Wednesday, March 17, 2021

ልብ የሚሰብር ዜና - የለውጥ ሐዋርያው የታንዛንያው ፕሬዝደንት ጆን ማጉፉሊ በ61 ዓመታቸው አረፉ።ሙስናን ለመዋጋት ተዓምር ሰርተዋል።፣ታንዛንያ ከምዕራብ ኩባንያዎች ጋር የገባችውን የማዕድን ውል ሀገሪቱን በሚጠቅም መልክ እንዲቀየር እየተጋደሉ ነው ያረፉት።አፍሪካዊ መሪዎቻችንን እናክብር! እንጠብቅ!



ለምዕራባውያን የማዕድን ኩባንያዎች የራስ ምታት ነበሩ።ለታንዛንያ መድሃኒት ነበሩ።በአጭር ጊዜ ተአምራዊ የተሰኘ ለውጥ አምጥተዋል።የስም ማጥፋት ዘመቻ በውጭ ሚድያዎች ተካሂዶባቸዋል።የ''ዎል ስትሪት'' ድረ-ገፅ ከሰዓታት በፊት የዕረፍት ዜናቸውን የዘገበበት ርዕስ አነጋጋሪ ነው።''ከማዕድን ኩባንያዎች ጋር ውዝግብ የገቡት የታንዛንያው ፕሬዝዳንት በ61 አመታቸው አረፉ'' ይላል። ይህ ርዕስ በራሱ የታንዛንያው ፕሬዝዳንት ምን ያህል ለምዕራብ ኩባንያዎች የራስ ምታት እንደነበሩ፣ለታንዛንያ ደግሞ ሩቅ አሳቢ እንደነበሩ አመላካች ነው። 

ፕሬዝደንት ጆን ማጉፉሊ ካለፈው የካቲት ጀምሮ ለሕዝብ አልታዩም ነበር።ፕሬዝዳንቱ ያረፉት በዳሬሰላም ሆስፒታል ሲሆን ለሞታቸው ምክንያት የልብ ህመም መሆኑን የሚናገሩ አሉ።በሌላ በኩል በኮቪድ ምክንያት እንዳረፉም የሚወጡ ዘገባዎች አሉ።የታንዛንያው ምክትል ፕሬዝዳንት በመንግስት ቴሌቭዥን ለሕዝባቸው መርዶውን ካረዱ በኃላ በቀጣይ 14 ቀናት በታንዛንያ የሐዘን ቀን እንደሚሆን እና የሀገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ ዝቅ ብሎ እንደሚውለበለብ ተወስኗል።
ስለ ፕሬዝዳንቱ ሸገር ራድዮ የዛሬ ሶስት ዓመት በመቆያ ፕሮግራም ያቀረበውን እስከመጨረሻ ያድምጡ።


ከምሥራቅ አፍሪካ መሪዎች የታንዛንያውን ፕሬዝዳንት ጆን ማጉፉሊ ማረፍ በተመለከተ ከተባሉት 








********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

No comments:

የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።

Foto : Fana digital  የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም...