ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, April 3, 2021

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በእዚህ ሳምንት ውሃ በጠጡ ቁጥር ለአባይ ግድብ ማዋጣት አለማዋጣታቸውን እራሳቸውን መጠየቅ አለባቸው።ዶ/ር ስለሺ በቀለ፣የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር በመጪው ቅዳሜ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ያገኛሉ።

  • በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ይህ ዕድል ሊያመልጣቸው ይችላል።ግድቡ ሊጠናቀቅ የቀረው 20% ብቻ ነው።ለራስዎም ለልጆችዎም የታሪኩ አካል ሳይሆኑ ሊያልፍ ነው።

ኢትዮጵያ በክፍለዘመኑ አቅጣጫ ቀያሪ የተባለለትን የዓባይ ግድብ መገንባት ከጀመረች መጋቢት 24/2013 ዓም 10ኛ ዓመቷን ደፈነች።በእነኝህ ዓመታት በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ቢያደርጉም አሁንም ግን በውጭ ከሚኖረው ኢትዮጵያዊ አቅም እና ብዛት አንፃር ሲታይ ብዙ እንደሚቀር ይታወቃል።በተለይ ለግድቡ አስተዋፅኦ ከአውሮፓ እና አሜሪካ ይልቅ በመካከለኛው ምስራቅ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አስተዋፅኦ መብለጡ በአውሮፓ እና አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚያስቆጭ መሆኑን ብዙዎች ይናገራሉ።

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ባለፈው ስርዓት ወቅት ከመንግስት ጋር በነበሩ ቅራኔዎች እና በዓባይ ፕሮጀክት ግልፅ አሰራር ላይ በነበራቸው ጥያቄ መሰረት ብዙዎች በግድቡ መዋጮ ላይ አልተሳተፉም።ይህ ማለት በከፍተኛ ደረጃ ያዋጡ የሉም ማለት አይደለም። ሆኖም ግን ከነዋሪው ቁጥር አንፃር ሲታይ መዋጣት ባለበት ደረጃ አልተዋጣም ለማለት ነው።አሁን ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ደረጃ ሊያዋጡ የሚችሉበት ዕድል ተከፍቶላቸዋል።ይህ በራስዎ፣በልጆችዎ እና በቤተሰብ ስም ጭምር የአቅምዎትን የሚያዋጡበት ታላቅ ዕድል ነው።ይህ ዕድል ሊያመልጥ ይችላል።በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ይህ ዕድል ሊያመልጣቸው ይችላል።ግድቡ ሊጠናቀቅ የቀረው 20% ብቻ ነው።ለራስዎም ለልጆችዎም የታሪኩ አካል ሳይሆኑ ሊያልፍ ነው።

በያዝነው ሳምንት ልዩ የአባይ ግድብ ሳምንት ብለው ለራስዎ ቃል ይግቡ።ውሃ በጠጡ ቁጥር ለአባይ ግድብ ማዋጣት አለማዋጣትዎን እራስዎን ይጠይቁ።ካላዋጡ አሁኑኑ የታሪኩ አካል ይሁኑ።
ይህ በእንዲህ እያለ በሚያዝያ 2/2013 ዓም (ማርች 10/2021 ዓም) በኖርዌይ የሚገኙ የሲቪክ ድርጅቶች በኖርዲክ ሀገሮች የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና ከኢትዮጵያ ማኅበረሰብ (ኮሚንቲ) በኖርዌይ ጋር በአንድነት ሆነው ልዩ የዓባይ ግድብ አስተዋፅኦ መርሐግብር በዙም አዘጋጅተዋል።ቀደም ብሎ በኖርዌይ የሚገኙ ሲቪክ እና ኮሚንቲ በአንድነት ለግድቡ ሲያሰባስቡ ነበር የሰነበቱት።በእዚህ በመጪው ሚያዝያ 2/2013 ዓም (ማርች 10/2021 ዓም) በኖርዌይ የሰዓት አቆጣጠር ከ15 ሰዓት ጀምሮ በተዘጋጀው መርሃግብር ላይ ዶ/ር ስለሺ በቀለ፣የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር፣ አምባሳደር ድሪባ ኩማ በኖርዲክ ሀገሮች የኢትዮጵያ አምባሳደር እና ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፤ ደራሲና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋና የሥነ ጽሑፍ መምህር ይገኛሉ።

በዕለቱ ከኖርዌይ የተዋጣውን የገንዘብ መጠን ይገልጣል።አሁን የእርስዎ ተራ ነው።ላለፉት ዓመታት በልዩ ልዩ ምክንያቶች ለዓባይ ግድብ አዋጥተው የታሪክ አካል ካልሆኑ።አሁን አያምልጥዎት።

ለዓባይ ግድብ ገቢ የሚያደርጉበት የባንክ  ሂሳብ ወይንም ቪፕስ ቁጥር 
የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ (ኮምዩኒቲ) የባንክ ሂሳብ ቁጥር  15034313420 ሲሆን በቪፕስ ለመላክ ለምትፈልጉ 647675 በመጠቀም የታሪኩ አካል መሆን ይችላሉ።

ሚያዝያ 2/2013 ዓም (ማርች 10/2021 ዓም) በኖርዌይ ሰዓት አቆጣጠር 15 ሰዓት (3PM) ጀምሮ ለሚኖረው የዙም መርሐግብር መግቢያ ከእዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠርያ (ሊንክ) እና መግቢያ ኮድ ይጠቀሙ።

Topic: GERD Norway 
Time: Apr 10, 2021 03:00 PM Oslo 

Join Zoom Meeting 

Meeting ID: 665 4122 0386 
Password: GERD 

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቧን ይጠብቅ።
*********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 





No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...