ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, November 29, 2019

በያዝነው ሳምንት መጀመርያ በቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ ቄሮ በሚል ስም ግጭት ከፈጠሩት ውስጥ አንዱን ያዳኑት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ናቸው። (ቪድዮ ይመልከቱ)

  • የቦሌ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ከተከሉት የቤተ ክርስቲያን አሰሪ ኮሚቴ አባላት ውስጥ አርበኛው አብዲሳ አጋ እንዳሉበት ያውቃሉ?
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በተደራጀ መልክ ጥቃት እየተፈፀመ እንደሆነ የሚታይ ነው።በቤተ ክርስቲያን ላይ ጥቃት የሚያደርሱት አካላት በዋናነት በፅንፍ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ እና በተደራጀ መልክ ከፅንፈኞች አመራር እንደሚቀበሉ ይነገራል። እራሱን ቄሮ ከተሰኘው ቡድን ውስጥ ብዙዎች በሰላማዊ መንገድ እንደሚንቀሳቀሱ  እና ፅንፈኘነትን እንደማይደግፉ በእየሚድያው ላይ ሲናገሩ ይሰማል።ሆኖም ግን ከቄሮ ውስጥ አሁንም በፅንፍ አደረጃጀት ከፅንፍ አካል መመርያ የሚቀበሉ እንዳሉ የሚናገሩ ግን ብዙዎች ናቸው።

ህዳር 15/2012 ዓም በቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ ይሄው የፅንፍ ቡድን በቤተ ክርስቲያን ላይ ጥቃት ለመፈፀም ሞክሯል።ጳጉሜን 3/2011 ዓም ላይም በአውደ ምህረት ላይ ''አላህ ወአክበር'' ለማለት የሞከረ እና ብጥብጥ ለመፍጠር የሞከረ ነበር። በሰሞኑ ጥቃት ግን አንዱ በተለይ ከጅማ የመጣ የተባለውን ሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ አስገብተው ከህዝብቁጣ ያዳኑት እና ለሕግ አካላት በመስጠት መልካም ተግባር የፈፀሙ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ሊመሰገኑ ይገባል።

በነገራችን ላይ የእዚህ ፅሁፍ አቅራቢ የቦሌ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ለረጅም ጊዜ የሚያውቀው ከመሆኑ አንፃር የቤተ ክርስቲያኑ የኃላ ታሪክ ላይ ቤተ ክርስቲያኑ ተከላ ላይ ኮሚቴ ከነበሩት አባቶች መካከል በቦሌ መንገድ ወሎ ሰፈር መኖርያቸው  የነበረው አርበኛው አብዲሳ አጋ እንደነበሩ መረጃውን በወቅቱ ከነበሩት አባቶች በቀጥታ መስማቱን በእዚህ አጋጣሚ ለመግለጥ ይፈልጋል። ዛሬ በቄሮ ስም የተደራጁ የፅንፍ አካሎች የአርበኛ አብዲሳ አጋን ሥራ  ለማፍረስ የሚደረግ ሙከራም መሆኑን ልብ ይሏል።

ህዳር 15/2012 ዓም በቦሌ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ምን ተፈጠረ? ቪድዮውን ይመልከቱ።

ከደብሩ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ምክትል ሊቀመንበር እና የሰንበት ትምህርት ቤቱ አገልጋይ ከአቶ መስፍን  በዳዳ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ 


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...