ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, November 30, 2019

አቶ ለማ መገርሳ መደመር እና የኢሕአዴግ ውህደትን አስመልክተው ለቪኦኤ የሰጡት ቃለ ምልልስ ምክንያት ምንድነው? በቀጣይስ ምን ሊከሰት ይችላል?

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ እና አቶ ለማ መገርሳ 

ጉዳያችን / Gudayachn
ህዳር 20/2012 ዓም (ኖቬምበር 30/2019 ዓም)

ዓርብ ህዳር 19/2012 ዓም ምሽት ላይ  ቀደም ብሎ ሐሙስ ዕለት በኦስሎ፣ኖርዌይ ጃዋር መሐመድ የሰበሰባቸው የኦሮሞ ኮሚኒቲ አባላት መካከል በኦሮምኛ ከፊት በኩል የተቀመጡ አንዲት እናት የተናገሩትን ድምፁን በመሃል እያቆመ ኦስሎ የሚኖር የኦሮሞ ኢትዮጵያዊ ወዳጄ እየተረጎመ ያሰማኝ ነበር።እኝህ እናትበጣም አክራሪ ብሄርተኛ እንደሆኑ ከወዳጄ ትርጉም ተረድቻለሁ።በንግግራቸው  ጀዋርን ይወቅሱታል።ጀዋርን የሚወቅሱት ደግሞ ለማ ብቻውን ሆኖ ሳታግዘው መቅረትህ ብቻውን እንዲሆን አርገህ፣ካሉ በኃላ ዓቢይ ማኅበረሰባቸውን (የኦሮሞን ማለት ነው) እንደከዳ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያወራሉ።በመሃል ላይ ንግግራቸው በመርዘሙ ራሱ ጃዋርም እየሳቀ ያያቸው ነበር።አሁንም ይሄው ወዳጄ እንደተረጎመልኝ በቃዎት ሰዓት አበቃ ተብለው ነው ማይኩን የሰጡት።የእርሳቸው ንግግር ግን የውስጥ አዋቂ ንግግርም ይመስል ነበር።ከእዚሁ ወዳጄ ጋር እንዴት ዓብይን በእዚህ ደረጃ እንደከዳ ይቆጥሩታል? በማለት ጥያቄ ሰነዘርኩ። 

ቪድዮውን ማየት ቀጠልኩ በእዚሁ በጃዋር ስብሰባ ላይ የትግራይ ማኅበረሰብ በኖርዌይ ሰብሳቢ አቶ ዳዊት በአማርኛ ንግግር እንዲያደርግ ዕድል ተሰጠው።አቶ ዳዊት ንግግሩን ሲጀምር ከተሰብሳቢዎቹ አንዱ ድምፁን ከፍ አድርጎ ''በትግርኛ ተናገር!'' ብሎ ሲናገር በቪድዮው ውስጥ ይሰማ ነበር።ዳዊት ለጥቂት ሰኮንዶች ንግግሩን ቆም አደረገ እና በአማርኛ ቀጠለ። ዳዊት ተሰብሳቢው እና እርሱን የሚያገናኘው አማርኛ መሆኑ ገብቶታል።ዳዊትን ከእዚህ በፊት ሁለት ጊዜ  ኦስሎ ውስጥ በተደረጉ  የማኅበረሰብ ስብሰባዎች አግኝቼዋለሁ።አድ ጊዜ የኢትዮጵያን የጋራ መድረ በኖርዌይ ባዘጋጀው የሁሉም የፖለቲካ አተያዮች መድረክ ላይ ሲሆን ሌላው በቅርቡ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በኖርዌይ ባዘጋጀው ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ባደረገው ውይይት ላይ ነበር።ከእርሱ ጋር  በሃሳብ የማንስማማባቸው ብዙ ነጥቦች ዙርያ ተከራክረናል።ስንከራከር ግን ስርዓት ባለው መልክ ስለነበር የዳዊት ሃሳብ አቀራረብ ከብዙ የህወሓት ደጋፊዎች የተሻለ አቀራረብ ያለው ግን  ያንኑ በመደጋገም የሃሳቡን ስፍራ ላለመልቀቅ የሚሟገት ሰው ነው።በጀዋር ስብሰባ ላይ መገኘቱ እና ንግግር ሲያደርግ በቪድዮ ላይ ሳየው ግን በቅርቡ ስለሞቱት ሰማንያ ስድስቱ ኢትዮዮጵያውያን አንስቶ ጀዋርን ተጠያቂ እንደሆነ ይነግረዋል ብዬ አስቤ ነበር። አላደረገውም።

ወደ አቶ ለማ ጉዳይ ልመለስ።የኦስሎው ስብሰባ ላይ ለማን እያሞገሱ ከተናገሩት ሴት መለስ ስል የማኅበራዊ ሚድያው አቶ ለማ የመደመር ሃሳብ እንዳልተቀበሉ ገለጡ የሚል ዜና ተለጥፎ አየሁ።ወደ ቪኦኤ ገፅ ስገባ ዜናውን አረጋገጠልኝ።ግን ሙሉ ዜናው ስላልነበር ምንም ለማለት አላስቻለኝም። ዛሬ ምሽት ግን ቪኦኤ አማርኛው ሙሉውን ዘገባ ለቆታል። በዘገባው ላይም አቶ ለማ የመደመር ሃሳብ ከመጀመርያው እንዳልተቀበሉት እና እንዳልገባቸው፣ይልቁንም ጉዳዩ የኦሮሞ ሕዝብ  አምኖ የሰጣቸውን እንደመክዳት እንደሚቆጠር ገልጠዋል።የአቶ ለማ ንግግር ለምን ቀድሞ አልተነሳም? በውህደቱ የኢሕአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይስ  ድምፃቸውን ሲሰጡ ለምን ተቃውሞ አልተነሳም? በተለይ ዛሬ ዘሐበሻ ዜና ላይ እንደዘገበው የኦዴፓ  ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ታዬ ደንዳ ለኤስኢቢኤስ ራድዮ ተናገሩት ባለው ዘገባ ላይ አቶ ለማ ከእዚህ በፊት በየትኛውም ቦታ የውህደቱን እና የመደመርን ጉዳይ አስመልክቶ ተቃራኒ ሃሳብ እንዳላቀረቡ  መግለጣቸውን ዘግቧል።ይህ ከሆነ ዛሬ ለምን አነሱት?

አቶ ለማ ምን ሆነው ነው?

እነኝህን እና ሌሎች ሁኔታዎችን ስንመለከት አቶ ለማ በአሁኑ ሰዓት ከኢትዮጵያዊነት ስሜቱ ይልቅ ያየለባቸው (ያስጨነቃቸው) በኦሮሞ ማኅበረሰብ ውስጥ እንደ ከሃዲ ልቆጠር ነው የሚለው ጭንቀት ነው።ከእዚህ ውጪ ከእዚህ በፊት በእየመድረኩ ከነገሩን አንፃር ስናየው የአቶ ለማ ሃሳብ ማጠንጠኛ ምላሽ የሚያገኘው ከመደመር እና ከኢሕአዴግ ውህደት ውጪ የተሻለ የሚያረካቸው ሃሳብ ሊገኝላቸው አይችልም።  እና አሁን አቶ ለማ ለምን እጃቸውን ሲያወጡ ባላፈሩበት ጉዳይ  ዛሬ ተቀይረው ሌላ ሃሳብ አነሱ? ጉዳዩ ጊዜ የሚፈታው ቢሆንም አሁን ባለው ሁኔታ ግን  የሚከተሉትን መሰረታዊ ጥያቄዎች ጠይቆ ማለፍ ይቻላል። እነርሱም -

  • አቶ ለማ መደመር እና የውህደቱ ሂደት እዚህ ደረጃ እንደማይደርስ እርግጠኛ የሆኑበት የማናውቀው በሚስጥር የያዙት ፕሮጀክት ስለነበር ነው እስከዛሬ ዝም ብለው የቆዩት?
  • አሁን ያ ያሉት ፕሮጀክት መክሸፉን ሲመለከቱ እራሳቸው በቀጥታ ሊገቡበት አሰቡ?
  • ወይንስ እንዳሉት መደመር እና ውህደቱ ሳይገባቸው እና ሳይስማሙበት ቆይተው ነበር?
በማስከተል የሚነሳው ጥያቄ አቶ ለማ ይህንን በማለታቸው በመደመር እና የኢህአዴግ ውህደት ላይ የሚመጣው ተፅኖ አለ ወይ? የሚለው ነው።የውህደቱ ጥያቄ ከኢህአዴግ በላይ እየገፉበት ያሉት የአጋር ድርጅቶች ናቸው።ከእስነርሱ ጋር የውህደት ደጋፊዎች ኢሕአዴጋውያን  እና የጎሳ ፖለቲካ ያሰጋው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከውህደቱ ጋር ቆሟል።ከእዚህ በተጨማሪ የተቃዋሚ የዜግነት እና የአንድነት ኃይሎች ሁሉ የውህደቱን ሂደት ይደግፋሉ። በአንፃሩ የጀዋር የፅንፍ ኃይል እና በኦዴፓ ውስጥ የተሰገሰጉ  የብሔር ድርጅቶች ውህደቱን ይቃወማሉ።ከእነሱ በተጨማሪ ህወሓት ዋነኛ ተቃዋሚ ብቻ ሳትሆን በመጪው ሳምንት ወደ ስድስት መቶ ሰዎች የሚሳተፉበት የፈድራሊስት አስተሳሰብ አራማጆች በማለት የተራቻቸውን አበል እየከፈለች መቀሌ ላይ ለመሰብሰብ አቅዳለች። 

በሌላ በኩል የውህደቱን ሃሳብ ካለምንም ድርድር እንደሚቀበለው በቀላሉ ልንረዳው የምንችለው የጦር ሰራዊቱ ነው።በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት አደረጃጀቶች የህዝቡ የጎሳ ስሜት ያላጠቃው አካል የሚገኘው በጦር ሰራዊቱ በተለይ በመካከለኛ እና የመስመር መኮንኖች እስከ ተራ ወታደር ያለው የውህደቱን ሃሳብ ይደግፋል። ይህ ደግሞ ተፈጥሯዊ ነው።የጦር ሰራዊቱ የአንዲት ኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ የሚያተኩር ሆኖ የተሰራ እንጂ በብሄር የተከፋፈሉ ፓርቲዎች የራሱ ራስ ምታት እንደሆኑ ስለሚያውቅ ፈፅሞ መከፋፈልን ሳይሆን የጠቅላይ ሚኒስትሩን የውህደት እና የመደመር ሃሳብ የሚቀበል  ለመሆኑ መጠራጠር አያስፈልግም። ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በጦር ሰራዊቱ መካከለኛ እና የመስመር መኮንኖች ጀምሮ እስከታችኛው ወታደር ድረስ በጣም የሚወደዱ መሪ ናቸው።ስለሆነም የውህደቱ ሂደት ፈፅሞ ሊገታ የሚችልበት ደረጃ አይደለም።  ለእዚህም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የብልፅግና ፓርቲ ገና የምስረታ ጉባኤ ሳይጠራ በኦሮምያ ክልል ያለውን ቢሮ እንዲያደራጅ ሹመት መስጠት የጀመሩት።

በቀጣይስ ምን ሊከሰት ይችላል?

የአቶ ለማ የአመለካከት ለውጥ ትናንሽ ጭረቶችን ከማምጣት ያለፈ በውህደቱም ሆነ በመደመር ሂደት ላይ አንዳች ለውጥ አያመጣም። ምክንያቱም ኢትዮጵያ አሁን ከገባችበት የፖለቲካ ቀውስ ለመውጣት በምንም መመዘኛ ለማየት ብንሞክር ከኢህአዴግ እውነተኛ ውህደት እና ከመደመር እሳቤዎች ውጪ  ህመሟን ልታስታግስበት  የሚችል አንዳች ነገር የለም።ይልቁንም ይህ የመፍትሄ ሂደት በፍጥነት ባይመጣ ኖሮ በኦደፓ እና በአደፓ ውስጥ የገባው የፅንፍ አስተሳሰብ ኢትዮጵያን ወደ አልታወቀ የማዕበል አዘቅት ውስጥ ሊወስዳት ተዘጋጅቶ እንደነበር ለማየት ይቻላል። በሌላ በኩል የአቶ ለማ የሃሳብ ልዩነት ምንም ጭረት አያመጣም ማለት አይደለም።በመጀመርያ ደረጃ አቶ ለማ ለይተው ወደ ፅንፍ ኃይሎች ጎራ ይገባሉ ወይንስ የራሳቸውን አስተሳሰብ ይዘው  የራሳቸውን እና የተከታዮቻቸውን ሃሳብ ይዘው ፓርቲ ይመሰርታሉ? የሚለው ጥያቄ ወሳኝ ጥያቄ ነው።ሌላው ጥያቄ አቶ ለማ በኦደፓ ውስጥ የለዘብተኛ መስመርን ነው ወይንስ የኦነግን መስመር ይከተላሉ? የሚለው  ነው።አቶ ለማ ወደ ፅንፍ ጎራ ይገባሉ ብሎ ማሰብ የሚቻል አይመስልም። ወደ ኦነግ ጎራም ይገባሉ ብሎ ማሰብ አይቻልም።ምክንያቱም ኦነግ እራሱ የፖለቲካ መሰረቱ ከመናጋት አልፎ ሃሳቡን መግለጥ ሲያቅተው እየተኮሰ እና እያስተኮሰ የራሱን ወገን የሚወጋ  አካል ሆኗል።ስለሆነም አቶ ለማ ለጊዜው የሚያደርጉት አንድ በልዩነት ተቀምጠው ለጥቂት ጊዜ ማየት አልያም የራሳቸውን የፖለቲካ ፓርቲ መስርተው በምርጫ መወዳደር ሊሆን  ይችላል።አቶ ለማ ሶስቱንም መንገድ ቢሄዱ ግን ኦደፓ ለሶስት መሰንጠቁ የማይቀር ነው።ኦደፓ ለሶስት ተሰነጠቀ የሚል ታሪክ ሳይፃፍበት ብልሁ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ  ውህደቱን በማብሰር ያለፈ ታሪኩ ሳይጎድፍ እንዲፃፍ ሊረዱት ይችላሉ። አቶ ለማ ይህንን የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሃሳብ ቢረዱ ኖሮ ዝም ቢሉትም ለሶስት ማለትም የውህደት ደጋፊዎች፣የፅንፍ አቅራሪ ኃይሎች እና የለዘብተኛ ብሄርተኞች ክፍል ሆኖ መከፈሉ የማይቀር ነበር።አቶ ለማ ትናንት የሰጡት ሃሳብም የእዚህ የስንጥቁ  አንድኛው ድምፅ ነው።

ማጠቃለያ 

ለማጠቃለል አቶ ለማ መገርሳ የፈለጉትን ሃሳብ መስጠታቸው የሚከበር እና ሊከበር የሚገባ ነው።ግለሰቡ ስብእናቸውም  የሚናቅ አይደለም።ቆራጥ እና ሀቀኝነት የታየበት አሰራር አሳይተዋል።ወደፊትም የኢትዮጵያ የክብር ሰው ሆነው መቀጠላቸው አይቀርም። በተለይ በቅንነት የኦሮሞ ብሔርተኝነት ይጨፈለቃል ብለው ለሚሰጉ እንደ አቶ ለማ ያሉ ኢትዮጵያዊ ሃሳብ ያላቸው ግን ብሔርተኝነትን  በአንክሮ የሚያዩ ሰዎች መኖራቸው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ጠቃሚ እንጂ ጉዳይ የለውም። አቶ ለማ አንዴ በጎ ኢትዮጵያዊ ሃሳባቸውን ገልጠዋል።ኢትዮጵያዊነታቸውን የሚወስድባቸውም ሆነ በችሮታ የሚሰጣቸው የለም። ድሮም አብሯቸው የኖረ  እና ወደፊትም የሚኖር ነው።ይህ ሁሉ ሆኖ አቶ ለማ የሚመዘኑት ከእዚህ በፊት ከሰሩት ይልቅ ከአሁን በኃላ በሚያደርጉት ነው።እንደ ብዙ ኢትዮጵያውያን ሃሳብ አቶ ለማ የውህደቱን ሂደት የሚያደናቅፍ አንድም ድርጊት ባያደርጉ እና  የመደመርን ሃሳብም በሳይንሳዊ መንገድ ከመተቸት አልፈው ወደ ሌላ አላስፈላጊ ተግባር እንዳይሄዱ  ምክሮች ሁሉ ተሰብስበው መናገር አለባቸው።ኢትዮጵያ በ21ኛው ክ/ዘመን እንደመሆኗ የብሔር ፖለቲካ ደክሟታል። ከእዚህ በላይ ትከሻዋ አይሸከምም።የብሔር ፖለቲካ ቶሎ ቆስሉ ስለማይድን እንጨፈለቃለን ብለው ለሚሰጉ እንደ አቶ ለማ ያሉ ወጣ ብለው ሁኔታውን እየተከታተሉ አገር ያረጋጉ ይህ ክፋት የለውም።የመጨረሻው መጨረሻ ሃሳብ ግን አቶ ለማ ሃሳብ ሌላ ጊዜ ሲኖርዎት እባክዎን የአገር ውስጥ ሚድያዎችን ይጠቀሙ።ይህ ሰነድ ነው።ይህ አገራዊ ጉዳይ ነው። በእዚህ ዘመን ሃሳብን ለመግለጥ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ ድረስ መሄድ ብዙም አያሳምንም። ይልቁንም አላስፈላጊ የባዕዳን ተወዳጅነት ለማትረፍ የተደረገ ቁጭ ብድግ ያስመስላል።ከእዚህ ውጪ አቶ ለማ በሃሳብዎ ልዩነት እናከብርዎታለን እንጂ አንጠላዎትም።ወደፊት በሚሄዱት አካሄድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመዳኘት በአንክሮ እርስዎን እና ተከታዮችዎን ይከታተላል። ውህደቱ እና መደመር ግን ይቀጥላል። የሚቀጥለው ደግሞ የተሻለ መንገድ ስለሌለ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም አዋጪ ስለሆነ ነው።በመጪው ጊዜም በግልጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድጋፉን የበለጠ የሚገልጥበት ጊዜ ይሆናል።  



ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Friday, November 29, 2019

በያዝነው ሳምንት መጀመርያ በቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ ቄሮ በሚል ስም ግጭት ከፈጠሩት ውስጥ አንዱን ያዳኑት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ናቸው። (ቪድዮ ይመልከቱ)

  • የቦሌ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ከተከሉት የቤተ ክርስቲያን አሰሪ ኮሚቴ አባላት ውስጥ አርበኛው አብዲሳ አጋ እንዳሉበት ያውቃሉ?
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በተደራጀ መልክ ጥቃት እየተፈፀመ እንደሆነ የሚታይ ነው።በቤተ ክርስቲያን ላይ ጥቃት የሚያደርሱት አካላት በዋናነት በፅንፍ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ እና በተደራጀ መልክ ከፅንፈኞች አመራር እንደሚቀበሉ ይነገራል። እራሱን ቄሮ ከተሰኘው ቡድን ውስጥ ብዙዎች በሰላማዊ መንገድ እንደሚንቀሳቀሱ  እና ፅንፈኘነትን እንደማይደግፉ በእየሚድያው ላይ ሲናገሩ ይሰማል።ሆኖም ግን ከቄሮ ውስጥ አሁንም በፅንፍ አደረጃጀት ከፅንፍ አካል መመርያ የሚቀበሉ እንዳሉ የሚናገሩ ግን ብዙዎች ናቸው።

ህዳር 15/2012 ዓም በቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ ይሄው የፅንፍ ቡድን በቤተ ክርስቲያን ላይ ጥቃት ለመፈፀም ሞክሯል።ጳጉሜን 3/2011 ዓም ላይም በአውደ ምህረት ላይ ''አላህ ወአክበር'' ለማለት የሞከረ እና ብጥብጥ ለመፍጠር የሞከረ ነበር። በሰሞኑ ጥቃት ግን አንዱ በተለይ ከጅማ የመጣ የተባለውን ሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ አስገብተው ከህዝብቁጣ ያዳኑት እና ለሕግ አካላት በመስጠት መልካም ተግባር የፈፀሙ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ሊመሰገኑ ይገባል።

በነገራችን ላይ የእዚህ ፅሁፍ አቅራቢ የቦሌ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ለረጅም ጊዜ የሚያውቀው ከመሆኑ አንፃር የቤተ ክርስቲያኑ የኃላ ታሪክ ላይ ቤተ ክርስቲያኑ ተከላ ላይ ኮሚቴ ከነበሩት አባቶች መካከል በቦሌ መንገድ ወሎ ሰፈር መኖርያቸው  የነበረው አርበኛው አብዲሳ አጋ እንደነበሩ መረጃውን በወቅቱ ከነበሩት አባቶች በቀጥታ መስማቱን በእዚህ አጋጣሚ ለመግለጥ ይፈልጋል። ዛሬ በቄሮ ስም የተደራጁ የፅንፍ አካሎች የአርበኛ አብዲሳ አጋን ሥራ  ለማፍረስ የሚደረግ ሙከራም መሆኑን ልብ ይሏል።

ህዳር 15/2012 ዓም በቦሌ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ምን ተፈጠረ? ቪድዮውን ይመልከቱ።

ከደብሩ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ምክትል ሊቀመንበር እና የሰንበት ትምህርት ቤቱ አገልጋይ ከአቶ መስፍን  በዳዳ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ 


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Thursday, November 28, 2019

The 2019 Nobel Peace Prize ceremony is coming soon! የኖቤል ሽልማት ቀን አንድ ሳምንት ቀረው

የኖቤል የሰላም ሽልማት ስነ ስርዓት በህዳር 30/2012 ዓም (ዴሴምበር 10/2019 ዓም) በኦስሎ ኖርዌይ ይከናወናል።
Nobel Peace Prize ceremony will be held in Oslo, Norway on December 10,2019.
Listen to the call between Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed Ali and Olav Njølstad, Secretary of the Norwegian Nobel Committee, recorded shortly after the public announcement of the 2019 Nobel Peace Prize.

Source : - Nobel Peace Prize


ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Sunday, November 24, 2019

Breaking News Ethiopia - ''There is a terrorist command center in USA working to destabilize Ethiopia and the horn of Africa'' Ethiopian journalist Eskindir Nega disclosed in Washington DC on November 24,2019.ማዕከሉን አሜሪካ ያደረገ የሽብር ቡድን ኢትዮጵያን ለማተራመስ እየሰራ ነው። (ቪድዮ)


  • የሽብር ቡድኑ በኢትዮጵያ ሴሎች፣የዕዝ ሰንሰለት እና ከመካከለኛው ምስራቅ የሚያገኘው የገንዘብ ፈሰስ አለ።
  • The terrorist team has his own cell, command chain and financial assistance from middle east
**********************************

ጉዳያችን / Gudayachn / November 24/2019 
ህዳር 14/2012 ዓም 
**********************************
Eskindir Nega is Economics graduate from American University (private research University in Washington DC) . He has completed his high school from Sanford American High school in Addis Ababa. In 1980s he traveled to USA for further study and came back home in 1991, when the dictator Mengistu rule was overthrown.Since 1991 Eskindir is working in Ethiopia with chief editor to his own  News paper. His News papaer is one of the  highest circulating news paper in the country. Eskindir is also a human rights activist as a result he has been jailed seven times by the former regime of Ethiopia before the reformists came to power in 2018.

Eskindir Nega is a winner of a number of international awards including -


  • 2012 PEN/Barbara Goldsmith Freedom to Write Award
  • 2014 World Association of Newspapers' Golden Pen of Freedom Award
  • 2017 International Press Institute World Press Freedom Hero
  • 2018 Oxfam Novib/PEN Award 

The below video is Eskindier Nega's speech, on the the existence of terrorist command center in USA, for thousands of Ethio-Americans residing in Washington DC and peripherals.





ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Friday, November 22, 2019

ጃዋር አሕመድ አውሮፓን እንዲረግጥ ሊፈቀድለት አይገባም። We care for Europe - UK,Belgium,Sweden,Norway and others must stop Jawar Mohamed from entering to their territory.

(አማርኛ ከእንግሊዝኛ ስር ያንብቡ)

Attention! to Europe - UK, Belgium, Sweden, Norway and other countries.

We care for Europe!

Jawar Mohamed is well known with his hate speeches and extremist position in Ethiopia. Recently he is claimed  and caused for the death of over 80 innocent people in Ethiopia. Next week, Jawar is planning to travel to European countries including UK, Belgium, Sweden and Norway for the purpose of collecting illegal public fund to use for the same hate speeches plus to inject his clashing  project among Ethiopians at home under the cover of ethnicity. Now a days he is challenged even from Oromo ethnics that he propagandized as if he stand for.

This is a notice to European countries to be aware and take the necessary action by stopping Jawar not to enter to Europe. For your detailed information about the mentioned individual, please click and read this link (https://www.gudayachn.com/2019/10/analysis-ja-war-aljazeera-bloodshed-and.html).

We care for Europe.


====================================

ጥላቻን በተሞላ ንግግሮቹ እና በማኅበራዊ ሚድያ ላይ በሚፅፋቸው ህዝብን ከህዝብ በሚያጋጩ ንግግሮቹ ምክንያች የበርካታ ኢትዮጵያንን ሕይወት እንዲቀጠፉ፣ወላጆች ካለ ልጆች፣ልጆችን ከወላጆቻቸው ውጭ እንዲኖሩ ምክንያት የሆነ ሰው ጃዋር መሐመድ ወደ አውሮፓ በመምጣት ለበለጠ ግጭቶች  የሚረዳው  ገንዘብ ለማሰባሰብ ወደ አውሮፓ ቤልጅየም፣ስዊድን፣ኖርዌይ እና እንግሊዝ ጨምሮ ከመጪው ሳምንት ጀምሮ ለመምጣት ማሰቡ ተሰምቷል።

ከእዚህ በፊት በአሜሪካ ሊያደርጋቸው ያሰባቸው ስብሰባዎች በሰብዓዊ መብት ተሟጋች ኢትዮጵያውያን በተቃውሞ አንዳንዶቹ ጋር ተረጋግጦ ስብሰባውን እንዳያደርግ፣በሌላ ቦታ ደግሞ ፈፅሞ ስብሰባውን እንዳያደርግ ማድረግ ችለዋል።በአውሮፓ እና አሜሪካ ማንም የፈለገውን ሃሳብ የመግለጥ እና የመሰብሰብ መብት አለው።ይህ በሕግ የተረጋገጠ መብት ነው። ሆኖም ግን በቅርቡ ብቻ ከ80 በላይ ንፁሃን ሕይወት መቀጠፍ ምክንያት የሆነ ሰው ለበለጠ ጥፋት የሚረዳው ገንዘብ እንዲያሰባስብ  የአውሮፓም ሆነ የአሜሪካ ሕግ አይፈቅድም።ስለሆነም ኢትዮጵያውያን ለአውሮፓ ሕብረት፣ለእንግሊዝ መንግስት እና ለሌሎቹም መንግሥታት ጃዋር የሚሰበስበው ገንዘብም ሆነ ስብሰባ ህገወጥ መሆኑን በቅድምያ ማሳወቅ በመቀጠልም በየትኛውም ቦታ ስብሰባው እንዳይደረግ በተቃውሞም ማስቆም ይገባቸዋል። 


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Wednesday, November 20, 2019

የኢትዮጵያ ወቅታዊው የፖለቲካ ሁኔታ (ጉዳያችን ምጥን)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ 

በእዚህ ፅሁፍ ስር በምጥን መልኩ የሚከተሉት ጉዳዮች ተነስተውበታል።
  • ወቅታዊው የፖለቲካ ትኩሳቱ፣
  • የኢህአዴግ የውሕደት ሂደት መውሰድ የሚገባው  ጥንቃቄ፣
  • የአክራሪ እስልምና ውጪያዊ እንቅስቃሴ ፣
  • የኦሮሞን ሕዝብ ለመረማመጃ የተጠቀመው ፅንፈኛ እንቅስቃሴ የሚቀጥለው እርምጃው  ምንድነው?
  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ 
  • ከፖለቲካ ፓርቲዎች ውጭ የሆነው ብዙሃኑ እና ወሳኙ ሕዝብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እንዴት ተፅኖ ፈጣሪ ይሁን?
**********************
ጉዳያችን /Gudayachn
ህዳር 10/2012 ዓም  (ኖቬምበር 20/2019 ዓም)
**********************
በኢትዮጵያ ፖለቲካ፣የመገናኛ ብዙሃን እና ካላይኛው አመራር በታች ያለው አመራር ጨምሮ የኢትዮጵያ ችግር የሃሳብ የማመንጨት አቅም ማነስ ነው።አዳዲስ ሃሳቦች ለሚገጥሙ ችግሮች ብቻ ሳይሆን የሚገጥሙ ችግሮችን በወጉ መትሮ ሰው በሚረዳው መልኩ የማቅረብ ችግርም ሌላው ችግር ነው።ለእዚህም ነው የሁኔታዎች ቅርፅ አስይዞ የሚተነተንበት ማዕከል ሲጠፋ ክፉ ሃሳብ ያላቸው ባለ ትንንሽ የሃሳብ ክሮች ብዙዎችን ይዘው  ወደፈለጉት የተሳሳተ መንገድ ይዘው የመንገድ ዕድል ያገኛሉ።ስለሆነም በሁኔታዎች ላይ አተያይን በሚገባ ማቅረብ አስፈላጊ ነው።

በእዚህ የጉዳያችን ምጥን ፅሁፍ  የሚከተሉት ሃሳቦች ላይ ጉዳያችን ምጥን ሃሳብ ትሰጣለች። እነርሱም -

  • ወቅታዊው የፖለቲካ ትኩሳቱ፣
  • የኢህአዴግ የውሕደት ሂደት መውሰድ የሚገባው  ጥንቃቄ፣
  • የአክራሪ እስልምና ውጪያዊ እንቅስቃሴ ፣
  • የኦሮሞን ሕዝብ ለመረማመጃ የተጠቀመው ፅንፈኛ እንቅስቃሴ የሚቀጥለው እርምጃው  ምንድነው?
  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ 
  • ከፖለቲካ ፓርቲዎች ውጭ የሆነው ብዙሃኑ እና ወሳኙ ሕዝብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እንዴት ተፅኖ ፈጣሪ ይሁን?
ወቅታዊው  የፖለቲካ ትኩሳቱ 

በአሁኑ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ትኩሳት ውስጥ በዋናነት የመንግስት የሕግ የማስከበር አቅምን የሚገዳደሩ ቡድኖች በእየቦታው እያቆጠቆጡ  ነው።በእዚህም ሳብያ ሕዝብ በዋናነት የፀጥታ እና የሕግ እንዲሁም የፍትህ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ ክፍተት መታየቱ  መጪውን ጊዜ እንዲፈራ ብቻ ሳይሆን አንዳንድ ቦታዎች ሕዝብ እራሱን ለመከላከል የስነ ልቦናም ሆነ የትጥቅ ዝግጅት የሚያደርግበት  ጊዜ ሆኗል።እነኚሁ ህገ ወጦች በዩንቨርስቲዎች ውስጥ ሳይቀር ተማሪዎችን እስከ መረበሽ እና ማጋጨት ይህ አሁን ላለው የፖለቲካ ትኩሳት ዋነኛ መንስኤ ሆኗል። 

የኢህአዴግ የውሕደት ሂደት መውሰድ የሚገባው  ሶስቱ  ጥንቃቄዎች 

ኢህአዴግ ለመዋሃድ ባለፈው ቅዳሜ ህዳር 6/2012 ዓም ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ወስኗል።በእዚህም መሰረት የውሁዱ አዲስ ስም ብልፅግና ፓርቲ  በሚል ስሙን ሰይሟል።የውህደቱ ሃሳብም ሆነ መተግበሩ በሕዝብ ዘንድ ብቻ ሳይሆን ቀድሞ አጋር በሚል ይጠሩ የነበሩት እንደ ሱማሌ እና አፋር ክልሎች በተለየ ደስታ ፈጥሯል።በአንፃሩ የኢትዮጵያዊ ሃሳብ አገንግኖ መውጣቱ ያሰጋቸው የብሔር ፖለቲካ ከኖረ ብቻ እንደሚኖሩ የምይስቡ ኃይሎች ነገሩ አልታማቸውም።

በውህደቱ ሂደት አዲሱ የኢህአዴግ ውሁድ ፓርቲ ሶስት የጥንቃቄ እርምጃ መውሰድ አለበት።የመጀመርያው ጥንቃቄ በክልሎች የነበረ ክልላዊ ስሜት እና በፓርቲው ውሁድ ሂደት ላይ መጋጨት እንዳይኖር በአንፃሩ የክልሎች ጉዳይ አከላለል ላይ ውሳኔ በቶሎ ያስፈልጋል።ይህ ካልሆነ የሁለት የምቃረኑ ሃሳቦችን አንድ ላይ ለማስኬድ የሚደረግ ጥረት እንዳይሆን ያሰጋል። ሁለተኛው ጉዳይ አዲሱ ውሁድ ፓርቲ በብዙ የፍላጎት ቡድኖች (interest groups) ጉተታ ውስጥ እንዳይገባ መጠንቀቅ አለበት።አንዳንዶች ፓርቲው በአውሮፓ የኢንዱስትሪ አብዮት ጋር ሚና ነበረው በሚሉት የግለኝነት አስተሳሰብ ከፕሮቴስታንት እምነት ጋር የምያገናኙበት ስሜት በብልፅግና ፓርቲ ውስጥም የተወሰኑ ቡድኖች ፍላጎት ማጠንጠኛ እንዳይሆን  እና ከነበረው የኢትዮጵያ ዕሴት ጋር ግጭት ውስጥ እንዳይገባ ከፍተኛ የመርህ፣የዲስፕሊን እና ሁሉን የማቀፍ ሂደት መከተል አለበት። በሶስተኛ ደረጃ ፓርቲው ኢትዮጵያዊ መገለጫው ላይ በግልጥ እና በትኩረት መስራት እና የማንም ባዕዳን አስተሳሰብ  በገንዘብ ኃይልም ሆነ በተፅኖ ብዛት ስር እንዳይወድቅ እራሱን የሚፈትሽበት መንገድ እንዲኖር ሥርዓቶችን በታማኝነት መዘርጋት የሚሉት  ናቸው። 


የአክራሪ እስልምና ውጪያዊ እንቅስቃሴ

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከየትኛውም ክፍል በበለጠ መልክ የአክራሪ እስልምና የትኩረት ቦታ ነች።ለእዚህም ዋነኛ ምክንያት አክራሪ እስልምና ከዓለም ላይ ካሉት አገሮች በቀላሉ  ሊሸገግበት ብቻ ሳይሆን የተወሰኑ የህብረሰብ ክፍሎችን ይዞ በአፍሪካውያን ውስጥ በሚነሱ ቅራኔዎች ሳብያ የራሱን ሥራ መስራት ስለሚፈልግ ነው።ስለሆነም ወደ አፍሪካ በሚያደርገው መስፋፋት ኢትዮጵያን እንደ አንድ ስጋት ይመለከታታል።ለእዚህም ከሃምሳ ሚልዮን በላይ ክርስቲያን መኖርን በመጥቀስ እና የኢትዮጵያ መሬት አቀማመጥ እስከ ሶስት ሺህ ሜትር ከባህር ጠለል በላይ መገኘቱ የመካከለኛውም ምስራቅንም ሆነ ዋነኛውን  የዓለም የንግድ መንቀሳቀሻ የቀይ ባህርን ኢላማ ውስጥ ለማስገባት ብቸኛው አመቺ ቦታ በመሆኑ ነው።

ሰለሆነም በኢትዮጵያ የወቅቱ ፖለቲካዊ ሽግግር ላይ ሂደቱን በሚፈልጉት መንገድ ለመዘወር የሚፈልገው አክራሪ አካል በኢትዮጵያ የምርጫ ሂደት ጭምር ገብቶ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሂደት እንደፈለጉት ለመዘወር ማሰባቸው አይጠረጠርም።በእዚህ በኩል ኢትዮጵያውያን በሚገባ መንቃት እና በትንንሽ ጉዳዮች ከመጠመድ በዋና ዋና እና ስልታዊ ሂደቶች ላይ ማተኮር አስፈላጊ አው። 


የኦሮሞን ሕዝብ ለመረማመጃ የተጠቀመው ፅንፈኛ እንቅስቃሴ የሚቀጥለው እርምጃው  ምንድነው?

የኦሮሞ የብሄርተኝነት ጥያቄ ያነሱ ኃይሎች ላለፈው ግማሽ ክፍለ ዘመን ያራመዱት ፖለቲካ የብሔር ፖለቲካ ብቻ ሳይሆን የአክራሪ እስልምና እንቅስቃሴ ሙከራም ነው።የኦሮምያ እስላሚያ የሚባለው  እንቅስቃሴ እራሱን በተለያዩ የኦነግ አንጃዎች ውስጥ በማስገባት የኦሮሞ የብሔር ጥያቄዎችን ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር በሚያጋጭ መልኩ  ብዙ ስራዎችን ሲሰራ ኖሯል።የእዚሁ ዓላማ አራማጅ የኦኤምኤን ሚድያ በመክፈት ለኦሮሞ ብሔር የቆመ መስሎ የሚታየው  ጃዋር በኦሮሞ ብሄርተኝነት ስም  የሚሄድበት ነዳጅ በቅርቡ እንደሚያልቅበት እና ሌላ ጭንብል ይዞ እንደሚወጣ ይጠበቃል።ጃዋር  መሐመድ ከእዚህ በፊት በአሜሪካ ባደረገው ስብሰባ ላይ አክራሪ እስልምናን ኢትዮጵያ ላይ ለማስፈን የሚሄድበት መንገድ የኦሮሞ ብሄርተኝነት እንደሆነ ኦሮምያ የአክራሪ እስልምና ምቹ መጋለብያ እንደሆነች ''የሜጫ'' ንግግሩ በተሰኘው ንግግሩ መግለጡ አይዘነጋም። 

 የፅንፈኛ ቡድኑ ቀጣይ እርምጃ የሚሆነው ኦሮምያን መከፋፈል እና የራሱ የሆነ የመፈንጫ ቀጠና መመስረት ነው።ለእዚህም እንዲመቸው በመጀመርያ በኦሮምያ የምትገኘውን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ለመክፈል ''ዮሮምያ ቤተ ክህነት'' የሚል ከፋፋይ ቢሮ እንዲከፈት በኦሮምያ ሚድያ ኔት ዎርክ ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ ላይ ይገኛል።  ስለሆነም የፅንፈኛ ቡድኑን ቀጣይ አላማ በተለይ በኦሮምያ ፖለቲካ ላይ እውቀቱ አለን የሚሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባቸዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ 

በኢትዮጵያ የለውጥ ነፋስ በነፈሰባቸው ሂደቶች በሙሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የመጀመርያ ተጠቂ ነች።የውጭ ወራሪ በመጣባቸው የኢትዮያ የፈተና ዘመናት ሁሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ቀዳሚ ዕላማ ሆና ኖራለች።ፋሺሽት ጣልያን በወረራው ጊዜ አይሮፕላኞቹ ቀድመው የሚያጠቁት የቤተ ክርስቲያኒቱን ህንፃ ሲሆን በአምስት ዓመታት ቆይታው የደብረ ሊባኖስ መነኮሳትን እያሰረ ወደ ገደል ከእነ ሕይወታቸው ከመጨመር ባለፈ ፓፓሳቶቿን በአደባባይ እስከመስቀል ያልተፈፀመ የግፍ አይነት የለም።የ1966 ዓም የለውጥ ንፋስ፣የ 1983 ዓም  የመንግስት ለውጥ እና በ2010 ዓም የኢህአዴግ ለውጥ ጊዜ ሁሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ዋነኛ ኢላማ ሆነዋል።

ባሳለፍናቸው ስድስት ወራት ውስጥም በኦሮምያ ክልል በተለየ መልኩ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት እየተቃጠሉ ምእመናንም እየተገደሉ ነው። ሁኔታው በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮያውያን ዘንድ ሁሉ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል።በጉዳዩ ላይ መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ እና ማብራርያ እንዲሰጥ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ አካል ቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ የማህበራት ህብረት ጭምር ጠይቀዋል።በቅርቡም በኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ማኅበረ ቅዱሳን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በቀጥታ ደብዳቤ መፃፉን ማኅበሩ ማስታወቁ ተሰምቷል።ይህ ሁሉ ድምፅ በመንግስት በኩል ተገቢው ምላሽ መሰጠት ያለበት እና የለውጥ ሂደቱን ጤናማ እንዲሆን ወሳኝ ሚና የሚጫወት ነው።ይህ ሁኔታ ኦርቶዶክሳውያንን ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ሂደት የመገለል አዝማምያ እንዲሰማቸው ከማድረጉም በላይ ከፍተኛ ያለመረጋጋት ምክንያት ሊሆን እንደምች ማንም ጥርጥር ሊገባው አይገባም። ምክንያቱም የቤተ ክርስቲያኒቱ ኢትዮጵያን የማረጋጋት አቅም ብቻ ሳይሆን ያለው ጠንካራ ማኅበራዊ አንድነት በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ በሚፈፀመው የጥፋት ሥራ ሳብያ የመናጋት አደጋው ትልቅ ያደርገዋል።ይህንን ደግሞ የፅንፍ ኃይሎች የሚፈልጉት ጉዳይ ነው። 

በኢትዮጵያ የመንግስትነት ታሪክ ከአንድ ሺህ አምስት መቶ አመታት በላይ ነገሥታቱን ህዝቡ የሚቀበላቸው ከቆለኛው የአክራሪ እስልምና የሚያድኑት ከሆነ ብቻ ነው። ይህንን የማያደርጉ ነገስታት ላይ ሕዝብ የመሸፈት እና እራሱን በራሱ የመከላከል ሥራ አይ ብቻ ተግባር ላይ ያተኩራል።አሁንም የሚታየው ከእዚህ ብዙ የራቀ አይደለም።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሕልውናን ለመጠበቅ እና ከፅንፈኛ አካሎች ለመከላከል ትጋት የማያሳይ መንግስትም ሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር በስልጣን ላይ የመቆየት  አቅሙ ፈፅሞ የመነመነ ነው።ይልቁንም በአሁኑ በያዝነው በ21ኛው ክፍለዘመን በተበታተነ መልክ ያለ የሚመስለው የቤተ ክርስቲያኒቱ የሰው ኃይል ብቃት፣ጆግራፍያዊ ስብጥር እና ዓለም አቀፍ አቅም ሁሉ የሚንቁት ጉዳይ አይደለም።ስለሆነም የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ መንግስት በፍጥነት ትኩረት መስጠት የሚገባው ይሄው የቤተ ክርስቲያኒቱን አጥቂዎች ለፍርድ ከማቅረብ እስከ  የመጠበቅ መንግስታዊ ኃላፊነቱን መወጣት ይዋል ይደር የማይባል አንገብጋቢው ጉዳይ ነው። ይህ ካልሆነ ግን የተጠቃ አካል ሁል ጊዜ እራሱን ለመከላከል ከመንቀሳቀሱ አንፃር ጉዳዩ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ የፖለቲካ መልክ የሚቀይር ጉዳይ አይመጣም ማለት ፈፅሞ አይቻልም።

ከፖለቲካ ፓርቲዎች ውጭ የሆነው ብዙሃኑ እና ወሳኙ ሕዝብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እንዴት ተፅኖ ፈጣሪ ይሁን?

አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳይ ተከታታይ እንጂ ዋና ተዋናይ አይደለም።ይህ ደግሞ በሁሉም አገር ያለ ነው።ተዋናዮች ጥቂት ተመልካቾች ግን ብዙዎች ናቸው።ሆኖም ግን በሌሎች አገሮች ያለው ሁኔታ ተመልካቹ በልዩ ልዩ መንገድ ተመልካች ብቻ ሳይሆን ተዋናዮቹ ላይ ተፅኖ አሳዳሪ ነው።በኢትዮጵያ ግን ይህ አይታይም።መሆን የሚገባው ግን ከተመልካችነት ተፅኖ ፈጣሪነት ማደግ አለበት።ተፅኖ  ፈጣሪነቱ በሚድያ፣በሰላማዊ የተቃውሞ መንገድ ሃሳብን በመግለጥ፣ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ በማንቀሳቀስ እና በመከታተል ሁሉ ይገለጣል።

የኢትዮያን ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳይ በተመለከተ ባጭሩ ከላይ የተጠቀሱት ከብዙ በጥቂቱ እና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች እንደሆኑ ጉዳያችን ታምናለች። የፖለቲካው ዋና አንቀሳቃሽ የምጣኔ ሃብቱ ጉአይ በርግጥም በአግባቡ መታየት ያለበት እንደሆነ ይታመናል። 

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Tuesday, November 19, 2019

«ከብላቴ ወታደራዊ ማሰልጠኛ እስከ ዐቢይ አህመድ ቤተ መንግሥት» አዲስ ቃለ መጠይቅ ከሙሐዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤልክብረት

ምንጭ = አደባባይ ሚድያ 
ክፍል አንድ 


  


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Sunday, November 17, 2019

Saturday, November 16, 2019

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ደህንነቷን ለመጠበቅ በፍጥነት መውሰድ የሚገባት ሁለት የመፍትሄ ርምጃዎች (የጉዳያችን ሀሳብ)



ጉዳያችን / Gudayachn
ህዳር 6/2012 ዓም (ኖቬምበር 16/2019 ዓም)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ የለውጥ ነፋስ በነፈሰ ቁጥር የመጀመርያ ኢላማ ስትሆን ኖራለች።በ1966 ዓም የቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ መውረድን ተከትሎ ፓትርያርክ ቲዎፍሎስ በደርግ ተገደሉባት፣በ1983 ዓም ኢህአዴግ አዲስ አበባን መቆጣጠሩን ተከትሎ አቡነ መርቆርዮስ ከመንበረ ፕትርክናቸው ተነስተው እንዲሰደዱ ምክንያት ሆነ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ሲኖዶስ ተከፍላ ቆየች።በ2010 ዓም ከኢህአዴግ ጥገናዊ ለውጥ በኃላ የቤተ ክርስቲያን ሲኖዶሳዊ አንድነት ቢመለስም የቤተ ክርስቲያን መቃጠል፣የምእመናን መገደል እና ስደት በተለይ በኦሮምያ ክልል ተባብሶ ቀጥሏል። ባሳለፍነው አንድ ወር ውስጥ ብቻ በመንግስት የተረጋገጠ ሰማንያ ስድስት ኢትዮጵያውያን በፅንፈኞች መገደላቸው ተገልጧል።

ለውጡን ተከትሎ የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ለማጥቃት መልካም አጋጣሚ ያገኙ የመሰላቸው የፅንፍ ኃይሎች ቤተ ክርስቲያንን ህንፃዋን ከማቃጠል እስከ ምመናኗን መግደል እና ከይዞታቸው መንቀል ድረስ ከፍተኛ ዘመቻ ከፍተዋል።በእዚህም መሰረት ከሲዳማ ዞን እስከ ባሌ፣አርሲ እና ምስራቅ ሐረርጌ ድረስ አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፣ሴት ልጅ ጭምር በድንጋይ ተወግራ ተገድላለች፣አዛውንት በስለት ተገድለዋል። ቅዱስ ሲኖዶስም ተከታታይ የምሕላ ፀሎት ከማወጅ ባለፈ ምዕመናንን ወርደው እስከ ማፅናናት ስራዎች እየሰሩ ነው።

በእነኚህ ሁሉ ፈተናዎች ውስጥ ቤተ ክርስቲያን  አፋጣኝ መፍትሄ መውሰድ የሚገባት በተለይ ከደህንነቷ አጠባበቅ ጋር በተያያዘ ምንድነው የሚለውን ጉዳያችን እንደሚከተለው ሃሳብ ታቀርባለች። ቤተ ክርስቲያን በቅዱስ ሲኖዶስ መመርያ ሰጪነት ሁለት አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ ይገባታል። እነርሱም -

1) የቤተ ክርስቲያን የጥበቃ (የዘበኛ)  ከቤተ ክህነት እስከ አጥብያ  በአዲስ ዲፓርትመንት ማለትም በወታደራዊ ሙያ በሰለጠነ እና ዘመናዊ መሳርያ ትጥቅ ማደራጀት እና  ማዋቀር 

በኢትዮጵያ  በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የሚገኙ መንግስታዊ መስርያ ቤቶች የጥበቃ ዲፓርመንት  ራሱን በቻለ ዲፓርትመንት የሚመራ ነው።ለምሳሌ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በምሳሌነት መውሰድ ይቻልል።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የጥበቃ ክፍል አዲስ አበባ ከሚገኘው ዋናው መስርያ ቤት  እስከ ጫፍ ዶሎ መና ባሌ ያለው የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የጥበቃ ክፍል የሚመራው ራሱን በቻለ ዲፓርትመንት ነው። ይህ ማለት የራሱ በጀት አለው፣በወታደራዊ ሙያ የሰለጠኑ ባለሙያዎች፣የፀጥታ አጠባበቅ መመርያ ሁሉ አለው።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በኩል ስንመለከት ይህ አሰራር ወጥነት ባለው እና በቂ በወታደራዊ ሙያ የሰለጠነ እና በቂ ትጥቅ ያለው የጥበቃ ኃይል የላትም። ይህ ግን በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ነው።ከእዚህ በፊት ቤተ ክርስቲያን  ከላይ በተጠቀሰው ደረጃ የጥበቃ ክፍሏን ያላጠናከረችው  ለሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮች በቀላሉ ለመንግስት የፀጥታ አካላት ለምሳሌ ለፖሊስ በማሳወቅ ችግሮች ይፈታሉ በሚል ነበር።አሁን በሚታየው ተጨባጭ ሁኔታ ግን ፖሊስ እራሱ የፀጥታ ችግር በሆነበት ሁኔታ ቤተ ክርስቲያን የራሷን የጥበቃ ኃይል በፍጥነት ማጠናከር ይጠበቅባታል።

በኢትዮጵያ ሕግ ማንኛውም ግለሰብ ቤት ሆነ የእምነት ድርጅት አጥር ግቢ  ካለፈቃድ መግባት ወንጀል ነው።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ንብረት ለመሆኑ የቤተ ክርስቲያኗን ስም በበበሩ ላይ መፃፍ አንዱ አስፈላጊ ጉዳይ ነው።ፅሁፉ እያለ በር ላይ የሚገኘውን የጥበቃ አካል አልፎ ለመግባት በተለይ በኃይል ለመግባት የሚሞክር ማናቸውም አካል ላይ ጥበቃ በያዘው መሳርያ ከማስጠንቀቅያ  ጋር ቤተ ክርስቲያንን ለመከላከል ማናቸውንም እርምጃ የመውሰድ ሕጋዊ መብት አለው።ስለሆነም ቤተ ክርስቲያን የጥበቃ ኃይሏን መብታቸው እና ግዴታቸውን ማሳወቅ አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን።ከጥበቃ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን  ለምታደርገው የጥበቃ አካላት ስልጠና እና የትጥቅ ማሟላት ሂደት ሁሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ ይገባዋል። ለምሳሌ የተቀጠሩትን የጥበቃ አካላት ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ ላይ እና ከኃላ ቀር መሳርያ ቢያንስ በክላሽ ደረጃ የታጠቁ የጥበቃ ኃይል እያንዳንዱ አጥብያ ከከተማ እስከ ገጠር እንዲኖር ለማድረግ መንግስት ሕጋዊ ስልጣኑን እና ትጥቅ በግዥም የማቅረብ ሥራ መስራት አለበት።ይህ ሥራ በራሱ የመንግስትን ሥራ በተለይ በፀጥታ በኩል የሚያቀልለት ሥራ መሆኑ እሙን ነው።እዚህ ላይ ቤተ ክርስቲያን የጥበቃ ስራውን እራሷ ባደራጀችው ሕጋዊ በሆነ የጥበቃ አካል እንጂ ቤተ ክርስቲያን አንዳንድ ድርጅቶች እንደሚያደርጉት ለጥበቃ ኤጀንሲዎች ስራውን ለመስጠት ከሞከረች ትልቅ ችግር ቤትክርስትያን ላይ ሊያስከትል ይችላል።ኤጀንሲዎች ተፈላጊ እንዲሆኑ እራሳቸው የፀጥታ ችግር የሚሆኑበት አጋጣሚ በብዙ አገሮች የታየ ነው።ስለሆነም ቤተ ክርስቲያን በጥንቃቄ በራሷ ልጆች ልፀራው የሚገባ ሥራ ነው።

የጥበቃ ክፍልን (ድፓርትመንት) ቤተ ክርስቲያን በአጭር ጊዜ ለማደራጀት የሚከተሉትን ተግባራት በቶሎ መስራት ትችላለች። እነርሱም -

  • የጥበቃ ክፍሉን በአገር አቀፍ ደረጃ ማዕከላዊ አደረጃጀት እንዲኖረው ማድረግ፣
  • ክፍሉ በአገረ ስብከት እስከ አጥብያ የሚወርድ ወጥ የሆነ አሰራር፣አጠባበቅ፣የስልጠና አቅም እና የመሳርያ ትጥቅ ማሟላት፣
  • የጥበቃ ክፍሉ በተለይ በማዘዣው በቤተ ክህነት ደረጃ ያለው የጥበቃ ዋና ክፍል በአገረ ስብከት ደረጃ እና እስከ አጥብያ ድረስ ያለውን የጥበቃ  ሁኔታ ለመከታተል እንዲረዳ ቢያንስ በኮለኔል ደረጃ የሚመራ ይሆናል፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጅች የሆኑ ነገር ግን በወታደራዊ ስልጠናም ሆነ ስነምግባር የተመሰገኑ መሆን ይገባቸዋል፣
  • የጥበቃ ዲፓርትመንት በአገሪቱ ውስጥ ያሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ አጥብያዎች ስጋት የተደቀነባቸውን እና ቅድምያ ትኩረት የሚሹትን አካባቢዎች ይለያል፣ መረጃ ይተነትናል አስፈላጊ ሲሆን መንግስት ትኩረት እንዲሰጥ የቅድመ አደጋ ጥንቃቄ ማስጠንቀቅያ ይሰጣል፣
  • የጥበቃ ክፍል ከኢትዮጵያ ቴሌኮምኒኬሽን ፈቃድ ያለው የራሱ የመገናኛ ራድዮ መገናኛ ይኖረዋል።በእዚህም መሰረት በአገረ ስብከት ደረጃ እስከ አጥብያ ያለው ጥበቃ ድረስ የሚገናኝበት በመንግስት ፈቃድ ያለው የራድዮ መገናኛ መስመር ይዘረጋል።
  • የጥበቃ ክፍሉ መተዳደርያ ደንቡ በቅዱስ ሲኖዶስ ፀድቆ ሥራ ላይ ሊውል ይችላል።

2) የአይቲ (ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ) ክፍል በመምርያ ደረጃ መመስረት  

አሁን ባለንበት ዓለም አይደለም ከሃምሳ ሚልዮን በላይ ሕዝብ በስሩ የያዘች እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ያለ ትልቅ አደረጃጀት ያላት አገራዊ  አካል ቀርቶ ትንንሽ ድርጅቶችም ከአይቲ (የኢንፎርሜሻን ቴክኖሎጂ) ክፍል በመምርያ ደረጃ በቤተ ክህነት መመስረት እና ክፍሉ ከአገረ ስብከት እስከ አጥብያ ድረስ በኔት ዎርክ ማያያዝ በፍጥነት መሰራት የሚችል ሥራ ነው። የአይቲ ኔትዎርክ መመስረት በጣም ውስብስብ ሥራ እና የማይቻል አድርጎ ማሰብ አይቻልም። 

ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ ሁለት ሀብት አላት።አንዱ የሰለጠነ እና የተማረ የሰው ኃይል ሲሆን ሌላው የገንዘብ አቅም ነው። ስለሆነም የአይቲ መረቡን መዘርጋት በቤተ ክህነት ደረጃ ቅዱስ ሲኖዶስ በፍጥነት መመርያ ቢሰጥበት  ስራውን የሚከታተል ልዩ ኮሚቴ ሰይማ ስራውን የሚሰሩ በአገር ውስጥ ወይንም በውጭ የታወቁ ኩባንያዎች በጨረታ ስራውን መስጠት ትችላለች።የኔትዎርኩ ሥራ በአንዴ ሁሉም ጋር ባይደርስ ደረጃ በደረጃ ለመስራት ስራውን መጀመር ግን ጊዜ የሚሰጠው አይደለም።የአይቲ መምርያ ማስቀመጥ እና አሰራርን በአይቲ አስደግፎ መስራት ከቤተ ክርስቲያኒቱ የፀጥታ ሥራ ጋር አብፎ የሚታይ ብቻ ሳይሆን መጪውን የዋጀ አሰራር የመዘርጋት ተግባር አካል ነው።የአይቲ መምርያ መስርቶ እስከ አጥብያ ድረስ ስራውን መተግበር ለቤተክርስቲያን  የሚከተሉትን ጥቅሞች ይሰጣል። እነርሱም -


  • የቤተ ክርስቲያን የገንዘብ አጠቃቀም፣የአጥብያ ሁኔታ፣ውሎ እና ተግባራት በቀጥታ በደቀቃዎች ውስጥ ሪፖርት ለአገረ ስብከት እና ለቤተ ክህነት ለመላክ ይረዳል፣
  • በእርቀት የሚገኝ አጥብያ የፀጥታ ስጋት ቢኖርበት በደቂቃዎች ውስጥ ለሚመለከተው ሁሉ ለመግለጥ አመቺ ሁኔታ ይፈጥራል፣ 
  • ከአገር ውስጥ እስከ ውጭ ያሉ አጥብያዎች በኔት ዎርክ እንዲገናኙ ያደርጋል፣
  • ወጥ የሆነ የእቅድ ፎርማት ለመላክ ለሁሉም አጥብያዎች ማድረስ ይቻላል፣
  • አጥብያዎች ወጥ የሆነ እቅድ ትግበራ ሪፖርት እንዲልኩ እና በአገረ ስብከት እና በቤተ ክህነት ደረጃ እንዲገመገም ይረዳል፣
  • ቤተ ክርስቲያን ያላትን የሰው ኃይል፣የገንዘብ እና የማይንቀሳቀስ ንብረት በሚገባ መዝግባ ለመያዝ እና የንብረቷን ሁኔታ ለመቆጣጠር  ይረዳታል፣
  • እያንዳንዱ አጥብያ በሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መዋቅር ውስጥ የአይቲ ክፍል እንዲኖረው ቃለ አዋዲው ማሻሻያ እንዲደረግበት ይረዳል። 


ለማጠቃለል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አሁን የገጠማትን የፀጥታ ችግር ከላይ በተጠቀሱት ሁለት መንገዶች ችግሩን በዘለቄታው ለመፍታት የሚያስችላት እንደሚሆን አምናለሁ።በተለይ የጥበቃ ክፍሉ በዲፓርትመንት (መምርያ) ደረጃ ስትመሰርት በርካታ የበጎ ፍቃድ አገልጋዮች ማንቀሳቀስ የምትችልበት ዕድል አላት።በጎ ፍቃድ የጥበቃ አካላት ለማንቀሳቀስ ግን ራሱን የቻለ ጉዳዩን የሚከታተል እና በወታደራዊ ሙያ የሰለጠነ አስተባባሪ ያስፈልጋል። በእዚህ ደረጃ የተጠናከረች ቤተ ክርስቲያንን እሳትና ጎመድ ይዞ ለሚመጣ ፅንፈኛ ከጥበቃ ክፍሉ የሚሰጠውን ምላሽ ስለሚረዳ በቀላሉ አንድ አጥብያ ለማጥቃት አይደፋፈርም። ምክንያቱም  የሁሉም አጥብያ ጥበቃዎች የቤተ ክርስቲያኑን አጥር ጥሶ የሚመጣ ማንኛውም አካል ላይ የመተኮስ እና ቤተ ክርስቲያኑን የመከላከል ሕጋዊ ስልጣን ስለሚኖረው ፅንፈኛም አደብ እንዲገዛ ያስገድደዋል። በሌላ በኩል የጥበቃ ክፍሉ አንዱ አጥብያ ላይ ችግር ካለ ሌላ አካባቢ ያሉ አጥብያ የጥበቃ አካላት በራድዮ መገናኛ ተጠቅመው ችግሩ ያለበት አጥብያ  በፍጥነት የሚደርሱበት ዕድል አለ።

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Wednesday, November 13, 2019

ከዲሞክራሲ በፊት ፍትህ እንፈልጋለን! ዲ/ን ዳንኤል ክብረት



ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Monday, November 11, 2019

የኢህአዴግ ውሕደት ላይ ያተኮረው የድርጅቱ ወሳኝ ስብሰባ የፊታችን ሮብ ይጀመራል።ውህደቱ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ወደ አንድ ምዕራፍ እንዲያሸጋግር ጉጉታችን ነው።ህወሓት በውህደቱ ከመሳተፍ ሌላ ምንም ምርጫ እንደሌለው ሶስት ምክንያቶች አሉ።

ጉዳያችን /Gudayachn
ሕዳር 1/2012 ዓም (ኖቬምበር 11/2019 ዓም)

ኢህአዴግ ቀድም ብሎ በሐዋሳ ላይ በወሰነው ውሳኔ መሰረት በውሕደቱ ላይ ያተኮረው ጉባኤውን ለማካሄድ በመጪው ሮብ ለስብሰባ ይቀመጣል።እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት በውህደቱ ላይ የተስማሙ የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) ፣የዓማራ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ዓዴፓ) እና የደቡብ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ደሕዴድ)  ሲሆኑ ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ግልጥ ውሳኔውን አላሳወቀም።ሆኖም ቀደም ብሎ ድርጅቱ ባወጣቸው መግለጫዎች ውህደቱን እንደሚቃወም አስታውቆ ነበር። በሌላ በኩል ህወሓት በውህደቱ ባይሳተፍ ይህ የድርጅት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሕዝብ ጉዳይ ስለሆነ ሌሎች የትግራይ ክልልን ወክለው በውህደቱ ሂደት ላይ ለመሳተፍ  የሚፈልጉ እንዳሉ ከአዲስ አበባ የሚሰሙ ዜናዎች አሉ።

ኢህአዴግ ወደ ውህደት ስመጣ ከእዚህ በፊት በኢትዮጵያ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ የጎላ ድርሻ ያልነበራቸው ማለትም በአጋርነት ብቻ ሲጠሩ የነበሩ የሐረሪ፣የቤንሻንጉል፣የጋምቤላ፣የአፋር እና የሱማሌ ድርጅቶች በአሁኑ የኢህአዴግ ውህደት ላይ ለመሳተፍ  ስምምነታቸውን መግለጣቸው ለማወቅ ተችሏል።ሆኖም ግን በውህደቱ የውሳኔ ድምፅ መስጠት ላይ ወሳኞቹ አራቱ ድርጅቶች ማለትም ኦዴፓ፣አዴፓ፣ህወሓት እና ድህዴድ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።ከውሳኔው በኃላ ግን አጋር ድርጅቶች የውሕደት ጥያቄያቸው ወዲያውኑ ተቀባይነት እንደሚኖረው እና ውሕደቱ እንደሚከናወን ይታመናል።

ህወሓት በውህደቱ ከመሳተፍ ሌላ ምንም አይነት ምርጫ የለውም 

ይህ በእንዲህ እያለ ህወሓት በእዚህ ውህደት ላይ ከመሳተፍ ሌላ ምንም አይነት አምራጭ እንደሌለው በሶስት ምክንያቶች ማወቅ ይቻላል።እነኝህ ምክንያቶችም -

1ኛ) የትግራይ ምሁራን እና የንግዱ ማኅበረሰብ ውሕደቱን ስለሚደግፍ


የትግራይ ምሁራን እና  በተለይ ላለፉት 27 ዓመታት ከፍተኛ ሀብት ያገኘው የትግራይ ባለሀብት አሁን የሚፈልገው በየትኛውም ቦታ አድልዎ ሳይደረግበት ካፒታሉን ማፍሰስ እና መስራት ነው።ሌላው ምክንያት አሁንም ከፍተኛው ሀብት ያለው በአዲስ አበባ እና በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍል ከመሆኑ አንፃር (በተለይ የማይንቀሳቀሰው ሀብት) ውህደቱን በከፍተኛ ደረጃ ይደግፋል። ህወሓት ውህደቱን ተቃውማ ብትቆም የመጀመርያ ጠብ ያለባት ከእዝህኛው የህብረተሰብ ክፍል ጋር ነው።

2ኛ) ህወሓት በሌላ የፖለቲካ ድርጅት የመተካት ዕጣ ሊገጥማት ስለሚችል

ህወሓት የኢህአዴግን ውህደት አልቀበልም ብትል ለተወሰነ ጊዜ ከማኩረፍ እና የተወሰኑ ችግሮች ለመፍጠር ከመሞከር ባለፈ በዘለቄታው ግን ሕወሃትን የሚቃረን የፖለቲካ ድርጅት በቀጥታ ወደ ውህደቱ የትግራይን ሕዝብ ወክሎ ሊቀላቀል ይችላል። ይህ ማለት ከአረና ትግራይ ጀምሮ ሌሎች አዳዲስ ድርጅቶች መፈጠራቸው ስለማይቀር ህወሓት በውህደቱ ባለመሳተፍ ትግራይ የነበራትን የፖለቲካ እና ማኅበራዊ መሰረት የማጣት ዕጣ ሊገጥማት ስለሚችል ከመዋሃድ ሌላ አማራጭ የለም።

3ኛ) ውህደቱ በራሱ ለሕወሀት ጥቅም ስላለው 

ህወሓት ከኢህአዴግ ውህደት ተጠቃሚ እንጂ ተጎጂ አይደለችም።ህወሓት የበላይ በሆነችበት ኢህአዴግ ውስጥ ውህደት ላይጠቅማት ይችላል።አሁን ግን የበላይነት በሌለበት የፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ህወሓት በውህደት ውስጥ በመሆን ቢያንስ ትግራይ ያላትን  የበላይነት በምርጫው ወቅት አስጠብቆ ሌላ አመቺ ጊዜ መጠበቅ ብቸኛው አማራጭ ነው።ስለሆነም  ውህደቱን ከመቀበል ውጪ አማራጭ የጥቅም ሜዳ ሊኖራት አይችልም።


ስለሆነም ውህደቱ ሙሉ በሙሉ የሚሳካ እንደሚሆን ከወዲሁ ማወቅ ይቻላል።

በመጨረሻም የኦሮሞ የፅንፍ ኃይሎች ይህንን ውህደት በመቃወም አንዳንድ መግለጫ ሲሰጡ እንደሰነበቱ ይታወሳል።ሆኖም ግን ይህ ውህደት አንዱ ይዞ የሚመጣው ጉዳይ  የፅንፍ የኦሮሞ ድርጅቶችን ለብቻቸው የመነጠል መልካም የአደጋ ዕድል ይዞላቸው ይመጣል። ለእዚህም ነው ውህደቱን የፈድራሊዝም ጠላት እንደሆነ ለመለፈፍ ሲሞከር የከረመው። በእርግጥ ውህደቱ በርካታ ጥያቄዎች የሉትም ማለት አይደለም። ለምሳሌ ከውህደቱ በኃላ ሌላ የተረኝነት ወይንም አንዱ የበላይ የሚሆንበት ሂደት እንዳይከሰት የሚወሰዱ ምን እርምጃዎች አሉ? ውህደቱ ፍፁም ውህደት ካልሆነ እና የጎሳ አደረጃጀችን ካላጠፋ መልሶ የጎሳ ስሜትን እንዳይፈጥር እንዴት መከላከል ይቻላል? እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች መመለስ ያስፈልጋል። በሌላ በኩል እነኝህ ጥያቄዎች የሚወሰኑት በክልሎች አከላል ዙርያ ያለው ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚነሳ ጥያቄ እንደሚሆን ይታመናል። ለሁሉም ግን የኢህአዴግ ውህደት የህዝብ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ፖለቲካ ወደ አንድ ምዕራፍ እንዲያሸጋግር ጉጉታችን ነው።

ድምፃዊ አብርሐም ገብረመድሕን ''አገሬ''



ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Tuesday, November 5, 2019

Leaked document: Cairo, Kampala, Juba conspiring against Addis Ababa ግብፅ፣ዑጋንዳ እና ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ ታላቁ ሕዳሴ ላይ እያሴሩ መሆኑን አንድ ምስጢራዊ ዶክመንት አመለከተ

El-Sisi (right, Museveni (left). Photo: Egypt Today/File
Kampala, November 5, 2019 (SSNA) — 
The leaders of South Sudan, Uganda, and Egypt are working days and nights to prevent Ethiopia from completing the construction of the $4 billion dollars Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD), a Ugandan ex-spy who uses a pseudonym name James Moises to protect his identity has claimed.
In a 3-page documented he delivered to a South Sudan News Agency’s (SSNA) reporter through an intermediary in Kampala, the former intelligence officer who previously worked for Uganda’ s External Security Organisation (ESO) exposes what seems to be an extensive campaign to put more pressure on Ethiopia through diplomatic and military means. The text also reveals how the three countries are coordinating their corporation to achieve their interests in the East African region.
“We have a situation where my country [Uganda] has become the number one ally of Egypt in the region. There is no problem of being an ally of a sovereign nation, but it is wrong when you do it to cause harm to other countries,” James wrote.
James’s claims point finger at Egypt, Uganda, and South Sudan.
“The Egyptian President Abdel Fattah El-Sisi, Ugandan President Yoweri Museveni, South Sudanese President Salva Kiir are conspiring against Ethiopia to make sure Ethiopian mega project Grand Ethiopian Renaissance Dam does not go forward,” he explains, adding, “I have worked for many years as a spy and most of my assignments were in the East African region. I have never seen anything like it before.”
The former ex-spy accuses the three nations of being driven by self-fish interests.
“El-Sisi, Museveni, and Kiir have their own interests they want to achieve. The President of Egypt wants to continue controlling the water of the Nile River, Uganda wants to keep Salva Kiir in power with help from Egypt, and South Sudan’s leader future depends on Museveni, James explains.
In the document, James says he uncovers “serious techniques” designed to prevent Addis Ababa from completing its Dam. He asserts that “the plan includes Uganda and South Sudan to assist Egypt” if Cairo decides to go to war with Addis Ababa.
James, who claims he has “Ugandan best intelligence connections” also accused Egypt of using ‘covert channels’ to deliver weapons to South Sudan.
“El-Sisi always delivers weapons and ammunition to Juba in two different ways. He delivers them in the form of medicines or agricultural products, or he uses Uganda as an intermediary. These are all cover channels,” he says.
The construction of the Ethiopian Grand Ethiopian Renaissance Dam began in 2011. The project encountered several obstacles before including an attack by a rebel group. The Ethiopian authorities accused Egypt and Eritrea of being the sponsors of the rebel.
The 6.4GW project is set to become the biggest hydropower dam in Africa if completed.
James Moises is known for being the first foreigner to expose secrets between Uganda and South Sudan. His July 2013 article exposed Kiir and Museveni’s plan in weeks, months, and years leading up to the eruption of civil war in December 2013.
Source = South Sudan News Agency 
                November 5, 2019 (SSNA) 
ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Saturday, November 2, 2019

የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን እራሱን እያጠናከረ ነው። አዲስ የቦርድ አባላት መርጧል።ኢትዮጵያውያን የራሳችሁን ድምፅ ደግፉ! (የ3 ደቂቃ ቪድዮ ይመልከቱ)

ጉዳያችን / Gudayachn
ጥቅምት 23/2012 ዓም (ኖቬምበር 3/2019 ዓም)
video = ESAT 


ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Friday, November 1, 2019

ኢትዮጵያውያን ከአገር ቤት እስከ ባህር ማዶ እጃችሁ ይያያዝ፣የኢትዮጵያ ትንሳኤ ቀርቧል። (ጉዳያችን መልዕክት)

ጉዳያችን / Gudayachn
ጥቅምት 22/2012 ዓም  (ኖቬምበር 2/2019 ዓም)

ከንፈር ሳይነቃነቅ ልሳን ሳይጋራ፣
በዝምታ ድባብ በዝምታ ጎራ፣
ሳየወሩ ማውራት መልካም ባልንጀራ።

የአንደኛ ደረጃ ተማሪ እያለሁ ግጥም ለመሞነጫጨር አንድ ሰሞን ተፍ ተፍ ያረገኝ ነበር።ከላይ ያለው ስንኝ አንድ በዝምታ በማውራት የሚግባቡ ገፀ ባህርያት ከአፋቸው አንዳች ቃላት ሳይወጣ የተግባቡ ሰዎች በገለጥኩበት መጣጥፍ ላይ የተጠቀምኩበት አገላለጥ ነበር። ዛሬ ይህንን ፅሁፍ ሳስብ ሃሳቤን የሚገልጥልኝ መሆኑን ስላሳመነኝ መግቢያ አደረኩት።

በዛሬው የጉዳያችን መልዕክት በረጅሙ ሃሳቦችን በማርዘም አላደክማችሁም።ሳይጀመር አለቀ እንዳትሉ እንጂ፣ የመልእክቱ ዋና ጭብጥ ሲጠቃለል ኢትዮጵያውያን ከደብረ ዳሞ፣ምፅዋ  እስከ ሞያሌ፣ ከአኮቦ እስከ ፈርፈር፣ከአሜሪካ እስከ ጃፓን፣ከፊንላንድ እስከ ደቡብ አፍሪካ ያላችሁ ኢትዮጵያውያን እጅ ለእጅ የምንያያዝበት፣ በጎሳ፣በሃይማኖት ሳንለያይ እና በልዩ ልዩ ጉዳዮች፣ በማኅበራዊ ቦታዎች ሁሉ ወጣቶች፣እናቶች፣አባቶች፣ሁላችሁ የምትያያዙበት ጊዜ ነው።

ኢትዮጵያውያንን በአንድነት ለማያያዝ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያላችሁ ሁሉ ኢትዮጵያውያን  እርስ በርስ ግንኙነታቸውን እንዲያዳብሩ ለመስራት ተነሱ።እናቶች ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን እጅ ለእጅ አያይዙ እንጂ ከቤታችሁ ሆናችሁ የምትተክዙበት ጊዜ አይሁን። አባቶች ወደ ጎዳናው ውጡ  ኢትዮጵያውያንን እጅ ለእጅ አያይዙ፣ የሃይማኖት አባቶች ወደ ጎዳናው ውጡ፣ በክልል መሬት የተጣሉትን እና የፖለቲካ እሾህ የተዘራባቸው የግጭት ቀጠናዎችን ባዶ የተረት ተረት ሥራ መሆኑን አውጁ። እናቶች ቡና ከቤታችሁ አታፍሉ፣ አውራ ጎዳናው ዳር ውጡ፣ጉዝጉአዙን ጎዝጉዙት ወጣቶቹን ጥሩ የሰፈራችሁን ሰው ጥሩ እጅ ለእጅ አያይዙ። የኢትዮጵያ አምላክ ኢትዮጵያውያንን ሊታደግ ከበር ላይ ቆሟል።እንዳይገባ በር የዘጋበት ኢትዮጵያውያን እጅ በእጅ አለመያያዝ ነው።

በባሕር ማዶ ያላችሁ።በአገር ቤት ሰላም ከማውራታችሁ በፊት በዋሽንግተን ጎዳና የተገለማመጠ ካለ እጅ ለእጅ አያይዙ፣ አገር ቤት ለሚመጣ ፈተና ሁሉ አለሁልህ ለማለት የባሕር ማዶዎቹ በቅድምያ ሳትውሉ ሳታድሩ እጅ ለእጅ ተያያዙ። የኢትዮጵያ ትንሣኤ በር ላይ ነው።ትንሣኤዋን ለማየት የምትታለፈውን ትንሽ መራራ መዝለል ብቻ ይፈለጋል።ይህችን ትንሽ መራራ  ለመዝለል ኢትዮጵያውያን ከአገር ቤት እስከ ባሕር ማዶ ሳትተያዩ የምትግባቡ እና አንዱ አንዱን ሳይጠብቅ እጅ ለእጅ የምትያያዙ  መሆን ያስፈልጋል። ለእዚህ ደግሞ እናቶች፣ወጣቶች እና አባቶች በሙሉ የማንንም ትእዛዝ ሳትጠብቁ ኢትዮጵያውያንን  ለማያያዝ ራሳችሁ ኃላፊነት ወስዳችሁ ከሰፈራችሁ ጀምሩ።ከንፈር ሳይነቃነቅ ተግባቡ፣ልሳን ንግግር ሳያወጣ ተግብሩት።ኢትዮጵያውያን ሳታወሩ ተግባቡ እና እጅ ለእጅ ተያያዙ።የኢትዮጵያ ትንሣኤ በር ላይ ነው።ይህ ተራ እና ባዶ ምኞት አይደለም።እውነት ነው።ውጤቱ እያንዳንዱ ግለሰብ በሚያሳየው ፍሬ ይወሰናል።

ከንፈር ሳይነቃነቅ ልሳን ሳይጋራ፣
በዝምታ ድባብ በዝምታ ጎራ፣
ሳየወሩ ማውራት መልካም ባልንጀራ።

ድምፃዊው ጥላሁን ገሠሠ መልዕክት አለው።



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።