ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, October 30, 2021

ኢትዮጵያን እንደሶርያ ሊበትናት ከተነሳው የትግራይ ወራሪ ለማዳን በሚልዮን የሚቆጠር ኢትዮጵያውያዊ አሁንም መነሳት አለበት።ሰሜን ወሎ ዋግህምራ ዞን የሰቆጣ እና አበርጌላ ዙርያ በኢትዮጵያ ኃይሎች እጅ ገብቷል።አሁን 8 ጉዳዮች ትኩረት ይፈልጋሉ።



===============
ጉዳያችን/ Gudayachn
===============
ኢትዮጵያን ለማፍረስ የባዕዳንን ቅጥረኝነት የወሰደው በህወሓት የሚመራው የትግራይ ወራሪ ቡድን በቀጥታ ከውጭ በሚሰጠው መመርያ መሰረት የህዳሴ ግድቡን እንዲያፈርስ ሁሉ ኃላፊነት ወስዶ ኢትዮጵያን ለማጥፋት እየዋተተ ነው። የትግራይ ወራሪ በምንም ዓይነት መንገድ እንጦጦ ቢደርስ መልሶ ኢትዮጵያን አይመራም።ዛሬ 1983 ዓም አይደለም።መደናበር የለም።ጠላትን መምጣት የመከላከያ ኃላፊነት ብቻ አይደለም።የኢትዮጵያ ሕዝብ ኃላፊነቱን ተቀብሏል።ድሮም ኢትዮጵያ የኖረችው እንዲህ ነው።ሁሉም ለሀገሩ ዘብ እየቆመ።ሰላም በምኞት አልመጣም።ከህወሓት ጋር ውይይትም ፈፅሞ እንደማይታሰብ ያለፉት ዓመታት ተሞክሮዎች ግልጥ ያደርጋሉ።

 አሁንም የኃይል ሚዛን በኢትዮጵያ እጅ እንደሆነ ምንም ጥርጥር የለውም።በአስር ሚልዮኖች የሚቆጠር የሰው ኃይል ሆነ ሀብት ያለው በኢትዮጵያ ኃይሎች ስር ነው።ከተሞችን ያዝን የሚሉት ከውስጥ ያሉ ባንዳዎች ቀድመው አውራ ጎዳና እየወጡ ሕዝቡን ለማደናበር ስለሞከሩ መሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል።ህወሓት ወደ መሃል ሀገር የመጣበት መንገድ ዋና ምክንያቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠር የታጠቀም ያልታጠቀም ሕዝብ አግተልትሎ ስለላከ ነው።መከላከያ፣ፋኖ እና ሚሊሻ በሺህ የሚቆጠሩትን ገድሏል።ወሎ በወራሪ የትግራይ ሰራዊት አስከሬን ተሞልቷል።ይህም ሆኖ በሺህ የሚቆጠር እንደ ሕዝብ እየላከ ነው።ለእዚህ ነው እንደ ሕዝብ ሁሉም ሲነሳ ነው ታሪክ የሚቀየረው የተባለው።

አሁን ስምንት ጉዳዮች ትኩረት ይፈልጋሉ።

1) በዋናነት አካባቢውንም ሀገሩንም በሚገባ የሚያቀው የአማራ ሕዝብ በሚልዮን ቁጥር ሆኖ ከቤቱ ያለውን ማናቸውንም መሳርያ ይዞ መነሳት አለበት።እንደ ሕዝብ የመጣ ወራሪ እንደህዝብ መነሳት አለበት።ማንም ለማንም ብሎ አይነሳም።ለራሱ፣ለልጆቹ እና ለሚስቱ ከመገደል ከመዘረፍ እና ከመደፈር ለማዳን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ እንዳትፈርስ የማዳን የሕልውና ጦርነት ስለሆነ።

2) በአማራ ክልል በዞን እና ወረዳ ደረጃ ያሉት አመራሮች አሁንም በሙስና እና በገንዘብ ጉጉት የናወዙ ሕዝብ ብዙ ነገር እያየ የታገሳቸው አሁንም በተልፈሰፈሰ አመራር እና ባልቆረጠ ልብ ሕዝብ ወደኃላ እየጎተቱት ነው።እነኝህን አሁን ካለው ጊዜ አንፃር መቀየር ባይቻልም በቶሎ በተለየ የጦርነት መዋቅር ከጎናቸው ሌሎች ሕዝብ እንዲያስተባብሩ ማስገባት ያስፈልጋል።

3) በህወሓት የሚመራው የትግራይ ወራሪ በመንግስት መዋቅርም ሆነ በንግድ ዘርፍ ሕቡዕ አደረጃጀት ያለባቸው ከተሞች ማለትም ደሴ፣ኮምቦልቻ እና አዲስ አበባ በቶሎ የጁንታው መዋቅር መፍረስ አለበት።በተለይ በአዲስ አበባ ሕዝብ የሚያውቃቸው ነገ ከተማዋን ቀድመው ለማንደድ የቆሙ ባንዳዎች እንዳሉ ሕዝብ አሁንም እየተናገረ ነው።ደሴ ላይ ትናንት እና ዛሬ የሆነው ትምህርት ነው።አብረው ከ30 ዓመት በላይ የኖሩ የትግራይ ወራሪ የቀረበ ሲመስላቸው ቀድመው ወደ መንገድ ወጥተው ከውጭ እንደገባ የጁንታው ሰራዊት ሕዝብ ሊረብሹ ሲሞክሩ ተይዘዋል።በአዲስ አበባም መከላከያ መቀሌን ለቆ ሲወጣ የጨፈሩት ዓይነት ከሃዲዎች መታየታቸው ነገ ከተማውን ለማፍረስ ቀዳሚ እንደሆኑ ትምህርት ሊሆን ይገባል።ከተሞች ውስጥ ከቤት ለቤት ፍተሻ አስፈላጊ ነው።

4) የትግራይ ወራሪ ትኩረቱን ወደ ደሴ ያደረገው አንዱ ምክንያት የምዕራብ ግንባርን ለማሳሳት መሆኑን መገመትም ተገቢ ነው።በእዚህ መሰረት የምዕራብ ግንባር ማጠናከር ችላ ሊባል አይችልም ይልቁንም እስከ ሽሬ አነስተኛ ኃይል በመላክ ጁንታውን የማዳከም ሥራ ሊሰራ ይገባል።

5) የህወሓትን ፕሮፓጋንዳ በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ውስጥ ሆነው የሚሰሩ አሉ።እነርሱም 
- አስፈላጊ የሆኑ ፕሮግራሞች በወቅቱ ለሕዝብ እንዳይደርሱ፣
- ዜናዎች ቶሎ በዩቱብ እና ማኅበራዊ ሚድያ ፕላትፎርም ላይ እንዳይጫኑ በማዘግየት፣
- የዜና ርዕሶቹ አሰልቺ እንዲሆኑ በማድረግ ሕዝቡን ማሰላቸት፣
- ኤዲት ተደርገው መቅረብ ያለባቸው ንግግሮች እና ፕሮግራሞች እንዳለ በማቅረብ መንግስትን ማሳጣት እና ሌሎችም እየሰሩ ነው።

6) የህወሓት ፕሮፓጋንዳ ወይንም ሌላ አፍ የሆኑ ዩቱበሮች እና ተቃዋሚ መሰል እንዲሁም በአማራ እና ኦሮሞ ስም የሚነግዱትን ፊት ለፊት ማጋለጥ እና የቅጣት እርምጃ ያስፈልጋቸዋል። ሀገር የመፍረስ አደጋ ላይ ሆና እነርሱ ሌላ ነዳጅ ሲጨምሩ መተው አይቻልም።ሁሉም የማንንም ጥያቄ ሳይቀበል በራሱ ዝም ማሰኘት አለበት።

7) ቁልፍ በሆኑ የባንክ እና ፋይናንስ እንዲሁም የአይቲ ኃላፊነት ላይ ያሉ ለጁንታው በመስራት የሚጠረጠሩ ሁሉ ለጊዜው ኃላፊነታቸው መዘግየት አለበት።ይህ የሀገር ጉዳይ ነው።

8) ከምሁር፣እስከ ባለሀብት፣በውጭ ከሚኖሩ የወታደራዊ ባለሙያዎች እስከ ወጣት ወንዶች እና ሴቶች ሁሉ ኢትዮጵያ አደጋ ላይ ስትሆን ዛሬም ተቀምጠው የሚያዩ፣ቢያንስ ሕዝብን በመቀስቀስ የማይሳተፉ የዳር ተመልካቾች አሁንም ዝምታቸውን መስበር እና እኔ ምን ላድርግ? ብለው መጠየቅ እና ከችሎታቸው አንፃር የድርሻቸውን ለክተው ለኢትዮጵያ አንድ ነገር መወርወር ያለባቸው ጊዜ አሁን ነው።ዘመን ይቀየራል።ኢትዮጵያም ከፈተናዋ ሁሉ በልጆቿ ትድናለች።ያን ጊዜ ግን ማን ዝም ብሎ አየ? ማን ለሀገሩ ያለውን ወረወረ? የሚታይበት ጊዜ ይመጣል።

የትግራይ ወራሪ መቸም የትም ቢደርስ የኢትዮጵያን ሕዝብ አይገዛም።በእርግጥ የትግራይ ወራሪ አስከሬን ይበዛል።ጁንታው እና የጁንታው ደጋፊዎች ያልተረዱት ጉዳይ የኢትዮጵያ ሕዝብ የዘር ማጥፋት ውስጥ እንዳይገባ እንጂ በእዚህ ደረጃ ከገፋፉት ግን አደገኛ ሁኔታ አይፈጥርም ማለት አይቻልም።ወደ ሲኦል እስክንገባ ኢትዮጵያን እናፈርሳለን እና አማራን እንበቀላለን ብለው የተናገሩትን መቼም የማይረሳ ነገር ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ በማሸነፍ እና አስፈላጊውን ፍርድ በመስጠት ይደመደማል።

ይህ በእንዲህ እያለ  ሰሜን ወሎ ዋግህምራ ዞን የሰቆጣ እና አበርጌላ ዙርያ በኢትዮጵያ ኃይሎች እጅ ገብቷል።በፋኖ እና ሚሊሻ የታጀበው የሰሜን ወሎ ጦርነት ቀጥሏል።የትግራይ ወራሪ ኃይል ከትግራይ እየራቀ በተለጠጠ ቁጥር ወደ ደቡብ ወሎ ሲገፋ ከላይ ከሰቆጣ የኢትዮጵያ ኃይሎች ቆርጠውታል። ይህ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሁንም ወጣቶች ማንንም ሳይጠብቁ ወደ ግንባር ሄደው ሀገራቸውን እንደ ሶርያ ከመፈረስ መታደግ ያለባቸው ጊዜ አሁን ነው።ሀገር በማኅበራዊ ሚድያ እና ፌስ ቡክ አይድንም።መሬት ላይ ያለውን ሥራ በመስራት ለውጥ ይመጣል።  

===========///==========

Friday, October 29, 2021

የፍትህ ሚኒስቴር በሰሜን እና ደቡብ ጎንደር እና በአፋር ክልል በህወሃት የሚመራው የትግራይ ወራሪ ቡድን በንጹሃን ላይ የፈጸመው ወንጀል ዛሬ ያቀረበው ሪፖርት

⮚ አንድን ሴት እስከ አስራ አምስት በመሆን እየተፈራረቁ ደፍረዋታል፤
⮚ እናት እና ልጅን በአንድ ላይ ደፍረዋቸዋል፤
⮚ ከተፈጥሮ ተቃራኒ የወሲብ ጥቃቶች ፈጽመዋል፣
⮚ ልጆችን በእናቶቻቸው ፊት ደፍረዋል፤
⮚ አንዲትን ሴት ከደፈሩ በኋላ በጠመንጃ አፈሙዝ ብልቷን በመውጋት የፌስቱላ ተጠቂ እንድትሆን አድርገዋታል፤
⮚ የ8 ወር እመጫትን ጨቅላ ልጇን በፈላ ዉሃ ዉስጥ እንጨምራለን በማለት እናትዋን አስፈራርተው ደፍረዋታል፤
⮚ አንዲት የሰባት ወር ነፍሰ ጡር ሴትን ለሶስት አስገድዶ ደፍረዋታል፤
====================
ሙሉ የሪፖርቱን ይዘት በጽሁፍ እና የቪድዮ ሪፖርት ከስር ያገኛሉ።


በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን እና ደቡብ ጎንደር ዞኖች ስር በተወሰኑ አካባቢዎች እንዲሁም በአፋር ክልል በሚገኙ ወረዳዎች በንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ወንጀል ምርመራን እና የመጀመሪያ ደረጃ ግኝቶችን ውጤቱን አስመልክቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
......................................................................
አዲስ አበባ ጥቅምት 19/2014 ዓ.ም (አደባባይ ሚድያ)
.......................................................................
መግለጫው በኢ.ፌ.ድ.ሪ የፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ እና በፌደራል ፖሊስ እንዲሁም ከክልል የምርመራ አካላት ጋር በትብብር በተዋቀረ የዐቃቤ ሕግ እና የፖሊስ የምርመራ ቡድን አማካኝነት የተከናወነ የወንጀል ምርመራ የመጀመሪያ ደረጃ ውጤት ለመግለጽ የተዘጋጀ ነው። ምርመራው የተካሄደው በአፋር እና በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሚገኙ በአሸባሪው ህወሃት ተይዘው በነበሩ እና ኋላ ላይ በሕግ ማስከበሩ ዘመቻው ነጻ በወጡ አካባቢዎች ላይ ነው።

የምርመራ ቡድኑ ቀድሞ በተሰጠው እቅድ እና ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ መሰረት ያከናወነው ምርመራ ትኩረቱን ያደረገው ከሰኔ ወር 2013 ዓ.ም. ጀምሮ መንግስት የተናጠል ተኩስ አቁም ካወጀ በኋላ የህወሃት አሸባሪ ቡድን በአፋር እና በአማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ መጠነ ሰፊ ወረራ በማካሄድ የአለም አቀፍ ሕግ ድንጋጌዎች እና የአለም አቀፍ የሰብዓዊነት ሕግጋትን በመጣስ በሰላማዊ ሕዝብ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ሲፈጽም ከቆየባቸው አካባቢዎች መካከል በደቡብ ጎንደር ዞን የላይ ጋይንት ወረዳ፣ የንፋስ መውጪያ ከተማ አስተዳደር፣ የጉና በጌምድር ወረዳ፣ የፋርጣ ወረዳ፣ እስቴ ወረዳ /በከፊል/፣ ደብረታቦር ከተማ አስተዳደር /በከፊል/ ፤ በሰሜን ጎንደር ዞን ደግሞ በዳባት፤ደባርቅ እና ዛሪማ ንዑስ ወረዳዎች እንዲሁም በአፋር ክልል ጋሊኮማ ቀበሌ በሚገኝ የተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያ እና በፈንቲረሱ ዞን ሥር በሚገኙ እዋ፣ አውራ እና ጉሊና ወረዳዎች ላይ ባልታጠቁ እና ሰላማዊ ህዝብ ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎችን ብቻ በመሆኑ ምርመራው በመንግስት በኩል ሕግ ለማስከበር ተሳታፊ የሆኑ ተዋጊ ወታደሮችን እና አጋዥ አካላት ለአብነትም ምርኮኞች ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎችን አያካትትም፡፡

ወንጀሉ በአሸባሪው ድርጅት መሪነት ከሐምሌ 2013 ዓ.ም ጀምሮ አካባቢዎቹ በፌዴራል እና በክልል የጸጥታ አካላት ቁጥጥር ስር ተመልሰው እስከ ገቡበት ጊዜ ድረስ ባሉት ጊዜያት የተፈጸሙ ሲሆን ምርመራው ከተጀመረበት ከመስከረም 05 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ እስከአሁን ድረስ የደረሰበትን የመጀመሪያ ደረጃ ግኝቶችን ለህዝብ ለማሳወቅ ስለሆነ በምርመራው ቀጣይነት የሚገኙ አዳዲስ ውጤቶች በቀጣይ በሚቀርቡ ሪፖርቶች የሚገለጽ ይሆናል፡፡
በዚህ መሰረት በደቡብ ጎንደር ዞን የተሰማራው የምርመራ ቡድን በጠቅላላው ከ790 በላይ ምስክሮችን የምስክርነት ቃል ፣ በሰሜን ጎንደር ዞን የተሰማራው የምርመራ ቡድን ደግሞ 285 የምስክሮች ቃል እንዲሁም በአፋር ክልል የተሰማራው ቡድን 148 ምስክሮች ቃል ተቀብሏል፡፡ ሶስቱም ቡድኖች ከተጠቀሰው የተጎጂዎችና ቀጥታ ምስክሮች የምስክርነት ቃል በተጨማሪ ከምስክርነት ቃል ውጭ ወንጀሎቹን ሊያስረዱ የሚችሉ የሰነድ ማስረጃዎችን፣ ገላጭ ማስረጃዎችን ፣ኤግዚቢቶችን እንዲሁም የቴክኒክ ማስረጃዎችን ለማሰባሰብ ችለዋል፡፡

በውጤት ደረጃም አሸባሪው ቡድን በሰሜን ጎንደር ዞን ለጊዜው በዝርዝር ማስረጃ የተለዩ የ96 ሰዎች ሞት፣ 53 የአካል ጉዳት፣ 29 አስገድዶ መደፈር፣ 11 ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ፣ 6 እገታ እንዲሁም የመንግስት፣ የግል እና የሀይማኖት የተለያዩ ተቋማት ንብረቶች ላይ መጠነ ሰፊ ዘረፋና ውደመት መፈጸሙ ተረጋግጧል፡፡ በደቡብ ጎንደር ዞን ባሉ አምስት ወረዳዎች ደግሞ በድምሩ የ129 ሰዎች ሞት፣ የ54 ሰዎች የአካል ጉዳት፣ በንፋስ መውጫ ከተማ ብቻ የ73 ሴቶች የአስገድዶ መድፈር ወንጀል እንዲሁም በርካታ ግለሰቦች ንብረት ላይ ውድመት ደርሷል፡፡ በሌላ በኩል በአፋር ክልል ነሃሴ 29 ቀን 2013 ዓ.ም. በጋሊኮማ ቀበሌ መጠለያ ጣቢያ ላይ በተፈጸመ ጥቃት የ240 ሰዎች ሞት፣ 42 ሰዎች የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን በቀሪዎቹ ሶስት ወረዳዎች ደግሞ የ17 ሰዎች ሞት እና ለ17 ሰዎች የአካል ጉዳት እንዲሁም 7 ሴቶች የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች እንደተፈጸመባቸው ተረጋግጧል፡፡

በሁለቱም ክልሎች ከሰላማዊ ዜጎች ንብረት በተጨማሪ በመንግስት እና በግል ተቋማት ላይ ማለትም ት/ቤቶች፣ ጤና ኬላዎች፣ የህብረት ስራ ማህበራት እንዲሁም በአብያተ ክርስቲያናት፣ በመስጊዶች እና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ላይ የዘረፋ እና ውድመት ድርጊቶች በስፋት መፈጸማቸው ተረጋግጧል፡፡
ድርጊቱ ሲፈጸምም የግለሰብ ቤቶችን እንደ ምሽግ መጠቀም፣ ታሪካዊ እና ሀይማኖታዊ ቦታዎችን እንዲሁም እንደ ዩኤስኤይድ፣ አክሸን ኤይድ እና በመንገድ ስራ ላይ የተሰማራ የቻይና መንገድ ተቋራጭ ድርጅትን ንብረቶችን ኢላማ ያደረገ ጭምር ነበር፡፡ እነዚህን ንብረቶች ለመዝረፍም የባለሙያ እገዛ የሚያስፈልጋቸውን በመለየት በተጠና እና ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ በሜካኒክ ፈትቶ እስከመውሰድ የደረሰ የዘረፋ ድርጊቶች ተስተውለዋል፡፡

ወንጀል አድራጊዎቹ ተቆጣጥረውት በነበርዋቸው ቦታዎች ድርጊቱን ሲፈጽሙ ከተናገሩት፣ ቤቶች ላይ በቀለም በተጻፉ ጽሁፎቻቸው እንዲሁም በወቅቱ የወንጀል ድርጊቱን ሲፈጽሙ ሲናገሩ ከነበሩት በመነሳት ለማረጋገጥ እንደሚቻለው አሸባሪው ድርጅት ይህንን መጠነ ሰፊ ጥቃት የፈጸመበት ዋንኛ አላማ ብሄር ተኮር ከሆነ ጥላቻ የመነጨ እና በአሸባሪው ድርጅት የበላይ አመራሮች ውሳኔ እና ትእዛዝ በብሄር የተመሰረተ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ፣ የተወሰነ ብሄርን እንደማህበረሰብ በኢኮኖሚ እና በሞራል የተጎዳ እንዲሆን ለማድረግ ከድርጊት በተጨማሪ ጸያፍ የሆኑ ስድቦችን በመጠቀም እና በመፈረጅ፣ የፌደራል መንግስት ተረጋግቶ ሀገር እንዳይመራ ለማድረግ፣ ህወሃት ከሌለ ሀገር አትመራም በማለት የተዳከመ የፌደራል መንግስት እንዲኖር ለማድረግ፤ ማህበረሰብ ባህሉ እሴቱ እና መሰረታዊ ስሪቱ እንዲጠፋ የማድረግ አላማ አድርጎ የተነሳ መሆኑን በምርመራው ሂደት የታዩ እውነታዎች ያስረዳሉ፡፡

በአጠቃላይ ከላይ በተገለጸው አግባብ አሸባሪው ቡድን ወንጀሉን ለመፈጸም ከተነሳበት ምክንያት እና ከምርመራው ግኝት ለማሳያነት የሚቀርቡ ዋና ዋና አሰቃቂ ኢሰብአዊ ድርጊቶች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡-
የአስገድዶ መድፈር ወንጀልን በተመለከተ፤-
⮚ አንድን ሴት እስከ አስራ አምስት በመሆን እየተፈራረቁ መድፈር፤
⮚ እናት እና ልጅን በአንድ ላይ መድፈር፤
⮚ ከተፈጥሮ ተቃራኒ የወሲብ ጥቃቶችን መፈፀም፣
⮚ ልጆችን በእናቶቻቸው ፊት መድፈር፤
⮚ አንዲትን ሴት ከደፈሩ በኋላ በጠመንጃ አፈሙዝ ብልቷን በመውጋት የፌስቱላ ተጠቂ እንድትሆን ማድረግ፤
⮚ የ8 ወር እመጫትን ጨቅላ ልጇን በፈላ ዉሃ ዉስጥ እንጨምራለን በማለት እናትዋን በማስፈራራት መድፈር፤
⮚ አንዲት የሰባት ወር ነፍሰ ጡር ሴትን ለሶስት አስገድዶ መድፈር፤
⮚ የመደፈር ወንጀል የደረሰባቸው ሴቶች ለአባላዘር እና ለአእምሮ ጤና መታወክ በሽታዎች ተጋላጭ ማድረግ፤
⮚ የተለየ የስነ ልቦና ጫና ለማድረስ በሚል የማህበረሰቡ ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ እሴቶች የሆኑትን የካህናት ሚስቶችን እና ቆራቢ መነኮሳትን ለይቶ አስገድዶ መድፈር፤
⮚ በአፋር ክልል ሴቶችን ለረዥም ጊዜ አግቶ በማቆየት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በተደጋጋሚ በመፈጸም እና የህክምና እርዳታም ሳያገኙ አቆይተው መልቀቀ ናቸው።
የተለየ ጨካኝነትን እና ነውረኝነትን የሚያሳዩ የግድያ እና ተያያዥ ወንጀል ድርጊቶች
⮚ ከ30 ቀን ጨቅላ ህጻን እስከ 70 ዓመት ሽማግሌ ድረስ ተጠቂ የሆኑባቸው ግድያዎች መፈጸማቸው፤
⮚ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ 6 ሰዎችን በጅምላ መግደል፤
⮚ በአብያተ ክርስቲያናት እና በመስጊዶች ውስጥ የነበሩ የሃይማኖት አገልጋዮችን መግደል፤
⮚ በዳባት ወረዳ ጭና ቀበሌ ሟች ጥላሁን ንጉሴ የተባሉ የ68 ዓመት አዛውንትን ጭንቅላቱን በጥይት በመምታት ገድለው ለአምስት ቀናት በቤት ውስጥ ሳይቀበር ሚስቱን ከአስክሬኑ ጋር በዚያው ቤት በማቆየት ለገዳዮች ምግብ እንድታዘጋጅ ማስገደድ፤
⮚ ደባርቅ ወረዳ አብርሃም ቀበሌ ሟች ዘለቀ አስመራ የተባለ አባትን ከህጻን ልጁ ፊት አንገቱን በማረድ ሶስት ልጆቹ እግሩን እና እጁን እዲይዙ በማድረግ ከአንገቱ እስከ ሆዱ በልጆቹ ፊት በሳንጃ አካሉን መሰንጠቅ፤
⮚ የማህበረሰቡ መኖሪያ ቤቶችን የሞቱ የሽብር ቡድኑ አባላትን ለመቅበሪያነት እና ለመጸዳጃ ቤት ለምግብ ማብሰያነት መጠቀም፣ እንዲሁም ቤቶችን በማፍረስ ፤
⮚ ሰዎችን በማገት አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን መፈጸም [በዚህም ብዙ ሰዎች እስከ አሁን የደረሱበት አልታወቀም]፤
⮚ በአፋር ክልል የስድስት ወር ህጻን የእናቱን ጡት እንደያዘ በከባድ መሳሪያ ከእነ እናቱ ተመትቶ ተገድሏል፡
⮚ በአፋር ክልል ሙሉ የስደተኛ ጣቢያ ላይ የተጠለሉ ስደተኞች በተኙበት ከሌሊቱ 9 ሰዓት ላይ የጅምላ ከባድ ተኩስ በመክፈት በተኙበት እንዲያልቁ አድርገዋል፤
በንብረት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎች
⮚ በመንግስት የጤና ተቋማትን መዝረፍ እና ሙሉ በሙሉ በማውድም ከአካባቢው ማህበረሰብ ባለፈ በወንጀሉ የአስገድዶ መድፈር እና የአካል ጉዳት የደረሰባቸውን ተጎጂዎች የህክምና አገልግሎት እንዳያገኙ ማድረግ፤
⮚ ማህበራዊ አገልገሎት የሚሰጡ ባንኮችን፣የቴሌኮም መሰረተ ልማቶች ላይ፣ የመብራት ኃይል አውታሮች ላይ ዘረፋ እና ጉዳት ማድረስ፤
⮚ አሸባሪው ቡድን በወረራቸው አካባቢዎች የግለሰብ ንብረት የሆኑ እንስሶችን በጥይት መግደል በተለይም ለእርሻ አገልግሎት የሚውሉ በሬዎችን እና የጋማ ከብቶችን፣ ለወተት የሚውሉ ላሞችን መግደል እና በራሳቸውም ለሽያጭ እና ለምግብነት የሚውሉ ዶሮዎችን መዝረፍ እና መግደል በአጠቃላይ ማህበረሰቡን ማደህየትን ዓላማ አድርጎ የተፈጸመ ሲሆን፤ ከዚህ ጋር በተያያዘም ከማህበረሰቡ እሴት እና ሞራል ፍጹም ተቃራኒ በሆነ መንገድ እርጉዝ ላምን ገድሎ ሽሏን በማውጣት ጠብሶ መብላት፤ ያልደረሱ እና ያልበሰሉ አትክልት እና ጥራጥሬን መመገብ፤ በተቆጣጠሩባቸዉ አካባቢዎች የቤት እንስሳትን እና ከብቶችን መግደል፣ በአጠቃላይ የገበሬው ህልውና መሰረት በሆኑት ነገሮች ላይ ፋት በመፈጸም፤
⮚ የገበሬውን አዝመራ አጭዶ መውሰድ አልያም የአትክልት ምርቶችን መንቀል እንዲሁም ለመሰብሰብ ያልደረሰውን ሰብል ማቃጠል እና ምርት እንዳይሰበሰብ በተሸከርካሪ እና በከባድ መሳሪያዎች መዳመጥ፤
⮚ ከጦርነት ቦታዎች በብዙ ኪሎሜትሮች በሚርቁ አካባቢዎች ላይ የከባድ መሳሪያ /የመድፍ/ ጥቃት መፈጸም፤
አለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶችን በተመለከተ
⮚ ለሰብዓዊ እርዳታ የሚውሉ መኪኖችን እና ምግቦችን ለጦርነት አላማ ማዋል፤
⮚ ንብረቶቻቸውን መዝረፍ፤ ለአብነት ያህል በደቡብ ጎንደር ዞን ጋይንት ወረዳ ንብረትነቱ ዩኤስኤድ/ ኤፍ ኤች ኢትዮጵያ/ የዋጋ ግምቱ 19 539 918.68 ብር የሚያወጡ ለድንገተኛ አደጋ ተጎጂዎች የሚውል 482.9569 ሜትሪክ ቶን የምግብ እህል፣ የመጋዘን እቃዎች ሞተር ሳይክ፣ መኪኖች እና ሌሎች ንብረቶች ተዘርዋል፤
የእምነት ተቋማትና አምልኮ ስፍራዎችን በተመለከተ
 አብያተ ክርስቲያናትና መስጊዶችን ለወታደራዊ ዓላማ ከመጠቀም በተጨማሪ ማቃጠልና ማውደም ለአብነትም በደቡብ ጎንደር ዞን ውስጥ የሚገኙ 22 አብያተ ክርስቲያናትና 1 መስጊድ በከባድ መሳሪያ በመምታት ማውደም፤ ንብረቶቹንም መዝረፍ
 ከሀይማኖታዊ እሴት ያፈነገጠና ነውነኝነትን በሚያሳይ ሁኔታ ለቁርባን የተዘጋጀን እህል በመዝረፍና በመጠቀም ሀይማኖታዊ ተግባርን የማራከስ ድርጊት መፈፀም
በአጠቃላይ ምርመራው በሂደት ላይ ያለ ከመሆኑ አንጻር እስከ አሁን በተደረሰበት ብቻ በሽብር ድርጅቱ እና በአባላቱ በሁለቱም ክልሎች በተፈጸሙት የወንጀል ድርጊቶች 482 ሞት፣ 165 የአካል ጉዳት እና 109 የአስገድዶ መድፈር ኢሰብዓዊ ድርጊቶች የተፈጸሙ ሲሆን ንብረትን በተመለከተ በመቶ ሚሊዮኖች የሚገመት ንብረት ውድመት እና እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ላለው ሰላማዊ ዜጋ ከቤት ንብረቱ መፈናቀል ምክንያት ሆኗል፡፡ ለአብነትም በአፋር ክልል 112,158 ዜጎች ፣ በሰሜን ጎንደር 135,310 ዜጎች እንዲሁም በደቡብ ጎንደር ከ 47000 በላይ ዜጎች ተፈናቅለዋል፡፡

በሌላ በኩል ምርመራው ያልተጠናቀቀ እንደመሆኑ በቀጣይ በተጠቀሱት ቦታዎች የተሰማራው የምርመራ ቡድን የጀመረውን ስራ በማጠናቀቅ ወንጀል ፈፃሚዎችን ለሕግ ለማቅረብ እንዲቻል ስራዎችን አጠናክረን የምንቀጥል ሲሆን ምርመራው ወዳልደረሰባቸው ቦታዎች ጭምር ሌሎች ቡድኖችን በማዋቀር ሰፊ የምርመራ ስራ ማካሄድ እና በየደረጃው ለህዝብ ማሳወቅ የሚሰራበት መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

የአሸባሪው ቡድን በአማራና አፋር ክልሎች የፈጸመው ወንጀል ሪፖርት

ፋና ብሮድካስቲንግ ጥቅምት 19/2014 ዓም (ኦክቶበር 29/2021 ዓም)



ሰበር ዜና - ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ በመሩት የሁሉም ክልሎች ፕሬዝዳንቶች እና የፀጥታ ኃይሎች በተሳተፉበት ዛሬ በባሕርዳር ተሰብስበው በሽብርተኛው ህወሓት ላይ ውሳኔ አሳልፏል።በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጥሪ አስተላልፏል።የመልዕክቱን ሙሉ ቃል ቪድዮ ይመልከቱ።

ቪድዮ - ኢቢሲ 
ቀን =ዓርብ ጥቅምት 19/2014 ዓም ባህርዳር ከተማ

Wednesday, October 27, 2021

የኢትዮጵያ ሕዝብ ጦርነት የጀመረው አሁን ነው። በህወሓት የሚመራው የትግራይ ወራሪ ቡድን ጀሌውም ሆነ የመሃል ሀገር ደጋፊው ከሞያሌ እስከ መቀሌ ይነቀላል።

  • ከፅሁፉ ስር የህወሓት እና የሸኔ ምስጢራዊ  የስልክ ንግግር የያዘ ዶክመንተሪ ፊልም ያገኛሉ።

የትግራይ ወራሪ ቡድን መሪ ደብረፅዮን ደሴ እና ኮምቦልቻ የተቆጣጠረ ይመስል።በአማራ ላይ የበቀል ጅራፋችንን ጨርሰናል የሚል መሰል ንግግር ተናግረዋል።ጦርነቱን ጨርሰናል የምትለውን ቃል ደብረፅዮንም ሆነ ጌታቸው ረዳ ለምን እንደሚጠቀሙ ከእዚህ በፊት በጉዳያችን ላይ ''...የመጨረሻ ውግያ የሚሉ ቃላት ሰሞኑን መጠቀም የፈለገባቸው ሦስት ምክንያቶች ታውቀዋል።'' በሚል ርዕስ ስር ለማብራራት ተሞክሯል።ላማንበብ ከላይ ርዕሱን ከፍተው ያንብቡ።

የትግራይ ወራሪ ቡድን የትግራይን ሕዝብ በብዛት በማምጣት ከአሮጊት እስከ ታዳጊ ወጣት እያስፈጀ አስከሬን በአስከሬን እየሆነ ነው ወሎ የደረሰው።የኢትዮጵያ ኃይሎች አሁን ከመቼውም ጊዜ በላይ በብዛት የሰለጠነ የጦር ኃይል በአጭር ጊዜ ተዘጋጅተዋል።ከጎጃም እስከ ጎንደር ልዩ ኃይል፣ከወሎ እና ሸዋ ፋኖ፣ከኦሮምያ እና ሱማሌ ልዩ ኃይል እስከ የደቡብ ዘማች የትግራይን ወራሪን ለመቅበር ተነስቷል።የጎንደር ፋኖ ለወሎ ሕዝብ ደርሷል።የጎጃም ፋኖ ወደ ወሎ ከቷል። የትግራይ ወራሪ ሰሜን ጎንደር ደባርቅ ላይ እንዳይድን ተደርጎ ተመቷል።አፋር ላይ አፈር ለብሷል።መከላከያ ሰራዊቱ በሁሉም ግንባሮች ከሁሉ በላቀ ደረጃ በአየር ኃይል ጭምር ተሰልፏል።

ከሊጥ እስከ የብረት ድስት ወጥ የሚልሰው የትግራይ ወራሪን በሃሳብ እና በገንዘብ የሚደግፉት የመሃል ሀገር የድብቅ ጀሌዎች ኢትዮጵያን ከድቶ እና አፈርሳለሁ ብሎ ዝቶ፣ሕፃናትን ገድሎ እና ሴቶችን ደፍሮ  ለባዕዳን ለመስጠት የሚደራደረው የትግራይ ወራሪን የሚደግፉ ሁሉ የጠሏት ኢትዮጵያ እንደማታውቃቸው ቁርጣቸውን የመንገርያው ጊዜ አሁን ነው።አሁን እየተሽሞነሞኑ የሚሄዱበት ጊዜ አይደለም።የትግራይ ወራሪ ቡድን ደጋፊ መሃል ሀገር ሆኖ የኦነግ ሸኔን እየደገፉ ኢትዮጵያን እያደሙ ነው።ይህ ከአሁን በኃላ አይቀጥልም።የትግራይ ወራሪ በኢትዮጵያ ላይ መቼም ሊያንሰራራ አይችልም።የኢትዮጵያ ሕዝብ ጦርነት የጀመረው አሁን ነው። በህወሓት የሚመራው የትግራይ ወራሪ ቡድን ጀሌውም ሆነ የመሃል ሀገር ደጋፊው ከሞያሌ እስከ መቀሌ ይነቀላል።ኢትዮጵያን የወጉትን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዴት እንደሚቀጣ ያውቅበታል።

የህወሓት እና የሸኔ ምስጢራዊ  የስልክ ንግግር የያዘ 
ጥቅምት 17/2014 ዓም (ኦክቶበር 27/2021 ዓም) የወጣ አዲስ ዶክመንተሪ ፊልም  





Tuesday, October 26, 2021

ጆሮ ያለው ይስማ! ሽብርተኛው፣ ከህወሓት ቡድንነት ወደ የትግራይ ወራሪነት መቀየሩን የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁን አምኗል።በመሃል ሀገርም ሆነ በውጪ የሚኖረው የትግራይ ማኅበረስብ ይህንን ወራሪ ከመቃወም መዘግየቱ ዋጋ የሚያስከፍለው ሰዓት የደረሰ ይመስላል።


የትግራይ ወራሪ ከአማራ ክልል ዘርፎ ሲሄድ (ፎቶ ኤኤፍፒ)

ጉዳያችን በየጊዜው የኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ የግለቱ ልኬት፣የሚሄድበት አቅጣጫ እና መድረሻ በተረዳችው ልክ ስታሳስብ አስር ዓመታት ሆኗታል።ወደ ኃላ ሄዶ ያለችው እና የሆነውን መመዘን የአንባቢ ፋንታ ነው።የተረዱትን ሳይናገሩ ከመቅረት ተናግሮ ቸል ያለው በቸልታው ይቀጥል።የተረዳው ደግሞ ነቅቶ እራሱንም አጥፊዎችንም ተጣልቶ መዳን ይችላል።

ኢትዮጵያ ላለፈው ግማሽ ክ/ዘመን በላይ እድገቷን ከገታባት፣የቁልቁለት ጉዞ ካስኬዷት የጠላት ጥፋቶች ውስጥ ከትግራይ የተነሳው ጎጠኛ እና በታኝ ወረራ አንዱ ነው።ይህ ከትግራይ የበቀለው የጥፋት፣የዘረኝነት እና የመሰሪ አስተሳሰቦች ሁሉ ወላጅ ሆኖ የወጣው ቡድን እራሱን ህወሓት/ወያነ በሚል አደራጅቶ ኢትዮጵያውያንን እና ኢትዮጵያን እያደማ ለ27 ዓመታት ሲገዛት ለመጪ ዓመታት የሚሆን መርዙን ተፍቶ ወደ ትግራይ ማፈግፈጉ ይታወቃል።

ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያ ይህንን መርዘኛ ቡድን '' የእናት ሆድ ዥንጉርጉር'' በሚል እንደ የቤት ልጅ አጥፊ እየታየ ብዙ ትዕግስት አሳይተዋል።በተለይ ቡድኑ በትግራይ ሕዝብ ውስጥ እንደመደበቁ የሕዝቡ ሃሳብ ሳይሆን የጥቂት ሰዎች እኩይ ሃሳብ ነው እየተባለ ከሚገባው በላይ በአንቀልባ እንደታዘለ ሕፃን ተይዞ ኖሯል።ይህ መርዛማ ቡድን በኤርትራ እና አማራ ሕዝብ ተደግፎ በ1983 ዓም አዲስ አበባ ገብቶ ስልጣን ከተረከበ በኃላ በርካታ ዕድሎች አበላሽቷል። ቀዳሚው በ1983 ዓም የተመሰረተው የሽግግር መንግስት ላይ ሲሆን ሁለተኛው በ1997 ዓም በተደረገው ምርጫ በመቀጠል በ2010 ዓም በተደረገው ሕዝባዊ ንቅናቄ ሁሉ የተሰጠውን ዕድል እንደ ጊዜ መግዣ እየወሰደ ዛሬ ደርሷል።

ባለፉት አራት ዓመታት ውስጥ ከመጣው ለውጥ የነበረውን ሂደት ብንመለከት ይህንን ጎጠኛ ቡድን ባላገለለ መንገድ በመጀመርያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ወደ መቀሌ ሄደው ለክልሉ ምክርቤት ''ወርቅ ሕዝብ'' የሚል ሙገሳ የታከለከብት ንግግር አድርገው ሁኔታዎች በእርቅ እና በይቅርታ እንዲፈቱ ጥረት አደረጉ፣በመቀጠል ጳጳሳት እና ሸሆች እንዲሁም ታዋቂ ሰዎች ያካተተ ልዑክ መቀሌ ድረስ ሄዶ እናቶች እያለቀሱ የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደብረ ፅዮን ባሉበት ለመኗቸው።ሆኖም ለሽማግሌዎቹ ክብር ሳይሰጡ ገፍተው መለሷቸው። የብልፅግና ፓርቲ ውስጥ እንዲካተት ተለመኑ አሻፈረኝ አሉ።በዝርዝር የተደረጉ የሰላም ጥረቶችን ለመከለስ ይህንን ሊንክ ከፍተው ያድምጡ።

የዛሬ ዓመት ጥቅምት 24/2013 ዓም ህወሓት በኢትዮጵያ መከላከያ ላይ ጥቃት ከፈፀመ በኃላ መከላከያ በቀናት ህወሓት እና ጀለውን ጠርጎ መቀሌ ከገባ በኃላም ሙሉ በሙሉ መደምሰስ የሚለው ቀርቶ ለገበሬው የእርሻ ጊዜ ለመስጠት፣የተናጥል ተኩስ አቁም ብሎ መንግስት ትግራይን ለቆለት ወጣ። ይህም ሆኖ ግን በመጨረሻው ዙር ላይ እንደ ህወሓት ሳይሆን እንደ የትግራይ ሕዝብ ሆኖ በአማራ እና አፋር ክልሎች ላይ ወረራ ፈፅሟል።በወረራው የተሳተፈው ጥቂት ቡድን ሳይሆን የትግራይ ሕዝብ እንደ ሕዝብ እጁን እየነከረ ለመሆኑ በቂ ማስረጃዎች ተገኝተዋል። በወረራ ብቻ ሳይሆን በዘረፋ ላይ የትግራይ ነጋዴ ሁሉ ተሳትፏል።ከዝርፍያ በላይ የሴቶች መደፈር ሕፃናትን ሳይቀር ሆን ብሎ በጅምላ መፍጀት በአፋር እና በአማራ የትግራይ ወራሪ ከሰራቸው ግፎች ውስጥ ናቸው።

የትግራይ ወራሪ የወረራው ግብ ሕዝብ መበተን፣ሀገር ማፍረስ እና ኢትዮጵያን ለባዕዳን አሳልፎ መስጠት ነው።ቡድኑ የህወሓት ቡድን ሲባል የኖረው አባባል አሁን በግልጥ የትግራይ ወራሪ ማለት የሚቻልበት ጊዜ ላይ ተደርሷል።ምክንያቱም አሁን ወደ አማራ እና አፋር ዘምቶ ከትምህርት ቤት እስከ ክሊኒክ፣ከገበሬ ጎተራ እስከ የተቦካ ሊጥ እየዘረፈ የሚሄደው የህወሓት ወታርደር ብቻ ሳይሆን ተራው የትግራይ ሕዝብ ሁሉ የተሳተፈበት ነው።

ይህ ምን ማለት ነው? መልሱ ቀላል ነው። የተዘረፈው ሕዝብ ጥላቻው ወደ የትግራይ ሕዝብ እንደዞረ ግልጥ ሆኗል።ከትግራይ ካህናት እና ሸሆች ተዉ የሚሉ አልተሰሙም።የተሰረቀ አልበላም ያለ የትግራይ ገበሬ ተቃውሞ አልተነሳም።ይህ ነገ ከባድ መዘዝ አለው የሚል የትግራይ ምሑር ውስጥ ከሁለት እና ሶስት በላይ አልተሰሙም።ጆሮ ያለው ይስማ! ሽብርተኛው፣ ከህወሓት ቡድንነት ወደ የትግራይ ወራሪነት መቀየሩን የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁን አምኗል።በመሃል ሀገርም ሆነ በውጪ የሚኖረው የትግራይ ማኅበረስብ ይህንን ወራሪ ከመቃወም መዘግየቱ ዋጋ የሚያስከፍለው ሰዓት የደረሰ ይመስላል።የኢትዮጵያ ሕዝብ የጃሮስላው ካዚንኪ ''ሰላም ከፈለክ ለጦርነት ተዘጋጅ'' የሚለውን አባባል ደጋግሞ ከንፈሩ ላይ እየመላለሰው ነው።
"If we want to avoid the worst, that is war, we have to act according to the old rule: 'If you want peace, prepare for war,'" Jaroslaw Kaczynski said

አሁን ሕዝብ መሮታል።የትግራይ ወራሪ እንደ አንድ የእናት ኢትዮጵያ ልጅ ሳይሆን እንደ ምናምንቴ ቆጥሮ በቃኝ! ብሎ በአንቀልባ የታሰረ ልጅ ከእናቱ ጀርባ ተገፍትሮ እንደሚያፈርጠው የምያፈርጥበት ጊዜ እራሱ ግፉ እየገፋው ነው።የትግራይ ወራሪን የእናት ልጅ እንደሚቀጣው ያለ ቅጣት ሳይሆን እንደምናምንቴ ቆርጦ ለመጣል የትግስቱ ልክ መጠን አልፏል።ብዙ ኢትዮጵያውያን በትግራይ ወረራ ላይ የተሳተፉ፣የረዱ እና በተዘዋዋሪ የተሳተፉ ሁሉ ኢትዮጵያዊነት ዜግነታቸው ተገፎ ከሀገር እንዲባረሩ እየጠየቁ ነው።ይህ ብቻ አይደለም።የትግራይ ወራሪን ለሕሊናቸው ሲሉ መቃወም ቀርቶ በእናቶች መደፈር፣በህፃናት ግድያ እና በምስኪን ገበሬዎች መዘረፍ የሚሳለቁ ሁሉ ''ወይ ኢትዮጵያ!'' የሚያሰኝ ቅጣት እንደሚያስፈልጋቸው ሕዝብ እንዳመነበት በደንብ እየታየ ነው።ሕዝብ ከወሰነ ማንም አያቆመውም።
=======///=======

Monday, October 25, 2021

Full speech of Ethiopian PM Abiy Ahmed (PhD) at Sudanese transitional government peace agreement in 2019 (video)

በሱዳን የሽግግር መንግስት የሰላም ስምምነት ላይ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እአአ 2019 ዓም ያደረጉት ንግግር (ቪድዮ)


 

Tuesday, October 19, 2021

መንግስት የሰብዓዊ ቀውሱን ለማስቆም እና ሀገርን ለማዳን ወሳኝ ወደ ሆነው ወደየማይፈለገው ነገር ግን አማራጭ ወደ የሌለው እርምጃ የግድ መግባት ሊኖርበት ይችላል።


===========
ጉዳያችን ምጥን  
===========
የሽብርተኛው የህወሓት ቡድን ሁለት ወሳኝ ዕድሎቹን አበላሽቷል።የመጀመርያው ወደመቀሌ ከከተተ በኃላ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሂደት ውስጥ መሳተፍ ሲሆን ሁለተኛው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰኔ 21/2013 ዓም የትግራይ ሕዝብ የፅሞና ጊዜ እንዲያገኝ፣ገበሬው የእርሻ ሥራውን እንዲያከናውን መቀሌን ለቆ ከወጣ በኃላ ያለው ጊዜ ነው።የመጀመርያውን በኢትዮጵያ መከላከያ ላይ ጥቅምት 24/2013 ዓም ጥቃት በመፈፀም ሲያበላሸው፣ሁለተኛው ደግሞ ትግራይን ይዞ ሕዝቡ እድንያገግም ከመስራት ይልቅ ወደ አማራ እና አፋር በመውረር ያጠፋው ዕድሉ ነው። 

የኢትዮጵያ መንግስት የህወሓትን ወረራ በሙሉ አውዳሚ መንገድ እየተዋጋው አይደለም።ለምሳሌ ለስልጠና የሚሰበስባቸው ወጣቶች ገና በማሰልጠኛ እያሉ በአየር ኃይል አልመታም።መንገድ ላይ የሚንቀሳቀሰው ማንኛውም የታጠቀ የህወሓት ጀሌን አልደበደበም።ይህም ወጣቶቹ በግድ መታፈሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸው አሁንም በፍላጎት አልላኩም ከሚል እሳቤ ሊሆን ይችላል።

ይህ ሁሉ ትዕግስት ግን ለህወሓት የልብ ልብ ሰጥቶት እጅግ አረመኔያዊ በሆነ መንገድ ገበሬውን እየረሸነ፣ልጆቹን እየደፈረ እና ሰብሉን እያቃጠለ የጥፋት ስራውን ቀጥሏል።ከእዚህ ሁሉ ጥፋት ጋር በሺህ የሚቆጠር ሕዝብ እየተሰደደ ነው።ይህ ፅሁፍ እየተፃፈ ብዙ ሺዎች የደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞችን በስደት አጣበዋል።ይህ ሁኔታ አሁን ባለበት መንገድ አይቀጥልም።

ሽብርተኛው ህወሓት በሰዓታት ውስጥ በአማራ ክልል የወረራቸውን ቦታዎች ለቆ መውጣት ካልቻለ መንግስት ኢትዮጵያን የማዳን እና ያለማዳን ወሳኝ  እና ወደየማይፈለገው ነገር ግን አማራጭ ወደ የሌለው እርምጃ የግድ መግባት ሊኖርበት ይችላል። ይህ እርምጃ ምንድነው? ብሎ መጠየቅ ይችላል።ነገር ግን ሀገር የማዳን ሥራ በትሕትና የሚሰራ አይደለም።ይህ ጦርነት በምንም ዓይነት መንገድ በፍጥነት  መጠናቀቅ አለበት።ለእዚህ ደግሞ ወሳኝ እርምጃ የሚጠይቅበት ጊዜ ሆኗል።ይህ እርምጃ ግን የትግራይን መሰረተ ልማት እስከ ሰማንያ ከመቶ አያፈርስም ማለት አይቻልም። ወታደራዊ ውሳኔዎች ዋና ግባቸው ሀገር ማዳን ነው።የትግራይ ሕዝብ ህወሓትን ማውረድ እና ትግራይንም ሆነ ሕዝቡን ማዳን ብቸኛው አማራጭ ሲሆን ሌላው አማራጭ የሽብርተኛው ህወሓት በአማራ ሕዝብ ላይ የሚያደርሰውን ግፍ እያዩ ህወሓትን እያሽሞነሞኑ ትግራይን ማውደም ነው።  መንግስት የሰብዓዊ ቀውሱን ለማስቆም እና ሀገርን ለማዳን  ወሳኝ ወደ ሆነው ወደየማይፈለገው ነገር ግን አማራጭ ወደ የሌለው እርምጃ የግድ መግባት ሊኖርበት እንደሚችል አለመጠበቅ ግን አይቻልም።እስካሁን ህወሓትን ለማስታመም የተሄዱባቸው ሂደቶች በሙሉ ለመጪው ትውልድም በታሪክነት ተመዝግበው ትውልድ የራሱን ፍርድ ይሰጣል።የአንዳንድ ጦርነቶች አጨራረስ የራሱ የሆነ ባህሪ ይኖረዋል።ከሀገር እና ከጠቅላላ ሕዝብ በላይ የሚሆን ቡድንም ሆነ አስተሳሰብ የለም።
============///==========

Monday, October 18, 2021

ኢትዮጵያን ሊያፈርሷት እያደሟት ነው።አሁን ታሪክ የመስርያ ጊዜ ነው።በውጭም በውስጥም ያለው ሕዝብ እና መንግስት ትኩረት ሊሰጧቸው የሚገቡ ሰባቱ ቁልፍ ተግባራት።

In the last Five days, terrorist TPLF killed Hundreds and looted thousands of civilians in Amhara Region in Ethiopia.International Humanitarian Organizations and Media are quite.

 

=============

Gudayachn

=============

It is becoming more clear that the International Media loyal to the west is quiet, when Terrorist TPLF killed innocent civilians in Amhara and Afar Regions in Ethiopia. On the other hand, during the Ethiopian National Defence Force law enforcement process, almost all channels of the International media talk about Human Right issues and start to criticize the Ethiopian Government.


Starting from the end of June 2021, terrorist TPLF killed, raped and looted thousands of Amhara and Afar civilians. These savage acts of TPLF are recorded and witnessed by the local people and even with aid workers. For the last Five days, terrorist TPLF randomly killed civilians for only being from the Amhara ethnic. The total death toll is increasing.However reports from Maychew, Weldia and North Wello administrative regions say the TPLF massacre on Amhara ethnics is on innocent civilians who do not have any involvement on the ongoing law enforcement. 


One sided, the so-called International Humanitarian Organizations and International media are very selective in their reports regarding  Ethiopia’s current case. Even though, since the end of June 2021, there have been multiple accusations of atrocities, killing and looting innocent civilians in Amhara and Afar Regions in Ethiopia, most of them were ignored by the Humanitarian and International media which seems intentional. 


More recently in the last Five days, the terrorist TPLF militias bombarded civilian residents in Wuchale city and killed a number of civilians that the local people are not yet finished counting the dead body.At the result of terrorist TPLF atrocities,only in the last three months, Tens of thousands of people have fled out from North Wello and increased Internal Displaced People (IDP) by another Ten thousands in addition to the previous one.


In General, Ethiopians and Africans as a whole are watching carefully the way how the west under the title of International Community is sided with the terrorist TPLF with its atrocities. There is no question and any doubt that Ethiopia will overcome the current internal and external influences. However,when times comes those who stand on the side of the terrorist TPLF will be ashamed with their own ignorance to the death of Ethiopian civilian people.

=======///=======

Saturday, October 16, 2021

ሰበር ዜና - ህወሓት በሰሜን ወሎ የመጨረሻ ውግያ ብሎ የላከው ጀሌ ክፉኛ ተመቷል።የመጨረሻ ውግያ የሚሉ ቃላት ሰሞኑን መጠቀም የፈለገባቸው ሦስት ምክንያቶች ታውቀዋል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ስር ቃል ኪዳን ሲገቡ 

================
ጉዳያችን/Gudayachn
===============

ህወሃት በውሸት ዜና ተጥለቅልቋል።ሰኔ 21/2013 ዓም የኢትዮጵያ መከላከያ ለትግራይ ሕዝብ የፅሞና ጊዜ ለመስጠት እና የእርሻ ጊዜው እንዳይታጎል በሚል የተናጥል ተኩስ አቁም አድርጎ ቢወጣም፣ከተደበቀበት ዋሻ እየወጣ በፍርሃት መቀሌ የገባው የተረፈው የህወሓት ቡድን የትግራይን ሕዝብ በራሱ በህወሓት ጥፋት ማለትም በኢትዮጵያ መከላከያ ላይ ባደረሰው ጥቃት ሳብያ የደረሰውን ጥፋት ለማስተካከል ከመጣር ይልቅ ወደ አማራና አፋር ሕዝብ ላይ ለመዝመት ሞክሮ አራት ወር ሙሉ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች አስፈጅቶ የጅብ እራት ካደረገ በኃላ ከሕዝቡ ጋር ውስጥ ውስጡን የምንተከተክ ቁርሾ ውስጥ ገብቷል።የህወሓት ይሄው የጥፋት መንገድ በትግራይ ሕዝብ እናቶች ላይ ከባድ ሰቀቀን ጥሎ ከመሄድ  አልፎ  የትግራይ ቤቶች ውስጥ በአሁኑ ሰዓት ብዙ ሕዝብ መርዶ እየጠበቀ ይገኛል።

ያለፈው ሳምንት ዓርብ ሽብርተኛው ህወሓት ድንገት ተነስቶ መንግስት በአየር እና በምድር ወረረኝ ብሎ መጮህ ጀመረ።ሰኞ ማለዳ በእንግሊዝኛ ይሄው ለቅሶ ወጣ።ይህንን አስመልክቶ ከመንግስት በኩል ምንም የወጣ ነገር አልነበረም።ከአራት ቀናት በኃላ መከላከያ በማህበራዊ ሚድያ ላይ ባወጣው ፅሁፍ ላይ ህወሓት በአማራ ክልል ደግማ ለመተኮስ ያደረገችውን ሙከራ ክፉኛ እንደተመታ ገለጠ።የህወሓት ለቅሶ ግን እስከ ዛሬ ቅዳሜ ድረስ ቆይቶ ''እራሱ ምን ብሎ እራሱ አለቀሰ'' እንዲል እራሱ ተጠቃሁ ያለው የሽብር ቡድን ዛሬ ቅዳሜ ድንገት ተነስቶ ደግሞ የመንግስት ወታደር አሸነፍኩ የሚል መግለጫ ሰጠ።የገታቸው ረዳ መግለጫ ከደብረፅዮን፣የፃድቃን ከታደሰ ወረደ እርስ በርስ የተምታታ መግለጫ መስጠታቸው የመከፋፈሉ ማሳያ ብቻ ሳይሆን የውጭ ኃይልም ዳቦ እያላሰ እንደ የቤት ድመት እያተራመሳቸው መሆኑ ይታያል። ቢቢሲ ጌታቸው ረዳን ሲያናግር፣ አንዱ የፈረንጅ አክትቪስታቸው ተነስቶ ፃድቃንን ያሞግሳል፣ የህወሓት ማኅበራዊ ሚድያ ታደሰ ወረደን ያሞግሳል።ያፈሰሰሱት ደም አክለብልቧቸዋል።

ከላይ ህወሓት ተወረርኩ ከሚለው ለቅሶ ቀጥሎ የተነገረው ጉዳይ ፃድቃን ለኒውዮርክ ታይምስ ሲናገሩም ሆነ ጌታቸው ረዳ ለትግራይ ሚድያ ሲናገሩ ከሰሞኑ ያመጧት አዲስ ፋሽን አለች። ''የመጨረሻው ውግያ ነው።በቅርቡ ጦርነቱን እንጨርሰዋለን።'' የሚሉ ቃላት ናቸው።ለምንድነው እነኝህን ቃላት መጠቀም የፈለጉት?
በቀውስ ውስጥ ያለው የህወሓት የሰሞኑ ስብሰባ መቀሌ 

ህወሓት የመጨረሻ ውግያ የሚሉ ቃላት ሰሞኑን መጠቀም የፈለገባቸው ሦስት ምክንያቶች

ህወሓት ከሰሞኑ የመጨረሻው ውግያ የሚልባቸው ምክንያቶች ሶስት መሆናቸው ታውቀዋል።
 
1)  የትግራይ ሕዝብም ሆነ የክልሉ ኢኮኖሚ ከእዚህ በላይ ጦርነት ለመቀጠል ህዝቡ በሙሉ ከቦታው መፈናቀል ይኖርበታል።ስለሆነም ህወሓት የመጨረሻው አቅሙ ላይ ስለደረሰ።

የህወሓት ዕቅድ ሰኔ ላይ ወደ አማራ እና አፋር ሲዘምት ጦርነቱን ቢያንስ ሰሜን ሸዋ አድርሶ እና የጅቡቲን መንገድ ዘግቶ ከቻለ አዲስ አበባ መምጣት ወይንም መንግስትን አስገድዶ ወደ  ድርድር ማምጣት የሚል ነበር።ይህንን ደግሞ ክረምቱ እንደ አመቺ ጊዜ ተወስዷል።ምክንያቱም መንግስት የበላይ በሆነበት የአየር ኃይል ውግያ በክረምቱ ምክንያት የጉም መሸፈን እንደሚረዳ ታስቦ ነበር።ሌላው ክረምቱ የተፈለገበት ምክንያት መንግስት መካናይዝድ ጦር በክረምት ጭቃ በተለይ ወደ ደጋው አካባቢ ማንቀሳቀስ አይችልም የሚል ታሳቢ ተደርጎ ነበር።

ይህ ሁሉ ግን አልሰራም ክረምቱም አለፎ ጥቅምት ከባተ ሳምንት ተቆጠረ።ስለሆንም ከትግራይ ሕዝብ የተነሳበት ጥያቄ በጦርነት ካልተሳካ በፍጥነት ከአማራ ክልል ለቃችሁ ወጥታችሁ ተደራደሩ የሚል ጥያቄ ወጥሮ ይዞታል።በቅርቡ መቀሌ ላይ ሽማግሌዎች ተሰብስበው ይህንኑ ጥያቄ ለደብረፅዮን አቅርበው ህወሓት አዋርዶ መመለሱ ከአክሱም እስከ አድዋ ያሉ ከተሞች ተሰምቶ ቁጣ ፈጥሯል።ስለሆነም ይህንን ሕዝብ ለመደለል ጦርነቱ የመጨረሻ ደረጃ ደረሰ፣በቅርቡ እንጨርሰዋለን የሚሉ ቃላት በመናገር ሕዝቡን ለመደለል ሞክረዋል።በነገራችን ላይ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ ያልተከፈላቸው ከመኖራቸው ጋር በስራቸው የሚያስተዳድሯቸው ቤተሰቦች ጨምሮ እና የመብራት እና ስልክ አገልግሎት ከመቆሙ ጋር እንዲሁም አዲሱ የትምህርት ዘመን ከመጀመር ጋር የትግራይ ሕዝብ ህወሓትን ወጥሮ ይዟል።

2) በውጭ የሚኖረው የህወሓት ደጋፊ መከፋፈሉ መቀጠሉ።

በውጭ የሚኖረው የህወሓት ደጋፊ ቀድሞ በስሜት ሲፎክርበት የነበረው ''ግፋ በለው'' ፉከራ አሁን በትግራይ ሕዝብ ላይ ያደረሰው ጥፋት ብቻ ሳይሆን የሚያውቃቸው ቤተሰቦች ወደ አማራ እና አፋር እየተላኩ የማለቃቸው ዜና ሲሰማ እነጌታቸው ረዳን አንድ ዓይነት መፍትሄ በፍጥነት ካልደረሱ ትግራይን ሙሉ በሙሉ እንደሚያወድሙ የሚጠይቁ በዝተዋል።ሌላው አብረው ቆይተው የምንደግፈው ህወሓትን ሳይሆን ትግራይን ነው የሚሉ ሌላ አንጃዎች ተፈጥረው ሁሉም በአንድነት ጥያቄያቸው ወደ ገደል እየሄድን ነው።በቶሎ አንድ ነገር አድርጉ ይህ ካልሆነ ሌላ አደረጃጀት ተፈጥሮ ህወሓትን የሚቃወም ኃይል ተፈጥሮ ትግራይን ማዳን ላይ መስራት አለበት የሚለው ስሜት አይሏል።ስለሆነም ይህ የመጨረሻው ጦርነት ነው፣በቅርቡ እንጨርሰዋለን የሚለው መልዕክት ወጥሮ ለያዛቸው ለውጭው ደጋፊ መደለያ የቀረበች ነች።

3) የምዕራቡ ዓለም እረጅም ጊዜ ከህወሓት ጋር እንደማይቆይ እና ጊዜ እንደሌለው ይታወቃል።

የምዕራቡ ዓለም ጊዜ የለውም። የምስራቅ አፍሪካ ጉዳይ ጊዜ በተሰጠው ቁጥር ከእጁ ከመውጣቱ በላይ ለቻይና እና ሩስያ ስር የመስደድ ዕድል  እየበዛ ከመምጣቱ በላይ የምዕራቡ ዓለም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የባሰ ፀብ ከመግባት የህወሓት ጉዳይ ቶሎ ታውቆ የስልት ለውጥ ማድረግ እንደሚገደዱ ግልጥ ሆኗል።ስለሆነም የህወሓት መሸነፍ ዜና ከሱዳን ቀውስ ጋር ተዳምሮ የምዕራቡን ዓለም ተስፋ ስለሚያስቆርጠው ከኢትዮጵያ ጋር አዲስ አቀራረብ በተለየ ድብቅ ስልት ቀርቦ በሰጥቶ መቀበል መርህ ሊቀርብ ይችላል።በሌላ በኩል የምዕራቡ ዓለም ለህወሓት የሰጠው ''የማርያም መንገድ'' ረጅም ጊዜ መቆየት እንደማይችል በገደምዳሜ ለህወሓት አይነግሩትም ማለት አይቻልም።የምዕራቡ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋይ ለማፍሰስ ጊዜ የላቸውም ህወሓት የዘላለም ወዳጅ እንደማይሆን ግልጥ ነው።ስለሆነም ህወሓት ለምዕራቡ ዓለም ጦርነቱን ልንጨረሰው ነው፣በቅርቡ ያልቃል እያለ ለኒውዮርክ ታይምስ በፃድቃን አማካይነት መናገር ነበረበት።

ባጠቃላይ ህወሓት ሁለቱን ዋና ዋና ሞቶች ሞቷል።ሶስተኛው እና የመጨርሻው ሞቱ ሸህ ሁሴን ጀብሪል እንዳሉት ወሎ ላይ ነው ቀብሩ ያሉት ትንቢት የደረሰ ይመስላል።ሁለቱ ሞቶች በጥቅምት 24 በመከላከያ ላይ ጥቃት ከፈፀመ በኃላ ዋሻ እስከምገባበት ያለው ሲሆን ሁለተኛው በአፋር እና ወሎ ላይ የደረሰበት በአስር ሺዎች የሞቱበት እልቂት ሲሆን አሁን በአራት አቅጣጫ ወሎ ላይ ተከቦ የፍፃሜ ሞቱን እየጠበቀ ነው።የምዕራቡ ዓለም ምንም አይነት እቀባ ቢያደርግ ነፃነት በእቀባ አይቀየርም።ይህንን ደግሞ ከአሁኑ ግልጥ ሆኖላቸዋል።በባለስልጣናቱ ላይ ለይተው እቀባ ለማድረግ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ጀምሮ ይህ ነው የሚባል ሀብት በአሜሪካ የገንዘብ ድርጅቶች ውስጥ አለማግኘታቸው አበሳጭቷቸዋል።መግንስት ደግሞ በህወሓት ላይ አጠቃላይ ጥቃት የሚከፍትባትን ቀን እና ሰዓት ''ከአባት በቀር የሚያውቃት የለም'' እንዲል ከጥቂት ከፍተኛ መኮንኖች እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ውጭ የሚያውቀው የለም።መንግስት ከእዚህ በፊት እንዳየነው በህወሓት ላይ አጠቃላይ ጥቃት ሲጀምር እጅ እንዲሰጡ የ72 እና 48 ሰዓታት ማስጠንቀቅያ ስለሚሰጥ ይህንኑ ህወሓት በተስፋ ብትጠብቅ የተሻለ ሳይሆን አይቀርም።

========///==========




Friday, October 15, 2021

የምዕራቡ ዓለም በተለይ አሜሪካ ለዩጎዝላቭያ መፍረስ ምን አድርጋ እንደነበር የሚያሳይ ጥናታዊ ፊልም ከህወሓት ደጋፊ እስከ የፅንፍ የኦሮሞ ብሔርተኝነት አራማጆች፣ከአማራ አክራሪ ብሔርተኝነት እስከ ኢትዮጵያዊነት ይቅደም የምንል ሁሉ በትዕግስት እንመልከተው።


ፊልሙን ከተመለከትኩ በኃላ እነኝህ ነጥቦችን ያስታውሱ -
  • ኢትዮጵያ ውስጣዊ የፖለቲካ ግጭቶቿ ታሪካዊ ዳራ እና ስነልቦናው ከዩጎዝላቭያ ጋር አይመሳሰልም።ይህ ማለት ግን ለኢትዮጵያ ካልሰራን አደጋ የለብንም ማለት አይደለም::
  • ዩጎዝላቭያ የነበረው ሕዝብ የመከፋፈል አካሄድ፣ የአሜሪካ እና የምዕራቡ የጣልቃ ገብነት መጠን እና ደረጃዎች በትክክል አሁን እያደረጉት ካለው ጋር ይመሳሰላል።
  • በኢትዮጵያ በብ/ጄ አሳምነው ዙርያ የተነሳው የባህርዳሩ አስዛኝ የአመራሮች ሞት፣የአርቲስት ሃጫሉ መገደል፣በሰሜን ዕዝ ላይ በህወሓት የተወሰደው ማጥቃት ሦስቱ ኢትዮጵያውያንን እርስ በርስ አጋጭቶ ለማፍረስ የመጡ መቅሰፍቶች ነበሩ።እነርሱን አልፈናል።ለቀጣይ ተመሳሳይ አደጋዎች ቢፈጠሩ ወደ ብሔር ስሜት እንዳይሄድ እያንዳንዱ ምሁር፣ጋዜጠኛ፣የማኅበራዊ ሚድያ ተጠቃሚ ሳይቀር ኃላፊነቱ ምን ያህል ከባድ እንደሆነ ያሳያል።
  • የትም ሆንክ የትም፣ህወሓትን ደገፍክ፣ኦነግ፣ኢትዮጵያዊነትን አስቀደምክ አላስቀደምቅ በምትሰራው ሥራ ሕዝብ የሚከፋፍል እና ኢትዮጵያን ለባዕዳን ከሚያስማማ ድርጅት እንደ ህወሓት እና ኦነግ ሸኔ ጋር ከቆምክ ሕዝብህን፣እራስህን እና ልጆችን ወደባርነት እየመራህ መሆኑን እወቀው።
ብልህ ከሌላው ስህተት ይማራል።በትግስት ጥናታዊ ፊልሙን ይመልከቱ።






Tuesday, October 12, 2021

The US Government must respect the parliamentary decision of the land with over 3000 years of statehood history,Ethiopian Parliament decision.


==============
Gudayachn Alert 
=============

Ethiopia and United State diplomatic relations started in 1903. It has over a century of diplomatic relations which is unique  among African countries. Because following the Berlin conference, which is also known as the scramble of Africa signed in 1885, all African countries except Ethiopia were under colony. However, this Shiny and historical diplomatic relation is about to be spoiled due to the failed Foreign Policy of the current Biden administration.


After the end of the cold war, at the end of the 1980s, the Tigray Liberation Front (TPLF) got a chance to control the Political power of Ethiopia. It continues to rule the whole Ethiopia for almost 30 years. During that period, ten of thousands of Ethiopians were sent to prison and other thousands were killed without any justice. The resource of the country was controlled by the minority elites of ethnic Tigran loyal to the TPLF. Even though the majority of Ethiopians got down and poorer, the few elites from ethnic Tigray region got richer.


However, thanks to the 2018 popular movement against the TPLF ethnocentric rule, Ethiopians could control the political power and started the new reform. The reform has continued and on the last June,2021, the first and more accepted National election took place and the Prosperity party led by the 2019 Nobel Peace Prize winner, Abiy Ahmed (PhD) win the majority seats in the parlament.


In all the past 30 years, when Ethiopians suffered under the brutal rule of TPLF, the United States Government was the main supporter for the regime in all logistic, financial and even media coverage. When the reform started in 2018, Ethiopians were in a forgiving mood to any foreign power  assisting the TPLF regime,  as was expected the same support could be provided for the newly emerged Ethiopian Government. However, the current Biden administration failed Foreign Policy stands against both Ethiopia and the United States National interest.


Ethiopians at home and around the world are not feeling comfort with the Biden administration's Foreign Policy towards Ethiopia. The core reason for this discomfort is that the United States Government's disrespect the Ethiopian Parliament decision on categorizing TPLF as the terrorist group.


The Biden administration's attempt to dictate the Ethiopian highest legislative body, just by disregarding the sovereignty of Ethiopia, may cost a lot for the Ethio -US diplomatic relationship. The United States Government is clearly showing its support for the terrorist group TPLF. This was reflected in different ways including - 

  • The United States did not officially condemn the TPLF attacks on Ethiopian National Defence Force on November 2,2020.

  • The Biden administration did not appreciate properly for the Ethiopian Government's unilateral action of ceasefire. 

  • The Biden administration attempted to interfere with a very internal issue of Ethiopia including where to be assigned the regional army like the Amhara Region's local army.

  • The Biden administration did not condemn properly the TPLF genocide on Amhara and Afar regions in Ethiopia.

  • After all these terrorist acts of the TPLF and Ethiopian Parliament decision on categorizing TPLF as the terrorist organization, Secretary Antoni Blinken tweeted today, October 13,2021, as he met  with African Union High Representative Obasanjo, IGAD Chair, Sudan's PM Hamdok and the Ethiopian core Group of the European Union, France and Germany. In this particular tweet, the objective of all these talks was to bring TPLF as a legal body and  empower it to negotiate with the legally elected Ethiopian Government.


In General, it is quite clear that the US Government is violating the sovereignty of the Ethiopian Government. Ethiopia was a member of the League of Nations and the founder of the United Nations. All nations have equal rights and their relationship is based on mutual benefits. Therefore, since Ethiopia is not interfering in the internal issue of the US domestic politics, the US Government must also respect the 3000 years history of the  statehood country's parliament. That is the Ethiopian Parliament's decision on TPLF.


=============///=========





Monday, October 11, 2021

እንደሚገረፍ ያወቀ ልጅ አባቱ ገና ቀበቶውን ሲነካካ እሪ! ይላል።


----------------
ጉዳያችን/ Gudayachn
---------------

ጉዳያችን ምጥን 

ልጁ ገና አልተገረፈም።እሪታው ግን ሲገረፍ የማያወጣውን ድምፅ ነው የሚያውጣው።ልጅ ሆነን እንዲህ ሆነን አናውቅም? ግርፍያው እንደማይቀር ከአባታችን ፊት እናውቀዋለን።ቀጥሎ እያንዳንዱ የአባትን እንቅስቃሴ እንከታተላለን።በመቀጠል እጁን ወደ ቀበቶው ሰደድ ሲያደርግ እሪ! ማለቱ ይቀጥላል።ምናልባት አባት ለመግረፍ ሳይሆን ቀበቶውን ሊያስተካክል ሁሉ ሊሆን ይችላል።ልጅ ግን ጥፋቱን ያውቃልና ቀድሞ እሪታውን ያቀልጠዋል።የህወሓት አፈቀላጤ የጌታቸው ረዳ የዛሬ መግለጫ እንዲህ ነው።እንደሚገረፍ ያውቃል።እርሱና  ቡድኑ የሰራትን ያውቃል።በአማራ እና በአፋር ሕዝብ ላይ ብቻ ሳይሆን በራሱ በትግራይ ሕዝብ ላይ የፈፀመው ግፍ ከአሁን በኃላ ከራሱ ልጆቹን ካስጨረሰበት ከትግራይ ሕዝብም ምን ሊሆን እንደሚችል ያውቃል።መከላከያ በሀገር ላይ ለተሰራው ክህደት እርምጃ እንደሚወስድ እርግጠኛ ነው።ስለእዚህ ገና ሳይገረፍ የህወሓት ቃል አቀባይ በእንግሊዝኛ መግለጫ እሪታውን ዛሬ አቅልጦታል።መከላከያ ገና ዋና የማጥቃት ዘመቻውን አልጀመረም።ምናልባት ቀበቶውን ነካክቶ ይሆናል።

ጌታቸው ረዳ አባቱ ቀበቶውን ሲነካካ እንደተመለከተ ልጅ እሪ! ማለቱ ከ''ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ'' እና ሸፍጠኛ ደጋፊዎች ፈጣን እርዳታ አገኛለሁ በሚል እሳቤ ነው። ለነገሩ ግርፍያ ሲጀመር ለእሪታ ጊዜ አይኖርም።ከእንግሊዝኛ መግለጫው  ቀደም ብሎ ''መቀሌን አትነካም'' መሰል ፉከራም አሰምቷል።ለነገሩ ''ምን ያለበት ምን አይችልም'' መሆኑ ነው።በገደምዳሜ መቀሌን ማስተዳደር ስላልቻለ መከላከያ መቀሌ ቢገባለት የፈለገ ይመስላል።መከላከያ በጌታቸው ብልጣብልጥ አካሄድ አይመራም።የመከላከያ ዕቅድ እና አካሄድን ለማወቅ አይቻልም።የትግራይ ሕዝብም ህወሃትን አሽቀንጥሮ በመጣል መከላከያን በክብር መጥራት የራሱ ፋንታ ነው።ይህ ካልሆነ የዛሬ ዓመትም ህወሓት ትግራይን ማውደሙን ይቀጥላል።እስከ ዛሬ ዓመትም የትግራይ ሕዝብ ህወሓትን እያዳነቀ መኖር ከቀጠለ ትግራይ ሽፍታ የሰለጠነባት ሕዝብ ተሰዶ የሚያልቅባት ምድር እንደምትሆን ለማወቅ ጠቢብ መሆን አያስፈልግም።

በነገራችን ላይ ዛሬ በመላዋ ኢትዮጵያ ትምህርት ቤት ተከፍቷል።የትግራይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት አይሄዱም።
በእዚህ ወር መጨረሻ የሚሰጠው የማትሪክ ፈተናም መውሰድ አይችሉም።ለእዚህ ሁሉ ተጠያቂው ህወሓት እና ቅምጥሎቹ 
በውጭ ሀገር እና በሀገር ውስጥ ያሉ የህወሓት አድናቂዎች ሁሉ ናቸው።

መከላከያ ቶሎ መቀሌ ገብቶ ትምህርት ቢጀመር፣መብራት ቢለቀቅ ደስ የማይለው የትግራይ ክልል ነዋሪ የለም ማለት አይቻልም።
ይህ ምን ማለት እንደሆነ በውጭ ሀገር ተቀምጠው የራሳቸውን ልጆች ወደ ትምህርት ቤት እየላኩ የትግራይ ልጆች ግን የጅብ ራት 
ሲሆኑ ትንሽ ቅር የማይላቸውን አይጨምርም። አሁን ጥያቄው አንድ ነው። በትግራይ ሰላም ለማምጣት ህወሓት መጥፋት አለበት።ህወሓት በመኖሩ ብቻ ትግራይን ጨምሮ ለመላዋ ኢትዮጵያ ጥፋት ነው።ህወሓትን ማውረድ የራሱ የትግራይ ሕዝብ ኃላፊነት መሆኑን ማወቅ አለበት።ከአሁን በኃላ መከላከያ መቀሌ እንዲገባ እና ሰላም በትግራይ ወርዶ ተማሪዎች በሰላም ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄዱ ሕይወት እንደገና እንዲቀጥል እራሱ ህዝቡ ህወሓትን አውርዶ መከላከያን መጥራት አለበት።ይህ ካልሆነ ዝም ብሎ ህወሃትን አይን አይኑን እያዩ ለውጥ አይመጣም።

መከላከያ ከሰሜን ወሎ ጠራርጎ ያስወጣል።የኢትዮጵያን ድንበር ይጠብቃል።ህወሃትን ማውረድ እና መከላከያን መጥራት የራሱ የትግራይ ሕዝብ ሥራ ነው። ዛሬ ጌታቸው ረዳ ቀበቶ ገና ሲነካካ እሪ! ማለቱ ለትግራይ ሕዝብ ጥሩ አጋጣሚ ነው።የትግራይ ህወሓትን ዘወር በል ማለት ያለበት አሁን ነው።አይ! ህወሓትን እያሽሞነሞንኩ የትግራይን ሕዝብ ሲፈጅ ዝም እላለሁ ማለት ሌላው አማራጭ ነው። ይህ መንገድ ግን መጨረሻው ሞት ነው።መከላከያ የሁሉ አባት፣የሁሉ እኩል ዳኛ ነው።መከላከያ መቀሌ ተለምኖ እንጂ ተገላምጦ እንደማይገባ ማወቅ  ብልህነት ነው።
========/////=======


Friday, October 8, 2021

Breaking News - CNN can face charges and stand in front of International court for its fake news on Star Alliance member, Ethiopian Airlines.


Gudayachn / ጉዳያችን 

October 8,2021

  • CNN fake News may cost over 100 thousand Americans.
  • The recent CNN allegation against Ethiopian Airlines has seriously annoyed many Africans.

Cable News Network (CNN) fake news on the Star Alliance member airline, Ethiopian Airlines may result in a court charge from Ethiopian Airlines. The news released by CNN says ''Ethiopian Airlines used to transport arms for the military''. Ethiopian Airlines press release responding to CNN says '' Ethiopian Airlines strongly refutes the recent allegation by CNN''. 


Ethiopian Airlines is a leading airline in Africa and member of the Star Alliance. Star Alliance is a global airline network which was established by five airlines, Air Canada, Lufthansa, Scandinavian Airlines, THAI and United on May 14, 1997. It has grown to 27 member airlines to become the first truly global airline alliance to offer worldwide service. Among these 27 member airlines Ethiopian is one of them.

Ethiopian Airlines was founded on December 30,1945, by Emperor Haile Selassie. The Airline  provides basic pilot and aviation maintenance training to trainees from African countries including Rwanda, Tanzania, Chad, Djibouti, Madagascar, Sudan. And its training service is also extended to Europe and the Middle East countries. The number of countries using its pilot and aviation maintenance training is increasing from time to time. In the near future, Ethiopian Airline will upgrade its training center to Aviation University.

Currently, Ethiopian Airlines is one of the huge global companies which provides job opportunities for over 100 thousand Americans. The Airline purchasing power from American and other parts of the world is over a billion dollars. All these purchases give an opportunity to thousands of workers globally, particularly in the USA over 100 thousand Americans are benefited. Therefore, it is clear that the recent CNN's fake news may affect 100 thousands Americans also.

The recent CNN allegation against Ethiopian Airlines has seriously annoyed many Africans. A Ugandan living in Norway said to Gudayachn that this is not less than opening a clear war against African icon, Ethiopian Airlines. Now the 'talk of the town' in Addis and other African cities is the importance of Ethiopian Airlines needing to open charges against CNN for its fake news. The latest press release from Ethiopian Airlines seems ''a yellow sign'' to CNN to give the last chance to ask for an official apology. If not, Ethiopian may be obliged to open charges against CNN. Many are saying this can be a good lesson to CNN to respect both international Media ethics and business law.

Here is Ethiopian Airlines press release on CNN.











================///==================

Wednesday, October 6, 2021

ክቡር ጠ/ ሚ/ር ዓቢይ አሕመድ አዲሱን ካቢኔ አስተዋወቁ።3 ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ተካተዋል። የመከላከያ ሚኒስትር ከትግራይ ተሹመዋል።የተሿሚዎች ስም ዝርዝር ሊንኩን ከፍተው ያገኛሉ። PM Abiy Ahmed introduced the new cabinet members.He included 3 opposition political party leaders. Defence Minister is appointed from Tigray.(See the list of the new appointed ministers).

አዲስ ተሿሚ ሚኒስትሮች ቃለ መሃላ ሲፈፅሙ
ፎቶ - ዋልታ 

=================
ጉዳያችን/ Gudayachn
============
Pls. Read in English under Amharic version here below.

ዛሬ መስከረም 26/2014 ዓም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ አዲሱን የካቢኔ አባላት ለአዲሱ የተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው አፀድቀዋል። በእዚህ መሰረት ከተመረጡት የካቢኔ አባላት ውስጥ ከሦስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ማለትም ከኢዜማ፣አብን እና ኦነግ የተካተቱበት ሲሆን የመከላከያ ሚኒስትር ከትግራይ ተሹመዋል።የተሾሙት ስም ዝርዝር በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ከእዚህ በታች ያገኛሉ።

አዲስ የተሾሙ ሚኒስትሮች ዝርዝር 

1.አቶ ደመቀ መኮንን ሀሰን -             ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

2 አብርሃም በላይ (ዶ/ር) -             የመከላከያ ሚንስትር 

3.አህመድ ሽዴ -                           የገንዘብ ሚኒስትር

4.ሙፈሪሃት ካሚል-                       የከተማ ልማት ሚኒስትር

5.ኡመር ሁሴን ኦባ -                       የግብርና ሚኒስትር

6.ኢንጂነር አይሻ መሐመድ -             የመስኖ እና ቆላማ ልማት ሚኒስትር

7.ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ ገለታ-      የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር

8.ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ-                    የትምህርት ሚኒስትር

9.ዳገማዊት ሞገስ -                          የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር

10.ገብረመስቀል ጫላ -                     የንግድና የክልል ውህደት ሚኒስትር

11.አቶ መላኩ አለበል -                     ኢንዱስትሪ ሚኒስትር

12.ብናልፍ አንዱዓለም -                   የሰላም ሚኒስትር

13.ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ፒኤችዲ) -     የፍትህ ሚኒስትር

14. / ሊያ ታደሰ -                     የጤና ጥበቃ ሚኒስትር

15.በለጠ ሞላ -                              ፈጠራ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር

16.አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ -               የቱሪዝም ሚኒስትር

17.አያሌው ሐይቅ -                         የገቢዎች ሚኒስትር

18.ጫልቱ ሳኒ ኢብራሂም -                የከተማ እና የመሠረተ ልማት ሚኒስትር

19.ኢንጂነር ታከለ ኡማ በንቲ -           የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር በመሆን

20.ከጀላ መርዳሳ ቱሉ -                    የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር

21.እርጎጌ ተስፋዬ ( / ) -              የሴቶችና የማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር

22.ፍፁም አሰፋ ( / ) -                የዕቅድና ልማት ሚኒስትር

Facts from today's new cabinet ministers proposed by the PM Abiy Ahmed and ratified by Ethiopian Parliament

Right pointing backhand indexThree big opposition party leaders are included
Right pointing backhand indexSix of them are women
Right pointing backhand indexThe defence minister is from Tigray region
List of Cabinet Minister members

1.Demeke Mekonnen Hassen –  Deputy Prime Minister and foreign affairs minister

2.. Abrham Belay (Ph.D.) - Defence Minister

3.Ahmed Shide –  Finance Minister

4.Muferihat Kamil-  Urban Development Minister

5.Oumer Hussen Oba – Minister of Agriculture

6.Engineer Aisha Mohammed –  Irrigation and Lowland Development Minister

7.Engineer Habtamu Itefa Geleta- Water and Energy Minister

8.Professor Birhanu Nega- Education Minister

9.Dagemawit Moges –  Transport and Logistics Minister

10.Gebremeskel Chala –  Trade and Regional Integration Minister

11.Melaku Alebel –  Industry Minister

12.Binalf Andualem –  Peace Minister

13.Gedion Timothewos (Ph.D.) –  Justice Minister

14.Dr. Lia Tadesse –  Health Minister

15.Belete Mola –  Innovation and Technology Minister

16.Ambassador Nasise Chali – Tourism Minister

17.Lake Ayalew –  Revenue Minister

18.Chaltu Sani Ibrahim –  Urban and Infrastructure Minister

19.Engineer Takelle Uma Benti –  Mines and Petroleum Minister

20.Kejela Merdasa Tulu –  Culture and Sports Minister

21.Ergoge Tesfaye (Ph.D.) –  Women and Social Affairs Minister

22.Fitsum Asefa (Ph.D.) –  Plan and Development Minister

 

 ===================/////===============

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።