ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, March 30, 2021

የኢትዮጵያን ፀጥታ ለማረጋገጥ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ራሳቸውን እና ቤተሰባቸውን ከሽ.ነ.ድ. መጠበቅ አለባቸው።

  • የውጪ ባዕዳን እና በውስጥ ያኮረፉ ከሊቅ እስከደቂቅ ያለው ኢትዮጵያዊ ላይ ሊዘምቱበት የሚዘጋጁት በሽነድ ነው።

ኢትዮጵያ በጥገናዊ ለውጥ ውስጥ ከገባች ነገ መጋቢት 24/2013 ዓም ሦስተኛ ዓመቷን ትይዛለች።በእነኝህ ሦስት ዓመታት ውስጥ በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል።ይህ ለውጥ ባይመጣ ኖሮ ኢትዮጵያ ዛሬ እጅግ አደገኛ ብቻ ሳይሆን ሕልውናዋም ጥያቄ ውስጥ የማይገባበት ምክንያት አይኖርም።ምክንያቱም የነበረው የውስጥ ቅራኔ ውስብስብ ከመሆኑ አንፃር በቀጥታ የእርስ በርስ ጦርነት አይኖርም ማለት አይቻልም።አንዳንዶች ይህ ሲባል ዛሬ ያለችው ኢትዮጵያ ከሦስት ዓመት ከነበረችው የባሰ ነው ብለው የሚናገሩ በማኅበራዊ ሚድያ የሚገልጡ ከአጠቃላይ ኢትዮጵያ የነበረችበት የችግር ጥልቀት ያልተረዱ ናቸው።ባለፉት ሦስት ዓመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች በሙሉ ወደ ሀገር ቤት ገብተዋል፣ስደተኞች ወደ ሀገራቸው በነፃ መግባት መውጣት ችለዋል፣በሺህ የሚቆጠሩ እስረኞች ተፈትተዋል፣የመገናኛ ብዙሃን ነፃነት በአንፃራዊ መልኩ የተሻለ ነው፣የትምህርት ፖሊሲ በአዲስ መልክ ተዘጋጅቷል፣የኢትዮጵያ ምድር ኃይል እና አየር ኃይል መዋቅር ማሻሻያ ተሰርቷል፣የፍትሕ፣የፖሊስ እና ሌሎች መዋቅሮች ማሻሻያ ተጀምሯል፣የዓባይ ግድብ ፕሮጀክት በአዲስ መልክ ተከልሷል፣በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መሃከል ሰላም ተፈጥሯል ሌላም ስራዎች ተሰርተዋል።እነኝህ እያንዳንዳቸው ቢተነተኑ ብዙ ገፅ ማብራርያ የሚፈልጉ ናቸው።

ከላይ በመጠኑ የተጠቀሱት ስራዎች እና ሌሎች ያልተጠቀሱት ተግባራት የተሰሩ እና እየተሰሩ ቢሆኑም በሌላ በኩል ደግሞ የሕዝብ መፈናቀል፣የጎሳ ግጭቶች እና የእምነት ቦታዎች መቃጠል የተፈፀሙ አሳዛኝ ድርጊቶች ናቸው።ይህ ሁሉ ሆኖ ግን አጠቃላይ ሂደቱን ስንመለከት ኢትዮጵያ ከግዙፍ ችግሮቿ ለመውጣት ከትናንቱ እጅግ በላቀ መስመር ላይ እንዳለች መረዳት ይቻላል።ሆኖም ግን በቀጣይ ወራት ኢትዮጵያ ከምትተገብራቸው ሁለት ግዙፍ ስራዎች ማለትም የአባይ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ መሙላት ተግባር እና የብሔራዊ ምርጫ አንፃር የኢትዮጵያን መነሳት የሚያሰጋቸው ባዕዳን እና በውስጥ ያኮረፉ በውጭ እና በሀገር ውስጥ ያለውን ኢትዮጵያ ከሊቅ እስከደቂቅ ሊዘምቱበት የሚዘጋጁት በሽነድ ነው።

ሽ.ነ.ድ ኢትዮጵያን ለማጥቃት የኢትዮጵያ ጠላቶች ቀደም ባሉ ዓመታት ሲጠቀሙበት የነበረ ድርጅት ነው።ቃሉ ለመጀመርያ ጊዜ የሰማሁት የአንድ ዓመት የኮሌጅ ተማሪ ሳለሁ የዛሬ 30 ዓመት የኢትዮጵያ ኮሌጆች እና ዩንቨርስቲዎች ወደ ብላቴ የአየርወለድ ማሰልጠኛ ሲዘምቱ በሄድኩበት ወቅት ወደ አስር ሺህ የሚቆጠሩ ተማሪዎች ውስጥ ተማሪዎቹን ለማሸበር የሚወሩ ወሬዎችን ተማሪው የሰጠው ስም ነበር።ሽነድዎች በጣም ጥቂት ሲሆኑ የጠላት ተልዕኮ ይዘው በወቅቱ የነበሩት ሽምቅ ተዋጊዎች ለማግነን የታሰበ  የውሸት ወሬ እየፈጠሩ የሚያወሩ ናቸው።እነኝህን ኃይሎች ተማሪው ወድያው ስለነቃባቸው በግዙፉ የብላቴ ተራራ ላይ አስር ሺህ ተማሪ በተሰበሰበበት ነው ሽነድ የሚለው ስም በይፋ የተሰጣቸው።ሽ.ነ.ድ ማለት ሽብር ነዥ ድርጅት ማለት ነው።

ሽ.ነ.ድዎች ዛሬ የት ናቸው ?

ሽነድዎች በብላቴ ተማሪውን በተለያየ ወሬ ለመረበሽ ሞክረው እንደነበር ሁሉ ዛሬ ሽነድዎች የኢትዮጵያን ሕዝብ ከታች ሊስትሮ እስከ ጠጅ ቤት፣ከገጠር ጠላ ቤት እስከ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል፣ከታክሲ ተሳፋሪ እስከ ቦይንግ 767፣ከቤተ መቅደስ እስከ መስጊድ፣ከዩንቨርስቲ እስከ ቀበሌ ፅህፈት ቤት፣በውጭ ደግሞ በዩቱብ መስኮት ላይ ተንጠላጥለው ይገኛሉ።

ዛሬ ሽነድዎች ሸነድ መሆናቸውን የሚያውቁ እና የማያውቁ ተብለው በሁለት ይከፈላሉ።  
 
ሽነድዎች እንዲሆኑ የሰለጠኑ እና መሆናቸውን የሚያውቁ የመኖራቸውን ያህል ሽነድ መሆናቸውን ሳያውቁ የሽነድን ሥራ የሚሰሩ አሉ።ሽነድ መሆናቸውን የሚያውቁ ሆን ብለው ህዝቡ መሃል ሆነው ከቤተሰባቸው ጀምሮ በቀን ውሏቸው ያገኙአቸውን ሁሉ በተሰጣቸው የውሸት ወሬ ሁሉ ላገኙት ሲያሰራጩ የሚውሉ ናቸው።ጧት ከባላቸው ወይንም ከሚስታቸው ቀጥሎ ጎረቤቶቻቸውን ሁሉ  ኢትዮጵያ እንዲህ ልትሆን ነው፣አዲስ አበባ ልትጠፋ ነው፣አንድ ሰው ሞተ ሲባሉ አንድ መቶ ሰው ሞተ እያሉ የሚያወሩ ናቸው። ሽነድ መሆናቸውን የሚይውቁ ሰዎች እንዳይታወቁ የሚጠነቀቁ ናቸው።የውሸት ወሬ አከፋፋይ እና አመንጪ ስለሆኑ እነርሱ የውሸቱን ወሬ የመለኮስ ሚና እንጂ ማቀጣጠሉን እራሳቸው ሽነድ መሆናቸውን ለማያውቁ ማቀበሉ ላይ ነው የሚተጉት።

ሽነድዎች አንዱ ተግባራቸው ሕዝብ ተስፋ እንዲቆርጥ የሚያደርጉ ማናቸውንም ወሬዎች ማውራት ነው።በጣም አሰቃቂ ነገር ሲፈፀም ይፈነጥዛሉ።ሕዝብ በመንግስት እና በመሪዎቹ ላይ ተስፋ እንዲቆርጥ በዋናነት በጠቅላይ ሚኒስትሩ እና በሌሎች ኢትዮጵያን ብለው በሚሰሩ ባለሙያዎች ላይ ሁሉ የውሸት ወሬ ይከፍቱባቸዋል።በእዚህም ሕዝብ ውሸት ሲደጋገምለት ያምናል በሚል ስራዬ ብለው ሕዝቡን ማሸበር ላይ በመስራት ላይ ናቸው።ሌላው ቀርቶ ዛሬ ኢትዮጵያ በመጪው ዓመት ካሜሮን ላይ ለሚደረገው የአፍሪካ ዋንጫ ማለፍዋ አናዷቸዋል።በማኅበራዊ ሚድያ ሰሞኑን በሚያወሩት ወሬ እና በጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ላይ በከፈቱት የውሸት ዘመቻ ሕዝቡን ያስተከዙት እና ተስፋ ያስቆረጡት መስሏቸው ባለበት ሰዓት ከመቅፅበት ከአይቨሪኮስት የተሰማው የኢትዮጵያ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ሕዝብ አውራ ጎዳና ላይ ወጥቶ ማስጨፈሩ ሽነድ የደከመበትን ሕዝቡን የማስተከዝ ሥራ ገደል መክተቱ አናደዳቸው።

ሸነድዎች በቀጣይ ሊሄዱበት ያሰቡበት መንገድ ያልላካቸውን እግዚአብሔር እንደላካቸው እያደረጉ በክርስትናውም ሆነ በእስልምናው መምህራንን በገንዘብ እየገዙ ትንቢት ተገለጠልን እያሉ ማውራት ነው።ዘመኑ ደግሞ የዩቱብ ዘመን ስለሆነ በቀላሉ ህዝቡ ጋር እንደሚደርሱ ያስባሉ።ሽነድዎች ጥቂት በመሆናቸው በወሬ የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማሸበር አቅም የላቸውም። ነገር ግን ሽነድ መሆናቸውን ሳያውቁ የሽነድዎችን የሐሰት ወሬ የሚያሰራጩ መብዛታቸው ወሬው እንደፈለገ እንዲዞር እረድቷቸዋል።

በውጭ ሀገርም ሆነ በሀገር ቤት እጅግ ቅኖች፣ለሀገር አሳቢዎች እና የኢትዮጵያን ከፍ ማለት የሚፈልጉ ብቻ ሳይሆን በተጠሩበት ሁሉ ቀድመው ለሀገራቸው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስለ ኢትዮጵያ ከሽነድዎች በሚሰሙት የውሸት እና የተጋነነ ወሬ ተጨንቀው ሌሎችን በማስጨነቅ ሳያውቁት የሽነድ ቫይረስ ያስተላልፋሉ።ሽነድዎች ዋና ዓላማቸው ይህ ነው።ሕዝብ እንዳይረጋጋ፣እንዳይደሰት እና ተስፋ እንዳይታየው ማድረግ ስለሆነ ሽነድ መሆናቸውን ሳያውቁ የሽነድን ሥራ የሚሰሩትን ከቤተሰብነት እስከ መልካም ወዳጅ ቀርበው የውሸቱን ወሬ ይነዙባቸዋል።

ባጠቃላይ በቀጣይ ወራት ኢትዮጵያን ለመረበሽ በጦር ሜዳ ያልተሳካለት የውስጥም ሆነ የባዕዳን ኃይሎች የቀራቸው ብቸኛ መንገድ ሽነድ ( ሽብር ነዥ ድርጅት) ነው።መንግስትም ሆነ ሕዝብ ከጠጅ ቤት እስከ ሸራተን ባር፣በሞባይል ልስክ ከሚለቀቅ የውሸት ወሬ እስከ የዩቱብ የውሸት ወሬ ነዥ ተናበው ነው የሚሰሩት።ሸነድ በተራ መንደር ውስጥ ብቻ የሚገኙ አይደሉም።በመንግስት መስርያቤት እና በመንግስት መገናኛ ብዙሃንም ሳይቀሩ የሚዘጋጁ ፕሮግራሞች ላይ የረቀቁ የስነ ልቦና ዘመቻ የምትከፍት ቃላት በመሰንቀር ወይንም መልካሙን ዜና በመደበቅ ካልተቻለ ቆርጦ በማስተላለፍ ሁሉ ሸነድ ኢትዮጵያን ለማተራመስ ይሰራል።ስለሆነም ከሀገር ቤት እስከ ባሕር ማዶ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከቤተሰብ እስከ ጎረቤት፣የቅርብ እና የሩቅ ወዳጅ ሁሉ ሳያውቀው የሸነድ አስተላላፊ እንዳይሆን ነቅተው እና ተግተው እራሳቸውንም ቤተሰባቸውንም መጠበቅ አለባቸው። 

========================//////================

 ********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 
  

Sunday, March 28, 2021

በሙ/ጥ/ዲ/ ዳንኤል ክብረት ለኢትዮጵያ እንደራሴዎች ምክርቤት ምርጫ ቅስቀሳ ማስጀመርያ መርሐግብር ላይ የመሐመድ ካሳ ምስክርነት ፣የዶ/ር ዳኛቸው ንግግር እና የዕጩ ተወዳዳሪው ሙ/ጥ/ዲ/ ዳንኤል ክብረት ንግግር (ቢመለከቷቸው ብዙ የሚያተርፉባቸው 3 ቪድዮዎች)

ሙ/ጥ/ዲ/ ዳንኤል ክብረት በያዝነው ዓመት 2013 ዓም በሚደረገው ብሔራዊ እንደራሴዎች ምርጫ የግል ዕጩ ተወዳዳሪ ናቸው።ትናንት መጋቢት 18/2013 ዓም በአዲስ አበባ ካፒታል ሆቴል የምርጫ ቅስቀሳ ማስጀመርያ መርሐግብራቸው ላይ የተደረጉ ሦስት ድንቅ ንግግሮች ቪድዮዎች ከእዚህ በታች ቀርበዋል።

የመሐመድ ካሳ ምስክርነት  

የዶክተር ዳኛቸው አሰፋ ንግግር 

የሙ/ጥ/ዲ/ ዳንኤል ክብረት ንግግር 


********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Thursday, March 25, 2021

رئيس الوزراء سد النهضة مصدر إزدهار وليس مصدر قلق لدول The Renaissance Dam is a source of prosperity not a source of concern for downstream countries

رئيس الوزراء سد النهضة مصدر إزدهار وليس مصدر قلق لدول المصب
''The Renaissance Dam is a source of prosperity not a source of concern for downstream countries'' The PM of Ethiopia,Abiy Ahmed.
Watch full video in Arabic version.

********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Monday, March 22, 2021

በአዲሱ የኢትዮጵያ የትምህርት ፖሊሲ እና ፍኖተ ካርታ አማራጮችና አተገባበሮቻቸው ላይ ከትምህርት ሚኒስትሩ ከዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን መኩርያ ማብራርያ (ቪድዮ)

ቪድዮ = ኢቲቪ መጋቢት 13/2013 ዓም (ማርች 22/2021 ዓም)

********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Sunday, March 21, 2021

አቶ ሽመልስ እና የክልሉ አስተዳደር ኦሮምያን ማስተዳደር እንዳቃተው በግልጥ መናገር አለበት።ብልጥግና በፍጥነት ተሰብስቦ በኦሮምያ ክልል ላይ ውሳኔ ማሳለፍ አለበት።



የኦሮምያ ክልል፣ላለፉት ሦስት ዓመታት በተለየ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት ክልሎች  ውስጥ የፀጥታ  ችግር ሆኖ ቀጥሏል። ክልሉ በመጀመርያ ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ የገባው ከሱማልያ ክልል ጋር ነበር።በእዚሁ በተነሳው የክልል መስመር ጭቅጭቅ ወደ አንድ ሚልዮን የሚጠጋ ሕዝብ ተፈናቀለ።በመቀጠል በስም ኦነግ ሸኔ እየተባለ ነገር ግን የክልል ሚሊሻ መሆናቸው የተነገረ በጌድዮን ሕዝብ ላይ ጥቃት ፈፀሙ።መቶ ሺዎች ተፈናቀሉ።እናቶች እና ሕፃናት በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።በእዚህ ብቻ አላበቃም።በምዕራብ ወለጋ በተደጋጋሚ፣በሐረር ደጋማ ቦታዎች፣በአርሲ እና ሻሸመኔ ላይ የተፈፀሙት ጥቃቶች በሙሉ ከኦሮምያ ክልል ሚሊሻ እና ቢሮክራሲ የታገዘ ነው።ጥቃቶቹ በእዚህ ብቻ አላቆሙም።በመተከል እና በአጣዬ ሰሜን ሸዋ የተፈፀሙት ጥቃቶች በሙሉ በንፁሃን ላይ የተፈፀሙ የሽብር ጥቃቶች ናቸው።

ከላይ የተፈፀሙት ጥቃቶች በሙሉ በጅምላ በእናቶች እና ሕፃናት ላይ መፈፀማቸው ብቻ ሳይሆን በተደጋጋሚ በዙር የተደረጉ ከመሆናቸው በላይ ፈፃሚዎቹ ላይ በአርሲ እና የሻሸመኔ እንዲሁም ሐረር ላይ ወንጀል የፈፀሙት ታስረዋል፣ምዕራብ ወለጋ ላይ ባለው ሽብርተኛ ቡድን ላይም እርምጃ ተወስዷል እየተባለ ቢነገርም የኦሮምያ ክልልም ሆነ የፈድራል መንግስት ላይ ያሉት ባለስልጣናት ቁርጥ የሆነ እርምጃም ሆነ ጉዳዩን በተገቢው  ሲኮንኑት አይታዩም።ለምሳሌ በያዝነው ሳምንት መጨረሻ በሰሜን ሸዋ አጣዬ  ከተማ ላይ የኦሮምያ ክልል ሚልሻ በሕዝቡ ላይ በቀጥታ በፈፀመው ጥቃት ከ20 በላይ ንፁሃን መገደላቸው መነገሩ ይታወቃል። የሚገርመው ጥቃቱን ያደረሰው የኦሮምያ ክልል መግለጫ ሳይሰጥ እና ክልሉ ምን ዓይነት እርምጃ እንደወሰደ ሳይገልጥ የተጠቃው የአማራ ክልል ነው መግለጫ የሚሰጠው። በተለይ የሰሜን ሸዋው  ጥቃት የብልጥግና ፓርቲ በቶሎ ተሰብስቦ ወሳኝ እርምጃ እንዲወሰድ ካላደረገ የሀገሪቱ ትልቅ የፀጥታ ችግር  እንደሚሆን መረዳት ቀላል ነው። 

አሁን ብልጥግና ጊዜ የለውም።ብልጥግና ብቻ ሳይሆን የመከላከያ ሰራዊቱም በኦሮምያ ክልል ሽብርተኛ አስተሳሰብ የተሟሸ ነው የሚል ስሜት በከፍተኛ ደረጃ በሕዝቡ ውስጥ እየተደመጠ ነው።ይህ አደገኛ የፀጥታ አደጋ ነው። በትናንትናው የአጣዬ ጥቃት ላይ የፌድራል ጦር ከመጣ በኃላ አጥቂውን የኦሮምያ ክልል ሚሊሻ የመውጫ መንገድ መስጠቱ እና ሕግን ከማስከበር ይልቅ የሚዘርፉትን ''የያዛችሁትን ይዛችሁ ሂዱ'' ሲሉ ተመለከትን ያሉ የሰሜን ሸዋ ነዋሪዎች በመንግስት ላይ ከፍተኛ ቅሬታ ተሰምቷቸዋል።

ለማጠቃለል የአማራ ክልል ሕዝብ  እንደሌላው ኢትዮጵያዊ በሕግ እና በመንግስት ላይ ከጥንት የመጣ መተማመን ያለው ሕዝብ ነው። ሕግ ያከብራል፣መንግሥትንም ያከብራል።ለእያንዳንዱ ጉዳይ ምክንያታዊ እና አሳማኝ ነገሮች ይፈልጋል።''በሕግ ከሄደው በሬዬ ያለፍትሕ የሄደችው ዶሮዬ ትቆጨኛለች'' የሚል ሕዝብ የፍትህ እና የመንግስት ሰራዊት አድሎ በእዚህ ደረጃ መገለጡን ከተመለከተ ይወስናል።ውሳኔውን ለማስቀየር ሌላ አንድ መቶ ዓመታት አይበቁም።መንግስት በጊዜው ማሰብ አለበት። የኦሮምያ ክልል ሚሊሻ እና ቢሮክራሲ ውስጥ የተደበቀው የኦነግ መዋቅር እና አስተሳሰብ ለአማራ  ክልል ብቻ ሳይሆን ለአፋር፣ለሱማሌ፣ለደቡብ እና ለትግራይም አደጋ እንደሆነ ሁሉም ያውቃሉ።ስለሆነም በተሰበሰቡበት የብልጥግና ፓርቲ ውስጥ በቶሎ ተሰብስበው መሬት የወረደ ለውጥ ማምጣት አለባቸው።ይህ ካልሆነ የኦሮምያ ክልል ላይ  ሌሎች የብልጥግና ፓርቲ አባላት ግንባር ገጥመው በክልሉ  ውስጥ የበቀለውን የሽብር ቡድን ስርዓት ሊያስይዙት ይገባል። አቶ ሽመልስ እና የክልሉ አስተዳደር ኦሮምያን ማስተዳደር እንዳቃተው በግልጥ መናገር አለበት።ብልጥግና በፍጥነት ተሰብስቦ በኦሮምያ ክልል ላይ ውሳኔ ማሳለፍ አለበት።
********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Wednesday, March 17, 2021

ልብ የሚሰብር ዜና - የለውጥ ሐዋርያው የታንዛንያው ፕሬዝደንት ጆን ማጉፉሊ በ61 ዓመታቸው አረፉ።ሙስናን ለመዋጋት ተዓምር ሰርተዋል።፣ታንዛንያ ከምዕራብ ኩባንያዎች ጋር የገባችውን የማዕድን ውል ሀገሪቱን በሚጠቅም መልክ እንዲቀየር እየተጋደሉ ነው ያረፉት።አፍሪካዊ መሪዎቻችንን እናክብር! እንጠብቅ!



ለምዕራባውያን የማዕድን ኩባንያዎች የራስ ምታት ነበሩ።ለታንዛንያ መድሃኒት ነበሩ።በአጭር ጊዜ ተአምራዊ የተሰኘ ለውጥ አምጥተዋል።የስም ማጥፋት ዘመቻ በውጭ ሚድያዎች ተካሂዶባቸዋል።የ''ዎል ስትሪት'' ድረ-ገፅ ከሰዓታት በፊት የዕረፍት ዜናቸውን የዘገበበት ርዕስ አነጋጋሪ ነው።''ከማዕድን ኩባንያዎች ጋር ውዝግብ የገቡት የታንዛንያው ፕሬዝዳንት በ61 አመታቸው አረፉ'' ይላል። ይህ ርዕስ በራሱ የታንዛንያው ፕሬዝዳንት ምን ያህል ለምዕራብ ኩባንያዎች የራስ ምታት እንደነበሩ፣ለታንዛንያ ደግሞ ሩቅ አሳቢ እንደነበሩ አመላካች ነው። 

ፕሬዝደንት ጆን ማጉፉሊ ካለፈው የካቲት ጀምሮ ለሕዝብ አልታዩም ነበር።ፕሬዝዳንቱ ያረፉት በዳሬሰላም ሆስፒታል ሲሆን ለሞታቸው ምክንያት የልብ ህመም መሆኑን የሚናገሩ አሉ።በሌላ በኩል በኮቪድ ምክንያት እንዳረፉም የሚወጡ ዘገባዎች አሉ።የታንዛንያው ምክትል ፕሬዝዳንት በመንግስት ቴሌቭዥን ለሕዝባቸው መርዶውን ካረዱ በኃላ በቀጣይ 14 ቀናት በታንዛንያ የሐዘን ቀን እንደሚሆን እና የሀገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ ዝቅ ብሎ እንደሚውለበለብ ተወስኗል።
ስለ ፕሬዝዳንቱ ሸገር ራድዮ የዛሬ ሶስት ዓመት በመቆያ ፕሮግራም ያቀረበውን እስከመጨረሻ ያድምጡ።


ከምሥራቅ አፍሪካ መሪዎች የታንዛንያውን ፕሬዝዳንት ጆን ማጉፉሊ ማረፍ በተመለከተ ከተባሉት 








********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Monday, March 15, 2021

በ1952 ዓም ኢትዮጵያዊቷ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ብዙአየሁ አጎናፍር ''በጭፍን ጥላቻ (Prejudice)'' ላይ ከህንድ፣እንግሊዝ፣አሜሪካ እና ኖርዌይ ተማሪዎች ጋር በአሜሪካ ያደረገችው ድንቅ ውይይት።(ቪድዮ)1959 High School Students from Ethiopia,Norway,UK,India and USA discussion on Prejudice.

ውይይቱ - 
- በወቅቱ የነበረውን የዓለምንም ሆነ የኢትዮጵያዊ ትውልድ ስሜት  ያሳያል፣
- በወቅቱ የነበረው የሁለተኛ ደረጃ  ኢትዮጵያዊ ተማሪ ብስለት እና ችሎታ ያሳያል።
- የኢትዮጵያን የወቅቱ የትምህርት ደረጃ ያሳያል።
********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Sunday, March 14, 2021

ታታሪዎቹ የወልቃይቴ ባለ ሐብቶች ስለተፈፀመባቸው ግፍ የተናገሩት አዲስ ቪድዮ


********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Wednesday, March 10, 2021

The Tigray region of Ethiopia is becoming more safe after the TPLF was removed. Over 40 Ambassadors and Diplomats were enjoying themselves in Mekelle today.

Over 40 Ambassadors and diplomats after visiting Mekele, March 10,2021


Gudayachn News

Ethiopia's transition to democracy is continuing with great support of the new generation. Even though there were ups and downs in the political environment of the country, Ethiopians' journey to democracy is becoming more visible. One of the recent events that will be a pushing factor towards democracy and stability is the National Election to be held in May,2021. Currently, it is possible to say most unstable situations, in different parts of the country,are almost under the control of the central Government led by Prime Minister Abiy Ahmed(PhD). In fact there are some armed groups in Western Welega zone and even in the Tigray region those who are cut from information and lost their directions. These are not well organized armed groups and will not even pass from the single campaign of the local militias.


It is a tremendous effort that the Ethiopian Government's accomplishment of its law enforcement process in Tigray region. Tigray People Liberation Front (TPLF),which was also killing and exploiting the region's people, was getting rid to fight with the central government for almost three consecutive years. However the Ethiopian National Defence Force (ENDF) can finalized the law enforcement process just within a few days. This is not only due to the ENDF's high standard capacity to mobilize any kind of war in any geographical area, but it was also because the TPLF's outdated and ethnocentric ideology has never been accepted by Ethiopians.


Today's event in Mekelle is another indicator of how the situation is almost under control.According to Ethiopian Foreign Minister official source, State Minister H.E. Ambassador Redwan Hussien and 40 resident Ambassadors and diplomats,including US Ambassador, in Addis Ababa have paid a visit to Mekelle city today,March 10/2021.The news elaborate that upon arrival at Alula Aba Nega Airport, in Tigray region capital Mekelle, they were warmly welcomed by H.E. Dr. Mulu Nega, Chief Executive of the Interim Administration of Tigray. Dr. Mulu Nega, and colleagues briefed the Ambassadors about current situations in Tigray, particularly on the rehabilitation and rebuilding efforts as well as security issues in the region.


It was recalled that in the recent press release of the Foreign Minister spokesperson, Amb. Dina Mufti, the Ethiopian Government has already covered 70% of food and other basic necessity demands of the Tigray Region. Now the Government is demanding Aid agencies and the international community,only to cover the remaining 30%, to provide all the necessary humanitarian support using the unfettered access granted to them by the federal government.


Here below are photos when over 40 Ambassadors and diplomats visit Mekele on March 10,2021

Source : MFA




********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 


Open letter to the Secretariat of the UN Security Council -The Humanitarian Crisis in Tigray, Ethiopia, and the Need for Balance



 


By Aklog Birara (Dr) 

March 9/2021 

Dr. Aklog Birara Sr. Advisor at World Bank Washington, District of Columbia, United States

1. Ethiopia is a founding member of the UN and a major contributor to peacekeeping  operations. It hosts the African Union and numerous UN specialized agencies. 

2. For decades, Ethiopia stood out as a pillar of stability, a promising model for sustainable  and equitable development in Africa. 

3. Ethiopia’s reform process over the past 3 years was poised to establish multi-party  democracy through free and fair elections; and restore public confidence in Government  officials at all levels of government after almost 30 years of corrupt governance. The  reform process was marred by the defection of the Tigray People’s Liberation Front  (TPLF) that sponsored at least 133 ethnic conflicts in the past 12 months alone.  

4. The TPLF committed treason and heinous crimes against humanity in its selective  murders of non-Tigrean military officers and soldiers affiliated with Ethiopia’s Northern  Command in Tigray; followed by its wholesale massacres of Amhara at the village of Mai  Kadra where 1,200 innocent people, including day laborers were slaughtered.  

5. The international community failed to hold the TPLF and its allies accountable for the  numerous reported and unreported Mai Kadra like killings throughout Ethiopia. Reversing the matter and accusing the victims as responsible for crimes they never  committed is unprecedented in the annals of recent history. This undermines the moral  high ground and authority of international institutions including the UN and the AU. 

6. Over the 27 years of brutal governance, the TPLF promulgated draconian civil society  and anti-terrorist laws; killed tens of thousands of Oromo, Somali, Annuak, Amhara and other nationalities, most of them young; stole, siphoned off and illicitly moved out of  Ethiopia an estimated $40 billion that it is currently using to lobby, conduct  cyberwarfare, disseminate disinformation, and finance the resurgence of the TPLF.  

7. The TPLF must be designated as a terrorist organization. It committed heinous crimes  and treason. It is also determined to make Ethiopia another Syria, Somalia and or  Yemen. This is hardly in the interest of Africa or the world community.  

8. A unified, stable, and prosperous Ethiopia is in the interest of the international  community. This is where the community of nations must focus. 

9. Tragically, TPLF resurgence is being orchestrated in cohort with Ethiopia’s traditional  enemies including Egypt and Sudan. The recent invasion of Ethiopia by Sudan, the  annexation of Ethiopian sovereign territory by Sudan, the Defense pact signed by Egypt  and Sudan and the stalled tripartite negotiation concerning the filling and operation of  the Grand Ethiopian Renaissance Dam (the GERD) all pose imminent danger for Ethiopia  and the entire Horn of Africa.  

10. Tripartite negotiation on the GERD must continue under the auspices of the African  Union. Further involvement by the UN, the European Union, the United States, and the World Bank in this African matter will undercut and severely impair the role of the  African Union. The UN Security Council must refrain from entertaining Egypt’s demand.  

11. The Ethiopian people need peace. Ethiopia needs national reconciliation and consensus,  and not more internal conflicts and proxy wars. The war in Tigray caused incalculable  damage estimated at billions of Ethiopian Birr. The humanitarian crisis and the scars of  war require long-term investment by the Government of Ethiopia and its international  partners. Ethiopian society needs to heal. This is where the UN Security Council and the  African Union can help. 

12. Sanctioning Ethiopia will do the exact opposite. Economic and other sanctions against  Ethiopia will inflame the situation further. It will be unprecedented. This option must  not even be contemplated by the UN. Such a move will in fact embolden extremist,  jihadist, terrorist, and other dangerous forces in the Horn of Africa.  

To be relevant, the UN Security Council Must be Fair and Impartial  

From the League of Nations up to now, Ethiopia, as a country, has been committed to collective  security. It is committed to the foundational principle in the UN Charter of non-interference of  any state or organization in the domestic affairs of any other nation.  

Article 2.7 of the Charter provides that – "Nothing contained in the present Charter shall  authorize the United Nations to intervene in matters which are essentially within the  domestic jurisdiction of any state or shall require the Members to submit such matters  to settlement under the present.” Ethiopia deserves respect.  

The war in Tigray and the ensuing humanitarian crisis, including hunger, displacement,  any type of killing or rape or any other abuse of citizens is tragic. Equally tragic is the  fact that the international community has thus far failed to report that the Government  of Ethiopia is engaged in mitigating the crisis by providing 70 percent of the entire  humanitarian assistance in Tigray. The Government of Ethiopia did not start the war, 

It saddens those of us who are committed to inclusive governance in Ethiopia and who  mobilize and channel funds constantly to support humanitarian causes in Ethiopia  regardless of ethnic affiliation that the UN Security Council accepted an unverified  

report concerning large scale killings in the historic town of Aksum by Ethiopian and  Eritrean forces. 

Collateral damage in a war like environment is inevitable. There is no credible and  corroborated evidence to support large scale killing in Aksum. TPLF cadres are reported  to have shot at some innocent civilians with the intent of blaming it on Ethiopian and  Eritrean troops.  

Insiders report that church services at Aksum, one of Ethiopia’s most sacred places of  worship took place without incident. The TPLF attacked Eritrea and cities in Ethiopia’s  heartland with rockets. So, why did the UN Security Council fail to recognize this  criminal act and the fabricated dissemination of narratives by the TPLF? 

Insiders confirm that innocent civilians have been killed. Denial is therefore not credible.  Scale matters too. The wholesale and ethnically targeted massacre that deserves  international scrutiny is the one that took place in Mai Kadra. Why is that missing then? 

“Why did the UN Security Council fail to demand accountability for the genocide perpetrated by the TPLF’s youth wing, Samri, in Mai Kadra where more than 1,200  innocent lives were slaughtered?” Amnesty International and the UN High  Commissioner for Human Rights had reported this genocidal act by the TPLF. However, the UN High Commissioner for Human Rights who had expressed outrage then did not  follow through with action. Why the neglect? Is this deliberate?  

In Wolkait, Tegede, Telemt, Raya in the North (the Amhara region) and in Metekel, Beni Shangul Gumuz region and in Oromia hundreds of innocent civilians most of them  Amhara were massacred. There is no guarantee that more ethnically targeted murders  will not take place.  

In Beni-Shangul Gumuz, innocent farmers were killed with arrows and or hacked with  machetes. Hundreds killed were hauled and dumped into a mass grave. This  dehumanization undermines Ethiopian renowned burial ceremony of burying the dead  with utmost care and respect. Further, reports by independent entities and  communities reveal mass graves in Setit-Humera, in the Amhara region and in Tigray, all  committed by the TPLF. Mass graves are a standard practice of the TPLF.

Over 40 years, the TPLF evicted tens of thousands of indigenous people; expelled  hundreds of thousands from their homes and properties and forced them to seek  refugee status in neighboring nations. This occurred throughout the Amhara region.  Why is the UN system silent on this human tragedy?  

Rape by any person or group is abominable. The UN must understand that it was  standard practice for Tigrean men to maim or kill Amhara husbands and marry their  grieving spouses. It was a norm for the Amhara population in occupied lands to be  denied the right to speak their language or to practice their culture. The demographic  changes that took place in lands annexed by the TPLF are underreported or not reported  by the UN. Why is that? 

Despite these atrocities over 40 plus years, the Ethiopian people treated Tigrean Ethiopians with dignity and respect during the TPLF initiated war. Wounded and sick  Tigrean-Ethiopians were given health care in hospitals in Gondar, the Amhara region. Ethiopians Defense Forces made sure that leaders of the TPLF including Sebhat Nega  and others were treated with dignity and humanity, a hallmark of the Ethiopian people.  Ethiopian Defense Forces have an established track record for avoiding revengeful acts.  

Contrary to what is reported to it by hired hands and lobbyists, the UN Security Council  has an obligation to understand that non-Tigrean Ethiopians did not carry out revengeful actions such as rape in Tigray or in the liberated lands. This is especially true  regarding Ethiopia’s celebrated National Defense Forces.  

In the light of the above set of facts, the draft proposal by Ireland for the Security Council is misguided, precedent setting and a disservice to Black Africa. It must not be repeated.  

1. To their credit, China, India, and Russia did the right thing by vetoing the proposal.  

2. The term “violence in Tigray” is unprecedented and dangerous. The TPLF committed  treason. It caused the current humanitarian crisis. It normalized state and extrajudicial  violence in Ethiopia. In a single year, more than 133 ethnic-based conflicts took place,  most initiated by the TPLF.  

3. The Government of Ethiopia has the sole responsibility to ensure peace and security in  Ethiopia. Tigray cannot be an exception to this.  

4. Tigray is not an independent state. It is an integral part of Ethiopia. It is the heart of  Ethiopia. The UN Security Council and Western democracies have an obligation to treat  Ethiopia’s sovereignty; acknowledge its authority over the country’s diverse population; 

and refrain from undue interference in line with the UN Charter. The Security Council  must not be a bully.  

5. The Tigray crisis is purely a domestic matter. It is Ethiopia’s own business. The UN  Security Council must therefore refrain from taking sides. 

6. The international community, including the UN must assist the Government of Ethiopia  in dealing with the massive humanitarian crisis not only in Tigray but also in Beni Shangul Gumuz, where more than 400,000 innocent civilians are displaced.  

7. There is no doubt that innocent lives have been lost. The Government of Ethiopia must  do due diligence by establishing an independent commission to investigate all crimes  against humanity, crimes of war and genocide in Ethiopia, including Tigray.  

8. This requires funding. The UN Security Council can discuss and empower UN specialized  agencies and others to avail funds. The Government of Ethiopia must be encouraged to  hire international experts to assist the commission.  

9. The UN Security Council must refrain from repeating the same mistake. 

10. In this regard, the UN Security Council might benefit from a measured and relatively  balanced draft resolution in the U.S. Senate introduced on March 5, 2021. This draft  contains the following: 

Calls on the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) and the Government of  Ethiopia to protect the human rights of all Ethiopians and allow full humanitarian  assistance and allow full access to affected parts of the Tigray Region.  

Demands accountability for the November 9, 2021 massacre of an estimated  1,200 innocent civilians in Mai Kadra by the TPLF. This heinous crime was  reported and vetted by Amnesty International, the UN High Commission for  Human Rights, the Ethiopian Human Rights Commission, and the Ethiopian  Human Rights Council.  

Implores the Ethiopian Government to allow for independent and transparent  investigations into all alleged human rights abuses committed. 

Acknowledges that the Tigray conflict is occurring alongside other humanitarian  crises in Ethiopia, including recurring ethnic-based massacres in Beni Shangul Gumuz and Oromia where the primary targets are Amhara, Agaw, etc. 

Chronicles the escalatory provocations leading up to the conflict in Tigray: the  TPLF holding a regional election in defiance of the Federal Government’s  postponement due to the Pandemic; the TPLF’s confession of perpetrating the unprovoked attack of Ethiopia’s Northern Command, a key component of the Ethiopian National Defense Forces (ENDF) in the early hours of November 4,  2020. 

Urges an end to the hostilities as soon as possible.  

Calls on the Government of Ethiopia to apprehend remnants of the TPLF  leadership in hiding with minimum military force and avoiding civilian casualties. 

Urges the Government of Ethiopia to release opposition party leaders; stop the  Prosperity Party’s undue interference by curtailing freedom of movement, assembly & free expression, allow unfettered political participation and cease  the use of threatening and inflammatory languages against targeted and specific  opposition groups.  

In summary, the most encouraging part of the draft resolution by the U. S. Senate that most Ethiopians at home and abroad appreciate and share is the call for national dialogue for peace  and national reconciliation among all Ethiopian stakeholders: representatives of all nonviolent  and non-extremist political parties, ethnic communities, religious groups, and civil society  organizations (CEOs). This is where the UN system must invest heavily to help Ethiopia.  

Ethiopian society deserves genuine multiparty democracy. This can occur only through national  consensus, peace, personal security for citizens and reconciliation.  

The international community has a moral obligation to help achieve this by refraining from  undue interference in Ethiopia’s domestic affairs.  

To be constructive, the international community must empower Ethiopian stakeholders. It must  avoid, always, not fall into the temptation of leveraging aid as an instrument of public policy.  That will only be punishing the poor.  

Aklog Birara, Ph.D. served in various capacities for 30 years with the World Bank, the latest as  Senior Senior Advisor. He has written 6 books since retiring. He writes commentaries on the  political economy of Africa.  

------------------------///-----------------

Dr. Aklog Birara Sr. Advisor at World Bank Washington, District of Columbia, United States

He can be reached at abt.semegn@gmail.com

********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

EXCLUSIVE UNDP Memo Echoes Ethiopian Talking Points on Tigray

Agency memo sidesteps questions around government’s role in Tigray.

BY , 
 | 

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።