ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, December 31, 2019

የአዲስ አበባ ከተማ - የከተማዋን ነዋሪ ስነ-ልቦና ፣ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ማዕከልነትን ታሳቢ ያደረገ የፖሊስ ኃይል ያስፈልጋታል።


ጉዳያችን  GUDAYACHN  
ታህሳስ 21/2012 ዓም (ዴሰምበር 31/2019 ዓም)

የአራዳ ዘበኛ  

አዲስ አበባ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመርያውን የፖሊስ ሥራ ያስተዋወቀች ከተማ ነች።ዘመኑ 1901 ዓም ነበር አዲስ አበባ የመጀመርያውን የፖሊስ ሰራዊት ጥንስስ የአራዳ ዘበኛ በሚል ስም ያደራጀችው።የኢትዮጵያ የፖሊስ ሰራዊት ታሪክ ጥንስስም እዚህ ላይ ይጀምራል።በወቅቱ ንጉሰ ነገስት ምንሊክ የመጀመርያውን የኢትዮጵያ ፖሊስ የአራዳ ዘበኛ በሚል ለሕዝቡ ሲያስተዋውቁ ያወጡት አዋጅ እንዲህ የሚል እንደነበር ጳውሎስ ኞኞ 'አጤ ምንሊክ' በተሰኘው መፅሐፉ ላይ ጠቅሶታል።


ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ
ምኒልክ ስዩመ እግዚአብሄር
ንጉሰ ነገስት ዘኢትዮጵያ

አዋጅ!
ለሊት ሌባ እንዳይበዛ፣ ቀን አነባብሮ እንዳያነሳ፣ በተረፈ ክፉን ነገር ሁሉ የሚጠብቅ ዘበኛ ብናቆም ሁሉም ዘበኛ ነኝ እያለ እንዳይዝ ቁጥር እና ባንዲራ ያለበት በራስ ላይ የሚደረግ ምልክት አበጅቻለሁ። ያንን ምልክት ያደረገ ዘበኛ ቢይዝህ መያዝ ነው እንጂ ይህን ጥሰህ የተጣላህ ሰው ትቀጣለህ።
ሚያዝያ ፳፱ ቀን ፲፱፻፩ አመተ ምህረት አዲስ አበባ ከተማ። ይላል።

የአራዳ ዘበኛ ኮፍያው ላይ 'የምስጢር ዘበኛ' የሚል ፅሁፍም ነበረው።

የአራዳ ዘበኛ እስከ 1928 ዓም ጣልያን ኢትዮጵያን እስኪወር ድረስ ዘለቀ።ጣልያን ከኢትዮጵያ ተባሮ ከወጣ ከ1934 ዓም ጀምሮ የኢትዮጵያ ፖሊስ አዲስ ምዕራፍ ተከፈተለት።ሰራዊቱ በአዋጅ ቁጥር 6/1934 በወቅቱ ስሙ አባዲና ፣የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሌጅ መመስረት ጋር ተከትሎ የፖሊስ ሥራ ሳይንሳዊ በሆነ መልክ የሚሰሩ መኮንኖች ሰራዊቱን መቀላቀል ጀመሩ።

የፖሊስ ሰራዊት የህዝብን ፀጥታ የማስከበር ሥራ እስከ 1967 ዓም ድረስ የሚያስከብርበት የተለያየ መንገድ ይጠቀም ነበር።ለምሳሌ የሚሊሻ ታጣቂዎች ከፖሊስ ጋር እንዲሰሩ ማድረግ፣አውጣጭኝ በሚል ሕብረተሰቡን ሰብስቦ በአንድ አካባቢ ሰብስቦ ወንጀል እንዲጋለጥ ከማድረግ ጀምሮ እስከ ፖሊስ እና ርምጃው የሚል ጋዜጣ እና የራድዮ ፕሮግራም እያደገ መጣ።እስከ 1967 ዓም ድረስ የፖሊስ ሰራዊት ሥራ በኅብረተሰቡ ውስጥ የተከበረ ሙያ ነበር። ፖሊስ የሆነ ሰውም የማይዋሽ፣በሕዝቡም ውስጥ የተሻለ ተሰሚነት ነበረው።ከ1967 ዓም ለውጥ በኃላ በከፍተኛ የፖሊስ ሙያ የሰለጠኑ ባለሙያዎች ወደ ማዕከላዊ ምርመራ ተሳቡ የቀሩት ወደ ደርግ የምድር ጦር እና የፖሊስ ሰራዊት መኮንኖች ውስጥ ሲዋቀር የፖሊስ ኃይሉም የሰለጠነ የሰው ኃይል ተዳከመ።ደርግ የህዝቡን መብት ለማፈን የፖሊስ ኃይሉ በቂ ስላልነበር የፖሊስን ሥራ የአብዮት ጠባቂ እና የደህንነት ክፍሉ አፋኝ ቡድን ወሰደው።በመቀጠል ፖሊስ ለትንንሽ የሌብነት ስራዎች ወይንም የፖለቲካ ጉዳይ የለባቸውም ለሚባሉ ወንጀሎች ብቻ የሚፈለግ ሆነ።

በ1983 ዓም ኢህአዴግ ስልጣን ሲይዝ በአራዳ ዘበኛ ጥንስስ የተጀመረው የፖሊስ ሥራ በየክልሉ እንዲከፋፈል ተፈረደበት።የፖሊስ ኃይሉ በክልሎች ደረጃ ሲዋቀር የፖሊስ ማሰልጠኛዎችም በየክልሉ የመክፈት ሥራ ቢይታይም በጥራት እና በደረጃ ግን ዘመኑን የተከተለ ሳይሆን በቂ ስልጠና የሌለው ፖሊስ ሰራዊቱን መቀላቀል ጀመረ።

አዲስ አበባ የራሷ ፖሊስ ኃይል ለምን ተነፈገች?

በዘመነ ደርግ አዲስ አበባ በአብዮት ጥበቃ ስር ብትሆንም የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የሸዋ ፖሊስ ዋና መስርያ ቤቱን ከካሳንቺስ ወረድ ብሎ የሚገኘውን ህንፃ ተከራይቶ ይሰራ ነበር።በዘመነ ኢህአዴግ ግን የአዲስ አበባ ፖሊስ ደካማ ሆኖ እንዲደራጅ ከመደረጉም በላይ የፈድራል ፖሊስ ከፍ ተደርጎ እንዲደራጅ ተደረገ።በእዚህ ሳብያ ዘመናዊነት የሚታይባት አዲስ አበባ የከተሜ ማዕረግ ያለው ፖሊስ እንዳማራት ዓመታት ነጎዱ።የኢትዮጵያ ፖሊስ በአባዲና ኮሌጅ በጀመረው አሰለጣጠን መንገድ ዛሬ በ21ኛው ክ/ዘመን የኮምፕዩተር እና ኢንተርኔት ዘመን በሚመጥን መልኩ በብዛት እና በጥራት ማሰልጠን  ይጠበቃል።

ከ2010 ዓም  የለውጥ ሂደት በኃላ የአዲስ አበባ የራሷ ፖሊስ የማግኘት መብት አሁንም አልተከበረም።ሌላው ቀርቶ ከእዚህ ለውጥ በፊትም ሆነ ከለውጡ በኃላ በሕገ መንግስቱ የተቀመጠውን ክልሎች የራሳቸው የፖሊስ ኃይል እንደሚኖራቸው  የተጠቀሰውን መብትም ሳይቀር አዲስ አበባ ላይ ሲደርስ ታግቷል።ይህ ደግሞ አዲስ አበባ የፖለቲካ እና የምጣኔ ሃብቱ ማዕከል እንደመሆኗ መንግሥታት አዲስ አበባን በቀጥታ በሚመሩት የፀጥታ ኃይል ስር የማድረግ ፅኑ ፍላጎት ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ - የከተማዋን ነዋሪ ስነ-ልቦና ፣ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ማዕከልነትን ታሳቢ ያደረገ የፖሊስ ኃይል ያስፈልጋታል።

የፖሊስ ኃይል አባል አካባቢውን በደንብ የሚያውቅ መሆኑ ብዙ ጥቅም አለው።በመጀመርያ ደረጃ የህዝቡን ስነ ልቦና፣ማኅበራዊ ሕግ  እና አስተሳሰብ የሚረዳ የፖሊስ ኃይል የሚያደርገውን የሚያውቅ ብቻ ሳይሆን የችግር አፈታት መንገዱም አካባቢውን ከማያውቅ በተሻለ መንገድ ሕዝብ የማገልገል አቅም ይኖረዋል።

ከእዚህ አንፃር የአዲስ አበባን ሁኔታ ስንመለከት ደግሞ አዲስ አበባ ከሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞች የተለየ ባህሪ እንዳላት እንመለከታለን።አዲስ አበባ በመጀመርያ ደረጃ ሕብረ ብሔራዊ ሕዝብ የሚኖርባት ከተማ ነች።የብሔር ፖለቲካ አንግቦ የሚመጣ ኃይል ለአዲስ አበባ የተናቀ ሥራ ነው።ፖሊስን አዲስ አበባ የምታውቀው ከአራዳ ዘበኛ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ሌሎች በጎሳ ዓይን ሲመለከቷት ለአዲስ አበቤ ግን ፖሊስ ፖሊስ ነው።

በሌላ በኩል አዲስ አበባ ከህብረ ብሔር ከተማነቷ በላይ በዓለም ላይ ከኒውዮርክ እና ጀኔቫ ቀጥሎ  ከፍተኛ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ የሚገኝባት  ከተማ ነች።የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ፣የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአንድ መቶ አምስት በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻው መነሻው አዲስ አበባ ነች።በቅርቡ ደግሞ ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን ካለቪዛ የመግባት ፍቃድ  መስጠቷን ተከትሎ ያለውን ሁኔታ ሁሉ ስንቃኝ አዲስ አበባ በምን ያህል ደረጃ ከአዲስ አበባ ጋር የተናበበ የፖሊስ ኃይል  እንደሚያስፈልግ መረዳት ይቻላል።ሌላው ቀርቶ አሁን በአዲስ አበባ የሚያዙት ሌቦች ከአዲስ አበባ የመጡ ብቻ ሳይሆን ከኬንያ እና ታንዛንያ ጭምር የመጡ ወንጀለኞች እየታዩ ነው።ይህ ማለት በየትኛውም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጣብያ ቢያንስ በእንግሊዝኛ በበቂ ሁኔታ ቃል ሊቀበል የሚችል የፖሊስ መኮንን ያስፈልጋል ማለት ነው።

ባጠቃላይ የአዲስ አበባ የራሷ ፖሊስ የመኖሩ ጉዳይ እጅግ አንገብጋቢ ጉዳይ ነው።የፒያሳ ልጆችን ፀባይ፣የቄራ ልጆችን ብሽሽቅ፣ የጉለሌ ልጆችን ዱላ፣የቦሌ ልጆችን አስተዳደግ፣የቀጨኔ ልጆችን አስተሳሰብ የሚረዳ የፖሊስ ኃይል ያስፈልጋታል። ከእዚህ ውጪ በክልል ሰልጥኖ ወደ አዲስ አበባ የሚገባ የፖሊስ ኃይል የአዲስ አበባን ስነልቦና የማይረዳ ብቻ ሳይሆን የአዲስ አበባ ልጅ በሙሉ የክልል ሰው የሚንቁ መስሎ የሚታየው እና በንግግር እና ሃሳብ ሊግባባ የማይችል ፖሊስ በአዲስ አበባ ላይ ማሰማራት በመንግስት እና በአዲስ አበባ ሕዝብ መሃል ያለውን ግንኙነት የሚያበላሽ ብቻ ሳይሆን አዲስ አበባ የፀጥታ ሁኔታዋ እንዳይበላሽ ያሰጋል። አሁንም ለመድገም የአዲስ አበባ ከተማ - የከተማዋን ነዋሪ ስነ-ልቦና ፣ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ማዕከልነትን ታሳቢ ያደረገ የፖሊስ ኃይል ያስፈልጋታል።

አዲስ አበባ Addis Ababa City - New Flower of Ethiopia (ቪድዮ)



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

ኢትዮጵያ ለሊብያ ሰላም እየሰራች ነው።የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አማካሪ ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ክብረት ከሊብያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያይተዋል።Ethiopia is working for the effort of peace in Libya

Advisor of Ethiopian PM Abiy Ahmed, Daniel Kibret and Libya FM Mohamed Sayala 

ጉዳያችን ዜና  GUDAYACHN News 
ታህሳስ 21/2012 ዓም (ዴሰምበር 31/2019 ዓም)
(Please read in English under Amharic version here below)

ኢትዮጵያ ለሊብያ የሰላም ስኬት እየሰራች መሆኗን ሊብያ ኦብሰርቨር የተሰኘው የድረ ገፅ ጋዜጣ በትናንትናው ዕለት ከሊብያ ዘግቧል።እንደዘገባው ከሆነ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ያለፈው እሁድ ሐምሌ 19/2012 ዓም የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካንን በመምራት  በሊብያ ከውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከሞሀመድ ሳያላ  ጋር መወያየታቸውን እና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ህብረት እና ከተባበሩት መንግሥታት ሉዑክ ጋር በመሆን ጥረቷን እንደምትቀጥል መግለጣቸውን ዘገባው ገልጧል።

በሌላ በኩል የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ሞሐመድ ሳያላ በኢትዮጵያ እና በሱማልያ መካከል ያለው ግንኙነት በመልካም ሁኔታ መቀጠል እንዳለበት ገልጠው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ ለሊብያ ቀውስ ሰላም ለማፈላለግ ለሚያደርጉት ጥረት ሁሉ ሊብያ በደስታ የምትቀበለው መሆኑን ገልጠዋል።ሊብያ ኦብሰርቨር የተሰኘው የድረ ገፅ ጋዜጣ ሊብያ ውስጥ ካሉት የድረ ገፅ ጋዜጦች ውስጥ በቀዳሚነት የሚገኝ የዜና ገፅ ነው።

==================================

Ethiopia backs efforts of peace in Libya

Adviser of the Ethiopian Prime Minister, "Dikon Daniel", confirmed on Sunday, during his visit with a government delegation to Libya, his country's desire to support efforts in bringing stability to Libya through a political solution, in coordination with the African Union and the UN mission.
Daniel discussed with Libyan Foreign Minister, Mohamed Sayala avenues of enhancing cooperation between the two countries in many fields.
For his part, Sayala commended the relationship between the two countries and welcomed the efforts of the Ethiopian Prime Minister "Abiy Ahmed" to contribute to solving the Libyan crisis.
Source - Libya Observer (https://www.libyaobserver.ly/inbrief/ethiopia-backs-efforts-peace-libya

 www.gudayachn.com

Thursday, December 26, 2019

ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል የታክሲ ላይ ፖስተር ወስደው የሙስሊሙን ማኅበረሰብ ለመቀስቀስ የተጠቀሙበት መንገድ የኃይማኖት ሰው ናቸው ወይንስ የፖለቲካ አክቲቪስት? የሚል ጥያቄ ጭሯል።


ጉዳያችን / Gudayachn
ታሕሳስ 16/2012ዓም (ደሴምበር  26/2019 ዓም)

እንደአውሮፓውያን አቆጣጠር ታህሳስ 21/2019 ዓም ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል በፌስ ቡክ ገፃቸው ላይ ይዘው የወጡት የአንድ ሚኒ ባስ ላይ የተለጠፈ ፖስተር ጠቅሰው ከሞጣ መስጂድ የቃጠሎ አደጋ ጋር ለማገናኘት የሄዱበት ርቀት አስደንጋጭ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።ኡስታዝ አሕመድ ጀበል በሚኒ ባስ የውጪ ክፍል ላይ ተለጥፎ ያነሱት  ፎቶ እና እንደ ትልቅ ወንጀል ያብጠለጠሉበት  ፖስተር ''የአባቶቻችንን ታሪክ እንደግማለን '' የሚለውን  ፅሁፍ  ነው።

በቅድምያ በየትኛውም ቦታ የሚደረግ የሃይማኖት ቦታ የማቃጠል፣የመግደል እና የመንቀፍ ተግባር የሚወገዝ ብቻ ሳይሆን፣ይህንን የፈፀሙም ሆነ እንዲፈፀም የረዱ ለፍርድ መቅረብ አለባቸው።በሞጣ መስጂድም ሆነ በባሌ፣ሐረር እና ሲዳማ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ቃጠሎ ያደረሱ በሙሉ ለፍርድ መቅረብ እና ተመጣጣኝ ቅጣት ማግኘት አለባቸው።ይህንን ኢትዮጵያውያን ሙስሊምም ሆነ ክርስቲያኑ ከአደባባይ ንግግር እስከ ማኅበራዊ ሚድያ ደጋግሞ የገለጠው እና ሁላችንም የምንስማማበት ጉዳይ ነው።

ለእዚህ ፅሁፍ መነሻ ያደረገኝ አደገኛ አካሄድ ግን የሐይማኖት ቀዳሚ ሰዎች ወደ አክትቪዝም መግባት አደገኛ አካሄድ ነው። ኡስታዝ አህመዲን ጀበል በፌስ ቡክ ገፃቸው ላይ በአንድ የሚኒባስ ታክሲ ውጪያዊ ክፍል ላይ የተመለከቱትን ''የአባቶቻችንን ታሪክ እንደግማለን'' የሚል ሌላ ቦታ የተፃፈ ጥቅስ ከሞጣ የመስጊድ ቃጠሎ ጋር አገናኝተው ለመቀስቀሻነት  ሲጠቀሙ  እንዲህ የሚል ዓረፍተ ነገር በፌስቡክ ገፃቸው ላይ ተጠቅመዋል።እንዲህ ይነበባል -''"የአባቶቻችንን ታሪክ እንደግማለን" ሲሉ የቱን ታሪክ ሊደግሙ ነው ብለህ መቁጠር ብትጀምር ባለፈው አንድ ዓመት ዉስጥ ብቻ  ብዙ መቁጠር ትችላለህ። ለምሳሌ ትናንት ምሽት በሞጣ ከተማ መስጂዶችን እና የሙስሊሞችን ንብረቶች አቃጥለው' ----' በማለት  ያብራራሉ።

የአባቶቻችን ታሪክ መልካም የሆነውን የማንደግመበት ምክያት ምንድን ነው? የኢትዮጵያን ነፃነት ለመጠበቅ ያደረጉት ተጋድሎ፣ኢትዮጵያን ከዓለም ቀዳሚ  ለማድረግ ከስነ ፅሁፍ እስከ ስነ ህንፃ የሰሩትን መልካም ሥራ፣ግጭቶችን በሰላም ለመፍታት ታቦትና ድንጋይ ተሸክመው ይቅር መባባላቸው  እና ሌሎቹን የማንደግመብት ምክንያት ምንድነው? ኡስታዝ አህመዲን በኢትዮጵያ መስራች አባቶች ላይም ሆነ ላለፉት ሁለት መቶ ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ጉዳዮች ላይ ወሳኝ ሚና የተጫወቱትን አባቶች ሁሉ መስጂድ ያቃጠሉ ይመስል በፈስቡክ ያብጠለጠሉበት  አግባብነት የሌለው አገላለጥ አደገኛ የታሪክ ትርክት ውስጥ እየገቡ እንደሆነ አመላካች ነው።አባቶቻችን የመሐመድን ቤተሰቦች  ያስጠጉ፣ አስጠግተውም በእምነታቸው ላይ ተፅዕኖ ሳይፈጥሩ በሰላም ወደ መካ የላኩ የተከበሩ አባቶች የነበሩባት ምድር ነች ኢትዮጵያ። አባቶቻችን ከሸህ ሁሴን ጀብሪል ጋር ተመራርቀው የኖሩ፣ከአባጅፋር ጋር ተመካክረው የኖሩ አባቶች ናቸው ያሉን።ይህንን መልካም ተግባር መድገም ጥፋቱ ምኑ ላይ ነው?

ኡስታዝ አሕመዲን የዛሬ ዓመት ገደማ ለ'ኢትዮ ቱብ' በሰጡት ቃለ መጠይቅ ላይ ኢትዮጵያን እስር ቤት ከመግባታቸው  በፊት በደንብ እንደማያውቁ እና እስር ቤት ከገቡ በኃላ እንዳወቁ አብራርተው ነበር።በእርግጥ እርሳቸው መጅሊሱ አካባቢ ባሉ አለመግባባቶች ውስጥ ለረጅም ጊዜ የሄዱበት ጉዳይ እንዳለ ይሰማል።ይህ በራሱ ጉዳዩን በሚያውቁ ቢብራራ ይሻላል።ኡስታዝ አህመዲን ግን ከእስር ከተፈቱ በኃላስ የኢትዮጵያን ሕዝብ ያውቁታል ወይ? ካወቁትስ ቀረብ ብለው ተረድተውታል ወይ? ሙስሊም ከክርስቲያኑን ለማጋጨት ይህ ትውልድ ያልኖረውን የአባቶቹን ታሪክ እየጠቀሱ ያውም በ16ኛው ክ/ዘመን አንድ ሙስሊም ተገድሎ ነበር በሚል አገላለጥ ከላይ የጠቀስኩትን የታክሲ ፖስተር ጋር አያይዘው ግራ እና ቀኙን ያልለየ  ምስኪን ኢትዮጵያዊ ሙስሊም እና ክርስቲያን ላይ ለምን የሞት አዋጅ የሚጠራ የቅስቀሳ ፅሁፍ ይፅፉበታል? ለምን? ይህ ከአንድ የሃይማኖት  አስተምሮ እንዳለው ከሚናገር ሰው የሚጠበቅ አይደለም።አሁንም ርጋታ፣ማስተዋል እና ወደ በጎ ህሊና መመለስ ጠቃሚ ነው።

በያዝነው ሳምንት ውስጥ ከአንድ ሙስሊም የተላለፈ ታላቅ ምክር፤ ለኢትዮጵያ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች (ቪድዮ)

ምንጭ = አደባባይ ሚድያ 




ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Thursday, December 19, 2019

የምስራች! ኢትዮጵያ የመጀመርያዋን ሳተላይት ወደ ጠፈር አምጥቃለች። Ethiopia’s first remote sensing satellite, ETRSS-1, launched to space this morning at 03:21 GMT December 20/2019.(ቪድዮ ይመልከቱ)


ጉዳያችን /Gudayachn

ታህሳስ 10/2012 ዓም (ዴሰምበር 20/2019 ዓም)

የምስራች! ኢትዮጵያ የመጀመርያዋን ሳተላይት ወደ ጠፈር  አምጥቃለች። 
Ethiopia’s first remote sensing satellite, ETRSS-1, launched to space this morning at 03:21 GMT December 20/2019.

According to African News this morning the 70 kg multi-spectral civil Earth observation will provide data for Ethiopia’s authorities and research institutions to monitor the environment and study weather patterns for better agricultural planning, early warning for drought, mining activities and forestry management.

ሳተላይቷ -
- በምድር ላይ ያለ 13 ሜትር ርዝመት ያለውን ነገር ሳይቀር ከጠፈር ላይ ለይታ መረጃ ትልካለች
- የምልከታዋ ፍጥነት መሬት በራሷ ዛብያ ላይ ከምትዞርበት በፈጠነ መልክ መረጃ ትልካለች 
- በአራት ቀናት መላዋ ኢትዮጵያ ያለውን መረጃ መሰብሰብ ትችላለች።
- በሃምሳ አምስት ቀናት መላው ዓለም ያለውን መረጃ የመሰብሰብ አቅም አላት፣
- ኪሎዋ 70 ኪሎ ነው።
- ከምድር 700 ኪሜትር ከፍታ ላይ ትገኛለች።
- በማዕድን፣የአየር ንብረት፣በደን ሽፋን፣ ብዙ አልተወራም እንጂ ለፀጥታ ጉዳይ ሁሉ ጥቅሟ ብዙ ነው።
- የመቆጣጠር ሥራው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን በእንጦጦ ተራራ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ህዋ ምርምር ጣብያ ይከናወናል።
- በቀጣይ አስር ዓመት ኢትዮጵያ እስከ አስር የሚደርሱ ሳተላይት ወደ ጠፈር ለመላክ እቅድ እንዳላት አንድ ከፍተኛ የኢኖቨሽን እና ሳይንስ ባለስልጣን አስታውቀዋል።

ቪድዮ ይመልከቱ 


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Tuesday, December 17, 2019

ምሁራዊ ጀሃድ በኢትዮጵያዊነት፣በታሪክ ምሁራን፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እና በአገልጋዮቿ ላይ ዘመቻ ከፍቷል።ሁሉም ሊመክተው ይገባል።


Cartoon picture source = coast2coastmixtapes.com

ጉዳያችን / Gudayachn
ታኅሳስ 8/2012 ዓም (ዴሴምበር 18/2019 ዓም) 

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር  ቅዳሜ፣ጥቅምት 13/2001 ዓም የወጣው የ''ኒውዮርክ ታይምስ'' ጋዜጣ ''The deep Intellectual Roots of Islamic Terror'' በሚል ርዕስ ስር ባሰፈረው ፅሁፍ ላይ እንዲህ የሚል ፅሁፍ ሰፍሮ ይገኛል።
     ፅንፈኛ የእስልምና ጀሃድ አባላት በ1981 ዓም እኤአ  የግብፁን መሪ  አንዋር ሳዳት ከገደለ በኃላ ''The Neglected duty'' (ችላ የተባለው ተግባር) በሚል ርዕስ ስር ባለ ሃምሳ አራት ገፅ  ሰነድ አሰራጭቶ ነበር።የሰነዱን ይዘት ይሄው የኒው ዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ሲያብራራ ቡድኑ ለመግደሉ ''ትክክለኛነት'' ለማሳመን የተጠቀመበት ሰነድ ሲሆን እንደ ሰነዱ አባባል ''ትክክለኛ እስልምና'' የማይቀበሉ መንግሥታት ላይ ግድያ እና በሰዎች ላይ የሚደርስ ጭፍጨፋን ያበረታታል።የዓለማችን ቀንደኛ ሽብርተኛ ቢንላደን የእዚሁ ፅንፈኛ ቡድን አባል የሆነው ከዓመታት በፊት እንደነበር ጋዜጣው ያትታል።

አሁን ባለንበት ዘመን ጅሃድ በቀጥታ ንፁሃንን መግደል ብቻ አይደለም።ከመግደል የሚቀድም ''ምሁራዊ ጀሃድ'' ነው።

ምሁራዊ ጀሃድ ምንድነው?

በ1985 ዓም እኤአ ባል ስቴት ዩንቨርስቲ (Ball State University) ሊንዳ ኮሎኮትሮኒስ (Linda K.Kolocotronis)  ''An intellectual historical study of Islamic Jihad during the life of Muhammad and in the twentieth century" በሚል ርዕስ በፃፉት የየዶክትሬት ማሟያ ፅሁፋቸው ''አብስትራክት'' ላይ ጅሃድ በጦርነት ብቻ ሳይሆን ''ዲፕሎማሲያዊ ጀሃድ'' የዘመናዊው ዓለም መተግበርያ እንደሆነ ካተተ በኃላ ጀሃድ በፊት ለፊት ሰው ከመግደል ባለፈ ሌሎች ስልቶች እንዳሉት ያትታል።

ምሁራዊ ጀሃድ የፊት ለፊት ንፁሃንን ከመግደል በፊት የቀደመ ፕሮፓጋንዳ ነው።በተለይ በዘመናዊው የመገናኛ መንገድ ምሁራዊ ጀሃድ በረቀቀ መንገድ አገራት ላይ መረቡን እየዘረጋ የስነ ልቦና ጦርነት ያካሂዳል።ምሁራዊ ጀሃድ የሚከወነው በከፍተኛ ደረጃ በተማሩ እና የትምህርት ችሎታቸውን ግን ለተንኮል እና እውነተኛውን የአገራት ታሪክ በማጣመም፣ቀዳሚ የታሪክ እና የሃይማኖት ምሁራንን ስም ማጥፋት፣ ለዓላማቸው ማስፈፀምያነት የማይስማማቸውን መንግስት እና የመንግስት መሪ፣ፖለቲከኛ እና  ታዋቂ ጋዜጠኞች ላይ ጭምር በምሁር ቃላት የተከሸኑ የጥፋት ፕሮፓጋንዳ ይከፍታሉ። የምሁራዊ ጀሃድ አራማጆች የአፈፃፀም ስልቱን እና የሰው ኃይል ምልመላቸውን የሚያካሂዱት በረቀቀ መንገድ ከመሆኑም በላይ በገንዘብ ኃይል ከጀርባ ይደገፋሉ።

ምሁራዊ ጀሃድ በኢትዮጵያ ስራውን ከጀመረ ቆየት ያለ ጊዜ አለው።ይህ በአካል ንፁሃን ክርስቲያኖችን በመጨፍጨፍ እና አብያተ ክርስቲያናትን ለሚያቃጥለው የጥፋት ኃይል የተኩስ ሽፋን በመስጠት ለእኩይ ድርጊቱ የሐሰት ፍትሃዊ ፅሁፎች በማጉረፍ ለድርጊቱ ሌላ ምክንያት በመስጠት ሟቾች መሞት እንደነበረባቸው ለመተረክ የሚደፍር አይን አውጣ ቡድን ነው። የምሁራዊ ጀሃድ አባላት እንደማንኛውም ሰው ህዝቡ ውስጥ ገብተው የሚኖሩ አንዳንዶቹ በስልጣን እርከን ውስጥ ተሰግስገው የመንግስትን መዋቅር በማዳከም እና ሕዝብ በመንግስት እንዲማረር ሌት ተቀን የሚደክሙ ናቸው።በሌላ በኩል ምሁራዊ ጀሃድ  አባላት በዩንቨርስቲ ውስጥ ከታሪክ ምሁርነት እስከ ፅንፈኛ የጎሳ ሚድያዎች ውስጥ ተሰግስገው የሚሰሩ ናቸው። የእዚህ ቡድን አባላት ከሚሰሯቸው የጥፋት ስራዎች ውስጥ የሚከተሉት ተጠቃሽ ናቸው። እነርሱም -

  • የኢትዮጵያን ታሪክ እያጥላሉ በማኅበራዊ ሚድያ መልቀቅ፣
  • ኢትዮጵያ የምትባል አገር የለችም፣ኢትዮጵያ ጥንት የሚባለው ምስራቅ አፍሪካ በሙሉ ነበር የሚል ትርክት በመተረክ የታሪክ አሻራ የሌላት አገር አድርጎ ማቅረብ፣
  • በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የማጥላላት ዘመቻ በመክፈት እና ከአንድ ብሔር ጋር እያያዘ ለመነጠል መሞከር፣ቤተ ክርስቲያን ኢትዮጵያን ወደ ኃላ ያስቀረች አስመስሎ የሚያቀርብ የውሸት ጥናት መሰል ፅሁፍ ማዥጎድጎድ፣
  • ባለፈው ማንነቱ የማይኮራ ትውልድ ለመፍጠር የውሸት ትርክት ማስፋፋት፣
  • የኢትዮጵያ ጥቅም በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሁሉ በተቃዋሚ ስም በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ማጥላላት እና ማጠልሸት፣
  • በኢትዮጵያዊነታቸው የሚያምኑ እና ይህንኑ በሥራ ያስመሰከሩ ጋዜጠኞች፣ምሁራን እና የሃይማኖት ምሁራን ላይ በቀጥታ የስም ማጥፋት ዘመቻ መክፈት። እዚህ ላይ ሰሞኑን በሙሐዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል እና ''አክራሪ እስልምና በኢትዮጵያ'' የተሰኘው መፅሐፍ አዘጋጅ በመልአከ ኤዶም ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ ላይ የተከፈተው የማኅበራዊ ሚድያ ዘመቻ መጥቀስ ይቻላል፣
  • ከፅንፈኛ የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በመገናኘት በአገር ውስጥ ላላቸው ሕዋስ እና  የፅንፍ መገናኛ ብዙሃን ድጋፍ በማግኘት በአገር ውስጥ በጎሳዎች መሃል ግጭት እንዲፈጠር ማሴር እና 
  • ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ቀውስ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲፈጠር ካደረጉ በኃላ የፖለቲካ ስልጣን ለመያዝ መስራት የሚሉ ተጠቃሾች ናቸው።
የምሁራዊ ጀሃድ ዋና አንቀሳቃሾች በአሁኑ ወቅት በአክትቪስትነት ተከስቷል።ለስውር ስራው ሽፋን ደግሞ አንድ ጊዜ በጎሳ ፅንፈኛ ኃይሎች ስም በመደራጀት፣ሌላ ጊዜ ደግሞ በቀጥታ የኢትዮጵያን አንድነት በመፃረር በአገሪቱ ውስጥ የፅንፍ እስልምና እንቅስቃሴ ሲያበረታታ ይታያል። በኢትዮጵያ ውስጥ የምሁራዊ ጀሃድ ሥራ ላይ የተሰማራው ቡድን ረዘም ላለ ጊዜ እራሱን ለመደበቅ በመሞከር ለሚሰራቸው የቅሰጣ ስራዎች የጎሳ ፖለቲካ እና የብሔር ግጭቶችን እንደሽፋን ሲጠቀም እና በእዚህም እያስታከከ ኢትዮጵያዊነትን ሲያጥላላ፣ኢትዮጵያዊነት ላይ የሚኖሩትን ሲያሳድድ እና በቅርቡ ደግሞ ለረጅም ጊዜ በፕሮፓጋንዳ  ሲሰራበት የነበረውን ኢትዮጵያን እና የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሲያጥላላ  ኖሮ የፀጥታ ችግር በተፈጠረባቸው ክፍተቶች ሁሉ ባገኘው አጋጣሚ ክርስቲያኖችን ሲገድል እና አብያተ ክርስቲያናትን ሲያቃጥል  በግልጥ ታይቷል።የምሁራዊ ጀሃድ ዋና ተግባር ኢትዮጵያን ማናጋት ነው።ለእዚህ ደግሞ ዋና ምክንያቱ  ከትርምሱ እንደሚያተርፍ ያስባል።ትርምሱ ሲቀጥል ኢትዮጵያን ከስር ወደላይ ለመገልበጥ በሰይፍ ዓላማውን ለማስፈፀም ያሰፈሰፈ  የጥፋት ቡድን ነው።

ለማጠቃለል የምሁራዊ ጀሃድ ቡድን በፅንፍ የጎሳ ፖለቲካ ከኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ እስከ ቤንሻንጉል፣ከባሌ ዶሎ መና እስከ አርሲ የተሞከረው የጎሳ እልቂት ድግስ ባለመሳካቱ በግልጥ የነበረ እውነተኛ መልኩን ማለትም የኢትዮጵያ ሙስሊም ወገኖቻችን ፈፅመው የማይቀበሉትን ኢትዮጵያዊነትን እና ኦርቶዶክስ ሃይማኖትን ለመናድ በማኅበራዊ ሚድያ በግልጥ ለመምጣት ተገዷል። በነገራችን ላይ የምሁራዊ ጀሃድ አራማጅ ቀደም ብሎ በአሜሪካ የፅንፈኛው ኃይል መንገድ ሜንጫ  መሆኑን ሳያውቀው የተነፈሰው ፈልጎት አልነበረም።ድንገት ሳያውቀው የወጣበት ሚስጥር ነው።ሰሞኑን በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ  ደካማ እና የተረት ተረት ወግ ጥረቃ ፅሁፎች በማኅበራዊ ሚድያ ላይ የመለቀቅ እውነተኛ ምስጢር ተስፋ የመቁረጥ ውጤት ነው።በታሪክ እና የሃይማኖት ምሁራን ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ መከፈቱም ሌላው የመደናገጥ እና የመደናበር ውጤት ነው። ይህ ማለት ግን የሕግ እና ስርዓት የማስከበር ኃላፊነት ያለበት መንግስት የምሁራዊ ጀሃድ አራማጆችን እና የህዝቡን ፀጥታ ለማወክ በሚንቀሳቀሱ ላይ ሕጋዊ ሥራ መስራት አለበት።ጉዳዩን በቸልተኝነት ሊያልፈው አይገባም። ሕዝቡም ካለምንም ማመንታት የጀሃድ ምሁራን ቡድኖችን በየትኛውም የተቃውሞ አክትቪዝም ስራም ሆነ የፖለቲካ ተቃዋሚ ወይንም የመንግስት መዋቅር ውስጥ ቢገኙ ማጋለጥ እና ለሕግ እንዲቀርቡ ማድረግ ይገባዋል። በሌላ በኩል ኃላፊነት የሚሰማው ኢትዮጵያዊ ምሁር በሙሉ የምሁራው ጀሃድ አራማጆችን ፅሁፍ እግር በግር እየተከታተለ ማምከን እና የውሸት መጋረጃ በአደባባይ ማጋለጥ አለበት።  




ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Monday, December 16, 2019

የኢትዮጵያ የመንግስት ራድዮ እና ቴሌቭዥን ዜና ይዘት ስብጥር ጉዳይ ካልተስተካከለ ለአገር አንድነት አደጋ አለው (ጉዳያችን ሃሳብ)

ጉዳያችን / Gudayachn
ታኅሳስ 6/2012 ዓም (ዴሰምበር 16/2019 ዓም)

በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን በአገሪቱ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ አስተሳሰቦች ላይ የራሳቸውን አሻራ በአጭር እና በረጅም ጊዜ ማስቀመጣቸው የማይካድ ሀቅ ነው።ጥያቄው ግን የመገናኛ ብዙሃኑ ተፅኖ በምን ያህል መጠን እየሄደ ነው? ተፅኖው አዎንታዊ ነው ወይንስ አዎንታዊ? የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ ከስር ከስር እየተከታተለ የሚያጠና አካል አለመኖሩ ጉዳት አለው።የሚከታተለ እና ሪፖርቱን ለሕዝብ የሚያቀርብ አካል አለመኖሩ ግን የመገናኛ ብዙኃኑን አዎንታውም ሆነ አሉታዊ ተፅኖ ከመፍጠር ግን የሚገታቸው አይደለም። እዚህ ላይ መንግሥታዊው የመገናኛ ብዙኃን ኤጀንሲን አልዘነጋሁትም።ይህ ድርጅት ግን ብዙውን ጊዜ ከፖሊሲ እና መመርያ አንፃር የመገናኛ ብዙሃንን ከመከታተል ባለፈ ጠለቅ ያለ ጥናት አስጠንቶ ለሕዝብ ሲያቀርብ አልገጠመኝም።

በአሁኑ ወቅት ያለው ዜና በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ምን ይመስላል?


የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ከ2010 ዓም የኢህአዴግ የለውጥ ጅማሬ በፊት ከነበሩበት አቀራረብ በብዙ ተቀይረዋል።ከተቀየሩበት መንገድ አንዱ በተቻለ የተለያየ የኅብረተሰብ ክፍል ይነካል ያሉትን ዜና ለማካተት ጥረት አለ።ለምሳሌ በቀድሞ ጊዜ ከነበረው የደረቀ ፕሮፓጋንዳ አሁን በቴክኒክም ሆነ በአቀራረ የተሻለ ሁኔታ አለ።ለምሳሌ ቀድሞ ከአራት ኪሎ ብቻ ለሚወጡ  ምናልባት የፓርላማውን መክፈቻ ብቻ ያውም ከስንት አንዴ በመንግስት ከታዘዙ ብቻ የቀጥታ ስርጭት ይሸፍኑ የነበሩ የመገናኛ ብዙኃን አሁን በበርካታ ክንውኖች ላይ የቀጥታ ስርጭት ያሳያሉ።በሌላ በኩል የዜና ዝግጅቶች በተመሳሳይ ሰዓት በቀጥታ በማኅበራዊ ሚድያ መታየታቸው እና በዩቱብ መጫናቸው ቀደም ብሎ የተጀመረ ቢሆንም አሁን ግን ካለምንም መቆራረጥ እና በዕለቱ ማግኘት የሚቻልበት ሁኔታ አለ።ይህም ሆኖ ግን የዜና ሽፋኞቹ  በክልል የታጠሩ እና አንዱ ስለሌላው በሚገባ እንዲያውቅ የሚያደርግ አይደለም።


 የኢትዮጵያ የመንግስት ራድዮ እና ቴሌቭዥን ዜና ይዘት ስብጥር ጉዳይ ካልተስተካከለ ለአገር አንድነት አደጋ አለው

በእዚህ አነስተኛ ፅሁፍ ለማንሳት የምሞክረው  ዋናው ጉዳይ የመንግስት ራድዮ እና ቴሌቭዥን ዜና ይዘት መላው ኢትዮጵያን የካለለ አለመሆኑ በአጭርም ሆነ በረጅም ጊዜ የሚፈጥረው አደገኛ የመለያየት ጥፋት ይኖራል።ለእዚህ መነሻዬ የተጠና መረጃ ኖሮኝ አይደለም።ነገር ከራሴ ምልከታ ነው።ምልከታው ግን ትክክል እንደሆነ እና የአደጋው ውጤት በራሱ ከገመትኩትም በላይ ሊሆን ይችላል።

የዜና ስብጥሩ ችግሩ እና መፍትሄው 


ስለአንድ የጋራ አገር የተለያየ መረጃ የደረሰው ትውልድ ነገ ይጣላል።ለዛሬው  የወጣቶች በዩንቨርስቲ ግቢ ውስጥ ፀብ አንዱ መነሻ ትናንት የተሰጠው የመገናኛ ብዙሃን በአንድ አገር ውስጥ የተለያየ መረጃ መሰጠቱ ነው።በመንግስት መገናኛ ብዙሃን በአማርኛ፣ኦሮምኛ፣ትግርኛ፣ሱማልኛ፣አፋርኛ የሚተላለፉ ዜና ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ይደርሰዋል? ለምሳሌ ሁሉም ዜና በተለያየ ልሳን ሲያቀርቡ ቀዳሚ የሚያደርጉት በመንግስት ቀዳሚ የሆነውን ዜና ለምሳሌ በጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ወይንም የተወካዮች ምክርቤት የተደረገ እና ሌላም ዜና በተመሳሳይ መልክ ያቀርባሉ።ይህ ተገቢ ነው የዕለቱ ቀዳሚ አጀንዳ ለሁሉም ልሳን ዜና መቅረቡ ተገቢ ነው። 


የመረጃ ክፍተቱ የሚመጣው ግን እዚህ ላይ አይደለም።ወደ ክልሎቹ ስመጣ ነው ችግሩ። የአማርኛ ልሳን ዜና ላይ ስለ አዲስ አበባ እና ከክልሎችም በጣም ተመርጠው የጎሉ የተባሉት ይቀርባሉ።በኦሮምኛ ልሳን የሚነበበው ደግሞ በቀዳሚ የመንግስት የዕለቱን ዜና ካወራ በኃላ በዝርዝር ወደ ኦሮምያ ክልል ያሉ ዜናዎች ያወራል። የትግርኛውም፣የሱማለውም ሆነ የአፋሩ ተመሳሳይ እንደ አማርኛው፣ኦሮምኛው እና ትግርኛው በዝርዝር ስለክልላቸው የሚዘግቡትን ያህል የአማርኛው ስለ አዲስ አበባ ያለውን ዝርዝር ለኦሮምኛው ልሳን አድማጭ አይነግሩትም፣የአማርኛው ዜና ላይም በዕለቱ አምቦ ከተማ ምን እንደተደረገ ከኦሮምኛው ወስዶ ለአማርኛ ልሳን ሰሚው አያወራም።ሁሉም ላይ የሚታየው ችግር ይህ ነው።ለእዚህ ደግሞ ዋናው ምክንያት አንዳቸው ከአንዳቸው በእየእለቱ ዜና አይቀያየሩም።ስለ ኦሮምያ ክልል መረጃ ለማግኘት ከአማርኛው ዜና አጠናቃሪ በተሻለ የኦሮምኛ ክፍሉ የልሳኑ ተናጋሪ  በመሆኑ የበለጠ ዝርዝር መረጃ የማግኘት ዕድል አለው።በሌላውም እንዲሁ ነው። ሁሉም በየራሱ ልሳን ያጠናቀረውን ዜና ያቀርባል እንጂ የሌላውን ዝርዝር ገብቶበት ለሌላው አይነግረውም።በእዚህም አዲስ አበቤ በአንድ መቶ ኪሎ ሜትር ርቀት ስለምትገኘው አዳማ (ናዝሬት) መረጃ ያጥረዋል።የአዳማ ነዋሪም ስለ ባህርዳር ለማወቅ የአማራ መገናኛ ብዙሃን ልያስስ ነው ለእዛውም የልሳን ማወቅ እና አለማወቅ ካልገደበው። በጠገላብጦሽም ብናየው ተመሳሳይ ነው። 


ይህ ጉዳይ ደግሞ ከፍተኛ የመረጃ ክፍተት በአንድ አገር በሚኖር ሕዝብ መሃከል ፈጥሯል።ይህ የመረጃ ክፍተት ደግሞ ፖለቲካውን፣ማኅበራዊ  ኑሮውን እና ምጣኔ ሃብቱን ሳይቀር በአጭር እና በረጅም ጊዜ ይጎዳዋል።ጉዳቱ ደግሞ በአጭር ጊዜ ብቻ ሳይሆን በረጅም ጊዜ አገር የሚለያይ እና የተለያየ አስተሳሰብ ያለው ትውልድ የመፍጠር አደጋ አለው።

 የመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ዋናውን ብሔራዊ ዜና በጋራ ካዘጋጁ በኃላ የአማርኛው ልሳን ከኦሮምኛው እና ትግርኛው ልሳን ያሉትን ዜናዎች  አስተርጉሞ በዝርዝር ስለ ኦሮምያ ክልል ትግራይ ክልል እና ሌሎችም ያሉትን ዝርዝር ጉዳዮች በዜና እንዲያቀርብ እንፈልጋለን። የአፋር፣የሱማለውም ሆነ የሌላው እንዲሁ የአማርኛ ዜናዎች የያዙትን የዕለቱን ይዘት  በዝርዝር ተርጉመው ለአድማጮቻቸው ማስደመጥ አለባቸው።ኢትዮጵያውያን እርስ በርስ የተሳሰሩ ናቸው።ባህርዳር ያለው ስለ ደምቢዶሎ ውሎ ማወቅ ይፈልጋል።አሳይታ ያለው ስለሞያሌ ውሎ ማወቅ ይፈልጋል።አዲስ አበቤ ስለ ዶሎ መና ያለው የአንዲት መንደር መንገድ ጠረጋ ዜናም ቢሆን መስማት ይፈልጋል።ከዜናው ትንሽነት እና ትልቅነት አይደለም ጉዳዩ። ሕዝብ የሚተነትንበት የራሱ አይን አለው።አንዱ ስለአንዱ በዝርዝር ካወቀ ችግሩንም ሆነ ጉዳቱን፣ደስታውንም ሆነ ሀዘኑን ይረዳል።በመረዳት ብቻ አይቆምም ርዳታ ሲፈልግ ይደርስለታል።አሁን ያለውሁኔታ ግን ሁሉም እንደ ጋሪ ፈረስ በየልሳኑ የምቀለውን  የአካባቢውን ዜና እያቀረበ ሌላው ሳይሰማው እንደ ጋሪ ፈረስ ሕዝብ በእየአካባቢው እንዲያስብ የሚያደርግ አደገኛ አካሄድ ነው። እዚህ ላይ ሁሉም ዜና በየልሳኑ የተወሰነ ስለሌላው አያወራም እያልኩ አይደለም።ጥልቀት ያንሰዋል።ጫፍ ጫፉን ነው የምትንነግሩን፣ባለ ልሳኑ የሚያወራውን ዜና ያህል የጠለቀ ዝርዝር እኩል እንወቅ እያልን ነው። በእርግጥ በአንድ የዜና ሽፋን ጊዜ ሁሉን መሸፈን አይቻል ይሆናል።ነገር ግን ሁለት አማራጭ አለ። አንዱ በእየለቱ ሁሉም በልሳኑ የሌላው ልሳን ያዘጋጀው ዜና ላይ ጉልህ የሆኑትን ከሁሉም ክልሎች የማቅረብ ግድታ ቢገባ የሚለው ሲሆን፣ ሌላው ከዋና የዜና እወጃ በተለየ በሳምንት ሁለት ወይንም ቢያንስ አንድ ቀን ሰፊ የክልሎች ዜና በስፋት ሁሉም የዜና እወጃ በልሳኑ በጥልቀት እንዲዘግብ እና ዘገባው ደግሞ ሁሉንም ክልሎች የሳምንት ዜና  የሸፈነ እንዲሆን ማድረግ ነው።የመረጃ ክፍተቱ የሚፈጥረው አደጋ ይታየን።

ለማተቃለለ ይህ ጉዳይ ጊዜ የሚሰጠው አይደለም።በነገራችን ላይ  ህዝቡ የቪኦኤ እና ዶቼቬሌ ራድዮን የሚከታተለው የተለየ ነገር ሆኖ አይደለም።የዜና ሽፋናቸው አብዛኛውን ክልል ስለምሸፍን ነው።መረጃዎች ከባህር ማዶ ሲመጡ ደግሞ ከውጭ አገር ማሰራጫው ፖሊሲ ጋር የተያያዘ ስለሆነ በራሱ የጠራ አይደለም። የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ይህንን ቢያስቡበት ተገቢ ነው።

የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን  በ1955 ዓም ሲከፈት (ቪድዮ )



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Thursday, December 12, 2019

ኢትዮጵያን በተመለከተ በኦስሎ፣ኖርዌይ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የተከፈተውን ዓውደ ርዕይ (ኤግዚብሽን) በቪድዮ ይጎብኙ።




ኢትዮጵያን በተመለከተ በኦስሎ፣ኖርዌይ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የተከፈተውን የኖቤል ዓውደ ርዕይ (ኤግዚብሽን) በቪድዮ ይጎብኙ።
ትናንት ታህሳስ 1/2012 ዓም በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዓቢይ አህመድ በኦስሎ ኖርዌይ የተከፈተው Cross Roads Ethiopia a country in transition የተሰኘውን የኖቤል ኤግዚቢሽን ይጎብኙ። 

ቪድዮውን ለመከታተል ይህንን ሊንክ ይጫኑ ዩቱብ ሊንክ ይክፈቱኝ 

 https://www.youtube.com/watch?v=NGjYDcgSjp0&feature=youtu.be

On December 12/2019 Nobel Peace Center Cross Roads Ethiopia a country in transition Exhibition was officially opened by Ethiopian Prime Minster Abiy Ahmed in Oslo.Here is Nobel Peace Center Exhibition live visit by Gudayachn editor Getachew Bekele
To watch the video Click here 

ጉዳያችን (https://www.youtube.com/watch?v=NGjYDcgSjp0&feature=youtu.be)
ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Wednesday, December 11, 2019

ሰበር ዜና - የጥምቀት በዓል በዩኔስኮ በዓለም አቀፍ ቅርስነት ተመዘገበ።UNESCO decided to inscribe TIMKET on the List of the Intangible Cultural Heritage of Humanity



ዛሬ ረቡዕ ታህሳስ 1/2012 ዓም የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣የሳይንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በእየዓመቱ ጥር 11 ቀን የሚከበረውን የጥምቀት በዓል በዓለም አቀፍ የማይዳሰስ ቅርስነት እንደመዘገበው ገልጧል።ድርጅቱ ይህንን ውሳኔ ያደረገው በኮሎምቢያ፣ቦጎታ እያካሄደ ባለው ስብሰባው ነው።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ካሏት ሁለት ዓመታዊ ክብረ በአሏች ውስጥ ከእዚህ በፊት መስቀል በዓለም ቅርስነት መመዝገቡ ይታወሳል።

UNESCO decided to inscribe TIMKET on the List of the Intangible Cultural Heritage of Humanity. 
According to UNESCO website,Ethiopian Epiphany was expressed as follows -
''Ethiopian Epiphany is a colorful festival celebrated all over Ethiopia to commemorate the baptism of Jesus Christ. The commemoration starts on the eve of the main festival, when people escort their parish church TABOT, a representation of the Tables of the Law, to a pool, river or artificial reservoir. Celebrants then attend night-long prayers and hymn services, before taking part in the actual festival the following day, when each TABOT is transported back to its church. The Ethiopian Epiphany is a religious and cultural festival whose viability is ensured through continuous practice and the pivotal contribution of the Orthodox clergy''.

ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Friday, December 6, 2019

በጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ቢሮ የተጀመረው ምቹ የስራ ቦታን የመፍጠር ሳይንስ (ኤርጎኖሚክስ) የኢትዮጵያን የመንግስት ቢሮዎች እና የሰራተኞችን ምቾት በሚያስደንቅ መልኩ ቀይሮታል። (ቪድዮ)

ኢትዮጵያ ያሉትን የመንግስት ቢሮዎች ከእዚህ በፊት የምታውቁ ይህንን ቪድዮ ተመልክቶ ካለምንም ማጋነን አለመደመም አይቻልም።ጉዳያችን በእውነት በጣም ረክታበታለች።


ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Tuesday, December 3, 2019

የኖቤል የሰላም ሽልማት በተመለከተ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ምን አሉ? (ዛሬ የተለቀቀ አዲስ የኢሳት ቴሌቭዥን ዝግጅት) Etiopiere i Oslo kommenterer 2019s Nobels fredspris som vil bli gitt til statsminister Abiy 10. desember 2019.


ስለ ኖቤል መርሐግብር አዳዲስ መረጃ ለመከታተል  ይህንን የፈስቡክ ሊንክ ይጫኑ >> ኖቤል 2019 ለሌሎች ያካፍሉ።


ምንጭ - ኢሳት

Ethiopian Satellite TV (ESAT TV) 


ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Sunday, December 1, 2019

ሰበር ዜና - የብልፅግና ፓርቲን የተቀላቀሉ ድርጅቶች የስምምነት የፊርማ ስነ-ስርዓት ዛሬ ዕሁድ ህዳር 21/2012 ዓም በአዲስ አበባ ሲደረግ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ያደረጉት አስደናቂ ንግግር ይመልከቱ።

እኛን ብቻ መተቸት በቂ አይደለም።አማራጭ ሃሳብ ማምጣት ያስፈልጋል።  ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ ዛሬ የተናገሩት።
ሙሉውን ንግግር  ይመለክቱ።



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Saturday, November 30, 2019

አቶ ለማ መገርሳ መደመር እና የኢሕአዴግ ውህደትን አስመልክተው ለቪኦኤ የሰጡት ቃለ ምልልስ ምክንያት ምንድነው? በቀጣይስ ምን ሊከሰት ይችላል?

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ እና አቶ ለማ መገርሳ 

ጉዳያችን / Gudayachn
ህዳር 20/2012 ዓም (ኖቬምበር 30/2019 ዓም)

ዓርብ ህዳር 19/2012 ዓም ምሽት ላይ  ቀደም ብሎ ሐሙስ ዕለት በኦስሎ፣ኖርዌይ ጃዋር መሐመድ የሰበሰባቸው የኦሮሞ ኮሚኒቲ አባላት መካከል በኦሮምኛ ከፊት በኩል የተቀመጡ አንዲት እናት የተናገሩትን ድምፁን በመሃል እያቆመ ኦስሎ የሚኖር የኦሮሞ ኢትዮጵያዊ ወዳጄ እየተረጎመ ያሰማኝ ነበር።እኝህ እናትበጣም አክራሪ ብሄርተኛ እንደሆኑ ከወዳጄ ትርጉም ተረድቻለሁ።በንግግራቸው  ጀዋርን ይወቅሱታል።ጀዋርን የሚወቅሱት ደግሞ ለማ ብቻውን ሆኖ ሳታግዘው መቅረትህ ብቻውን እንዲሆን አርገህ፣ካሉ በኃላ ዓቢይ ማኅበረሰባቸውን (የኦሮሞን ማለት ነው) እንደከዳ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያወራሉ።በመሃል ላይ ንግግራቸው በመርዘሙ ራሱ ጃዋርም እየሳቀ ያያቸው ነበር።አሁንም ይሄው ወዳጄ እንደተረጎመልኝ በቃዎት ሰዓት አበቃ ተብለው ነው ማይኩን የሰጡት።የእርሳቸው ንግግር ግን የውስጥ አዋቂ ንግግርም ይመስል ነበር።ከእዚሁ ወዳጄ ጋር እንዴት ዓብይን በእዚህ ደረጃ እንደከዳ ይቆጥሩታል? በማለት ጥያቄ ሰነዘርኩ። 

ቪድዮውን ማየት ቀጠልኩ በእዚሁ በጃዋር ስብሰባ ላይ የትግራይ ማኅበረሰብ በኖርዌይ ሰብሳቢ አቶ ዳዊት በአማርኛ ንግግር እንዲያደርግ ዕድል ተሰጠው።አቶ ዳዊት ንግግሩን ሲጀምር ከተሰብሳቢዎቹ አንዱ ድምፁን ከፍ አድርጎ ''በትግርኛ ተናገር!'' ብሎ ሲናገር በቪድዮው ውስጥ ይሰማ ነበር።ዳዊት ለጥቂት ሰኮንዶች ንግግሩን ቆም አደረገ እና በአማርኛ ቀጠለ። ዳዊት ተሰብሳቢው እና እርሱን የሚያገናኘው አማርኛ መሆኑ ገብቶታል።ዳዊትን ከእዚህ በፊት ሁለት ጊዜ  ኦስሎ ውስጥ በተደረጉ  የማኅበረሰብ ስብሰባዎች አግኝቼዋለሁ።አድ ጊዜ የኢትዮጵያን የጋራ መድረ በኖርዌይ ባዘጋጀው የሁሉም የፖለቲካ አተያዮች መድረክ ላይ ሲሆን ሌላው በቅርቡ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በኖርዌይ ባዘጋጀው ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ባደረገው ውይይት ላይ ነበር።ከእርሱ ጋር  በሃሳብ የማንስማማባቸው ብዙ ነጥቦች ዙርያ ተከራክረናል።ስንከራከር ግን ስርዓት ባለው መልክ ስለነበር የዳዊት ሃሳብ አቀራረብ ከብዙ የህወሓት ደጋፊዎች የተሻለ አቀራረብ ያለው ግን  ያንኑ በመደጋገም የሃሳቡን ስፍራ ላለመልቀቅ የሚሟገት ሰው ነው።በጀዋር ስብሰባ ላይ መገኘቱ እና ንግግር ሲያደርግ በቪድዮ ላይ ሳየው ግን በቅርቡ ስለሞቱት ሰማንያ ስድስቱ ኢትዮዮጵያውያን አንስቶ ጀዋርን ተጠያቂ እንደሆነ ይነግረዋል ብዬ አስቤ ነበር። አላደረገውም።

ወደ አቶ ለማ ጉዳይ ልመለስ።የኦስሎው ስብሰባ ላይ ለማን እያሞገሱ ከተናገሩት ሴት መለስ ስል የማኅበራዊ ሚድያው አቶ ለማ የመደመር ሃሳብ እንዳልተቀበሉ ገለጡ የሚል ዜና ተለጥፎ አየሁ።ወደ ቪኦኤ ገፅ ስገባ ዜናውን አረጋገጠልኝ።ግን ሙሉ ዜናው ስላልነበር ምንም ለማለት አላስቻለኝም። ዛሬ ምሽት ግን ቪኦኤ አማርኛው ሙሉውን ዘገባ ለቆታል። በዘገባው ላይም አቶ ለማ የመደመር ሃሳብ ከመጀመርያው እንዳልተቀበሉት እና እንዳልገባቸው፣ይልቁንም ጉዳዩ የኦሮሞ ሕዝብ  አምኖ የሰጣቸውን እንደመክዳት እንደሚቆጠር ገልጠዋል።የአቶ ለማ ንግግር ለምን ቀድሞ አልተነሳም? በውህደቱ የኢሕአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይስ  ድምፃቸውን ሲሰጡ ለምን ተቃውሞ አልተነሳም? በተለይ ዛሬ ዘሐበሻ ዜና ላይ እንደዘገበው የኦዴፓ  ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ታዬ ደንዳ ለኤስኢቢኤስ ራድዮ ተናገሩት ባለው ዘገባ ላይ አቶ ለማ ከእዚህ በፊት በየትኛውም ቦታ የውህደቱን እና የመደመርን ጉዳይ አስመልክቶ ተቃራኒ ሃሳብ እንዳላቀረቡ  መግለጣቸውን ዘግቧል።ይህ ከሆነ ዛሬ ለምን አነሱት?

አቶ ለማ ምን ሆነው ነው?

እነኝህን እና ሌሎች ሁኔታዎችን ስንመለከት አቶ ለማ በአሁኑ ሰዓት ከኢትዮጵያዊነት ስሜቱ ይልቅ ያየለባቸው (ያስጨነቃቸው) በኦሮሞ ማኅበረሰብ ውስጥ እንደ ከሃዲ ልቆጠር ነው የሚለው ጭንቀት ነው።ከእዚህ ውጪ ከእዚህ በፊት በእየመድረኩ ከነገሩን አንፃር ስናየው የአቶ ለማ ሃሳብ ማጠንጠኛ ምላሽ የሚያገኘው ከመደመር እና ከኢሕአዴግ ውህደት ውጪ የተሻለ የሚያረካቸው ሃሳብ ሊገኝላቸው አይችልም።  እና አሁን አቶ ለማ ለምን እጃቸውን ሲያወጡ ባላፈሩበት ጉዳይ  ዛሬ ተቀይረው ሌላ ሃሳብ አነሱ? ጉዳዩ ጊዜ የሚፈታው ቢሆንም አሁን ባለው ሁኔታ ግን  የሚከተሉትን መሰረታዊ ጥያቄዎች ጠይቆ ማለፍ ይቻላል። እነርሱም -

  • አቶ ለማ መደመር እና የውህደቱ ሂደት እዚህ ደረጃ እንደማይደርስ እርግጠኛ የሆኑበት የማናውቀው በሚስጥር የያዙት ፕሮጀክት ስለነበር ነው እስከዛሬ ዝም ብለው የቆዩት?
  • አሁን ያ ያሉት ፕሮጀክት መክሸፉን ሲመለከቱ እራሳቸው በቀጥታ ሊገቡበት አሰቡ?
  • ወይንስ እንዳሉት መደመር እና ውህደቱ ሳይገባቸው እና ሳይስማሙበት ቆይተው ነበር?
በማስከተል የሚነሳው ጥያቄ አቶ ለማ ይህንን በማለታቸው በመደመር እና የኢህአዴግ ውህደት ላይ የሚመጣው ተፅኖ አለ ወይ? የሚለው ነው።የውህደቱ ጥያቄ ከኢህአዴግ በላይ እየገፉበት ያሉት የአጋር ድርጅቶች ናቸው።ከእስነርሱ ጋር የውህደት ደጋፊዎች ኢሕአዴጋውያን  እና የጎሳ ፖለቲካ ያሰጋው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከውህደቱ ጋር ቆሟል።ከእዚህ በተጨማሪ የተቃዋሚ የዜግነት እና የአንድነት ኃይሎች ሁሉ የውህደቱን ሂደት ይደግፋሉ። በአንፃሩ የጀዋር የፅንፍ ኃይል እና በኦዴፓ ውስጥ የተሰገሰጉ  የብሔር ድርጅቶች ውህደቱን ይቃወማሉ።ከእነሱ በተጨማሪ ህወሓት ዋነኛ ተቃዋሚ ብቻ ሳትሆን በመጪው ሳምንት ወደ ስድስት መቶ ሰዎች የሚሳተፉበት የፈድራሊስት አስተሳሰብ አራማጆች በማለት የተራቻቸውን አበል እየከፈለች መቀሌ ላይ ለመሰብሰብ አቅዳለች። 

በሌላ በኩል የውህደቱን ሃሳብ ካለምንም ድርድር እንደሚቀበለው በቀላሉ ልንረዳው የምንችለው የጦር ሰራዊቱ ነው።በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት አደረጃጀቶች የህዝቡ የጎሳ ስሜት ያላጠቃው አካል የሚገኘው በጦር ሰራዊቱ በተለይ በመካከለኛ እና የመስመር መኮንኖች እስከ ተራ ወታደር ያለው የውህደቱን ሃሳብ ይደግፋል። ይህ ደግሞ ተፈጥሯዊ ነው።የጦር ሰራዊቱ የአንዲት ኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ የሚያተኩር ሆኖ የተሰራ እንጂ በብሄር የተከፋፈሉ ፓርቲዎች የራሱ ራስ ምታት እንደሆኑ ስለሚያውቅ ፈፅሞ መከፋፈልን ሳይሆን የጠቅላይ ሚኒስትሩን የውህደት እና የመደመር ሃሳብ የሚቀበል  ለመሆኑ መጠራጠር አያስፈልግም። ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በጦር ሰራዊቱ መካከለኛ እና የመስመር መኮንኖች ጀምሮ እስከታችኛው ወታደር ድረስ በጣም የሚወደዱ መሪ ናቸው።ስለሆነም የውህደቱ ሂደት ፈፅሞ ሊገታ የሚችልበት ደረጃ አይደለም።  ለእዚህም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የብልፅግና ፓርቲ ገና የምስረታ ጉባኤ ሳይጠራ በኦሮምያ ክልል ያለውን ቢሮ እንዲያደራጅ ሹመት መስጠት የጀመሩት።

በቀጣይስ ምን ሊከሰት ይችላል?

የአቶ ለማ የአመለካከት ለውጥ ትናንሽ ጭረቶችን ከማምጣት ያለፈ በውህደቱም ሆነ በመደመር ሂደት ላይ አንዳች ለውጥ አያመጣም። ምክንያቱም ኢትዮጵያ አሁን ከገባችበት የፖለቲካ ቀውስ ለመውጣት በምንም መመዘኛ ለማየት ብንሞክር ከኢህአዴግ እውነተኛ ውህደት እና ከመደመር እሳቤዎች ውጪ  ህመሟን ልታስታግስበት  የሚችል አንዳች ነገር የለም።ይልቁንም ይህ የመፍትሄ ሂደት በፍጥነት ባይመጣ ኖሮ በኦደፓ እና በአደፓ ውስጥ የገባው የፅንፍ አስተሳሰብ ኢትዮጵያን ወደ አልታወቀ የማዕበል አዘቅት ውስጥ ሊወስዳት ተዘጋጅቶ እንደነበር ለማየት ይቻላል። በሌላ በኩል የአቶ ለማ የሃሳብ ልዩነት ምንም ጭረት አያመጣም ማለት አይደለም።በመጀመርያ ደረጃ አቶ ለማ ለይተው ወደ ፅንፍ ኃይሎች ጎራ ይገባሉ ወይንስ የራሳቸውን አስተሳሰብ ይዘው  የራሳቸውን እና የተከታዮቻቸውን ሃሳብ ይዘው ፓርቲ ይመሰርታሉ? የሚለው ጥያቄ ወሳኝ ጥያቄ ነው።ሌላው ጥያቄ አቶ ለማ በኦደፓ ውስጥ የለዘብተኛ መስመርን ነው ወይንስ የኦነግን መስመር ይከተላሉ? የሚለው  ነው።አቶ ለማ ወደ ፅንፍ ጎራ ይገባሉ ብሎ ማሰብ የሚቻል አይመስልም። ወደ ኦነግ ጎራም ይገባሉ ብሎ ማሰብ አይቻልም።ምክንያቱም ኦነግ እራሱ የፖለቲካ መሰረቱ ከመናጋት አልፎ ሃሳቡን መግለጥ ሲያቅተው እየተኮሰ እና እያስተኮሰ የራሱን ወገን የሚወጋ  አካል ሆኗል።ስለሆነም አቶ ለማ ለጊዜው የሚያደርጉት አንድ በልዩነት ተቀምጠው ለጥቂት ጊዜ ማየት አልያም የራሳቸውን የፖለቲካ ፓርቲ መስርተው በምርጫ መወዳደር ሊሆን  ይችላል።አቶ ለማ ሶስቱንም መንገድ ቢሄዱ ግን ኦደፓ ለሶስት መሰንጠቁ የማይቀር ነው።ኦደፓ ለሶስት ተሰነጠቀ የሚል ታሪክ ሳይፃፍበት ብልሁ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ  ውህደቱን በማብሰር ያለፈ ታሪኩ ሳይጎድፍ እንዲፃፍ ሊረዱት ይችላሉ። አቶ ለማ ይህንን የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሃሳብ ቢረዱ ኖሮ ዝም ቢሉትም ለሶስት ማለትም የውህደት ደጋፊዎች፣የፅንፍ አቅራሪ ኃይሎች እና የለዘብተኛ ብሄርተኞች ክፍል ሆኖ መከፈሉ የማይቀር ነበር።አቶ ለማ ትናንት የሰጡት ሃሳብም የእዚህ የስንጥቁ  አንድኛው ድምፅ ነው።

ማጠቃለያ 

ለማጠቃለል አቶ ለማ መገርሳ የፈለጉትን ሃሳብ መስጠታቸው የሚከበር እና ሊከበር የሚገባ ነው።ግለሰቡ ስብእናቸውም  የሚናቅ አይደለም።ቆራጥ እና ሀቀኝነት የታየበት አሰራር አሳይተዋል።ወደፊትም የኢትዮጵያ የክብር ሰው ሆነው መቀጠላቸው አይቀርም። በተለይ በቅንነት የኦሮሞ ብሔርተኝነት ይጨፈለቃል ብለው ለሚሰጉ እንደ አቶ ለማ ያሉ ኢትዮጵያዊ ሃሳብ ያላቸው ግን ብሔርተኝነትን  በአንክሮ የሚያዩ ሰዎች መኖራቸው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ጠቃሚ እንጂ ጉዳይ የለውም። አቶ ለማ አንዴ በጎ ኢትዮጵያዊ ሃሳባቸውን ገልጠዋል።ኢትዮጵያዊነታቸውን የሚወስድባቸውም ሆነ በችሮታ የሚሰጣቸው የለም። ድሮም አብሯቸው የኖረ  እና ወደፊትም የሚኖር ነው።ይህ ሁሉ ሆኖ አቶ ለማ የሚመዘኑት ከእዚህ በፊት ከሰሩት ይልቅ ከአሁን በኃላ በሚያደርጉት ነው።እንደ ብዙ ኢትዮጵያውያን ሃሳብ አቶ ለማ የውህደቱን ሂደት የሚያደናቅፍ አንድም ድርጊት ባያደርጉ እና  የመደመርን ሃሳብም በሳይንሳዊ መንገድ ከመተቸት አልፈው ወደ ሌላ አላስፈላጊ ተግባር እንዳይሄዱ  ምክሮች ሁሉ ተሰብስበው መናገር አለባቸው።ኢትዮጵያ በ21ኛው ክ/ዘመን እንደመሆኗ የብሔር ፖለቲካ ደክሟታል። ከእዚህ በላይ ትከሻዋ አይሸከምም።የብሔር ፖለቲካ ቶሎ ቆስሉ ስለማይድን እንጨፈለቃለን ብለው ለሚሰጉ እንደ አቶ ለማ ያሉ ወጣ ብለው ሁኔታውን እየተከታተሉ አገር ያረጋጉ ይህ ክፋት የለውም።የመጨረሻው መጨረሻ ሃሳብ ግን አቶ ለማ ሃሳብ ሌላ ጊዜ ሲኖርዎት እባክዎን የአገር ውስጥ ሚድያዎችን ይጠቀሙ።ይህ ሰነድ ነው።ይህ አገራዊ ጉዳይ ነው። በእዚህ ዘመን ሃሳብን ለመግለጥ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ ድረስ መሄድ ብዙም አያሳምንም። ይልቁንም አላስፈላጊ የባዕዳን ተወዳጅነት ለማትረፍ የተደረገ ቁጭ ብድግ ያስመስላል።ከእዚህ ውጪ አቶ ለማ በሃሳብዎ ልዩነት እናከብርዎታለን እንጂ አንጠላዎትም።ወደፊት በሚሄዱት አካሄድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመዳኘት በአንክሮ እርስዎን እና ተከታዮችዎን ይከታተላል። ውህደቱ እና መደመር ግን ይቀጥላል። የሚቀጥለው ደግሞ የተሻለ መንገድ ስለሌለ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም አዋጪ ስለሆነ ነው።በመጪው ጊዜም በግልጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድጋፉን የበለጠ የሚገልጥበት ጊዜ ይሆናል።  



ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Friday, November 29, 2019

በያዝነው ሳምንት መጀመርያ በቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ ቄሮ በሚል ስም ግጭት ከፈጠሩት ውስጥ አንዱን ያዳኑት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ናቸው። (ቪድዮ ይመልከቱ)

  • የቦሌ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ከተከሉት የቤተ ክርስቲያን አሰሪ ኮሚቴ አባላት ውስጥ አርበኛው አብዲሳ አጋ እንዳሉበት ያውቃሉ?
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በተደራጀ መልክ ጥቃት እየተፈፀመ እንደሆነ የሚታይ ነው።በቤተ ክርስቲያን ላይ ጥቃት የሚያደርሱት አካላት በዋናነት በፅንፍ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ እና በተደራጀ መልክ ከፅንፈኞች አመራር እንደሚቀበሉ ይነገራል። እራሱን ቄሮ ከተሰኘው ቡድን ውስጥ ብዙዎች በሰላማዊ መንገድ እንደሚንቀሳቀሱ  እና ፅንፈኘነትን እንደማይደግፉ በእየሚድያው ላይ ሲናገሩ ይሰማል።ሆኖም ግን ከቄሮ ውስጥ አሁንም በፅንፍ አደረጃጀት ከፅንፍ አካል መመርያ የሚቀበሉ እንዳሉ የሚናገሩ ግን ብዙዎች ናቸው።

ህዳር 15/2012 ዓም በቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ ይሄው የፅንፍ ቡድን በቤተ ክርስቲያን ላይ ጥቃት ለመፈፀም ሞክሯል።ጳጉሜን 3/2011 ዓም ላይም በአውደ ምህረት ላይ ''አላህ ወአክበር'' ለማለት የሞከረ እና ብጥብጥ ለመፍጠር የሞከረ ነበር። በሰሞኑ ጥቃት ግን አንዱ በተለይ ከጅማ የመጣ የተባለውን ሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ አስገብተው ከህዝብቁጣ ያዳኑት እና ለሕግ አካላት በመስጠት መልካም ተግባር የፈፀሙ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ሊመሰገኑ ይገባል።

በነገራችን ላይ የእዚህ ፅሁፍ አቅራቢ የቦሌ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ለረጅም ጊዜ የሚያውቀው ከመሆኑ አንፃር የቤተ ክርስቲያኑ የኃላ ታሪክ ላይ ቤተ ክርስቲያኑ ተከላ ላይ ኮሚቴ ከነበሩት አባቶች መካከል በቦሌ መንገድ ወሎ ሰፈር መኖርያቸው  የነበረው አርበኛው አብዲሳ አጋ እንደነበሩ መረጃውን በወቅቱ ከነበሩት አባቶች በቀጥታ መስማቱን በእዚህ አጋጣሚ ለመግለጥ ይፈልጋል። ዛሬ በቄሮ ስም የተደራጁ የፅንፍ አካሎች የአርበኛ አብዲሳ አጋን ሥራ  ለማፍረስ የሚደረግ ሙከራም መሆኑን ልብ ይሏል።

ህዳር 15/2012 ዓም በቦሌ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ምን ተፈጠረ? ቪድዮውን ይመልከቱ።

ከደብሩ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ምክትል ሊቀመንበር እና የሰንበት ትምህርት ቤቱ አገልጋይ ከአቶ መስፍን  በዳዳ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ 


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Thursday, November 28, 2019

The 2019 Nobel Peace Prize ceremony is coming soon! የኖቤል ሽልማት ቀን አንድ ሳምንት ቀረው

የኖቤል የሰላም ሽልማት ስነ ስርዓት በህዳር 30/2012 ዓም (ዴሴምበር 10/2019 ዓም) በኦስሎ ኖርዌይ ይከናወናል።
Nobel Peace Prize ceremony will be held in Oslo, Norway on December 10,2019.
Listen to the call between Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed Ali and Olav Njølstad, Secretary of the Norwegian Nobel Committee, recorded shortly after the public announcement of the 2019 Nobel Peace Prize.

Source : - Nobel Peace Prize


ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Sunday, November 24, 2019

Breaking News Ethiopia - ''There is a terrorist command center in USA working to destabilize Ethiopia and the horn of Africa'' Ethiopian journalist Eskindir Nega disclosed in Washington DC on November 24,2019.ማዕከሉን አሜሪካ ያደረገ የሽብር ቡድን ኢትዮጵያን ለማተራመስ እየሰራ ነው። (ቪድዮ)


  • የሽብር ቡድኑ በኢትዮጵያ ሴሎች፣የዕዝ ሰንሰለት እና ከመካከለኛው ምስራቅ የሚያገኘው የገንዘብ ፈሰስ አለ።
  • The terrorist team has his own cell, command chain and financial assistance from middle east
**********************************

ጉዳያችን / Gudayachn / November 24/2019 
ህዳር 14/2012 ዓም 
**********************************
Eskindir Nega is Economics graduate from American University (private research University in Washington DC) . He has completed his high school from Sanford American High school in Addis Ababa. In 1980s he traveled to USA for further study and came back home in 1991, when the dictator Mengistu rule was overthrown.Since 1991 Eskindir is working in Ethiopia with chief editor to his own  News paper. His News papaer is one of the  highest circulating news paper in the country. Eskindir is also a human rights activist as a result he has been jailed seven times by the former regime of Ethiopia before the reformists came to power in 2018.

Eskindir Nega is a winner of a number of international awards including -


  • 2012 PEN/Barbara Goldsmith Freedom to Write Award
  • 2014 World Association of Newspapers' Golden Pen of Freedom Award
  • 2017 International Press Institute World Press Freedom Hero
  • 2018 Oxfam Novib/PEN Award 

The below video is Eskindier Nega's speech, on the the existence of terrorist command center in USA, for thousands of Ethio-Americans residing in Washington DC and peripherals.





ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Friday, November 22, 2019

ጃዋር አሕመድ አውሮፓን እንዲረግጥ ሊፈቀድለት አይገባም። We care for Europe - UK,Belgium,Sweden,Norway and others must stop Jawar Mohamed from entering to their territory.

(አማርኛ ከእንግሊዝኛ ስር ያንብቡ)

Attention! to Europe - UK, Belgium, Sweden, Norway and other countries.

We care for Europe!

Jawar Mohamed is well known with his hate speeches and extremist position in Ethiopia. Recently he is claimed  and caused for the death of over 80 innocent people in Ethiopia. Next week, Jawar is planning to travel to European countries including UK, Belgium, Sweden and Norway for the purpose of collecting illegal public fund to use for the same hate speeches plus to inject his clashing  project among Ethiopians at home under the cover of ethnicity. Now a days he is challenged even from Oromo ethnics that he propagandized as if he stand for.

This is a notice to European countries to be aware and take the necessary action by stopping Jawar not to enter to Europe. For your detailed information about the mentioned individual, please click and read this link (https://www.gudayachn.com/2019/10/analysis-ja-war-aljazeera-bloodshed-and.html).

We care for Europe.


====================================

ጥላቻን በተሞላ ንግግሮቹ እና በማኅበራዊ ሚድያ ላይ በሚፅፋቸው ህዝብን ከህዝብ በሚያጋጩ ንግግሮቹ ምክንያች የበርካታ ኢትዮጵያንን ሕይወት እንዲቀጠፉ፣ወላጆች ካለ ልጆች፣ልጆችን ከወላጆቻቸው ውጭ እንዲኖሩ ምክንያት የሆነ ሰው ጃዋር መሐመድ ወደ አውሮፓ በመምጣት ለበለጠ ግጭቶች  የሚረዳው  ገንዘብ ለማሰባሰብ ወደ አውሮፓ ቤልጅየም፣ስዊድን፣ኖርዌይ እና እንግሊዝ ጨምሮ ከመጪው ሳምንት ጀምሮ ለመምጣት ማሰቡ ተሰምቷል።

ከእዚህ በፊት በአሜሪካ ሊያደርጋቸው ያሰባቸው ስብሰባዎች በሰብዓዊ መብት ተሟጋች ኢትዮጵያውያን በተቃውሞ አንዳንዶቹ ጋር ተረጋግጦ ስብሰባውን እንዳያደርግ፣በሌላ ቦታ ደግሞ ፈፅሞ ስብሰባውን እንዳያደርግ ማድረግ ችለዋል።በአውሮፓ እና አሜሪካ ማንም የፈለገውን ሃሳብ የመግለጥ እና የመሰብሰብ መብት አለው።ይህ በሕግ የተረጋገጠ መብት ነው። ሆኖም ግን በቅርቡ ብቻ ከ80 በላይ ንፁሃን ሕይወት መቀጠፍ ምክንያት የሆነ ሰው ለበለጠ ጥፋት የሚረዳው ገንዘብ እንዲያሰባስብ  የአውሮፓም ሆነ የአሜሪካ ሕግ አይፈቅድም።ስለሆነም ኢትዮጵያውያን ለአውሮፓ ሕብረት፣ለእንግሊዝ መንግስት እና ለሌሎቹም መንግሥታት ጃዋር የሚሰበስበው ገንዘብም ሆነ ስብሰባ ህገወጥ መሆኑን በቅድምያ ማሳወቅ በመቀጠልም በየትኛውም ቦታ ስብሰባው እንዳይደረግ በተቃውሞም ማስቆም ይገባቸዋል። 


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Wednesday, November 20, 2019

የኢትዮጵያ ወቅታዊው የፖለቲካ ሁኔታ (ጉዳያችን ምጥን)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ 

በእዚህ ፅሁፍ ስር በምጥን መልኩ የሚከተሉት ጉዳዮች ተነስተውበታል።
  • ወቅታዊው የፖለቲካ ትኩሳቱ፣
  • የኢህአዴግ የውሕደት ሂደት መውሰድ የሚገባው  ጥንቃቄ፣
  • የአክራሪ እስልምና ውጪያዊ እንቅስቃሴ ፣
  • የኦሮሞን ሕዝብ ለመረማመጃ የተጠቀመው ፅንፈኛ እንቅስቃሴ የሚቀጥለው እርምጃው  ምንድነው?
  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ 
  • ከፖለቲካ ፓርቲዎች ውጭ የሆነው ብዙሃኑ እና ወሳኙ ሕዝብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እንዴት ተፅኖ ፈጣሪ ይሁን?
**********************
ጉዳያችን /Gudayachn
ህዳር 10/2012 ዓም  (ኖቬምበር 20/2019 ዓም)
**********************
በኢትዮጵያ ፖለቲካ፣የመገናኛ ብዙሃን እና ካላይኛው አመራር በታች ያለው አመራር ጨምሮ የኢትዮጵያ ችግር የሃሳብ የማመንጨት አቅም ማነስ ነው።አዳዲስ ሃሳቦች ለሚገጥሙ ችግሮች ብቻ ሳይሆን የሚገጥሙ ችግሮችን በወጉ መትሮ ሰው በሚረዳው መልኩ የማቅረብ ችግርም ሌላው ችግር ነው።ለእዚህም ነው የሁኔታዎች ቅርፅ አስይዞ የሚተነተንበት ማዕከል ሲጠፋ ክፉ ሃሳብ ያላቸው ባለ ትንንሽ የሃሳብ ክሮች ብዙዎችን ይዘው  ወደፈለጉት የተሳሳተ መንገድ ይዘው የመንገድ ዕድል ያገኛሉ።ስለሆነም በሁኔታዎች ላይ አተያይን በሚገባ ማቅረብ አስፈላጊ ነው።

በእዚህ የጉዳያችን ምጥን ፅሁፍ  የሚከተሉት ሃሳቦች ላይ ጉዳያችን ምጥን ሃሳብ ትሰጣለች። እነርሱም -

  • ወቅታዊው የፖለቲካ ትኩሳቱ፣
  • የኢህአዴግ የውሕደት ሂደት መውሰድ የሚገባው  ጥንቃቄ፣
  • የአክራሪ እስልምና ውጪያዊ እንቅስቃሴ ፣
  • የኦሮሞን ሕዝብ ለመረማመጃ የተጠቀመው ፅንፈኛ እንቅስቃሴ የሚቀጥለው እርምጃው  ምንድነው?
  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ 
  • ከፖለቲካ ፓርቲዎች ውጭ የሆነው ብዙሃኑ እና ወሳኙ ሕዝብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እንዴት ተፅኖ ፈጣሪ ይሁን?
ወቅታዊው  የፖለቲካ ትኩሳቱ 

በአሁኑ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ትኩሳት ውስጥ በዋናነት የመንግስት የሕግ የማስከበር አቅምን የሚገዳደሩ ቡድኖች በእየቦታው እያቆጠቆጡ  ነው።በእዚህም ሳብያ ሕዝብ በዋናነት የፀጥታ እና የሕግ እንዲሁም የፍትህ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ ክፍተት መታየቱ  መጪውን ጊዜ እንዲፈራ ብቻ ሳይሆን አንዳንድ ቦታዎች ሕዝብ እራሱን ለመከላከል የስነ ልቦናም ሆነ የትጥቅ ዝግጅት የሚያደርግበት  ጊዜ ሆኗል።እነኚሁ ህገ ወጦች በዩንቨርስቲዎች ውስጥ ሳይቀር ተማሪዎችን እስከ መረበሽ እና ማጋጨት ይህ አሁን ላለው የፖለቲካ ትኩሳት ዋነኛ መንስኤ ሆኗል። 

የኢህአዴግ የውሕደት ሂደት መውሰድ የሚገባው  ሶስቱ  ጥንቃቄዎች 

ኢህአዴግ ለመዋሃድ ባለፈው ቅዳሜ ህዳር 6/2012 ዓም ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ወስኗል።በእዚህም መሰረት የውሁዱ አዲስ ስም ብልፅግና ፓርቲ  በሚል ስሙን ሰይሟል።የውህደቱ ሃሳብም ሆነ መተግበሩ በሕዝብ ዘንድ ብቻ ሳይሆን ቀድሞ አጋር በሚል ይጠሩ የነበሩት እንደ ሱማሌ እና አፋር ክልሎች በተለየ ደስታ ፈጥሯል።በአንፃሩ የኢትዮጵያዊ ሃሳብ አገንግኖ መውጣቱ ያሰጋቸው የብሔር ፖለቲካ ከኖረ ብቻ እንደሚኖሩ የምይስቡ ኃይሎች ነገሩ አልታማቸውም።

በውህደቱ ሂደት አዲሱ የኢህአዴግ ውሁድ ፓርቲ ሶስት የጥንቃቄ እርምጃ መውሰድ አለበት።የመጀመርያው ጥንቃቄ በክልሎች የነበረ ክልላዊ ስሜት እና በፓርቲው ውሁድ ሂደት ላይ መጋጨት እንዳይኖር በአንፃሩ የክልሎች ጉዳይ አከላለል ላይ ውሳኔ በቶሎ ያስፈልጋል።ይህ ካልሆነ የሁለት የምቃረኑ ሃሳቦችን አንድ ላይ ለማስኬድ የሚደረግ ጥረት እንዳይሆን ያሰጋል። ሁለተኛው ጉዳይ አዲሱ ውሁድ ፓርቲ በብዙ የፍላጎት ቡድኖች (interest groups) ጉተታ ውስጥ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለበት።አንዳንዶች ፓርቲው በአውሮፓ የኢንዱስትሪ አብዮት ጋር ሚና ነበረው በሚሉት የግለኝነት አስተሳሰብ ከፕሮቴስታንት እምነት ጋር የምያገናኙበት ስሜት በብልፅግና ፓርቲ ውስጥም የተወሰኑ ቡድኖች ፍላጎት ማጠንጠኛ እንዳይሆን  እና ከነበረው የኢትዮጵያ ዕሴት ጋር ግጭት ውስጥ እንዳይገባ ከፍተኛ የመርህ፣የዲስፕሊን እና ሁሉን የማቀፍ ሂደት መከተል አለበት። በሶስተኛ ደረጃ ፓርቲው ኢትዮጵያዊ መገለጫው ላይ በግልጥ እና በትኩረት መስራት እና የማንም ባዕዳን አስተሳሰብ  በገንዘብ ኃይልም ሆነ በተፅኖ ብዛት ስር እንዳይወድቅ እራሱን የሚፈትሽበት መንገድ እንዲኖር ሥርዓቶችን በታማኝነት መዘርጋት የሚሉት  ናቸው። 


የአክራሪ እስልምና ውጪያዊ እንቅስቃሴ

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከየትኛውም ክፍል በበለጠ መልክ የአክራሪ እስልምና የትኩረት ቦታ ነች።ለእዚህም ዋነኛ ምክንያት አክራሪ እስልምና ከዓለም ላይ ካሉት አገሮች በቀላሉ  ሊሸገግበት ብቻ ሳይሆን የተወሰኑ የህብረሰብ ክፍሎችን ይዞ በአፍሪካውያን ውስጥ በሚነሱ ቅራኔዎች ሳብያ የራሱን ሥራ መስራት ስለሚፈልግ ነው።ስለሆነም ወደ አፍሪካ በሚያደርገው መስፋፋት ኢትዮጵያን እንደ አንድ ስጋት ይመለከታታል።ለእዚህም ከሃምሳ ሚልዮን በላይ ክርስቲያን መኖርን በመጥቀስ እና የኢትዮጵያ መሬት አቀማመጥ እስከ ሶስት ሺህ ሜትር ከባህር ጠለል በላይ መገኘቱ የመካከለኛውም ምስራቅንም ሆነ ዋነኛውን  የዓለም የንግድ መንቀሳቀሻ የቀይ ባህርን ኢላማ ውስጥ ለማስገባት ብቸኛው አመቺ ቦታ በመሆኑ ነው።

ሰለሆነም በኢትዮጵያ የወቅቱ ፖለቲካዊ ሽግግር ላይ ሂደቱን በሚፈልጉት መንገድ ለመዘወር የሚፈልገው አክራሪ አካል በኢትዮጵያ የምርጫ ሂደት ጭምር ገብቶ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሂደት እንደፈለጉት ለመዘወር ማሰባቸው አይጠረጠርም።በእዚህ በኩል ኢትዮጵያውያን በሚገባ መንቃት እና በትንንሽ ጉዳዮች ከመጠመድ በዋና ዋና እና ስልታዊ ሂደቶች ላይ ማተኮር አስፈላጊ አው። 


የኦሮሞን ሕዝብ ለመረማመጃ የተጠቀመው ፅንፈኛ እንቅስቃሴ የሚቀጥለው እርምጃው  ምንድነው?

የኦሮሞ የብሄርተኝነት ጥያቄ ያነሱ ኃይሎች ላለፈው ግማሽ ክፍለ ዘመን ያራመዱት ፖለቲካ የብሔር ፖለቲካ ብቻ ሳይሆን የአክራሪ እስልምና እንቅስቃሴ ሙከራም ነው።የኦሮምያ እስላሚያ የሚባለው  እንቅስቃሴ እራሱን በተለያዩ የኦነግ አንጃዎች ውስጥ በማስገባት የኦሮሞ የብሔር ጥያቄዎችን ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር በሚያጋጭ መልኩ  ብዙ ስራዎችን ሲሰራ ኖሯል።የእዚሁ ዓላማ አራማጅ የኦኤምኤን ሚድያ በመክፈት ለኦሮሞ ብሔር የቆመ መስሎ የሚታየው  ጃዋር በኦሮሞ ብሄርተኝነት ስም  የሚሄድበት ነዳጅ በቅርቡ እንደሚያልቅበት እና ሌላ ጭንብል ይዞ እንደሚወጣ ይጠበቃል።ጃዋር  መሐመድ ከእዚህ በፊት በአሜሪካ ባደረገው ስብሰባ ላይ አክራሪ እስልምናን ኢትዮጵያ ላይ ለማስፈን የሚሄድበት መንገድ የኦሮሞ ብሄርተኝነት እንደሆነ ኦሮምያ የአክራሪ እስልምና ምቹ መጋለብያ እንደሆነች ''የሜጫ'' ንግግሩ በተሰኘው ንግግሩ መግለጡ አይዘነጋም። 

 የፅንፈኛ ቡድኑ ቀጣይ እርምጃ የሚሆነው ኦሮምያን መከፋፈል እና የራሱ የሆነ የመፈንጫ ቀጠና መመስረት ነው።ለእዚህም እንዲመቸው በመጀመርያ በኦሮምያ የምትገኘውን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ለመክፈል ''ዮሮምያ ቤተ ክህነት'' የሚል ከፋፋይ ቢሮ እንዲከፈት በኦሮምያ ሚድያ ኔት ዎርክ ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ ላይ ይገኛል።  ስለሆነም የፅንፈኛ ቡድኑን ቀጣይ አላማ በተለይ በኦሮምያ ፖለቲካ ላይ እውቀቱ አለን የሚሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባቸዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ 

በኢትዮጵያ የለውጥ ነፋስ በነፈሰባቸው ሂደቶች በሙሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የመጀመርያ ተጠቂ ነች።የውጭ ወራሪ በመጣባቸው የኢትዮያ የፈተና ዘመናት ሁሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ቀዳሚ ዕላማ ሆና ኖራለች።ፋሺሽት ጣልያን በወረራው ጊዜ አይሮፕላኞቹ ቀድመው የሚያጠቁት የቤተ ክርስቲያኒቱን ህንፃ ሲሆን በአምስት ዓመታት ቆይታው የደብረ ሊባኖስ መነኮሳትን እያሰረ ወደ ገደል ከእነ ሕይወታቸው ከመጨመር ባለፈ ፓፓሳቶቿን በአደባባይ እስከመስቀል ያልተፈፀመ የግፍ አይነት የለም።የ1966 ዓም የለውጥ ንፋስ፣የ 1983 ዓም  የመንግስት ለውጥ እና በ2010 ዓም የኢህአዴግ ለውጥ ጊዜ ሁሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ዋነኛ ኢላማ ሆነዋል።

ባሳለፍናቸው ስድስት ወራት ውስጥም በኦሮምያ ክልል በተለየ መልኩ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት እየተቃጠሉ ምእመናንም እየተገደሉ ነው። ሁኔታው በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮያውያን ዘንድ ሁሉ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል።በጉዳዩ ላይ መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ እና ማብራርያ እንዲሰጥ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ አካል ቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ የማህበራት ህብረት ጭምር ጠይቀዋል።በቅርቡም በኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ማኅበረ ቅዱሳን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በቀጥታ ደብዳቤ መፃፉን ማኅበሩ ማስታወቁ ተሰምቷል።ይህ ሁሉ ድምፅ በመንግስት በኩል ተገቢው ምላሽ መሰጠት ያለበት እና የለውጥ ሂደቱን ጤናማ እንዲሆን ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው።ይህ ሁኔታ ኦርቶዶክሳውያንን ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ሂደት የመገለል አዝማምያ እንዲሰማቸው ከማድረጉም በላይ ከፍተኛ ያለመረጋጋት ምክንያት ሊሆን እንደምች ማንም ጥርጥር ሊገባው አይገባም። ምክንያቱም የቤተ ክርስቲያኒቱ ኢትዮጵያን የማረጋጋት አቅም ብቻ ሳይሆን ያለው ጠንካራ ማኅበራዊ አንድነት በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ በሚፈፀመው የጥፋት ሥራ ሳብያ የመናጋት አደጋው ትልቅ ያደርገዋል።ይህንን ደግሞ የፅንፍ ኃይሎች የሚፈልጉት ጉዳይ ነው። 

በኢትዮጵያ የመንግስትነት ታሪክ ከአንድ ሺህ አምስት መቶ አመታት በላይ ነገሥታቱን ህዝቡ የሚቀበላቸው ከቆለኛው የአክራሪ እስልምና የሚያድኑት ከሆነ ብቻ ነው። ይህንን የማያደርጉ ነገስታት ላይ ሕዝብ የመሸፈት እና እራሱን በራሱ የመከላከል ሥራ አይ ብቻ ተግባር ላይ ያተኩራል።አሁንም የሚታየው ከእዚህ ብዙ የራቀ አይደለም።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሕልውናን ለመጠበቅ እና ከፅንፈኛ አካሎች ለመከላከል ትጋት የማያሳይ መንግስትም ሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር በስልጣን ላይ የመቆየት  አቅሙ ፈፅሞ የመነመነ ነው።ይልቁንም በአሁኑ በያዝነው በ21ኛው ክፍለዘመን በተበታተነ መልክ ያለ የሚመስለው የቤተ ክርስቲያኒቱ የሰው ኃይል ብቃት፣ጆግራፍያዊ ስብጥር እና ዓለም አቀፍ አቅም ሁሉ የሚንቁት ጉዳይ አይደለም።ስለሆነም የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ መንግስት በፍጥነት ትኩረት መስጠት የሚገባው ይሄው የቤተ ክርስቲያኒቱን አጥቂዎች ለፍርድ ከማቅረብ እስከ  የመጠበቅ መንግስታዊ ኃላፊነቱን መወጣት ይዋል ይደር የማይባል አንገብጋቢው ጉዳይ ነው። ይህ ካልሆነ ግን የተጠቃ አካል ሁል ጊዜ እራሱን ለመከላከል ከመንቀሳቀሱ አንፃር ጉዳዩ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ የፖለቲካ መልክ የሚቀይር ጉዳይ አይመጣም ማለት ፈፅሞ አይቻልም።

ከፖለቲካ ፓርቲዎች ውጭ የሆነው ብዙሃኑ እና ወሳኙ ሕዝብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እንዴት ተፅኖ ፈጣሪ ይሁን?

አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳይ ተከታታይ እንጂ ዋና ተዋናይ አይደለም።ይህ ደግሞ በሁሉም አገር ያለ ነው።ተዋናዮች ጥቂት ተመልካቾች ግን ብዙዎች ናቸው።ሆኖም ግን በሌሎች አገሮች ያለው ሁኔታ ተመልካቹ በልዩ ልዩ መንገድ ተመልካች ብቻ ሳይሆን ተዋናዮቹ ላይ ተፅኖ አሳዳሪ ነው።በኢትዮጵያ ግን ይህ አይታይም።መሆን የሚገባው ግን ከተመልካችነት ተፅኖ ፈጣሪነት ማደግ አለበት።ተፅኖ  ፈጣሪነቱ በሚድያ፣በሰላማዊ የተቃውሞ መንገድ ሃሳብን በመግለጥ፣ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ በማንቀሳቀስ እና በመከታተል ሁሉ ይገለጣል።

የኢትዮያን ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳይ በተመለከተ ባጭሩ ከላይ የተጠቀሱት ከብዙ በጥቂቱ እና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች እንደሆኑ ጉዳያችን ታምናለች። የፖለቲካው ዋና አንቀሳቃሽ የምጣኔ ሃብቱ ጉአይ በርግጥም በአግባቡ መታየት ያለበት እንደሆነ ይታመናል። 

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Tuesday, November 19, 2019

«ከብላቴ ወታደራዊ ማሰልጠኛ እስከ ዐቢይ አህመድ ቤተ መንግሥት» አዲስ ቃለ መጠይቅ ከሙሐዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤልክብረት

ምንጭ = አደባባይ ሚድያ 
ክፍል አንድ 


  


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Sunday, November 17, 2019

Saturday, November 16, 2019

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ደህንነቷን ለመጠበቅ በፍጥነት መውሰድ የሚገባት ሁለት የመፍትሄ ርምጃዎች (የጉዳያችን ሀሳብ)



ጉዳያችን / Gudayachn
ህዳር 6/2012 ዓም (ኖቬምበር 16/2019 ዓም)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ የለውጥ ነፋስ በነፈሰ ቁጥር የመጀመርያ ኢላማ ስትሆን ኖራለች።በ1966 ዓም የቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ መውረድን ተከትሎ ፓትርያርክ ቲዎፍሎስ በደርግ ተገደሉባት፣በ1983 ዓም ኢህአዴግ አዲስ አበባን መቆጣጠሩን ተከትሎ አቡነ መርቆርዮስ ከመንበረ ፕትርክናቸው ተነስተው እንዲሰደዱ ምክንያት ሆነ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ሲኖዶስ ተከፍላ ቆየች።በ2010 ዓም ከኢህአዴግ ጥገናዊ ለውጥ በኃላ የቤተ ክርስቲያን ሲኖዶሳዊ አንድነት ቢመለስም የቤተ ክርስቲያን መቃጠል፣የምእመናን መገደል እና ስደት በተለይ በኦሮምያ ክልል ተባብሶ ቀጥሏል። ባሳለፍነው አንድ ወር ውስጥ ብቻ በመንግስት የተረጋገጠ ሰማንያ ስድስት ኢትዮጵያውያን በፅንፈኞች መገደላቸው ተገልጧል።

ለውጡን ተከትሎ የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ለማጥቃት መልካም አጋጣሚ ያገኙ የመሰላቸው የፅንፍ ኃይሎች ቤተ ክርስቲያንን ህንፃዋን ከማቃጠል እስከ ምመናኗን መግደል እና ከይዞታቸው መንቀል ድረስ ከፍተኛ ዘመቻ ከፍተዋል።በእዚህም መሰረት ከሲዳማ ዞን እስከ ባሌ፣አርሲ እና ምስራቅ ሐረርጌ ድረስ አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፣ሴት ልጅ ጭምር በድንጋይ ተወግራ ተገድላለች፣አዛውንት በስለት ተገድለዋል። ቅዱስ ሲኖዶስም ተከታታይ የምሕላ ፀሎት ከማወጅ ባለፈ ምዕመናንን ወርደው እስከ ማፅናናት ስራዎች እየሰሩ ነው።

በእነኚህ ሁሉ ፈተናዎች ውስጥ ቤተ ክርስቲያን  አፋጣኝ መፍትሄ መውሰድ የሚገባት በተለይ ከደህንነቷ አጠባበቅ ጋር በተያያዘ ምንድነው የሚለውን ጉዳያችን እንደሚከተለው ሃሳብ ታቀርባለች። ቤተ ክርስቲያን በቅዱስ ሲኖዶስ መመርያ ሰጪነት ሁለት አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ ይገባታል። እነርሱም -

1) የቤተ ክርስቲያን የጥበቃ (የዘበኛ)  ከቤተ ክህነት እስከ አጥብያ  በአዲስ ዲፓርትመንት ማለትም በወታደራዊ ሙያ በሰለጠነ እና ዘመናዊ መሳርያ ትጥቅ ማደራጀት እና  ማዋቀር 

በኢትዮጵያ  በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የሚገኙ መንግስታዊ መስርያ ቤቶች የጥበቃ ዲፓርመንት  ራሱን በቻለ ዲፓርትመንት የሚመራ ነው።ለምሳሌ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በምሳሌነት መውሰድ ይቻልል።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የጥበቃ ክፍል አዲስ አበባ ከሚገኘው ዋናው መስርያ ቤት  እስከ ጫፍ ዶሎ መና ባሌ ያለው የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የጥበቃ ክፍል የሚመራው ራሱን በቻለ ዲፓርትመንት ነው። ይህ ማለት የራሱ በጀት አለው፣በወታደራዊ ሙያ የሰለጠኑ ባለሙያዎች፣የፀጥታ አጠባበቅ መመርያ ሁሉ አለው።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በኩል ስንመለከት ይህ አሰራር ወጥነት ባለው እና በቂ በወታደራዊ ሙያ የሰለጠነ እና በቂ ትጥቅ ያለው የጥበቃ ኃይል የላትም። ይህ ግን በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ነው።ከእዚህ በፊት ቤተ ክርስቲያን  ከላይ በተጠቀሰው ደረጃ የጥበቃ ክፍሏን ያላጠናከረችው  ለሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮች በቀላሉ ለመንግስት የፀጥታ አካላት ለምሳሌ ለፖሊስ በማሳወቅ ችግሮች ይፈታሉ በሚል ነበር።አሁን በሚታየው ተጨባጭ ሁኔታ ግን ፖሊስ እራሱ የፀጥታ ችግር በሆነበት ሁኔታ ቤተ ክርስቲያን የራሷን የጥበቃ ኃይል በፍጥነት ማጠናከር ይጠበቅባታል።

በኢትዮጵያ ሕግ ማንኛውም ግለሰብ ቤት ሆነ የእምነት ድርጅት አጥር ግቢ  ካለፈቃድ መግባት ወንጀል ነው።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ንብረት ለመሆኑ የቤተ ክርስቲያኗን ስም በበበሩ ላይ መፃፍ አንዱ አስፈላጊ ጉዳይ ነው።ፅሁፉ እያለ በር ላይ የሚገኘውን የጥበቃ አካል አልፎ ለመግባት በተለይ በኃይል ለመግባት የሚሞክር ማናቸውም አካል ላይ ጥበቃ በያዘው መሳርያ ከማስጠንቀቅያ  ጋር ቤተ ክርስቲያንን ለመከላከል ማናቸውንም እርምጃ የመውሰድ ሕጋዊ መብት አለው።ስለሆነም ቤተ ክርስቲያን የጥበቃ ኃይሏን መብታቸው እና ግዴታቸውን ማሳወቅ አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን።ከጥበቃ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን  ለምታደርገው የጥበቃ አካላት ስልጠና እና የትጥቅ ማሟላት ሂደት ሁሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ ይገባዋል። ለምሳሌ የተቀጠሩትን የጥበቃ አካላት ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ ላይ እና ከኃላ ቀር መሳርያ ቢያንስ በክላሽ ደረጃ የታጠቁ የጥበቃ ኃይል እያንዳንዱ አጥብያ ከከተማ እስከ ገጠር እንዲኖር ለማድረግ መንግስት ሕጋዊ ስልጣኑን እና ትጥቅ በግዥም የማቅረብ ሥራ መስራት አለበት።ይህ ሥራ በራሱ የመንግስትን ሥራ በተለይ በፀጥታ በኩል የሚያቀልለት ሥራ መሆኑ እሙን ነው።እዚህ ላይ ቤተ ክርስቲያን የጥበቃ ስራውን እራሷ ባደራጀችው ሕጋዊ በሆነ የጥበቃ አካል እንጂ ቤተ ክርስቲያን አንዳንድ ድርጅቶች እንደሚያደርጉት ለጥበቃ ኤጀንሲዎች ስራውን ለመስጠት ከሞከረች ትልቅ ችግር ቤትክርስትያን ላይ ሊያስከትል ይችላል።ኤጀንሲዎች ተፈላጊ እንዲሆኑ እራሳቸው የፀጥታ ችግር የሚሆኑበት አጋጣሚ በብዙ አገሮች የታየ ነው።ስለሆነም ቤተ ክርስቲያን በጥንቃቄ በራሷ ልጆች ልፀራው የሚገባ ሥራ ነው።

የጥበቃ ክፍልን (ድፓርትመንት) ቤተ ክርስቲያን በአጭር ጊዜ ለማደራጀት የሚከተሉትን ተግባራት በቶሎ መስራት ትችላለች። እነርሱም -

  • የጥበቃ ክፍሉን በአገር አቀፍ ደረጃ ማዕከላዊ አደረጃጀት እንዲኖረው ማድረግ፣
  • ክፍሉ በአገረ ስብከት እስከ አጥብያ የሚወርድ ወጥ የሆነ አሰራር፣አጠባበቅ፣የስልጠና አቅም እና የመሳርያ ትጥቅ ማሟላት፣
  • የጥበቃ ክፍሉ በተለይ በማዘዣው በቤተ ክህነት ደረጃ ያለው የጥበቃ ዋና ክፍል በአገረ ስብከት ደረጃ እና እስከ አጥብያ ድረስ ያለውን የጥበቃ  ሁኔታ ለመከታተል እንዲረዳ ቢያንስ በኮለኔል ደረጃ የሚመራ ይሆናል፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጅች የሆኑ ነገር ግን በወታደራዊ ስልጠናም ሆነ ስነምግባር የተመሰገኑ መሆን ይገባቸዋል፣
  • የጥበቃ ዲፓርትመንት በአገሪቱ ውስጥ ያሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ አጥብያዎች ስጋት የተደቀነባቸውን እና ቅድምያ ትኩረት የሚሹትን አካባቢዎች ይለያል፣ መረጃ ይተነትናል አስፈላጊ ሲሆን መንግስት ትኩረት እንዲሰጥ የቅድመ አደጋ ጥንቃቄ ማስጠንቀቅያ ይሰጣል፣
  • የጥበቃ ክፍል ከኢትዮጵያ ቴሌኮምኒኬሽን ፈቃድ ያለው የራሱ የመገናኛ ራድዮ መገናኛ ይኖረዋል።በእዚህም መሰረት በአገረ ስብከት ደረጃ እስከ አጥብያ ያለው ጥበቃ ድረስ የሚገናኝበት በመንግስት ፈቃድ ያለው የራድዮ መገናኛ መስመር ይዘረጋል።
  • የጥበቃ ክፍሉ መተዳደርያ ደንቡ በቅዱስ ሲኖዶስ ፀድቆ ሥራ ላይ ሊውል ይችላል።

2) የአይቲ (ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ) ክፍል በመምርያ ደረጃ መመስረት  

አሁን ባለንበት ዓለም አይደለም ከሃምሳ ሚልዮን በላይ ሕዝብ በስሩ የያዘች እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ያለ ትልቅ አደረጃጀት ያላት አገራዊ  አካል ቀርቶ ትንንሽ ድርጅቶችም ከአይቲ (የኢንፎርሜሻን ቴክኖሎጂ) ክፍል በመምርያ ደረጃ በቤተ ክህነት መመስረት እና ክፍሉ ከአገረ ስብከት እስከ አጥብያ ድረስ በኔት ዎርክ ማያያዝ በፍጥነት መሰራት የሚችል ሥራ ነው። የአይቲ ኔትዎርክ መመስረት በጣም ውስብስብ ሥራ እና የማይቻል አድርጎ ማሰብ አይቻልም። 

ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ ሁለት ሀብት አላት።አንዱ የሰለጠነ እና የተማረ የሰው ኃይል ሲሆን ሌላው የገንዘብ አቅም ነው። ስለሆነም የአይቲ መረቡን መዘርጋት በቤተ ክህነት ደረጃ ቅዱስ ሲኖዶስ በፍጥነት መመርያ ቢሰጥበት  ስራውን የሚከታተል ልዩ ኮሚቴ ሰይማ ስራውን የሚሰሩ በአገር ውስጥ ወይንም በውጭ የታወቁ ኩባንያዎች በጨረታ ስራውን መስጠት ትችላለች።የኔትዎርኩ ሥራ በአንዴ ሁሉም ጋር ባይደርስ ደረጃ በደረጃ ለመስራት ስራውን መጀመር ግን ጊዜ የሚሰጠው አይደለም።የአይቲ መምርያ ማስቀመጥ እና አሰራርን በአይቲ አስደግፎ መስራት ከቤተ ክርስቲያኒቱ የፀጥታ ሥራ ጋር አብፎ የሚታይ ብቻ ሳይሆን መጪውን የዋጀ አሰራር የመዘርጋት ተግባር አካል ነው።የአይቲ መምርያ መስርቶ እስከ አጥብያ ድረስ ስራውን መተግበር ለቤተክርስቲያን  የሚከተሉትን ጥቅሞች ይሰጣል። እነርሱም -


  • የቤተ ክርስቲያን የገንዘብ አጠቃቀም፣የአጥብያ ሁኔታ፣ውሎ እና ተግባራት በቀጥታ በደቀቃዎች ውስጥ ሪፖርት ለአገረ ስብከት እና ለቤተ ክህነት ለመላክ ይረዳል፣
  • በእርቀት የሚገኝ አጥብያ የፀጥታ ስጋት ቢኖርበት በደቂቃዎች ውስጥ ለሚመለከተው ሁሉ ለመግለጥ አመቺ ሁኔታ ይፈጥራል፣ 
  • ከአገር ውስጥ እስከ ውጭ ያሉ አጥብያዎች በኔት ዎርክ እንዲገናኙ ያደርጋል፣
  • ወጥ የሆነ የእቅድ ፎርማት ለመላክ ለሁሉም አጥብያዎች ማድረስ ይቻላል፣
  • አጥብያዎች ወጥ የሆነ እቅድ ትግበራ ሪፖርት እንዲልኩ እና በአገረ ስብከት እና በቤተ ክህነት ደረጃ እንዲገመገም ይረዳል፣
  • ቤተ ክርስቲያን ያላትን የሰው ኃይል፣የገንዘብ እና የማይንቀሳቀስ ንብረት በሚገባ መዝግባ ለመያዝ እና የንብረቷን ሁኔታ ለመቆጣጠር  ይረዳታል፣
  • እያንዳንዱ አጥብያ በሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መዋቅር ውስጥ የአይቲ ክፍል እንዲኖረው ቃለ አዋዲው ማሻሻያ እንዲደረግበት ይረዳል። 


ለማጠቃለል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አሁን የገጠማትን የፀጥታ ችግር ከላይ በተጠቀሱት ሁለት መንገዶች ችግሩን በዘለቄታው ለመፍታት የሚያስችላት እንደሚሆን አምናለሁ።በተለይ የጥበቃ ክፍሉ በዲፓርትመንት (መምርያ) ደረጃ ስትመሰርት በርካታ የበጎ ፍቃድ አገልጋዮች ማንቀሳቀስ የምትችልበት ዕድል አላት።በጎ ፍቃድ የጥበቃ አካላት ለማንቀሳቀስ ግን ራሱን የቻለ ጉዳዩን የሚከታተል እና በወታደራዊ ሙያ የሰለጠነ አስተባባሪ ያስፈልጋል። በእዚህ ደረጃ የተጠናከረች ቤተ ክርስቲያንን እሳትና ጎመድ ይዞ ለሚመጣ ፅንፈኛ ከጥበቃ ክፍሉ የሚሰጠውን ምላሽ ስለሚረዳ በቀላሉ አንድ አጥብያ ለማጥቃት አይደፋፈርም። ምክንያቱም  የሁሉም አጥብያ ጥበቃዎች የቤተ ክርስቲያኑን አጥር ጥሶ የሚመጣ ማንኛውም አካል ላይ የመተኮስ እና ቤተ ክርስቲያኑን የመከላከል ሕጋዊ ስልጣን ስለሚኖረው ፅንፈኛም አደብ እንዲገዛ ያስገድደዋል። በሌላ በኩል የጥበቃ ክፍሉ አንዱ አጥብያ ላይ ችግር ካለ ሌላ አካባቢ ያሉ አጥብያ የጥበቃ አካላት በራድዮ መገናኛ ተጠቅመው ችግሩ ያለበት አጥብያ  በፍጥነት የሚደርሱበት ዕድል አለ።

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Wednesday, November 13, 2019

ከዲሞክራሲ በፊት ፍትህ እንፈልጋለን! ዲ/ን ዳንኤል ክብረት



ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Monday, November 11, 2019

የኢህአዴግ ውሕደት ላይ ያተኮረው የድርጅቱ ወሳኝ ስብሰባ የፊታችን ሮብ ይጀመራል።ውህደቱ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ወደ አንድ ምዕራፍ እንዲያሸጋግር ጉጉታችን ነው።ህወሓት በውህደቱ ከመሳተፍ ሌላ ምንም ምርጫ እንደሌለው ሶስት ምክንያቶች አሉ።

ጉዳያችን /Gudayachn
ሕዳር 1/2012 ዓም (ኖቬምበር 11/2019 ዓም)

ኢህአዴግ ቀድም ብሎ በሐዋሳ ላይ በወሰነው ውሳኔ መሰረት በውሕደቱ ላይ ያተኮረው ጉባኤውን ለማካሄድ በመጪው ሮብ ለስብሰባ ይቀመጣል።እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት በውህደቱ ላይ የተስማሙ የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) ፣የዓማራ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ዓዴፓ) እና የደቡብ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ደሕዴድ)  ሲሆኑ ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ግልጥ ውሳኔውን አላሳወቀም።ሆኖም ቀደም ብሎ ድርጅቱ ባወጣቸው መግለጫዎች ውህደቱን እንደሚቃወም አስታውቆ ነበር። በሌላ በኩል ህወሓት በውህደቱ ባይሳተፍ ይህ የድርጅት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሕዝብ ጉዳይ ስለሆነ ሌሎች የትግራይ ክልልን ወክለው በውህደቱ ሂደት ላይ ለመሳተፍ  የሚፈልጉ እንዳሉ ከአዲስ አበባ የሚሰሙ ዜናዎች አሉ።

ኢህአዴግ ወደ ውህደት ስመጣ ከእዚህ በፊት በኢትዮጵያ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ የጎላ ድርሻ ያልነበራቸው ማለትም በአጋርነት ብቻ ሲጠሩ የነበሩ የሐረሪ፣የቤንሻንጉል፣የጋምቤላ፣የአፋር እና የሱማሌ ድርጅቶች በአሁኑ የኢህአዴግ ውህደት ላይ ለመሳተፍ  ስምምነታቸውን መግለጣቸው ለማወቅ ተችሏል።ሆኖም ግን በውህደቱ የውሳኔ ድምፅ መስጠት ላይ ወሳኞቹ አራቱ ድርጅቶች ማለትም ኦዴፓ፣አዴፓ፣ህወሓት እና ድህዴድ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።ከውሳኔው በኃላ ግን አጋር ድርጅቶች የውሕደት ጥያቄያቸው ወዲያውኑ ተቀባይነት እንደሚኖረው እና ውሕደቱ እንደሚከናወን ይታመናል።

ህወሓት በውህደቱ ከመሳተፍ ሌላ ምንም አይነት ምርጫ የለውም 

ይህ በእንዲህ እያለ ህወሓት በእዚህ ውህደት ላይ ከመሳተፍ ሌላ ምንም አይነት አምራጭ እንደሌለው በሶስት ምክንያቶች ማወቅ ይቻላል።እነኝህ ምክንያቶችም -

1ኛ) የትግራይ ምሁራን እና የንግዱ ማኅበረሰብ ውሕደቱን ስለሚደግፍ


የትግራይ ምሁራን እና  በተለይ ላለፉት 27 ዓመታት ከፍተኛ ሀብት ያገኘው የትግራይ ባለሀብት አሁን የሚፈልገው በየትኛውም ቦታ አድልዎ ሳይደረግበት ካፒታሉን ማፍሰስ እና መስራት ነው።ሌላው ምክንያት አሁንም ከፍተኛው ሀብት ያለው በአዲስ አበባ እና በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍል ከመሆኑ አንፃር (በተለይ የማይንቀሳቀሰው ሀብት) ውህደቱን በከፍተኛ ደረጃ ይደግፋል። ህወሓት ውህደቱን ተቃውማ ብትቆም የመጀመርያ ጠብ ያለባት ከእዝህኛው የህብረተሰብ ክፍል ጋር ነው።

2ኛ) ህወሓት በሌላ የፖለቲካ ድርጅት የመተካት ዕጣ ሊገጥማት ስለሚችል

ህወሓት የኢህአዴግን ውህደት አልቀበልም ብትል ለተወሰነ ጊዜ ከማኩረፍ እና የተወሰኑ ችግሮች ለመፍጠር ከመሞከር ባለፈ በዘለቄታው ግን ሕወሃትን የሚቃረን የፖለቲካ ድርጅት በቀጥታ ወደ ውህደቱ የትግራይን ሕዝብ ወክሎ ሊቀላቀል ይችላል። ይህ ማለት ከአረና ትግራይ ጀምሮ ሌሎች አዳዲስ ድርጅቶች መፈጠራቸው ስለማይቀር ህወሓት በውህደቱ ባለመሳተፍ ትግራይ የነበራትን የፖለቲካ እና ማኅበራዊ መሰረት የማጣት ዕጣ ሊገጥማት ስለሚችል ከመዋሃድ ሌላ አማራጭ የለም።

3ኛ) ውህደቱ በራሱ ለሕወሀት ጥቅም ስላለው 

ህወሓት ከኢህአዴግ ውህደት ተጠቃሚ እንጂ ተጎጂ አይደለችም።ህወሓት የበላይ በሆነችበት ኢህአዴግ ውስጥ ውህደት ላይጠቅማት ይችላል።አሁን ግን የበላይነት በሌለበት የፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ህወሓት በውህደት ውስጥ በመሆን ቢያንስ ትግራይ ያላትን  የበላይነት በምርጫው ወቅት አስጠብቆ ሌላ አመቺ ጊዜ መጠበቅ ብቸኛው አማራጭ ነው።ስለሆነም  ውህደቱን ከመቀበል ውጪ አማራጭ የጥቅም ሜዳ ሊኖራት አይችልም።


ስለሆነም ውህደቱ ሙሉ በሙሉ የሚሳካ እንደሚሆን ከወዲሁ ማወቅ ይቻላል።

በመጨረሻም የኦሮሞ የፅንፍ ኃይሎች ይህንን ውህደት በመቃወም አንዳንድ መግለጫ ሲሰጡ እንደሰነበቱ ይታወሳል።ሆኖም ግን ይህ ውህደት አንዱ ይዞ የሚመጣው ጉዳይ  የፅንፍ የኦሮሞ ድርጅቶችን ለብቻቸው የመነጠል መልካም የአደጋ ዕድል ይዞላቸው ይመጣል። ለእዚህም ነው ውህደቱን የፈድራሊዝም ጠላት እንደሆነ ለመለፈፍ ሲሞከር የከረመው። በእርግጥ ውህደቱ በርካታ ጥያቄዎች የሉትም ማለት አይደለም። ለምሳሌ ከውህደቱ በኃላ ሌላ የተረኝነት ወይንም አንዱ የበላይ የሚሆንበት ሂደት እንዳይከሰት የሚወሰዱ ምን እርምጃዎች አሉ? ውህደቱ ፍፁም ውህደት ካልሆነ እና የጎሳ አደረጃጀችን ካላጠፋ መልሶ የጎሳ ስሜትን እንዳይፈጥር እንዴት መከላከል ይቻላል? እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች መመለስ ያስፈልጋል። በሌላ በኩል እነኝህ ጥያቄዎች የሚወሰኑት በክልሎች አከላል ዙርያ ያለው ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚነሳ ጥያቄ እንደሚሆን ይታመናል። ለሁሉም ግን የኢህአዴግ ውህደት የህዝብ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ፖለቲካ ወደ አንድ ምዕራፍ እንዲያሸጋግር ጉጉታችን ነው።

ድምፃዊ አብርሐም ገብረመድሕን ''አገሬ''



ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።