ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, May 31, 2015

ሰበር ዜና - በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በፓትሪያርኩ ፅሕፈት ቤት እና የሰንበት ት/ቤቶች ሀገር አቀፍ አንድነት ዓመታዊ ጉባኤ መካከል ከፍተኛ ውጥረት ተፈጥሯል።የፓትርያርኩን ዳተኝነት በማጋለጥ ፍትሕን የሚጠይቁ የዐደባባይ ሰላማዊ ሰልፎች ይካሔዳሉ

4ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊዎች በከፊል 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአንድ በኩል በፓትርያሪኩ እና በሙስና እና ሃይማኖት ቅሰጣ  የተሰማሩ ግለሰቦች በሌላ በኩል ሙስናንና የሃይማኖት ቀሳጮችን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ለመንቀል በቆረጡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ መካከል ያለው ውጥረት ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደደረሰ በጉዳዩ ላይ ተከታታይ መረጃ የሰጠው ''ሐራ ተዋህዶ'' የተሰኘው ድረ-ገፅ  ሰሞኑን በተከታታይ ባወጣው ዘገባ አስታወቀ።

በተለይ ዛሬ ግንቦት 23/2007 ዓም 4ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ባለ 18 ነጥቦች የአቋም መግለጫ በማውጣት መጠናቀቁን እና አቡነ ማትያስን ለማነጋገር በጉባኤው የተወከሉ አባቶች እና ተሳታፊዎች ላይ ፓትሪያርኩ በር መዝጋታቸውን ዘግቧል።በድረ-ገፁ ላይ ከወጡትን ዘገባዎች ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል።
  • ፓትርያርኩ ጠቅላላ ጉባኤው በላካቸው ብፁዓን አባቶች እና ተሳታፊዎች ላይ በራቸውን ዘጉ
  • የፓትርያርኩን ዳተኝነት በማጋለጥ ፍትሕን የሚጠይቁ የዐደባባይ ሰላማዊ ሰልፎች ይካሔዳሉ
  • በአማሳኞች እና በተሐድሶ መናፍቃን ላይ የሚደረገው ተጋድሎ በየአጥቢያዎቹ ይቀጣጠላል
  • ማስረጃ የተገኘባቸውን አማሳኞች በአገሪቱ ሕግ ለመጠየቅ የባለሞያዎች ቡድን ተቋቁሟል
፬ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ባለ18 ነጥቦች የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፤ ከመግለጫው ነጥቦች ውስጥ የሚከተሉት ይገኛሉ፡-
  • በአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የቀረበው ጥያቄ የኹሉም አህጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤያት የጋራ አቋም በመኾኑ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጠው ተጠይቋል፤
  • የቤተ ክርስቲያን ሀብት እና ንብረት ለግል ጥቅማቸው በማዋል የቤተ ክርስቲያንን አቅም የሚያዳክሙ አማሳኞች ማስረጃ ተጠናቅሮ በአገሪቱ ሕግ መሠረት ለፍርድ እንዲቀርቡ ተጠይቋል፤ 
  • አንዳንድ የገዳማት እና አድባራት ሓላፊዎች ‹‹የተሳሳተ አመክንዮ›› ሳቢያ በሰንበት ት/ቤቶች ላይ እየደረሰ ያለው እስር፣ እንግልት እና ወከባ እንዲቆም ተጠይቋል፤
  • የመንግሥት የፍትሕ አካላት ከአጥፊዎች ጋራ በመተባበር የሰንበት ት/ቤት አባላትን ከማሰር እና ከማንገላት እንዲቆጠቡ ይደረግ ዘንድ ተጠይቋል፤
  • በቤተ ክርስቲያን ተልእኮ አፈጻጸም ላይ ተጽዕኖ እየፈጠረ ያለውን የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ለማጋለጥ ከሀገር አቀፍ አንድነት እስከ አጥቢያ ማስረጃ የማሰባሰቡ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል፤
  • ማስረጃ በቀረበባቸው ላይ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እንዲሰጥ እና ውሳኔውንም ተግባራዊ ለማድረግ ኹሉም የቤተ ክርስቲያን አካላት አስፈላጊውን ርምጃ እንዲወስዱ ተጠይቋል፤
  •        ከ25 በላይ አማሳኝ የአድባራት አለቆች እና ጸሐፊዎች ላይ በቂ ማስረጃዎች ተሰብስበዋል
  •       የተሐድሶ አራማጅ ሰባክያንን የሚጋብዙ አለቆችና የስብከተ ወንጌል ሓላፊዎች ተለይተዋል
  •       የደብረ ናዝሬት ቅ/ዮሴፍ፣ የመካነ ሰማዕት ቅ/ቂርቆስ እና ጃቲ ኪዳነ ምሕረት ተጠቅሰዋ
  •       የሀ/ስብከቱ ሥ/አስኪያጅ የሰንበት ት/ቤቶቹን አመራሮች ‹‹እኔ ራሴ አሳስራችኋለኹ››             አሏቸው
  •      ‹‹እንቅስቃሴው ይቀጥላል፤ የመላው የአ/አ ሰንበት ት/ቤቶች እና የአንድነቱ የጸና አቋም ነው››
በድረ-ገፁ ላይ ተከታታይ መረጃዎች አሁንም እይተለቀቁ ሲሆን ስለ ጉባኤው ዝርዝር ለማንበብ ይህንን  ይጫኑ  



ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ግንቦት 24/2007 ዓም (ጁን 1/2015) 

Thursday, May 28, 2015

የዛሬ 24 ዓመት ኢህአዴግ አዲስ አበባን ባይቆጣጠር ኖሮ ዛሬ የኢትዮያ እድገት ከብራዚል ጋር ይስተካከል ነበር።(የጉዳያችን ማስታወሻ)


====================================
ደርግ 17 ዓመታት ሙሉ በህወሓት እና ሻብያ የተከፈተውን ጦርነት ሲዋጋ እንደነበር እና ጦርነቱ በቀን ብቻ በሚልዮን የሚቆጠር ብር ያስወጣ ነበር።በመቶሺዎች የሚቆጠር ሰራዊት መግቦ፣ታንክ እና ብረት ለበስ ተሽከርካሪ ነዳጅ 
እና ግዥ ፈፅሞ ማደር በራሱ ከፍተኛ ወጪ ነበር።ይህ ገንዘብ እንዳሁኑ የእርዳታ እና የብድር ገንዘብ ሳይሆን ህዝቡ ለእናት ሀገር እያለ ከሚያዋጣው እንደነበር ይታወቃል።በእርግጥ የሩስያ እርዳታ እና ብድር እንዳለ ሆኖ።

በአንድ ወቅት ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማርይም የሰሜኑ ጦርነት ባይኖር በጥቂት አመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምዕራብ እስከ ምስራቅ በባቡር ማገናኘት በተቻለ ነበር።ሲሉ መደመጣቸው ይታወሳል።በተለይ ህወሓት በዋነኛነት ድልድዮች እና መንገዶችን ማፍረስ ስራዬ ብሎ ይዞ ስለነበር እነርሱን ተከታትሎ መጠገን ሌላው ሥራ ነበር።የመከላከያ ኮንስትራክሽን ድርጅት (መኮድ) የተሰኘው ድርጅት አንዱ ስራው ህወሓት ያፈረሰውን 
ድልድይ እና መንገድ መልሶ መጠገን ነበር።

በደርግ የመጨረሻ አመታት ታድያ ኮ/ል መንግስቱ የመንግስታቸውን ቅርፅ ለመቀየር ወስነው ነበር።ቅይጥ ኢኮኖሚ ታወጀ።ሚኒስትሮች በአዲስ መልክ ተሾሙ።ብዙዎቹ በምዕራብ ዓለም የተማሩ ነበሩ።ኢኮኖሚውም ሆነ ፖለቲካው ለቀቅ ያለ መስሎ ነበር።በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው የመመለስ ዕድል እንዳላቸው ምህረት እንደሚደረገም ተወራ።ፕሮፌሠር መስፍን ወ/ማርያምን ጨምሮ ሌሎች ምሁራን ከአመታት በኃላ እንደገና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን የማናገር፣በሀገሪቱ መፃኢ ዕድል ላይ የመነጋገር ዕድል አገኙ።

በወቅቱ በተያዘው መልክ የሀገሪቱ ሰላም ቢረጋጋ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ የህወሃትን የጎሳ ፖለቲካ እና የሻብያ ኤርትራን የመገንጠል አጀንዳ እንደመጥላቱ በነበረው ሕብረት ቢቀጥል ኖሮ፣በውጭ ይኖር የነበረው ሕብረተሰብ ወደሀገር ቤት ገብቶ የመስራት፣በሀገር ውስጥ ያለው ካለ ምንም የጎሳ ክፍፍል የመስራት እና ትላልቅ ኩባንያዎችን የመመስረት እድሉ ሰፊ ነበር። ዛሬ ኤፈርት እና ጥቂት ባለ ሀብቶች የሃገሩትን ሀብት ሁሉ እንዲህ ጠቅልለው ሚልዮን ኢትዮጵያውያን በድህነት ውስጥ አይዳክሩም ነበር።

አሁንም በተጀመሩ የሽግግር ሂደት ደርግ ስልጣኑን ቢለቅ እና የሽግግር መንግስት ተመስርቶ ቀጥሎም ወደ እውነተኛ ምርጫ ኢትዮጵያ ሄዳ የእራሷ የሆነ መንግስት ቢኖራት ኖሮ ዛሬ ከ 24 ዓመታት በኃላ ኢትዮጵያ ካለምንም ጥርጥር ብራዚል ከደረሰችበት የእድገት ደረጃ የመድረስ ዕድል ነበራት።እዚህ ላይ ብራዚል ቀደም ብላ በውጭ ኃይሎች የመገዛቷ እና በርካታ የባህል ተቃርኖ ቢኖርም እኛ ካለን የባህል ሀብት ጋር በምጣኔ ሀብት ደረጃ እና በፈጠራ እንዲሁም በአዲስ ቴክኖሎጂ ክህሎት ሁሉ በእጅጉ የምንራመድበት የመነቃቃት አመታት ነበሩ።በእነኝህ 24 አመታት ውስጥ ከተባለው ደረጃ ለመድረስ እንችል እንደነበር እንደማሳያ የምረዳኝን  ኢትዮጵያ ሊኖሯት እና ላይኖሯት የሚችሉት ነገሮች ሁለት ክፍል ከፍዬ ለማሳየት እና እነኝህ ጉዳዮች ማለትም ኢትዮጵያ ሊኖሯት የሚችሉት ነገሮች ምን ያህል ወደፊት እንደሚያራምዱን እና ላይኖሩ የሚችሉት ደግሞ ምን ያህል ወደኃላ እንደወሰዱን ለመመልከት ይረዳናል።እነኝህን ነጥቦች ለመንደርደርያ አነሳሁ እንጂ ጠለቅ ያለ ጥናት ቢደረግ ብዙ ጉዳዮችን ሊያሳየን እንደሚችል መረዳት ይቻላል።

ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ዓመታት ውስጥ ሊኖሯት የሚችሉት 

 1/ የባንክ ኢንዱስትሪያችን ቢያንስ በ 5 የአፍሪካ ሁለት የመካከለኛው ምስራቅ እና አንድ አውሮፓ እንዲሁም 3 በአሜሪካ ቅርንጫፍ ከፍተው ግዙፍ የፋይናንስ ተቋም በሆኑ ነበር፣

2/ እነ ጣና በለስ የመስኖ ልማት በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ ሞደል የተባለ ምርቶቹ ከኢትዮጵያ አልፈው ለመላው ዓለም የሚልክ በአውሮፓ የስቶክ ኤክስቸንጅ ገበያ የሚገባ ኩባንያ ይሆን ነበር፣

3/ ኢትዮጵያ ከሻብያ ጋር በኤርትራ ጉዳይ ባትግባባ ቢያንስ በአሰብ ጉዳይ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተደራድራ ወደቧን ታስከብር ነበር።በሌላ በኩል እንደ ህወሓት በመሃል ሀገር የሚኖሩ ትውልደ ኤርትራውያንን ከሀገር ስለማታስወጣ በሂደት እነኝሁ ትውልደ ኤርትራውያን የኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር አብሮ መኖር ሽንጣቸውን ገትረው የሚከራከሩ በሆኑ ነበር።እዚህ ላይ በደርግ ዘመን ከፍተኛ ተደማጭ የነበሩ የኤርትራ ቆላው ተወካዮች የነበራቸውን ተሰሚነት ማሰብ ይገባል።እነኝህ ሁሉ በህወሓት ስሳደዱ እና ሲገፉ 24 ዓመታት ተቆጠሩ።

4/ ኢትዮጵያ የመከላከያ ኃይሏ ጠንካራ ስለነበር በደቡብ ሱዳን ጉዳይም ሆነ የሱማልያ አልሸባብ ፈፅሞ ስጋት ሊሆኑ አይችሉም ይልቁንም በአካባቢው ሃያል ሀገርነቷ እስከ ግብፅ እና መካከለኛው ምስራቅ ድረስ ይናኝ ነበር።የአይኤስ ኤስ ጥቃት መፈፀሙ በተሰማ በ24 ሰዓታት ውስጥ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከደብረ ዘይት ተነስተው የሱዳንን የአየር ክልል ጥሰው በርካታ የአሸባሪው ይዞታዎችን ሊብያ ውስጥ ያጠቁ ነበር።በእዚህም ሌሎች ተቀናቃኝ ሀገሮችን ሊያስደምም ይችል ነበር።

5/ በጦርነት ውስጥ የነበረ ኢኮኖሚ ያንን ያህል የስራ ዕድል ለወጣቱ መፍጠር ከቻለ ከጦርነት በኃላ ላለፉት 24 ዓመታት ውስጥ ቢያንስ ከ አስር ያላነሱ ከባድ የብረት ኢንዱስትሪዎች፣የነዳጅ ማውጣት ሥራ (ሱዳን ባቅሟ ነዳጅ ስታወጣ ኢትዮጵያ በሙስና ያልባለገ መንግስት ቢኖራት ኖሮ እስካሁን የነዳጅ ምርት በጀመረን ነበር)፣ 

6/ በኢትዮጵያ ተጀምረው የነበሩት የመካናይዝድ እርሻ ልማቶች በሰፊ ይስፋፉ ነበር።ኢትዮጵያ ጤፍ በብዛት በማምረት ለዓለም ብቸኛ አምራች እና ላኪ ሀገር ትሆን ነበር።

7/ የበርካታ ሃገራት ትላልቅ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መዋለ ንዋይ ለማፍሰስ ይጎርፉ ነበር።በተለይ ደርግ የወደቀበት ወቅት የምስራቅ አውሮፓ ሃገራት ገና ከሩስያ ተፅኖ እየወጡ፣በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም እየተነቃቁ ስለነበር ከወቅቱ ጋር የሚሄድ የድርጊት መርሃ ግብር እና ከሙስና በተቻለ መጠን የፀዳ መንግስት ስለሚኖር ኩባንያዎቹ ከማንም የአፍሪካ ሃገራት ኢትዮጵያን እንደሚመርጡ ሳይታለም የተፈታ ነበር።ይህም ባለፉት 24 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ ከብራዚል እኩል የምትጠራ ሀገር ትሆን ነበር።

8/ ናዝሬት የተጀመረው የትራክተር መገጣጠምያ ፋብሪካ ምርቱን አሻሽሎ በሌሎች ቦታዎች ማምረት እና የኢትዮጵያን ገበሬ በከፊልም ቢሆን ከበሬ አስተራረስ ዘዴ እንወጣ ነበር።

9/ ወላጆቻቸው የሞቱባቸው ማሳደጊያ እና መንከባከቢያ ማዕከል ''ሕፃናት አምባ'' በሁሉም ክፍለ ሀገሮች ተመስርቶ እናት አባት የሞቱባቸውን በተለይ ባለፉት 24 ዓመታት ቁጥራቸው በመቶ ሺዎች የሆኑትን ሕፃናት ወደ ማዕከሉ አስገብቶ ኃላፊነት የሚሰማቸው ትውልድ ማፍራት ይቻል ነበር።የማዕከሉም አስተዳደር በባለሥልጣን ደረጃ ተዋቅሮ ኢትዮጵያውያን በወር ከደሞዛቸው እያዋጡ በርካታ እናት አባት ያጡ ሕፃናትን ሕይወት መታደግ ይቻል ነበር።ኢህአዴግ ማዕከሉ የነበሩ ሕፃናትን የደርግ ልጆች ብሎ በምሽት እንዳባረራቸው እና ማዕከሉን አንዴ የካድሬ ማሰልጠኛ ሌላ ጊዜ የግብርና ማሰልጠኛ እያደረገው መሆኑ ይታወቃል።


ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ዓመታት ውስጥ ላይኖሯት  (ላይሆንባት) የሚችሉት 

1/ ሀገሪቱ በጫት እንዲህ አትበከልም ነበር።ወጣቶቿ በስፖርት እና በልዩ ልዩ ሙያ ላይ እንጂ የጫት ተገዢ አይሆኑም ነበር፣

2/ ከሶስት መቶ ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችን ወደ መካከለኛው ምስራቅ ለግዳጅ ሥራ አይጋዙም ነበር፣

3/ የጣና በለስ ፕሮጀክት አይፈርስም ነበር፣

4/ ኢትዮጵያ የባህር በር የሌላት ሀገር አትሆንም ነበር፣

5/ ኢትዮጵያ በጎሳ የተደራጀ ፓርቲ አይኖራትም ነበር።ሀገሩም በጎሳ የተከፋፈለ አስተዳደር አይኖራትም ነበር።
6/ ኢትዮጵያውያን ጎሳቸው ሳይሆን ኢትዮጵያዊነታቸው ብቻ በፈለጉት ቦታ ሄደው የመስራት መብት ይኖራቸው ነበር፣

7/ ኢትዮጵያውያን በመላው ዓለም ክብራችን ዝቅ ተደርጎ እንዲታይ አይደረገም ነበር። አንድ ችግር ሲገጥመን ወደ ኤምባሲያችን ሄደን ችግራችንን እንፈታ ነበር፣

8/ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለሁለት የተከፈሉ አባቶች አስተዳደር አይኖራትም ነበር፣

9/ ከ11 ቢልዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ከሀገር በሕገ ወጥ መንገድ አይወጣም ነበር፣

10/ የብሔራዊ ባንክ በቀትር ፀሐይ ወርቁን ለሌቦች አስረክቦ አርተፍሻል ወርቅ አይቀበልም ነበር፣

11/ የተማረ የሚከበርባት እና ሥራ የምያገኝባት እንጂ ኮብል ስቶን ተራቢ እንዲሆን አይደረገም ነበር፣

12/ የሕፃናት አምባ ወላጆቻቸው የሞቱባቸው ሕፃናት በምሽት በኢህአዴግ ወታደር አያባረሩም እና ሴቶች ለሴተኛ አዳሪነት ወንዶቹ ለጎዳና ተዳዳሪነት አይዳረጉም ነበር።

13/ ኢትዮጵያ ሕፃናቶቿን በጉዲ ፈቻነት በመሸጥ በአፍሪካ ቀዳሚ አትሆንም ነበር።

ባጠቃለይ ኢትዮጵያ በህወሓት አገዛዝ ስር እሩብ ክ/ዘመን (25 ዓመታት) ሊሞላት አንድ ዓመት ብቻ ቀራት።ሃያ አምስት አመታት በርካታ ሃገራት ወደ መካከለኛ ገብ ደረጃ የደረሱበት ነው።የዛሬ 24 ዓመት አንጎላ ጦርነት ላይ ነበረች።ዛሬ አንጎላ በከፍተኛ እድገት ላይ የምትገኝ ሀገር ነች። የዛሬ 24 ዓመት ቦትስዋና ብዙም የምትደነቅ ሀገር አልነበረችም ዛሬ ቦትስዋና የአልማዝ አምራች ሀገር ነች።የዛሬ 24 ዓመት ጋና ስሟ እምብዛም አይነሳም። ዛሬ ጋና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ መንግስት የምትቀይር እና የነዳጅ ሀብት ባለቤት የሆነች ሀገር ነች።ሃያ አራት ዓመት እንደ ኢትዮጵያ ላለ ጠንካራ ሰራተኛ ሕዝብ፣በብዙ ውጣ ውረድ ላለፈ ሕዝብ እና በርካታ እድሎች ከፊቱ ላሉት ሕዝብ ዛሬ ብራዚል ለደረሰችበት ደረጃ የመድረስ አቅም ነበረው።ነገር ግን በጎሰኛ መንግስት ተጠልፎ የጥቂቶችን የተንደላቀቀ ሕይወት እየተመለከተ እንዲኖር ተፈርዶበታል።አሁንም ከነገ ዛሬ ይቀድማል እና ለኢትዮጵያ ነፃነት አንድነታችንን እናጠናክር።ከጎሰኞች ማዶ ለምትመሰረተው የሁላችንም ኢትዮጵያ የበኩላችንን እናድርግ። 


ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ግንቦት 20/2005 ዓም (ሜይ 28/2015)

Wednesday, May 27, 2015

ኢህአዲግ/ወያኔ በዋናውም ሆነ የከተሞች ''ምክርቤት'' ውስጥ አይልም እንጂ ግማሽ ያህል ወንበር ለተቃዋሚዎች ሰጥቻለሁ ቢልም ኢትዮጵያ ውስጥ ለፈጠረው የፖለቲካ ችግር አንዳች መፍትሄ አይሰጥም (የጉዳያችን ማስታወሻ)

Picture source - Pampazuka news (Pan-African voice for freedom and justice) 

አንዳንዶች ላለፉት 24 ዓመታት ኢትዮጵያ አሁን በስልጣን ላይ ባለው ስርዓት ሳብያ የገባችበትን ውስብስብ ችግር በጥገናዊ ለውጥ የሚስተካከል ይመስላቸዋል።ይህ ግን ፈፅሞ የማይታሰብ ነው።ሌሎች ደግሞ ሁል ጊዜ 100% ከመጠበቅ የመጣ አባዜ ስለያዘን እንጂ ስርዓቱ የተወሰነ የፓርላማ ወንበር ከለቀቀ ቢያንስ ብዙ ነገር ማስተካከል ይቻላል የሚል ''የመለስተኛ ፕሮግራም'' አቀንቃኞች አሉ።ይህ አስተሳሰብ ግን በአብዛኛው ሕዝብ ዘንድ አለ ማለት አይደለም።በሆነ ጥቅም ከስርዓቱ ጋር በተሳሰሩት እና ከወያኔ ውጭ ያለች ኢትዮጵያን ፈርተው ከሚመለከቱ አንዳንድ የዋሃን በቀር የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁን ያለበት የፖለቲካ ብስለት ደረጃ ጥሩ የሚባል ይመስለኛል።እርግጥ ነው በኑሮ ውጣ ውረድ፣ልጆቹን ለማሳደግ እና በልቶ ለማደር መታተሩ በራሱ የፈጠሩበት እጅግ ፈታኝ የሆነ መስሎ የማደር እና ነገሮች በጣም ጫፍ እስኪደርሱ የመጠበቅ አዝማምያ አይኖርም ማለት አይቻልም። 

አሁን ግን ትንሽ ማለት የምፈልገው በተሻለ ኑሮ ላይ የሚኖሩ ሀገራቸውን የሚወዱ ግን ደግሞ ወያኔ በኢትዮጵያ ላይ እያደረሰ ያለው፣ያደረሰው እና ወደፊት ያቀደውን ዕቅድ በሚገባ ያልተረዱ፣አልያም ተረድተው ግን የሆነች የቸልታ አይሉት የኑሮዬ አልያም የግል ፕሮግራም እንዳትነካ ብቻ ነገሮች እንዳሉ ቢቀጥሉ የሚፈልጉ፣ ግን ትንሽ የመደለያ የለውጥ እርጥባን ከስርዓቱ ቢወረወር እና ''ይህንን ሕዝብ የሚያስታግስ ነገር ቢኖር'' ብለው  የሚመኙ ሁሉ ነገ ወያኔ/ኢህአዴግ ለተቃዋሚዎች ትንሽ ወንበር በእርጥባንነት ቢወረውር በሀገሪቱ የፖለቲካ ሕይወት ውስጥ ለውጥ ይመጣል ብለው በእየካፌው ለማውራት የተዘጋጁ ናቸው።

ግራም ነፈሰ ቀኝ ግን ወያኔ/ኢህአዴግ በውሸት ጀምሮ በውሸት ባለቀው ምርጫ ተብዬው ግርግር በኃላ ለተቃዋሚዎች ግማሽ የምክር ቤት ወንበር ለቅቅያለሁ ቢልም አንዳች ለውጥ ኢትዮጵያ ላይ አይመጣም።ለምን? 
ይህንን በሚከተሉት ማስረጃ ነጥቦች መግለፅ ይቻላል።

1ኛ/ የተወካዮች ምክር ቤት በመንግስት መዋቅር ውስጥ በስመ 'ሕግ አውጪ' ስም ቢሰጠውም በተግባር ግን የህወሓት ማዕከላዊ ምክር ቤት የወሰነለትን እንዲቀበል እና እንዲያጨበጭብ ብቻ የተፈጠረ አካል ነው።

እዚህ ላይ የሀገር ቁልፍ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ለምሳሌ ኢትዮጵያ ከግብፅ ጋር ያደረገችውን ስምምነት ቀድሞ በጉዳዩ ላይ መወያየት፣ማጥናት እና መወሰን ሲገባው አቶ ሃይለማርያም ከተፈራረሙ በኃላ ነው ለምክርቤት የቀረበው።የግብፅ እና የሱዳን ምክር ቤቶች ግን ተወያይተዋል አንቀፅ በአንቀፅ ተመልክተውታል።ይልቁንም ምሁራን በመገናኛ ብዙሃን ሁሉ ሃሳብ ሰጥተውበታል።የኢትዮጵያ ምክርቤት ግን የውሉን ይዘት ለማግኘት የግብፅ ''አልሃራም ኦን ላይን'' ድረ-ገፁ ላይ እስክፅፍ መጠበቅ ነበረበት።ይህ ውል የምክር ቤቱን ጥርስ አልባነት የሚያሳይ ትልቅ ምሳሌ ነው።ምክር ቤት የሚል ስም ለመስጠት የምጎሉት በርካታ ነገሮች እንዳሉ ስለማስብ እዚህ ላይ በእዚህ ደረጃ መጥራቱ ተገቢ እንዳልሆነ እረዳለሁ።

2ኛ/ የምክር ቤቱ ተወካዮች በሀገሪቱ ፖሊሲ ላይ ምንም አይነት ሃሳብ የማመንጨት መብትም አቅምም የላቸውም።

3ኛ/ የምክር ቤቱ ተወካይ አባላት በእራሳቸው ከእስር ቤት ባነሰ ፍርሃት ውስጥ ነው ያሉት።ማንም የወያኔ/ኢህአዴግ ካድሬ ሊነዳቸው ይችላል።

ሌላም ብዙ ብዙ መጥቀስ ይቻላል።ባጭሩ ተቃዋሚ ምክር ቤት መግባቱ የሚያመጣው አንዳች ለውጥ የለም።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ ነፃነት፣አጠቃላይ የፖሊሲ እና የፖለቲካ፣ምጣኔ ሀብት እና ወታደራዊ አደረጃጀት እና  መዋቅር ለውጥ ነው።

አንዳንድ ጊዜ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ችግርን ከእስረኞች መፈታት፣ከምርጫ ሂደት፣ከጋዜጣ ህትመት መፈቀድ እና ሃሳብን ከመግለፅ መብቶች ጋር ብቻ አያይዞ መመልከት እና ይህንን እንደ መጨረሻ ግብ መመልከት በእራሱ አደጋ አለው።ይህ ማለት እነኝህ ቁልፍ ጉዳዮች አያስፈልጉም ማለት አይደለም።ነገር ግን እነኝህ ጉዳዮች ወደ ግብ መድረሻ ስልት ናቸው እንጂ ዋና የኢትዮጵያን ችግር ፈተው የሚጨርሱ አይደሉም።እንበል ነገ ወያኔ/ኢህአዴግ እስረኞችን ሁሉ ቢፈታ፣ጋዜጦች ቢታተሙ ወዘተ በቃ ነገር አለሙ አበቃ ማለት ነው? አይመሰለኝም።ከኢህአዴግ/ወያኔ የሚጠበቀው መሰረታዊ የፖሊሲ ማለትም ከጎሳ ፖለቲካ መውጣት፣የስልጣን ሽግግርን ግልፅ እና ታማኝነት ባለው መንገድ መከወን፣የሀገርን እና የህዝብን ጥቅም ካለምንም ማዳላት ማስጠበቅ፣የምጣኔ ሀብት ድልድሉን እና አደረጃጀቱን ከአንድ ጎሳ እጅ አውጥቶ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል ዕድል መስጠት እና የወታደራዊ መዋቅሩን  አሁንም ከአንድ ጎሳ እጅ አውጥቶ ኢትዮጵያዊ ማድረግ የሚሉት የመጀመርያ ደረጃ እና ካለምንም ቅድመ ሁኔታ መከናወን ያለባቸው ናቸው።

እነኝህ ከላይ የተጠቀሱት ቁልፍ ጥያቄዎች ሳይመለሱ እስረኛ ፈታ፣ጋዜጣ ፈቀደ፣ጥርስ አልባ ለሆነው ምክርቤቱ ሰላሳ ወንበር ፈቀደ ወዘተ ለኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግር ላይ ለጊዜው ነገሮችን ያረገቡ ይምሰሉ እንጂ አንዳች የሚፈይዱት ነገር የለም።ስርዓቱን ስንቃወም መሰረታዊ ፖሊሲውን እና ዘረኛ እና አድሏዊ ሂደቱን መቀየር እንዳለበት እያተኮርን እንጂ ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ብናተኩር ማናልባት ለስርዓቱ እድሜ ይጠቅም እንደሆነ እንጂ አንዳች አይፈይድም። መሰረታዊው የሕዝብ ጥያቄ የሚመልስ እና የኢትዮጵያን አቅጣጫ  ከአናካሽ የጎሳ አደረጃጀት (ይህም በይምሰል ሳይሆን ዋስትና በሚሰጥ መልኩ) አውጥቶ ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ለማስቀጠል አሁንም ድፍረቱ፣ፍላጎቱም ሆነ እድሉ ያለው በተቃዋሚዎች እጅ ነው።ኢህአዴግ/ወያኔ ምን ያህል ጥገና አደረኩ ቢል የኢትዮጵያን የፖለቲካ ችግር ኢምንት ያህል የመቅረፍ አቅሙም ተፈጥሮውም የለውም።በመሆኑም ኢህአዲግ/ወያኔ በዋናውም ሆነ የከተሞች  ''ምክርቤት'' ውስጥ (አይልም እንጂ) ግማሽ ያህል ወንበር ለተቃዋሚዎች ሰጥቻለሁ ቢልም ኢትዮጵያ ውስጥ ለፈጠረው የፖለቲካ ችግር አንዳች መፍትሄ አይሰጥም።

ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ግንቦት 19/2007 ዓም  (ሜይ 27/2015)

Tuesday, May 26, 2015

እውን የኢትዮጵያን ችግር እንዳላዩ በማለፍ እና በቸልተኝነት የህሊና እረፍት ይገኛል? የእንቅልፍ ዘመናችን ያብቃ! ስለ ኢትዮጵያ ሁላችንም ያገባናል እንበል። (የጉዳያችን አጭር ማስታወሻ)


ኢትዮጵያን ዛሬ  ለደረሰችበት ደረጃ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ አስተዋፆ ማድረጉን መካድ አይገባም።በቀጥታ ወይንም በተዘዋዋሪ በዝምታ።ከዛሬ 24 ዓመት ወዲህ ብዙዎች ኢትዮጵያን ብለው በእየእሥር ቤቱ ማቀዋል፣ተገርፈዋል፣ተሰደዋል፣ልጆቻቸው ካለ አሳዳጊ ቀርተዋል፣ሀብት ንብረታቸውን ተነጥቀው የጎዳና ተዳዳሪ ሆነዋል።ለእዚህ ሁሉ መከራ እና ስቃይ የተዳረጉት ኢትዮጵያውያን ስለ ምንም ብለው አይደለም።ስለ ኢትዮጵያ እና ህዝቧ ነው።

ለምን ይህ ሆነ?

ጋዜጠኛ እስክንድር በተሻለ ኑሮ ከሚኖርበት ከአሜሪካ ድረስ መጥቶ ማደርያውን ቃሊቲ ለምን አደረገ?
በቀለ ገርባ ከዩንቨርስቲ መምህርነቱ እስር ቤትን ለምን ቤቱ አድርጎ ኖረ? 
ፕሮፌሰር መስፍን እለት ከእለት የስርዓቱን ግልምጫ እና ጡጫ ችለው በጠባብ አፓርታማቸው ለምን ተኮራመቱ?
ዶ/ር ብርሃኑ ከተደላደለ ህይወቱ ኢትዮጵያ ድረስ መጥቶ ለእስር ለምን ተዳረገ? ቀጥሎስ ለምን ተሰደደ? 
አቶ አንዳርጋቸው ከእንግሊዝ ኤርትራ በረሃ ለምን ገቡ? ቀጥሎስ ወያኔ እስር ቤት ስቃይ ለምን እንዲቀበሉ ሆኑ?
ወጣቶቹ ዞን ዘጠኞች ለምን ብዙ ተስፋ ከሚጠብቃቸው ሕይወት እርቀው እስር ቤት ተወረወሩ? 
አሰፋ ማሩ በጠራራ ፀሐይ ለምን ተገደሉ?
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለምን ተንገላታ? ለምን እስር ቤት ተወረወረ?
የመቀሌ ዩንቨርስቲ መምህሩ አብርሃ ደስታ እየሳቀ መኖር አቃተው? ለምን እውነትን በመናገሩ ብቻ ለእስር ተዳረገ?
የ1997 ምርጫ ተከትሎ ከአንድ መቶ ዘጠና ሶስት በላይ ኢትዮጵያውያን ለምን በጠራራ ፀሐይ በአዲስ አበባ ከተማ የጥይት አረር ሆኑ?
ሚልዮኖች ከሀገራቸው ወጥተው ለምን ተሰደዱ?

ብዙ መጠየቅ ይቻላል።እነኝህን ጥይቄዎች ለመመለስ ግን አንድ እና መሰረታዊ ጥያቄ ማንሳት ተገቢ ነው።ኢትዮጵያ ከላይ ያነሳናቸው እና ያላነሳናቸው ሌሎች ኢትዮጵያን ብለው ለወደቁት እና ወህኒ ለተጣሉት ብቻ ነች እንዴ? የኢትዮጵያን ችግር እንዳላዩ በማለፍ እና በቸልተኝነት የህሊና እረፍት ይገኛል? አንድ ሰው ከህሊናው ጋር ካልተስማማ እንዴት መኖር ይችላል? ሕሊናን በምን መሸንገል ይቻላል? ስንቶች ለሞቱላት እና በእስር ለሚማቅቁባት ሀገር ያለንን እና የአቅማችንን ልናደርግላት ካልቻልን ኢትዮጵያዊነታችን ምኑ ላይ ነው?

አንዳንዶች ሀገሬን በነፃነት እንዳያት ምን ላድርግ? እኔ ምንም ማድረግ አልችልም።ብለው በተስፋ ቢስነት ይቀመጣሉ።ይህ ግን ፈፅሞ ስህተት ነው።በእዚህ በ21ኛው ክ/ዘመን ቢያንስ አንድ ሰው ብዙ ነው።አንድ ሰው ሃሳብ ማፍለቅ እና ዓለምን የማነቃነቅ አቅም እንዳለው የተመሰከረበት ዘመን ላይ ደርሰናል።ዛሬ አንድ ሰው ሃሳቡን ለመግለፅ የግድ የቴሌቭዥን ጣቢያ መጠበቅ ወይንም ዓለም አቀፍ መገናኛ ማማከር የለበትም።ከፅሁፍ እስከ ፊልም ድረስ ማናቸውም መልክቶች በደቂቃ ውስጥ ለመላው ዓለም ማሰራጨት ይችላል።

ኢትዮጵያውያን ምሁራንስ የት ናቸው?


ኢትዮጵያውያን ምሁራን በመላው ዓለም ተበትነው ድምፃቸውን አጥፍተው ለእራሳቸው እና ለቤተሰባቸው ብቻ የሚኖሩበት ዘመን ማብቃት አለበት።ከታሪክ አቅም በሙያው ባልሰለጠኑ በስሜት በሚነዱ ዘመነኞች ታሪክ እንደፈለገው ሲቀረደድ ዝም ማለት ኢትዮጵያዊ ያስብለናል? ዝምታ ያዋጣናል? ችግሩን እና መፍትሄውን ሻይ ቡና ሲሉ ብቻ ከወዳጅ ዘመድ ጋር በማውጋት የኢትዮጵያን ሕዝብ መድረስ ይቻላል? በተለይ በውጭ ያሉት የተለያዩ አደረጃጀቶችን ፈጥረው እና መድረኮች እየፈጠሩ ወጣቱን ማስተማር፣ማሳወቅ እና የነገዋ ኢትዮጵያ ተረካቢ እንዲሆን እንዲሁም ለነፃነቱ እንዲቆም ማስቻል የምሁሩ ሥራ አይደለም? የነገዋን ኢትዮጵያንስ ከወዲሁ ማሳየት እና ለነገው ሥራ መጀመር ብሎም ማነቃቃት የምሁሩ ግንባር ቀደም ሥራ አይደለም?

ሌሎች በሀገር ቤት መከራ እና ስቃይ ሲቀበሉ ባህር ማዶ ሆኖ ዝምታ የት ያደርሳል? አዎን! ብዙዎች ሀገር ቤት ሲገቡ የሚደርሰውን ፈተና እና እዝያ ያለ ንብረት ደህንነት ሊይዛቸው ይችላል።ነገር ግን የኢትዮጵያ የአሁን ችግር በንብረት ጉዳይ በማውራት በእዚህ ደረጃ የወረደ ነው? ሌሎች ኢትዮጵያን ብለው ተሰደው ፈተና የደረሰባቸው ከሌሎቻችን በላይ ኢትዮጵያዊ ሆነው ነው? አይደለም።ይልቁንም ይህ ወቅት  በእዚህ ፍርሃት ውስጥ የሌሉ ነገር ግን ነገር አለሙን ትተው በባህር ማዶ ሆነው የኢትዮጵያን ጉዳይ ከሚድያ ብቻ እየተከታተሉ ያሉቱኑ በእጅጉ የእነርሱም ሀገሬን ብለው መነሳት እና መንቃትን የሚፈለግበት ጊዜ ነው።የብዙዎች ዝምታ ጥቂቶች በኢትዮጵያ ላይ እንዲፈነጩ ዕድል ሰጥቷል።እኔ ለሀገሬ ነፃነት ምን እያደረኩ ነው? ምንስ ማድረግ ይገባኛል? ከእራሳችን ጋር ተማክረን መልስ ልንሰጠው የሚገባን ጥያቄ።


ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ግንቦት 18/2007 ዓም (ሜይ 26/2015)

Friday, May 22, 2015

ሰበር ዜና - ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ''የአርበኞች-ግንቦት 7'' ሊቀ መንበር ሕዝቡ ዳግም እንዳይታለል የምርጫ ካርዱን ቀዶ በመጣል ለለውጥ ያለውን ቁርጠኘነት እንዲያሳይ የሚገልፅ መልዕክት አስተላለፉ።(የጉዳያችን ጡመራ መንደርደርያ ሃሳብ እና የመልዕክታቸው ሙሉ ፅሁፍ ተያይዟል)

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የአርበኞች ግንቦት 7 የአንድነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር 

የጉዳያችን ጡመራ መንደርደርያ 

የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዲሞክራሲ አሰራር፣ሕግን እና ስርዓትን ለማክበር ብቃት እና ዝግጁነት ያለው መሆኑን በተደጋጋሚ ቢያሳይም በጠበንጃ ኃይል ስልጣን ላይ የተፈናጠጠው ወያኔ/ኢህአዴግ ዛሬም ሕዝቡን ማሸበሩን ቀጥሏል።የሚቀናቀኗቸውን ተቃዋሚዎች በሙሉ በአሸባሪነት በይፋ ሲኮንን ከመክረሙም በላይ ትናንት ሐሙስ የታየው ክስተት ደግሞ ከምርጫው በኃላ ምን እንደሚደረግ በይበልጥ ግልፅ ሆኗል።ሐሙስ ግንቦት 13/2007 ዓም ስርዓቱ በአዲስ አበባ የሰበሰባቸው የጥቃቅን እና የኮብል ስቶን ሰራተኞች እንዲሁም የስርዓቱ የጥቅም ተጋሪዎችን ሰብስቦ ያሳየው ትዕይንት የጦርነት ትዕይንት ሲሆን ወጣቶች ክላሽ ይዘው ሲገሉ እና ሲሮጡ የሚያሳይ ትዕይንት በአዲስ አበባ ስታድዮም መሃል ሜዳ ላይ ሲተወን ሕዝብ ተመልክቶ አዝኗል።

ይህ የሚያሳየው ምርጫ በዘመነ ወያኔ ፈፅሞ የሰላማዊ የስልጣን መሸጋገርያ እንደማይሆን ነው።ይህንኑ ጉዳይ በዕለቱ ባለ 99.6% የይስሙላ ምክር ቤት ቀርበው የተናገሩት አቶ ኃይለ ማርያም ከምርጫ በኃላ ስለሚሰሩት የቂም ተግባር በግልፅ አስቀምጠዋል።ለእዚህም ማስረጃው ሌላው ቀርቶ ባለፈው ሳምንት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጋር የተከራከሩትን የመድረኩ ዶ/ር መራራን ''ስርዓቱ በአድልዎ የማይሰራ ቢሆን የጤና ባለሙያው ዶ/ር ቴዎድሮስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ ምን ይሰራል?'' የሚለውን የክርክር ሃሳብ ላይ ሳይቀር ስርዓቱ ቂም የያዘ እና ለበቀል እየተዘጋጀ መሆኑን በሚገልፅ መልኩ አቶ ኃይለማርያም ''አንዳንድ ተቃዋሚዎች በምርጫ ክርክሩ ወቅት ባለስልጣናትን መስደብ በመቻላቸው እንዳይኩራሩ'' የሚል  መልዕክት ማስተላለፋቸው ክርክሩን በእራሱ ''በስድብነት'' መመዝገባቸው እና ለበቀል እየተዘጋጁ መሆናቸውን ለኢትዮጵያ ሕዝብ በግልፅ አስታውቀዋል። 

ባለፉት 24 ዓመታት ውስጥ ለምንም ነገር መታመን ያልቻለው በጎጥ ላይ የተመሰረተው ስርዓት ያለፈ የቆሸሸ ታሪኩን ተመልክተን የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መግለጫ ስናነብ ምን ያህል ትክክለኛ እና ኢትዮጵያውያን ካለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ነፃነታቸውን ለመቀዳጀት መቁረጣቸውን የሚያሳዩበት ታሪካዊ አጋጣሚ በውሸት ምርጫ ላይ ባለመሳተፍ የመጀመርያ እርምጃ መሆን እንዳለበት ህሊናውን የማይደልል ሰው ሁሉ የሚረዳው እውነት ነው። የመልዕክቱን ሙሉ ቃል ከእዚህ በታች ይመልከቱ።ፅሁፉን ከዶ/ር ታደሰ ብሩ ገፅ ላይ የተወሰደ ነው።

=======================================================================
ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር በድርጅታቸው እና በእራሳቸው ስም ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያስተላለፉት መልዕክት 

የተከበራችሁ እናቶቼና አባቶቼ፤ እህቶቼና ወንድሞቼ እንዲሁም ልጆቼ የምትሆኑ ወጣቶች!!
አገራችን የምትገኝበትን አስጨናቂ ሁኔታ ሁላችንም እንረዳለን። የህወሓት/ኢሕአዴግ ፋሽስቶች ቡድን እየገረፈ፣ እያሰረና እየገደለ በካርዳችሁ መርጣችሁ የምርጫ ድግሴን ካላሞቃችሁልኝ እያለ ነው። እንኳንስ ዛሬ ታዛቢ በሌለበት፤ ታዛቢ እያለም እንኳን ወያኔ የሕዝብን ድምጽ በትክክል ቆጥሮ አያውቅም። ወያኔ ለሕዝብ ድምጽ ምንም ደንታ የሌለው የኋላቀር ወሮበሎች ቡድን ነው::
ለስንት አስርት ዓመታት ለወያኔ ባርነት እንገብራለን? ለሀያ አስምስት ዓመታት ተገዛን፣ ተገደልን፣ ተቀጠቀጥን፣ ታሰርን፣ ተሰቃየን፣ ልጆቻችን በአገራቸው ተስፋ ቆርጠው ሲሰደዱ በበረሀ ንዳድ አለቁ፤ በባህር ሰጥመው ቀሩ፤ በባዕዳን አረመኔዎች እንደከብት ታረዱ፤ ቤንዚን ተርከፍክፎባቸው ተቃጠሉ። ሀይማኖታችን ተዋረደ፤ ባህላችን ረከሰ፤ ታሪካችን ተናቀ። በልማት ስም ወልደን ከከበድንበት ተፈናቀልን፤ አገራችን አደገች እያለ ሕዝብ በኑሮ ውድነት ተሰቃየ። በልቶ ማደር ብርቅ ነው። እንደሙጫ የሚያጣብቀንን ማኅበረሰባዊ ትስስር በስልጣን ለመቆየትና ኅብረተሰቡን ለመዝረፍ ሲል ሆን ብሎ እያፈራረሰው ነው:: ይኽ ሁሉ አይበቃንምን? ይኸ ሁሉ አይመረንምን? 
ወላጆቼ፣ እህት ወንድሞቼ!ውርደት ይብቃን። የተረገጥንና የተገደልን አንሶን ፍጹም ማንንም ሊያሞኝ በማይችል የለበጣ ምርጫ ወደን የተረገጥን፤ ፈልገን የተገዛን ለማስመሰል ወያኔ የሚያደርገውን ሩጫ እናክሽፈው:: ከፊታችን ያለውን ምርጫ ባለመሳተፍ ምሬታችንን እንግለጽ። 
ዛሬ በግሌ እና በአርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ስም ጥሪዬን አቀርባለሁ። በዚህ ምርጫ አትሳተፉ። የምርጫ ካርዳችሁን ቀዳችሁ ጣሉት። እናምርር። ካላመረርን ለውጥ ሊመጣ አይችልም። ይልቅስ ለማይቀረው የመጨረሻው ትግል ራሳችንን እናዘጋጅ::
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሞ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር ትብብር በመፍጠር የአገር አድን ኃይል በመገንባት ላይ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት አንከፋፈልም። ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ያካተተ ስብስብ ፈጥረን በኅብረት አገዛዙን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ ትግል ነው። የትግሉም ባለቤት የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ ነው። ክርስቲያን ሙስሊም፤ ወንድ ሴት፤ ወጣት አረጋዊ ሳንል፤ በብሔርም ሆና በቋንቋ ሳንከፋፈል ሁላችንም ይህን አስከፊ ሥርዓት በቃህ እንበለው። 
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! ይህንን የውሸት ምርጫ ባለመሳተፍ ለለውጥ ያለህን ዝግጁነት አሳይ! ደግሜ እለዋለሁ - የምርጫ ካርድህን ቅደድ!!!
የጦርና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!
እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። በወገኖቻችሁ ላይ አትተኩሱ። ይልቁንስ አፈሙዛችሁን አገራችንን ለውርደት በዳረገውና በሙስና በተጨማለቀው ዘራፊው የህወሓት አገዛዝ ላይ አዙሩት። ታሪካችሁን ከምታበላሹ፤ ታሪክ ሥሩ። ለራሳችሁ፣ ለቤተሰቦቻችሁ፣ ለልጆቻችሁ እና ለሕዝብ የሚጠቅም አገርና መንግሥት እንዲኖረን የእናንተ የግልም ሆነ የጋራ ተነሳሽነት ወሳኝ ነው። ወያኔ ህዝቡን የሚዘርፈው በእናንተ ትከሻ ላይ ቆሞ እንደሆነ ላንዳፍታም አትርሱት:: እንደመላው ህብረተሰብ እናንተም በነጻነትና በኩራት የምትኖሩበት ሀገር እንደምትሹ አልጠራጠርም:: ስለዚህም ይህን የህወሓት የውሸት ምርጫ ተቃወሙ። ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ። 
የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ ትግላችን እስከ ነፃነት ድረስ ይቀጥላል። ነፃነታችንን በእርግጠኝነት በትግላችን እንቀዳጃለን። የምትወዷት፣ የምትኮሩባት አገር - ኢትዮጵያ - ትኖረናለች። ለዚህ ግን ዛሬ ተደራጅተን፣ ፀንተን መታገል የሁላችንም ኃላፊነት ነው። ዛሬ ሁላችንም በፍላጎትና በመንፈስ የተገናኘን ነንና ሁሉም በያለበት ትግሉን ያጧጡፍ። ውጤቱ ቀድሞ በታወቀው በዚህ ምርጫ አለመሳተፍ ለትግሉ ያለንን ቁርጠኝነት ማሳያ ነውና ለውሸት ምርጫ ያለን የመረረ ተቃውሞ በምርጫው ባለመሳተፍ እናሳይ። 
ነፃ እንወጣለን!
የኢትዮጵያ ሕዝብ የነፃነቱ ባለቤት ይሆናል!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!
ብርሃኑ ነጋ
የአርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር
=============================
መልዕክቱን በድምፅ ለመስማት ይህንን ይጫኑ

ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ግንቦት 14/2005 ዓም (ሜይ 22/2015)

Monday, May 18, 2015

ሰበር ዜና - ''ዋሽግተን ፖስት'' በዛሬ ግንቦት 10/2007 ዓም (ሜይ 18/2015) እትሙ የመጪው ዕሁድ የኢትዮጵያ ምርጫ ''ዜጎች አዲስ መንግስት የማይመርጡበት ትርጉም የለሽ ምርጫ'' በማለት አጣጣለው።As Ethiopia votes, what’s ‘free and fair’ got to do with it? Washington Post May 18,2015

''The voting that will take place on May 24 will not provide citizens a meaningful role in selecting their next government.'' 
Washington Post May 18,2015
Ethiopian journalist Simegnish “Lily” Mengesha (R) sits with President Obama during a round table with persecuted journalist for World Press Freedom Day at the White House in Washington, DC, May 1, 2015. JIM WATSON/AFP/Getty Images

As Ethiopia votes, what’s ‘free and fair’ got to do with it?

 May 18 at 9:05 AM


Ethiopia, Washington’s security partner and Africa’s second most populous country, is scheduled to hold national elections on May 24. The ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) and its allied parties won 99.6 percent of the seats in the last round of elections in 2010. There is no doubt that the ruling party will win again.
The party has ruled since 1991 when it seized power following a prolonged civil war. It dominates all major political, economic, and social institutions, has virtually eliminated independent political space, and opposition parties are fractured and harassed. Ethiopia has jailed more journalists than any other country in Africa.
The EPRDF is an extremely strong and effective authoritarian party. Yet Wendy Sherman, the Under Secretary of Political Affairs in the Department of State, recently said, “Ethiopia is a democracy that is moving forward in an election that we expect to be free, fair and credible.” What roles do elections play in authoritarian states and what, if anything, do they have to do with “free, fair, and credible” standards?

Part of the answer is to recognize that elections and political parties in autocratic states play different roles than they do in democratic states. Electoral processes are used by authoritarian regimes to consolidate power and to demonstrate the ruling party’s dominance, as argued by scholars of comparative politics such as Schedler and Gandhi and Lust-Okar. Research by Geddes shows that single-party authoritarian regimes tend to be more stable and last longer than military or personalistic ones. Strong partiesmanage instability by encouraging intra-elite compromise, co-opting opposition, and institutionalizing incentives to reward loyalty. Elections and strong political parties thereby contribute to “authoritarian resilience,” as scholars note with reference to ChinaIran and Syria, and Zimbabwe.

Non-competitive elections are common in authoritarian states and incumbents often win by incredible margins. In Sudan, President Omar al-Bashir won 94 percent of the vote in April 2015 elections, Uzbek President Islam Karimov over 90 percent in March 2015, and Kazak President Nursultan Nazarbayev 97 percent in April 2015. Rwandan President Paul Kagame, when asked if his 93 percent landslide in 2010 represented the will of the people, reportedly answered: “So, 93 percent – I wonder why it wasn’t higher than that?” The EPRDF’s 99.6 percent victory in 2010 created credibility problems in North American and European capitals where diplomats often asked, “Couldn’t they have just won by 60 or 75 percent?” But the point of elections under authoritarian rule is not to obtain a working majority or to win international approval. The purpose is to dominate domestic politics completely and thereby deter any leader from thinking he or she could challenge ruling party successfully. The dramatic, overwhelming victories send an important domestic message of strength and power, even as they strain credibility abroad.

The EPRDF recognizes the dangers it faces from competitive elections and that it democratizes at its peril. In 2005 Ethiopia held competitive elections, complete with significant opposition participation, major rallies, and televised debates. According to official results, the opposition’s share of seats in parliament increased from 12 to 172, representing 31 percent of the total. The opposition parties swept all the seats in Addis Ababa and many cabinet ministers and high-ranking officials lost their positions. This shift represented the potential for an important advance in democratization and a major break in the ruling party’s domination.
Members of the opposition, however, refused to accept the results and claimed that massive fraud had denied them outright victory. Some opposition leaders boycotted the parliament. Post-election demonstrations turned violent and were brutally put down by the Ethiopian military, leaving nearly 200 dead and an estimated 30,000arrested. The 2005 election began with a democratic opening but ended with what the Department of State characterized as the criminalization of dissent.
In the aftermath of the 2005 crisis, the EPRDF responded by demonstrating its extraordinary strength in using the levers of state power and its considerable organizational capacities to control all aspects of political life. New laws largely eliminated civil society institutions and the Anti-Terrorism Proclamation has been used against journalists and other critics. Just before a visit by Secretary of State Kerry in April 2014, the regime arrested a group of young bloggers who called themselves Zone Nine and charged them with terrorism. Washington recently urged Addis Ababa “to refrain from using its Anti-Terrorism Proclamation as a mechanism to curb the free exchange of ideas.”
As a consequence of its restrictions on politics over the past decade, the ruling party has little to worry about with regard to the opposition parties competing in the upcoming elections. The limits on formal political competition have made social mobilization outside of the electoral process more important. A series of non-violent protests in 2012 by Ethiopian Muslims provided an important model of sustained, peaceful social mobilization. The regime arrested the movement’s leadership and has tried to link the protests to external enemies and terrorism. In 2014, the security services quickly suppressed demonstrations on university campuses by Oromos, highlighting the historical sense of marginalization perceived by many in Ethiopia’s single largest ethnic group. In April 2015, a government organized rally to mourn the killing of Ethiopian migrants in Libya by the Islamic State (ISIS) ended with arrests and clashes between security forces and protestors. The Ethiopian regime has managed each of these challenges without significant difficulty but the underlying grievances remain.
Under Secretary of State Sherman characterized Ethiopia’s elections in terms of “free, fair, and credible” but that obscures the nature of the regime and mischaracterizes the functions of elections under authoritarianism. A Washington Post editorial recently criticized Sherman and argued: “If the election is not judged by independent observers to live up to Ms. Sherman’s billing, the administration should swallow her words — and change its approach.” But the results in Ethiopia and other authoritarian regimes holding elections are largely settled months if not years in advance, as powerful ruling parties restrict political opposition, civil society, and independent media in ways that virtually eliminate competition. The voting that will take place on May 24 will not provide citizens a meaningful role in selecting their next government. Such elections, however, are not pointless. As in other authoritarian states, elections play a key role in providing the setting for the ruling party to demonstrate its domination.
Terrence Lyons is an Associate Professor at the School for Conflict Analysis and Resolution, George Mason University. He began his research on Ethiopia in 1987, served as Senior Advisor to the Carter Center’s election monitoring mission to Ethiopia in 2005, and currently is writing a book on Ethiopian politics since 1991.

Sunday, May 17, 2015

ደብረ ሊባኖስ እና ትኩረት ያልተሰጠው ግንቦት 13 የሰማዕታት ቀን (የቪድዮ ምስክርነት)

ደብረ ሊባኖስየአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም በየዓመቱ ግንቦት 12 የፃድቁ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ፍልሰተ አፅም ዓመታዊ በዓል ይከበርባታል።በማግስቱ ግንቦት 13 ቀንም ብዙ ጊዜ ትኩረት የማይሰጠው ታሪካዊ ቀን ነው።ፋሽሽት ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት ከሶስት መቶ በላይ መነኮሳት በአንድ ቀን የፈጀበት ዕለት።

ከእነኝህ ሰማዕታት ውስጥ እውቁ የቀዶ ጥገና ሐኪም፣የቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ የግል የጤና ዶ/ር  የነበሩት በኃላም የመአሕድ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሠር አስራት ወልደየስ አባት ይገኙበታል።ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ አባታቸውን
ጣልያን ደብረ ሊባኖስ ገዳም ውስጥ ሲገድልባቸው የዘጠኝ ዓመት ልጅ ነበሩ።ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ በኢህአዴግ እስር ተፈርዶባቸው በእስር ቤት በህመም ሲሰቃዩ ቆይተው በሕይወታቸው መጨረሻ ላይ ለህክምና ወደ አሜረካ እንዲሄዱ በተደረጉ በቀናት ውስጥ ሕይወታቸው ማለፉ ይታወቃል።

ከእዚህ በታች የምትመለከቱት ፊልም ፋሽሽት ሀገራችንን በወረረ ወቅት በሕይወት የነበሩ አባትን ምስክርነት ያሳያል።
ቪድዮ - ከሰማዕቱ እስጢፋኖስ ገፅ




ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

Friday, May 15, 2015

ይቅርታ! ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ዲሞክራሲ እና ነፃነትን በተግባር እንጂ በፎቶ አያሳዩን



ከእዚህ በላይ ያለውን ፎቶ ዛሬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የፌስ ቡክ ገፃቸው ላይ ለጥፈው ስመለከት የሚሰራው እና የሚለቀቀው የፕሮፓጋንዳ ፎቶ ብዛት አሳዛኝ ሆኖ አገኘሁት።ፎቶው የአጋጣሚ ነው።ምናልባት ኢቲቪ ቢሮ ስቱድዮ እስኪዘጋጅ ሻይ እንዲጠጡ ተብሎ የተነሱት ፎቶ ሊሆን ይችላል። ምንም ይሁን ምን ግን ሰማያዊ ፓርቲ ላይ የደረሰው እና በኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ጉዞ የቁልቁለት ጉዞ አንፃር ይህ ፎቶ የበለጠውን የታይታ ቀልድ መስሎ የሚታይ ነው።
ለማንኛውም ዶ/ር ቴዎድሮስ ፎቶውን የማላደንቅልዎ ስለ ሁለት ምክንያቶች ነው -

1/ አቶ መለስም የዛሬ አስር ዓመት ይህንን አድርገውት ነበር 

ይህንን ፎቶ ተመልክቶ 'አሳሪ እና የነገ ታሳሪ አንድ ላይ ሻይ ጠጡ'' ብሎ ጮቤ የሚረግጥ ኢትዮጵያዊ የለም።ይህንን ስል ለምን አብራችሁ ሻይ ጠጣችሁ እያልኩ አይደለም።ይህ የላይ ከላይ የኢህአዴግ ሽፋን እንደሆነች እኔ አይደለሁም የምትጠጡባት ስኒም ይገባታል።ለእዚህም ማስረጃው አቶ መለስም በ1997 የምርጫው ሰሞን እንዲሁ አድርገውት ነበር።እንዲያውም ሲተቃቀፉ አይተን ነበር።ልክ የዛሬ አስር ዓመት ግንቦት 7 ምሽት ላይ በአንደበታቸው አዋጅ ሲያውጁብን የምርጫ ጣቢያዎች ገና አልተዘጉም ነበር።እዚህ ድረስ ነው ታይታችሁ ማለቴ ነው። በእኛ እርዳታ ነፃነታቸውን ያገኙ የአፍሪካ ሃገራት መሪዎች ከተቃዋሚዎች ጋር ያላቸውን ግንኙነት እና የዲሞክራሲ ሂደት ከእኛ ምን ያህል የላቀ እንደሆነ የማያውቀውን የዋሁን ሕዝብ ለማታለል  ከሆነ አይሳካም።

2/ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሙሉ ነፃነቱን እና እውነተኛ ዲሞክራሲ እንጂ ታይታ አይፈልግም።

ለኢትዮጵያ ሕዝብ መስጠት ያለባችሁ ምርጫ ስትደርስ የምትነሱትን ፎቶ ሳይሆን ሙሉ ነፃነቱን ነው።ደካማ የድርጅትዎ ካድሬዎች ይህንን ይዘው አዲስ ሃሳብ ማፍለቅ የተሳነውን አዕምሯቸውን ሊያሟሹበት ይሞክሩ ይሆናል።እኔ ግን የእርስዎ ድርጅት የኢትዮጵያውያንን ነፃነት ምን ያህል እንደገፈፈ እና በእኛው እርዳታ ነፃነታቸውን ካገኙ በርካታ የአፍሪካ ሃገራት አንፃርም ሲታይ ምን ያህል ወደ ኃላ እንደወሰዳችሁን ለማነፃፀር እነ ጋናን መመልከቱ ብቻ ይበቃል ባይ ነኝ።
እናንተ ከመኪና ላይ ገፍትራችሁ አልሞት ያላችሁን መሃንዲስ ጋር አብራችሁ ሻይ ስለጠጣችሁ እንደ ትልቅ ውለታ እንደማልቆጥረው ይረዱልኝ። ኢትዮጵያ በመንግሥትነት እረጅም ዓመት ያሳለፈች ሀገር ነች።ዛሬ በ21ኛው ክ/ዘመን ላይ ክላሽ ደግናችሁብን ምርጫ እያላችሁ የምትመፃደቁባት ሀገር አልነበረችም።ይህ ሕዝብ መብት እና ግዴታውን የሚያውቅ፣ማን እንደነበረ እና ወዴት መድረስ የሚገባው እንደሆነ የሚረዳ ሕዝብ ነው።ተቃዋሚን አይደለም የማረኩትን የጦር ምርኮኛ  እኩል የሚያስተናግዱ መሪዎች ያፈራች ሀገር ነች።ኢትዮጵያ! እናም ገና ብዙ ብዙ እርቀት ይቀርዎታል።ከፎቶ ታይታ ይልቅ የተግባር ነፃነት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ይመለስለት።

ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ግንቦት 7/2007 ዓም (ሜይ 15/2015)

Wednesday, May 13, 2015

ችግሩን ሁሉ በአቶ ኃይለማርያም ላይ በማሳበብ በስልጣን መዝለቅ አይቻልም።የኢትዮጵያ የችግሮቿ ምንጭ እራሱ ኢህአዴግ/ወያኔ ነው (ጉዳያችን)

አቶ ኃይለማርያም 

አቶ ኃይለማርያም  ደሳለኝ በፓርቲያቸው ሰዎች አንድ ቀን በፈጀ ግምገማ ክፉኛ መነቀፋቸውን እና እንባ እየተናነቃቸው ምላሽ መስጠታቸው እንዲሁም አቦይ ስብሃትን በተለይ ''ይጮሃል እንደ አሞራ ይዞረኛል'' እስከማለት መድረሳቸውን ኢሳት ራድዮ እና ቴሌቭዥን ግንቦት 5/2007 ዓም ባሰራጨው ዘገባ ገልጧል።

ጎሳን መሰረት ያደረገ ፖሊሲውን፣በሙስና የታሹ የባለስልጣናቱን ነውር ሥራ እና የምጣኔ ሀብት ውድቀቱን ምክንያት ሁሉ በአቶ ኃይለማርያም ላይ አሳቦ ሕዝብን ማታለል አይችልም።አቶ ኃይለማርያም የአቅም ችግር እንዳለባቸው ዛሬ ነው እንዴ የታወቀው? አቶ ኃይለማርያምን ለምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት የመረጡት አቶ መለስስ አይደሉም እንዴ? የእዚህን ያህል የአቅም ችግር እንዳለባቸው እየታወቀ አቶ መለስ ለምን አቶ ኃይለማርያምን  ለምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት መረጡ? መልሱ አቶ መለስ እራሳቸው የመምረጥ የአቅም ችግር ተጠቂ ነበሩ ወይንም እራሳቸው ጎልተው እንዲታዩ ሲሉ ሆን ብለው ከአቅም በታች የሆነ ሰው መርጠዋል የሚል ካልሆነ ሌላ ሊሆን አይችልም።

ኢህአዴግ/ወያኔ የአቶ ኃይለ ማርያምን ግምገማ በተለይ አሁን ለምን እንደ አዲስ ለመተረክ ፈለገ? መልሱ ቀላል ነው።ኢህአዲግ/ወያኔ  ከገጠር እሰከ ከተማ ባለው ኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ ከመቸውም ጊዜ በላይ 'አይንህን ላፈር' መባሉ ነው። በተለይ በሊብያ የወገኖቻችን መሰዋት እና እርሱን ተከትሎ በስርዓቱ የተወሰደው የቸልተኝነት ሂደት ይብሱን አዲሱን ትውልድ ሙሉ በሙሉ በኢህአዴግ/ወያኔ ተስፋ እንዲቆርጥ አደረገው። ለእዚህም ነው ከአስር አመታት ወዲህ ለመጀመርያ ጊዜ ከፍተኛ ተቃውሞ  በአዲስ አበባ ወጣቶች የተሰማው።ይህ የህዝብ ቁጣ ማየል ስጋት ላይ የጣለው ስርዓት ታድያ አንድ አይነት መውጫ ይፈልግ ገባ።ለመውጫው ብቸኛ መንገድ ያደረገው ''ለችግሮች ሁሉ ምክንያቱ ኢህአዴግ/ወያኔ ሳይሆን  አቶ ኃይለ ማርያም ነው'' የሚል ተረታ ተረት ይዞ ቀረበ።ምናልባት ከምርጫው በፊትም ኢህአዴግ ባደረገው ግምገማ አቶ ኃይለ ማርያም ከስልጣን ወረዱ የሚል ዜና በመልቀቅ የህዝብ ጆሮ በማቆም እና ቁጣውን ወደ ሌላ ትኩረት ለማዞር ይሞከር ይሆናል።ይህ ሁሉ ግን ከንቱ ሙከራ ከመሆን አያልፍም።

ኢህአዴግ/ወያኔስ እንደ ድርጅት አቶ ኃይለማርያምን ሊቀመንበሩ እንዲሆኑ ሲመርጥ ገና ድርጅቱ የአቅም ችግር ያጥለቀለቀው መሆኑን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሚስጥር አይደለም። ኢትዮጵያን በዕውር ድንብር ሲመራ የኖረው ድርጅት ዛሬ የሀገሪቱ ሀብት ተሟጦ ከሄደ በኃላ፣ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት እንደቀረበው ሪፖርት ከ11 ቢልዮን ዶላር (ከ200 ቢልዮን ብር) በላይ በሕገ ወጥ መንገድ ለማጣቷ፣ዜጎች በመላው ዓለም በተለይ በአረብ እና ጎረቤት ሃገራት እጅግ በተዋረደ መልክ ሕይወት መግፋት ለመጀመራቸው፣ኑሮ ውድነቱ ጣርያ ደርሶ ቤተሰብ የተባለ የሕብረተሰቡ አንዱ እና ዋናው አካል የፈረሰው፣ሙስና ቅጡን አጥቶ የሶስት ሺ ብር ደሞዝተኛ ባለስልጣን የአስር ሚልዮን ብር ቤት የሚሰራው፣ፍትህ መድረሻ አጥታ ዜጎች እንደ ከብት በእየእስር ቤቱ የሚታጎሩት እና ሌሎች ማለቅያ የሌላቸው የሀገሪቱ ችግሮች የተከሰቱት ድርጅቱ ኢህአዲግ/ወያኔ በአቅም ችግር የተወረረ በመሆኑ እና በሥርዓት አልበኛ ባለስልጣናት ስለሚዘወር መሆኑን የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠንቅቆ ያውቃል።አቶ ኃይለ ማርያም እራሳቸው የማን ውጤት ናቸው? አሁን በአስራ አንደኛው ሰዓት ላይ ቆማችሁ የኢትዮጵያን ሕዝብ አታታልሉትም።ባጭሩ ስልጣኑን ለሕዝብ መልቀቅ ከመሰለ ብቸኛ አማራጭ ሌላ ለኢህአዲግ/ወያኔ ወርቅ የሆነ መንገድ ፈፅሞ አይገኝም።

በሌላ በኩል ግን አቶ ኃይለ ማርያምም ወደ ስልጣን እንደ መጡ አንስተውት የነበረው የሙስና ጉዳይ ተዳፍኖ ለምን ቀረ? ብሎ የመጠየቅ መብት የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው።የሙስና ኮሚሽን ደብዛው እንዲጠፋ የተደረገው በህወሓት ባለስልጣናት አይደለም እንዴ? አቶ ኃይለ ማርያም ይህንን ሁሉ ጉዳይ የሚነግሩን ወቅት ይኖር ይሆናል አልያም እራሳቸው  ጣፋጭ ቀምሼ ነው ብለው ግለ ሂስ አድርግ ተብለው ይገደዱ ይሆናል።አቶ ኃይለ ማርያም በቀረቻቸው ሁለት ሳምንታት ውስጥ ማድረግ የሚችሉት በሙስና የተዘፈቁ ባለስልጣናትን በሙሉ ለፍርድ ማቅረብ አንዱ መሆን ይችላል።ከቤተ መንግስት አትክልተኛ ጀምሮ በአንድ ጎሳ እና በሙስና የተዘፈቀ ስርዓት ውስጥ ይህንን ማድረግ እንደማይችሉ የታወቀ ነው።አቶ ኃይለ ማርያም  የጦር ኃይሎች አዛዥ የሚል ማዕረግም ባለቤትም ናቸው ለካ!።እና ጦሩን ይዘዙት እንዴ? ማን ሰምቷቸው? 

 አንድ ሰሞን አቶ ኃይለ ማርያም ''ሙስና አጠፋለሁ'' ብለው ጮክ ብለው በሚናገሩባቸው እነኛ ወርቃማ ወራት ውስጥ (የዛሬ ሁለት ዓመት) ዋናው ኦዲተር በሀገሪቱ ያለውን የመንግስት ባለስልጣናት የአንድ ዓመት ብቻ  የሙስና ንቅዘት እንዲህ አስቀምጦት ነበር።

'- 1.4 ቢሊዮን ብር ያልተወራረደ ሒሳብ አለ፡፡
- 313.6 ሚሊዮን ብር ዕዳ ሳይመልሱ የተሸጡ ድርጅቶች አሉ፡፡
- 897.5 ሚሊዮን ብር ሕጋዊ ያልሆነ ክፍያና ወጪ ተደርጓል፡፡
- ያልተወራረደው 1.4 ቢሊዮን ብር በ57 የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የታየ ነው፡፡
- 15 ድርጅቶች ወይም መሥሪያ ቤቶች ከልዩ ልዩ ገቢ ማስገኛ ምንጮች ገቢ የሚሰበስቡ ቢሆኑም፣ የገቢ   ሪፖርት የማያደርጉ በመሆኑ ኦዲት ማድረግ አለተቻለም፡፡
- በ13 ናሙና መሥሪያ ቤቶች የተሟላ ማስረጃ ሳይቀርብ 132.364 ሚሊዮን ብር በወጪ ተመዝግቧል፡፡
- 22 መሥሪያ ቤቶች 13.8 ሚሊዮን ብር ማስረጃ የሌለው ወጪ አድርገዋል፡፡
- 30 መሥሪያ ቤቶች ደንብና መመርያ በመጣስ 353.568 ብር የሚያወጣ ግዥ ፈጽመዋል፡፡
- በውሎ አበልና በትርፍ ሰዓት ተመን 11 መሥሪያ ቤቶች 1.4 ሚሊዮን ብር አባክነዋል፡፡
- በኤርፖርት ተርሚናል የተሰማራ አንድ የግል ድርጅት ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ ለመቀበል ፈቃድ ሳይኖረው ከአሥር ዓመታት በላይ እየሠራ እንደሚገኝና ተቆጣጣሪ አካላት ያደረጉት ምንም ነገር የለም፡፡
- 134.7 ሚሊዮን ብር ብድር ያልመለሱ የመንግሥት ድርጅቶች ሲኖሩ፣ የመንግሥት ትርፍ ድርሻ የሆነ 18.549 ሚሊዮን ብር ሳይከፍሉ የተሸጡ ድርጅቶች አሉ፡፡ 44.254 ሚሊዮን ብድር ያለባቸው ሲሸጡም የገዛው አካል ለመንግሥት መከፈል የነበረበትን ያልከፈለ መሆኑን ያስረዳ ነበር።

ይህ ሁሉ ተረሳና ዛሬ ሙሰኞቹ እራሳቸው አንድ አቅመ ቢስ ላይ ከበው አናት አናቱን ይሉ ገቡ።ባጭሩ የአቅም ማነስ ችግሩ የአቶ ኃይለ ማርያም ብቻ ሳይሆን የእራሱ ጎሳው ድርጅትም ጭምር ነው።ኢህአዲግ/ወያኔ ኢትዮጵያን የምታክል ታላቅ ሀገር የመምራት አቅም የለውም።ችግሩን ሁሉ በአቶ ኃይለማርያም ላይ በማሳበብ በስልጣን መዝለቅ አይቻልም።

ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ግንቦት 6/2007 ዓም (ሜይ 14/2015)

Monday, May 11, 2015

ኖርዌይ እና ኢትዮጵያ፣ Norway and Ethiopia, Norge go Etiopia




ኖርዌይ እና ኢትዮጵያ
በኢትዮጵያ እና በኖርዌይ መካከል ረዘም ያለ ታሪካዊ ግንኙነት አለ።ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ እና የኖርዌይ ንጉሳዊ ቤተሰብ በቅርብ የተዋወቁት በሁለተኛው ዓለም ጦርነት መጀመርያ አካባቢ ለንደን ላይ ነበር።በወቅቱ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ የጣያንን ኢትዮጵያ መውረር በወቅቱ የዓለም ማኅበር ተብሎ ለሚጠራው የዛሬው የተባበሩት መንግሥታት ለማቅረብ ለአቤቱታ እንግሊዝ ነበሩ። ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ ኖርዌይን የጎበኙት በ1954 ዓም እንደ ኤውሮፓውያን አቆጣጠር ነበር ።በመቀጠል የኖርዌይ ንጉስ ኦላቭ ኢትዮጵያን በ1959 ዓም እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር ይፋዊ ጉብኝት አደረጉ።ኖርዌይ ኢትዮጵያ የባህር ኃይሏን ምፅዋ እና አሰብ ላይ ስትመሰርት በስልጠና የረዳች የመጀመርያ ሀገር ነች።ኢትዮጵያ ዛሬ በአምባገነን ስርዓት ውስጥ ወድቃ ትገኛለች።ሚልዮኖች በስርዓቱ ምክንያት ተሰደዋል፣ታስረዋል ለከፋ ጉስቁልና ተዳርገዋል።ዛሬም ኢትዮጵያውያን ለሰብአዊ መብት እና ለዲሞክራሲ ለሚያደረጉት ትግል ሁሉ በመደገፍ ኖርዌይ የዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ግዴታዋን እንደምትወጣ ተስፋ እናደርጋለን።
===========================
Norway and Ethiopia
Strong ties between Ethiopia and Norway were formed during the second World War when Emperor Haile Selassie of Ethiopia and the Norwegian royal family met in London. This led to mutual state visits; the emperor visited Norway in 1954, and King Olav visited Ethiopia in 1966. Norway is one of the first training assistance provider when Ethiopia form her Navy force in Massawa and Assab.Currently Ethiopia is under dictatorship and ethnic rule of power.At the result millions displaced and refugee in all over the world others are living in miserable life. We all have reasonable hope as Norway will play a key role in assisting Ethiopians struggle towards Democracy.
=================
Norge og Etiopia
Sterke bånd mellom Etiopia og Norge ble dannet under den andre verdenskrig da keiser Haile Selassie av Etiopia og den norske kongefamilien møtte i London. Dette førte til gjensidige statsbesøk; keiseren besøkte Norge i 1954, og kong Olav besøkte Etiopia i 1966.Norge er en fo første trening bistand leverandøren når Etiopia danne hennes Navy kraft i Massawa og Assab.Foreløpig Etiopia er under dictator go etnisk regel malt. På resultatet millioner fordrevne og flyktninger i hele verden og andre lever i miserable liv. Vi har rimelig håp som Norge vil spille en nøkkelrolle i å hjelpe Etiopias kamp mot demokrati. Vi har rimelig håp som Norge vil spille en nøkkelrolle i å hjelpe Etiopias kamp mot democrat.


ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ግንቦት 3/2007 ዓም ( May 11/2015)

Friday, May 8, 2015

ሰበር ዜና - ኖርዌይ በመጪው የኢትዮጵያ ምርጫ ወቅት ዜጎቿ ከምርጫው በፊት፣በምርጫው ወቅት እና ከምርጫው በኃላ ከምርጫ አካባቢ፣ሕዝብ ከተሰበሰበባቸው ቦታዎች እና ከሰላማዊ ሰልፎች አካባቢ እራሳቸውን እንዲያርቁ አስጠነቀቀች



የኖርዌይ መንግስት ዛሬ ሚያዝያ 30/2007 ዓም ባወጣው መግለጫ ''መረጃ ለኖርዌጃውያን ዜጎች በሙሉ'' በሚል የጀመረው መግለጫ ''ወደኖርዌይ የሚሄዱ ዜጎች ምርጫው እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ግንቦት 24/2015 ከመደረጉ በፊት፣በምርጫው ወቅትም ሆነ ከምርጫው በኃላ ምርጫው በሚፈፀምበት አካባቢ ዜጎች እንዳይገኙ እና ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።ማሳሰቢያው በመቀጠልም የኖርዌይ ዜጎች እራሳቸውን ሕዝብ በብዛት ከተሰበሰቡበት ቦታዎች እና ሰላማዊ ሰልፍ ከሚደረግባቸው ቦታዎች በሙሉ እራሳቸውን እንዲያርቁ ያሳስባል።ከእዚህ በፊት በነበሩት ምርጫዎች እንደታየው ስልክ እና ኢንተርኔትም  ሊቆረጥ ስለሚችል አሁንም ዜጎች ጥንቃቄ አድርጉ ሲል መግለጫው ያብራራል።

ኖርዌይ የኢትዮጵያን ምርጫ አስታኮ የስጋት መግለጫ በመስጠት ከምዕራባውያን ሀገሮች ቀዳሚ ሆናለች።ኖርዌይ በአውሮፓ ህብረት ውስጥ የኢትዮጵያን ሰብአዊ መብት ይዞታ ጉዳይ እንድትከታተል የተመረጠች ሀገር መሆኗ ይታወቃል። የኖርዌይ መንግስት ያወጣውን መግለጫ በኖርዌጅያን እና እንግሊዝኛ ቋንቋ ከእዚህ በታች ይመልከቱ።
=====================================

Valg i Etiopia - informasjon til norske borgere

Sist oppdatert: 08.05.2015 // Den norske ambassaden i Addis Abeba oppfordrer norske borgere til å utvise aktsomhet ved reiser til eller opphold i Etiopia før, under og etter det etiopiske valget 24. mai 2015. 
Vi anbefaler alle å unngå demonstrasjoner og andre større folkeansamlinger. Norske borgere bør også holde seg unna valglokalene på valgdagen, og være oppmerksom på spesielle forbud, f.eks. fotoforbud, ved valglokaler eller andre steder av politisk betydning. Ambassaden anbefaler videre norske borgere å holde seg løpende oppdatert via lokale media og internett. Vi gjør for øvrig oppmerksom på at telefon- og internettjenester tidvis kan komme til å bli sperret, da dette har forekommet under tidligere valg i Etiopia. 
Ambassaden anbefaler alle norske besøkende å registerer seg på utenriksdepartementets portal for utenlandsopphold (www.reiseregistrering.no)
=======================================================
Election in Ethiopia - information to Norwegian citizens
Last updated: 05/08/2015 // The Norwegian Embassy in Addis Ababa encourage Norwegian citizens to exercise caution when traveling to or stay in Ethiopia before, during and after the Ethiopian elections on 24 May 2015.
We advise everyone to avoid demonstrations and other large gatherings of people. Norwegian citizens should also stay away from the polling stations on election day, and be aware of specific bans, for example. foto ban, at polling stations or other places of political importance. The embassy recommends Norwegian citizens to remain continuously updated via local media and the internet. Please also be aware that telephone and internet services can occasionally come to be blocked, as this has occurred during previous elections in Ethiopia.
The embassy recommends all Norwegian visitors to register on the State Department's portal for study abroad (www.reiseregistrering.no)

ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።