ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, April 23, 2021

ሕዝብ አስር ጊዜ ቢጠይቅ መንግስት አስር ጊዜ ደጋግሞ የማስረዳት ግዴታ አለበት!



በመንግስት እና በሕዝብ መሃከል ያለው አንዱ የመገናኛ መስመር ሕዝብ ለሚጠይቃቸው ማናቸውም ጥያቄዎች አክብሮ እና ዋጋ ሰጥቶ መመለስ እና ማስረዳት ነው።ሲሆን መንግስት ሳይጠየቅ ቀድሞ እያንዳንዱን ክስተቶች ምን እና እንዴት እንደተፈፀሙ የማስረዳት፣የማሳወቅ እና የሚከተሉትን ችግሮች ሁሉ ቀድሞ ተንትኖ ለሕዝብ ማቅረብ እጅግ አስፈላጊ ነው።መንግስት በሰው ኃይልም አደረጃጀትም፣ ከህዝብ በሚሰበስበው ሀብት እና የመረጃ መዋቅሩ የተሻለ አደረጃጀት እና የላቀ መረጃዎችን ቀድሞ የማወቅ አቅም አለው።

ሰሞኑን በአማራ ክልል እየተካሄዱ ያሉት ሰላማዊ ሰልፎች ጥያቄ በተለይ በኦሮምያ ክልል ዘርን መሰረት አድርገው የሚፈፀሙት ግድያዎች ይቁሙ፣ገዳዮቹ ለፍርድ ይቅረቡ ለወደፊትም ግድያዎቹ እና ጥቃቶቹ እንዳይፈፀሙ መንግስት እርምጃ ይውሰድ ነው።እነኝህ ጥያቄዎች የዜግነት እና የሰብዓዊነት ጥያቄዎችም ጭምር ናቸው።ሕዝብ የመጠየቅ፣መንግስትም የመመለስ መብት እና ግዴታ አለባቸው።ለጥያቀዎቹ ዋና መነሻ ምክንያት የድርጊቱ ዘግናኝ አፈፃፀም እና የሰላም ዋስትና የማጣት መሆናቸው ግልጥ ነው።ከእዚህ ውጪ ነገሮቹን ወደ አላስፈላጊ የእልህ እና ውስብስብ ጉዳዮች መምራቱ እንደሃገርም እንደ ህዝብም አይጠቅምም።

ስለሆነም መንግስት  የመከላከያ ሚኒስትር፣የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፀጥታ ጉዳይ አማካሪ እና የኦርምያ ክልል ፕሬዝዳንት በተገኙበት ስለ ጉዳዩ በቂ ማብራርያ በሚከተሉት ጉዳዮች ዙርያ መስጠት አለበት። እነርሱም -
  • ክስተቱ በእነማን እንደተፈፀመ፣
  • መንግስት ምን እንዳደረገ
  • ወደፊትም ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳይከሰቱ ምን ዓይነት እርምጃ ለመውሰድ እንደታሰበ 
  • ከሕዝብ ምን እንደሚጠበቅ እና 
  • በደረሱት ሁሉ ከልብ ማዘኑን መግለጥ አለበት 
ሕዝብ አስር ጊዜ ቢጠይቅ መንግስት አስር ጊዜ ደጋግሞ የማስረዳት ግዴታ አለበት! ለጥያቄዎች መልስ አለመስጠት ሕዝብ በተለየ መልክ እንደተናቀ ይሰማዋል።ውጤቱ ደግሞ አደገኛ ነው።ይልቁንም ለአክራሪ ኃይሎች 'ሰርግና ምላሽ' ነው።ሕዝቡን ወደ ፅንፍ ለመውሰድ 'ድሮም ስንል የነበረው ይሄ ነው' እያሉ ሕዝብን ይቀሰቅሱበታል።ስለሆነም በመንግስት እና በሕዝብ መሃል ያለውን የግንኙነት መስመርን በሚገባ አለመጠበቅ ሃገርን ዋጋ ያስከፍላል።በአማራ ክልል ያለው ሕዝብ የመንግስት የክልሉን ተወላጆች ላይ ባነጣጠረ መልኩ እየተፈፀሙ ያሉ ጥቃቶች እንደሚያሳስቡት መግለጡ ምኑ ላይ ነው ወንጀሉ? መንግስት በግንኙነት (communication) ሥራ ላይ ችግር እንዳለበት ማመን አለበት። ለሕዝብ እራስን ዝቅ አድርጎ ማስረዳት ሕዝብን አገለግላለሁ ለሚል መንግስት እንዴት ከበደው? ይህ እንዳይደረግ የሚሞግቱ ካሉ እነኝህ ኢትዮጵያ እንዳትረጋጋ የሚፈልጉ ናቸው።ሕዝብ አስር ጊዜ ቢጠይቅ መንግስት አስር ጊዜ ደጋግሞ የማስረዳት ግዴታ አለበት! ለነገሩ ሕዝብ በሦስት ዓመት አንዴ አሁን ነው የጠየቀው።



ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...