ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, September 21, 2023

''አክቲቪዝም ከጆርናሊዝም'' የደባለቀባቸው ዩቱበሮች በአማራ ክልል የሚፈሰው የመከላከያ እና የአማራ ክልል ህዝብ ደም አልታያቸው ብሏል። በኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሊባሉ ይገባል።


  • የሰው ደም እየፈሰሰ መከላከያና የአማራ ክልል ታጣቂ ኃይል አይነጋገር የሚሉት በውጪ ሀገር ሶፋ ላይ የተቀመጡት መሆናቸውን ልብ ይሏል።
  • የሰላም ንግግሮችን ለማጣጣል የሚሞክሩትን አጥብቀን መቃወም ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታችን ነው።
============
ጉዳያችን 
============

ኢትዮጵያ በወንድማማቾች ጦርነት ስትታመስ 50 ሙሉ ዓመት ዘንድሮ ይሞላታል። የኢትዮጵያ አብዮት በ1966 ዓም ከፈነዳ እነሆ በያዝነው 2016 ዓም 50 ዓመት ይሞላዋል።የወቅቱን ለውጥ ተከትሎ ከተነሳው የቀይሽብር እና ነጭ ሽብር ፍጅት ጀምሮ ከሻብያ እና በኋላ የእርሱ ውላጅ የሆነው ህወሓት ጋር ለ17 ዓመታት የተደረገው ጦርነት መቶ ሺዎችን ገብሮ የሃገሪቱን አንጡራ ሃብት በልቶ፣በጣት የሚቆጠሩ ስደተኞች የነበሯት ኢትዮጵያ ልጆቿ እንደጨው በመላው ዓለም ተዘርተው የወታደራዊ መንግስት ወድቆ የጎሳ ፖለቲካ የሚያቀነቅነው የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት ሌላ የመከራ ምዕራፍ በኢትዮጵያ ላይ ከፈተ።

በ27 ዓመቱ የጎሳ ፖለቲካ የኢትዮጵያ ልጆች ስደት ከአውሮፓና አሜሪካ እንዲሁም ጎረቤት የአፍሪካ ሀገሮች ወደ መካከለኛው ምስራቅ የኢትዮጵያ የነገ ተስፋ የሆኑ ወጣት ልጆች የስደት ዘመን ሆነ። ከግማሽ ሚልዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ባብዛኛው ወጣት ሴት እህቶቻችን በመካከለኛው ምስራቅ ብቻ ተበተኑ፣ኢትዮጵያ የባህር በር የሌላት ባለ 120 ሚልዮን ህዝብ ሆነች። ይህ ሁሉ ጥፋት ከውጭ ብቻ የተሴረ የሴራ ውጤት ብቻ አይደለም። የእኛው በጥቅምና በስልጣን ያበዱ ፖለቲከኞቻችን የተደናበረ የፖለቲካ አዙሪት ውጤትም ነው።

ባለፉት 5 ዓመታትም የኢትዮጵያ የጸጥታ ሁኔታ ችግር ተባብሶ የጎሳ ፖለቲካው የበለጠ አገንግኖ ወጥቶ የክልሎች የግጦሽ ቦታ እና ትንንሽ መንደሮች የእኔ ነው የእኔ ነው ተራ ንትርክ ሁሉ እስከ ሚልዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን የሚያፈናቅል፣ሺዎችን የሚያሰድድ እና ወደ የበለጠ ድህነት የሚከት ሆነ። ኢትዮጵያ የተሻለ መንገድ ለመያዝ ስትታትር አዳዲስ ግጭቶች እየተፈለፈሉ እና ፖለቲከኞቻችን ደግሞ ዘለው እያቦኩት (እነርሱን እሳቱ አይነካቸውም) ህዝቡን ለበለጠ መከራ እየማገዱ ሀገሪቱን የሽብር ምድር ለማድረግ ከላይ ታች እያሉ ነው።

መንግስት በሌላ በኩል የቆረጠ አቋም እና ወጥ የሆነ አሰራር እና የጸጥታ መዋቅር እንደመመስረት በየክልሉ ያሉ የጎሳ አደረጃጀቶች እና ታጣቂዎች ከወለጋ እስከ ቤኒሻንጉል ከጌድዮ እስከ ቦረና ህዝብ ሲያፈናቅሉና ከተሞች ሲያወድሙ የመረረ እርምጃ ከመውሰድ ጋር የተለየ እና አዲስ አቅጣጫ ማስቀመጥ ስለተሳነው ኢትዮጵያ በጎበዝ አለቃ የምትመራ ሀገር እስክትመስል ድረስ ከአንዱ የሀገሪቱ ክፍል ወደ አንዱ የሀገሪቱ ክፍል መሄድ እንደ ትልቅ ዕድል እንዲቆጠር ሆኗል።

ወደወቅታዊው የሀገራችን ሁኔታ ስንመጣ በአማራ ክልል እና በተቀረው የኢትዮጵያ ክፍል ከፍተኛ ቅቡልነት የነበረው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግስት በኦሮምያ ክልል ያለው የብልጽግና የቀድሞው ኦህዴድና በውስጡ የተሰገሰገው የኦነግ ሸኔ ቡድን ባራመዱት የጎሳ ፖለቲካ እና የማንአለብኝነት ጥቃት በተለይ የአማራ ተወላጆች በሆኑት የወለጋ እና ሌሎች ቦታዎች ላይ የፈጸሙት ግፍ አሁን በአማራ ክልል ለተነሳው የጸጥታ መደፍረስ ምክንያት ሆኗል።በእዚህም በብሄርተኝነት የመቀስቀስ ስራው ለብሄርተኞች አመቺ ሆኖላቸዋል።  

''አክቲቪዝም ከጆርናሊዝም'' የደባለቀባቸው ዩቱበሮች በአማራ ክልል የሚፈሰው የመከላከያ እና የክልሉ ህዝብ ደም አልታያቸው ብሏል። በኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሊባሉ ይገባል።

በአማራ ክልል የተነሳው ቁጣ በኦሮምያ ክልል አክራሪ ቡድኖች የፈጸሙት ጥላቻን የተሞላ የግፍ ውጤት መሆኑ ተደጋግሞ ተነግሯል።ይህ ማለት ግን ኢትዮጵያ የመከላከያ ኃይሏን በራሷ ህዝብ ፈጅታ ሌላ የታሪክ ጠባሳ ይቀመጥ ማለት አይደለም። መንግስት በውስጡ ያሉትን በኦሮሞ ስም የሚነግዱትን አክራሪ ብሔርተኞች ማስወጣት ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን ወደ የለየለት የእርስበርስ ጦርነት የሚከተውን የጎሳ ፖለቲካ እና አደረጃጀት በሕግ የማገድ ውሳኔ ድረስ ካልሄደ ነገሮች ከተበላሹ በኋላ እና ሁሉም ነፍጥ ካነሳ በኋላ ''እንደ 1966ቱ የእንዳልካቸው ካቢኔ '' በኋላ ከረፈደ የጎሳ ፖለቲካ ታግዷል ወዘተ ቢሉት አይሰራም። ሁሉም መከወን ያለበት በጊዜው ነው።

ከእዚህ ጋር በተያያዘ በአሁኑ ወቅት በአማራ ክልል ያለው በመከላከያና በአማራ ክልል ታጣቂ (ፋኖ) መሃከል ያለው ግጭት በምንም መልኩ መቆም ያለበትና ያሉት ጉዳዮች ሁሉ ወደ ንግግር መምጣት አለባቸው። ይህ የመነጋገር ጉዳይ ሲነሳ ያዙኝ ልቀቁኝ የሚሉት አክቲቪዝም ከጆርናሊዝም የተደባለቀባቸው ዩቱበሮች ናቸው። እነኝህ ዩቱበሮች ከውጭ ሆነው ''እስከ መጨረሻው ተጫረሱ'' ዓይነት መልዕክት ብቻ ሳይሆን ወደ ንግግር ይመጣ ሲባል ''ይሄ ባንዳ፣የአማራ ጠላት '' እያሉ ከምሁራን እስከ የሃይማኖት አባቶች በመሳደብ እና በማሸማቀቅ ሰው ለሀገሩ ያለውን ሃሳብ በነጻነት እንዳይሰጥ ከሽብር ያላነሰ ተግባር እየፈጸሙበት ነው። የዛሬ 50 ዓመት በኢትዮጵያ የነበረው ቀይ ሽብር ብቻ አልነበረም።የወቅቱ መንግስት ተቃዋሚዎችም ነጭ ብለው የሚጠሩት ሽብር ነበራቸው። በወቅቱ ሁሉም ለሚሰራው ለራሱ እና ለደጋፊዎቹ '' እንደ ቅዱስ ስራ '' እየተወሰደ ይሞከሻሹበት ነበር። ዛሬም በ21ኛው ክ/ዘመን ተቀምጦ '' ብልጽግና የሆነውን በሙሉ ፍጀው፣በለው'' የሚባልበት ጊዜ ላይ ተደርሷል። በሌላ በኩል የፋኖ ታጣቂ ብቻ ሳይሆን ለፋኖ የምትደግፉ ናችሁ እየተባሉ ዜጎች ፍዳቸውን እያዩ ነው። ሁሉም እንደየቀይ ሽብር ዘመን የራሱን ያሞግሳል። የአሁኑን የከፋ የሚያደርገው ለአቅመ ጋዜጠኝነት ያልደረሰ ሁሉ ለዩቱብ ክፍያ ብሎ ሀገር ወዳድ መስሎ ግጭቶጭ እንዲጠመቁ ቀን ሙሉ ላይ ታች ሲል መዋሉ ነው። በወንድማማቾች መሃክል ያለ የደም ወሬ በማዛመት ከዩቱብ የተገኘ ገንዘብ ለቤተሰብስ ጤና ይሆናል? ይህንን በጊዜ የምናየው ነው። ዩቱበሮች ስለየምስኪኑ ገበሬ ቁስል አውሮፓና አሜሪካ ተቀምጠው ሊሰማቸው አልቻለም። የእነርሱ ልጆች ትምህርት ቤት እየሄዱ ሃገር ቤት ያለው የገበሬው ልጅ ህይወት ግን ገና አልተሰማቸውም። ይልቁንም ''ከመከላከያ ጋር አንዳች ንግግር ታደርኛ'' እያሉ የማሸማቀቅ እኩይ ተግባራቸውን ቀጥለውበታል። 

ኢትዮጵያ ከእዚህ በላይ የምትሸከመው የጦርነት ትከሻ የላትም። 50 ዓመታት ያህል ደም ፈሶባታል።መንግስት በኦሮምያ ክልል ያለው ጽንፍ የረገጠ አስተሳሰብና የዕብሪት አካሄዶችን አደብ ማስገዛት ብቻ ሳይሆን የጎሳ ፖለቲካውን የሚያከስም የህግ ማዕቀፍ በቶሎ አውጥቶ ስራ ላይ ማዋል አለበት። በአማራ ክልል ያሉት ታጣቂ የፋኖ አባላትም ከመከላከያ ጋር በቶሎ እርቅ ፈጽሞ እና በክልሉ ሰላም እንዲመጣ በመነጋገር የጋራ ኢትዮጵያን ለመጠበቅ መነሳት አለባቸው። ህዝብ ሁሉንም እየታዘበ ነው።ታዝቦ ታዝቦ ለሰላም አልቆም ያለው ማናቸውም ኃይል ላይ ማለትም መንግስት ላይም ሆነ በአማራ ክልል ያለው ታጣቂ ላይ ድንገት ይነሳል። ከእዚህ ሁሉ በፊት ሁሉም አደብ የመግዣ ጊዜው አሁን ነው። የኢትዮጵያ ገበሬ ደግሞ ከፖለቲከኛው በተሻለ መንግስት ምን ማለት እንደሆነ ያውቃል። የመንግስት ድንበር ይፍረስ የሚል አይደለም። ከመጠን ያለፈ የሕግ መጣስ ያስቆጣዋል። ይህ ቁጣ ግን የታጠፈው ሕግ ተመልሶ ሲዘረጋ ይመለሳል።

ባጠቃላይ የባዕዳን ጣልቃ ያልገባበት የመነጋገር እና ኢትዮጵያ ከገባችበት የፖለቲካ ቅርቃር የሚያውጣ የመፍትሄ መንገድ ከመንግስትም ከፋኖም ይጠበቃል። አሜሪካን አውሮፓ ቁጭ ብለው መንግስት ለመገልበጥ ነው መሄድ ያለብህ የሚለው ስብከት ኢትዮጵያን ወደ መበተን ደረጃ የሚያደርስ አደገኛ አካሄድ ስለሆነ ጆሮ ሊሰጠው የሚገባ አይደለም። መንግስት ይቀየራል።የሚቀየረው ግን በጦርነት ክልልን በማውደም አይደለም። ትግል ሲያስፈልግ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሰላማዊ ትግሎች መንገዶች አሉ።ከእዚህ ባለፈ የምርጫ ሰሌዳን ተከትሎ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ የሚፈልገውን በመምረጥና ድምጹ እንዲከበር በመታገል ወደ የሚፈለገው ለውጥ መምጣት ይቻላል።ቢያንስ በ21ኛው ክ/ዘመን መንግስት ባልሰለጠነ መንገድ በማውረድ ሀገር ከመበተን መታደግ የሁሉም ግዴታ መሆኑን ማወቅ አለብን።ከእዚህ ጋር የሰላም ንግግሮችን ለማጣጣል የሚሞክሩትን አጥብቀን መቃወም ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታችን ነው።

+++++++++++++++++++++++++++++


Saturday, September 16, 2023

Is the biblical ark of the covenant hidden in an Ethiopian church?

በመጽሐፍ ቅዱስ የምናውቀው የሙሴ ታቦተ ሕግ በኢትዮጵያ ተደብቋልን? በሚል ርዕስ የኢየሩሳሌም ፖስት ጋዜጣ ዛሬ ቅዳሜ መስከረም 5፣2016 ዓም ምሽት የጻፈው አዲስ ጽሑፍ።

ጽሑፉ ተመራማሪዎች ታቦተ ሕጉ በኢትዮጵያ ለ3 ሺህ ዓመታት ተደብቆ እንደሚገኝ ይገልጻሉ በሚል መግቢያ ይጀምራል።

ሙሉውን ጽሑፍ ከስር ያንብቡ።

በቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴ የተገነባው የአክሱም ጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን።

Is the biblical ark of the covenant hidden in an Ethiopian church? 

  • Researchers claim the ark hidden for 3,000 years in Ethiopia.
By WALLA! 
Published: SEPTEMBER 16, 2023 19:20
Jerusalem Post
===================
Where is the Ark of the Covenant, the vessel that, according to Jewish tradition and the Bible, safeguarded the Tablets of the Covenant?

The gold-coated ark adorned with a gold wreath once resided in the First Temple until the Babylonian army's destruction in 587 BC. While records don't mention its fate, it's improbable that such a sacred and precious object disappeared unnoticed.

So, did it survive the destruction, and if so, where does it rest today?
The ark, also known as the Ark of God or the Ark of the Testimony, was positioned within the Holy of Holies in the First Temple. It held immense significance, described as the primary "seat of the Shekinah," and it hasn't been seen since the First Temple's ruin.

Sages hold two opinions on its whereabouts.

Rabbi Eliezer and Rabbi Shimon believe the ark was taken to Babylon and destroyed, while Rabbi Yehuda claims it remained in the temple's confines but was later relocated and rediscovered elsewhere. The Ark of the Covenant's location remains a mystery that scholars, adventurers, rabbis, and enthusiasts have sought for over 2,000 years.

A peculiarly shaped stone unearthed years ago in the ruins of an ancient temple near Jerusalem raises the possibility that it may be the "great stone" upon which the Ark of the Covenant rested, housing the sacred Tablets of the Covenant.

On the other hand, a substantial number of Bible scholars propose that the ark's final resting place is a church in Ethiopia. They assert that it was clandestinely transported there from Israel during the reign of King Manasseh of Judah (697 BC to 642 BC), and it has remained hidden there for 3,000 years, meticulously guarded by virginal nuns.

For millennia, the ark's whereabouts, said to possess magical powers and bring death to those who touch it, have been enigmatic. Ethiopian Christians contend that the Ark of the Covenant resides in a chapel within the small town of Axum, where they believe it arrived nearly three millennia ago, watched over by a group of nuns who are forbidden to leave the chapel until their demise.

A report by Fox News suggests that the Church of Our Lady Mary of Zion in Axum houses one of the world's most coveted biblical relics, including the Ten Commandments and Aaron's "staff of miracles."

Numerous Torah scholars are convinced that the Ark of the Covenant was covertly transported from its original resting place beneath the Temple Mount all the way to Africa, carried by Jews expelled from Israel during Manasseh's rule. Since its disappearance, multiple theories about its location have surfaced, including submersion in the Sea of Galilee, concealment beneath the Temple Mount's foundation, surrender to the Americans, and the increasingly supported claim of its presence in Ethiopia.

According to the Bible, the Israelites crafted the Ark of the Covenant in the Sinai desert after leaving Egypt. Its vanishing coincided with the Babylonian conquest of Jerusalem in 587 BC.

One account narrates how the Jordan River stood still as priests carrying the ark crossed it, while other stories describe its role in battles where its mystical powers aided the Israelites. When captured by the Philistines, the ark's presence caused outbreaks of tumors and diseases, compelling them to return it to the Israelites. Some tales even mention death befalling anyone who touched or gazed upon the ark.

As mentioned earlier, certain researchers propose that the Ark of the Covenant traveled extensively before ultimately reaching ancient Israel. According to the Maccabees, it was concealed in a cave on Mount Nebo by the prophet Jeremiah. In Hasmoneans 2, it is recounted how Jeremiah discovered a hidden cave on the mountain and buried the Ark of the Covenant, admonishing exiles not to mark its location until God reunites His people from exile and returns them to their homeland.

Another narrative, currently gaining credence, asserts that the Ark of the Covenant found its way to Ethiopia and now resides in the Church of Our Lady Mary of Zion. According to this belief, Ethiopian Orthodox Christians transported it to Axum through Menelik, the son of the Queen of Sheba and King Solomon of Israel, after Jerusalem's fall in 586/587 BC and the destruction of Solomon's Temple.

Britons also claim the ark's possession, with one theory proposing that the Knights Templar, also known as the Order of the Knights of Solomon's Temple, discovered it in Jebel al-Madhbah in Petra, potentially the biblical Mount Sinai. Some legends suggest the Templars hid the Ark of the Covenant in Ethiopia, while another theory suggests British Baron Ralph de Sudeley, known for generous religious donations, transported it to his estate at Temple (temple) Hardwick. Notably, this location is currently owned by the British Ministry of Defense and is securely sealed.

To this day, no definitive historical theory exists about the Ark's fate, with some researchers even questioning its initial existence.

Curious to find out?

You'll need to wait, as Jewish sources prophesy the ark's revelation near the coming of the messiah. The Ramban wrote that it will be unveiled "in the building of the house or in the future wars before the messianic king."




Sunday, September 3, 2023

የግሪካውያን የኢትዮጵያ ወዳጆች ማኅበር እና በኢትዮጵያ የግሪክ ማኅበረሰብ አመራሮች በጣልያን፣ፈረንሳይና ግሪክ የኢትዮጵያ ክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ሃሚሳ ጋር በአቴንስ ከተማ ተገናኙ። የግሪካውያን የኢትዮጵያ ወዳጆች ማኅበር እኤአ መስከረም 30/2023 አቴንስ ላይ ልዩ ዝጅግት አዘጋጅቷል።

ክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ከኢትዮጵያ ወዳጆች የግሪክ ኮሚኒቲ አባላት ጋር በአቴንስ፣ግሪክ


  • ''በአዲስ አበባ የሚገኘው የግሪክ ኮሚኒቲ ከመንግስት ጋር የገባውን ችግር በተመለከተ ጉዳዩ በፖለቲካና ዲፕሎማሲያዎ ደረጃ የሚፈታ ነው '' ክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ሃሚሳ

==========================
ጉዳያችን ልዩ ዘገባ/Gudayachn Exclusive
===========================
የግሪካውያን የኢትዮጵያ ወዳጆች ማኅበር እና በኢትዮጵያ የግሪክ ማኅበረሰብ አመራሮች በጣልያን፣ፈረንሳይና  የኢትዮጵያ ክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ሃሚሳ እና የኤምባሲው ሁለተኛ ጸሐፊ አዲሱ መልካሙ ጋር በአቴንስ ከተማ መገናኘታቸውን ከሰሞኑ ለጉዳያችን ከኢትዮጵያ ወዳጆች ግሪካውያን ማኅበ አመራሮች የደረሳት ዘገባ ያመለክታል።ከክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ጋር የነበረው ውይይት በአቴንስ ሜልያ ሆቴል የተደረገ ሲሆን፣በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ ወዳጆች የግሪክ ማኅበረሰብ ምክትል ፕሬዝዳንት ሚስተር ጆርጂዮስ ሚካኤልደስ፣የዳይሬክተሮች ቦርድ ተወካይ ኪሜትሪዮስ ስትራጋሊስ እና ከአዲስ አበባ የግሪክ ኮሚኒ ማኅበር ፕሬዝዳንት ኦዲስየስ ተገኝተው ነበር።  

በእዚህ ውይይት ላይ በቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴ ለግሪክ ህዝብ የተከናወነ የግብረሰናይ ተግባር የከወኑበት የአቢሲንያ አደባባይ በአቴንስ ከተማ ምክርቤት ስሙን በቋሚነት የማስመዝገብ ስራ ዙርያ ላይ ምክክር መደረጉን ለማወቅ ተችሏል።በእዚህ መሰረት የኢትዮጵያ ወዳጆች የግሪካውያን ማኅበር ቦታው በአቴንስ ከተማ ምክርቤት እንዲመዘገብ ከአቴንስ ከተማ ከንቲባ ኮስታስ ባኮያኒስ ጋር ስለጉዳዩ መነጋገራቸውን እና ከንቲባው በጎ ምላሽ እንደሰጡ ለጉዳያችን የተላከው የማኅበሩ መረጃ ያብራራል።ክቡር ከንቲባው ማኅበሩ በቦታው ላይ ለማቆም ያቀደው የኢትዮጵያና የግሪክን ታሪካዊ ግንኙነት የሚያስታውስ ሃውልት ስራ በተመለከተ ድጋፋቸው መግለጻቸውን ለማወቅ ተችሏል።

የመስከረም 30/2023 ዓም እኤአ በአቴንስ አቢሲንያ አደባባይ ለሚሰራው የኢትዮጵያና ግሪክ መታሰብይ ሃውልት ማስጀመርያ መርሃግብር በተመለከተ ማብራርያ የተሰጠ ሲሆን በዝግጅቱ ለመታሰብያ ሃውልቱ ማሰርያ የገንዘብ ማሰባሰብያ መርሃግብር የሚኖር ሲሆን ለሃውልቱ ማሰርያ ከሚፈለገው በላይ ገንዘብ ከተገኘ በኢትዮጵያ በቦረና ለውሃ ማውጫ ተግባር እንደሚውል ተወስቷል።

ይህ በእንዲህ እያለ በአዲስ አበባ የሚገኘው የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርትቤት ከትምህርት ሚኒስትር ጋር የተገባው ውዝግብ አስመልክቶ ማብራርያ ለክብርት አምባሳደር ተሰጥቷል።በእዚ መሰረት የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርትቤቱ ጉዳይ ላይ የተነሱትን ውዝግቦች አስመልክቶ ማብራርያ ተሰጥቷል። በአዲስ አበባ የሚገኘው የግሪክ ኮሚኒቲ ትምሕርትቤት በተመለከት ጉዳያችን የዘገብችውን ዝርዝር ጉዳይ በእዚህ ሊንክ ተጭነው ያንብቡ።በእዚሁ ስብሰባ ላይ የአዲስ አበባ ግሪክ ኮሚኒቲ ማህበር ፕሬዝዳንት የኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስቴር በኮሚኒቲው ትምህርትቤት ላይ የወሰደውን እርምጃ አስታውሰው እኛ ወደ ፍርድ ቤት መሮጥ የምንፈልግ ማህበረሰብ ሳንሆን የኢትዮጵያን ህግ የሚያከብር ማህበረሰብ ነን ሲሉ አሳስበዋል።

በውይይቱ ላይ አምባሳደር ዴሚቱ በሰጡት ምላሽ :

በሁለቱ ህዝቦች መካከል ያለው የቆየ ግንኙነት ጠንካራ በመሆኑ በቀጣይነትም ተባብረን መቀጠል አለብን። ለብዙ መቶ ዓመታት ወደ የነበሩ ግንኙነቶች እንደነበሩ ጠቅሰው፣ የትምህርት ቤቱ ጉዳይ በፖለቲካ እና በዲፕሎማሲያዊ ደረጃ የሚፈታ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት የማህበረሰቡን ንብረት የመውረስ ዓላማ እንደሌለው አሳስበዋል።

በአቢሲኒያ አደባባይ በሚሰራው ሀውልት ጉዳይ ላይ የሁለቱን ህዝቦች ግንኙነት ለትውልድ ለማስተላለፍ ጥረት የሚያመላክት በመሆኑ እጅግ ጠቃሚ ተነሳሽነት ነው በማለት አምባሳደሯ አብራርተዋል። ሀውልቱ በጋራ በኢትዮጵያና ግሪክ ተቀርጾ የሁለቱን ህዝቦች የቆየ ግንኙነት የሚያንፀባርቅ እንዲሆን እና የሃውልቱ ምረቃ ላይ የሁለቱ ሃገሮች ጠቅላይ ሚኒስትሮች የሚገኙበት እንዲሆን ምኞታቸውን ገልጸዋል።ከእዚህ በተጨማሪ በጥቅምት ወር ለአበበ ቢቂላ መታሰብያ በአቴንስ አንድዓይነት ዝግጅት ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተነስቷል።

በመጨረሻም የኢትዮጵያውያን ወዳጆች በግሪክ ማኅበር በቀጣይ ከአምባሳደሯ ጋር በማኅበሩ ጽህፈት ቤት ዳግም እንደሚገናኙና በጋራእራት እንደሚመገቡ ተስፋቸውን ገልጸው እጅግ መግባባት ለሰፈነበት ስብሰባ ምስጋናቸውን አቅርበው የዕለቱ ስብሰባ ተጠናቋል።

ከእዚህ በታች የኢትዮጵያውያን ወዳጆች የግሪካውያን ማኅበር ለጉዳያችን ውይይቱን አስመልክቶ የላከው የግሪክኛ ቋንቋ ትርጉም ከእዚህ በታች ይመልከቱ።
=================

MEETING OF THE ASSOCIATION OF GREEKS OF ETHIOPIA (A.G.E.) WITH THE ETHIOPIAN AMBASSADOR

On Thursday, August 24th, at the MELIA Hotel in Athens, a delegation of the Board of Directors of A.G.E., consisting of the 2nd Vice President Mr. Georgios Michaelides, the Treasurer Mr. Theodoros Panas and the member of the Board of Directors Mr. Dimitrios Stragalis, together with the President of the Greek Community Association of Addis Ababa Mr. Odysseas Parris, had a meeting with the Ambassador of Ethiopia to Italy who is accredited in Greece Mrs. Demitu Hambisa Bonsa, who was accompanied by the Second Secretary of the Embassy Mr. Addisu Melkamu Kebede.

The 2nd Vice President, referred to the intervention of the A.G.E. to the Municipality of Athens when rumors circulated about renaming of the historic Abyssinia Square in Monastiraki and the assurance of the Mayor of Athens Mr. Kostas Bakoyannis that there is no such intention. The Mayor supported the proposal of A.G.E. for the placement of a memorial monument and signage.

The 2nd Vice President noted the positive response of the Ethiopian Community living in Greece to the initiative to create this monument that will mark the long-standing relations between the two peoples. He said that the cost will be covered by sponsorships and actions of members and friends of S.E.A and Ethiopian Communities living in Greece and other countries abroad. He stressed that if the amount raised exceeds the cost of the monument, the remaining amount will be allocated to the BORENA area for the creation of a drinking water well, according to the wish of the Ethiopian Community in Greece.

The September 30, 2023 event at Abyssinia Square will mark the beginning of the celebrations for a century of the renaming of the Square by decision of the Municipality of Athens in 1924 to Abyssinia Square after the significant donation given by Ethiopia to the Greek refugees of the Asia Minor Catastrophe, and the over a century establishment of diplomatic relations.

The President of the Greek Community Association of Addis Ababa, reported on actions and claims of the Ethiopian Ministry of Education, which attempted to convert the English section of the Greek Community Schools owned by the Greek Community Association of AA, into a Charitable Endowment. A form that means the transfer of ownership of the school buildings through the Endowment to the Ethiopian State and dispossession of the Community's property. For the operation of the English section, the Greek Community Association of AA has established a new organization provided by the legislation for establishing an INTERNATIONAL SCHOOL from the 2023-24 school year and requested permission, which was not granted. He stressed that we are not a Community that wants to run to court but a Community that operates respecting Ethiopian laws.

He referred to the fact of the appointment of an Interim Administration by designs of the Ministry of Education, without any discussions or consultations, for the management of the English section of the school. The Interim Administration has exceeded its mandate by prohibiting the Board members of the Community to have access to the premises of the Community, issuing orders for the removal of residents from the houses that the community had provided them, etc. Still in excess of its authority, it is involved in purely community matters such as its social policy on indigent people, the management of the Greek St. Frumentius Church, the Cemetery, etc. Lastly they interfere in the Greek Section of the Schools that operate under the Greek Ministry of Education.

He pointed out that in May, the country's auditing mechanisms have taken the accounting documents of the Community for audit. No findings have been announced and the Bank accounts of both the Community and the personal accounts of the members of the Board of Directors of the Community have been frozen, despite the fact that the current Board, it is only one year in office, and since the beginning it met with this situation of interference.

He informed the Ambassador that the ownership of the Community Schools is not the same as the other schools where land was allocated for building. The Greek Community Schools were built on land which was purchased by the Greek community from the donations and sponsorships of its members.

The 2nd Vice President pointed that the Greek Community Association of AA has the full support of A.G.E., since A.G.E. represents the vast majority of the Community members living in Ethiopia at the time of the great exodus, who created and sustained the Community property, and that were forced to leave by the Derg Regime in 1975-76.

The Treasurer, Mr. Panas Theodoros, informed about the Marathon Road Museum and the request of the Municipality of Marathon to enrich the museum with exhibits from Ethiopian marathon runners. He also mentioned the cooperation of the A.G.E. with the "Pelargos" Association, which are families who have adopted children from Ethiopia, to teach Ethiopian culture to these children. From the bilingual books of "Pelargos” a part goes to support the literacy of young people in Ethiopia.

The Ambassador's statement was:

The long-standing relations between the two peoples have been strong and we must continue to deepen them. Relations that go back for hundreds of years.

The issue of the School will be resolved at the political and diplomatic level and she stressed that it is not the intention of the Ethiopian Government to take over the Community property. She regretted the turn the matter had taken.

On the issue of the monument in Abyssinia Square, she said that it is a very important initiative because that will show to future generations the relations between the two peoples. The initiative should be raised to a higher level, with the participation of the Ethiopian Ministry of Tourism and Culture, and when the unveiling ceremony is held, the two Prime Ministers should be invited to be present. She said that they have a wish that the monument should be jointly designed and reflect the long-standing relationship between the two peoples and asked to see the proposal of A.G.E.

She pointed out that they are planning some event for Abebe Bikila in Athens in October, of which they will inform A.G.E. in due time.

Regarding the marathon road museum, the Embassy's Second Secretary said that he would support the effort and took the initiative to find exhibits.

On the part of A.G.E. thanks were expressed for the time the Ambassador took to inform the Association and invited her on her next visit to be received at the A.G.E. offices for a briefing and then to have a dinner.

The whole discussion took place in an extremely friendly and family-like environment and all agreed to continue the constructive channel of communication that has started.

On August 25, a meeting took place between the President of A.G.E. Dr. Alexandros Grous, who came urgently and met with the Ambassador of Ethiopia.

============///==========

Tuesday, August 29, 2023

ኢትዮጵያ በብሪክስ አባል መሆኗ የአፍሪካ ሕብረት ከሀምሳ ዓመታት በፊት በአዲስ አበባ ከተመሰረተ በኋላ የተገኘ የመጀመርያ ከፍተኛው የዲፕሎማሲ ድል ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው።

============
ጉዳያችን ምጥን
===========

ብራዚል፣ሩስያ፣ህንድና ደቡብ አፍሪካ በጥምረት የመሰረቱት ብሪክስን ለመቀላቀል ቬኒዝዌላ፣ኢንዶኔዥያና አልጀርያን ጨምሮ 23 ሀገሮች ያመለከቱ ቢሆንም በመጪው ጥር 1፣2024 ዓም እኤአ ጀምሮ ብሪክስ  የተቀበላቸው ሀገሮች ግን ኢትዮጵያን ጨምሮ ስድስት ሀገሮችን ብቻ እንዲሆኑ በሙሉ ድምጽ ወስኗል። እነርሱም ኢትዮጵያ፣ግብፅ፣ኢራን፣የተባበሩት አረብ ኢምሬት፣ሳውዳረብያ እና አርጀንቲናን ተቀብሏል።

ብሪክስ ኢትዮጵያን ከሳሃራ ሀገሮች በታች በብቸኝነት ሲመርጣት ከአፍሪካ ደቡብ አፍሪካን ሳንጨምር ከሁለቱ አንዱ ማለትም ከግብጽ ጋር መርጧታል። ይህ የብሪክስ ኢትዮጵያን የመቀበል ጉዳይ አንዳንድ የምዕራብ ሀገሮችን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ ሀገሮችም ለምሳሌ ናይጄርያ የመሳሰሉ ሀገሮች የተጽዕኖ አቅም በኢትዮጵያ በበለጠ ደረጃ ጥላ እንዳጠላበት በትልጽ ታይቷል። ጉዳዩ ኢትዮጵያ አሁን አሰላለፏ ከእነ ብራዚል፣ኢራን፣የተባበሩት አረብ ኢምሬትና አርጀንቲና ጋር ያለው ጠንካራ የሚባል ኢኮኖሚ አንጻር ያላትን መጪ የማደግ አቅም፣የፈተናዎች የመቋቋም አቅምም፣ ለዓለም ካበረከተችው ታሪካዊ አስተዋጽኦ፣ወሳኝ እና ስልታዊ አቀማመጥ፣የተፈጥሮ ሃብት፣ከአፍሪካ ሁለተኛ የህዝብ ብዛት እና ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ስራ ሁሉ ኢትዮጵያ ተመራጭ ሀገር አድርጓታል።

''ሠላሳ ሚልዮን ህዝብን በአራት ሚልዮን ህዝብ የምንቀይር ሞኝ አይደለንም ''

ሠላሳ ሚልዮን ህዝብን በአራት ሚልዮን ህዝብ የምንቀይር ሞኝ አይደለንም ያሉት በ1969 ዓም በኢትዮጵያ የሩስያው አምባሳደር ነበሩ። ለእዚህ ምላሻቸው መነሻው ደግሞ ሩስያ ሱማልያን ስታስታጥቅ ቆይታ ለምን ወደ ኢትዮጵያ ፊቷን በፍጥነት አዙራ የኢትዮጵያ አጋር ሆነች? የሚል ጥያቄ ሲጠየቁ ነበር። በወቅቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት 30 ሚልዮን ሲሆን ሱማልያ 4 ሚልዮን ህዝብ ነበራት። ዛሬም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከናይጀርያ ቀጥላ ሁለተኛ የህዝብ ብዛት ያላት ባለ 123 ሚልዮን ህዝብ መሆኗ ብቻ በአፍሪካ ቀንድም ሆነ በመካከለኛው ምስራቅ ላይ ያላት ተጽዕኖ በቀላሉ አይታይም። አንዳንዶች ብሪክስ ኤርትራ ካላት የጸረ ምዕራቡ አቋም አንጻር ለአባልነት ይጋብዛታል ብለው የሚያስቡ ነበሩ። ነገር ግን ጉዳዩ የ120 ሚልዮን ህዝብን የመምረጥ ስሌት ለብሪክስ አባላት ከባድ ሂሳብ አይደለም። 
 
ብዙ የአፍሪካ ሀገሮች የብሪክስ አባል ለመሆን ቢያስቡም የሩቅ ህልም ሆኖባቸዋል።

የብሪክስ አባል ሆኖ በቀጣይ ከምዕራብም ሆነ ከብሪክስ አባላት ጋር የልማት አጋርነትን ማጎልበት የብዙ አፍሪካ ሀገሮች ምኞት ነው። በእዚህም በኢትዮጵያ በብዙ በአዎንታዊ መልኩ ቀንተዋል። የናይጀርያ አንዳንድ ጋዜጦች መንደሪኑን ከዛፉ ለመቅጠፍ የዘለችው ጦጣ በዝላይ አለመድረሷን ስታውቅ ድሮም መንደሪኑ አይጣፍጥም ብላ ሳትቀምስ እንደሄደችው ዓይነት ነው። ናይጀርያ እንዴት አመልክታ አልገባችም ለሚለው አንዳንድ ምሁራን ምላሽ ለመስጠት ብሪክስ በቅርቡ ውጤቱ የሚታይ አይደለም በረጅም ጊዜ ነው የሚታየው የሚል ጽሑፍ በመጻፍ ምሁራኑን ለማጽናናት ሞክረዋል።

ከሳሃራ በታች ያሉ ሀገሮች ኢትዮጵያ ያላትን ያህል የምጣኔ ሃብት ነጻነት ስለሌላቸው ዘው ብለው ብሪክስ ውስጥ ቢገቡ በሚቀጥለው ቀን ከባንኮች እስከ ግዙፍ የምጣኔ ሃብት ተቋም ድረስ የተያዙት በውጪ ኩባንያዎች በመሆኑ እንደፈለጉ የመወሰን አቅማቸው የሚታሰብ አይደለም። የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት በምንም መልኩ አሁንም በውጭ ብድር እና እርዳታ የታገዘ ቢሆንም ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች አንጻር በአንጻራዊ መልኩ የተሻለ የተጽዕኖ መቋቋም አቅም ይታይበታል። ከሁሉም ደግሞ ቀድሞ ከነበሩት ሦስት መንግስታትም ጊዜም ቢሆን ኢትዮጵያ አሁንም ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች አንጻር አንጻራዊ ነጻነት ያላት ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ፖሊሲ አውጪው የመወሰን አቅሙ የተሻለ ነው። የብሪክስ መስራቾችም በናይጀርያ እና በኢትዮጵያ መሃል ያለው የመወሰን የነበረ አቅም የገባቸው ይመስላል።

የብሪክስ አባል መሆን ማለት የምዕራብ ግንኙነትን ማራገፍ ማለት አይደለም።

ኢትዮጵያ ካለፉት ታሪኳ ልትማር ይገባል። ብሪክስም ይጠቅማታል፣ከምዕራቡ ጋርም ያላት ግንኙነት ይጠቅማታል።በቀዝቃዛው ጦርነት ዘመን ብዙ ሀገሮች ከአንዱ ጎራ እየተጠቀለሉ ሲገቡ እንደህንድ ያሉ ሀገሮች ደግሞ ገለልተኛ በሚል ድርጅት መስርታ የሁለቱንም የልማት ጥቅም በማግኘት ጊዜውን አልፋዋለች። ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባል ሀገሮች ለምሳሌ ከህንድ እና ከደቡብ አፍሪካ አንጻርም ሲታይ የባህል እና የታሪክ ጋርዮሿ በራሱ ለልማስ ስኬት የሚያመጣው አዎንታዊ አስተዋጾ ቢኖረውም በሚልዮን የሚቆጠሩ ተወላጆቿ የሚኖሩበት እና የቴክኖሎጂ ግንኙነቷም እየሰፋ የመጣው የምዕራቡ ግንኙነቷን ፈጽሞ ገለል ማድረግ አትችልም። አንዳንድ ምሁራን እና ሚድያዎች ጉዳዩን ከቀኝ ወደ ግራ የመዞር ያህል አድርገው ለማቅረብ የሚሞክሩት ትንሽ ብስለት የጎደለው አካሄድ ትክክል አይደለም። በእርግጥ በሳምንቱ መጨረሻ ላይ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የኢትዮጵያ ወደ ብሪክስ የመግባት ጉዳይ አስመልክተው ሲናገሩ ጉዳዩ ከአንድ ጎራ ወደ ሌላ የመሄድ ጉዳይ አለመሆኑን ገልጸዋል። ይህ መሰረታዊ ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያ የማደግ ተስፋዋን በአጋርነት ከቆሙት ጋር ሁሉ አብራ የምትሰራ መሆኗን በተግባር ማሳየት ነገር ግን የበለጠ የሚያግዟት ጋር ተባብራ መስራት አዋጪ መንገዷ ነው።

ኢትዮጵያ በብሪክስ አባል መሆኗ የአፍሪካ ሕብረት ከሀምሳ ዓመታት በፊት በአዲስ አበባ ከተመሰረተ በኋላ የተገኘ የመጀመርያ ከፍተኛው የዲፕሎማሲ ድል ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው።

የኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሆና ከቀዳሚ ስድስት የዓለማችን ሀገሮች ጋር መመረጧ ዛሬም ደጋግመን እኛ እራሳችንን ያላወቅን፣ከሆኑ ዓመታት በኋላ እራሳችንን ዝቅ አድርገን የምናይ እኛ ማን ነን? ማን ነበርን? ዛሬስ የት ላይ ነን? ወደፊስ የምንሄደው? እራሳችንን ሳናውቅ ሌሎች ያወቁን ምናችንን ነው? ብለን ደግመን የመጠየቂያ ጊዜ አሁን ነው። ኢትዮጵያ ላለፉት 50 ዓመታት ገደማ በዓለም ላይ ያላት የዲፕሎማሲ አቅም በተለይ ከንጉሱ ከስልጣን መውረድ በኋላ ደብዝዞ ኖሯል። በንጉሱ ዘመን ከተሰራው የኢትዮጵያን ማዕከልነት እና ዓለም አቀፋዊም ሆነ አህጉራዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ካጎሉት ውስጥ ጉልሁ እና አሁንም ድረስ ቀጣይ ፋና የሆነው የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አሁን የአፍሪካ ሕብረት በአዲስ አበባ የመመስረቱ ጉዳይ ነበር።

የአፍሪካ ሕብረት ጉዳይ ኢትዮጵያን የግዙፍ አህጉራዊ ዲፕሎማሲ የማሳለጥ አቅሟን አሳድጎታል። ከአፍሪካ ሕብረት በኋላ ኢትዮጵያ የባሕር በር አልባ ከመሆኗ እና በምግብ እራሷን ያለመቻሏ ሁሉ ተደማምሮ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ መሪነት አቅም በእጅጉ ከመፈታተን አልፎ ትናንሽ ሀገሮች ከኋላዋ ተነስተው የተሻለ ተጽዕኖ ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ ተመልካች ሆናለች። ከእዚህ ሁሉ በኋላ ኢትዮጵያ ከእነብራዚል፣የተባበሩት አረብ ኢምሬት እና አርጀንቲና ጋር ተጋፍታ ከሳሃራ በታች ካሉ ሀገሮች በሁሉም መስፈርቷ ያለፈውን እና የመጪ ተስፋዋንም ጭምር በሚገባ መርምረው የብሪክስ መስራች ሀገሮች ሲመርጧት ኢትዮጵያን በከፍተኛ ደረጃ ያላትን የዲፕሎማሲ፣ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ግርማ በፍጥነት አሳድጎታል። ይህንን በብዙ ማስረጃዎች ማስረዳት ይቻላል።በእርግጠኝነት ማለት የሚቻለው ግን ኢትዮጵያ በብሪክስ አባል መሆኗ የአፍሪካ ሕብረት ከሀምሳ ዓመታት በፊት በአዲስ አበባ ከተመሰረተ በኋላ የተገኘ የመጀመርያ ከፍተኛው የዲፕሎማሲ ድል ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል መሆኑ ነው። ይህ ደግሞ በርካታ ንግግሮች፣ውይይቶች፣አቅምን አግዝፎ የማቅረብ የተለያዩ ስልቶች እና የነበረ እና ዘላቂ ወዳጅነትን ለማጽናት የተደረጉ በርካታ የዲፕሎማሲ እና ሁለንተናዊ ጥረቶች እንደነበሩ ለመረዳት ከባድ አይደለም።

ለማጠቃለል፣ አሁን የእኛ ቦታ ከእነብራዚል፣አርጀንቲና እና የተባበሩት አረብ ኢምሬት ጋር በእኩል ደረጃ መሆኑና ተፈላጊነታችን በእዚህ ደረጃ መናሩ ለእኛ አልታየን ከሆነ ለሌሎች መታየቱ ግልጽ ሆኗል። የእኛ እንደምንፈለገው ደረጃ መሆን ብቻ ሳይሆን እራሳችንን በምን ያህል የቀረንን ሞልተን በቶሎ ከመረጡንም ከተመረጡት ጋርም በፍጥነት አስተካክለን በፍጥነታቸው ልክ ለመሄድ ተዘጋጅተናል? የሚለውን ጥያቄ መመለሱ ነው ቁም ነገሩ። የማደግ ተስፋችን ከፊታችን ቆሞ እኛ ግን በብሄር ፖለቲካ እና በመንደርተኝነት እየተቧደኑ ከሚገፉን እና ሀገር ከሚበትኑ ጋር ከቆምን ዛሬም ኢትዮጵያ የገጠማትን የማደግ ተስፋ መልሰን የምናጨልም ሆነን የመጪውንም ትውልድ ዕድል ዘጊዎች እንዳንሆን መጠንቀቅ አለብን። ኢትዮጵያ ከሁሉም አጋሮቿ ጋር አብራ እንድትለማ በውስጧ ጋሬጣ የሆኑ ሃሳቦች የሚዘሩባትን መጋፈጥ ብቸኛው አማራጭ ነው።
==================/////===============

Saturday, August 26, 2023

አዲሱ የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ትናንት ዓርብ ነሐሴ 19/2015 ያደረጉት ሙሉ ንግግር።(ቪድዮ)

አቶ አረጋ በመቀሌ የአቶ ሽመልስ ተወካይ ነኝ በማለት ህዝብ ከህዝብ ለማጋጨት የሞከረ ንግግር ያደረጉትን ግለሰብ ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ወቅሰዋል፣ አስጠንቅቀዋል። ሙሉውን ንግግር ይመልከቱ። 
የቪድዮ ምንጭ =አሜኮ


Thursday, August 17, 2023

''አንዱ ሲናገር ሌላው አያቋርጥ!'' የሦስተኛ ክፍል ተማሪዎች ክፍል ውስጥ የሚነገራቸው እና የሚያከብሩትን መመርያ ፓርላማው ገና አልተለማመደውም።

የተከበሩ አቶ ባያብል ሙላቴ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል።

======
ጉዳያችን
======

በእዚህ ሳምንት የተሰበሰበው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ብዙ ኢትዮጵያውያንን የስብሰባ አካሄዱ ደረጃውን የጠበቀ ሆኖ አላገኘውም።የተጀመረ ሃሳብ አዳምጦ ሃሳቡ ላይ ሌላ ሃሳብ ከመስጠት ይልቅ በማኅበራዊ ሚድያ አሉባልታ በሰሙት ወሬ እራሳቸውን እና የወከሉትን ህዝብ ክብር በማይመጥን ደረጃ ንግግሮችን ሲያቋርጡ እና ሃሳቦችም እንዳይሰጡ ሲሞክሩ ትዝብት ላይ ወድቀዋል።

የተወካዮች ምክርቤት አባላት የተሰበሰቡት ኢትዮጵያውያንን ወክለው ነው። ኢትዮጵያውያንን መወከል ማለት ደግሞ የተከበረ ባሕል፣መከባበርና አስተዋይነት አብሮ ሊታይበት ይገባ ነበር። አንድ የምክር ቤት አባል ወደ ምክርቤቱ ሲገባ የፓርቲዬን ሃሳብ በእጅም በእግርም ብዬ ማሳለፍ ብቻ በሚል ከሃሳብ ሙግት ውስጥ የሚገኝ አዲስ ለሃገር የሚበጅ በጎ ሃሳብ ፈልቅቆ ለማግኘት የሚይስችል ስብዕና ይዞ ካልገባ ከሚቀመጥበት ወንበር ብዙ አይለይም። የሚባለውን ሁሉ እየተቀበለ ለማሳለፍ እንጂ በሃሳብ ለመሞገት ያልተዘጋጀ የፓርላማ አባል እቤቱ ቢቀመጥ እና በሌላ መገናኛ መንገድ ድምጹን መላክም ይችላል።

ህዝብ የፓርላማ አባል የመረጠው እንደራሴ ሆነህ በአፍህ ተናገርልኝ፣ሞግትልኝ በአዕምሮህ እኔን ሆነህ አስበህ ሃሳብ አፍልቅልኝ በማለት እንጂ ሌላው የሚናገረውን አዳምጦ በሚገባ እና አሳማኝ በሆነ ምክንያት ከማቅረብ ይልቅ ህጻናት የማያደርጉትን እየተንጫጫ የሚናገር ሰው እንዲያቋርጥ አይደለም።''አንዱ ሲናገር ሌላው አያቋርጥ!'' የሦስተኛ ክፍል ተማሪዎች ክፍል ውስጥ የሚነገራቸው እና የሚያከብሩትን መመርያ ፓርላማው ገና ያልለመደው ትንሽ ቆይቶ በሱማሌ የምናየው ዓይነት የፓርላማ መንጫጫት እንዳናይ እየፈራን ነው። ትልቅ ሰው ባትፈሩ፣ልጆች እየተመለከቷችሁ ነው። እነርሱ በትምህርት ቤታቸው አስተማሪ አንዱ ተናግሮ ሳይጨርስ ሌላው አይናገርም! የሚለውን መመርያ ክፍላቸው ውስጥ አይጥሱትም።ከሰሞኑ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የቀድሞው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የጸጥታ ጉዳይ አማካሪ ሲናገሩ የነበረው የፓርላማ አባላት የተባለው ትክክልም ይሁን አይሁን በአጽንዖት የማዳመጥ ትዕግስት የማጣት ሁኔታ በእርግጥም ከተራ ስነምግባርም ባለፈ የተባለውን ሰምቶ በምክንያት የመሞገት የአቅም ውሱንነት የታየበት ነው።

አሁን ያለው ፓርላማ ከኢህአዴግ/ህወሃት ዘመን ፓርላማ ጋር ሲነጻጸር በሰው ኃይሉ የትምህርት ዝግጅትም ሆነ በልምድ የተሻለ እና አንጻራዊ መሻል አለበት ብለው የሚያስቡ ነበሩ።በክርክር ሃሳብ ሰልቶ እንዲወጣ በማድረግ ለሃገር የተሻለውን መንገድ እንድትጠቁሙ የተቀመጣችሁ የፓርላማ አባላት ህዝቡ ውስጥ የሚሰማውን የተለያዩ ሃሳቦች፣ሙግቶች፣ድጋፎችም ጭምር ሲንጸባረቁ ማየት የምንፈልግበት ቦታ ፓርላማ ነው። ፓርላማው የአንድ የፓርላማ አባሉን ሃሳብ ወደደውም ጠላውም ለማዳመጥ እና ተናጋሪው ሲጨርስ ሃሳብ የመስጠት ትዕግስት ካጣ ህዝቡማ ከመነጋገር ይልቅ ዱላ ልምዘዝ ቢል ምን ሊፈረድበት ነው?

አሁንም አልረፈደም። ፓርላማው እንዴት መነጋገር፣መሞገት እና በነጻነት ሃሳቡን የማንሸራሸር መብቱን ቁጭ ብሎ መክሮ ያስተካክል። በ21ኛው ክ/ዘመን ተቀምጠን እንድ የህዝብ ተወካይ ሲናገር ለመስማት የሚያስችል ትዕግስት እንዴት እንደሚገኝ መማሩ እጅግ አስፈላጊ ነው።

በእዚህ ሳምንት የአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማጽደቅ በተተራው ስብሰባ ላይ አቶ ገንዱ አንዳርጋቸው ሲናገሩ የፓርላማ አባላት ላሳዩት ትዕግስት ያጣ የማቋረጥ ሙከራ የምክር ቤቱ አባል የተከበሩ አቶ ባያብል ሙላቴ እንዲህ በማለት አምርረው ገልጸውታል።



Tuesday, August 15, 2023

በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተሰላም ከተማ ላይ የድሮን ጥቃት እንደሆነ የታመነው የመንግስት ጥቃት በጦር ወንጀለኝነት የሚያስጠይቅ ነው።በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ አጣሪ ኮሚቴም ካስፈለገ መቋቋም ያለበትና በድርጊቱ የሚጠየቁትን በትክክል ለፍርድ ማቅረብ ይገባል።


የቪኦኤ አማርኛ አገልግሎት ሙሉ ዘገባ ከስር ተያይዞ ያገኛሉ።

=======
ጉዳያችን
=======


በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተሰላም ከተማ ላይ የድሮን ጥቃት እንደሆነ የታመነው የመንግስት ጥቃት እንደ የፍኖተሰላም ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ ለቪኦኤ አማርኛ እንደገለጹት በጥቃቱ እስካሁን 26 መሞታቸው የተረጋገጠና 50 በላይ መቁሰላቸው ተረጋግጧል። ድርጊቱን አስመልክቶ የአሜሪካ ድምጽ ራድዮ የአማርኛው አገልግሎት የዐይን እማኞችን አነጋግሮ ያቀረበው ሪፖርት ደረጃውን የጠበቀ እና በስፍራው የነበረውን ሁኔታ ገለልተኛ በሆነ መልክ የተጠናቀረ ሪፖርት መልክ ያለው ነው።

ይህ ጥቃት እንደየዐይን እማኞች ገልጻ ቀደም ብሎ ድሮን በሰማይ ላይ ከመታየቱና ቃኚ አይሮፕላን ከማለፉ ጋር ተያይዞ እና በአካባቢው ሌላ ምንም ዓይነት የከባድ መሳርያ መጠመድ ባለመኖሩ የዐይን እማኞች የድሮን ጥቃት እንደሆነ እና በፒካፕ መኪናው ዙርያ ያልታጠቁ በርካታ ሰዎች መኖራቸው በግልጽ እየታየ የተፈጸመ ጥቃት መሆኑን በእዚሁ ዘገባ ላይ ነዋሪዎች ለቪኦኤ የአሜሪካ ራድዮ የአማርኛ አገልግሎት ተናግረዋል።

ይህ ማለት ድርጊቱ በጦር ወንጀል የሚያስጠይቅና ይህ እንዲፈጸም ትዕዛዝ ያስተላለፈው ማን እንደሆነ መንግስት መርምሮ ጉዳዩን ለህዝብ መግለጽ ያለበት ጉዳይ ነው። በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ አጣሪ ኮሚቴም ካስፈለገ መቋቋም ያለበትና በድርጊቱ የሚጠየቁትን በትክክል ለፍርድ ማቅረብ ይገባል።

የቪኦኤ አማርኛው አገልግሎት ሙሉ ዘገባ ሰኞ ነሐሴ 8፣2015 ዓም (ኦገስት 14፣2023 ዓም)



Friday, August 11, 2023

ጥያቄው እየመገብን ስናሳድግ የኖርነው ወደፊትም ማሳደግ የምንፈልገው የቱን ነው? የሚለው ነው። መጪው የኢትዮጵያ ዕጣም የሚወሰነው በእዚሁ ነው።



==========
ጉዳያችን ምጥን
==========

አባት እና ልጅ ዛፍ ስር ተቀምጠው ያወራሉ። ከዛፉ ስር ሁለት ድንቢጦች ጥሬ ይለቅማሉ። ከሁለቱ ድንቢጦች ፈንጠር ያለች ሌላ ድንቢጥ (እናት ድንቢጥ) ያገኘችውን አንዴ ለራሷ፣ሌላ ጊዜ ደግሞ ለሁለቱ ድንቢጦች እያመጣች እንዲበሉ ፊታቸው ታስቀምጣለች።ከሁለቱ ድንቢጦች ውስጥ አንዱ ተንኮለኛ ነው። ሦስተኛዋ ድንቢጥ እያመጣች ከሁለቱ ድንቢጦች ፊት የምትጥለውን ተንኮለኛው ድንቢጥ ሌላውን እየኮረኮመ ቀድሞ ይበላል። ሌላኛው አለምብላቱን የምታይ እናት ድንቢጥ ደግሞ ነገሩን እንደዋዛ አይታ ተመልሳ ሌላ ጥሬ ለማምጣት ትሄዳለች። አሁንም ግን መልሳ የምታመጣውን የሚበላው ተንኮለኛው ድንቢጥ ነው።

አባት እና ልጅ የድንቢጦቹን ድርጊት ይመለከታሉ። ልጅ በድንቢጦቹ ድርጊት እያየ ይስቃል።አባት ነገሩን በአንክሮ ይመለከታል። ከቆይታ በኋላ አባት ልጃቸውን፣ሰማህ ልጄ! እነኝህ ሁለት ድንቢጦች በእኛ ውስጥ ያሉ ሃሳቦች ምሳሌ ናቸው።ሁለቱ ድንቢጦች እንደ ባላንጣ ለሚበሉት እንደሚሻሙ ሁሉ በውስጣችንም ያለው ሃሳብ እንዲሁ እርስ በርሱ ይዋጋል። የእዚህ የውስጣችን ሀሳብ የመጣላት እና አንዱ አሸንፎ የመውጣቱ ፋይዳ የወደፊት እኛነታችንን ብቻ ሳይሆን በዙርያችን ያሉትንም ዕጣ ሁሉ ይወስናል።ጥሬውን የሚነጥቀው በውስጣችን ያለው የክፉ፣የጎሰኝነት፣ሌላውን የማጥላላት ምሳሌ ነው።የዋሁ እና ገሩ ድንቢጥ ደግሞ የመልካም፣ለሌላው የማሰብ፣ከጎጥ ይልቅ የሁላችን ኢትዮጵያ የሚለው ሀሳብ ምሳሌ ነው። በማለት አባት የድንቢጦቹን ምሳሌነት አፍታተው ነግረው የልጃቸውን ትኩረት ሳቡት። ልጅ ግን ጠየቀ፣ አባዬ ግን ከሁለቱ ሃሳቦች ማን ያሸንፋል? በማለት ጠየቀ።አባት መለሱ የበለጠ እየመገብን ያሳደግነው ያሸንፋል።የዘረኝነት፣የጎጥ እና የክፉውን ሀሳብ እየመገብን ካፋፋነው እርሷ ያሸንፋል።ኢትዮጵያ ለሁሉም፣ጎጠኝነት ይጥፋ፣እርስ በርስ አንጠፋፋ የሚለውን ሀሳብ እየመገብን ካሳደግነው ደግሞ እርሱ ያሸንፋል በማለት መለሱለት።

በኢትዮጵያ በህወሃት/ኢህአዴግ እና ኦነግ የተተከለው የጎሳ ፖለቲካ ትውልድ በክሎ ዛሬ ላይ በአማራ ብሔርተኝነት አገንግኖ ወጥቶ የኦሮሞንም ሆነ የትግራይን ብሄርተኝነት ወይንም የጎሳ ፖለቲካ የሚገዳደርበት ደረጃ ደርሷል።እዚህ ላይ ምንም ያህል ቢሽሞነሞን፣ ምንም ያህል የሌላው የበደል መጠን ጥግ ማለፍ ያስነሳው ቢሆን፣ምንም ያህል መድረሻው ኢትዮጵያዊነት ነው ቢባል፣ የአማራ ክልል የተነሳው እንቅስቃሴ ምድቡ ከብሄርተኝነት እንቅስቃሴ የሚመደብ ነው።ይህንን የሚያራምዱትም የሚክዱት አይደለም። እዚህ ላይ የብዙዎቻችን ለኢትዮጵያ ያለን ምኞትና ሕልም ግን ከየትም ጥግ፣ምንም ዓይነት መልኩን ቀይሮ ይምጣ የብሔርተኝነት እንቅስቃሴ ኢትዮጵያን የሚያፈርስ አደገኛ የመርዝ ብልቃጥ መሆኑን አይቀይረውም።

ሩቅ የማያይ የዛሬው አይገባውም።ዛሬ የሚሆነውን እያየ ይህ ኢትዮጵያን ወዴት ነው የሚወስዳት ብሎ ማማተር ያልቻለ ከአፍንጫ እስከ ከንፈር ድረስ ብቻ የማሰብ የተሰናከለ አስተሳሰብ ነው። ኢትዮጵያን ስናስባት የት እንድትደርስ የምናስብላትን መድረሻ እያሰብን ካልሄድን የፊት፣የፊትን እያዩ የመሄድ አደገኛ መንገድ የትኛውንም ኢትዮጵያዊ ሆነ ኢትዮጵያን ፈጽሞ አይጠቅምም።የኢትዮጵያ መጪ ዘመን የሚወሰነው እየመገብን ባሳደግነው ድንቢጥ ይወሰናል።

አሁንም ጥያቄው እየመገብን ስናሳድግ የኖርነው ወደፊትም ማሳደግ የምንፈልገው የቱን ነው? የሚለው ነው። መጪው የኢትዮጵያ ዕጣም የሚወሰነው በእዚሁ ነው።ለችግር መፍትሄ ተመሳሳይ ችግር በመድገም አይፈታም።በተቃራኒው በመሄድ ነው ማሸነፍ የሚቻለው። በሌላው በኩል ያለ ጎጠኝነት ጎዳን ተብሎ በተመሳሳይ መንገድ በመሄድ ለጊዜው ስሜትን ያረካ፣ንዴትን ያበርድ ካልሆነ በቀር ዘለቄታዊ መፍትሄ ለሀገር አይሰጥም።ከጎሰኝነት በተቃራኒው በፍጹም ኢትዮጵያዊነት መንገድ በመሄድ እና ስለ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እና ኢትዮጵያ ከልብ በመነጨ የፍቅር ስሜት በመሄድ እና ለእዚህም እስከ የህይወት መስዋዕትነት ድረስ በመክፈል ሀገር ይቆማል።ስለሆነም ስንመግብ የኖርነውን አውቀን፣ወደፊት ለመመገብ የምናስበውን ከአሁኑ በምናቅደው ልክ የነገዋ ኢትዮጵያ ትታወቃለች። መሬት ላይ ያለው ትልቁ የአብዛኛው ህዝብ እውነት ዛሬም የጋራ የሆነች እና ከጎሰኝነት የተጣላች ከፍቅር የታረቀች፣ሁሉንም ወገኔ የምትል ኢትዮጵያን ማየት ነው።
================////===========

Sunday, August 6, 2023

መሬት ላይ ያለው እውነታ፣ መከላከያ ፋኖ ላይ መተኮስ አይፈልግም።ፋኖም መከላከያ ላይ መተኮስ አይፈልግም።መንግስት ጉዳዩን በሰላም በመፍታት ኢትዮጵያን ከእርስበርስ ጦርነት የማዳን ታሪካዊ ኃላፊነት አለበት።

=========
ጉዳያችን ምጥን
=========

ጦርነት ውስጣዊ ቁጣ እና ፍትሃዊ የሆነ የመዋጋት ስሜት ይፈልጋል። ከእዚህ በፊትም ለመግለጽ እንደሞከርኩት በአማራ ክልል የተነሳው ህዝባዊ እንቅስቃሴ ድንገት ደራሽ አይደለም።የእዚህ ዓይነት የትጥቅ ትግል መነሳት በማናቸውም ጊዜ ሊነሳ እንደሚችል ጉዳያችን ላይ የዛሬ 5 ዓመት ከእነምክንያቱ ተጽፎ ነበር። ሊንኩን እዚህ ላይ ተጭነው መመልከት ይችላሉ።

አሁን መሬት ላይ ያለው እውነታ

አሁን መሬት ላይ ያለው ሁኔታ የሚያሳየው መከላከይ ፋኖ ላይ መተኮስ አይፈልግም። ፋኖም መከላከያ ላይ መተኮስ አይፈልግም። ለእዚህ ደግሞ ምክንያቱ ግልጽ ነው። መከላከያ የተዋቀረው በኢትዮጵያዊ ስሜት ነው። ፋኖንም በሀገር አንድነት ትግል ላይ ከህወሃት ጋር ሲያውቀው ኢትዮጵያን ሲያከብር እንጂ የማፍረስ ስሜት አላየበትም። ስለሆነም ከውስጥ የወጣ የጥላቻ ስሜት አብቅሎ አንዱ አንዱ ላይ ለመተኮስ ፈጽሞ የስሜት ጥላቻው በእዚያ ደረጃ የናረ ሁኔታ የለም።ይህ እንደ ሀገር ሲታይ ይህንን ጦርነት የሰው ህይወት ሳይጠፋ፣ንብረት ሳይወድም ለማስቆም የሚቻልበት እድል ትልቅ ነው ማለት ነው።

መንግስት ጉዳዩን በሰላም በመፍታት ኢትዮጵያን ከእርስበርስ ጦርነት የማዳን ታሪካዊ ኃላፊነት አለበት 

ይህ የእርስበርስ ጦርነት ነው። ውጤቱ ደግሞ በሁሉም ወገን ያለው የኢትዮጵያውያን ሞት የሚያመራው ኢትዮጵያን ይዞ ወደ ሌላ የመከራ ማጥ የሚያመራ ነው። እስካሁን ከደረሰው ጥፋት ሌላ ጥፋት ሳይከተል፣እዚህ ላይ ለማቆም በመጀመርያ ማናቸውንም ግጭት አስቁሞ ወደ መነጋገር መምጣት ያስፈልጋል። ከእዚህ ውጪ መከላከያ በአማራ ክልል ከተሞችን በመቆጣጠሩ ብቻ ድል ብሎ ሊቆጥር አይችልም።አሁንም መከላከያ የኢትዮጵያ ሃብት ነው።መከላከያ ኢትዮጵያን በዘመናዊ ጦርነት ለመከላከል እንጂ ከራሱ ወገን ታጣቂ ጋር ጉልበቱን አድክሞ ሀገርን ለውጭ ወረራ ማጋለጥ ሀላፊነት የሚሰማው ውሳኔ አይደለም። 

ይህ በእንዲህ እያለ በደብረማርቆስ ፖሊስ ኮሌጅ ውጪ እስካሁን ይህ ነው የሚባል የዝርፍያ ሁኔታ በሰሞኑ የአማራ ክልል እየተሰማ አይደለም። ለእዚህ ደግሞ የመረጃ እጥረት ካልሆነ በቀር እየተሰማ ያለው የታጣቂው ኃይል በተቻለ መጠን ለመንግስት እና የግለሰብ ንብረት ጥበቃ ለማድረግ እየሞከረ መሆኑ እንደሆነ እየተሰማ ነው። የደብረማርቆስ ፖሊስ ኮሌጅ ዘረፋ በተመለከተ የአንከር ሚድያ ላይ ቀርቦ የተናገረ አንድ ታጣቂ እንደገለጸው በደብረማርቆስ ፖሊስ ኮሌጅ የደረሰውን እንደሰማ እና ከዝግጅት ማነስ አንዳንድ ሌቦች አይኖሩም ማለት አይደለም በማለት ገልጾታል። ዝርፍያን እና ጸጥታ በተመለከተ የፋኖ ታጣቂዎች በፈለጉት መጠን ጸጥታ ለመጠበቅ ቢሞክሩም በቀጣይ ግን ፈተናዎች አይገጥሙም ማለት አይቻልም። እስካሁን ታጣቂዎች በገቡባቸው አካባቢዎች አካባቢዎች የኢንተርኔት አገልግሎት የተቋረጡባቸው አካባቢዎች ቢኖርም የቀጥታ ስልክ ግን በአንዳንድ ቦታዎች ቢያስቸግሩም፣የእዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ዛሬ እንዳረጋገጠውም በባህርዳር የቀጥታ ስልክ፣ውሃ እና መብራት አሁንም አገልግሎት አለ።

አሁን ላለው ወቅታዊ ሁኔታ ብዙ ጭቅጭቅ አያስፈልግም።የፋኖ ታጣቂ እጃቸው የገቡ የመከላከያ አባላት ላይ የደረሰውን ሞት አይደለም፣ መቁሰል እያሳዘናቸው እንደሆነ ዛሬ ዘሐበሻ በቪድዮ አስደግፎ ባቀረበው የአንድ የፋኖ አባል ቃለመጠይቅ አሳይቷል። በሌላ በኩል የአንከር ሚድያ ያነጋገረው የመከላከያ አባልም በተመሳሳይ የፋኖ ታጣቂዎች ለኢትዮጵያ ሲደሙ እንደሚያውቃቸው ገልጾ ፈጽሞ የመውጋት ፍላጎት እንደሌለው ገልጿል። አሁን ጥያቄው አንድ ነው።ተጨማሪ የሰው ህይወት ሳይጠፋ፣መከላከያንም ከህዝብ ጋር ደም ሳይቃባ እና ኢትዮጵያ ወደ የባሰ ግጭት ሳትገፋ፣ መንግስት ጉዳዩን በሰላም በመፍታት ኢትዮጵያን ከእርስበርስ ጦርነት የማዳን ታሪካዊ ኃላፊነት አለበት።ጉዳዩን በኃይል ለመፍታት መሞከር በምንም መልኩ ኢትዮጵያን አይጠቅማትም።ከህወሓት እና ሸኔ ጋር ተቀምጦ የተነጋገረ መንግስት በአማራ ክልል ከተነሳው ታጣቂና ፋኖ ጋር ለመወያየት የሚያግደው ጉዳይ ምንድን ነው? ከእዚህ ጽሑፍ በፊት እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከማወጁ በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሃላፊነት በተሰማው መንገድ በአማራ ክልል ለተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ መተግበር የሚገቧቸው ሦስት ተግባራት በሚሉት ሃሳብ ለማቅረብ ተሞክሯል።ይህንን ሊንክ በመጫን ማንበብ ይቻላል።

ለማጠቃለል አሁን ያለው ሁኔታ የሆነ ተአምር ይዞ የሚመጣ መስሎት በስሜት ውስጥ የገባውም ሆነ ብቻ እነእገሌ ይወገዱ እንጂ የሚሉ ሁሉም ጥቅሉን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ብቻ ሳይሆን ከእዚህ በፊት ሃገሪቱ ያለፈችበትን ተመሳሳይ የስሜታዊነት መንገድ ያልተገነዘቡ ኢትዮጵያ በምን ያህል ደረጃ በአካባቢዋ እና በውስጧ ሊያጠፏት የተጠመዱ የፈንጅ ዓይነቶች ካለማወቅ የሚመነጭ ነው።የውስጥ ቁርሾ ይበርዳል።በውስጥ ቁርሾ መከላከያን ማድከም ግን የማይሽር ጠባሳ ለሀገር ጥሎ ይሄዳል። ስለሆነም መከላከያን ማዳን እና አለማዳከም ከፋኖም ሆነ ከመንግስት የሚጠበቅ እኩል ሀገራዊ እና ታሪካዊ ሃላፊነት ነው። ሁለቱም ይህንን ታሪካዊ ሃላፊነት ሊወጡ የሚችሉበት መንገድ ደግሞ ቁጭ ብሎ በመነጋገር ነው።

==================///============






Wednesday, August 2, 2023

በአማራ ክልል የተነሳው አለመረጋጋትን በፍትሐዊ እና ርቱዕ በሆነ መንገድ ለመፍታት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ማድረግ የሚገባቸው ሦስት ተግባራት።




=========
ጉዳያችን
=========

ያለመተማመኑ መናር 

በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ፣ደቡብ ጎንደር፣ጎጃምና ሰሜን ወሎ የፋኖ ታጣቂ ኃይል ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ግጭቶች መፈጠራቸውና አንዳንድ ቦታዎች ላይ ደግሞ ለሰዓታት የተራዘመ የተኩስ ልውውጥ መደረጉ ተሰምቷል። ይህ ድንገት ደራሽ ጉዳይ አይደለም።የእዚህ ዓይነት ህዝባዊ እንቅስቃሴ በድንገት ሊፈጠር እንደሚችል በተለያየ ጊዜ በኦሮምያ ክልል የተፈጸሙት ዘርን መሰረት ያደረጉ ማፈናቀሎች፣የክልሉ ባለስልጣናት ከኦነግ ሸኔ ጋር እየተናበቡ የፈጸሙት ህገ ወጥ ድርጊት ብቻ ሳይሆን ትዕቢት የተሞሉ ንግግሮች ሁሉ ሲሰሙ አንድ ቀን የህዝብ ቁጣ እንደሚያስገነፍል የሚጠበቅ ነው። አሁን በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት በተለየ መልኩ በኦሮምያ ክልል በሚሆነው እና በሌሎች ተለዋዋጭ ጉዳዮች ሳብያ በተለየ መልኩ የአማራ ክልል ነዋሪ የነበረ እምነቱ ተሸርሽሯል። ይህ መሸርሸር ደግሞ ከህወሓት ጋር በፕሪቶርያ ከተደረገው ስምምነት ተከትሎ በርካታ ጉዳዮች ብዥታ ፈጥረዋል። በእዚህ ያለመተማመን እና የጥርጣሬ ስሜት ውስጥ የክልል ልዩ ኃይሎች እና ሌሎች ኢመደበኛ ታጣቂዎች ትጥቅ የማስፈታት ጉዳይ ሲመጣ ያለመተማመኑን ደረጃ በእጅጉ አናረው።

ይህ ዛሬ የተፈጠረው ሊፈጠር እንደሚችል የዛሬ አምስት ዓመት ግንቦት 1/2010 ዓም ጉዳያችን ላይ ''ሰሚ ያጣው የአማራ ዘርን የማፅዳት እኩይ ተግባር ፍትሃዊ የተባለ ጦርነት ሊያስነሳ ይችላል።'' በሚል ርዕስ የወጣውን ጽሑፍ መመልከት ለጊዜው በቂ ነው።አሁን እየሆነ ያለው ባጭሩ ድንገት ደራሽ አይደለም።


 ህዝባዊ እንቅስቃሴው ብሔርተኛ እንቅስቃሴ ነው ወይንስ ኢትዮጵያን የሚል እንቅስቃሴ ነው?

አንዳንዶች የአማራ ክልል ምንም ዓይነት የብሔር እንቅስቃሴ መነሻውን ቢያደርግም፣''አማራ ሁሌ ለኢትዮጵያ የቆመ ነው፣ኢትዮጵያን አይከዳም '' የሚል የተለመደ አነጋገር በተለይ ከአማራ ክልል ተወላጆችም ሆነ ከደቡብ ኢትዮጵያውያን የሚሰሙ አነጋገሮች ናቸው። ሆኖም የፖለቲካ እንቅስቃሴ በራሱ በእንቅስቃሴው ባሕሪ፣ አነሳስ እና የወደፊት አቅጣጫ እንጂ አንዱ ክልል የተለየ ቅዱስ እና ምንም ዓይነት የአክራሪ ብሔርተኞች መነሃርያ የማይሆን ሌላው ደግሞ የተለከፈ ብቻ የሚለው አካሄድ አያስኬድም። የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ከመነሳቱ በፊት በጀርመን የናዚ ዓይነት የከፋ መንግስት ይነሳል ብሎ ቢያንስ በእዚያ ደረጃ የጠበቀ የጀርመን ህዝብም ሆነ የውጭ መንግስታት እንዳልነበሩ ታሪክን በትንሹ በማገላበጥ መረዳት ይቻላል።  ይህ ማለት የአማራ ክልል እንቅስቃሴ ፍጹም ብሔርተኛ እና በአደገኛ ኃይሎች እጅ ውስጥ በአሁኑ ሰዓት ገባ ለማለት አሁን በህዝባዊ እንቅስቃሴ ደረጃ ከመሆን አልፎ አመራሩ ነጥሮ ስላልወጣ እንዲህ ነው እንዲያ ነው ለማለት የማይቻል ቢሆንም እንቅስቃሴው ግን በምንም የመጠለፉ አደጋ ግን መቼም ሆነ መቼ የለም ለማለት አይቻልም። ለእዚህ አብነት የሚሆነው እና ማነጻጸርያ የሚሆነው በሰኔ 3፣2010 ዓም ''የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሰኘ አዲስ ንቅናቄ ባህርዳር ላይ ተመስርቷል።የንቅናቄው እድሎች እና ፈተናዎች ምንድናቸው?'' በሚል የቀረበው ጽሑፍ ስር ድርጅቱ ሊገጥሙት ከሚችሉት ዕድሎችና ፈተናዎች ውስጥ ፈተናዎች በሚለው ስር የሚከተሉት ተዘርዝረው ነበር።እነርሱም ፡ 
  • የከረረ ብሔርተኝነት ያላቸው ወደ አመራሩ ከመጡ ከኢትዮጵያዊነት ጋር አጣጥሞ ለመሄድ የመቸገር ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል፣
  • በህወሓት ሰርገው እንዲገቡ የሚደረጉ ግለሰቦች የሚፈጥሩት አሉታዊ ስዕል በንቅናቄው ላይ የሚሰጠው መልካም ያልሆነ ስዕል እና ከሌሎች ብሔሮች ጋር ለማጋጨት የሚደረጉ ሙከራዎች፣
  • እራሱን በቶሎ ወደ ኢትዮጵያዊ ንቅናቄ ካልቀየረ በከረረ ብሔርተኝነት ስሜት የተመሰጡ አባላቱን ወደ ሃገራዊ አጀንዳ ባለቤትነት ለመቀየር የመቸገር ሁኔታ መፈጠር።የእዚህ አይነቱ ችግር አሁን ህወሓት እራሱ ገጥሞት የሚገኘው ችግር ነው።መግብያ ሲዘጋጅ መውጫው አብሮ መታየት አለበት።
  • በተሰሩ ግፎች እና ጥፋቶች ላይ ከሚገባው በላይ በመዘከር የይቅርታ እና የአንድነት መንገዶች እንዲከፈቱ ማድረግ ካልቻለ አማራን ብቻ ሳይሆን በብሔራዊ ደረጃ ወደ አደገኛ መንገድ የመሄድ አዝማምያ እንዳይኖር ጥንቃቄ ያስፈልጋል።የሚሉ ነበሩ።
አሁን ያለውን እንቅስቃሴ ከስሜት በተለየ በሚገባ ወዴት ሊሄድ ይችላል? ኢትዮጵያዊነት በተመለከተ ኢህአዴግ ውላጅ የሆነው ትውልድ ''አማራ ፊርስት '' የሚል ነው ወይንስ ''ኢትዮጵያ ፈርስት '' የሚል ነው? የሚለው አሁንም መፈተሽ ያለበት ጉዳይ ነው። 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጉዳዩን በኃይል ከመፍታት ይልቅ ማድረግ የሚገባቸው ሦስት ተግባራት።

በእዚህ ጽሑፍ መግቢያ ላይ ለማንሳት እንደተሞከረው በዘመነ ኢህአዴግም ሆነ ባለፉት አምስት ዓመታት በጀዋር መሐመድ ''ስልጣን ይዘናል '' ከሚለው ጽሑፍ እስከ አቶ ሽመልስ ''ሰበርናቸው'' የመስቀል አደባባይ ንግግር፣ከመቶ ሺዎች የወለጋ እና የሸገር መፈናቀል እስከ ፍትሕ ያጡ የደቡብ እና ሱማልያ ክልል ነዋሪዎች ጭምር የብሶቱ ጣርያ ከመጠን ያለፈ ነው። ይህንን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም፣መከላከያም፣ብልጽግናም ካለምንም ማጉረምረ ሊውጡት የሚገባ እውነት ነው። ለእዚህ እውነት እዚህ ላይ መዘርዘር ጊዜ ማጥፋት ነው። አሁን ያለውን ወቅታዊ ጉዳይ ለመተንተን የሚነሳ የመንግስት አካል መነሳት ያለበት ይህንን እውነት ከመቀበል ካልሆነ ቀጣይ የመፍትሄ ሂደቱ ሁሉ የተሳሳተ እና አለባብሶ የመሔድ ከንቱ ድካም ይሆናል። በመሆኑም ይህንን እውነት ጠቅላይ ሚንስትሩም አምነው እና ተቀብለው ወደ መፍትሔ መሄድ ተገቢ ነው። 

ወደ ሦስቱ የመፍትሄ መንገዶች ስንመጣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሚከተሉትን ሦስት ተግባራት በፍጥነት መፈጸም አለባቸው። እነርሱም 

1) የመወቃቀሻ እና እውነቱን የማንጠርያ መድረክ ከአማራ ክልል እጅግ የተከበሩ ሽማግሌዎች፣የሃይማኖት አባቶች፣መከላከያ የኦሮምያ ክልል አመራሮች እና የፋኖ አመራሮች ጋር በፍጥነት መፍጠር።
  • መድረኩ ከውይይት በኋላ ለህዝብ መቅረብ ያለበት ለበለጠ ግጭት የማይዳርገው ክፍል ተለይቶ ነገር ግን ዋና ሃሳቡን ያልጣለ የመወቃቀሻ መድረኩ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥንና ራድዮ በቀጥታ መተላለፍ አለበት።
  • በመወቃቀሻ መድረኩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ከአማራ ክልል ጋር በተያያዘ እና በኦሮምያ ክልል ለሆነው ሁሉ ያሳዩት ለዘብተኝነት ላይ በግልጽ ይጠየቁ፣እርሳቸውም ከእዚህ በፊት ያልሰማናቸውን ጉዳዮች ጨምረው ለምላሽ ይዘጋጁ።ውይይቱ ስሜት የሚነካ እና ፍጹም ግልጽነት የታየበት መሆን አለበት።
  • ሀገር በሆነ ባልሆነው ወደ ግጭት እየገባች የትውልድ ሞት ከሚከተል ለእዚህ ዓይነት መወቃቀስ መዘጋጀት እና ስህተትን ውጦ ለነገ ስህተትን አስተካክሎና መተማመንን በምንም ወጪ ቢሆን ከፍሎ ሀገርን ማስቀጠል ግዴታ ነው። 
  • ስለሆነም ይህ የመወቃቀሻ መድረክ እጅግ በፈጠነ መንገድ ማድረግ ብዙ ችግሮችን ያስወግዳል።
2) በኦሮምያም ሆነ በአማራ ክልል ያሉ አመራሮች በሙሉ እስከ መካከለኛ ድረስ ያሉትን ከባለሙያዎች ውጭ በሙሉ ከስልጣን ማንሳት እና አዲስ ከጎሳ ፖለቲካ አክራሪ የተሻለ አቋም ላይ ያሉትን መተካት።
  • አሁን በሁለቱም ክልል ያሉት አመራሮች በሴራ ሹክቻ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በሙስና የተነከሩበት ደረጃ ማንም ወንጀለኛ የሚነዳቸው ስለሆኑ ያከረሩ የጸብና የግጭት መነሻ ናቸው።
  • በተለይ በኦሮምያ ክልል ያለው ከጎሳ ፖለቲካ መበስበስ አልፎ ፈጽሞ ለማንኛውም ኃይል ተገዢ ብቻ ሳይሆን የመሰረታዊ የኢትዮጵያ ዕይታቸው ከጥላቻ ባለፈ ወደ ፍጹም ፋሺሽታዊ መንገድ እየሄደ በመሆኑ 
  • በቀጣይ ኢትዮጵያ እንድትሄድበት ከሚፈለገው የአንድነት መንገድ አንጻር በሁለቱም ክልሎች ያሉ አመራሮች በብሄር ፖለቲካ የተደናበሩ ስለሆነ እና  
  • ወቅታዊ ችግሩን በአዲስ አሰራር በመቀየር ቁርጠኝነትን የማሳያ አንዱ መንገድ ስለሆነ።
3) የጎሳ ፖለቲካ የመጪዋ ኢትዮጵያ የፖለቲካ አቅጣጫ እንዳልሆነ እና እስከዛሬ የነበረው በህወሓትና ኦነግ የተተረኩት የውሸት ትርክቶች ጉዳይ ምዕራፍ ለመዝጋት ግልጽ፣አሳማኝና ተግባራዊ ስራ መንግስት እንደሚሰራ ጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጽ ብቻ ሳይሆን በቁርጠኝነት የማሳያቸው ጊዜ ከመቼውም ጊዜ በላይ አሁን መጥቷል።
  • እዚህ ላይ ህገመንግስቱ ላይ ያሉት መሰረታዊ ችግሮች ማስተካካል። ሀገር በጦርነት ከሚታመስ ህገመንግስትን በማረም ማስተካከል ተገቢ ነው።
  • በአማራ ላይ፣በኦሮሞ ላይ እና ሌሎችም ላይ ያሉ ጸብ ጫሪ ትርክቶች በወንጀለኝነት የሚያስጠይቁ ማድረግ፣
  • የአኖሌን ሃውልት ከማፍረስ ማናቸውም የጎሳ ቀስቃሽ ንግግር ያደረገ እና የጻፈ በፍጥነት በህግ መቅጣጥ
  • ዲጂታል ጎሳ አልባ መታወቂያ ከታቀደው ጊዜ በፈጠነ መልኩ ተግባራዊ ማድረግ
  • የክልሎች አከላለል ጎሳን መሰረት ያደረገ እንዳይሆን በፍጥነት ተግባራዊ ማድረግ። እዚህ ላይ በፍጥነት የሚለው ቃል የምጠቀመው ዘመን በማርዘም ችግር ከማባባስ ይልቅ በተግባራዊነቱ የኢትዮጵያን ህዝብ ድጋፍ አግኝቶ ሀገር ማቆም ከሁሉ የተሻለው አማራጭ መሆኑ ቢያንስ ያለፉት አምስት ዓመታት አስተማሪ ስለሆነ ነው።
ለማጠቃለል 

የአማራ ክልል ህዝብ በግልጽ መወቃቀስ የነበሩትን ችግሮች በማስተካከል ለጋራ ሕግ አብሮ እንዲቆም ማድረግ ይቻላል። ለእዚህ አንዱ ማስረጃ ክልሉ ካለው ማኅበራዊ ባሕል አንጻር ህግ የማክበር ባሕሉ እጅግ የጠነከረ ነው።እስኪያምንህ ይዘገያል።ካመነህ አብሮ ይዘልቃል።አይቶ አይቶ ካላመነ በቃኝ ብሎ ይነሳል። ያላየበትን መንገድ በቅንነት እና በእንባ ጭምር ስታስረዳው መልሶ ይሰማሃል። አንዴ ከሰማህ በኋላ መልሰህ ስትዋሽ ካገኘህ ግን  ነገሩ አበቃ ማለት ነው። አሁን ያለበት ደረጃ መንግስት ስህተቱን አምኖ ለማስተካከል እድል እንዲሰጠው የማሳመን እና ለገባው ቃል ተግባራዊ እንዲያደርግ እድል ያለበት ጊዜ ነው። አሁን የተፈጠረው መከራ ብቻ አይደለም።ለተሰራው ስህተት ማረምያ፣የጎሳ ኃይሎችን ማስታገሻ አድርጎ ወደ መልካም ሀገራዊ ዕድል መቀየርም ይቻላል።

ይህ ሁሉ ሲሆን ግን ሀገር ገልብጠን፣ ነፍጥ ከመነቅነቅና መከላከያን ከመበተን መለስ ያለ ንግግር እና ስህተትን የማረም ሂደት አያስፈልግም የሚሉ እነ''በለው'' ባዮች አይነሱም ማለት አይደለም። ሆኖም ህዝብ በግልጽ ይመንበት፣ከደም መፋሰስ ይልቅ ስህተትን በማረምና ሀገራዊ አቅጣጫን ከማስተካከል መለስ ያሉ ካልበተን አናርፍም ለሚሉ እራሱ ህዝብ ምላሽ ይሰጣል።ከእዚህ በተረፈ ግን በአማራ ክልል የተከሰተው የጸጥታ ችግር በወታደር ኃይል ለመፍታት መሞከር አይቻልም።ጦርነት ውስጣዊ ስሜት እና ለመሞት እርግጠኛ የሆነ የስሜት ደረጃ ይፈልጋል።መከላከያ ደግሞ ከአማራ ክልል ጋር የሚያደርገው ጦርነት ፈጽሞ ምክንያታዊ አለመሆኑን ይረዳል። በመሆኑም በሙሉ ስነልቦና አይዋጋም። ይህ ማለት ግን መከላክያ ላይ የሚሆነውን ሁሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ይቀበላል ማለት አይደለም። የኢትዮጵያ ህዝብ የመንግስት ኢፍትሃዊ አካሄድ ለችግሩ መፈጠር ምክንያት መሆኑን ስለሚያውቅ መንግስት በይቅርታ እና በማስተካከል ሥራ እንዲጀምር፣በፋኖ ታጣቂ በኩልም በመከላከያ ላይ ምንም ዓይነት ግጭት እንዳይፈጠር በሰላማዊ መንገድ ችግሮችን አንጥሮ በማቅረብ ደረጃ በደረጃ እንዲፈቱ በቅንነት መነሳት ይገባል።ከኢትዮጵያ መታወክ አይደለም ዜጎቿ ጠላቷቿም በሚገባ ቢያስቡት አይጠቀሙም።

==================//////===========







Saturday, July 29, 2023

ወደብ አልባዋ ኢትዮጵያ እንዴት የቀጥታ ወደብ አገልግሎት ማግኘት ትችላለች? አልጅዚራ ''ኢንሳይድ ስቶሪ'' በእዚህ ሳምንት ያስተላለፈው (ቪድዮ)።How will landlocked Ethiopia get direct access to a port? (video)

 Guests:

Kemal Hashi Mohamoud – Member of the Ethiopian Parliament

Martin Plaut – Journalist specializing in the Horn of Africa and a fellow at the Institute of Commonwealth Studies at the University of London

Kwaku Nuamah – Senior lecturer and chairman of the International Peace and Conflict Resolution Program at American University

Aljazeera English Inside story, July 26,2023



Wednesday, July 19, 2023

ልዩ ዘገባ - የግሪክና የኢትዮጵያን ታሪካዊ ግንኙነት ለማጠናከር የሚተጉት የግሪካውያን ማኅበር ለኢትዮጵያ መታሰብያ አቴንስ ላይ ሃውልት ለማቆም እንቅስቃሴ ጀመሩ የቦታ ፈቃድ አግኝተዋል፣ በአዲስ አበባ ከተመሰረተ 113 ዓመታት ያስቆጠረው የግሪክ ማኅበረሰብ (ኮሚኒቲ) ትምሕርት ቤት የተፈጠረው ሁኔታ ማኅበሩ ላይ ትልቅ ቅሬታ ፈጥሮበታል።



አዲስ አበባ የግሪክ ብሔራዊ ቀን ዋዜማ የግሪክ አምባሳደር ኒኮላስ ፓታኪያስ ፎቶ ሲያነሱ።


በእዚህ ጽሑፍ ስር የሚከተሉትን ርዕሶች ያገኛሉ  -
  • የግሪክና የኢትዮጵያን ታሪካዊ ግንኙነት ለማጠናከር የሚተጉት ግሪካውያን ለኢትዮጵያ መታሰብያ አቴንስ ላይ ሃውልት ለማቆም እንቅስቃሴ ጀምረዋል
  • የግሪክ ማኅበረሰብ ትምሕርት ቤት በተመለከተ በኢትዮጵያ መንግስት የተወሰደው እርምጃ ምንድነው? የጉዳዩ የመንግስት የአያያዝ ክፍተት ሦስት ጉዳዮች ምን ምን ናቸው?
  • ከእዚህ በታች የግሪካውያን የኢትዮጵያ ወዳጆች ማኅበር በአዲስ አበባ ግሪክ ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት ላይ ያለውን ቅሬታ የገለጸበት ሙሉ ጽሑፍ በተለይ ለጉዳያችን የላኩትን ዝርዝር የጉዳዩ ዳራ እና ሂደት እና
  • የግሪክ ማኅበረሰብ (ኮሚኒቲ) ትምህርት ቤት በትዝታችን ኢቢኤስ (ቪድዮ)
=============
ጉዳያችን ልዩ ሪፖርታዥ
=============

የኢትዮጵያ እና የግሪክ ግንኙነት ከክርስቶስ ልደት በፊት የነበረ መሆኑ ቢታወቅም በዘመናዊ የኢትዮጵያ ታሪክ ሁለቱ ሀገሮች የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩት በ1917 ዓም እኤአ ሲሆን በቆንስላ ደረጃ የነበረው ግንኙነት ወደ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያደገው ጣልያን ከኢትዮጵያ ተሸንፎ በወጣበት ዓመት 1935 ዓም እኤአ ነበር። በኢትዮጵያ እና ግሪክ ያለው ግንኙነት የተበላሸው የወታደራዊው መንግስት ወደስልጣን ከመጣ በኋላ ነው። በእዚህ ወቅት በርካታ ግሪካውያን በወቅቱ በነበረው የግል ንብረትን ወደ መንግስት የማዞር ጉዳይ ያፈሩት ንብረቶች ተወረሱባቸው።አሁን ድረስ የተወረሱ ንብረቶች ጉዳይ ላይ ጥያቄ ያላቸው ግሪካውያን እንዳሉ ይሰማል። ይህም ሆኖ ግን እንደ ባምቢስ ያሉ ባለሃብቶች በወታደራዊው መንግስት ጊዜም በኢትዮጵያ በንግድ ሥራ ላይ ተሰማርተው ቆይተዋል።

ግሪካውያን ኢትዮጵያን እጅግ ይወዳሉ።ማንኛውም ግሪካዊ ጋር በአቴንስ ከተማ ብታናግሩ ኢትዮጵያን ይወዳል።ከታክሲ ሹፌር እስከ ከፍተኛ የመርከብ ባለቤቶች ባሉኝ አጋጣሚዎች ስለ ኢትዮጵያ በጠየኳቸው ጊዜ ልዩ ክብር እና ፍቅር እንዳላቸው ለመረዳት ችያለሁ። ግሪክ ታላቅ ሀገር ነች። በእዚህ የሉላዊነት ዘመን ግሪክ የገጠሟት ፈተናዎች እና ወደፊት የሚገጥሙ ፈተናዎች ኢትዮጵያ ከገጠማትም ሆነ ወደፊት ከሚገጥማት ጋር ተመሳሳይ ነው።ግሪክን እግዚአብሔር ባይፈጥር ኖሮ የዓለም የሳይንስ ጥበብ ምናልባት አሁን በምናየው  ደረጃ ሊሆን ፈጽሞ እንደማይችል ለመረዳት ዛሬ ከፊዚክስ እስከ ምህንድስና ከግሪክ የተወሰዱ ጥበቦችን መቃኘት ነው።

ግሪካውያን በኢትዮጵያ ዘመናዊ ስልጣኔ ላይ የነበራቸው አሻራ በሚገባ አልተከተበም እንጂ ትልቅ ፋይዳ ያለው ነው። ከአራዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያ ስራ እስከ የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ምስረታ ከጣልያን በፊት የግሪክ ማኅበረሰብ አባላት አሻራዎች ናቸው።ይህ ብቻ አይደለም በህክምና ሙያ ላይ ተሰማርተው ኢትዮጵያን ያገለገሉ ግሪካውያን ያውም ገና ኢትዮጵያውያን ሀኪሞች በሚገባ ሳይሰለጠኑ በነበረበት ዘመን ነው።ለምሳሌ ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ በራሳቸው የጻፉት ''ሕይወቴ እና የኢትዮጵያ እርምጃ'' በተሰኘው መፅሐፍ ላይ የአልጋ ወራሽ እያሉ በዓለማያ ሐይቅ ላይ በጀልባ ሲሄዱ የደረሰባቸው የጀልባ መገልበጥ ተከትሎ በአካባቢው የነበረ ግሪካዊ ሐኪም ደርሶ ባያድናቸው ኖሮ በቀጣይ ዘመናቸው የኢትዮጵያ ንጉስ ለመሆን ላይችሉ እንደነበር በእዚሁ መጽሐፋቸው ላይ ጠቅሰዋል።

የግሪክና የኢትዮጵያን ታሪካዊ ግንኙነት ለማጠናከር የሚተጉት ግሪካውያን ለኢትዮጵያ መታሰብያ አቴንስ ላይ ሃውልት ለማቆም እንቅስቃሴ ጀምረዋል

ኢትዮጵያ የተወለዱ፣በኢትዮጵያ ሰርተው ሀብት ያፈሩ፣በልዩ ልዩ ሙያ ኢትዮጵያን በሙያቸው ያገለገሉ ግሪካውያን አቴንስ ላይ ማኅበር እንዳላቸው ሰምቼ ነበር።ባለፈው ሳምንት ላይ ግን የማኅበሩን አስተባባሪዎች አቴንስ ላይ ለማግኘት ዕድል አገኘሁ። ስለ ኢትዮጵያ ሲናገሩ እንባ ይተናነቃቸዋል። የኢትዮጵያና የግሪክ ታሪካዊ ግንኙነት እና ወደፊት የሚገጥሟቸው ተግዳሮቶችም ተመሳሳይ እንደሆኑ ከተለያዩ አቅጣጫዎች አንጻር አወራን።ከሁሉም ለመስራት ያላቸው የሞራል ዝግጅት ከውስጣቸው በሚወጣ ጥልቅ ስሜት የሚገልጹበት መንገድ እጅግ አስደናቂ ነው።በውይይታችን መሃል አዲስ አበባ ስለሚገኘው እና ከ113 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የግሪም ማኅበረሰብ (ኮሚኒቲ) ትምሕርት ቤት ላይ የተወሰደው እርምጃ እጅግ አሳዝኗቸዋል።በእውነቱም በእዚህ ደረጃ ያለ የሁለት ሀገሮች ግንኙነት የሚመለከት ትምሕርት ቤት የተያዘበት መንገድ በራሱ እዚህ ከፍተኛ ጥያቄ አስነስቷል።

ይህ በእንዲህ እያለ በግሪክ የሚኖሩ ግሪካውያን ኢትዮጵያን የሚያውቁ እና በኢትዮጵያ የተወለዱ ግሪካውያንን ጨምሮ አቴንስ በሚገኘው የአቢሲንያ አደባባይ ኢትዮጵያን የሚያስታውስ ሀውልት ለመስራት ዝግጅት ላይ ናቸው።አቴንስ የሚገኘው የአቢሲንያ አደባባይ ስያሜውን ያገኘው ከሁለተኛ ዓለም ጦርነት ፍጻሜ ሰሞን ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ግሪክ በጦርነቱ ማግስት በተቸገረችበ ጊዜ ንጉሱ በርካቃ የቁም ከብት ገዝተው እና አሳርደው ህዝቡን ያበሉበት ቦታ ነው። ከዚያን ጊዜ በኋላ ቦታውን የአቢሲንያ አደባባይ ተባለ። አሁን ታሪኩ ተድበስብሶ እንዳይቀር ኢትዮጵያን የሚያውቁ ግሪካውያን በቦታው ላይ የኢትዮጵያና ግሪክን ታሪክ የሚያስታውስ እንዲሆን ሀውልት ለመስራት እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
https://www.ellinoethiopic.gr/wp-content/uploads/2023/02/Logo.ellinoethiopic.jpg

የኢትዮጵያውያን ግሪካውያን ማኅበር የተመሰረተው በ1967 ዓም የኢትዮጵያ አብዮትን ተከትሎ ወደግሪክ በተሰደዱ ግሪካውያን የተመሰረተ እና በአሁኑ ጊዜ በአቴንስ ማዕከሉን አድርጎ እየሰራ ይገኛል።ማኅበሩ አቢሲን ያ አደባባይ ሀውልቱ ሊሰራ የታሰበበት ቦታ ከአቴንስ ከተማ ፍቃድ ያገኘ ሲሆን ቦታው ከስር የምትመለከቱት ቦታ ላይ ነው።ለሀውልቱ ግ ንባታ ለማስተዋወቅ የፊታችን እሁድ ሐምሌ 16/2023 ዓም እኤአ በእዚሁ በአቢሲንያ አደባባይ ኢትዮጵያውያንን እና ግሪካውያንን ጠርቶ የነበረ ቢሆንም በሳምንቱ ካለ ሙቀት አንጻር መርሃግብሩን ለሌላ ጊዜ ማስተላለፉን ዛሬ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ መታሰቢያ ሀውልት የሚሰራበት ቦታ አቴንስ፣ግሪክ


ዝግጅቱ ለሌላ ጊዜ ማስተስላለፉን ቀድሞ በለቀቀው ፖስተር ላይ ዛሬ አስታውቋል።


የግሪክ ማኅበረሰብ ትምሕርት ቤት በተመለከተ በኢትዮጵያ መንግስት የተወሰደው እርምጃ ምንድነው? የጉዳዩ የመንግስት የአያያዝ ክፍተት ሦስት ጉዳዮች ምንድን ናቸው?

በአዲስ አበባ የሚገኘው የግሪክ ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት በተመለከተ የኢትዮጵያ መንግስት የወሰደውን እርምጃ በተመለከት አዲስ ማለዳ ጥቅምት 13/2022 ዓም እኤአ ባወጣው ዘገባ ላይ እንዲህ ይላል 
''ትምህርት ሚኒስቴር ለዓመታት ያለ ዕውቅና እና የሚጠበቅበትን ግብር ሳይከፍል ሲሠራ የኖረውን የግሪክ ማኅበረሠብ ትምህርት ቤት፣ ዕውቅና እንዲኖረውና ከተሠጡት ሦስት አማራጮች አንዱን ይዞ እንዲቀጥል ትዕዛዝ መስጠቱን ለአዲስ ማለዳ ገለጸ።

በዚህም፣ የማኅበረሠብ ትምህርት ቤት፣ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት ወይም መደበኛ የግል ትምህርት ቤት ኾኖ እንዲቀጥልና በአምስት ሳምንት ውስጥ አንዱን መርጦ ውሳኔውን እንዲያሳውቅ በግሪክ ኤምባሲ በኩል ለትምህርት ቤቱ ትዕዛዝ እንደተላለፈለት ነው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የገለጸው።

ኾኖም በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ያሉበት የእንግሊዘኛ ክፍሉ (English Section) እንዴት ኾኖ የግሪክን ሥርዓተ ትምህርት ሊከተል ይችላል በሚል ለቀረበው ጥያቄ፣ በሚኒስቴሩ የትምህርት ኢንስፔክሽን ጀኔራል ዳይሬክተር የሆኑት ሙሉቀን ንጋት(ዶ/ር) ማንም የፈለገውን አገር ሥርዓተ- ትምህርት ለመማር ፍላጎት እስካለው ድረስ አይከለከልም የሚል መልስ ሠጥተዋል።

ትምህርት ቤቱ እስካሁን በግሪክ ኤምባሲ ሥር ሆኖ መቆየቱን የግሪክ አምባሳዳር ቀርበው አስረድተዋል ያሉት ዳይሬክተሩ፣ የመማሪያ ቋንቋው ግሪክኛና እንግሊዝኛ ተብሎ ተከፋፈለ እንጂ ኹለት ትምህርት ቤት እንዳልሆነ አምባሳደሯ መናገራቸውን ነው ያስረዱት።
ዳይሬክተሩ ይህን ይበሉ እንጂ፣ ትምህርት ቤቱ ይህን እንደማይቀበልና ከኤምባሲው ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት ኖሮት እንደማያውቅ ለትምህርት ሚኒስቴር ደብዳቤ ጽፎ እንደነበር ከተማሪ ወላጆች የተገኘው ደብዳቤ ያመላክታል።

እስካሁን በነበረው አሠራር ኢንተርናሽናልና ማኅበረሠብ ትምህርት ቤቶችን ለመቆጣጠር የተዘጋጀ የሕግ ማዕቀፍ ባለመኖሩ መቆጣጠር አስቸጋሪ ነበር ያሉት ዳይሬክተሩ፣ አሁን ላይ የግሪክ ማኀበረሠብ ትምህርት ቤትም ሕጋዊ መስመር ይዞ እንዲሠራ ትዕዛዝ እንደተሠጠው አብራርተዋል። በዚህም በተለይ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት ለመሆን ከወሰነ፣ የኢንቨስትመንት ፈቃድ፣ ንግድ ፈቃድ፣ እንዲሁም ከካምብሪጅ የሥርዓተ-ትምህርት ፈቃድ ማምጣት እንዳለበት ጠቁመዋል።

ኾኖም የትምህርት ቤቱ ግሪክ ክፍል ከ100 ዓመታት በላይ፣ የእንግሊዘኛ ክፍሉ ደግሞ ከ25 ዓመታት በላይ በሥራ ላይ መቆየቱን አዲስ ማለዳ አስታውሳ፣ እንዴት የንግድም ይሁን የኢንቨስትመንት ፈቃድ መጀመሪያ አልተጠየቁም በሚል ላቀረበችላቸው ጥያቄ፣ የራሳቸውን ዜጎች ለማስተማር የግሪክ ማኅበረሠብ ትምህርት ቤት በሚል ፈቃድ ካገኘኙ በኋላ፣ በዚህ ሠበብ የኢትዮጵያና ሌሎች አገራት ተማሪዎች የሚማሩበትን የእንግሊዘኛ ክፍል አቋቁመው እንደሚያስተምሩ ሳይታወቅ እንደቆየ ጠቅሰዋል።

አያይዘውም፣ የሚከታተላቸው ቡድን ቦታው ድረስ ሔዶ ትምህርት ቤቱን ካየ በኋላ፣ ኹሉም ነገር በሥርዓት እየተከናወነ ነው ብሎ ለትምህርት ሚኒስቴር ሪፖርት ሲያደርግ እንደኖረ ገልጸዋል።'' የአዲስ ማለዳ ዘገባ መጨረሻ።

የትምህርት ሚኒስቴር እርምጃ አካሄድ ብቻ ሳይሆን የኦሮምያ ክልል በትምህርት ቤቱ ይዞታ ላይ ምን አድርጓል? የሚለው ዝርዝር ጉዳይም በሚገባ መታየት ያለበት ቢሆንም የኢትዮጵያ መንግስት ከኮሚኒቲ ትምህርት ቤቱ አንጻር የሄደበት የአካሂያድ ሂደት በስህተት የተሞላ ነው።እነርሱም 

1/ ማናቸውም የውጭ ዜጎችን የሚመለከት ጉዳይም ሆነ ተቋም መጀመርያ መመራት እና ክትትል እንዲያደርግ ማድረግ የሚገባው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነበር። በእዚህም ከግሪካውያኑ ጋር የሚደረጉ ንግግሮች የዓለም አቀፍ ሕጎችን የሚመለከቱ ስለሚሆኑና የእዚሁ የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሙያዎች ደግሞ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንጂ በትምህርት ሚኒስቴር የሉም።

2/ የትምህርት ቤቱ ጉዳይ የግሪክና የኢትዮጵያን ግንኙነት እንዳያበላሽ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ ነበረበት

3/ በጉዳዩ ዙርያ ከግሪክ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መምከር ይገባ ነበር።በእዚህም ከግሪክ መንግስት ጋር በጋራ ኮሚቴ መስርቶ መከታተል ይገባ ነበር።

ከእዚህ በታች የግሪካውያን የኢትዮጵያ ወዳጆች ማኅበር በአዲስ አበባ ግሪክ ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት ላይ ያለውን ቅሬታ የገለጸበት ሙሉ ጽሑፍ በተለይ ለጉዳያችን የላኩትን የጉዳዩ ዳራ እና ሂደት

ASSOCIATION OF GREEKS OF ETHIOPIA (S.E.A.):

THE GREEK COMMUNITY OF ADDIS ABABA IN DANGER


SUMMARY

With actions and claims of the Minister of Education of Ethiopia, an attempt is being made to convert the English section of the Greek Community Schools belonging to the Greek Community AA into a Charitable Endowment, which means the transfer of ownership of the schools through the Endowment to the Ethiopian State, and the dispossession of the Community's property.  The Hellenic Community AA has established a new organization (INTERNATIONAL SCHOOL) provided for by the legislation to start from the 2023-24 school year and has requested permission. Permission which was not given. It also communicated its intention to close the English section if the form of INTERNATIONAL SCHOOL was not accepted. 

Instead, the Minister has continually smeared Greeks as corrupt, without evidence, to justify his actions and has hastily and eccentrically embarked on the installation of an interim administration of the English section, which has banned entry to the Board members of the Greek Community of AA.  And daily he is practicing a regime of intimidation on the staff, teachers, pupils and parents. It also intervenes in actions that concern the Community and not the English section, such as: opening and using the Community's bank accounts, leaving unpaid 29 employees, racist comments to Greek-Ethiopians to choose whether to be Greek or Ethiopian, attempt to dismiss the Community's lawyers, trying to prohibit the Community's social benefits to people in need of such assistance, accounts are blocked and exit permits to travel abroad to the members of the Boars of HGCA, etc The intervention extends to the Greek section of the GCS (which are under the Greek Ministry of Education) with unpaid staff (Greek Civil Servants) and various prohibitions, etc. Finally, abusing disruptive actions of a small group (Trojan Horses of the community), an attempt is made to change the composition of the Board of Directors of the Community.

https://www.ellinoethiopic.gr/elliniki-koinothta-aa-se-kindyno-2/

 

HISTORICAL FACTS

The Greek Community of Addis Ababa-Ethiopia was founded in 1910. At that time a Primary School was started with donations from the Community members. The Greek-speaking mixed semi-gymnasium of the Community (the first 3 classes of the sixth grade high school) was opened in 1944.  Its recognition by the Greek State was granted in 1947 by the Decree 2, Government Gazette 152/24-07-1947, Vol. 

By the year 1950, all three upper grades were created and thus the semi-gymnasium became a full sixth-grade Gymnasium, which was recognized as equal to the Gymnasiums of the Greece by Decree 5, Government Gazette 177/17-08-1950, vol. The "old" school was built under the presidency of Mr. George Kalogeropoulos and was located in the centre of the town. With a curriculum and teaching staff that came from the Ministry of Education of Greece. These schools were attended by Greeks and Cypriots from Ethiopia and the wider East African region.

The New Greek Community Schools were built under the presidency of Athanasios Michos on a plot of 33,000 square meters. The land belonged to an Armenian named Mena, who had Ethiopian citizenship. And according to the Ethiopian laws of the time, he could not sell to a foreign national without the special permission of Emperor Haile Selassie. With the intervention of the president of the Community, Mr. Athanasios Michos and its treasurer, Mr. Alexandros Ganotakis, permission was granted by the Emperor to purchase the land in the name of the Greek Community of Addis Ababa. A fundraiser was held by the prosperous residents of Addis Ababa, which raised the money for the purchase of the land. The Great Benefactors: Athanasios Mihos, Michael Zekos and Nicholas Diamantas, whose names the school community buildings bear, undertook their construction.  

In 1961, the Community completed the construction of three school buildings within the community's own land, the "Michio High School", the "Zekio Elementary School" and the "Diamanteio Kindergarten".



ΜΙΧΕΙΟ.JPG

MICHIO SECONDARY


ΖΕΚΕΙΟΣ.JPG

ZEKIO PRIMARY


ΔΙΑΜΑΝΤΕΙΟ.JPG

DIAMANTIO
KINDERGARDEN


ΟΙΚΟΤΡΟΦΕΙΟ.JPG.

The Community Boarding School was also funded by the Ministry of Foreign Affairs, when the late Evangelos Averoff was Foreign Minister, following the intervention of Athanasios Michos. In 1961, the building of the Community Boarding School, which at that time housed about 250 students, was completed.

The Community Boarding School is the largest in the African continent and its operating costs have been fully covered by the Community to date, without any financial support.  To the young expatriate students the Community offers accommodation in the Community Boarding School for the duration of their studies in the Community Schools (Primary, Secondary and High School), full board, clothing and medical care.


Olympiakos1.jpg

In addition, the facilities of the Greek Athletic Union "Olympiacos" were built on part of the land, with benefactor and under the presidency of Mr. Ioannis Velissariou.  

With the great exodus of the community, especially in 1975-76, when the dictatorial military regime of Derg took over, the Greeks were forced to leave Ethiopia, losing their properties. The schools, however, continued to function with the few remaining students. 

Since 1985 an English section has been established and has been operating successfully alongside the Greek schools, with approximately 1,000-1,300 foreign students of about 52 nationalities (initially non-Ethiopians and children of diplomatic and administrative staff of African and other countries based in Addis Ababa), who are taught Greek from grade 1 to grade 6 . Later, the Ethiopian Ministry of Education allowed Ethiopian students to enroll as well. The English School section is considered one of the best in the Ethiopian capital.


ΚΑΛΟΓΕΡΟΠΟΥΛΕΙΟ.JPG

In the English section, the English curricula of the University of Cambridge, which has recognised the Greek Community School as an official examination centre for the IGCSE, A/S and A-levels international diplomas, are applied

In 1997, the English section moved into the new building, a gift of the then President of the Greek Community of Addis Ababa, Mr. Konstantinos Kalogeropoulos.

THE PRESENT SITUATION

Within the land of the Greek Community Schools (GCS) two schools are operating. The Greek section, which is under the Greek Ministry of Education and the English section which operates under a permission of the Ethiopian Ministry of Education. Both under the responsibility of the HGCA. 

The Ethiopian Ministry of Education issued ne guidelines for the operation of International and Community schools in March 2021, with the aim of increasing control over them.

At the same time (July 2022) a new Administration (Board of Directors) was elected in the Greek Community of AA, with a mandate to clean the mess of previous administrations.

In order to renew the schools' license, the Ethiopian Ministry of Education asked the Community to create a new legal entity which will manage the English section School and to which the Community will endow the school buildings. 

During the year the Greek Community of AA, reported that it did not accept the form of Charitable Endowment and proposed the INTERNATIONAL SCHOOL format which is one of the 4 forms of schools that the Ethiopian Ministry of Education allows to operate. It also informed, as of February 2023, the Ministry in this regard that it has fulfilled all the conditions required and requested that the INTERNATIONAL SCHOOL be opened from the 2023-24 school year. Finally, the Greek Community of AA prominently stressed that if the permit for the INTERNATIONAL SCHOOL was not granted, it preferred to close the English section School, which is its sovereign right as the owner of the GCS. 

The current situation is the result of the actions and demands of the Minister of Education, Professor Berhanu Nega PhD., calling for a change of the Board of Directors, of the English School, now composed of members of the Greek AA Community, so that the school is run by a state-affiliated body, in order to install its own board.

In one of his documents, the Minister announced that he would take over the Greek Schools, install an administration of his personal choice, which administration would transfer the Greek Property to a Charitable Endowment which would be controlled (as the law requires for these legal forms) by the Ethiopian State, i.e. a usurpation of the Community's property.

EktaktiEidisi.jpg

The Greek Ambassador arrived on the spot, trying to find out who ordered this occupation. The entire Board of Directors of the Greek Community AA, Residents, Parents of children, employees of the Community protested. The armed police ordered those present to leave. The threat of force is a serious violation of the human rights of diplomatic institutions.

The Minister's response was that they had to accept his terms by 31/03/2023, or else he would proceed unilaterally. So by a verbal notice issued by ACSO (the department of social organisations) and the Department of Education announced that it would proceed with the appointment of an Interim Administration that will lead to a Charitable Endowment.

 

 Asfal.metra (2).jpg

The Minister's response was that they had to accept his terms by 31/03/2023, or else he would proceed unilaterally. So by a verbal notice issued by ACSO (the department of social organisations) and the Department of Education announced that it would proceed with the appointment of an Interim Administration that will lead to a Charitable Endowment.

 


fed.police-gcs.jpg.

The entire Board of Directors of the Hellenic Community of AA, Parishioners, Parents of children, Community employees and the Greek Ambassador arrived on the scene, trying to find out who ordered this occupation. The Ambassador and other members of the Community Board as well as those present inside the Greek Community office entrance area were threatened by the armed men who armed their Kalashnikovs demanding that they leave. The incident was captured on video and the threat of violence is a serious breach of diplomatic rules.


gc-aa4.jpg

On a daily basis in the following days, community members attended the premises on a daily basis, preserving Community property. The Greek Foreign Ministry and other authorities were contacted, TV channels and Radio Stations were alerted, and together with residents, parents and students demanded the removal of the federal police.

 

And while awaiting the injunction decision of 14/06/2023, the Minister called the parents and threatened them not to endanger their children as on 14/06/2023 he would enter with a strong federal police force to implement the installation of a new interim administration. Which he did without resistance as the community and parents fearing bloodshed did not line up at the entrance. Following the unacceptable actions of the Minister of Education to appropriate the Addis Ababa Greek Community school complex by attempting to arbitrarily change the board of directors which was made up of members by the Greek Community of AA, actions for which the Greek Community of AA has taken to the courts and the case is pending.

 

The interim administration intervenes in actions concerning the Community and not the English section, such as: opening and using the Community's bank accounts, racist remarks to Greek-Ethiopians to choose whether to be Greek or Ethiopian, attempt to dismiss lawyers and other Community staff (chief of staff, accountants, etc.) an attempt to prohibit the social benefits of the Community to 83 expatriates and people over 65 in need of such assistance, taking care of Greek religious properties: Church, Cemetery, the Greek Archbishop’s residence some of which have unpaid utility bills (power & water supplies) etc. Finally, through the divisive actions of a small group (Trojan Horses of the community), it tries to change the composition and control the Board of Directors of the Community.

 

The interim administration also started interfering in the Greek section of the GCS, which is out of its jurisdiction. Several teachers of the Greek section (Greek civil servants), are facing a situation whereas their salaries and other benefits are not paid. They are also facing expulsion from teachers’ chambers in GCS, while their travel to Greece for family re-union are not allowed.

 

The interim administration issued several orders: banning members of the Greek Community of AA Board from entering, prohibiting faculty and administrative staff from discussing anything related to the situation (under penalty of expulsion), and announced that it would soon install the Charitable Endowment administration with individuals appointed by the Department of Education, the Ministry of Justice, the Ministry of Finance, the Ministry of Women's Social Affairs, the Greek Community School Parents' Association, and the Greek Athletic Association "Olympiacos", placing in this position its vice-president. Thus the real owner, i.e. the Greek Community AA, which was elected by the 147 members that make up the Community, is excluded, and the Minister "rewards" the unrecognized and separatist Greek Community Organization Aid Idir, which was created by the 8-member administration of the Greek Athletic Association Olympiacos 11 months ago to be an alternative solution as a "Trojan Horse" in the hands of the Minister, by people who oppose the Greek Community of AA. They even tried to appropriate the Diplomatic car of the Embassy that was on the site.

apagoreysi.jpg  

The interim administration also said the employees over-65s will be expelled. Threats are still being hurled at anyone (teachers, parents, students, or members of the Hellenic Community of AA administration) through the mass media or social media networks who refer to the current situation. Orders were given to break into the offices of the Community. This constitutes a regime of intimidation and is not consistent with human rights and academic freedom principles that accommodate school institutions. Community lawyers were "fired" i.e. deprived of the Constitutionally guaranteed right to legal defense.

 

The interim administration for the English Department of the school, appointed by the Minister of Education, has issued a document denying access to the members of the Community Board because they are "obstructing" their work.  (document opposite).

 

More broadly, the whole affair is said to be related to intra-governmental power struggle between the tribal parties that make up the current federal government of Ethiopia, with the current Minister of Education wanting to raise his "stock", saying that he "brought" a significant fortune to the Ethiopian state.  

He is said to have the same plans for the French, German and Italian schools. 

The situation that has been created does not reflect the almost two centuries close cooperation and friendship between Greeks and Ethiopians in the latest period. The two proud Nations met each other for thousands of years and build up co-operation of mutual respect and trust specially because Greeks were never a colonial force. Needless to recall that the very name of the Country derives from the ancient Greek Homeric word Aethiops.  These relations have deep roots in the official (i.e. adopted by the then kings) Christianization of Ethiopia by St. Frumentius or Abu Salama, the help of Greeks in important moments in Ethiopia (1896 Battle of Adwa, 1936 Mussolini invasion), the significant help of Negus Tafari for the Asia Minor disaster (1923 Abyssinia Square) and the care of orphans of the Asia Minor disaster and World War II, etc. The Greeks participated in important developmental public works: the construction of monuments and important buildings, Banks, Hotels, the building of the railway, etc. In addition, they had made significant investments in the economy (coffee, mills, viticulture, textile industry, building materials, etc.). Greeks were also active at assisting the Nation during the Great Famine that struck Ethiopia. Relationships that, among other things, continue to this day with the existence of a large Ethiopian community in Greece, the construction of a monument in the Abyssinia Square in Athens, the studies of Ethiopians in Greek Universities, the provision of scholarships for postgraduate studies in Greece with the support of the Greek Diocese of Axum, the special relations with the Greek Church (provision of churches, studies of the Ethiopian clergy in Greece), with cultural exchanges (performance of "Socrates barefoot" at the Herodes theater (under Acropolis), with the participation in the Ethiopian Film Festival, with bilateral trade forums, etc. 



Greek.School.in.uphill.with.Gvt.jpg

 A question has already been submitted to the European Commission by the Member of the European Parliament of the New Democracy Party, Mr. Man. Kefalogiannis, asking the European Commission whether "it has been informed about the events in Addis Ababa" and "what actions it intends to take to avoid the obvious intention of the Ethiopian government to appropriate the school complex of the Greek Community, which was acquired by the Greek Community and is its property". 

Lideta.Court.Decission.jpg

Ledeta (2).jpg 

.The long-awaited decision of the Lideta Supreme Court  was finally delivered on    24 May 2023.

Notable features of this decision are the reference to "confiscation" only on suspicion of mismanagement and without evidence. A global legal prototype. And secondly the  replacement  

of the notorious splitter (it seems those who used him realized his negative role). The Greek Community of AA has stated that it is continuing the legal process and will challenge all these decisions. 

The Association of Greeks of Ethiopia (S.E.A.) stresses that the uninterrupted cooperation with the Ethiopian Community organizations in Greece must continue, and that the friendly relations and feelings towards them and Ethiopia nurtured by the expatriate former Greek community of Ethiopia in Greece or elsewhere should not be disturbed, contrary to the current situation towards the HGCA in Ethiopia.

Interim-Meeting-Staff.jpg

 It is disgraceful the fact that the Nationals and persons of Greek origin living today in Ethiopia, after more than two centuries of presence of Greeks in your Country, are not any more equally treated, and in fact they are “threatened and discriminated”. This was recorded by an incident that took place on the 29th of June 2023, when Mr Getachew Tefera, Representative of the Minister of Education and Chairperson of the IAB, in the presence of all school staff, employees and a number of parents, humiliating and threatening the Greek Ethiopians working and teaching at the Greek Community School saying (word by word): “If you the Biracial/Metis wish to remain and work here, you must take off from your soul and spirit anything Greek that you still carry in you”. Such Racist Declarations have caused serious anxiety among our compatriots of mixed race. We expect that proper measures are taken.

In addition, following  two Verbal Notes were sent by the Ministry of Foreign Affairs of Greece to the Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia (the last given on the 5th of July 2023), the appeal is made  to achieve a just and swift resolution, permitting the survival of the Greek Community, the wellbeing and respect of the Greek Nationals in accordance to the International Human Rights Declaration and the EU – Ethiopian (African) Bilateral Agreement.

The Association of Greeks of Ethiopia (S.E.A.) will support with every legal means the struggle of the Greek Community of Addis Ababa for the prevention of the expropriation of the property of the Greek Community by the unacceptable actions of the Ethiopian Minister of Education and individuals who act as a "Trojan Horse" aiming at the property of the Greek Community of Addis Ababa and the Greek Athletic Union "Olympiacos". This property was created by the contributions of the Greek expatriates of Ethiopia and the 5 benefactors, and belongs to the tradition of all. 

Hellenic.Community.School.of.Addis.Ababa.jpg   

 S.E.A. calls on to the Greek expatriates of Ethiopia their friends and relatives everywhere to react, to sign the petition (https://chng.it/D5cWGVJGKh), to address authorities of the place where they reside and to denounce the injustice and illegality against the Greek Community of AA. To cooperate with the Greek Diaspora and Ethiopian organizations abroad to express their protest. 


https://www.ellinoethiopic.gr/wp-content/uploads/2023/02/Logo.ellinoethiopic.jpg


S.E.A. calls on to the Greek expatriates of Ethiopia their friends and relatives everywhere to react, to sign the petition (https://chng.it/D5cWGVJGKh), to address authorities of the place where they reside and to denounce the injustice and illegality against the Greek Community of AA. To cooperate with the Greek Diaspora and Ethiopian organizations abroad to express their protest. 


=====================////======================

PUBLICATIONS

 

PETITION:   https://chng.it/D5cWGVJGKh

 

https://www.ellinoethiopic.gr/petition-stop-the-ministry-of-education-of-ethiopia-to-take-over-illegally-the-greek-community-school/diafora/ 

 

https://www.capitalethiopia.com/2023/06/12/greek-community-school-in-uphill-discord-with-govt/

 

https://www.protothema.gr/greece/article/1381726/aithiopia-agonia-gia-to-mellon-tou-ellinikou-sholikou-sugrotimatos/

 

https://eleftherostypos.gr/ellada/se-kindyno-to-elliniko-scholeio-tis-aithiopias-ti-ekane-i-kyvernisi-tis-antis-abeba/

 

https://www.vimanews.gr/epikairotita/απαράδεκτες-ενέργειας-της-κυβέρνησ/

 

https://www.triklopodia.gr/ο-ελληνισμοσ-τησ-αιθιοπιασ-σε-μεγάλο-κ/

 

https://www.ellinoethiopic.gr/elliniki-koinothta-aa-se-kindyno/

 

https://www.ellinoethiopic.gr/elliniki-koinothta-aa-se-kindyno-2/

 

https://hellenic-diaspora.net/el/greek-diaspora/afriki/502-i-elliniki-koinotita-addis-ampempa-aithiopias-se-kindyno/

 

https://hellenic-diaspora.net/en/greek-diaspora/africa/503-petition-stop-the-ethiopian-government-trying-to-take-over-illegally-the-greek-community-school

 

https://www.youtube.com/watch?v=3jTuxUg-cQU

 

https://www.defence-point.gr/news/epeigon-ypopsin-ypex-o-aithiopikos-stratos-gyro-apo-to-elliniko-scholeio/

 

https://www.facebook.com/groups/ellinoethiopic.events.actions/permalink/3324500897799234/

 

https://www.facebook.com/groups/134006380116/

 

https://www.facebook.com/100010888398952/videos/1148264453230625/

 

https://www.facebook.com/groups/134006380116/permalink/10167753562555117/

 

https://www.facebook.com/reel/939807277232961/

 

https://www.facebook.com/groups/2205023582/permalink/10160056195548583/

 

https://www.facebook.com/groups/ellinoethiopic.events.actions/permalink/3343095552606435/

 

https://www.hrw.org/africa/ethiopia

 

https://www.sofokleousin.gr/kefalogiannis-se-ee-aparadektes-energeies-tis-kyvernisis-tis-aith

 

«APOGEVMATINI» newspaper of Constantinople, 20/06/2023

 

 

 

 

 

 

 

''አክቲቪዝም ከጆርናሊዝም'' የደባለቀባቸው ዩቱበሮች በአማራ ክልል የሚፈሰው የመከላከያ እና የአማራ ክልል ህዝብ ደም አልታያቸው ብሏል። በኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሊባሉ ይገባል።

የሰው ደም እየፈሰሰ መከላከያና የአማራ ክልል ታጣቂ ኃይል አይነጋገር የሚሉት በውጪ ሀገር ሶፋ ላይ የተቀመጡት መሆናቸውን ልብ ይሏል። የሰላም ንግግሮችን ለማጣጣል የሚሞክሩትን አጥብቀን መቃወም ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታችን ...