ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, November 26, 2023

በውግዘት ውስጥ ላሉት፣አሁንም በድፍረት ለሚሄዱት ለትግራይ የቀድሞ ጳጳሳት አልቅሱላቸው።


  •  አክሱም ጽዮን በክርስትና ታሪክ ለሁለት ሺህ ዓመታት ያህል ያላየችውን የድፍረት ስራ በቅዱስ ሲኖዶስ በተወገዙት የትግራይ አባቶች እያየች ነው።
  • የእነርሱን አካሄድ እየተመለከተ ዝም ብሎ የሚገለገለው የትግራይ ምዕመን፣ የእዚህ ዓይነት አካሄድ ከአባቶቻችን አልተማርንም ተዉ! ማለት ይገባዋል።

እራሳቸውን ከቅዱስ ሲኖዶስ ለይተው፣ክርስትናን በመንደር ለመመተር የሚሞክሩት የትግራይ አባቶች ከቅዱስ ሲኖዶስ ውግዘት እና ስልጣነ ክህነት መያዝ በኋላም አባ ሰረቀን ጵጵስና ሾመናል ብለዋል። ይህ የድፍረት ስራ አክሱም ጽዮን በክርስትና ታሪክ  ለሁለት ሺህ ዓመታት ያህል ያላየችውን የድፍረት ስራ በትግራይ አባቶች እያየች ነው።

ይህ በትግራይ ያሉ አባቶች እያደረጉት ላለው አዕምሮውን የሳተ ሰው ስራ ምንም ሃተታ አያስፈልገውም።ድርጊቱ ስንት የበቁ አባቶች ዘግተው ቀን ከሌሊት ለዓለም የሚጸልዩ አባቶች ባሉባት የትግራይ ክልል እና በአክሱም ጽዮን ፊት የተፈጸመ ድፍረት ነው።ጥፋት በበለጠ ጥፋት አይስተካከልም።በውግዘት ውስጥ ላሉት፣አሁንም በድፍረት ለሚሄዱት ለትግራይ የቀድሞ ጳጳሳት አልቅሱላቸው።አሁን ለአባቶች የሚያስፈልጋቸው ለቅሶ ነው።ከልቦናቸው አይደሉም።ከልቦናው የሆነ አባት ቅዱስ ፓትርያሪክ በብዙ ድካም ከደጁ ሲመጣ የቤተክርስቲያን ደጅ ዘግቶ አይሸሸግም፣ቡራኬ ሊቀበል እየተጣደፈ ሄዶ ጉልበት ስሞ ይባረካል።

አሁን የትግራይ አባቶች ከቀልባቸው አይደሉም።ምን እያደረጉ እንደሆነ፣ምን እየሰሩ እንደሆነ ከአዕምሯቸው ጋር ስላልሆኑ አያውቁትም። አሁን የሚያስፈልጋቸው የሚያደርጉትን አያውቁምና የሚያለቅስላቸው፣ ወደ ቀልባቸው መልሳቸው ብሎ የሚያነባላቸው ሰው ያስፈልጋቸዋል። የእነርሱን አካሄድ እየተመለከተ ዝም ብሎ የሚመለከተው የትግራይ ምዕመንስ? ቢያንስ የእዚህ ዓይነት አካሄድ ከአባቶቻችን አልተማርንም አይልም? በመንደር ተሰባስቦ ከቅዱስ ሲኖዶስ አንድነት ወጥቶ እንደፈለጉ በመሄድ የሚሰጥ ስልጣነ ክህነትን የትግራይ ምዕመናን ከአባቶቻችን አልተማርነውም።ከየት አመጣችሁት ብሎ አይጠይቅም? 



Saturday, November 25, 2023

Tuesday, November 21, 2023

አቡነ ኤርምያስ ከተናገሩት ውስጥ እውነት ያልሆነ አንድ ቃል ማግኘት አልቻልኩም።

አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ
  • ''በማንም ተጽዕኖ ውስጥ ወድቄ በማንም ተናገር ተብዬ የተናገርኩት የለም.።ወደፊትም እናገራለሁ ብዬ አላስብም።መንፈስቅዱስ ይጠብቀኝ። '' አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ

=========
ጉዳያችን ምጥን
=========

የሰሜን ወሎ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ አቡነ ኤርምያስ ሰሞኑን ከላስታ ላሊበላ ህዝብና ካሕናት ጋር በተደረገ ስብሰባ ላይ የተናገሩትን መነሻ በማድረግ ሁሉም ለምን የእኔን ሀሳብ አላንጸባረቁም? በሚል የተለያዩ ስሞታም፣ወቀሳም አለፍ ሲልም ዘለፋ ሲዘነዘር እየሰማን ነው። በሌላ አንጻርም አቡነ ኤርምያስ የተናገሩት እውነት መሆኑን የተናገሩም፣የመሰከሩም አሉ።በአቡነ ኤርምያስ ከተናገሩት አንዳንዶችን የከነከናቸው ነገር ግን በቀጥታ ጉዳዩን ሳያነሱ ዙርያ ጥምጥም የሚሄዱባቸው ሦስቱን ነጥቦች ብቻ እንመልከት።ወደ ሦስቱ ነጥቦች ከመሄዴ በፊት ለሁሉም ግንዛቤ እንዲሆን ሁለት ነጥቦች ላንሳ።

የመጀመርያው ነጥብ፣የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች የስነ መንግስት ጉዳይ የማይገባቸው እንዲያው ካለ እውቀት እንደተናገሩ አስመስለው የሚያቀርቡ በጣም እንደተሳሳቱ ማስረዳቱ ጥሩ ነው።የአባቶች ብቃት ከዓለማዊው ትምሕርት ባለፈ መንፈስቅዱስ ባወቀ የሚረዱትን የመረዳት አቅምም መኖሩን ማሰብ ተገቢ ነው።

ሁለተኛው ነጥብ፣የስነ መንግስትን ጉዳይ መግፋት የቤተክርስቲያን ጉዳይ አይደለም።ይህም ሆኖ በነባራዊው ዓለም ላይ የምትኖር ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ዘመንም የመንግስት ጉዳይ አንስተው ክርስቶስን ለመፈተን ''ከፈሪሳውያንና ከሔሮድስ ወገን ሰዎችን ላኩ'' በማለት  መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያለው ቃል ይነግረናል። ንባቡ እና የአባቶቻችን ትርጓሚ እንደሚከተለው ነው።

የማርቆስ ወንጌል 12፣14 - 17  ''መጥተውም። መምህር ሆይ፥ የሰውን ፊት ሳትመለከት በእውነት የእግዚአብሔር መንገድ ታስተምራለህና እውነተኛ እንደ ሆንህ ለማንምም እንዳታደላ እናውቃለን፤ ለቄሣር ግብር መስጠት ተፈቅዶአልን ወይስ አልተፈቀደም? እንስጥን ወይስ አንስጥ? አሉት። እርሱ ግን ግብዝነታቸውን አውቆ። ለምን ትፈትኑኛላችሁ? አየው ዘንድ አንድ ዲናር አምጡልኝ አላቸው። እነርሱም አመጡለት። ይህች መልክ ጽሕፈቲቱስ የማን ናት? አላቸው፤ እነርሱም። የቄሣር ናት አሉት።ኢየሱስም መልሶ። የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር አስረክቡ አላቸው። በእርሱም ተደነቁ።''

በአባቶቻችን ትርጓሜ ጌታችንን ለመፈተን የመጡት ግብር መስጠት ተፈቅዷል ካለን ይሄ ምድራዊ ነው እንጂ ሰማያዊ አይደለም ስለምድራዊ ግብር ያወራል ሊሉት፣ ግብር አትስጡ ቢላቸው ደግሞ ለመንግስት ሄደው ግብር አትክፈሉ የሚል ተነስቷል ብለው ሊከሱት እንደሆነ አውቋልና ዲናሯን አምጡ ብሎ ዲናሩ ላይ ያለችውን ጽሕፈት አሳይቶ የቄሳርን ለቄሳር፣የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሄር ስጡ ብሎ በመመለሱ የሚከሱበት አጡ በማለት የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን አብራርታ ታስተምራለች።

ቤተክርስቲያንን ከፖለቲካ ዕይታቸው አንጻር ለመለወስ እና ጥፋት ነቁጥ ለመንቀስ የሚደክሙ በየትኛውም የጎሳ ስብስብ ውስጥ ቢሆኑ ከላይ ከተጠቀሱት ከፈሪሳውያንና ከሔሮድስ ወገን አስተሳሰብ የተለዩ አይደሉም። አቡነ ኤርምያስ የአባትነታቸውን የተናገሩትን እውነት ለአንዳንዶች የራስ ምታት ቢሆንባቸውም ዕውነትነቱ ላይ ግን የሚያመጣው አንዳች ለውጥ የለም።

አቡነ ኤርምያስ ከተናገሩት ውስጥ እውነት ያልሆነ እስኪ አንዲት ቃል አውጡ? 

''አራት ኪሎ ቢገባስ''

አንዳንዶች የአቡነ ኤርምያስን እውነት አልዋጥ ካላቸው ውስጥ በቀጥታ አያናገሩትም እንጂ ከላይ በተጠቀሰው መድረክ ላይ ከተናገሩት  ቀደም ብለው ችግሮች እንዳይፈጠሩ ለእርቅ የሄዱበት መንገድ እንደነበርና በኋላ አንድም ካህን ቢመጣ በጥይት እንለዋለን ድረስ የሚሉ ቃላት በአማራ ክልል በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች በኩል መሰማቱን በመጠኑ ጠቁመው፣ በታጣቂዎቹ አካሄድ ላይ ግን እንደማይስማሙ አባታዊ ምክራቸውን ሲለግሱ እንዲህ ብለዋል ''በወንድሞቼ አካሄድ አልስማማም። ደግሞስ አራት ኪሎ ቢገባስ'' ካሉ በኋላ ዘላቂ  መፍትሄ እንደማይሰጥ ይህ ደግሞ ሌላው እስኪዘጋጅ እንጂ ዘላቂ ሀገራዊ ሰላም እንደማያመጣ መክረዋል። ከእዚህ ዕውነት ውስጥ ምን ውሸት መንቀስ ይቻላል? በ21ኛው ክ/ዘመን ስልጣን በጠበንጃ በመነጣጠቅ መፍትሄ እንደማይመጣ ከእዚህ ይልቅ ሌሎች የሰላማዊ የትግል መንገድ መከተል አስፈላጊነት ላይ ምን ስህተት ይወጣለታል?

''ላሊበላ ለምን ከተሙ?''

አቡነ ኤርምያስ ያነሱት ሌላው ነጥብ ላሊበላ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናቱ ብቻ ሳይሆኑ ከተማዋ በራሷ ከተማ ሳትሆን የተቀደሰ ቦታ ነች።መገዳደል ያስቀስፋል በሚል የገለጹበት እውነት ነው። በእዚህም ላሊበላ መክተም ለምን? የሚለው መሰረታዊ ጥያቄ እና ከገዳሙ አውጥቶ መግደል ምን ዓይነት ህሊና እንደሆነ የገለጹበት መንገድ ምን ነቁጥ ይገኝበታል?

''ውጪ ሆነው ሬሳ እየሸጡ የሚኖሩ''

ይሄ ውሸት ነው? የዩቱበር ሸቀጥ ለመሸቀጥ ያልሞተ ሞተ፣የወደቀውን ተሰበረ፣ እያለ በውጭ ሀገር ሶፋ ላይ ተቀምጦ የራሱን ልጆች ወደ ትምህርት ቤት እየላከ በአማራ ክልል ከሦስት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ልጆች እስከ ኅዳር ወር መጀመርያ ድረስ በጸጥታ ችግር አለመመዝገባቸው ትንሽ ቅሬታ ያልፈጠረበት፣ነገር ግን ''በለው!'' እያሉ ሲፎክሩ የሚውሉ እያየን አይደለንም እንዴ? እነኝህ አስከሬን ካልታየ ዩቱባቸው ይሸጣል? ይህንን እውነት ለምን እንክዳለን? የህወሓት አድናቂዎች በትግራይ ምስኪን ህዝብ ሞት ከውጭ ሆነው ሲያበረታቱ የነበሩ ዛሬ ሞቶን እና መርዶውን ለምስኪን የትግራይ እናቶች አስታቅፈው እነርሱ ዛሬ የት ናቸው? በአማራ ክልልስ እየሆነ ያለው በወሬ የሬሳ ሽያጭ መነገድ የተለየ ነገር አለ? 

''በጦርነት ሰላም አይመጣም፣ ወንድም ወንድሙን አጥቅቶ፣ፋኖ መከላከያን አጥቅቶ ወሰን ሊያስከብር አይደለም፣ ጉዳዩ ይህ እንደ ሀገር ያሰጋል።''

እዚህ ላይ የሚነቀስ ምን ውሸት አለ? እውነቱን ከሚናገሩት ጥቂቶች በቀር፣ ሁሉም ''ካድሬ ይሉኛል'' ብሎ አፉን ይዞ ነው እንጂ ምንም ይሁን ምን መከላከያውን የበላ ህዝብ የሚበላው ጠላት ዕለቱን መጥቶ እንደሚበትነው፣ እርስ በርሱም ወደ የማያባራ ጦርነት እንደሚገባ ከሶርያ ባንማር፣ከሊብያ፣ከሊብያ ባንማር ከየመን፣ ከእነኝህ ሁሉ መማር ቢያቅተን እንዴት ከቅርብ ጎረቤታችን ሱዳን መማር አቃተን። አቡነ ኤርምያስ ሀገር እንዲህ መሄድ የለበትም ሲሉ አለመስማት ብቻ ሳይሆን ለስድብ አፍን ማሾል ምን ዓይነት መረገም ነው?

አቡነ ኤርምያስ በእዚሁ መድረክ ላይ መንግስትንም በተገቢ ቃላት ወቅሰዋል።በአማራ ክልል የሚገኙ ታጣቂዎችን ጉዳይም ለመንግስት በሚገባ አካሄዱን እንዲፈትሽ ሲያሳስቡ ከተናገሩት ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል 
  • የተቆጡ ወገኖች አሉ።ሁላችንም እኔንም ጨምሮ ተቆጥተናል።
  • እነኝህ ወገኖች ከመከላከያ ጋር አብረው የተዋደቁ ናቸው።
  • መንግስት ዝቅ ብሎ ለእነኝህ ወገኖች የሚመጥን መድረክ መንግስት አዘጋጅቶ መፍትሄ ማምጣት አለበት።
  • ክርስቶስ ዝቅ ብሎ መጥቶ አዳምን አድኖ የነበረበትን መንገድ ምሳሌ ጠቅሰዋል።
  • መከላከያ ከገባ በኋላ ተፈጽሟል የተባለውን ዘረፋ መከላከያ አጣርቶ ይህንን ያደረጉትን እንዲቀጣ አሳስበዋል።
  • ''የመረረው ድሃ ይገባል ከውሃ'' እንዲሉ መንግስት ባለበት ሀገር ዛሬ ከዋና ከተማዋ ተነስቶ ሰው እንዴት ለመሄድ የሚፈራበት ሁኔታ ይፈጸማል?
እና ሌሎችም ምክረሃሳቦችን አቅርበዋል።

ለማጠቃለል፣ከአቡነ ኤርምያስ ምክረሃሳብ ውስጥ የሚገኝ አንድ ውሸት ካለ እስኪ አውጡ? ስለሌለ የምታወጡት አንድም ውሸት የለም። በእዚህ የውይይት መድረክ ላይ ከተሳታፊዎች ደጋግሞ ከተነሳው ቅሬታ ውስጥ አንዱ እና ህዝቡን ያስቆጣው ጉዳይ ግን ነበር። የከባድ መሳርያ ድምጽ በእዚያ መጠን ለምን እንዲተኮስ ተደረገ የሚለው ገዢው ሃሳብ ነው። ይህንን ጉዳይ መከላከያ በከፍተኛ ትኩረት ሊመለከተው የሚገባ ነው።አሁንም ወደ ህዝቡ ወርዶ የሚሰጠው ማብራርያ ካለ ጉዳዩን ማብራራት አለበት።ይህ ጉዳይ የአብዛኛው ተሳታፊን እና ካሕናቱን አስተያየት የሸፈነ ነበር። አቡነ ኤርምያስ ዘግይተው በሰጡት ማብራርያ ደግሞ ''በማንም ተጽዕኖ ውስጥ ወድቄ በማንም ተናገር ተብዬ የተናገርኩት የለም.።ወደፊትም እናገራለሁ ብዬ አላስብም።መንፈስቅዱስ ይጠብቀኝ። '' በማለት ተናግረዋል።ሀገርን ያለ አንድ መስካሪ ባዶ አይተዋትም። 

የአቡነ ኤርምያስን እና የተሳታፊዎችን አስተያየት የያዘው ቪድዮ



 

Tuesday, November 14, 2023

በአጼ ቴዎድሮስ፣ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴና ኮ/ል መንግስቱ ላይ የሰራነውን የመሪዎቻችንን በጎ ሀሳብ የመጎተት ክፉ ባሕል በጠ/ሚ/ር ዐቢይ ላይ አንደግምም!


ፎቶ - አጼ ቴዎድሮስ፣አጼ ኃይለስላሴ፣ኮ/ል መንግስቱና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ
  • ዛሬ አጼ ቴዎድሮስ፣ቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴ፣ ኮ/ል መንግስቱ እያልን ስንጣራ መሪዎቹን ክነበረ ህልማቸው በየዘመናቸው ያልጎተትን  ጨዋዎች እንመስላለን።
============
ጉዳያችን ምጥን
============

የመሪዎቻችንን በጎ ሀሳብ ጎታቾቹ እኛ!

ኢትዮጵያ በታሪኳ ድንቅ መሪዎች መርተዋታል። የመሪዎቿን አስደናቂነት እኛ ከጻፍነው በላይ በየዘመኑ ''ሰለጠኑ'' ከሚባሉ ሀገሮች የመጡ ጸሐፊዎች የጻፉት እና አድንቀው የገለጡበት መንገድ ይበልጣል። ድንቅ የተባሉ መሪዎቻችንን ርዕይ በመጎተት ወደፊት እንዳይሄዱ በማድረግ ግን የሚያክለን የለም።

አጼ ቴዎድሮስ

አጼ ቴዎድሮስ በቀድሞ ስማቸው ካሣ፣ከቋራ ምዕራብ ጎንደር ተነስተው የኢትዮጵያ ንጉሰነገስት ለመሆን ሲነሱ አንዱና ዋናው ዓላማቸው  በዘመኑ በዘመነ መሳፍንት ታውካ የነበረችው ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ እና ወደ የቀደመ ክብሯ መመለስ መሆኑን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ መናገራቸውን የታሪክ ድርሳናት ያሳዩናል። ንጉሱ ከነገሱ በኋላ በወረራ ውስጥ ያለች ኢየሩሳሌምን ገና ነጻ ያወጣሉ ተብሎ ይነገርላቸውም ነበር። ይህንንም አዝማሪ ሳይቀር
 '' ካሳ ብሎ ፈረስ ካሳ ብሎ ስም፣
    ዓርብ፣ዓርብ ይሸበራል ኢየሩሳሌም።''

እያለ የሚያበረታታቸው የመኖሩን ያህል፣ ሌት ተቀን እጁን በአፉ ላይ አድርጎ ሲያማ የሚውልም ነበር። ንጉሱ አይቻልም የሚሉት ነገር የለም።ኢትዮጵያ ከመላው ዓለም ጋር የነበራት ግንኙነት ከ16ኛው ክ/ዘመን በኋላ በጣም በተዳከመበት ዘመን የነበሩት ንጉስ ከአውሮፓ የሚመጡ ጥቂት ሰዎች ጋር በጥልቅ በመወያየት ስለ ቴክኖሎጂ በመረዳታቸው ሴቫስቶቮል የተሰኘ መድፍ ለማሰራት ጥረት ያደርጉ መሪ ናቸው። እኝህ የኢትዮጵያን አንድነት ከዘመነ መሳፍንት በኋላ ለመመለስ ህይወታቸውን ሰጥተው የታገሉ መሪ፣ኢትዮጵያን ከዘመኑ የቅኝ ገዢዎች በደከሙበት የአንድነት ትግል መሰረት የጣሉ እና ኢትዮጵያን ለማሻገር ቀን ከሌሊት ያለሙ መሪ በመጨረሻ ላይ እኛ ጎታቾቹ እንግሊዞች ሲወሯቸው መቅደላ ላይ ብቻቸውን አጋፍጠን፣ እራሳቸውን እንዲሰዉ ከማድረግ በላይ ልጃቸውና ባለቤታቸው ታግታ ስትወሰድ ያጀብን መሆናችንን ማሰብ አለብን። በወቅቱ ከንጉሱ በኢትዮጵያ ላይ ከነበራቸው ህልም ይልቅ የመንደር ቂጣ መጉደል ከትልቅ ነገር ወስደው በንጉሱ መሞት ላይ የፈነደቁ ነበሩ። የእኛ ታሪክ ለኢትዮጵያ ህልም የነበራቸውን መሪዎች እግር መጎተት የነበረ አሳፋሪ ታሪካችን ነው።

አጼ ኃይለሥላሴ 

አጼ ኃይለሥላሴን እግር የመጎተት ሥራ የተጀመረው ገና አባታቸው ራስ መኮንን የአጼ ምንሊክ ባለሟል ሆነው ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ የጀመረ ነው።አጼ ኃይለስላሴ ከአልጋወራሽነት ዘመናቸው በኋላ የጣልያን ጦር ተሸንፎ እንደወጣ የገጠማቸው የእግር ጉተታ ይህ ነው የሚባል አይደለም። ንጉሱ በሱዳን፣በኦሜድላ በኩል ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ጎጃም ላይ ከነበሩት አርበኞች ውስጥ በላይ ዘለቀ አንዱ ነበር። ንጉሱ በጎጃም በተዘጋጀ የእንኳን ደህና መጡ ሰልፍ ላይ አርበኞች በንጉሱ ፊት ሰላምታ እያቀረቡ ሲያልፉ በላይ ዘለቀ ግን የንቀት መልክ አሳይቶ ማለፉን ይህንን ታሪክ የሚያውቁ አባት የነገሩትን የእዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ሰምቷል። ከእዚህ በኋላ ንጉሱ በክብር አስጠርተው ደጋግመው በላይ ዘለቀን አነጋግረውታል። በአንድ ወቅት ንጉሱ ምናልባት በትምሕርት ብዙ አለመግፋቱ ይሆናል እኛ የምናየው የኢትዮጵያ አደጋ ለእርሱ ያልታየው አሁንም ለመሸፈት ያስባል የሚል ዜና ንጉሱ ደርሷቸው በነጻ ወደ ትምሕርት ቤት ከመግባትና የማዕረግ እና የ ሀገር ሹመት የትኛውን እንደሚመርጥ ለበላይ ዘለቀ እስከማቅረብ ንጉሱ ደርሰው ነበር።

ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ኢትዮጵያን ለማሳደግ ጊዜ አትሯቸው ይሮጣሉ። በሌላ በኩል ግን የገበሬ አመጽ አንድ ጊዜ ከጎጃም፣ሌላ ጊዜ ከባሌ ሌላ ጊዜ ደግሞ ከትግራይ ቀዳማዊ ወያኔ የተነሱ የገበሬ አመጾች ኢትዮጵያን ወደ ዘመናዊ ምዕራፍ ለማሻገር የገጠሟቸው የእግር ጉተታ ፈተናዎች ነበሩ።ንጉሱ በቀረ ዘመናቸው እነኛን ሁሉ የእግር ጉተታዎች አልፈው በእርጅና ዘመናቸው ቀድመው የስልጣን ወንበሩን ሳያስተካክሉ ቢቀሩም በመጨረሻ በተነሳው አብዮት ግን መፍትሄ እንዲሆን የመርማሪ ኮሚሽን ተቋቁሞ ነገሩን በህግ ለመምራት ቢያስቡም፣ወታደሩም መፈንቅል በአራተኛ ክ/ጦር ተሰብስቦ እያደረገ መሆኑን እየሰሙ እና የክብር ዘበኛ ሄደን እንዋጋ ቢላቸውም ''ተዉ! እኛው ያስተማርናቸው ናቸው '' ለክፉ አይጥሉም በሚል ቤተመንግስታቸው ተቀምጠው ቢጠብቁም፣ በመጨረሻ እኛ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ እና ለዓለም ድንቅ ሥራ የሰሩ መሪ ክብራቸውን ያዋረድን መስሎን በቮልስዋገን መኪና ጭነን ከመሳለቅ ባለፈ ህይወታቸው እንዲያልፍ አድርገን እና የቀሩ 60 ባለስልጣኖችን እና ለኢትዮጵያ መልካም የሰሩ ልጆቿን በአንድ ቅዳሜ ምሽት ገድለን  አብዮት ተካሄደ ብለን የፎከርን የአሳፋሪ ታሪክ ባለቤትም ነን። የመሪዎቻችንን እግር መጎተት የነበረ ክፉ ባህላችን ነው።

ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማርያም 

ኮ/ል መንግስቱ የንጉሱን መንግስት ተክተው ''ታሪካ የጣለብን አደራ ነው '' በሚል የወታደራዊ ደርግ እየመሩ ኢትዮጵያን መሩ። ኮ/ል መንግስቱ በመጀመርያ የስልጣን ዘመናቸው ኢትዮጵያ በተለይ ከሱማልያ ለገጠማት ወረራ ያደረጉትን ጥሪ ህዝብ ሰምቶ ኢትዮጵያን ታድጓል።በመቀጠል ከኮ/ል መንግስት የአስተዳደር ግድፈት እንዳለ ሆኖ ነገር ግን የደርግ መንግስት በመራቸው በሦስት ቁልፍ ጉዳዮች ላይ የኢትዮጵያ ህዝብ አድምቶ ቢሰራበት ኖሮ እና ከእግር ጉተታ ብንድን ኖሮ ኢትዮጵያን በብዙ መንገድ እናሳድጋት ነበር። ይሄውም የደርግ መንግስት ያቀዳቸው የሰፈራ እና መንደር ምስረታ ( የመለስተኛ ከተሞች ፈጠራ)፣ የመሰረተ ትምሕርት ዘመቻ እና የኢትዮጵያ በቀይባሕር ላይ ያላት ታሪካዊ ባለቤትነት የሚሉት ይጠቀሳሉ። ሆኖም ግን በእነኝህ ቁልፍ ዳዮች ላይ ከፍተኛ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ በመደረጉ የመንግስት ተቀያያሪነትን ተገንዝቦ የልማት ፕሮጋራሞቹን ግን ወደፊት ይዞ  ከመሄድ ይልቅ በማጥላላት ላይ ውለን አደርን። ውጤቱ ግን ኢትዮጵያ ከረሃብ ያልተላቀቀች ብቻ ሳይሆን የነበራትን ወደብ ያጣች ሀገር ሆነች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ 

በያዝነው 21ኛው ክ/ዘመን መጀመርያ ላይ ኢትዮጵያ ባለችበት የለውጥ ሂደት ላይ ኢትዮጵያን የመምራት ዕድል ያገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በአስተዳደራቸው ሂደት ላይ የቱንም ያህል ጥያቄ ያለው ሰው ቢኖር መጠየቁ እና ይህ ይስተካከል፣ ይህ ይታረም ማለቱ እና በምክንያታዊ መንገድ መሞገት በራሱ ጥፋት አይደለም። ይልቁንም ከሴራ አስተሳሰብ በራቀ መንገድ ሙያዊ ሙገታ እና እንዲስተካከል በሰላማዊ መንገድ መታገሉ ሊኖር የሚገባው ነው። ከእዚህ ባለፈ ዛሬም እየደገምነው ያለው የነበረ ክፉ ባሕላችን ግን አሁንም በዩቱበሮች እና የነገን ሳይሆን የዛሬን ከከንፈር እስከ አፍንጫ ብቻ የሚያይ አስተሳሰብ ይዘን ግዙፍ የሆኑ እና ትውልድ አሻጋሪ የሆኑ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሀሳቦች ላይ ቁጭ ብሎ አቃቂር በማውጣት ከአጼ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ የተሰራውን የእግር ጉተታ እኩይ ተግባር ለመድገም የሚደረገው እሽቅድምድም ሌላ አሳፋሪ የታሪካችን አካል እንዳይሆን ሁሉም ይህ ክፉ ታሪክ እንዳይደገም ለኢትዮጵያ ልዕልና ሲል ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዘመን ተሻጋሪ ሀሳቦች ጋር አብሮ መቆም ተገቢ ነው።ስለ የኢትዮጵያ የባሕር በር ሲነሳ የኢትዮጵያን እንጀራ በልቶ እንዳላደገ ሰው ሀሳቡን ችላ ማለት፣ ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ተክል እናልብሳት ሲባል የሚያሾፍ፣ የከተማ ወንዞችን እናልማ ሲባል አቃቂር የሚያወጣ፣ መጻሕፍት ቤት ሙዜየም ሲሰራ ለማቃለል የሚጣደፍ ይህ ሁሉ እግር ጎታችነት ብቻ ሳይሆን የነበረ እኩይ ባሕላችንን የመድገም ሙከራ ነው።ኢትዮጵያውያን አንጸባራቂ ታሪክ ያለንን ያህል የመልካም እና ብሩህ አዕምሮ መሪዎቻችን ለሀገራቸው ያላቸውን መልካም ርዕይ ለማኮሰስ የምንሮጠው ሩጫ እና የእግር ጉተታ አሳፋሪ ነው።የመሪዎች መልካም ርዕይ ትውልድ ተሻጋሪዎች እንጂ የአንድ መንግስት ዕድሜ የሚኖራቸው አይደለም። ስለሆነም ከመሪዎች መልካም ርዕይ ጎን መቆም እና ትውልድ ተሻጋሪ ስራዎች ላይ ሁሉ መተባበር ውዴታ ብቻ ሳይሆን ግዴታ መሆኑን ማወቅ አለብን።


ለመጠቅለል፣ በአጼ ቴዎድሮስ፣ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴና ኮ/ል መንግስቱ ላይ የሰራነውን የመሪዎቻችንን በጎ ሀሳብ የመጎተት ክፉ ባሕል በጠ/ሚ/ር ዐቢይ ላይ አንደግምም። ኢትዮጵያ እንደቀደሙት ዘመናት አትታለልም። ትውልዱም ካለፈው ስህተት በብዙተምሯል።ከዘመን እና ትውልድ አሻጋሪ የመሪዎች ሀሳብን በማንም የባዕዳን እና የባዕዳን ቁራሽ ተመጽዋች እግር ጎታች ሀሳብ አንቀይረውም።
=====================/////===============

Monday, November 6, 2023

የአማራ ክልል ህዝብ የወደቀበትን የመከራ መአት የሚያወራለት አንድም ''ዩቱበር'' አጥቷል። ህዝብ የገባበት ማጥ ሌላ፣ በውጭ ሃገር ሆነው የጥይት ባሩድ የማይሸታቸው የሚያወሩት ሌላ ሆኗል።ስለ የህዝቡ መከራ የሚናገር የለም።ዩቱበሮች ጦርነት ህዝብ የማይጎዳበት አበባ የመበተን ያህል አስመስለው ሲናገሩት ''አጀብ'' ያሰኛል።

ጃናሞራ መሸሃ እርዳታ ሲከፋፈል መስክረም፣2023
  •  ''ከ3 ሚልዮን በላይ ተማሪዎች እስካሁን ትምሕርት ለመጀመር አልተመዘገቡም'' አቶ መኳንንት አደም የክልሉ ምክትል ትምሕርት ኃላፊ፣
  •  ከፍተኛ ረሃብ በክልሉ በተለይ በጃናሞራ መግባቱ ተሰምቷል።የምክር ቤቱ አባል በአቶ ባያብል ሙላቴ የተራቡትን ለመደገፍ እንቅስቃሴ ተጀምሯል። 
  •  ክልሉ ከአሁኑ ጦርነት በፍጥነት መውጣት ካልቻለ በተጨማሪ የወራት ጦርነት በልማት 60 ዓመታት ወደኋላ ሊቀር ይችላል። 
  • ዝምታው ይሰበር።

============
ጉዳያችን ምጥን
============

 በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ጦርነት የክልሉን የንግድ፣ኢንዱስትሪና ማኅበራዊ ተቋማት በከፍተኛ ደረጃ እያሽመደመደ ነው።ከአንድ ወር በፊት ከአንድ ሺህ ሁለት መቶ በላይ ኢንዱስትሪዎች ስራ መስተጓጎሉ የተገለጸ ሲሆን ከትናንት በስቲያ የክልሉ ምክትል ትምሕርት ኃላፊ አቶ መኳንንት አደም እስካሁን ከ3 ሚልዮን በላይ ተማሪዎች የዘንድሮን ትምሕርት ለመማር እስካሁን እንዳልተመዘገቡ ገልጸዋል።ከእዚህ በተጨማሪ ክልሉ የወባ በሽታ አደጋም ተጋርጦበታል።የክልሉ ረሃብ በተመለከተ የተወሰኑ ዜናዎች በመንግስት መገናኛ ብዙኃን ለአንድ ሁለት ቀናት ያህል ከተሰማ በኋላ ስለረሃቡ ብዙም አይሰማም።

ከእዚህ ሁሉ በተለየ በጃናሞር ያለውን የድርቅ ጉዳት ለመደገፍ  በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጃናሞራ ተወካይ አቶ ባያብል ሙላቴ እያስተባበሩ የሚገኙት የቴሌግራም ግሩፕ ላይ በጎ አድራጊዎች የቻሉትን እያደረጉ ይገኛል። የገንዘብ ማሰባሰብያ የባንክ ሂሳብ በጥምረት ማለትም በአቶ ባያብል ሙላቴ፣ፕሮፌሰር ጌታሁን መንግስቱ እና በወ/ሮ እኝሽ ገብሬ እንዲንቀሳቀስ የተደረገ ሲሆን በቴሌግራሙ ገጽ ላይ የተለጠፈው የሂሳብ ቁጥርም ከስር እንደሚከተለው ይታያል።
================================================================
ለጠለምት፣ ጃናሞራና በየዳ ህዝብ ፈጥነን እንድረስት📣

የኢትዮጽያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 
1️⃣0️⃣0️⃣0️⃣5️⃣7️⃣9️⃣0️⃣9️⃣3️⃣5️⃣6️⃣4️⃣

በሰሜን ጎንደር ዞን (ጃናሞራ በየዳና ጠለምት) ቆላማ ቀበሌዎች በተከሰተው ድርቅና ርሃብ ችግር ውስጥ ለሚገኙ ወገኖቻችን ድጋፍ የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ ባንክ ሂሳብ ተከፈተ።

የባንክ ሂሳቡ ፈራሚዎች
1.ፕሮፌሰር ጌታሁን መንግስቱ
2.ወ/ሮ እንይሽ ገብሬና
3. አቶ ባያብል ሙላቴ ናቸው

በመሆኑም ለወገን ደራሽ ወገን ነውና በሃገር ውስጥና በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን በሞት አፋፍ የሚገኘውን ወገናችንን ለመታደግ የምንችለውን እንድናደርግ የድጋፍ ጥሪ እናቀርባለን።
=====================================

የተከበሩ አቶ ባያብል ሙላቴ የጃናሞራ ህዝብ ተወካልይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት


ይህ በየምክር ቤት አባል አቶ ባያብል እና የአካባቢው ተወላጆች የተጀመረው የተራቡትን የመርዳት ስራ እጅግ ሊበረታታ የሜገባው እና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ሊሳተፉበት የሚገባ ነው።''ጨለማን ሲረግሙ ከመዋል አንድ ሻማ ማብራት '' የሚለውን አባባል በተግባር ያሳየ አርአያነት ያለው ተግባር ነው።
  
የአማራ ክልል ያለው ግጭት በቶሎ መፍትሄ ካላገኘ ክልሉን ወደ የከፋ አደጋ ከመምራት ባለፈ የኢትዮጵያን አንድነት በከፍተኛ አደጋ ላይ የሚጥል ነው። ለእዚህ ደግሞ ዋነኛው ማሳያ የሚሆነን በአጭር ጊዜ ውስጥ የደረሰው ጥፋት ብቻ ሳይሆን ከህዝቡ ብዛት፣የመልክዐ ምድሩ አቀማመጥ የሚያዋስናቸው ክልሎች ብቻ ሳይሆን ከሀገሮች ጋርም መዋሰኑ የራሱ የሆነ ተጽዕኖ አለው።

አሁን የመንግስት ሚድያዎች ስለ የአማራ ክልል ጦርነት ዕለት ከዕለት ዜና እያሰሙ አይደለም። ስለ ክልሉ ጦርነት እየነገሩን ያሉት ዩቱበሮች ናቸ። ዩቱበሮቹ ግን ስለ የህዝቡ ሰቆቃ አያወሩም። ረሃቡን ደብቀዋል፣የወባ በሽታውን አይናገሩም፣ከሦስት ሚልዮን በላይ ተማሪዎች እንዳልተመዘገቡም አያወሩም።እነርሱ አሽትተውት ስለማያውቁት ባሩድ ከባሕር ማዶ ተቀምጠው እያወሩ፣በፊልም የሚያውቁትን ጦርነት ከአሜሪካ ሆነው በለው፣በለው! እያሉ ያሟሙቃሉ።

ክልሉ እየወረደበት ስላለው የመከራ ዶፍ የሚተነፍስ ዩቱበር የለም። ይህ ክልሉ በጸጥታ ወደ ከፍተኛ ቀውስ የመግባት አደጋ ላይ ነው።''ከትናንት ቢዘገይ ከነገ ይቀደማል '' እና ዛሬም የክልሉ ባለሃብቶች፣ሙሑራን እና የሃይማኖት አባቶች በጋራ ተሰብስበው በነፍጥ የሚመራ ክልል እንዳይሆን እና ያሉት ጥያቄዎች አግባብነት ባለው መልክ ቀርበው በምክክር እና በሰላም እንዲፈታ ጥረት ካላደረጉ ጉዳዩ በባዕዳን እጅ ገብቶ ኢትዮጵያን በከፋ መልኩ ወደ ኋላ 60 ዓመት ሊጎትተው ይችላል።የክልሉ ጉዳይ የሚመለከተው የተወሰኑ ዩቱበሮችን ሊሆን አይገባም። በመከራው ጊዜ የሚያወራለት የሌለው ህዝብ ዓይናችን እያየ አንዳችም ምሑራዊ ውይይት አድርገው ለችግሮች መፍትሄ ከማምጣት ይልቅ በቀለጠ ፕሮፓጋንዳዊ ስራ ላይ የተጠመዱ ዩቱበሮች መከራውን እንዲደብቁ እና ክልሉን ፍጹም ሲወድም አያየን በመመልከት ወደ የባሰ ጥፋት ሲመሩ ሊሰጣቸው አይገባም። ዝምታው ሊሰበር ይገባል!
===================/////==============


Friday, November 3, 2023

Ethiopia’s prime minister wants a Red Sea harbour

November 2/2023








            



Nerves are jangling once again in the Horn of Africa, just a year after the end of a brutal civil war in Ethiopia that led to the deaths of perhaps 385,000-600,000 people. Now foreign diplomats and analysts fear that in his bid to get a port on the Red Sea, Abiy Ahmed, Ethiopia’s prime minister, risks sparking another conflict, this time next to one of the world’s busiest shipping routes.

In a jingoistic documentary aired on state television on October 13th, Abiy argued that landlocked Ethiopia must acquire a port on the Red Sea to break its roughly 120m people out of a “geographic prison”. Turning to history, he quoted a 19th-century Ethiopian warrior who had proclaimed that the Red Sea was the country’s “natural boundary”.

Ethiopia, Abiy noted, had indeed been a sea power with a navy and two ports, Massawa and Assab. It lost these along with the rest of its coastline in 1993, when Eritrea seceded to form a new country. Now, Abiy suggested, the moment was nigh to right a historic wrong. “It’s not a matter of luxury,” he insisted, “but an existential one.” Foreign diplomats say this reflects what Abiy has been declaring in private for months.

Ethiopia’s neighbours are rattled, particularly because Abiy had not raised the issue with them before making his threats. “The whole country thinks the man is mad,” says an adviser to Somalia’s president. A fight over ports would further destabilise a region already in turmoil. Sudan, Ethiopia’s neighbour to the west, has been plunged into what the un calls “one of the worst humanitarian crises in recent history”. Fighting between two warlords there has forced almost 7m people from their homes. And Ethiopia itself faces simmering rebellions in Oromia, its largest and most populous region, and Amhara.

Abiy says that Ethiopia’s demands can be met through peaceful negotiations with its neighbours. Better to discuss the matter now, he argues, than to risk an armed conflict in the future. But Abiy has reportedly said in private that he is ready to use force if talks fail. “If it is not achieved by other means, war is the way,” says an Ethiopian official. A few days after the broadcast Abiy flexed his muscles with a military parade in the capital, Addis Ababa, in which the army displayed its new weapons including a Russian-made electronic-warfare system. Troop movements have been detected along both sides of Ethiopia’s border with Eritrea in recent weeks. A well-connected source in Addis Ababa says that the armed forces are exercising in preparation for another conflict. On October 22nd the head of the air force warned his troops to ready themselves for war.

Ethiopia’s Red Sea conundrum dates back to at least the start of its bloody border war with Eritrea in 1998. Though a ceasefire was reached in 2000, the two countries remained at loggerheads. Ethiopia could not ship goods through Assab and Massawa. Now 90-95% of its external trade flows through Djibouti, to which it pays some $1.5bn a year in port fees.

In 2018, soon after Abiy came to power, he ended the nearly two decades-long stand-off with Eritrea by signing a peace deal with its dictator, Issaias Afwerki. Though the contents of the deal were never made public, it was generally understood that Ethiopia would regain tax-free access to Eritrea’s ports in exchange for returning disputed territories it had occupied since the end of the war. The following year Abiy was awarded the Nobel peace prize.

But plans for Ethiopia to use Eritrea’s ports never materialised. Instead, two years later, a power struggle between Abiy and Tigray’s ruling party, the Tigrayan People’s Liberation Front (tplf), sparked civil war. Eritrean troops joined in on Abiy’s side to fight against the tplf, which Issaias has long hated.

The two leaders have fallen out since then, possibly because Ethiopia signed a peace deal with the tplf in late 2022. Each sees the other as a threat to their influence over the region. “Abiy and Issaias cannot co-exist in this region,” says an Ethiopian opposition leader. “War is inevitable.”

Increased tensions with Eritrea could exacerbate Ethiopia’s existing internal conflicts. Under the peace deal Abiy struck with the tplf last year, it was supposed to disarm and demobilise its fighters while Eritrea was meant to withdraw its forces from Tigray. But Eritrea remains in control of at least 52 districts of northern Tigray, according to the region’s interim administrators. In recent weeks, Eritrean troops have expanded their presence along the border areas, reports a visiting foreign researcher. Tigrayan forces have handed over most of their heavy weaponry to the Ethiopian army. But they still have some 200,000 men and women under arms.

Another party in the multi-sided civil war in Tigray was Ethiopia’s Amhara regional government, which sent its own militias and troops to fight alongside Abiy’s federal forces. These troops were also supposed to have withdrawn from disputed territories inside Tigray that they occupied at the start of the war. But they have yet to do so. Instead, they have turned on Abiy’s government, accusing it of betraying Amhara’s interests. In August they fought federal forces for control of several towns.

Shifting alliances

With so much bad blood and so many armed groups jostling for influence within Ethiopia, Abiy’s threats are extremely reckless when it comes to his own country’s security. They are damaging to Ethiopia’s relations in the wider region. Djibouti, which now provides Ethiopia’s main access to the sea, has furiously responded that its “territorial integrity cannot be disputed”. Somalia, similarly, insisted its territorial integrity and sovereignty are “sacrosanct and not open for discussion”.

Some Ethiopian officials play down Abiy’s fighting talk. “It’s about diverting attention from domestic issues,” says an ally of the prime minister. Although the Eritrean port of Assab, which was once part of the former Ethiopian Empire, has particular symbolic value for Ethiopians, Abiy has also floated the possibility of negotiating for a strip of land around the ancient port of Zeila in the breakaway Somali region of Somaliland. In exchange, Ethiopia might offer to recognise Somaliland statehood. “Abiy has no interest in being part of another conflict for the moment,” says an analyst in Addis Ababa.

But the Ethiopian prime minister is notoriously unpredictable. “Nobody except himself can be certain if he is serious or not,” says a tplf official. Little more than three years ago Abiy insisted he would not go to war in Tigray. Many diplomats and regional leaders took him at his word, which he soon broke. They would be wise not to make the same mistake again.

==================////===========


ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...