ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, October 28, 2022

A Loud and Clear Lesson – For Ethiopia and the World

ዓለም እና ኢትዮጵያ (ከምዕራቡ ዓለም የሰሞኑ የሽብርተኛው ህወሃትን መደገፍ) ትልቅ ትምሕርት ይውሰዱ! በሚል የእንግሊዙ ጸሓፊ ዛሬ ያወጣው ሙሉ ጽሑፍ በርካታ ጉዳዮችን ይዳስሳል።
  • Without US support — militarily and politically — the TPLF would have been unable to wage war on the Ethiopian State.
  • No US support no war
===============
The British writer - Graham Peebles
      October 28/2022
================

First things first: as I write so-called peace talks are underway between the democratically elected government of Ethiopia and The Terrorist TPLF. That in itself is a bizarre sentence, and prompts an array of related questions, and issues around law and order, justice, national governance. To be clear, the TPLF have never wanted peace, and are not in South Africa (where the talks are taking place) to find a way to end the conflict that they started and perpetuated for two long and deeply painful years. They want power, they have engaged in talks because they have been defeated, but talks about what?

Holding hands with the TPLF men at, or more likely, under the table — out of sight — are US/UN ‘observers’. The reason for their attendance is, one assumes, to ensure TPLF bosses are kept out of prison and allowed to slip away in the night and find amnesty somewhere. Canada has been mentioned as a possible destination, although why the Canadians (or anyone else in fact) would want them is a mystery. A cell in the Hague would be my choice as they eke out their days waiting to be tried in the International Criminal Court.

In the days and weeks leading up to the negotiations, the Ethiopian National Defence Force (ENDF) has taken control of remaining towns in Tigray, including the capital Mekelle, and the fighting appears to have subsided. The only thing left to negotiate, then, is what to do with the TPLF leaders; this is not a difficult conundrum that requires hours or diplomatic chit-chat, and foreign advisers. They, the TPLF are terrorists, and should be treated in the same way that say, ISIS commanders would be, i.e., like criminals — arrested, imprisoned and tried. Their foreign assets (they stole an estimated $30 billion when in office) frozen and seized, and the monies utilized to fund rebuilding work.

The TPLF may have a few members of the “international community” rubbing up against them in Pretoria, but the Ethiopian government sits proud with millions and millions of Ethiopians and friends of Ethiopia packed into the room, and they are roaring! Wide-ranging support for the government, and love for their countrymen and women, of all ethnic backgrounds, was displayed on 22 October, when, in cities throughout the land people, young and old, assembled, marched, sang and danced. Massive crowds demanded an end to foreign intervention in the internal affairs of the nation, and wrapped their arms around the government as it prepared for the African Union convened ‘peace talks’.

No US support no war

Throughout their destructive 27 year reign, the TPLF worked relentlessly to divide communities; systematically setting ethnic groups, that had for generations lived together harmoniously, against one another. But nothing unites a nation more than a shared enemy, and Ethiopia has had two since November 2020 – the TPLF and America/The West, three if we include corporate media. The people are now united, and that sense of fellowship includes the people of Tigray – all are Ethiopians, all share the pain of the nation and all long for peace. The TPLF is the enemy, the US is the enemy, corporate media is the enemy, not Tigrayans.

Without US support — militarily and politically — the TPLF would have been unable to wage war on the Ethiopian State; no war, no death, no rape, no displacement of persons, no destruction of property burning of land, killing of livestock, no national trauma. The US is not simply complicit in the terrorism carried out by the TPLF over the last two years, and indeed during their 27 years in office, they are the enabler. The US Policy of Aggression and Derision directed against the Ethiopian government and the people, the economic sanctions, against one of the poorest nations in the world, the conspiring and duplicity, the misleading briefings and media dis/misinformation campaign emboldened the TPLF and granted them false legitimacy.

And where the US goes her allies and puppets, follow, including corporate media, which has been integral to the mis-dis information campaign, as have, somewhat bizarrely, the US Holocaust Museum, which has recently joined the party. And as talks go on these forces of duplicity and confusion continue to treat the TPLF as if they were an equivalent party to the government, rather than the monsters they are. It is shameful, but when truth and facts become a matter of opinion to be spun according to motive and self-interest it is extremely dangerous. Groups like the TPLF can only exist in the shadows, within Caves of Deceit; throw the light of truth upon them, and like the Many Headed Hydra, they shrivel up and die.

Looking for real friends

The US-supported war in Ethiopia has revealed, if demonstration were needed, in the most vivid manner, the fabric of US foreign policy and where American/Western loyalties lie. Unsurprisingly it’s with their own vested interests, or what they perceive these to be; geo-political reach, regional power, no matter the cost — human, environmental and/or social.

So, the lesson loud and clear, and perhaps this is something worth articulating in Pretoria, is the realization that, the US and ‘the West’ more broadly, including media and some institution are not to be trusted. This fact and the hurt caused by what Ethiopians rightly regard as a betrayal, will no doubt influence how Ethiopia moves forward, who it sees as ‘friends’ and allies, where it looks for support, and who it can trust and depend on.

Outrage has been felt, not just in Ethiopia but across Africa, both at the terrorist attack on their neighbour, and the response of the US/West. This will strengthen pre-existing suspicions and further energise Pan Africanism, already strengthened in recent years, and foster greater unity across the region and continent.

African nations have long been exploited by colonial powers, post-colonial institutions — the International Monetary Fund, World Bank etc, and imposed financial systems (the scandalous Structural Adjustment Programmes e.g.), which, while masquerading as ‘aid’ and/or ‘development programmes’, have ensured countries remain more or less poor, dependent and therefore malleable.

Former colonial bodies of repression and violence (US, European countries, UK), are now in crisis themselves. Economic and political instability, ideological failure and cultural insecurity abound. And as the socio-economic model that has dominated policy making (including foreign affairs) for decades disintegrates in front of our eyes, politicians, lacking humility and vision, wedded to the past, have no answers and continually stack failure upon failure.

The legacy of the global Neo-Liberal experiment is deeply divided societies of largely unhealthy people, and a man-made environmental catastrophe. Mental health illness is at epidemic proportions and climate change/ecological breakdown caused by reckless consumerism threatens the very survival of the race.

A development model, shaped around the same socio-economic paradigm that has caused the chaos has been forced on Ethiopia and all Sub-Sharan African nations. Countries are not seen as nation states with rich individual cultures, but potential marketplaces and natural resource banks.

The model is inherently unjust, benefitting a few at the expense of the many, and is made more so when applied to so-called developing nations (such terms, like the ideals they refer to and the divisions they strengthen should be consigned to the past). It is a corrupt model that, as Ethiopia moves forward and African nations look increasingly towards one another, needs to be closely examined, and in the light of need, not exploitation and profit, re-defined.

Discussions around theses issues, as well as the nature of development, democracy, environmental concerns and regional/continental unity can slowly begin to be taken up, nationally and regionally. Platforms for debate and participation established throughout the country and a vibrant space created in which people from all ethnic groups can contribute. For now though, as Ethiopia gently emerges from the violent shadow of the TPLF, united but scarred, the focus must firstly be on healing and re-construction.

Many will be traumatized and recovery will take time; the rebuilding work will be immense (construction/repair of schools, health services, housing etc), and government will require substantial support, both financial, technical and practical.

But there is no limit to what can be achieved by a united populace, building upon a platform of peace and brotherhood. The people are resolute, weary yes, but strong, supportive of one another and deeply kind, and this is potentially (we must add that caveat), the beginning of a new chapter in the life of the country. An ancient nation with a rich diverse culture that has suffered much and for far too long; a new day, quiet and full of joy let us pray, a time free from conflict and the vile poison of the TPLF.

========

Graham Peebles is a British freelance writer and charity worker. He set up The Create Trust in 2005 and has run education projects in Sri Lanka, Ethiopia and India.  E: grahampeebles@icloud.com  W: www.grahampeebles.org

=========

You can read also read the above article on counterpunch.org

=======

Gudayachn

========

Sunday, October 16, 2022

ወቅቱ በውጪም ሆነ በሃገር ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያውያን የባዕዳን መግቢያ ቀዳዳዎችን መድፈን ላይ ማትኮር የሚገባቸው ወሳኝ ጊዜ ነው።


=========
ጉዳያችን ምጥን
=========

ኢትዮጵያን ለመበተን የአጭር እና የረጅም ጊዜ ዕቅድ ይዘው የተነሱባት ጠላቶቿ ዛሬም ከግማሽ ክፍለዘመን በላይ የዘለቀ ዕቅዳቸውን ለማሳካት እየሮጡ ነው። ኢትዮጵያውያን የሚዘናጉበት ጊዜ አይደለም። እያንዳንዱን ክስተቶች በኢትዮጵያ ላይ ያላቸውን ዘለቄታዊ አደጋዎችን በደንብ የመረዳት አቅም ከሚድያዎች ጀምሮ እስከ እያንዳንዱ ዜጋ ድረስ ያስፈልጋል። ስለሆነም ወቅታዊ ሁኔታዎችን በሚገባ መትሮ የመረዳት አቅምን በተለይ ለአዲሱ ትውልድ ማስታጠቅ ያስፈልጋል።

ኢትዮጵያን እየወጉ ያሉት ባዕዳኑም ናቸው

በትግራይ ከሽብርተኛው ህወሃት ጋር የተደረገው ጦርነት ሙሉ በሙሉ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር የተደረገ ጦርነትም ጭምር ነው።ግብጽ ለህወሃት ከሁለት ሚልዮን ዶላር ከመስጠቷ በላይ የጦር መሳርያዎች እና ሌሎች የሎጀስቲክ ድጋፎች ማድረጓ በቅርቡ የወጣው አዲስ መረጃ አመልክቷል።ከእዚህ በተጨማሪ በየሁለት ሳምንቱ ግማሽ ሚልዮን ዶላር ለህወሃት ሽብርተኞች እየተከፈለ እንደሆነ ነው መረጃው የሚያመለክተው።ከእዚህ በተጨማሪ አድሏዊ በሆነ የፕሮፓጋንዳ እና የዲፕሎማሲ ድጋፍ እንዲሁም የሳተላይት መረጃዎች የሚሰጡ አንዳንድ የምዕራብ ሃገሮችን ጨምሮ ጥቅማችንን ያስከብራል ለሚሉት ለህወሃት የውክልና ጦርነት ድጋፍ እየሰጡ መሆናቸው የአደባባይ ምስጢር ነው።

ከላይ የተጠቀሱት ሁሉ በኢትዮጵያ ላይ ተወርውረውም የኢትዮጵያ ህዝብ ባሳየው ቁርጠኝነት፣የመከላከያ እና የጥምር ኃይሉ ተጋድሎ ህወሃት ከባዕዳን ጋር ገጥሞ በኢትዮጵያ ላይ የቃጣውን ወረራ በሚገባ ተቀልብሷል። በአሁኑ ጊዜ የትግራይ ህዝብ ከህወሃ ነጻ ለመውጣት ዋዜማው ላይ ይገኛል።ይህ ማለት ግን ሥራዎች ሁሉ አብቅተዋል ማለት አይደለም።የኢትዮጵያውያን (በውጪም ሆነ በውስጥ ያሉ) ከመቼውም ጊዜ በላይ ለኢትዮጵያ የሚቆሙበት ጊዜ አሁን ነው።

ኢትዮጵያ እየተዋጋች ያለው ከሽብርተኛው ህወሃት እና ሸኔ ጋር ብቻ አይደለም።እነርሱ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ወይንም ለማዳከም እንዲረዱ ከመደገፍ ባለፈ ዋና ዓላማው የኢትዮጵያን አንጡራ ሃብት ለባዕዳን የሚያስረክብ ለእጅ አዙር ቅኝ አገዛዝ የተመቸ መንግስት አራትኪሎ ላይ ማቆም ነው።በአፍሪካ የምሥራቅ አፍሪካን መሪዎች ጨምሮ በቀጥታ ለአንዳንድ የምዕራብ ሃገሮች የሃገራቸውንም ሆነ የጎረቤቶቻቸውን የማዕድን ሃብት ለባዕዳን ኩባንያዎች በማቀበል የስልጣን ዘመናቸውን የሚያራዝሙ ናቸው።ለእዚህም የኮንጎ የሰላም እጦት አንድ መነሻ ይሄው መሆኑን መጥቀሱ እና ለሰላሟ መጥፋት እና ማዕድኗን እያዘረፉ ለባዕዳን አንዳንድ የምዕራብ ኩባንያዎች በማቀበል የሩዋንዳ እና የዩጋንዳ መንግስታት ይታማሉ።የሽብርተኛው ህወሃትን ለመደገፍ ተፍ ተፍ ሲሉ የነበሩ አንዳንድ የአፍሪካ መንግስታት ታይተው የነበሩት መንግስታቱ ሲመሰረቱም የአፍሪካን አንጡራ ሃብት በማስመዝበር ብቻ የስልጣን ዘመናቸው ስለሚራዘም ነው።ኢትዮጵያ ከእዚህ ሁሉ ጋር ነው አሁን ገጥማ የምትገኘው። ሽብርተኛው ህወሃትም ኢትዮጵያን ለመሸጥ የሚሮጥበት ደረጃ በእዚህ ያህል የከፋ መሆኑን ማወቅ እና ከጀርባው ያለው የቀጥታ እና የእጅአዙር ቅኝ አገዛዝን ማስፈን ይህ ካልሆነ ግን ሃገሩ ተበትኖ ባዕዳን በቀጥታ የሚገቡበትን መንገድ ማሰላሰል ነው የተያዘው። 

የውስጥ አጀንዳ ፈልፋዮች

የኢትዮጵያን ጉዞ ለማደናቀፍ እና ከውስጥ ለመቦርቦር በአገር ላይ ከሚሸረበው ተንኮል አንዱ አጀንዳ ፈጥሮ ህዝብን ከመንግስት ጋር ማጣላት ነው።በእዚህ ሂደት ደግሞ ከሽብርተኛው ህወሃት ጀምሮ መተዳደርያቸው የጎሳ ግጭት እንዳይበርድ የሚፈልጉት እና በኦፌኮ እና ሸኔ ስር ያሉ ሁሉ ከኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር እንደሚሰሩ ከድርጊታቸው እና ከአጀንዳዎቻቸ ሁሉ ለመረዳት ቀላል ነው። ይህ ብቻ አይደለም በአማራው ማኅበረሰብ ስም ከሚነግዱት የዩቱበር ተዳዳሪዎች እስክ ሌሎች የማኅበራዊ ሚድያ አቀንቃኞች ሁሉ ኢትዮጵያውያንን የሚከፋፍሉ አጀንዳዎች ለመፍጠር እና ለማሰራጨት ከሚሞክሩት ውስጥ ናቸው።በመሆኑም የውስጥ አጀንዳ እየፈጠሩ ኢትዮጵያውያንን ለመከፋፈል የሚፈልጉትንም ሆነ የባዕዳንን ጣልቃ ገብነት ለመቋቋም ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ሊሰሯቸው የሚገቡ ሥራዎች አሉ።

ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች አሁንም መስራት ያሉባቸው ወቅታዊ ሥራዎች ውስጥ 

በመሆኑም ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በቀጣይ ከባዕዳን የሚሰነዘሩትን ማናቸውም የፕሮፓጋንዳ እና የተጽኖ መፍጠር ሙከራዎችን እና የግጭት አጀንዳ ለመፍጠር የሚደረጉ ሙከራዎችን ለማክሸፍ ዛሬም ወገባቸውን ጠበቅ ማድረግ ሊሰሯቸው ከሚገቡት ሥራዎች ውስጥ -

  • በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የዲፕሎማሲ ዘመቻውን መቀጠል።በተለይ የአሜሪካ የምክርቤት ምርጫ ከመድረሱ አኳያ ኢትዮጵያውያን ተጽዕኖ የሚፈጥሩበትን መንገድ እንደገና ማንቀሳቀስ፣ተከታታይ ሰልፎች በማድረግ በውጭ የሚኖረው ቀረጥ ከፋይ ህዝብ የራሳቸው መንግስት የሚሰራው የተሳሳተ የውጭ ፖሊሲ ማሳወቅ።

  • አዲስ አጀንዳዎች በኢትዮጵያ ጠላቶች ሲፈጠሩ አጀንዳዎቹን በሚገባ ሳይረዱ ከስሜታዊነት መራቅ እና ወቅታዊውን የኢትዮጵያ ሁኔታ ባገናዘበ መልክ መረዳት፣ከአጀንዳዎቹ ጀርባ ያሉትን የኢትዮጵያ ጠላቶች ፍላጎት መረዳት።

  • በርካታ የዜና ዩቱቦች እየተከፈቱ ነው።ከእነኝህ ዩቱቦች ውስጥ ህወሃትን የሚነቅፉ ዜናዎች የሚያቀርቡ ግን በመሃል ድብቅ የህወሃት አጀንዳ የሚይራምዱ ዜናዎችን አልፎ አልፎ የሚለቁትን በጥንቃቄ መመልከት። አንዳንዶቹ በቀጥታ በባዕዳን መንግስታት የደህንነት ቢሮዎች የሚተዳደሩ እና በተሻለ የአቀራረብ ጥራት እና የአማርኛ ዜና አነባበብ ሁሉ የሚለቀቁ ስለሆኑ፣በሂደት ሥራዎቻቸውን በማጤን መከታተል እንደሚያስፈልግ መረዳት።

  • በትዊተር የኢትዮጵያን ጥቅም የሚቃረኑ ጽሑፎችን መቃወም እና እውነታውን ለዓለም የሚያሳዩ አዳዲስ ሃሳቦችን በማፍለቅ መጻፍ መቀጠል ከኢትዮጵያውያን የሚጠበቅበት ጊዜ ነው።
===========///==========

Tuesday, October 4, 2022

''መታዘዝ ከመስዋዕትነት ይበልጣል...እልከኝነትም ጣዖትን እንደማምለክ ነው። '' 1ኛ ሳሙኤል - 15፣22-23 በውጪ ሀገር በሚገኙ አንዳንድ የኢ/ኦ/ተ/አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ስለቅዱስ ሲኖዶስ አና ሊቃነ ጳጳሳት የተዛቡ መረጃዎች በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሚያሰራጩ መኖራቸው ምዕመናን የቅዱስ ሲኖዶስንም ሆነ የሊቃነ ጳጳሳት ማዕረገ-ክህነት ሳያውቁ እንዲደፋፈሩ እና ከህገ ቤተክርስቲያን እንዲወጡ እያደረጋቸው ነው።


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን  ከቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ እስከ አጥብያ ቤተክርስቲያን ያለው መዋቅር

=================
በአዚህ ጽሑፍ ስር ከሚያገኙት ርዕሶች ውስጥ  - 
  • ቅዱስ ሲኖዶስ አንዴት ተጀመረ? ከቅዱስ ሲኖዶስ ውጪ የሆነች ቤተክርስቲያን ኦርቶዶክሳዊ ቤተክርስቲያን ትባላለች?
  • የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔ የጀመሩ ከጌታችን እግር ስር የተማሩት ሐዋርያት ናቸው።
  • የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔያት ሃይማኖታችንን አፅንተዋል።
  • ቅዱስ ሲኖዶስ እግዚአብሔር ሃሣቡን ፈቃዱን ለልጆቹና ለቤተ ክርስቲያን የሚያስተላልፍበት መንፈሳዊ ጉባዔ ነው፡፡
  • ከቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ዋና ተግባራት ውስጥ ምን ምን ይገኛሉ?
  • ቅዱስ ሲኖዶስ ይሳሳታል? ቢሳሳት የሚስተካከለው አንዴት ነው?
  • ሀገረ ስብከት ምንድነው?
  • የሀገረ ስብከት ቅድመ ታሪክ
  • ቃለ አዋዲ ምንድነው?
  • የቃለ ዓዋዲው ተቀዳሚ ዓላማ
  • ቃለ አዋዲውን ሙሉ ይዘት ለማንበብ የሚችሉበት ማስፈንጠርያ (ሊንክ) ያገኛሉ።


መግቢያ 

በውጭ ሀገር የሚገኙ አንዳንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት የሥርዓት አካሄድ ለቅስፈት አንዳይዳርግ የሚያስፈራበት ሁኔታ ላይ ነን።አለማወቅን በመማር፣እልህን በትሕትና መለወጥ ከአገልጋይም ከምዕመናንም ይጠበቃል።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓት ሰዎች አንደፈለጉ የደነገጉት አይደለም።የሚያጸድቅና የሚያስኮንን ነው።ሁሉም ሰው ሲወለድ ጀምሮ የቤተክርስቲያን መሰረታዊ ትምሕርቶች አብረውት አልተፈጠሩም።በአርግጥ ፀጋውን ያደላቸው ለተመረጡት ይህ ተደርጎ ይሆናል።የቀረው ምዕመን አና አገልጋይ ግን በቤተክርስቲያኒቱ የትምሕርት ሥርዓት ስር አልፎ ወይንም ከመምህራን ጉባዔ ተምሮ አልያም አንብቦ ትክክለኛውን የቤተክርስቲያንቱን ትምሕርት መማር ይችላል።ይህ ያለንበት የ21ኛው ክ/ዘመን ደግሞ ማንኛውንም ትክክለኛ መረጃ ለማግኘት የደቂቃዎች ጊዜ ቢፈልግ እንጂ ብዙ ውስብስብ አይደለም።ዋናው ቁምነገር ትክክለኛ ምንጩን ማወቅ ነው።

አሁን ባለንበት ዘመንም አንዳንድ አገልጋዮች ቀለል አድርገው የሚያቀርቡት ምዕመናንም ሳያውቁ ችላ ያሉት ጉዳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ሰማያዊ ክብር አና የሊቃነ ጳጳሳት ስልጣን ነው።ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ የሊቃነ ጳጳሳት ስልጣነ ክህነት ሰማያዊ እና እራሱ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስርቶ፣ከጌታችን የተማሩት ሃዋርያት ያስፋፉት እና ሊቃውንት ያመሰጠሩት ነው።

በቅዱስ ሲኖዶስ ላይ ከምዕነናን ወይንም አገልጋዮች የሚቀርብ ቅሬታ፣አቤቱታ፣ጥያቄ በየትኛውም መልክ መኖሩ በራሱ ችግር አይደለም።ያልገባውን መጠየቅ ኃጢአት አይደለም።አምላካችንም የመጠየቅ፣ባልገባን መልክ አቤቱታ ማቅረብ አልከለከለንም።በመፅሐፈ ዕዝራ ላይ አንደምናነበው ዕዝራ ከአግዚአብሔር ጋር አሞግታለሁ ብሎ ተነስቶ ነበር።አግዚአብሔር የፍቅር አምላክ ስለሆነ የዕዝራ መጠየቅን ከኃጢአት አልቆተረበትም።ይልቁንም መልአኩ ቅዱስ ዑራእልን ልኮ ያሉትን ጥያቄዎች ሁሉ መለሰለት።ስለሆነም ጥያቄ መጠየቅ አምላካችንም አልከለከለም። ሕጉን አና ሥርዓቱን መጣስ ግን አልፈቀደልንም። ይህም የምንጎዳበት ስለሆነ አንጂ አርሱ ሊከብርበት አይደለም።

የዘመናችን አካሄድ ግን ከአዚህ አየተለየ ነው።ትውልዱ የቅዱስ ሲኖዶስን ክብር አና የሊቃነ ጳጳሳት ስልጣን ዝቅ አድርጎ ለማቅረብ የማይኬድበት መንገድ የለም።የታዘዙትን ካለመስራት አንስቶ አስከ የአውደ ምሕረት እና አንድ በአንድ ግንኙነት ላይ ሁሉ ቅዱስ ሲኖዶስን አና ጳጳሳትን አንዳንድ ነገሮች አየነቀሱ ትውልዱ አንዲጠላቸው የሚደረገው ድርጊት መልሶ ቤተክርስቲያንን አንደሚጎዳ በተለይ በውጭ ያሉ አብያተክርስቲያናት ሊገነዘቡት ይገባል።የፕሮቴስታንት እምነት ሲጀመር የካቶሊክን እምነት አባቶች የማስጠላት ትልቅ ዘመቻ ላይ ነበር።ይህ ተግባር ምእመኑ ላይ ያመጣው ውጤት ግን የካቶሊክ አባቶችን መጥላት ብቻ ሳይሆን ክርስትና የተባለ እምነትን በሙሉ የሚጠላ ትውልድ ዛሬ አንደምናየው ወልዶ ቁጭ አለ።የካቶሊክ አባቶች ብቻ ይጠላሉ ብሎ ዘመቻ የከፈተው የፕሮቴስታንት ዓለም ፕሮቴስታንትንም ማንንም የማያምን ኢ-አማኒ ትውልድ ፈጥሮ ሁሉንም ሜዳ ላይ አንሳፎ ዓለማችንን ወደ ጥፋት ይዞ ነጎደ።

ዛሬም በውጭ ያሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት አባቶችም ሆኑ አገልጋዮች በምንም መልኩ ለምዕመናንም ሆነ ምዕመናን ለልጆቻቸው ቅዱስ ሲኖዶስ አና ሊቃነ ጳጳሳት ላይ ነቁጥ ስነቅሱ መዋሉ ፅድቅ ሳይሆን ኩነኔ መሆኑም ማወቅ አለባቸው።አባቶቻችን አንደኛው የሰው ባሕሪ የተላበሱ ናቸው።የቤተክርስቲያን ስርዓት ሲጣስ ያሳለፉት ለቤተክርስቲያን ታዛዥ የነበረ ያለፈ ትውልድን በአኛ ደፋር አነጋገር ተተክቶ ሲመለከቱ ይበሳጫሉ፣ይቆጣሉ።ይህ የሰው ከአሳት ባሕሪ የመፈጠሩ ተፈጥሮ አንጂ አነርሱ ከአኛ የበለጠ ኃጢአተኞች ሆነው ከመሰለን ተሳስተናል።ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስም በቤተመቅደስ ሲሸጡ አና ሲለውጡ ተመልክቶ ጅራፍ አንስቶ ሰዎችን ገርፏል፣ንግዳቸውን አነ ሸቀጣቸውን ገልብጦታል።ይህ ግን የባህሪ አምላክነቱን ለሰው ልጅ ያለው ፍቅርን የሚቀንስ አይደለም።አባቶቻችንም አንዲሁ ናቸው።በአኛ ሲናደዱ ይቆጣሉ፣ነገር ግን በርህራኄ መልሰው ስለኛ ይፀልያሉ።ብዙዎች ምዕመናን ከአባቶች ጋር ቀርቦ የማወቅ ዕድል ስላላገኘን አሩቅ ለማየት አግዶናል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊት ናት።የቅዱስ ሲኖዶስ ስርዓትን፣የካህናት አና ጳጳሳት ስልጣናትን የተማረችው በቅድምያ ከጌታችን አና ከጌታችን ከተማሩት ከሐዋርያት ነው።ሊቀካህን እየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ጴጥሮስ የሰጠው ልስጣነ ክህነት ሲወርድ ሲዋረድ መጥቶ አሁን ያለንበት ደረጃ ደርሷል።ይህንን ስልጣን ያከበረ ይከብራል።ያላከበረ ግን አይከብርም።

ከአዚህ በታች ስለቅዱስ ሲኖዶስ፣ሀገረ ስብከት ምንነት አና ተያያዥ ጉዳዮች መሰረታዊ ግንዛቤ በአንዳንድ የውጭ ሀገራት በሚገኙ ምዕመናን ዘንድ ባለመኖሩ ጉዳያችን ከልዩ ልዩ የቤተክርስቲያናችን የትምሕርት ገፆች ላይ ያገኘችውን ለማቅረብ ትሞክራለች።መረጃዎቹን በሚገባ አንብበን መጠቀም የአኛ ፈንታ ነው።ጽሑፎቹ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ከማኅበረ ቅዱሳን ገፆች አና አቡነጎርጎርዮስ ካልዕ ''የቤተክርስቲያን ታሪክ'' መፅሃፍ የተወሰዱ ናቸው። 

ቅዱስ ሲኖዶስ አንዴት ተጀመረ? 
ከቅዱስ ሲኖዶስ ውጪ የሆነች ቤተክርስቲያን ኦርቶዶክሳዊ ቤተክርስቲያን ትባላለች?

ቅዱስ ሲኖዶስ አበው ሊቃነ ጳጳሳት ስለቤተክርስቲያን ዶግማ ቀኖና ሥርዓትና ትውፊት እንዲሁም አስተዳደር የሚመክሩበት በመንፈስ ቅዱስ የሚቃኝ ጉባዔ ነው፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ የበላይ መንፈስቅዱስ ነው።የሚመራውም መንፈስ ቅዱስ ነው።ይህም «ቅዱስ ሲኖዶስ ማለት ፓትርያርክ ሊቃነ ጳጳሳት ጳጳሳትና ኤጲስ  ቆጶሳት የሚያደርጉት ዓቢይ ጉባዔ ነው፡፡» ተብሎ በሕገ ቤተ ክርስቲያን የተገለፀው ነው፡፡ /ሕገ ቤተክርስቲያን አንቀጽ 2(2)/፡፡በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ብቻ አይደለም።በመላው ምሥራቃውያን አብያተክርስቲያናት ውስጥ ከቅዱስ ሲኖዶስ ዕይታ፣ቁጥጥር እና ትዕዛዝ ውጪ የሆነ ቤተክርስቲያን ኦርቶዶክሳዊ ቤተክርስቲያን አትባልም።ይህ ቤተክርስቲያናችን በክርስቶስ መስራችነት መመስረቷን፣በሃዋርያት ትምህርት መሰበኳና በሰማዕታት ደም መጽናቷ መገለጫ ነው።

የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔ የጀመሩ ከጌታችን እግር ስር የተማሩት ሐዋርያት ናቸው።

ሊቃውንት የቅዱስ ሲኖዶስን ሥርዓት አጀማመር ጌታ ከሐዋርያት ጋር ያደረጋቸው ስብሰባዎች መነሻ አድርገው ያመጣሉ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት በመጽሐፍ ቅዱስ ተመዝግበው የሚገኙ ሦስት ጉባዔያትን አድርገዋል፡፡ የመጀመሪያው በይሁዳ ምትክ አንድ አባት መርጠው ሐዋርያ ለመሾም ያደረጉት ጉባዔ ነው፡፡/የሐዋ 1፥15-16/ ሁለተኛው ሰባቱን ዲያቆናት ለመሾም የተደረገው ጉባዔ (ሲኖዶስ) ነው፡፡ /የሐዋ 6.1-6/ የመጨረሻው ከአሕዛብና ከአይሁድ ወደ ክርስትና በመጡት መካከል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት የተደረገው ነው፡፡/የሐዋ.15፥1/

የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔያት ሃይማኖታችንን አፅንተዋል።

በጉባዔ ኬልቄዶን ምክንያት የሃይማኖት መከፋፈል ከመጀመሩ በፊት የአካባቢ ሲኖዶሶች እምብዛም የተለመዱ አልነበሩም፡፡ ዛሬ በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ሦስቱ ጉባዔት ብቸኞቹ ዓለም አቀፍ ጉባዔያት ናቸው፡፡ እርሱም በኒቅያ በ325 ዓ.ም በቁስጥንጥንያ በ381 ዓ.ም እንዲሁም በኤፌሶን 431 ዓ.ም የተካሔዱት ናቸው፡፡

ከዚያ በኋላ ግን ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት በየራሣቸው መንበር የአካባቢ ሲኖዶስ ማድረግ ቀጥለዋል፡፡ እነሆ የእኛም ቤተ ክርስቲያን በራሷ ሲኖዶስ መመራት ከጀመረች ከግማሽ ምእት ዓመት በላይ ሆኗል፡፡

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋነኛ ዓላማ የቤተ ክርስቲያንን አንድነት መጠበቅ ነው፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያን የአንድነቷ መገለጫ ነው፡፡ በየጊዜው በሚወለዱ ክስተቶች ዶግማዊ ቀኖናዋ ሥርዓቷ ትውፊቷ እንዲሁም አስተዳዳሯ እንዳይፈታ መጠበቂያ ነው፡፡ በዚህም በመሠረት እምነቷ ላይ ጥያቄ ሲነሳ ማብራሪያ መስጠት አዳዲስ አስተምህሮዎች ሲመጡ በዶግማዊ መሠረት ማረቅ ማቅናት የጾም የጾሎት ሥርዓትን መሥራት ልጆቿን የሚመሩ አበው ሊቃነ ጳጳሳትን መሾም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋነኛ ተግባራት ናቸው፡፡

አስቀድመን እንደገለጽነው ክርስትና በማኅበር የሚኖርበት በማኅበር ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር የሚደረግ ጉዞ ነው፡፡ይህ ማኅበር በአንዳች ምክንያት እንዳይበተን የአንድነት መገለጫው ቅዱስ ሲኖዶስ ነው፡፡

ምዕመናን ሁል ጊዜ ሊሰሙት የሚገባው የቤተ ክርስቲያን ድምጽ ይህ የአንድነቷ መገለጫ ከሆነው ከቅዱስ ሲኖዶስ የሚወጣው ድምጽ መሆን አለበት፡፡ አንድ ክርስቲያን በአኗኗሩ ሁሉ ቅዱስ ሲኖዶስ ለሚደነግጋቸው ድንጋጌዎች ተገዢ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህ አልተስማማኝም ይህ ጐረበጠኝ ብሎ በግልም በቡድንም መጓዝ ከሕይወት መንገድ ይለያል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ እግዚአብሔር ሃሣቡን ፈቃዱን ለልጆቹና ለቤተ ክርስቲያን የሚያስተላልፍበት መንፈሳዊ ጉባዔ ነው፡፡

ለእስራኤል ዘሥጋ ሥለ አንድነታቸው ስለአኗኗራቸው በነሊቀነብያት ሙሴ በኩል ሥርዓትን የሠራ እግዚአብሔር በሐዲስ ኪዳን ለምንኖር ክርስቲያኖች እስራኤል ዘነፍስም ሥለ አንድነታችን ማኅበራችን እንዴት በሥርዓት ልንኖርበት እንዲገባ ሥርዓቱን የሚሠራልን በብጹአን አበው አማካኝነት ነው፡፡ በዚህም ከመንጋው ተለይቶ ላለመቅበዝበዝ የቅዱስ ሲኖዶስን ድምጽ መስማት ተገቢ ነው፡፡

ከቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ዋና ተግባራት ውስጥ 

ከቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ዋና ተግባራት መካከል ለቅዱሳን አንድ ጊዜ የተሰጠውን ሃይማኖት መጠበቅና ማስጠበቅ፣ ሕግ ማውጣትና ማስፈጸም፣ ትልልቅ ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን መመርመርና ዘመኑን በዋጀ ሥርዓት ትውልድን መምራት፣ በገዛ ደሙ በዋጃት የእግዚአብሔር በተክርስቲያን ጳጳሳት አድርጎ ለሾማቸው መንፈስ ቅዱስ በመታመን ለራሳቸውና ለመንጋው መጠንቀቅ ይጠቀሳሉ፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ ይሳሳታል? ቢሳሳት የሚስተካከለው አንዴት ነው?

እንደ ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ከሆነ ቅዱስ ሲኖዶስ ፍጹምና የማይሳሳት አይደለም፡፡ ነገር ግን ሲኖዶስ ተሳሳተ ተብሎ ሌላ አቋራጭ መንገድ መከተል ደግሞ የበለጠ ለጥፋት የሚዳርግ ነው፡፡ ሲኖዶስ ቢሳሳት የሚስተካከለው በራሱ በሲኖዶሱ ሥርዓትና ደንብ ብቻ ነው፡፡ለቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መገዛት የማኅበረ ምዕመናን አባልነት በዚህ ምድር ያላችው የእግዚአብሔር መንግሥት ነዋሪነት መገለጫ ነው፡፡

ሀገረ ስብከት ምንድነው?

ሀገረ ስብከት ሀገረ ስብከት ቤተ ክህነቱን ወክሎ የሚሠራ ተቋም ሲሆን፣ ሃይማኖቱን እና ቀኖናውን ለመጠበቅ እና ለማስጠበቅ፣ ከክርስቶስ ጀምሮ የመጣውን ሀብተ ክህነት ለመጠበቅ እና ለማስተላለፍ፣ ስብከተ ወንጌል እንዲስፋፋ፣ ገዳማት እና አድባራት እንዲረዱ፣ አብያተ ክርስቲያናት እንዲተከሉ፣ ምእመናን ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኙ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጋዊ መብት እንዲከበር፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልግሎት ወጥ እና ሥርዓቱን የጠበቀ እንዲሆን፣ የካህናት አስተዳደር እና አገልግሎት በቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግ መሠረት እንዲሆን፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሀብት እና ንብረት በሕግ እና በሥርዓት መሠረት እንዲጠበቅ፣ ምእመናን በቤተ ክርስቲያኒቱ ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኙ እና እንዲሰጡ ማድረግ ዋና ዋናዎቹ ተግባሮቹ ናቸው፡

የሀገረ ስብከት ቅድመ ታሪክ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቃለ ዐዋዲ ምዕራፍ ስድስት፣ ዐንቀጽ ሠላሳ ስምንት እስከ አርባ አምስት ድረስ በተዘረዘረው መሠረት ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ጽ/ቤት ቀጥሎ በቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር መሠረት የመንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት መሥርቶ እና አጠናክሮ መሥራቱ ለቤተ ክርስቲያን አንድነት አስፈላጊ እና ወሳኝ ነው፡፡

በእንግሊዝኛው «ዳዮሰስ» የሚለው ቃል dioikesis ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ነው፡፡  በመሆኑም ሀገረ ስብከት ማለት በአንድ ሊቀ ጳጳስ የሚመራ አንድ አካባቢ ማለት ነው፡፡
ሀገረ ስብከት ለመጀመርያ ጊዜ በሥራ ላይ የዋለው ቅዱሳን ሐዋርያት የጌታችንን ትምህርት ተግባራዊ ለማድረግ ዓለምን ዕጣ በዕጣ ተከፋፍለው ለማስተማር በወጡ ጊዜ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ይመቻል፣ አይመችም ሳይሉ በተሠማሩበት ሀገረ ስብከት ገብተው አብያተ ክርስቲያናትን በመትከል፣ ምእመናንን አስተምረው በማጥመቅ፣ ካህናትን እና ዲያቆናትን በመሾም የወንጌልን ቃል ለዓለም አዳርሰዋል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በሮም ሀገረ ስብከቱ፣ ዮሐንስ ወንጌላዊው በታናሽ እስያ ሀገረ ስብከቱ፣ ቶማስ በሕንድ ሀገረ ስብከቱ፣ማርቆስም በእስክንድርያ የሠሩት ሥራ ለዚህ ማስረጃችን ነው፡፡
በቃለ ዐዋዲው ዐንቀጽ አርባ ሦስት ቁጥር አንድ ላይ እንደ ተገለጠው «የመንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በሀገረ ስብከቱ ክልል ውስጥ ለሚገኙ ገዳማት፣ አድባራት እና የገጠር አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም በየደረጃው ለተቋቋሙት ሰበካ መንፈሳውያን ጉባኤያትና ለወረዳ ቤተ ክህነት የሥራ አመራርና ከፍተኛ የአስተዳደር ኃላፊነት ያለው መሥሪያ ቤት ነው»

ቃለ አዋዲ ምንድነው?

ቃለ ዓዋዲ ቀጥተኛ ትርጉሙ “የአዋጅ ነጋሪ ቃል” ማለት ነው፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ የአዋጅ ነጋሪ ቃል ብሎ የተነበየለት መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስን ነበር፡፡ /ኢሳ.40፥1፵፥፩/ ከጌታችን ከመድኀኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋዊ ልደት ስድስት ወራትን ቀድሞ የተወለደው ቅዱስ ዮሐንስ ጥርጊያውን እያስተካከለ ሰዎችን ለንስሐ እየጠራ ለአማናዊው በግዕ ለኢየሱስ ክርስቶስ አዘጋጅቷቸዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያናችን መተዳደሪያ ደንብም /ቃለ ዓዋዲ/ ሦስቱ ጾታ ምእመናንን/ ካህናት፣ ወንዶች እና ሴቶች/ በሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን እየተመሩ ሕይወታቸውን እንዲጠብቁ ስለሚያውጅ ቃለ ዓዋዲ ተብሎ ተሰይሟል፡፡ ቃለ ዓዋዲ የተባለው መጽሐፍ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ያለውን አስተዳደራዊ መዋቅር ያካተተ የሕግ መጽሐፍ ነው፡፡ በዚህም ብቻ ሳይወሰን ከምእመናን ጀምሮ እስከ ካህናት ድረስ ያሉትን የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች መብትና ግዴታ በውሉ የሚያስገነዝብ መመሪያም ነው፡፡

ቃለ ዓዋዲ ቤተ ክርስቲያናችን የምትመራበት የሕግ መጽሐፍ ነው ሲባል፤ ቃለ ዓዋዲ ከመኖሩ በፊት ቤተ ክርስቲያን በምን ትተዳደር ነበር? የሚል ጥያቄ ያስነሣ ይሆናል፡፡ ይህንን ጥያቄ የምንመልሰው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ለረዥም ዘመን በሓላፊነት አገልግለው በሞተ ሥጋ የተለዩንን የአባ አበራ በቀለን የአንድ ወቅት ቃለ ምልልስ መሠረት በማድረግ ነው፡፡ አባ አበራ በቀለ እንዳሉት “ቃለ ዓዋዲ ከመፈጠሩ በፊት ቤተ ክርስቲያናችን ትመራበት የነበረ አስተዳደራዊ መዋቅር አላት ከኒቂያ ጉባኤ በፊትም ቢሆን የአስተዳደር ሥርዓት ነበራት፡፡ ከሁሉ በፊት ግን እንደ ሕግ ሆኖ የሚመራት ዋናው የሕግጋት ምንጭ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ እርሱም የሃይማኖትና የሥነ ምግባርን ሕግ የያዘ ነው፡፡ በብሉይም ሆነ በሐዲስ ኪዳን ዘመን አባቶቻችን በዚህ ሲገለገሉ እንደ ነበር የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ይመሰክራል ወደ ሀገራችንም ስንመጣ ፍትሐ ነገሥቱ ከፍተኛውን ቦታ ይይዛል፡፡

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንና የኢትዮጵያ መንግሥት ከአብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ ንግሥ ጀምሮ እስከ ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሴ ድረስ አንድነት ነበራቸው፡፡ ቤተ መንግሥት ወደ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ይገባ ነበር፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ወደ መንግሥት አስተዳደር ትገባ ነበር፡፡ በዚያን ጊዜ ፍትሐ ነገሥቱ በሁለቱም ወገኖች ሲሠራበት ቆይቷል፡፡ ነገር ግን በዓፄ ኀይለ ሥላሴ ጊዜ አዳዲስ ሕጎች ሲወጡ ፍትሐ ብሔሩና ወንጀለኛ መቅጫው ሲወጣ የፍትሐ ነገሥቱ አሠራር እየቀዘቀዘ በአዲስ እየተተካ ሄደ፡፡ እንደሚታወቀው ፍትሐ ነገሥት ሁለት ክፍል አለው እርሱም፡-

  • ፍትሕ መንፈሳዊና
  • ፍትሕ ሥጋዊ በመባል ይታወቃል፡፡

ፍትሕ መንፈሳዊ አሁንም በቤተ ክርስቲያን ተጠብቆ እየተሠራበት ነው፡፡ የሥጋዊ አስተዳደሩ ደግሞ በቤተ መንግሥት በኩል በሌላ አዋጅ ተተክቷል፡፡

በዓለመ መላእክት፣ በሕገ ልቡና፣ በሕገ ኦሪት፣ መላእክትና ሰዎች እግዚአብሔርን ያመልኩበት የነበረ ሥርዓት አለ፡፡ በዘመነ አበው፣ በዘመነ መሳፍንት፣ በዘመነ ነገሥት፣ በዘመነ ነቢያትና በዘመነ ሐዲስም ይህ ሥርዓት የጸና ነው፡፡ የሥርዓት አስፈላጊነት በመጽሐፍ ቅዱስ ተደጋግሞ የተቀመጠ በመሆኑ አሁንም ለሕንፃ ቤተ ክርስቲያንና ለማኅበረ ምእመናን ሥርዓት ያስፈልጋቸዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ያለ ሥርዓት፣ ያለ ሕግ፣ ያለ ደንብ፣ ያለ መዋቅር የምትሠራው ምንም ዓይነት አገልግሎትና ድርጊት የለም፡፡ ሊቀ ጉባኤ እንዳሉት የሕግ ሁሉ ምንጩ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ ፍትሐ ነገሥቱም መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርጎ በፍትሕ መንፈሳዊና በፍትሕ ሥጋዊ ተጣምሮ አገልግሎቱን ሲሰጥ ከቆየ በኋላ ፍትሕ ሥጋዊ ወደ መንግሥት አስተዳደር ተጠቃልሏል፡፡

ቤተ ክርስቲያን ራሷን ችላ የምትመራበት ሕግ እንዲጸድቅላት በጠየቀችው መሠረት ከምእመናን ምጣኔ ሀብታዊ ጋር በተገናዘበ መልኩ ሁሉንም የሚያሳትፍ መዋቅር በሁለተኛው ፓትርያርክ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ዘመነ ፕትርክና የመጀመሪያው ቃለ ዓዋዲ ጥቅምት 14/፲፬ ቀን 1965/፲፱፻፷፭ ዓ.ም ታተመ፡፡ ቃለ ዓዋዲው ከመውጣቱ በፊት ረቂቁ  ለፓርላማ ቀርቦ ውይይት ከተካሄደበት በኋላ ለምእመናን እንዲደርስ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ተዘጋጅቶ በነጋሪት ጋዜጣ መልክ ወጣ፡፡ ይህ ቃለ ዓዋዲ ከ1965/፲፱፻፷፭ ዓ.ም እስከ 1970/፲፱፻፸ ዓ.ም ለአምስት ዓመታት ያህል እንዳገለገለ ሊቀ ጉባኤ አባ አበራ አያይዘው ገልጠዋል፡፡

የቃለ ዓዋዲው ተቀዳሚ ዓላማ

ሀ. ቅድስት፣ ከሁሉ በላይ ሐዋርያዊትና አንዲት የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን መጠበቅና አገልግሎቷም የተሟላ እንዲሆን ማድረግ ነው፡፡ ይህን ሓላፊነት የሚወጡት ከአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እስከ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ድረስ የሚገኙት የሥራ ሓላፊዎች ናቸው፡፡

ለ. የካህናት የኑሮ ደረጃ የተሻለ ሆኖ ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን በትጋት እንዲወጡ ማድረግ፡፡

ሐ. የምእመናን ቁጥር ከዕለት ወደ ዕለት እንዲጨምር እና ያሉትንም በምግባር በሃይማኖት ማጽናት፤ በመንፈሳዊ ዕውቀት እንዲበለጽጉ ማገዝ፤ ሁኔታዎችንም ማመቻቸት፡፡

መ. የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር እንዲሻሻል የገቢ ምንጮችና ልማቶች ተበራክተው በገንዘብ አቅም የጎለበተች ቤተ ክርስቲያን ሆና ከተረጂነት እንድትላቀቅ ማድረግ ነው፡፡

እነዚህን ዓላማዎች ግቡ አድርጎ የተመሠረተው ቃለ ዓዋዲ አፈጻጸሙ እንዲሳካ ከምእመናን ጀምሮ ሥልጣነ ክህነት እስካላቸው አገልጋዮች ድረስ የሠመረ ግንኙነት ሊኖራቸው ይገባል፡፡ በተለይ በዚህ ዘመን ምእመናን ስለ ቃለ ዓዋዲ ያላቸው ግንዛቤ በጣም አነስተኛ ነው፡፡ ለቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ ጉዞ ምቹ መሆን የካህናት ድርሻ ብቻ የተሟላ አያደርገውም፡፡ የምእመናንም ድርሻ ከፍተኛውን ድርሻ መያዝ አለበት፡፡ የቤተ ክርስቲያንን ጉዳይ ለተወሰኑ አካላት ብቻ የማንተወው በመሆኑ የእነሱና የእነሱ ሓላፊነት ብቻ እንደሆነ ማሰብ የለብንም፡፡ ቤተ ክርስቲያን የሦስቱም ጾታ ምእመናን ናትና ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት፡፡

ቃለ ዓዋዲ ተደንግጎ ጸድቆ ሰበካ ጉባኤ ተቋቁሞ በሥራ ላይ ውሎ አሁን ካለበት ደረጃ ለመድረስ በርካታ ፈተናዎችን አልፏል፡፡ በ1965/፲፱፻፷፭ ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ሊቀ ጉባኤ አባ አበራን ጨምሮ የተለያዩ እንግዶችን በመጥራት የመጀመሪያውን የቃለ ዓዋዲ ረቂቅ ለውይይት አቅርበዋል፡፡ ቅዱስነታቸው በሸዋ ሀገረ ስብከት በዐሥራ አንድ አውራጃዎች እየተዘዋወሩ ስለ ቃለ ዓዋዲ ለካህናትና ለምእመናን ማብራሪያ በመስጠት አዲሱን እቅድ አስተዋውቀዋል፡፡ ቅዱስ ፓትርያርኩ ልኡካንን መድበው በየአህጉረ ስብከት እየተዘዋወሩ እንዲያስተምሩ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡

ሆኖም ካህናቱና ምእመናኑ ተወካዮችን መርጠው ሰበካ ጉባኤና ቃለ ዓዋዲ የሚባል በባህላችን የማይታወቅ አዲስ አሠራር መጣብን ብለው ለንጉሠ ነገሥቱ /ኀይለ ሥላሴ/ አቤቱታ እስከማቅረብ ደርሰው ነበር፡፡

ይህንና የመሳሰሉትን ችግሮች ተሻግሮ በአገልግሎት ላይ የሚገኘው ቃለ ዓዋዲ ለመጀመሪያ ጊዜ ታትሞ ከወጣበት ከ1965/፲፱፻፷፭ ዓ.ም ጀምሮ ለ5/፭ ዓመታት አገልግሎ በ1970/፲፱፻፸ ዓ.ም የተለያዩ ማሻሻያዎች ታክለውበት ለሁለተኛ ጊዜ ታትሟል ከ1970/፲፱፻፸ ዓ.ም እስከ 1991/፲፱፻፺፩ ዓ.ም መግቢያ ድረስ ለሃያ አንድ ዓመታት ያገለገለው ቃለ ዓዋዲ ዳግመኛ ተሻሽሎ ለሦስተኛ ጊዜ በ1991/፲፱፻፺፩ ዓ.ም ታትሟል፡፡

ሙሉውን ቃለ ዓዋዲን ለማንበብ ይህንን ሊንክ ይጫኑ።

ባጠቃላይ የቤተክርስትያናችንን ሥርዓት ሰማያዊ አንደሆነ ጠንቅቀን አንወቅ።አለማወቅ ከጥፋተኝነት አያድንም።አውቆ መጠቀም ደግሞ የሁላችንም ፈንታ ነው።ከእዚህ ውጪ ቅዱስ ሲኖዶስ ላይም ሆነ ሊቃነ ጳጳሳት ላይ ለአንድ የሰፈር አዛውንት የሚሰጠውን ክብር ያህል መስጠት የተሳነው መልሶ መላልሶ የክርስትናው መሰረትን መመልከት ተገቢ ነው።አንዳንዶቻችን ቅዱስ ሲኖዶስ ላይ የሚዘመተው የማጥላላት ዘመቻ ተራ አለማወቅ አድርገን የምንመለከትበት ጉዳይ አደገኛ ነው።ከቅዱስ ሲኖዶስ የመነጠል ሂደት ግቡ ኦርቶዶክሳዊ ያልሆነች ቤተክርስቲያን የመቆርቆር አደገኛ አካሄድ ነው።በቅዱስ ሲኖዶስ ላይም ሆነ ከሊቃነ ጳጳሳት ጋር የሚነሱ ጥያቄዎችን በአክብሮት እና በታረመ አንደበት መጠየቅ እና ከአባቶች የሚነገረውንም በአንክሮ ማዳመጥ ተገቢ ነው። አንደበትን ከክፉ እና ከማይገባ ንግግር እርስ በርስ ስንነጋገርም ጭምር መጠበቅ እንደሚገባ መጽሓፍ ቅዱስ ያስተምረናል።

በያዕቆብ መልዕክት ምዕ 3፣5 እስከ 6 እንዲህ ይላል፡ 

''እንዲሁም አንደበት ደግሞ ትንሽ ብልት ሆኖ በታላላቅ ነገር ይመካል። እነሆ፥ ትንሽ እሳት እንዴት ያለ ትልቅ ጫካ ያቃጥላል።

አንደበትም እሳት ነው። አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአል፤ ሥጋን ሁሉ ያሳድፋልና፥ የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፥ በገሃነምም ይቃጠላል።''

=======================////=============


ከአዚህ በላይ ያሉት ጽሑፎች የተገኙት 


1/ ከአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ገጽ =  ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ድረ-ገፅ 


2/ ከማኅበረ ቅዱሳን ድረገፆች ውስጥ


https://eotcmk.org/a/%E1%89%83%E1%88%88-%E1%8B%93%E1%8B%8B%E1%8B%B2-2/ 


3/ የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርቲያን ቃለ ዓዋዲ 


https://static1.squarespace.com/static/5759a0b362cd94a47d9c6242/t/5c7d55cbe4966b9aba164a99/1551717869215/EOTC+-+%E1%89%83%E1%88%88+%E1%8B%93%E1%8B%8B%E1%8B%B2+%282009+Et.+Cal+Or+2017+Eur.+Cal%29.pdf 



ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...