።

 ''የዓለማችን ሁኔታ ከኮቪድ ወረርሽኝ በመጠኑ መቀነስ ተከትሎ እና የዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ገቢ መቀነስ፣የምዕራቡን ዓለም የሚገዳደሩት የቻይና፣ሩስያ እና ቱርክ እንደገና ማንሰራራት ውጥረቶች እየጨመሩ መጥተዋል።ይህም የዓለምን ሥርዓት እንደገና እንዲከለስ ያስገድዳል። ሥርዓቱ ደግሞ በደፈናው አይከለስም።አንድ ዓይነት የጉልበት መፈታተሾች ተካሂደው ወይንም ግልጥ ከሆነ ጦርነት በኋላ የኃይል አሰላለፍ ልዩነት እንደሚኖር አሁን ከመቼውም ጊዜ በላይ ግልጥ እየሆነ መጥቷል።''

ይህ የጉልበት መፈታተሽ በዩክሬን እና ሩስያ ተጀምሯል። ቻይና ታይዋንን በወቅቱ አጋጣሚ ለመቆጣጠር እያኮበኮበች ነው።አሜሪካ በሩቅ ምሥራቅ ያላትን ጥቅም እንዳታጣ ከአውስትራልያ እና በአካባቢው ካሉ ወዳጆቿ ጋር እየመከረች ነው። የዩክሬን ጦርነት በሩስያ እና በዩክሬን መሃከል ብቻ ላለመሆኑ ማሳያው ለዩክሬን መላው የምዕራቡ ዓለም ድጋፍ እያደረገ መሆኑ በራሱ መጪው የዓለም ሂደትን አመላካች ነው። ይህ ሁኔታ ጊዜ በወሰደ ቁጥር አገሮች የአሰላለፍ ለውጥ እያደረጉ ሲመጡ የሚተረተረው የክር እርዝመት የት እንደሚደርስ ለማውቅ አይቻልም። የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት በትናንትናው ዕለት እንግሊዝ ገብተው የተደረገላቸው አቀባበል እና የአውሮፓ ሕብረት በጦርነት ላይ ያለችውን ዩክሬንን የያዝነው የአውሮፓውያን ዓመት ከመጠናቀቁ በፊት በአባልነት ለመቀበል ሽር ጉድ ላይ መሆኑ በራሱ ውጥረቱ የት ድረስ እንደሚሄድ በደንብ አመላካች ነው።ዓለማችን ከጦርነት እንድጸዳ ጸሎት ያስፈልጋታል።

ዓለም አቀፋዊው ውጥረት በዓለም አቀፍ ሕግ የመመራት ቢያንስ በመጠኑ የመሸበብ ዕድሉ ሲላላ ትናንሽ የአካባቢ ጉልቤዎች በመንደራቸው ባሉ አገሮች ላይ ጉልበታቸውን ለማሳየት አጋጣሚ አይፈልጉም ማለት አይቻልም።ከእነኝህ አጉራ ዘለሎች መሃከል አንዳንድ የመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች ከኢትዮጵያ ጋር ባላንጣ ከሆነችው ከግብፅ ጋር ከእጅ አዙር ውግያ ወደ የቀጥታ ወረራ ሙከራ የሚያኮበኩቡበት ጊዜ አይሆንም ብሎ ማሰብ አይቻልም። ይህ ደግሞ በራሱ የኃያላኑ መፋጠጫ እና ኢከከኝ ልከክህ ሜዳ እንዳትሆን መሰራት ያለበት ጊዜ ነው።

የአገር ውስጡ ሁኔታ 

ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ በእዚህ አጭር ጽሑፍ ሙሉ ስዕሉን ማሳየት ከባድ ነው።ሆኖም ግን የ2014 ዓም ኢትዮጵያ ያለፈችበት የፈተና ውጣ ውረድ ውስጣዊ እና ውጫዊ ገጽታውን በማንሳት ብቻ ብዙ ጉዳዮች ግልጽ እንዲሆኑ ማድረግ ይቻላል።ይህ ዓመት ኢትዮጵያውያን የውስጣዊ ጉዳያችንን ታከው እነማን በምን ያህል ደረጃ ኢትዮጵያን ሰውተው በእራሷ ላይ ተረማምደው የራሳቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ ፍላጎት እንዳላቸው የተመለከቱበት ጊዜ ነው። 

ይህም ሆኖ ግን በኢትዮጵያውያን ላይ በህወሃት ፈረስነት በኢትዮጵያ ላይ የተዘራው የጎሳ ፖለቲካ የራሱ የሆነ ግልገል አድናቂዎች ስላሉት እና ከኢትዮጵያዊነት የራቁ ነገር ግን ለገንዘብ ወገናቸውን የሸጠ ትውልድ በየዘርፉ ስለተበተነ የኢትዮጵያ ፖለቲካም ሆነ ሌሎች የማኅበራዊ እና ምጣኔ ሃብት ተቋማት በእዚሁ ረብ የለሽ አስተሳሰብ እና የኢትዮጵያ ነቀርሳ በሆነ አስተሳሰብ የተበከለ አስተሳሰብ አራማጆች ኢትዮጵያን ካለችበት ፈተና እንዳትወጣ ጋሬጣ ሆነውባታል።

ይህ ጋሬጣ በየዘርፉ ቢኖርም በሌላ በኩል ደግሞ አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ እና በተለይ የጎሰኝነት መዘዝን በታላላቆቹ ስቃይ እና በኢትዮጵያ ላይ ያደረሰውን ጥፋት የተረዳ የቀደመውም ሆነ የአሁኑ ትውልድ ኢትዮጵያን ከጎሳ ፖለቲካ ገላግሎ፣የቀደመ ስህተቶችን አርሞ እና የራስን አቅም አዳብሮ ኢትዮጵያን ለማንሳት በከፍተኛ ደረጃ መነሳሳት እና የተግባር ሥራዎች እየታዩ ነው። እዚህ ላይ መንግስት አሁን የሚሰራቸው የአጭር ጊዜ ሳይሆን የረጅም ጊዜ አገር የሚጠቅሙ ስልታዊ ስራዎች ሁሉ በእዚሁ ጥረት ላይ የሚጠቃለሉ ናቸው።መንግስት በራሱ ያሉበት ተግዳሮቶች ከላይ የተጠቀሱት ሁሉ ነጸብራቆች እንጂ ከሌላ ዓለም የመጡ አይደሉም። አገርን እንደ አገር ለማቆም ደግሞ በጎውን የመንግስት ሥራ መደገፍ እና ኢትዮጵያን እንደ አገር ማንሳት የማንም ቅን ዜጋ ውዴታ ሳይሆን ግዴታ ነው።

በእንግሊዝኛ ሰላም ፈላጊ፣በትግርኛ ጦርነት የሚጎስመው ህወሃት 

አሸባሪው ህወሃት ለትግራይ እንደ አንድ የኢትዮጵያ ክልል እንደ አገር ደግሞ ለመላዋ ኢትዮጵያ መከራ ሆኖባታል።ህወሃት ኢትዮጵያ ልጆቿን በጎሳ ከፋፍሎባታል፣ሃብቷን ለራሱ እና ለባዕዳን ዘርፏል አዘርፏል። ይህ አልበቃ ብሎ ''ኢትዮጵያን በትኜ ሲኦል እገባለሁ'' በሚል በግልጽ ባወጀው አዋጅ አማካይነት በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ በከፈተው ጥቃት አብረውት በወደቁ እና በተነሱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ ምግብ ላይ መርዝ ከመጨመር እስከ የተኙበት ለመግደል ሞክሯል። ከእዚህ ባለፈ በመቶሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ገበሬ በአማራ እና በአፋር በሚኖሩ ሰላማዊ ገበሬዎች ላይ በፈጸመው ወረራ ንጹሃንን ገድሏል፣ገበሬውን ዘርፏል፣ሆስፒታል ዘርፏል፣ትምህርት ቤቶች አቃጥሏል፣አብያተ ክርስቲያናት እና አብያተ መስጊዶችን በከባድ መሳርያ ደብድቧል።

ከእዚህ ሁሉ በኋላ የኢትዮጵያ ህዝብ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ተነስቶ የፋሺሽታዊ የህወሃትን እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ሆኖ አከሸፈው።በህወሃት የተጫረው ጦርነት ሺዎች የትግራይ ወጣቶችን አስጨርሶ፣ ከስራቸው እና ከኑሯቸው አፈናቅሎ መቀሌ ተመልሶ የትግራይ ህዝብ ላይ ሌላ ዙር ዘመቻ ከፈተ።በውጭ የሚኖረው የህወሃት የጭፍን አምላኪ እና የትግራይ ህዝብ ስቃይ የማይሰማው ስብስብ ደግሞ በህዝብ ስቃይ በየቲክቶኩ በመዝለል ተከታዮቹን ለማደንዘዝ ይጥራል። 

በቅርቡ ለህወሃት የመጨረሻው መጨረሻ ዕድል ተሰጥቶታል። በህወሃት የታገተው የትግራይ ህዝብን ስቃይ ለማሳጠር ከመንግስት በኩልም አዎንታዊ ሂደት መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በቅርቡ በተወካዮች ምክር ቤት ጉዳዩን የሚከታተል ኮሚቴ መመስረቱን ቢናገሩም አሁንም ህወሃት የተለመደ የማጭበርበር ሥራውን ቀጥሎበታል። ይህንኑ ሂደት ተከትሎ ህወሃት ለውጪው ማኅበረሰብ በእንግሊዝኛ ለሰላም እንደሚደራደር ተናግሮ ለትግራይ ሕዝብ እና በውጭ ላሉ ደጋፊዎቹ ደግሞ ጦርነት እንደሚቀጥል በትግርኛ ከሰሞኑ ተናግሯል። 

የሽብር ቡድኑ መሪ ደብረጽዮን ከሰሞኑ በትግሪኛ በሰጠው መግለጫ ላይ ሙሉ ትኩረቱ የተለመደው ድንፋታ ላይ ያተኮረ መሆኑ በግልጽ ታውቋል። የቀድሞው የመቀሌ ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት እና አሁን ደግሞ የሽብርተኛው ቡድን የውጭ ግንኙነት ቃል አቀባይ ክንደይ ገብረሕይወት በትዊተር ገጹ ላይ በአንድ አገር ውስጥ ሁሉት ሰራዊት ይኑር፣ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ውጭ የትግራይ ሰራዊት የሚባል ይኑር በማለት የሽብር ቡድኑን አቋም በግልጽ አስታውቋል። ይህ ባጭሩ ጦርነት እንቀጥል ነው።

C:\Users\3060\Desktop\kinde.jpg
ህወሃት የትግራይ ተወላጆችን ዳግም እንዳያቄላቸው በእጅጉ ሊጠነቀቁ ይገባል።

ፋሽሽታዊ ድርጅቶች አንዱ የጋራ መለያቸው እያታለሉ የሚነዱትን ሕዝብ እየሞተ ሳለ፣ እየሞትክ አይደለም እያሉ ባፈጠጠ ውሸት መደለል ነው። ህወሃት የትግራይን ህዝብ ስንት ጊዜ እንደዋሸው ለማስታወስ መጀመርያ የትግራይ ህዝብ ከትግራይ ውጭ ያለው በሙሉ በኢትዮጵያ ህዝብ ሊጨፈጨፍ ነው እያለ በካድሪዎቹ የሃሰት ዜና መንዛት ጀመረ። ሁሉ ውሸት መሆኑ በሂደት ታወቀ።በመቀጠል መቶ ሺዎች ተደፈሩ የሚል ውሸት መንዛት ጀመረ፣የዘርማጥፋት ተፈጸመ አለ።የራሱ ደጋፊዎች እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ሳይቀሩ ውሸቱን አጋለጡበት። ከእዚህ በኋላ በቅርብ አዲስ አበባን እቆጣጠራልሁ ልጆቻችሁን አምጡ ብሎ መቶ ሺዎችን ህይወት አስቀጠፈ። አዲስ አበባ ቀርቶ ጎንደር እና ደሴ እንደናፈቁት ቀሩ። ተመትቶ ሲወጣም ሽንፈቱን ለመሸፋፈን በህልም እንጀራ የድል ወሬ የትግራይን ህዝብ ማወክ ይዟል።እዚህ ላይ የህወሃት አዲስ ዘፈን ''ሪፈረንደም '' የምትል ሙዚቃ ነች። ሪፈረንደም ለህወሃት ለትግራይ ህዝብ አስቦ ያነሳው ሳይሆን ለስልጣኑ ዋስትና ትግራይን ለባዕዳን አስይዞ ለስልጣኑ ዋስትና የሚሰጠው መንገድ አድርጎ ስለወሰደው ብቻ ነው።

የትግራይ ተወላጆች ህወሃት ዳግም እንዳይቄላቸው መጠንቀቅ ብቻ ሳይሆን ሙሉ የክልሉ ህዝብ ስደተኛ፣ከስራ የተፈናቀለ፣ እና ተመጽዋች ያደረገው ህወሃት ዛሬም ለሌላ እልቂት ሊዳርገው ሲነሳ መንቃት እና ህወሃት ሳይሆን ቀድሞም የሞተለት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መቀሌ እንዲገባ እና በውጤቱም ህዝቡ ሰላማዊ ኑሮውን እንዲኖር እና ልጆቹም ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለስ ማድረግ ከህዝቡ የሚጠበቅ ወቅታዊ ሥራ መሆን አለበት።ከእዚህ በላይ መታለል እና ህወሃት ለሰላም ቅረብ እየተባለ የተሰጠውን የመጨረሻ ዕድል ከረገጠ ክልሉ ሙሉ በሙሉ ይበትነዋል።

ማጠቃለያ

ህወሃት ካለጦርነት መኖር ይችላል እንዴ? 

የሽብርተኛው የህወሃት የጥፋት ትውልድ እየከሰመ ነው። ጦርነት እና ጎጠኝነት ሁሉም ኢትዮጵያዊ መስማት የማይፈልገው ጉዳይ ነው። ይህ ማለት ግን በኢትዮጵያዊነት ህልውናው ላይ የሚነሳ ማንንም ይታገሳል ማለት አይደለም።በሌላ በኩል አሁንም ህዝቡ ታጋሽ ብቻ ሳይሆን ድንቅም ህዝብ ነው። ህወሃት የዚያን ያህል መርዘኛ የሆነ የጎሳ ጦርነት የሚያስነሳ ዘርን ማዕከል ያደረገ ቅስቀሳ ብቻ ሳይሆን ግድያ ሲፈጽም በመሃል ሃገር የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ላይ አንዳች ግጭት ሳይፈጠር ህዝብ ተከባብሮ በሁሉም ማኅበራዊ ተቋማት ውስጥ ተከባብሮ መኖሩ የኢትዮጵያን ህዝብ ድንቅ ህዝብ ያደርገዋል። የህወሃትን ያህል ግፍ የፈጸመ የሽብር ቡድን በሌሎች የአፍሪካ አገሮች ቢኖር በህዝብ መሃል በምን ያህል ደረጃ ግጭት ይፈጠር እንደነበር ለመገመት ቀላል ነው። ኢትዮጵያ ግን በእውነትም እግዚአብሄርን የሚፈራ ሰውን የሚያፍር ህዝብ ያለባት አገር ነችና ሌላ ቦታ ህወሃት በጎሳ ስም ለፈጸመው ግድያ ከጎረቤቱ የሚጣላ ኢትዮጵያዊ የለም። ይህ ብስለት እና ማኅበራዊ አንድነትን ለመበጠስ ህወሃት አሁንም ለመጨረሻው መጨረሻ መሞከሩ አይቀርም። በመሆኑም የትግራይ ህዝብ በህወሃት ላይ አለመነሳት ያለውን አደጋ ለአሁኑ ብቻ ሳይሆን ለመጪውም ነቀርሳ ማስቀመጥ ነው።
ሽብርተኛው ህወሃት የኢትዮጵያ ህዝብ ተነስቶ ሲይዘው እሪታውን ያቀልጠዋል። ሲለቀው ደግሞ ፉከራው አይጣል ነው።በተመሳሳይ ከውጭ ሆነው የሚያዳንቁትም እንዲሁ ናቸው።ህወሃትን የኢትዮጵያ ህዝብ ሲቀጣው ሻርፕ ለብሰው መቅለስለስ፣ ህዝብ ሲነሳ ደግሞ በየቲክቶኩ መዝለል ሥራቸው ነው። አሁን የሚዘለልበት ጊዜ አይደለም። መቶ ሺዎች ተፈናቅለው፣ አራስ እናት ልጇን እያጠባች የምትበላው ባጣችበት ጊዜ በእርዳታ እህል የተነፋፉ እነ ጌታቸው ረዳን እያዩ መዝለል ምን ዓይነት የአዕምሮ ድህነት ነው?

አሁን ኢትዮጵያውያን በያላችሁበት ክልል በህወሃት የተቃኙ የጽንፍ ፋሽሽታዊ የጎሳ ስሜታቸው ከሰውነት አስተሳሰብ የባሰባቸው አሉ። የእዚህ ዓይነቶቹ በትግራይ ብቻ ሳይሆን በኦሮምያም በአማራም በሌሎችም ክልሎች አሉ። እነኝህ ለሠላሳ ዓመታት ውስጥ ተጸንሰው ያደጉ ናቸው። አሁን ጊዜው የህዝብ መሆን አለበት። ህዝብ የጎሳ ጽንፈኞች እንዲመሩት ዕድል ላለመስጠት በሁሉም መስክ መስራት አለበት።ትግራይ ለበቀለው ፋሺዝምም ሆነ በኦሮምያ የሚንቀሳቀሰው ሸኔ እንዲሁም በአማራ ስም የጽንፍ አስተሳሰብ የሚያራምድ ሁሉ በህዝብ መገታት አለባቸው። አስታራቂው መንገድ የኢትዮጵያ መንገድ ነው።በግብጽ ''ኢትዮጵያን እንደ ዩክሬን ካላደረኩ ሰላም 
አላገኝም '' የሚሉ ተናጋሪዎች በሚደነፉበት ጊዜ ኢትዮጵያውያን ከትግራይ እስከ ጅጅጋ፣ ከኢልባቦር እስከ ሓረር፣ከሞያሌ እስከ ጎንደር ሁሉ መተባበር እና ህወሃትን የመሰሉ የባዕዳን ወኪሎችን ለፍርድ የማቅረብ ሃላፊነት አለበት።ቀድሞም ይጠብቀን የነበረው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መቀሌ ይግባልን! ትግራይን ከኢትዮጵያ ለመገንጠል እና ለባዕዳን ለማስያዝ የሚሮጠውን ህወሃት ዳግም አይሸጠንም! የሚሉ ድምጾች ከትግራይ መሰማት አለባቸው።

ከኢቢሲ ሰኔ 8/2014 ዓም ካስተላለፈው ልዩ ቃለ መጠይቅ 


Tuesday, June 14, 2022

የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ለተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ያደረጉት ማብራርያ (ሙሉ ቪድዮ)

ቪድዮ ምንጭ = ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ሰኔ 7/2014 ዓም)

ክፍል አንድ 


ክፍል ሁለት





Sunday, June 12, 2022

A letter from GUDAYACHN to Addis Fortune Newspaper's June 4, 2022 article under the title ''Ethiopia sleeps at the Wheel in the Race for the Regional Integration''


By Getachew Bekele Damtew
Gudayachn Editor.

Dear Fortune News Paper, I read an article in your paper under the title ''Ethiopia sleeps at the Wheel in the Race for the Regional Integration'' dated June 4,2022. The article mentioned the African Development Bank’s (AfDB) most recent annual conference in Accra, Ghana. The fourth paragraph of the article stated ''A continental free trade area that brings down tariffs and duties could help countries leverage the strengths of their respective countries. Africa has the least intracontinental trade globally, with only 14.4pc of collective exports going to regional neighbors''. It is quite true that having free trade area and bringing tariffs and duties help African countries leverage. However, regarding Ethiopia, there are key issues that most Development Studies analysts or Economists are missing or do not take into consideration.

In relation to Ethiopia's integration with the Regional market of Africa, I think, there are three key points we should not forget.

One, Ethiopia is one of the ancient lands in the world that can not enter simply with any contemporary market. This is the land that has its own historical background and regional relationship. Therefore, it is important to understand the historical background of the country. This is a land that has never been colonized and her Economic structure is made by her own citizens since the end of the second world war but with great foreign influence. This may need more explanation. But for the time being, this is not the right platform to write more. 

Two, most of the Ethiopian business organizations are owned by her own citizens and shared partially by foreigners. Here I am not saying that there are not fully owned foreign companies in Ethiopia. However, compared to Kenya, Uganda, and Tanzania, Ethiopian Economy is more incorporated by the State or citizens. This means these nationally incorporated companies need to cross the borders and start investing within the region's countries.

Three, Ethiopia's Economy was almost fully under a state-led Economy til 1991. Even after 1991, an ethnocentric ideology of the brutal TPLF economic policy created more crises. The ethnocentric policy of TPLF has destabilized not only the Economic sector but the political and even the Education system which is the key producer of skilled manpower to the Economy. For the last four years, the current Government led by PM Abiy Ahmed (Ph.D.) is showing tremendous efforts to adjust the wrong policies of the former regime in all sectors.

Here, I fill so dares to comment on your article that your conclusion is not inclusive of all directions and it is just one-sided, without analyzing the real situations on the ground. The Ethiopian Economy is a giant Economy if we use the real multidimensional measurement  (i.e. if we are not putting every measurement in terms of the Euro or US dollar monetary value only). This is an economy with over 115 million people market and over 2.5 million diasporas all over the world active contribution both in skilled human capital and the Financial one.

When we back to the Regional Economic Integration issue of Africa, the current African Economy integration can not be seen without the direct or indirect role of the Multi-National Corporations (MNC) involvement, particularly in the case of Kenya, Tanzania, and Uganda. Because as I mentioned above the Foreign business involvement in these three East African countries' economies is more influential compared to Ethiopia. Therefore, economic integration is easy in other East African Countries. Because most MNC has branches in all countries. Therefore they are not only pushing for economic integration but also for shared wealth and investment. 

When we come to Ethiopia, the situation is a bit different. There is no single foreign Financial Institution in Ethiopia at this very time. All banking operations in the country, both the Government and private banks are owned by domestically incorporated Banks and they are operating their business soundly. In fact, the Ethiopian current Government said foreign banks will get permission to run their Banking business in the Ethiopian Financial market. The Telecom business in Ethiopia is now opening to foreign investors. 

Economic integration means for MNCs which have a long hand in the African Economy means to expand their market share in African Market and link each other by crossing the border under the name of different arrangments. However, when we come to Ethiopia's case, Economic integration means the real African incorporated companies link each other through sound regional trade laws and regulations. 

Now, it is better to conclude my comment with the following expressive words. The western world should understand the historical, cultural, and even historical resilient nature of the Ethiopian people in all aspects and must come only in a soft way in relation to any policy ideas. Once Ethiopians, believe in some sort of policy, that does not clash with the above-mentioned three values, they do not have a problem implementing it. However, if there is policy imposition by force, they will never accept it. Regional Economic Integration with the Horn of Africa will come today or tomorrow. However, it will be successful and brings benefits for all stakeholders including the western MNCs, if and only if it goes smoothly without any foreign policy imposition and provides full respect to the unique historical, cultural, and Economic background of Ethiopia. It is a big failure to put all African countries' market situations within one bag. 

============////==========

Tuesday, June 7, 2022

የዛሬ 60 ዓመት ንግስት ኤልሳቤጥ ኢትዮጵያን ሲጎበኙ (ቪድዮ) Sixty Years ago the Queen visited the historical land of Ethiopia.(Video)

የእንግሊዟ ንግስት ኤልሣቤጥ የሰባ ዓመታት የንግስና እና የአገልግሎት ዘመን እንግሊዝ ሰሞኑን በልዩ ሁኔታ እያከበረች ነው። የዛሬ 60 ዓመት ንግስት ኤልሳቤጥ ኢትዮጵያን ሲጎበኙ (ቪድዮ)
Her Majesty Queen Elizabeth became the first British monarch to celebrate a Platinum Jubilee, marking 70 years of service. Sixty Years ago the Queen visited the historical land of Ethiopia. (Watch the Video)



ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።