ጉዳያችን - በጉዳያችን ሚድያ፣ኮምኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት የሚዘጋጅ ሲሆን ከ2003 ዓም ጀምሮ በድረ-ገፅ ላይ የነበረ በአሁኑ ጊዜ ከአንድ ሚልዮን በላይ ጎብኚዎች ያሉት ገፅ ነው። Gudayachn is prepared by Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant Organization. It has been online since 2011. Currently, Gudayachn is being visited by over One-million readers from all over the world.
ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages
Friday, April 30, 2021
የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ተግዳሮቶቹ፣የተወሰዱ እርምጃዎች እና መጪው ተስፋ በተመለከተ ባለሙያዎቹ የሰጡት ዝርዝር ማብራርያ (ቪድዮ)
Wednesday, April 28, 2021
ከከያኒ እስከ ቀዳሽ፣ከወታደር እስከ አካል ጉዳተኛ፣ከመሪ እስከ ተመሪ-ሕዝብ ለኢትዮጵያ የምንቆምበት ጊዜ አሁን ነው።በአጀንዳ ለመጥለፍ የሚሞክሩትን ወደ ጎን ብለን ቁልፉ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ እናተኩር! የህልውና ጉዳይ ነው።
- ማናቸውም ዓይነት የፅንፍ ማኅበራዊ ሚድያ መገናኛዎችን ለመቆጣጠር ከግንቦት ወር መጀመርያ ጀምሮ መዘጋት አለባቸው።
- የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን እና ራድዮ በልዮ ሃገራዊ ዝግጅቶች ዝግጅቶቻቸው እና ዜናዎቻቸው ሁሉ መከለስ አለባቸው።
- አንድ ማዕከላዊ የመረጃ ሰጪ አካል (እንደ ''ፋክት ቼክ'') ያለ መንግስት ማስተዋወቅ እና ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለውጭ ሀገርም ብቃት ባለው መልክ የውሸት ዜናዎችን በማስረጃ የሚመልስ ማዕከል ያስፈልጋል።
- ከጦር ሰራዊት እስከ ፖሊስ በከፍተኛ ደረጃ ዘብ የሚቆሙበት ጊዜ መሆን አለበት።
- በኢትዮጵያ ላይ የማያቆም የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ላይ የተሰማሩት በተለይ የጦር ኃይሉን መኮንኖች ጨምሮ ምክንያት በሌለው የስም ማጥፋት እና ሕዝብ እና መንግስትን ለማጋጨት ሌት ከቀን የሚሰሩት ላይ የእርምት እርምጃ መወሰድ አለበት።
- ከውስጡ ያሉትን ሙሰኞች፣ጎሰኞች እና ብቃት የሌላቸውን ባለስልጣናት በተለይ የበታች ሹሞች ገለል ማድረግ።
- ኢትዮጵያዊ አሸናፊ ስነ ልቦናውን ከፍ ማድረግ እና በተለያየ መንገድ የስነ ልቦና ጦርነት የከፈቱበትን ከላይ የተጠቀሱትን አራት ኃይሎች ሰለባ እንዳይሆን ከግለሰብ ጀምሮ መዘጋጀት፣
- ሁል ጊዜ መጥፎ እየነገሩ በሀገሩ እና በመንግስት ላይም የተጋነነ ወሬ የሚያቀብሉትን ሚድያዎች እና ዩቱብ፣ማኅበራዊ ሚድያዎች በሙሉ ውሸት ማጋለጥ እና አለመመልከት፣የእነርሱን ወሬ ይዘው የሚመጡትን ቦታ አለመስጠት።
- ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተነሱ ኃይሎች ዋነኛ ትኩረት መጀመርያ ኢትዮጵያ ሃገረ መንግስቷን በምርጫ እንዳትመሰረት ማድረግ መሆኑን አውቆ በብዛት በምርጫው መሳተፍ እና መብቱን ማስከበር።
- መንግስት ከምርጫ በፊት እናስወግድ የምትል ውስጠ ወይራ ማናቸውም ዓይነት እንቅስቃሴ እና ፕሮፓጋንዳ ቀድሞ አውቆ የእዚህ ዓይነት ሃሳብ አራማጆችን ማሳፈር እና ማጋለጥ።
- ለማናቸውም ሃገራዊ አገልግሎት መነሳት እና ወጣቶችም ዝግጁ እንዲሆኑ መምከር።
- ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚፈልጉ ኃይሎች ብዙ እርቀት እንደሚሄዱ አውቆ እራሱን ማዘጋጀት እና የውስጥ ከሀዲዎችን በእኩል ደረጃ መዋጋት እና
ከኪነ ጥበብ ሰዎች በተለይ ከድምፃውያን የሚጠበቅ -
Saturday, April 24, 2021
በ1950ዎቹ የነበረውን የኢትዮጵያ ትውልድ የሚያሳይ ቪድዮ።
- ለአፍሪካ ትንሣኤ መነሻው ኢትዮጵያ ነች - ቪድዮው መግቢያ ላይ ምክንያቱን ያገኙታል።
- ተማሪዎች ወደ ክፍል ሲገቡ በምን ዓይነት የስነ ምግባር እና የሀገር ፍቅር ስሜት እንደሚገቡ ይመለከታሉ።
- በቪድዮው አዲስ አበባ፣አስመራ፣ደብረብርሃን፣ጎንደርን ይመለከቱበታል።
Friday, April 23, 2021
ሕዝብ አስር ጊዜ ቢጠይቅ መንግስት አስር ጊዜ ደጋግሞ የማስረዳት ግዴታ አለበት!
- ክስተቱ በእነማን እንደተፈፀመ፣
- መንግስት ምን እንዳደረገ
- ወደፊትም ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳይከሰቱ ምን ዓይነት እርምጃ ለመውሰድ እንደታሰበ
- ከሕዝብ ምን እንደሚጠበቅ እና
- በደረሱት ሁሉ ከልብ ማዘኑን መግለጥ አለበት
Tuesday, April 20, 2021
ለወቅታዊው የኢትዮጵያ ጉዳይ መፍትሔዎቹ
- በኦሮምያ ብልፅግና ውስጥ አክራሪ የፅንፍ ኃይሎች በተለየ መንገድ ከቢሮክራሲ እስከ ልዩ ኃይሉ ውስጥ መመሸጋቸው እና አሁንም የሚፈፀሙ ግድያዎች በእነኝሁ ኃይሎች አይዞህ ባይነት መደገፉ፣
- ሕገ መንግስቱ የአማራን ሕዝብ የማይጨምር መሆኑ እና ሀገር አልባ ሆኖ በኦነግ እና ትህነግ መሃል የተዘጋጀ ሰነድ መሆኑ በአማራ ክልል በኩል በመወሰዱ፣
- በሁለቱም ክልሎች ውስጥ ያሉት ህገ-ክልል መንግስታቸው በራሱ የተለያየ መሆኑ።ይሄውም የአማራ ክልል በውስጡ ላሉት ብሔረሰቦች የባለቤትነት መብት ሲሰጥ የኦሮምያ ግን በክልሉ ያሉትን ብሔር ብሔርሰቦች እንደማያውቃቸው የሚገልጥ አረፍተነገር መያዙ እና
- በሁለቱም ክልሎች የሚገኙ የፅንፍ የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች ለእየራሳቸው ሕዝብ አንዱ አንዱን ሊውጠው ነው የሚለው የማስደንበርያ አሰቃቂ የሐሰት ፕሮፓጋንዳዎች የሚሉት ዋና እና መሰረታዊ ጉዳዮች ናቸው።
Saturday, April 17, 2021
በኦሮምያ እና በዓማራ ተወላጆች ሕፃናት እና እናቶች ደም የታጠበው፣ በኦሮምያ የበቀለው ፋሺዝም በኢትዮጵያዊነት መንፈስ መነቀል አለበት።
- በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት የፈፀመውን የህውሓት ጀሌ ጁንታ የሚል ስያሜ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ እናቶችን እና ሕፃናትን በሳንጃ እየወጋ የገደለ እና በመከላከያ ላይ ጥቃት የፈፀመውን ቡድን ፋሽሽት የሚል ስያሜ ሰጥተው ከኢትዮጵያ ምድር ማፅዳት አለባቸው።
በመጨረሻም በኢትዮጵያ ህልውና ላይ የሚመጣ ማንም ሆነ ማን በቸልታ ሊታለፍ አይገባውም።በኦሮምያ የበቀለው ፋሺዝም ሱማሌን አፈናቅሎ፣ጌድዮን ለመበተን ሞክሮ፣ደቡብን ተንኩሎ አሁን በአማራ ክልል ላይ ላንቃውን ከፍቷል።የኦሮምያ ክልል፣ሁሉም ክልሎች በተለይ የኢትዮጵያ መከላከያን በዋናነት የሚያዙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮምያ የበቀለውን ፋሺዝም መንቀል ቀዳሚ ተግባራቸው መሆን አለበት።ይህ ፋሺሽታዊ ቡድን በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይም ጥቃት ፈፅሟል።በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት የፈፀመውን የህውሓት ጀሌ ጁንታ የሚል ስያሜ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ እናቶችን እና ሕፃናትን በሳንጃ እየወጋ የገደለ እና በመከላከያ ላይ ጥቃት የፈፀመውን ቡድን ፋሽሽት የሚል ስያሜ ሰጥተው ከኢትዮጵያ ምድር ማፅዳት አለባቸው።
================
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሆሳዕና ከተማ መስተዳድር የፈፀመው ሸፍጥ፣ግፍ እና ወንጀል (አዲስ የወጣ ልዩ ጥናታዊ ፊልም)
Wednesday, April 14, 2021
ሁለተኛ ዙር ብሔራዊ የጸሎት መርሐግርብ በኢትዮጵያ ከሚያዝያ 8 ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ይካሄዳል።ነቅተን እና ተግተን በጋራ ወደ ፈጣሪያችን እንጩኽ!
- የጸሎት መርሐግብሩ መክፈቻ እና መዝጊያ መርሐግርብ ላይ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የመንግስት ኃላፊዎች ይገኛሉ።
- በኢትዮጵያ የሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 3 እስከ 4 ሰዓት ድረስ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን በቀጥታ ይተላለፋል።
- ብሔራዊ ጸሎቱ አራት ጉዳዮችን ዓላማ ማድረጉን ለማወቅ ተችሏል። እነርሱም - ኢትዮጵያ ምርጫውን በሰላም እንድታጠናቅቅ፣የዓባይ ውኃ ሙሌቱን በቂ ዝናብ አግኝታ እንድትሞላ፣የእርስ በርስ ስምምነት እንዲጠነክር እና የኢትዮጵያን መጪ ሽግግር ላይ ያለመ ነው።
- በሳምንቱ ውስጥ የሚሰጡት ትምህርቶች ይቅርታ፣ ርህራሄ፣ ተስፋ፣ እምነት፣ ፍቅር እና ምስጋናን መሰረት ያደረጉ ይሆናሉ።
=================
ዜናውን አስመልክቶ ዋልታ ሚያዝያ 5/2013 ዓም ከእዚህ በታች ያለውን ዜና ዘግቧል።
ሁለተኛው ዙር በአይነቱና በይዘቱ ለየት ያለ ሀገር አቀፍ የጸሎትና ምህላ ሳምንት መታወጁን የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሀፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፣ ሀገሪቱ ያለችበት ሁኔታ፣ የሰላምና መረጋጋት እጦት እንዲሁም ብሄርና ሃይማኖትን ማዕከል ያደረገ ግድያ መበራከት ሀገራዊ የጸሎትና ምህላ ሳምንት እንዲታወጅ አድርጓል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ በጎረቤት ሀገራት ምስራቅ ቀጠና ላይ የሚታየው የድንበር አለመግባባቶችን በሚመለከት የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገራዊ ጸሎት ማድረግ ሌላኛው ወሳኝ ጉዳይ ተደርጎ እንዲወሰድ ማድረጉንም ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን በዚህ አሳሳቢ ወቅት ስለሆነውና እየሆነ ስላለው ሁሉ በደልና ጥፋት በፈጣሪ ፊት በመቅረብ በንስሃ ከራስና ከፈጣሪ ጋር እርቅ መፈጸም እንደሚገባ ያሳሰቡት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ፣ የጋራ መርሃ ግብሩ ሚያዝያ 7 ከቀኑ 9 ሰዓት እንደሚታወጅ አስታውቀዋል፡፡
መርሃ ግብሩም የሁሉም እምነት ተቋማት፣ በ6ኛው አገራዊ ምርጫ የሚሳተፉ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች በይፋ እንደሚታወጅ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
ከሚያዚያ 8 ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ሰባት ቀናት የሚቆይ በሁሉም አባል የሃይማኖት ተቋማት በተናጠል የሚዘጋጅ ጸሎትና ትምህርት በመገናኛ ብዙሃን ጣቢያዎች ይተላለፋልም ተብሏል፡፡
በመገናኛ ብዙሃን በሚተላለፍ ፕሮግራም የ1 ሳምንት ቆይታ በሚኖረው የቴሌቪዥን ስርጭት ከምሽት 3 እስከ 4 ሰዓት እንዲተላለፍ የሚደረግ ነው፡፡
ካለፈው ዓመት በተለየ መልኩ ዜጎች ከፈጣሪ ጋር በመቀራረብ በሀገሪቱም ላይ ፍትህ እንዲሰፍን ምርጫውም ሰላማዊ እንዲሆን በምልጃ የሚቀረብበት መሆኑንም ጠቅላይ ፀሐፊው አመልክተዋል፡
ወቅቱ በኦርቶዶክስ አብይ ጾም እና በሙስሊም እምነት ተከታዮች ዘንድ ደግሞ የረመዳን ጾም የሚከናወንበት እንዲሁም ሌሎች እምነት ተቋማት ለመልካም ተግባራት ተባባሪ በመሆናቸው የተወሰነ ስለመሆኑ በመግለጫው ተመላክቷል፡፡
ጸሎትና ምህላ የሃይማኖት ተቋማት ችግር መፍቻ እንደሆነ ታምኗል፤ የታመነበት በዚሀም ኢትዮጵያውያን በታሪክ በጋራ ተሻግረው የመጡ በመሆናቸውም ዛሬም የተደቀነባቸውን ፈተናዎች በጋራ እንደሚያልፉ የሚጠበቅ ስለመሆኑ ነው ተብሏል፡፡
በተቀሩት ቀናት ስለ ይቅርታ፣ ርህራሄ፣ ተስፋ፣ እምነት፣ ፍቅር እና ምስጋና በተመረጡ ርዕሶች ተከታታይ ትምህርቶችን ተደራሽ በማድረግ እንደመክፈቻው ሁሉ አርብ ሚያዚያ 15 ቀን 2013 ዓ.ም በልዩ ዝግጅት የመዝጊያ መርሃ ግብር እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ገልጿል፡፡
Friday, April 9, 2021
ኢትዮጵያዊነታችንን እና አንድነታችንን ይዘን በአንድነት እንድንጓዝ አደራ እላለሁ -ብፁዕ አቡነ ኤልያስ በኢትዮጵያ ኦ/ ተ/ ቤ/ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል እና በስዊድን እና ስካንዲኒቭያን ሀገሮች ሊቀጳጳስ ዛሬ ሚያዝያ 1/2013 ዓም 'በዓለም ዙርያ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ' በሚል ርዕስ ስር መልዕክት አስተላልፈዋል።
Monday, April 5, 2021
በኖርዌይ የዓባይ ግድብ ገቢ የገቢ ማሰባሰብያ መርሐግብር ቅዳሜ ሚያዝያ 2/2013 ዓም (አፕሪል 10/2021 ዓም)
Saturday, April 3, 2021
በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በእዚህ ሳምንት ውሃ በጠጡ ቁጥር ለአባይ ግድብ ማዋጣት አለማዋጣታቸውን እራሳቸውን መጠየቅ አለባቸው።ዶ/ር ስለሺ በቀለ፣የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር በመጪው ቅዳሜ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ያገኛሉ።
- በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ይህ ዕድል ሊያመልጣቸው ይችላል።ግድቡ ሊጠናቀቅ የቀረው 20% ብቻ ነው።ለራስዎም ለልጆችዎም የታሪኩ አካል ሳይሆኑ ሊያልፍ ነው።
የግሪክ አቴንሱ ''ኢትዮጵያዊው'' አውርቶ አዳሪው ''ዲያቆን'' እና ከጥንትም የኢትዮጵያ ጠላት የሆነው የ''አውርቶ አደር'' ማንነት
============= የጉዳያችን ማስታወሻ ============= ከጥንትም የኢትዮጵያ ጠላት የሆነው ''አውርቶ አደር'' ማንነት የኢትዮጵያ የታሪክ ስብራት ዋነኛዎቹ ምክንያቶች አውርቶ አደሮች ናቸ...
-
የቅዱስ ላልይበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ጉዳያችን/ Gudayachn ሰኔ 2/2011 ዓም (ሰኔ 8/2019 ዓም) ግንቦት 29/2011 ዓም ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል በለቀቀው ዜና እንዲህ ይነበባል: - ...
-
Foto source:- Royal Norwegian Embassy in Addis Ababa, Ethiopia http://www.norway.org.et/News_and_events/press_releases/New-Norwegia...
-
Gudayachn Report August 14,2020 Senior Hydrologists and water resource Engineers webinar presentation and discussions on creating awareness ...