ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, April 17, 2021

በኦሮምያ እና በዓማራ ተወላጆች ሕፃናት እና እናቶች ደም የታጠበው፣ በኦሮምያ የበቀለው ፋሺዝም በኢትዮጵያዊነት መንፈስ መነቀል አለበት።

  • በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት የፈፀመውን የህውሓት ጀሌ ጁንታ የሚል ስያሜ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ እናቶችን እና ሕፃናትን በሳንጃ እየወጋ የገደለ እና በመከላከያ ላይ ጥቃት የፈፀመውን ቡድን ፋሽሽት የሚል ስያሜ ሰጥተው ከኢትዮጵያ ምድር ማፅዳት አለባቸው።
ባለፉት ሦስት ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ  ካሉት ክልሎች በተለየ መልኩ የኦሮምያ ክልል በሰው አዕምሮ የማይታሰቡ እጅግ አሰቃቂ እልቂቶች ተፈፅመውበታል።በክልሉ የበቀለው ፋሺሽታዊ ስርዓት መጀመርያ በህወሓት/ኢህአዴግ ስር ተወሽቆ በክልሉ የሚገኙ የሌሎች ክልሎች ተወላጆች ላይ የጥፋት ላንቃውን ከመክፈቱ በላይ ክልል ተብሎ በተሰጠው ቦታ በላይ በመጀመርያ ከሱማሌ ክልል ጋር በተፈጠረ ግጭት ከስምንት መቶ ሺህ በላይ የሚሆን ሕዝብ ከኦሮምያም ሆነ ከሱማሌ እንዲፈናቀል ተደረገ።በመቀጠል በጌድዮ ሕዝብ ላይ ተመሳሳይጥቃት ከፈፀመ በኃላ የዓማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ላይ በንፁሃን ላይ ጥቃት እየፈፀመ ነው።በኦሮምያ የበቀለው ፋሺዝም ዋና ኢላማው በክልሉ የሚኖሩ የሌላ ክልል ተወላጆች በተለይ የአማራው ተወላጅ ብቻ አይደለም።በእርግጥ የአማራ ተወላጆች በቀዳሚነት ተገድለዋል፣ተሰደዋል፣በእዚህ ዘመን ይፈፀማል ተብሎ በማይታሰብ ደረጃ ሕፃናት እና እናቶች ሳይቀሩ በአሰቃቂ መንገድ ተገድለዋል።ይህም ሆኖ ግን የኦሮምያ ተወላጆች በወለጋ፣በአርሲ፣በሐረር እና በሰሜን ሸዋ ሳይቀር ነዋሪዎች እና የአካባቢ ባለስልጣናት ሳይቀሩ ተገድለዋል።

ቢቢሲ አማርኛ በዛሬው ዕለት እንደዘገበው የሰሜን ሸዋ ዞን የፀጥታ ጉዳይ ኃላፊ አቶ አበራ መኮንን ለቢቢሲ እንደገለፁት ጥቃቱ የተፈፀመው በዞኑ በሚገኙ አምስት ወረዳዎች ውስጥ ሲሆን "በጣም ከፍተኛ" ቁጥር ያለው የታጠቀ ኃይል "ወረራ" መፈፀሙን ተናግረዋል።የታጠቀው ኃይል "ቤቶችን ያቃጥላል፤ ሰዎችን ይገድላል" በማለትም ወደ አካባቢው የገባው የፌደራል የጸጥታ መዋቅርና የመከላከያ ሠራዊትም "ከአቅሙ በላይ" መሆኑን ለቢቢሲ አስረድተዋል።

በሌላ በኩል የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ለክልሉ መገናኛ ብዙሃን ተቋም እንደተናገሩት በጥቃቱ የደረሰው ጉዳት የከፋ መሆኑን አመልክተዋል።ለጥቃቱም "ኦነግ ሸኔ እና ሌላ ተከታይ" ያሉትን አካል ተጠያቂ አድርገዋል የዞኑ የፀጥታ ጉዳይ ኃላፊ በመቀጠልም በጥቃቱ የጸጥታ አካላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን አክለዋል።ከትናንት በስቲያ ሐሙስ ማታ ጀምሮ በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን እና በሰሜን ሸዋ ዞን መካከል በሚገኙ አካባቢዎች የጸጥታ ችግር መኖሩን ገልጸው፤ ይህ ግን ጋብ ብሎ እንደነበር ኃላፊው አስታውሰዋል።ይሁን እንጂ ትናንት አርብ ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ ከፍተኛ የታጠቀ ኃይል ወደ አካባቢው በመግባት በአጣዬ፣ በአንጾኪያና በኤፍራታ ላይ ጥቃት መፈጸሙን ተናግረዋል።ከላይ በዘገባው እንደተገለጠው በኦሮምያ ክልል የበቀለው ፋሽሽታዊ ቡድን ኦነግ ሸኔ ነው ወይንም ሌላ ስም እየሰጡ ምክንያት የሚደረደርበት ጊዜ አልፏል።የክልሉ ሀብት ለፋሺሽቱ መንቀሳቀሻ በግልጥ እየዋለ ክልሉ በጉዳዩ ላይ የሌለ ይመስል በተለያየ የቡድን ስሞች እየጠሩ ማሳበቡ አሁን ጊዜው ያለፈበት መሆኑ ግልጥ ሆኗል።

በመጨረሻም በኢትዮጵያ ህልውና ላይ የሚመጣ ማንም ሆነ ማን በቸልታ ሊታለፍ አይገባውም።በኦሮምያ የበቀለው ፋሺዝም ሱማሌን አፈናቅሎ፣ጌድዮን ለመበተን ሞክሮ፣ደቡብን ተንኩሎ አሁን በአማራ ክልል ላይ ላንቃውን ከፍቷል።የኦሮምያ ክልል፣ሁሉም ክልሎች በተለይ የኢትዮጵያ መከላከያን በዋናነት የሚያዙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮምያ የበቀለውን ፋሺዝም መንቀል ቀዳሚ ተግባራቸው መሆን አለበት።ይህ ፋሺሽታዊ ቡድን በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይም ጥቃት ፈፅሟል።በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት የፈፀመውን የህውሓት ጀሌ ጁንታ የሚል ስያሜ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ እናቶችን እና ሕፃናትን በሳንጃ እየወጋ የገደለ እና በመከላከያ ላይ ጥቃት የፈፀመውን ቡድን ፋሽሽት የሚል ስያሜ ሰጥተው ከኢትዮጵያ ምድር ማፅዳት አለባቸው።

================

ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...