ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, October 30, 2021

ኢትዮጵያን እንደሶርያ ሊበትናት ከተነሳው የትግራይ ወራሪ ለማዳን በሚልዮን የሚቆጠር ኢትዮጵያውያዊ አሁንም መነሳት አለበት።ሰሜን ወሎ ዋግህምራ ዞን የሰቆጣ እና አበርጌላ ዙርያ በኢትዮጵያ ኃይሎች እጅ ገብቷል።አሁን 8 ጉዳዮች ትኩረት ይፈልጋሉ።



===============
ጉዳያችን/ Gudayachn
===============
ኢትዮጵያን ለማፍረስ የባዕዳንን ቅጥረኝነት የወሰደው በህወሓት የሚመራው የትግራይ ወራሪ ቡድን በቀጥታ ከውጭ በሚሰጠው መመርያ መሰረት የህዳሴ ግድቡን እንዲያፈርስ ሁሉ ኃላፊነት ወስዶ ኢትዮጵያን ለማጥፋት እየዋተተ ነው። የትግራይ ወራሪ በምንም ዓይነት መንገድ እንጦጦ ቢደርስ መልሶ ኢትዮጵያን አይመራም።ዛሬ 1983 ዓም አይደለም።መደናበር የለም።ጠላትን መምጣት የመከላከያ ኃላፊነት ብቻ አይደለም።የኢትዮጵያ ሕዝብ ኃላፊነቱን ተቀብሏል።ድሮም ኢትዮጵያ የኖረችው እንዲህ ነው።ሁሉም ለሀገሩ ዘብ እየቆመ።ሰላም በምኞት አልመጣም።ከህወሓት ጋር ውይይትም ፈፅሞ እንደማይታሰብ ያለፉት ዓመታት ተሞክሮዎች ግልጥ ያደርጋሉ።

 አሁንም የኃይል ሚዛን በኢትዮጵያ እጅ እንደሆነ ምንም ጥርጥር የለውም።በአስር ሚልዮኖች የሚቆጠር የሰው ኃይል ሆነ ሀብት ያለው በኢትዮጵያ ኃይሎች ስር ነው።ከተሞችን ያዝን የሚሉት ከውስጥ ያሉ ባንዳዎች ቀድመው አውራ ጎዳና እየወጡ ሕዝቡን ለማደናበር ስለሞከሩ መሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል።ህወሓት ወደ መሃል ሀገር የመጣበት መንገድ ዋና ምክንያቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠር የታጠቀም ያልታጠቀም ሕዝብ አግተልትሎ ስለላከ ነው።መከላከያ፣ፋኖ እና ሚሊሻ በሺህ የሚቆጠሩትን ገድሏል።ወሎ በወራሪ የትግራይ ሰራዊት አስከሬን ተሞልቷል።ይህም ሆኖ በሺህ የሚቆጠር እንደ ሕዝብ እየላከ ነው።ለእዚህ ነው እንደ ሕዝብ ሁሉም ሲነሳ ነው ታሪክ የሚቀየረው የተባለው።

አሁን ስምንት ጉዳዮች ትኩረት ይፈልጋሉ።

1) በዋናነት አካባቢውንም ሀገሩንም በሚገባ የሚያቀው የአማራ ሕዝብ በሚልዮን ቁጥር ሆኖ ከቤቱ ያለውን ማናቸውንም መሳርያ ይዞ መነሳት አለበት።እንደ ሕዝብ የመጣ ወራሪ እንደህዝብ መነሳት አለበት።ማንም ለማንም ብሎ አይነሳም።ለራሱ፣ለልጆቹ እና ለሚስቱ ከመገደል ከመዘረፍ እና ከመደፈር ለማዳን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ እንዳትፈርስ የማዳን የሕልውና ጦርነት ስለሆነ።

2) በአማራ ክልል በዞን እና ወረዳ ደረጃ ያሉት አመራሮች አሁንም በሙስና እና በገንዘብ ጉጉት የናወዙ ሕዝብ ብዙ ነገር እያየ የታገሳቸው አሁንም በተልፈሰፈሰ አመራር እና ባልቆረጠ ልብ ሕዝብ ወደኃላ እየጎተቱት ነው።እነኝህን አሁን ካለው ጊዜ አንፃር መቀየር ባይቻልም በቶሎ በተለየ የጦርነት መዋቅር ከጎናቸው ሌሎች ሕዝብ እንዲያስተባብሩ ማስገባት ያስፈልጋል።

3) በህወሓት የሚመራው የትግራይ ወራሪ በመንግስት መዋቅርም ሆነ በንግድ ዘርፍ ሕቡዕ አደረጃጀት ያለባቸው ከተሞች ማለትም ደሴ፣ኮምቦልቻ እና አዲስ አበባ በቶሎ የጁንታው መዋቅር መፍረስ አለበት።በተለይ በአዲስ አበባ ሕዝብ የሚያውቃቸው ነገ ከተማዋን ቀድመው ለማንደድ የቆሙ ባንዳዎች እንዳሉ ሕዝብ አሁንም እየተናገረ ነው።ደሴ ላይ ትናንት እና ዛሬ የሆነው ትምህርት ነው።አብረው ከ30 ዓመት በላይ የኖሩ የትግራይ ወራሪ የቀረበ ሲመስላቸው ቀድመው ወደ መንገድ ወጥተው ከውጭ እንደገባ የጁንታው ሰራዊት ሕዝብ ሊረብሹ ሲሞክሩ ተይዘዋል።በአዲስ አበባም መከላከያ መቀሌን ለቆ ሲወጣ የጨፈሩት ዓይነት ከሃዲዎች መታየታቸው ነገ ከተማውን ለማፍረስ ቀዳሚ እንደሆኑ ትምህርት ሊሆን ይገባል።ከተሞች ውስጥ ከቤት ለቤት ፍተሻ አስፈላጊ ነው።

4) የትግራይ ወራሪ ትኩረቱን ወደ ደሴ ያደረገው አንዱ ምክንያት የምዕራብ ግንባርን ለማሳሳት መሆኑን መገመትም ተገቢ ነው።በእዚህ መሰረት የምዕራብ ግንባር ማጠናከር ችላ ሊባል አይችልም ይልቁንም እስከ ሽሬ አነስተኛ ኃይል በመላክ ጁንታውን የማዳከም ሥራ ሊሰራ ይገባል።

5) የህወሓትን ፕሮፓጋንዳ በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ውስጥ ሆነው የሚሰሩ አሉ።እነርሱም 
- አስፈላጊ የሆኑ ፕሮግራሞች በወቅቱ ለሕዝብ እንዳይደርሱ፣
- ዜናዎች ቶሎ በዩቱብ እና ማኅበራዊ ሚድያ ፕላትፎርም ላይ እንዳይጫኑ በማዘግየት፣
- የዜና ርዕሶቹ አሰልቺ እንዲሆኑ በማድረግ ሕዝቡን ማሰላቸት፣
- ኤዲት ተደርገው መቅረብ ያለባቸው ንግግሮች እና ፕሮግራሞች እንዳለ በማቅረብ መንግስትን ማሳጣት እና ሌሎችም እየሰሩ ነው።

6) የህወሓት ፕሮፓጋንዳ ወይንም ሌላ አፍ የሆኑ ዩቱበሮች እና ተቃዋሚ መሰል እንዲሁም በአማራ እና ኦሮሞ ስም የሚነግዱትን ፊት ለፊት ማጋለጥ እና የቅጣት እርምጃ ያስፈልጋቸዋል። ሀገር የመፍረስ አደጋ ላይ ሆና እነርሱ ሌላ ነዳጅ ሲጨምሩ መተው አይቻልም።ሁሉም የማንንም ጥያቄ ሳይቀበል በራሱ ዝም ማሰኘት አለበት።

7) ቁልፍ በሆኑ የባንክ እና ፋይናንስ እንዲሁም የአይቲ ኃላፊነት ላይ ያሉ ለጁንታው በመስራት የሚጠረጠሩ ሁሉ ለጊዜው ኃላፊነታቸው መዘግየት አለበት።ይህ የሀገር ጉዳይ ነው።

8) ከምሁር፣እስከ ባለሀብት፣በውጭ ከሚኖሩ የወታደራዊ ባለሙያዎች እስከ ወጣት ወንዶች እና ሴቶች ሁሉ ኢትዮጵያ አደጋ ላይ ስትሆን ዛሬም ተቀምጠው የሚያዩ፣ቢያንስ ሕዝብን በመቀስቀስ የማይሳተፉ የዳር ተመልካቾች አሁንም ዝምታቸውን መስበር እና እኔ ምን ላድርግ? ብለው መጠየቅ እና ከችሎታቸው አንፃር የድርሻቸውን ለክተው ለኢትዮጵያ አንድ ነገር መወርወር ያለባቸው ጊዜ አሁን ነው።ዘመን ይቀየራል።ኢትዮጵያም ከፈተናዋ ሁሉ በልጆቿ ትድናለች።ያን ጊዜ ግን ማን ዝም ብሎ አየ? ማን ለሀገሩ ያለውን ወረወረ? የሚታይበት ጊዜ ይመጣል።

የትግራይ ወራሪ መቸም የትም ቢደርስ የኢትዮጵያን ሕዝብ አይገዛም።በእርግጥ የትግራይ ወራሪ አስከሬን ይበዛል።ጁንታው እና የጁንታው ደጋፊዎች ያልተረዱት ጉዳይ የኢትዮጵያ ሕዝብ የዘር ማጥፋት ውስጥ እንዳይገባ እንጂ በእዚህ ደረጃ ከገፋፉት ግን አደገኛ ሁኔታ አይፈጥርም ማለት አይቻልም።ወደ ሲኦል እስክንገባ ኢትዮጵያን እናፈርሳለን እና አማራን እንበቀላለን ብለው የተናገሩትን መቼም የማይረሳ ነገር ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ በማሸነፍ እና አስፈላጊውን ፍርድ በመስጠት ይደመደማል።

ይህ በእንዲህ እያለ  ሰሜን ወሎ ዋግህምራ ዞን የሰቆጣ እና አበርጌላ ዙርያ በኢትዮጵያ ኃይሎች እጅ ገብቷል።በፋኖ እና ሚሊሻ የታጀበው የሰሜን ወሎ ጦርነት ቀጥሏል።የትግራይ ወራሪ ኃይል ከትግራይ እየራቀ በተለጠጠ ቁጥር ወደ ደቡብ ወሎ ሲገፋ ከላይ ከሰቆጣ የኢትዮጵያ ኃይሎች ቆርጠውታል። ይህ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሁንም ወጣቶች ማንንም ሳይጠብቁ ወደ ግንባር ሄደው ሀገራቸውን እንደ ሶርያ ከመፈረስ መታደግ ያለባቸው ጊዜ አሁን ነው።ሀገር በማኅበራዊ ሚድያ እና ፌስ ቡክ አይድንም።መሬት ላይ ያለውን ሥራ በመስራት ለውጥ ይመጣል።  

===========///==========

No comments: