ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, February 29, 2012

በ ታሪክ ''ጢቢ ጢቢ'' መጫወት እና መዘዙ -የአድዋ ድል/ victory of Adwa.


አሜሪካኖቹ ስለ ሃገራቸው ቀደም ስላሉት አመታት ሲናገሩ(ስለ ሁለት መቶ አመት ታሪክ ቢሆንም) የሚጠቀሙበት አንዲት ብሂል አለቻቸው።'' መስራች አባቶቻችን'' የምትል።ስለ ህገ መንግስታቸውም ሆነ ስለ የነፃነት ቀን ሲያወሱ ''መስራች አባቶቻችን'' የምትለው ቃል አትለያቸውም።አውሮፓውያንም ተመሳሳይ ሁኔታ ይጋራሉ።ህገ መንግስታቸው ከረቀቀ  ከመቶ ዓመታት  በላይ የሆናቸው በየዘመኑ አንዳንድ ማሻሻያ ከማድረግ በላይ መሰረቱን ሳያናጉት ይሄው ዛሬም አሉ።ለዚህም ሳይሆን አይቀርም ብዙዎች የአውሮፓ ሃገራት ምክር ቤቶች የመጀመርያውን ምክር ቤት ወይንም ፓርላማ መስራችዋን ሀገር እንግሊዝን ጨምሮ ስፍራቸውን ሳይቀይሩ የመስራች አባቶቻቸውን በማሰብ ቀደምቶቻቸው በሰሩት ህንፃዎች አሁን ድረስ የሚገለገሉት ።የካቲት 23/2004 ዓም (ማርች 2 /2012) የዓድዋ ድል አንድ መቶ አስራ ስድስተኛ ዓመቱ ታስቦ ይውላል። ዘንድሮ ደግሞ ብዙ ወጣቶች ታሪኩ በሚገባ ለትውልድ መተላለፍ አለበት ብለው ከሃገር ውጭ ባሉ ከተሞች እንደሚከበር እይተወሳ ነው።ጥሩ ጅማሮ ነው።በርቱ ማለት ደግሞ ጤናማ ና ኃላፊነት የሚሰማው ሰው ሁሉ  አስተሳሰብ ነው።
ቅድመ  የ ዓድዋ ድል  (1885 እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር)
እንደ  አውሮፓውያኑ አቆጣጠር የካቲት 16 /1885 ጀርመን በርሊን ከተማ በሚገኘው ውብ በሆነው የ ሀገሪቱ ቻንስለር ቬን ቢስማርክ ባለስልጣን መኖርያ ህንፃ ሳሎን ፌሽታ በ ፌሽታ ሆኗል።ሶስት ወር ሙሉ አሰልቺ ውይይት የተደረገበት ዋና ዋናዎቹ የ አውሮፓ ቅኝ ገዢዎች ተሰብስበው '' አንተ ይሄን ያዝ አንተ በእዚህ ውረድ''ተባብለው የ አፍሪካ ካርታ እንደምግብ በመካከላቸው ተዘርግቶ ከወታደራዊ ዘመቻ በፊት አፍሪካን የተከፋፈሉባት ቀን ነበረች። በ እዚህ ስብሰባ ከ 80 በ መቶ በላይ የ አፍሪካ መሬት በ ሃሳብ መስመር እያሰመሩ ተከፋፈሉት። የ በርልኑ ''General act of Berlin conference '' በ ታሪክ ባብዛኛው የሚታወቀው '' The division of Africa '' ወይንም ''scramble of Africa'' (አፍሪካን የ መቀራመት ጉባኤ) ተብሎ ነው ።በ እዚህ ጉባኤ ላይ ጀርመን፣ኦስትሮ-ሀንጋሪ፣ቤልጅየም፣ደንማርክ፣ፈረንሳይ፣ታላቅዋ ብሪታንያ፣ጣልያን ፣ኔዘርላንድ፣ፖርቱጋልን ጨምሮ የተገኙ ሲሆን ቅኝ ግዛትን ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት የተሞከረ ና በዚሁ መሰረት በ 1914 በ ፈረንጆቹ አቆጣጠር አብዛኛው የ አፍሪካ ግዛት በ ቅኝ ገዢዎች የወደቀበት ሁኔታ ነበር።

Thursday, February 16, 2012

Keiseren Haile Selassie sammen med kong Haakon under statsbesøket i Oslo Nov.1954. (Emeror Haile Selassie with King Haakon of Norway during state visit Nov.1954) and Ethiopian Asylem seeker's paradox question.






I

Keiseren Haile Selassie  sammen med kong Haakon under statsbesøket i Oslo Nov.1954. (Emeror Haile Selassie  with King Haakon of Norway during state visit Nov.1954)



Keiseren Haile Selassie  sammen med kong Haakon under statsbesøket i Oslo Nov.1954. (Emeror Haile Selassie  with King Haakon of Norway during state visit Nov.1954)


Saturday, February 11, 2012

George Ayittey is a Ghanaian economist known for his argument that “Africa is poor because she is not free."- wach his speech.

George Ayittey is a Ghanaian economist known for his argument that “Africa is poor because she is not free."

Wednesday, February 8, 2012

''ቡና ጠጡ'' የኢትዮጵያውያን የመረጃ ምንጭ

''ቡና ጠጡ'' የኢትዮጵያውያን የመረጃ ምንጭ 
በ እኛ  ኢትዮጵያውያን ዘንድ ''ቡና ጠጡ'' የምትለው ጥሪ የማናውቅ የለንም።ቢያንስ ልጅ ሆነን ''ሂድ ማሙሽ አልያም ሚሚ እገን ቡና ጠጡ በል ወይም በይ'' ተብለን  ስንላክ አድገናል።እኛም  አድገን '' ካፈ'' ቤት ጎራ ብለን ቡና  እየቀመስን  የ ልባችንን ከ ወዳጅ ዘመድ  ጋር ያላወጋን  ማን ነን? ሰሞኑን አንድ ወዳጀ  ቡና እየጠጣ የተነሳውን  ፎቶ  አየሁ እና ብዙ ነገር ስለ ቡና ትዝ አለኝ። በመቀጠል  ግን ስለ ቡና ያነበብኩትን እና ያስተዋልኩትን ትንሽ ማለት ፈለግሁ።

ቡና  ለ እኛ ለ ኢትዮጵያውያን ከ ገጠር እስከ ከተማ   የሚጠጣ ትኩስ መጠጣችን ነው። ስለ ቡና አመጣጥ ስረ መሰረት የ እንግሊዝኛው ''አንሳይክሎፕድያ'' በ አንድ ሲኒ ቡና ስእል ስር እንዲህ የሚል ፅሁፍ በ ማብራርያነት ያስነብበናል :- 
''ቡና መልኩ ጥቁር አልያም ቡናማ ሲሆን የተገኘው ከ ኢትዮጵያ ነው '' ይላል ( http://en.wikipedia.org/wiki/Coffee)
አዎን ቡና አሁን ላለችው ዓለም የራሱ  ድርሻ  አንዳለው ብዙዎቻችን ልብ ያልነው አይመስልም:: ለ እንዱስትሪው አብዮት ዋነኛ የ አዳዲስ ሳይንሳዊ፣ፖለቲካዊ፣አና ምጣነሃብታዊ ሃሳቦች መፍለቅያነት ምክንያት ከነበሩት አንዱ  የ ኢንዱስትሪ አብዮት መጠንሰሻ የነበረችው  የ እንግሊዝ የቡና መጎንጫ ቤቶች ''ኮፊ ሃውስ '' ይባሉ የነበሩት ቤቶች ሚና ቀላል አንድልነበር ታሪክ ያስረዳናል:: 


Thursday, February 2, 2012

ምስጋናችን እና ወቀሳችን

የ ምስጋና ባህላችን ገና ብዙ ይቀረዋል።ወቀሳችንም እንዲሁ:: ለ አዚህ ማሳያ አዲስ አበባ ንግድ ሥራ ኮሌጅ ሳለሁ አንድ መምህራችን ክፍል ውስጥ ያሉን አይረሳኝም እውነተኛ ታሪክ ስለሆነ አስተማሪም ነው።መምህሩ ከ አንግሊዝ ሀገር የ ፒአችዲ ዲግሪአቸውን አንደያዙ እኛ ክፍል መመደባቸው ነበር::

Wednesday, February 1, 2012

'' እያከበሩ ማፍረስ'' ጠቅላይ ሚንስትሩ የተናገሩት

'' እያከበሩ ማፍረስ''  ጠቅላይ ሚንስትሩ  የተናገሩት

'' እያከበሩ ማፍረስ'' የምትለው አባባል  የ  ዛሬ ሶስት  ዓመት ገደማ ጠቅላይ ሚንስትሩ  የተናገሩት ትዝ ይለኛል።
ወቅቱ ዝናብ በመጠኑ የሚጥልበት ወቅት ነበር። ።እለቱ ቅዳሜ ነበር ከረፋዱ አራት ሰዓት አካባቢ ቦሌ መንገድ የሚገኘው የ ''ሚሊንየም'' አዳራሽ ውስጥጠቅላይ ሚንስትሩ የ ቀን አበል የተከፈላቸውንም ጭምር ይዘው  አልፎ አልፎ እንደሚአደርጉት የ ፓርትያቸውን ደጋፊ ወጣቶች ሰብስበው ንግግር እያረጉ ነው።የለበሱት ጃኬት እና ያረጉት የወጣት ኮፍያ ከ ወጣቶቹ ጋር አመሳስሏቸዋል።

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።