Friday, August 28, 2026

የኢትዮጵያ ወዳጅ ንጉስ ልጅ ዛሬ ከእዚህ ዓለም አረፉ። ለኖርዌይ ትልቅ የሃዘን ቀን ሆኗል።Norway's King Harald V has died at the age of 89

በዚህ አጭር ዘገባ ውስጥ የሚከተሉትን ያገኛሉ።
  • ስለ ንጉስ ሃራልድ በጥቂቱ
  • የንጉስ ሃራልድ አባት ንጉስ ኦላቭ እና ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ የት ተዋወቁ?
ንጉስ ሃራልድ አምስተኛ የኖርዌይ ንጉስ



=====================
ጉዳያችን ልዩ ሪፖርት
Gudayachn Special Report
=====================
የኖርዌይ ንጉሥ ሃራልድ አምስተኛ ባለፈው ሳምንት ልዩ የደም ሕመም ሕክምና ከተደረገላቸው በኋላ እንደሚያገግሙ ተስፋ ተጥሎ ከቆየ በኋላ በ89 ዓመታቸው ዛሬ ማረፋቸው ታውቋል።በኦስሎ የሚገኘው ብሔራዊ ቤተ መንግሥት ዛሬ ዓርብ ነሐሴ 22፣2018 ዓም ( ነሐሴ 28/2026 ዓም እኤአ) በኦስሎ ዩንቨርስቲ ስር በሚገኘው ብሔራዊ ሆስፒታል (ሪስክ ሆስፒታል) የኖርዌይን ንጉስ ሃራልድ 5ኛ ማረፍ ከማለዳው በ06:35 የኦስሎ ሰዓት አቆጣጠር ከተገለጸ በኋላ በቤተ መንግሥቱ ጣሪያ ላይ ያለው የንጉሣዊ ባንዲራ ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ ሆኗል። የንጉሱ የቀብር ስነ ስርዓት እስኪከናወን ድረስም በኖርዌይ የሐዘን ቀን የታወጀ ሲሆን፣የንጉሱን ማረፍ የሰሙት ኖርዌጃውያን ከማለዳ ጀምሮ ወደ ቤተ መንግስት በመጉረፍ  አበባና የኖርዌይን ሰንደቅ ዓላማ በማስቀመጥ ላይ ይገኛሉ።

ሃራልድ ከ14ኛው ክፍለ ዘመን ወዲህ በኖርዌይ የተወለዱ የመጀመሪያው ንጉሥ ሲሆኑ። ልጃቸው ሃኮን በ53 ዓመታቸው ንግስናውን መተካታቸውን ከኖርዌይ የመጣው ዘገባ ያመለክታል።

ንጉስ ሄራልድ 5ኛ በስልጣን ዘመናቸው የኖርዌይ ንጉሣዊ አገዛዝ ስለ ንጉሣዊው ቤተሰብ የፋይናንስና የጤና ጉዳዮች የበለጠ እኩልነትና ግልጽነት እንዲያሳይ ያደረጉ ንጉስ ናቸው ሲሉ የኖርዌይ ታሪክ ምሁርና የቲቪ2 ንጉሣዊ ዘጋቢ ኦሌ-ጆርገን ሹልስሩድ-ሃንሰን ይናገራሉ።

ንጉስ ሃራልድ የተወለዱት የካቲት 21 ቀን 1937 ዓም እኤአ በኦስሎ አቅራቢያ በሚገኘው የስካጉም እስቴት ውስጥ ነው። አምባገነኑ አዶልፍ ሂትለር በሁለተኛው የዓለም ጦርነት መጀመሪያ ላይ የናዚ ጀርመን ኖርዌይን ወረራ ባዘዘበት ጊዜ የሦስት ዓመቱ ልጅ ነበሩ።

የሃራልድ እናት ከልጆቻቸው ጋር ወደ ስዊድን ድንበር አቋርጠው ሸሽታ በፕሬዝዳንት ፍራንክሊን ዲ ሩዝቬልት ግብዣ ወደ አሜሪካ ተጉዘዋል።

ልዑል ሃራልድ በጦርነቱ መጨረሻ ከቤተሰባቸው ጋር ወደ ኖርዌይ ተመልሰው እና ትምህርት እና የግዴታ ወታደራዊ አገልግሎታቸውን አጠናቀዋል። በ1957 እኤአ ሃራልድ የዘውድ ልዑል ሆኑ፣ ከ1960 እስከ 1962 ዓም እኤእ በኦክስፎርድ በሚገኘው ባሊዮል ኮሌጅ ማህበራዊ ሳይንስ፣ ታሪክ እና ኢኮኖሚክስ ተምየተማሩት ንጉስ ሃራልድ 5ኛ ወደ ትዳር ሕይወታቸው የገቡበት አጋጣሚም አስገራሚ ነበር። 

ነገሩ እንዲህ ነው፡ በአንድ ግብዣ ላይ የአንድ ነጋዴ ልጅ ሶንጃ ሃራልድሰንን የተዋወቁት የዛንጊዜው ልዑል ሃራልድ፣ እሷን ለማግባት እስኪፈቀድላቸው ዘጠኝ ዓመታት መጠበቅ ነበረባቸው። በመጨረሻም ሶንጃን ማግባት ካልቻሉ ላጤ ሆኖነው እንደሚቆዩ ለአባታቸው እንደነገሯቸው፣ ንጉሥ ሃራልድ በአንድ ወቅት ለኖርዌይ የህዝብ ብሮድካስተር (ኤንአርኮ) ተናግረው ነበር።ሆኖም አባታቸው በመጨረሻ ፈቃዳቸውን ስለ ሰጡ ጥንዶቹ በኦስሎ ካቴድራል ነሐሴ 29 ቀን 1968 ዓም እኤአ ተጋቡ።

በሐምሌ 2011 እኤአ ንጉስ ሃራልድ ኖርዌይ ከባድ ፈተና በገጠማት ጊዜ ማለትም በጽንፈኛው ብሬቪክ በኦስሎ ውስጥ በመኪና ቦምብ ስምንት ሰዎችን ሲገድልና፣ በኡቶያ ደሴት ወደሚገኝ የወጣቶች ካምፕ በመሔድ  69 ወጣቶች (ባብዛኛው የአርባይድስ ፓርቲ ወጣት ክንፍ አባላት ያሉበት ብዙዎቹ በአስራዎቹ ውስጥ የነበሩቱን) ከገደለ በኋላ በኖርዌይ በደረሰው ሃዘን ንጉስ ሃራልድ ሕዝቡን ያጽናኑበት መንገድ ዛሬም ድረስ በብዙ ኖርዌጅያውያኖች ዘንድ ሲታወስ ይኖራል። ንጉሱ በእዚሁ ለሕዝብ ባደረጉት ንግግር የእንባ ሳግ ለቅሶ እየተናነቃቸው በቴሌቭዥን ባሰሙት ንግግር እንደ አባት፣ አያት፣ ባል እና ንጉሥ ለተጎጂዎቹ እና ለቤተሰቦቻቸው በቀጥታ በተላለፈ የቴሌቭዥን መልዕክታቸው ሁኔታውን ሲገልጹ ፡ "የህመማችሁን ጥልቀት መገመት እችላለሁ። የዚህች ሀገር ንጉሥ እንደመሆኔ መጠን ለእያንዳንዳችሁም እጨነቃለሁ" ብለዋል።

እኤአ በ2016 ዓም ደግሞ ንጉሱ ሃራልድ የሰው ልጅ ዘር አንድ መሆኑን እና በኃይማኖትም ላይ ልዩነት መደረግ እንደሌለበት በገለጹበት ንግግር ላይ እንዲህ ብለው ነበር፡ ''ኖርዌጂያውያን "ከአፍጋኒስታን፣ ፓኪስታን እና ፖላንድ፣ ከስዊድን፣ ከሶማሊያ እና ከሶሪያ የመጡ መሆናቸውን ማወቅ አለብን '' ብለዋል።

ንጉስ ኦላቭ እና ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ


በኢትዮጵያ እና በኖርዌይ መካከል ረዘም ያለ ታሪካዊ ግንኙነት አለ።ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ እና  የኖርዌይ ንጉሳዊ ቤተሰብ በቅርብ የተዋወቁት በሁለተኛው ዓለም ጦርነት መጀመርያ አካባቢ ለንደን ላይ ነበር።በወቅቱ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ የጣያንን ኢትዮጵያ መውረር በወቅቱ የዓለም ማኅበር ተብሎ ለሚጠራው የዛሬው የተባበሩት መንግሥታት ለማቅረብ ለአቤቱታ እንግሊዝ ነበሩ።በወቅቱ የንጉስ ሃራልድ 5ኛ አባት ንጉስ ኦላቭ ከቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ጋር የተዋወቁበት ጊዜ ነበር።የሁለቱ ንጉሶች ግንኙነት ሀገሮቻቸው ከፋሺሽት እና ናዚ ነፃ ከወጡ በኋላም ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ጉብኝት በኦስሎ ኖርዌይ እኤአ 1954 ዓም


ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ ኖርዌይን የጎበኙት በ1954 ዓም እንደ ኤውሮፓውያን አቆጣጠር ነበር ።በመቀጠል የኖርዌይ ንጉስ ኦላቭ ኢትዮጵያን በ1959 ዓም እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር ይፋዊ ጉብኝት አደረጉ።ኖርዌይ ኢትዮጵያ የባህር ኃይሏን ምፅዋ እና አሰብ ላይ ስትመሰርት በስልጠና የረዳች የመጀመርያ ሀገር ነች።

ዛሬ ለኖርዌይ ሕዝብ ታላቅ የሃዘን ቀን ነው።ለአዲስ ዓመት በልዩ የማጽናኛና የማበረታቻ ቃላት ለሕዝቡ መልዕክት የሚያስተላልፉት፣በግንቦት 17 ቀን ለኖርዌይ ብሔራዊ የሕገመንግስት ቀን ላይ በቤተመንግስታቸው ሰገነት ላይ ሆነው በዓሉን ለመታደም በሰገነቱ ሥር የሚያልፉትን ከሕጻናት እስከ አዋቂ የሆኑ በሺህ የሚቆጠሩ ኖርዌጅያውያንን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ሆነው ሰላምታ እየሰጡ በልዩ ፈገግታ የሚቀበሉት ንጉስ ሃራልድ አርፈዋል።ይህ ለብዙዎች የእርሳቸውን ሚዛናዊ አስተሳሰብ እና ለሰውልጆች ሁሉ ያላቸውን ፍቅር ለሚያውቁ ሁሉ ታላቅ የሐዘን ቀን ሆኗል።ለንጉሱ ዕረፍተ ነፍስን ለቤተሰቦቻቸውና ለኖርዌይ ሕዝብ መጽናናትን እንመኛለን።
====================////==============

Friday, August 14, 2026

የኢትዮጵያ ወቅታዊ ፖለቲካ፣ የአፈጀው የአዛውንቶች ክበብ፣ ''ፅንዶ'' እና ቅምጥሎቹ ''ባንዳ'' ዩቱበሮች በአውሮፓና አሜሪካ።



+++++++++++++
ጉዳያችን ወቅታዊ ምጥን
+++++++++++++

መንደርደርያ

ኢትዮጵያ በዘመን አቆጣጠሯ ስንሔድ የሐያ አንደኛውን ክ/ዘመን የመዠመርያ ሩብ ክፍለዘመን ለማጠናቀቅ ሰባት ዓመታት ብቻ ቀርተዋታል። ያለፈው ሐያኛውን ክፍለዘመን በአጭሩ ለማስቀመጥ የነፃነት እና የሉዓላዊነት ክብሯን ለማስጠበቅ ከጣልያን ሁለተኛ ወረራ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ መስዋዕትነት የተከፈለበት። የነፃነት ድሉን ተከትሎ የዓለምን ወቅታዊ ሁኔታ ተንተርሶ እራሷን ነጥራ ለማውጣት የታገለችበት ጊዜ ሲሆን በእዚህ ትግል ውስጥ ንጉሱ በሐገር ውስጥ ከጎጃም እስከ ትግራይ በሽፍትነት፣ከባሌ እስከ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ በተቃውሞ፣ከቤተመንግስት እስከ የመንግስት ፍንቀላ ሙከራ ተደርጎባቸዋል። በእዚህ ሁሉ መሃል ግን የቀዳማዊ ኃይለስላሴ መንግስት ለኢትዮጵያ የዘመናዊ ስልጣኔ እና ትምሕርት በር ለመክፈት ዕድሉን ያገኘ መንግስት ነበር። ከንጉሱ ቀጥሎ ኢትዮጵያ በርዕዮተ ዓለም ንትርክ ውስጥ ገብታ ብትቸገርም ለሀገሪቱ ታሪካዊ ጠላቶች ያልተመቸች ሀገር ሆና ኖራለች።

ኢትዮጵያ ለታሪካዊ ጠላቶቿ አመቺ የሆነችው በኢሕአዴግ ሕወሓት ዘመን ነው። ይሄውም በቀዳሚነት የባሕር በሯን ትታ መሪዋ አቶ መለስ የባሕር በር '' የገበያ ጉዳይ ነው '' በሚል ትርክት እየተነገራት፣ሀገሪቱ የአስተዳደር ክልሏን በብሔር ከፋፍላና ''እስከመገንጠል '' የሚለውን ሕግ በአንቀፅ 39 ላይ ሰንቅራ የምትሔድ አሳዛኝ ሀገር ሆና ኖራለች። በእዚህ ዘመን የኢትዮጵያ ተቋማት የግለሰብ ብቻ ሳይሆን የሆነ አካባቢ የግል ቤት እስኪመስል ድረስ ከመቀረጹ በላይ የመከላከያ ሰራዊቷ በዕውቀት ላይ ያልተመሰረተ ዘመኑን ያልዋጀ እና እጅግ አደገኛ ደረጃ ላይ የነበረበት ጊዜ ነበር። በእዚህ ሁሉ ሂደት ውስጥ ነው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግስት ወደ ስልጣን የመጣው።

ወቅታዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ

አሁን ያለንበት የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሂደት ከምንግዜውም በላይ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች መዘውር በእጅጉ ከመራቁም በላይ የማይገመት አካሄዱ እና የግቡ እርቀት እና ምጥቀት ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተለያየ ተልዕኮ የያዙ ጠላቶቿን ግራ ያጋባ ሆኗል።
ፖለቲካው በመጀመርያ ደረጃ የጠራ አቋሙን በግልጽ አስቀምጧል ይሄውም በሀገር ውስጥ የኢትዮጵያን ሕብረብሔራዊ አንድነት ማረጋገጥ ሲሆን በውጭ የኢትዮጵያን ጥቅም በማንኛውም መንገድ አሳልፎ በማይሰጥ መልኩ ማስከበር ነው። በሀገር ውስጥ ያለው ፖለቲካ ክኢሕአዴግ የቀድሞው ሕወሃት ሰራሽ የጎሳ ፖለቲካ ጋር እየተማታ አልፎ አልፎ መንገራገጭ ቢገጥመው ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን ሐዲዱን በትክክል እንደያዘ ለመረዳት ብዙ ምርምር አይጠይቅም። ለእዚህ ደግሞ ዋና መሰረቱ የአብዛኛው ሕዝብ በተለይ በለየለት ጎሳዊ ፖለቲካ የተንገላታው ወጣት ሕብረብሔራዊ አንድነትን አጥብቆ መፈለጉ እና ይህ ብቻ ኢትዮጵያን ሊያሻግር መቻሉን የማመኑ ዕውነታ ነው። 

እዚህ ላይ መሰመር ያለበት ጉዳይ የአክራሪ ብሔርተኞች የፖለቲካውን መዘውር ለመቆጣጠር ጥረት አያደርጉም ወይንም ለማድረግ አልሞከሩም ማለት አይደለም።ነገር ግን ይህ ሙከራ ባብዛኛው ከሽፏል። የቀረው የያዘው የጎጥ በሽታ እስኪለቀው በትንንሽ ማባበያ ''ሕክምና'' እየተደረገለት ነው።ይህ ሂደት ቀጥሎ ተተኪው ትውልድ በሕብረ ብሔራዊ አስተሳሰብ ተቃኝቶ የኢትዮጵያን ተቋማት በሚገባ በኢትዮጵያዊነት ማረስረስ ሲጀምር የጃጀው ኢትዮጵያን የማመስ ፖለቲካ በራሱ ተሽመድምዶ ይንኮታኮታል። አሁን በምናየው መልኩም ከኢትዮጵያ ቴሌቭዥን እስከ የኢትዮጵያ ሙዜሞች፣ከትምሕርት ፖሊሲ እስከ ውጪ ፖሊሲ በዘመነ ኢህአዴግ እና የቀድሞው ሕወሃት የተጎሳቆለው ኢትዮጵያዊነት በሚገባ እየተቀነቀነ ነው። ይህ ሂደት ሃገር ይሰራል፣የተሳሳተ ትርክት ያርማል፣ ትውልድ ያጋምዳል።

ባፈጀ አስተሳሰብ የሚዳክረው የአዛውንቶች ክበብ  ''ፅንዶ'' ተልዕኮው ኢትዮጵያን ማፍረስ እንጂ መንግስት መቀየር አይደለም።

ከስሙ ስያሜ ገና ''ፅምዶ'' ይባል ''ፅንዶ'' ገና የሚጨቃጨቀው የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የዳቦ ስም እንደ 1969 ዓም የኢሕአፓ እና መኢሶን ''እናሸንፋለን '' ይባል '' እናቸንፋለን'' የሚለው ጭቅጭቅ ያልተላቀቀ ነገር ግን ከባዕዳን የሚገኝ ድርጎ በአንድ ጣሳ ውስጥ እንዲገኝ ያደረገው የዘመናችን ግራ የተጋቡ የአዛውንቶች ክበብ ሆኖ ብቅ ብሏል። ስካር እና ምኞት፣ ማለም እና ዕውነታ የተደባለቁበት ስብስብ ነው። ስብስቡ ''የጨነቀ ዕለት'' የሚሉት ነው። መሰረተ ሀሳቡን ከማኅበራዊ ትስስር እና ከቋንቋ ጋር ሊይስተሳስረው የሚሞክርበት ዐውድ በራሱ የዕውር ድንብር አካሄድ ነው። ፅንዶ የድፍረቱ ድፍረት ከአማራ እና ሌሎች ክልሎችንም ስነ ልቦና ሰልቦ በእርሱ ኢትዮጵያን የማፍረስ አጀንዳ ስር ለማሰለፍ ሲታትር ሰዎቹ የት ነው የነበሩት ያስብላል።

ቅምጥሎቹ ባንዳ ዩቱበሮች በአውሮፓና አሜሪካ የኢትዮጵያ የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ሽርሽር 

ይህ የአዛውንቶች ያፈጀ የጎጥ ጥምረት ወላጅ አባቱ ኢትዮጵያን ማተራመስ የምፈልጉቱ ታሪካዊ ጠላቶች ቢሆኑም በትግራይ እና በኤርትራ ሕዝብ እንዲሁም በዐማራው እና ኦሮሞው ደም እየነገዱ ኑሯቸውን በውጭ ሀገር ያደረጉት ቅምጥሎች ተግባር ግን በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ቅምጥሎቹ ከሚኖሩበት ሀገር ሶፋ ላይ ሳይወርዱ በዩቱብ የኢትዮጵያን ወጣቶች ተዋጉ እያሉ ሲለፍፉ ያመሻሉ። በቀጣይ ቀን ቅምጥሎቹ ዩቱበሮች በአሜሪካና አውሮፓ የኢትዮጵያውያን የእግርኳስ ውድድር ላይ ከልጆቻቸው ጋር ሲምነሸነሹ ማምሸታቸውን፣ ወይን እና ውስኪ መጠጣታቸውን እና ለልጆቻቸው የገዙትን መጫወቻ ከራሳቸው ጋር ካደረጉት የቴክሳስ ኮፍያ ጋር ብቅ እያሉ በአራዳ ቋንቋ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ '' ይላጡበታል '''። 

ለመሆኑ ሕሊና በእዚህ ደረጃ ተሸጦ ተቀርጥፎ ይበላል እንዴ? የአማራ ክልል ወጣት ተነሳ ሙት እያልክ ጦርነት ቀስቅሰህ እና በሚልዮን የሚቆጠር በተለይ የጎጃም ወጣት ከሦስት ዓመታት በላይ ከትምሕርት ገበታ እርቆ እና ትምሕርት እንደ ውሃ ጠምቶት እያለቀሰ፣እናት አባቱ በጥጋበኛ አጋች እየታገተ እና ገንዘብ አምጣ እየተባለ መከራውን እያየ፣ቅምጥሎቹ ባንዳ ዩቱበሮች በአውሮፓና አሜሪካ የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ልጆቻቸው ከትምሕርት ዕረፍት ጋር ይዘው ወዝ ወዝ ሲሉ ማየት የእዚህ ዓይነት የባንዳነት እና ባሳደገች ሀገር ላይ የመጨከን ዓይን ያወጣ አውሬነት ለገንዘብ ሲሉ እንዴት ተዘፈዘፉበት ያስብላል። እነኝህ ባንዳ ዩቱበሮች የድፍረታቸው ድፍረት ትናንት የኢትዮጵያ አንድነት እያሉ ሲያወሩን በሰማንበት አንደበት ዛሬ ላይ የጎጥ ፖለቲካ እያቀነቀኑ ብቻ ሳይሆን ከጠላት ሀገር ጋር መሞዳሞድ እና ኢትዮጵያን በአደባባይ መሸጥ ከፍ ሲልም የባሕር በሯ መዘጋትን እና የመጣባትን መከራ በተድበሰበሰ የስልጣን ጥያቄ እና አዲስ አበባ ላይ ጎርፍ አየን በሚል የቱቦ መደፈን እና መዘጋት ጉዳይ እያነሱ ሊያጃጅሉን ይሞክራሉ። ለራሳችሁ የመጃጃል መብታችሁን ብናከብርም ኢትዮጵያን ለማሻሻጥ የምታደርጉትን የባንዳነት ተግባር ግን አይደለም ይህ ትውልድ መጪው ትውልድም በይቅርታ የሚዘለው ጉዳይ አይደለም። ሌላው ቀርቶ ለገዛ ልጆቻችሁም ''የባንዳ ልጆች '' ከመባል አያስጥላቸውም።

ኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ የተኙ ለመሰሏችሁ።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ከግማሽ ክፍለዘመን በላይ ልጆቹን በጦርነት የማገዱትን የአዛውንት ክበቡን ፅንዶ፣ ያሳደገቻቸው እናታቸው ኢትዮጵያ እና ሕዝቧ የባሕር በር ተዘግቶበት እያዩ ዛሬም ለእናታቸው መውጫ በር ለመዝጋት የሚራወጡቱ እና ባንዳ ዩቱበሮችን ተግባሮቻቸውን ሁሉ በአንክሮ እየተከታተለ፣ ትዕግስቱን ከመፈታተን በላይ ከደሙ አልፎ አጥንቱን እያጋሉት መሆኑ አልገባቸውም። ይህ እንቆቅልሽ የሆነ ምድር ነው  ኢትዮጵያ፣ ይህ የተኛ ሲመስልህ እንደ አንበሳ አጓርቶ፣እንደ ግስላ የሚነሳ ሕዝብ ያለበት ሀገር ነው። ኢትዮጵያ ና የኢትዮጵያ ሕዝብ በአማራ፣በትግራይ እና በኦሮሞ ስም እያላችሁ በስሙ የነገዳችሁ ብቻ ሳትሆኑ ለባዕዳን ለመሸጥ እና ኢትዮጵያን ለማፍረስ የምታደርጉትን የአዛውንቶች ክበብ ስብስብም ሆነ በዩቱብ የባንዳነታችሁን ላንቃ የምትለቁበት ሁሉ ዕወቁት። የኢትዮጵያ ሕዝብ አልተኛም።ኢትዮጵያም አልተኛችም።እንዴት ተነስቶ ባንዳነትን እና ኢትዮጵያን ለማፍረስ የተውተረተሩትን ሁሉ እንደሚቀጣ ያውቅበታል።ከእዚህ በፊትም ሲነሳ ታውቁታላችሁ።ሀገሩ ተገማች አይደለም። ሕዝቡም እንዲሁ።
++++++++++++++/////++++++++++++++


Tuesday, August 11, 2026

የኢትዮጵያ የባሕር ኃይል አዛዥ ኮሞዶር ጌታቸው ስዩም በምፅዋ የኢትዮጵያ የባሕር በር ላይ እጅ አልሰጥም ብለው ያፈሰሱት ደም ዛሬም በባሕሩ ዳር ላይ ይጣራል።


በአስመራ የተወለዱት የኮሞዶር ጌታቸው ባለቤት፣በአዲስ አበባ የተወለዱት ልጆቻቸው ዛሬ ላይ ሆነው የሚነግሩን አለ 
ሙሉ ቪድዮውን ይከታተሉ።


Monday, August 3, 2026

በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጉዳይ ዛሬም ከምንጊዜውም በላይ የቅዱስ ሲኖዶስን የአፈጻጸም ጥብቅ ክትትል ትፈልጋለች።በሺህ የሚቆጠሩ ምእመናን ችግር ላይ ናቸው።


በጥንታውቷ ግሪክ ዋና ከተማ ከአቴንስ ወጣ ብሎ  ከስድስት ሺህ ካሬ በላይ ስፋት ያለው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስም የተገዛው ገዳም

=============
ጉዳያችን ልዩ ሪፖርት
=============

ኢትዮጵያና ግሪክ

ኢትዮጵያና ግሪክ ወደኋላ ከአምስት ሺህ ዓመታት በላይ ታሪክ ያላቸው ጥንታውያን አገሮች ውስጥ በቀዳሚነት ከሚቀመጡት ውስጥ ናቸው።800 ዓዓ አካባቢ የኖረው የግሪክ ባለቅኔ ሆሜር ኢትዮጵያን በጽሑፉ ከትቧታል። በግሪክ አይቲዮፕያ የጠይም ሰው መገለጫ ነው። ኢትዮጵያ እና ግሪክ የጥንቱ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን  ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ ስላላቸው ብቻ ሳይሆን በቀላሉ የማይቦረቦር ክፍለ ዘመናትን በኩራት የተሻገረ ባሕል ባለቤቶች ናቸው።ከእዚህ በዘለለ ወደ የጥንቱ የዓለም ታሪክ ስንሄድ ኢትዮጵያ በቀይባህር ላይ ባላት የበላይነት፣ግሪክ ደግሞ በሜዴትራንያን ባህር ላይ ባላት ስልታዊ ወሳኝ አቀማመጥ አንጻር ከንግድ ግንኙነት በላይ ተጽዕኖ ፈጣሪነታቸው ጉልህ ነበር።

በዘመናዊዋ ኢትዮጵያ በቀዳማዊ  አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን ኢትዮጵያ እና ግሪክ ግንኙነት ወደ ከፍተኛ ደረጃ የተሸጋገረበት ነበር።ንጉሱ በ1947 ዓም ግሪክ ዋና ከተማ አቴንስ ሲገቡ የአቴንስ ሕዝብ በከፍተኛ ቁጥር በአደባባይ ወጥቶ ተቀብሏቸዋል። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት በጸረ ፋሽሽት ትግል አኩሪ ገድል የፈጸመው የግሪክ ህዝብ በአውሮፓ ደርሶ እንደነበረው ጦርነቱ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር 1945 ዓም እንደተጠናቀቀ ረሃብ ገብቶ ነበር። በእዚህ ጊዜ ታድያ አፄ ኃይለሥላሴ አቴንስ ከተማ ተገኝተው ቁጥሩ ብዙ የሆነ የቁም ከብት ገዝተው ህዝቡን በአደባባይ ስጋ አብልተዋል። ይህ ሥጋ ህዝቡን ያበሉበት ቦታ አሁን ድረስ አቢሲኒያ አደባባይ ይባላል።የእዚህ ጽሑፍ አዘጋጅም ቦታው ድረስ ሄዶ በአደባባዩ ዙርያ ያሉ ባለሱቆችን ለምን የአቢሲንያ አደባባይ ተባለ ብሎ ሲጠይቃቸው ይህንኑ ንጉሱ የሰሩት የቸርነት ሥራ አስታውሰው ነግረውታል። 

ግሪኮች በቀድማዊ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግስት ጊዜ በተለይ ወደ ኢትዮጵያ እየመጡ በመኖር በንግድ፣በመምህርነት፣በግንባታ እና በተለያዩ ሙያዎች ተሰማርተው ለኢትዮጵያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል።በምሕንድስናው ዘርፍ መሃል አዲስ አበባ የሚገኘው የአራዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕንጻ ዲዛይን እስከ የንግድ ባንክ ህንጻዎች ግሪካውያን አሻራቸውን አስቀምጠዋል። እዚህ ላይ የሱፐርማርኬት ባለቤቱ እና ከቤቴ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ተለይቶኝ አያውቅም ያሉት አቶ ባምቢስን ማስታወስ ይቻላል።ይህ ሁሉ ሆኖ በአሁኑ ጊዜ ግን ኢትዮጵያውያን እና ግሪካውያን ግንኙነት ላይ በጣም የጠለቀ ግንኙነት አይታይም።አዳዲሶቹ የሁለቱ አገሮች ትውልዶች በሚገባ መተዋወቅ እንዲችሉ የባሕል ልውውጥ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ማሳደግ አለባቸው። እዚህ ላይ በኢትዮጵያ ይኖሮ የነበሩ ግሪካውያን የመሰረቱት የግሪክ ኢትዮጵያውያን ማኅበርን መጥቀስ ይቻላል። ማኅበሩ በየጊዜው የኢትዮጵያውያንን ባሕል እና ታሪክ በማስተዋወቅ የተጋ ማኅበር ሲሆን በአቴንስ የሚገኘውን የአቢሲንያ አደባባይ ሕጋዊ ይዞታ እንዲጠበቅ እና የቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴን ሃውልት ለማሳነጽ እንቅስቃሴ ላይ ያለ ማኅበር ነው። 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በግሪክ ሕጋዊ ዕውቅና እንዴት አገኘች?

በአቴንስ የምትገኘው የኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን በተለይ ከ1994 ዓ/ም ጀምሮ  የሰነድ ተቀባይት ችግሯን መፍትሔ ለመስጠት ሰበካ ጉባኤው በላከው ደብዳቤ በብፁዕ አቡነ ጳውሎስ በሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና የተሰጣት ሲሆን ይኽውም የሶማቲዎ (ማኅበር) የግብር መለያ ቁጥር (Tax No) 997874156  “AΙΘΙΟΠΙΚΗΣΟΡΘΟΔΟΞΗΣ ΕΚΚΛΗΣΙΑΣ ΤΗΣ ΑΘΗΝΑΣ” በሚል ንብረት ለማፍራት፣ ገንዘብ ለማንቀሳቀስ፣ በግብርና ተያያዥ ክፍያዎች አፈጻጸም ዙሪያ ያሉ ችግሮችንም ለመፍታት በሚያስችል መልኩ ቤተክርስቲያኒቱ እውቅና አግኝታለች። ይህንን እውቅና የዛሬ አስር ዓመት ቅዱስ ሲኖዶስ በሦስት ሰዎች አሳሳች ደብዳቤ ቀድመው በመጡት አባ ወልደሚካዔል ጣውዬ ላይ ተደርበው በመጡት አባ ገብረየሱስ ጊዜ የቤተክርስቲያኒቱ ፍቃድ በክስ ምክንያት ለማወዛገብ ተሞክሮ ነበር።

ይህም ሆኖ ግን በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ስም የተመዘገበው እና በሶማትዮ ማኅበርነት የሚታወቀው አደረጃጀች ዛሬም በግሪክ መንግስት እውቅና ያለው ብቻ ሳይሆን በመተዳደርያ ደንቡም ውስጥ ኦርቶዶክሳዊ ትምሕርቶችን ከግሪክ አልፎ እስከ መካከለኛው ምስራቅ ድረስ ማስፋፋት እንደሚችል በጸደቀለት ደንብ ተገልጿል። ከእዚህ በተለየ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ደንብ እና ስርዓት መሰረት ያለው አደረጃጀች በውስጥ ደንቡ መሰረት የሚነሱ ማናቸውም የሃይማኖት ክርክሮች እና ጥያቄዎች የሚፈታው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና መሰረት ብቻ እና ብቻ እንደሆነ ደንቡ ያዛል።ይህም በቤተርክስቲያኒቱ ላይ ለሚነሱ የሃይማኖት ቅሰጣዎች ሁሉ ዕድል የማይሰጥ ሆኖ የተደራጀ ጠንካራ አደረጃጀት ያለው ነው።

በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጉዳይ ዛሬም ከምንጊዜውም በላይ የቅዱስ ሲኖዶስን የአፈጻጸም ጥብቅ ክትትል ትፈልጋለች።

ቅዱስ ሲኖዶስ በመጋቢት/2017 ዓም አቡነ ጢሞቲዎስ እና አቡነ ጴጥሮስ ያሉበት ልዩ ልዑክ ግሪክ ድረስ ልኮ የግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ጉዳይ ለማየት ተሞክሯል። ከብፁአን ሊቃነ ጳጳሳት የአቴንስ ጉዞ ተከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ክሕነታቸው ተይዞ የነበረው የአባ ወልደሚካኤልን ስልጣነ ክሕነት የመለሰ ሲሆን ለአቴንስ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን በሕገ ቤተክርስቲያን መሰረት አዲስ አስተዳዳሪ ሊቀስልጣናት አባ ኪሮስ ጸጋዬን መድቦ፣በአሁኑ ጊዜ ምእመናን የአዲሱን አስተዳዳሪ መምጣት በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።ይህ በአሁኑ ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱ የምትገኝበት ተጨባጭ እውነት ነው።

ይህ በእንዲህ እያለ ከቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በኋላ በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዙርያ የሚከተሉት ሁኔታዎች ተከስተዋል እነርሱም ፡
  • አቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው ለአራት አስርተ ዓመታት ምእመናን ሲገለገሉባት የነበረችው የኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን በአጽራረ ቤተክርስቲያን በሆኑ በቤተክርስቲያን ውስጥ ፊሽካ ከመንፋት እስከ ደም ማፍሰስ ወንጀል በፈጸሙ እና አሁንም ጉዳያቸው በሕግ የተያዘ ግልሰቦች እና እራሱን ኪኖቲታ በማለት በሚጠራ የዕድር አደረጃጀት በፈጠሩት ሁከት አማካይነት ቤተክርስቲያኒቱ በግሪክ መንግስት እንድትዘጋ ሆነ።
  • ቤተክርስቲያኒቱ ከተዘጋች ወዲህ በአቴንስ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሚያስቀድሱበት ቦታ በተለይ በአቴንስ ከተማ ውስጥ አለመኖሩና ቤተክርስቲያኒቱን በግሪክ በሕጋዊነት እንዲያገለግሉ የተመደቡት ሊቀስልጣናት አባ ኪሮስ ጸጋዬ ወደ ግሪክ በቶሎ አለመምጣት መጪው የፍልሰታ የፆም ወቅት ሳይቀር ምእመናን ተቸግረው እንደሚያሳልፉ ቅዱስ ሲኖዶስም የሚያውቀው ጉዳይ ነው።
  • ይህ በእንዲህ እያለ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በአቡነ ኤልያስ ቤተክርስቲያኒቱን ያወከውን የዕድር አደረጃጀት (ኪኖቲታን) ማዕከል ያደረገ  በሆቴል ያደረጉት ''ጉባዔ'' አይደለም ሌላ የራሱ የኪኖቲታ ስር ናችሁ የተባሉ ምእመናንን ሳይቀር ማሰባሰብ ያልቻለ ብቻ ሳይሆን በቅዱስ ሲኖዶስም ምንም እውቅና የሌለው የጉባዔው ምንነት እና ሆቴል የተመረጠበትም ምክንያት ሳይታወቅ ተድበስብሶ ይሄው ሳምንታት ነጎዱ። 
  • ቤተክርስቲያኒቱ በስሟ የተገዛውን ከስድስት ሺህ ካሬ በላይ ስፋት ያለው በአውሮፓ የመጀመርያዋ የሆነውን ገዳም በተመለከተ ምን ደረሰ፣ይህ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ንብረት ነው ብሎ የሚከታተለው ሊቀጳጳስም ሆነ ሀገረስብከት ሳይኖረው ስምንት ዓመታትን ያሳለፈበት እውነታ ዛሬም መሬት ላይ ያለ ዕውነታ ነው።
  • አቡነ ኤልያስ በግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር በኩል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በግሪክ ያላቸው የኃላፊነት ደረጃ በግልጽ እንዲነገረው በአዲስ አበባ የሚገኘውን የግሪክ ኤምባሲ ቤተክሕነት ድረስ ሄዶ እና የሚመለከተውን መምርያ ተገናኝቶ እንዲገለጽለት ጠየቀ።
  • የግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር ይህንን ጥያቄ ያቀረበበት ምክንያት አቡነ ኤልያስ ተደጋጋሚ ደብዳቤ በተለይ ወደ የግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር በመላክ በግሪክ ያለውን ጉዳይ እኔ የምቆጣጠረው ነው በሚል ከጊዜያዊ አስተዳዳሪ ምደባ ጀምሮ በሚልኳቸው ደብዳቤዎች የሚኒስቴር መስርያቤቱ ግራ ስለተጋባ ነበር።
  • በእዚህ መሰረትም መስመር ኤምባሲው ወደ ቤተክሕነት ልዑክ ልኮ የአቡነ ኤልያስ የኃላፊነት መጠን በቤተክርስቲያን ሲጋበዙ መባረክ ብቻ መሆኑ ተገለጸለት።ይህ የማጣራት ሂደት በግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር ከደረሰው በኋላ አቡነ ኤልያስ በግሪክ በተጋበዙበት ቦታዎች የመባረክ ተግባራትን እንጂ በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በተመለከተ ማናቸውም ጉዳዮች የሚከወኑት እና የተፈጻሚነት ደብዳቤዎች የሚመጡት ከቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ መሆኑን የሃይማኖት ሚኒስቴር አረጋገጠ።
  • በእዚህም መሰረት ምንም እንኳን እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት እና ደንብ መሰረት የሃገረስብከቱ ሊቀጳጳስ ሚና ከፍተኛ ቢሆንም ከግሪክ አንጻር ግን የሃይማኖት ሚኒስቴር ባረጋገጠው የሕግ ተቃርኖ ትንተና መሰረት አቡነ ኤልያስ በአሁኑ ጊዜ በግሪክ ቤተክርስቲያን የመመስረትም ሆነ የማስቀጠል እንዲሁም በሃይማኖት ሚኒስቴር በኩል አስተዳዳሪ የመሾም መብት እንደሌላቸው በግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር በኩል የታወቀ ነው።
  • ለእዚህም ነው አንዳንድ በኪኖቲታ በኩል ያሉ ምእመናን ወንድሞች እና እህቶች ቤተክርስቲያን ልንገዛ ነው፣ገንዘብ አዋጡ ስትባሉ ሁለቴ አስቡ። አሰራሩ እንደዛ አይፈቅድም ገንዘቡን ለመዝረፍ ያሰፈሰፉ ዙርያችሁን አሉ እያልን ደጋግመን የምንመክረው።
  • በግሪክ ለምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የሚመደበው በቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ መሆኑ ለግሪክ የኃይማኖት ሚኒስቴር በድጋሚ ግልጽ ስለሆነ አሁንም ቅዱስ ሲኖዶስ የመደባቸው ሊቀ ስልጣናት አባ ኪሮስ ጸጋዬ ሲመጡ ብቻ ነው ቤተክርስቲያኒቱ በግሪክ ያላት የማስፈጸም አቅም የሚከፈተው።ይህ በግሪክ ያለው ተጨባጭ ሁኔታ ነው።
አሁን ቅዱስ ሲኖዶስ በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አንጻር ምን ማድረግ አለበት?

ቅዱስ ሲኖዶስ አሁንም በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አንጻር የሚከተሉትን አፋጣኝ ተግባራት ቢያከናውን የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን በግሪክ እንድታብብ ወሳኝነት ይኖረዋል። እነርሱም፡
  1. የሊቀስልጣናት አባ ኪሮስ ጸጋዬ የግሪክ ጉዞ በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ልዩ ክትትል በሚከተሉት ሁለት መንገዶች መከታተል እና ማስፈጸም ይችላል።
    • በአዲስ አበባ የሚገኘው የግሪክ አምባሳደርን ቅዱስ ፓትርያሪካችን ጠርተው ቤተክርስቲያኒቱ የመደበቻቸው አባት ወደ ግሪክ ተጉዘው በፍጥነት አገልግሎት እንዲጀምሩ እንዲያደርጉ ውይይት ማድረግ እና ለግሪክ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንም ደብዳቤ በመጻፍ ቤተክርስቲያኒቱ ቅሬታዋን ማቅረብ አለባት።
    • የግሪክ ሀገረ ስብከት አንዱ የገጠማት ችግር ሀገረስብከቱን አስተባብሮ የቤተክርስቲያንን ችግር ከመፍታት ይልቅ በግል እና የሀገረስብከቱን መዋቅራዊ አቅም ባገለለ መልክ ከግለሰቦች ጋር በሚደረግ  ግንኙነት ብቻ ለመምራት የሚሞክሩት የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ አካሄድ መሆኑ ፀሐይ የሞቀው እና ሊቀጳጳሱን የሚቀርቡ ሁሉ እጅግ ያዘኑበት ጉዳይ ነው። በመሆኑም ሀገሩን እና ዘመኑን የዋጀ የሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ምደባ አሁንም በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከቅዱስ ሲኖዶስ የምትጠብቀው አሁንም አንገብጋቢው ጉዳይ እና ቅዱስ ሲኖዶስም ከእዚህ አንጻር የጉዳዩን አንገብጋቢነት ለመረዳት መዘግየቱ አሁንም ድረስ በቅርብም ሆነ በሩቅ ያሉ የቤተክርስቲያኒቱን አባቶችም ሆነ ምእመናንን ግራ ያጋባ ጉዳይ ነው።
  2. በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ምደባ ጉዳይ ከቤተክርስቲያን ጉዳይነት በዘለለ የሀገር ገጽታ፣ ከእዚያም ሲያልፍ የኢትዮጵያና የግሪክ የረጅም ጊዜ ትስስር ነጸብራቅም ስለሆነ የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓ ዴስክ እና በጣልያን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲም በጥብቅ ተከታትሎ ሊያስፈጽመው የሚገባ ጉዳይ ነው።በውጪ የሚኖረው ማኅበረሰብ የራሱን ኃይማኖት በተገቢ መንገድ ማከናወን አለመቻሉ ከቤተክሕነትም አልፎ የኢትዮጵያውያን ጉዳይ ያገባኛል የሚል ማናቸውም ቢሮ ይመለከተዋል። ስለሆነም የተጠያቂነቱ አድማስ በቀላሉ የሚወሰን አይደለም።
ባጠቃላይ በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጉዳይ በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ በመላው ዓለም ከሚገኙ የቤተክርስቲያኒቱ ችግሮች በቀዳሚነት እና አንገብጋቢነት የሚገኝ መሆኑን ተመልክቶ ጥብቅ ክትትል አለማድረጉ ቤተክርስቲያንን በእጅጉ የሚጎዳ ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሔርም ሆነ በሰው ፊት የሚያስጠይቅ የጊዜያችን እጅግ አንገብጋቢ ጉዳይ መሆኑን ደግመን አሁንም እንደልጅነት ለብፁዓን አባቶቻችን ለማሳሰብ እንወዳለን።
=======================///=============

Tuesday, July 14, 2026

የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።

Foto : Fana digital

  •  የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት።
=========
ጉዳያችን ልዩ
=========

ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም ከ4 ሺህ በላይ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ ተሳታፊዎች እንደሚሳተፉና 93% የኢትዮጵያን ክፍል እንደሸፈነ የተነገረለት የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ በአዲስ አበባ ይከፈታል።የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አመሰራረትና አደረጃጀት ኢትዮጵያ በቅርብ ዓመታት እየገነባቻቸው ያሉት የተቋሞቿ የጥራት ደረጃ አንዱ ማሳያ ሊሆን ይችላል። ተቋም የሚለካው ከተቋማዊ መዋቅሩ አንጻር ብቻ ሳይሆን ከአመሰራረቱ ግልጽነት እና ሒደት ጭምር ነው። ከእዚህ አንጻር የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአመሰራረት ሂደትና የያዘው የሰለጠነ የሰው ኃይል ኢትዮጵያን በሚመጥን መልኩ የተቀናጀ ነው። 

ኮሚሽኑ ሰሞኑን በሸራተን አዲስ ሆቴል ለሚዲያዎች መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል። በዚህም የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር)፣ "ዋናው ሀገራዊ ጉባዔ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምር ይካሄዳል" ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ የመጨረሻው ዋና ጉባዔ በአዲስ አበባ ከተማ ከሦስት ሳምንታት ባልበለጠ ጊዜ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።
በትግራይ ክልል በሚስተዋለው የፖለቲካ አለመረጋጋት መግባት ባለመቻሉ የክልሉን አጀንዳ በአዲስ አበባ ከተማ መቀበሉን፣ በሌሎች ሁሉም ክልሎች በአካል በመንቀሳቀስ መቀበሉን ሲያስታውቅ ቆይቷል። በተያያዘ የቀረቡለት አጀንዳዎቹን ለባለድርሻ አካላት በማቅረብ ሀሳብ እየተቀበለ መሆኑን መሆኑን ከሰሞኑ ጭምር ገልጿል።
በውጭ ሀገራት ከሚገኙ ዳያስፖራዎችም አጀንዳ መቀበሉን ኮሚሽኑ ገልጿል።
ኮሚሽኑ መጀመሪያ በተሰጠው ሦስት አመታት ስራው ባለመጠናቀቁ ፓርላማው ለአንድ ዓመት ተጨማሪ ጊዜ ከሰጠው በኋላ፣ ያም ባለመብቃቱ ለሁለተኛ ጊዜ የስምንት ወራት ጊዜ ተጨምሮለት እየሰራ ይገኛል።

ኮሚሽኑ ከመላው ሀገሪቱ እና ከራሱ ከመንግስትም ጭምር አጀንዳዎችን ከተቀበለ በኋላ አጀንዳዎቹን በሚከተሉት ዋና ዋና ሃሳቦች ጠቅልሏቸዋል።

እነርሱም ፡-

👉 የሀገር ግንባታ

👉 የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣ 👉 የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ ጉዳይ፣ 👉 የሃይማኖት ጉዳዮች፣ታሪካዊ ቅሬታዎች እና እርቅ 👉 የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣ 👉 ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች
👉 ሙስና እና መልካም አስተዳደር እና የሰላም ግንባታ ናቸው፡፡

ይህ ጉባዔ የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነው

ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል። በእዚህ ጉባዔ ከባሕር ማዶ ተቀምጠው አቃቂር የሚያወጡ እና በገዛ እናታቸው ኢትዮጵያ የወደፊት ዕጣ ላይ የሚሳለቁ ወደ ሕሊናቸው እንዲመለሱ ይመከራሉ። በራስ ላይ መቀለድ ለጊዜው እንደ ቀላል ሕመም ሊታይ ይችላል።በአሁኑ እና በመጪው ትውልድ ላይ ለመቆመር መሞከርና በመዘባበት እንዲሁም ትውልዱ እያደረገ ያለውን ምክክር ለማጣጣል መሞከር ግን እንዲሁ በቀላል መታየት ያለበት ጉዳይ አይደለም። ትውልዱ እራሱ ተዉን! ተመካክረን ችግራችንን እንፍታበት! ብሎ ሊገስጻቸውና ከእዚያም ሲያልፍ መቅጣት መቻል አለበት።

አሁን ኢትዮጵያ እየመከረች ነው። መንግስትም የራሱን አጀንዳ እንደማንኛውም የሕብረተሰብ ክፍል አቅርቦ እኩል የሚወያይበት እና በኢትዮጵያ መጪው የፖለቲካ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ጎዳና ላይ ጉልህ አስተዋጽዖ የሚኖረው ሀገራዊ ውይይት እንዲሳካ እና ለሀገራችን ጥቃቅኖቹም ሆነ ግዙፍ የልዩነት ጉዳዮች መፍትሔ እንዲሰጥ የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት።

============///////==========

Tuesday, June 2, 2026

7ኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24፣2018 ዓም በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ተጠናቋል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ በሰባተኛው ብሔራዊ ምርጫ ድምፅ ሲሰጡ።

  • ስለምርጫው ዝርዝር ጉዳይ ምን ያውቃሉ?

✓ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ 42 ፓርቲዎች እና 73 የግል ተወዳዳሪዎች ለተለያዩ ምክር ቤቶች ዕጩዎች የቀረቡበት ነው።

✓ በዚህ ምርጫ በአጠቃላይ 2,198 ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲሁም 8,736 ለክልል ምክር ቤቶች መቀመጫዎች በዕጩነት ቀርበው ተወዳድረዋል።

✓ በዚህም በምርጫው የተወዳደሩት አጠቃላይ ዕጩዎች ቁጥር 10,934 ዕጩዎች መሆናቸውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ ያመለክታል።

✓ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለክልል ምክር ቤቶች ከፍተኛውን ዕጩዎች ያቀረቡት ሦስት ፓርቲዎች ናቸው።

✓  በዚህም ገዢው ብልጽግና 2,950 ዕጩዎችን በማቅረብ ቀዳሚ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) 1,256 እና ሦስተኛው ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 1,032 አቅርበዋል

✓ ሌሎች ፓርቲዎች እና የግል ተወዳዳሪዎችም በተለያየ ቁጥር ለተለያዩ ምክር ቤቶች መቀመጫ ለማግኘት ዕጩዎችን በምርጫው ላይ እንዲወዳደሩ አቅርበዋል።

 ✓ በአማራ ክልል ከሚገኙ 138 የምርጫ ክልሎች መካከል በስምንቱ ምርጫ እንደማይደረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ብሎ ማስታወቁ ይታወሳል።

✓ በአማራ ክልል ድምጽ የማይሰጥባቸው 8ቱ የምርጫ ክልሎች በደቡብ እና ምዕራብ ጎንደር፣ በአምባሰል እንዲሁም በደጋ ዳሞት የሚገኙ መሆናቸው ተገልጿል።

✓ በትግራይ ክልል ከሌሎች የአገሪቱ ክልሎች ጋር በአንድ ላይ ምርጫ አልተካሄደም።

 ✓ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዋ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ሰኞ ዕለት ድምጽ በማይሰጥባቸው ስምንት የምርጫ ክልሎች ወደፊት እንዲመርጡ እንደሚደረግ ገልጸዋል።

✓ በትግራይም 38 ወንበሮች ክልሉ በምርጫ ቦርድ በተቀመጠው የምርጫ ሒደትና ሕግ መሰረት የሚካሔድና ወንበሮቹ ክፍት ሆነው ይጠብቃሉ።

✓ ትናንት ግንቦት 24፣2018 ዓም የተደረገው ብሔራዊ ምርጫ 501 ዕጩዎችን ወደ የሕግ መወሰኛው ወይንም የተወካዮች ምክርቤት የሚያስገባና ምስክርም 25፣2019 ዓም በሚከፈተው የኢትዮጵያ ምክርቤት አዲሱ መንግስት ሥራ ይጀምራል።

✓ በእዚህ ምርጫ የኢትዮጵያን የመንግስት ስሪት ምርጫውን በማደናቀፍ ዕቅድ ተግባር የሸረቡ የቅርብና የሩቅ ቡድኖች በኢትዮጵያ ሕዝብ ጥንቁቅና የቆረጠ የምርጫ ተሳትፎ በእጅጉ ተበሳጭተዋል።

በሰባተኛው የኢትዮጵያ ምርጫ የተሳተፉ ብሔራዊና የክልል ፓርቲዎች ዝርዝር:-

ምንጭ:- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ምንጭ:- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ







Friday, May 29, 2026

ከሰባተኛው የኢትዮጵያ ምርጫ በቀጣይ የሚታዩ የሚታዩት ሦስት እውነታዎች

ኢትዮጵያ 7 ኛው የሕዝብ ተውወካዮች ምክርቤት ምርጫ ሰኞ ግንቦት 24፣2018 ዓም ታካሂዳለች።ይህንን ምርጫ አንዳንዶች ሊያቃልሉት እና በለሆሳስ ሊያልፉት ይሞክራሉ።ሌሎች ደግሞ ምርጫው ይልቅ ነው ብቅ ፉክክር አልታየበትም ይላሉ።የቀሩት ሞቅ ሞቅ አላለልንም ይላሉ።እነኝህኞቹ ተፎካካሪዎች የሆኑ የድራፍት ቤት መነጋገርያ የሆኑ ቃላት ሲቀያየሩ ካላዩ ደስ የማይላቸው ናቸው።

ይህ ምርጫ ግን የኢትዮጵያን መጻኢ መንገድ የሚያቀና ነው።ምርጫው ከ ሀምሣ ሚልዮን በላይ ሕዝብ የሚሳተፍበት ሲሆን ለመጀመርያ ጊዜ በዲጂታልም ጭምር የሚከናወን ምርጥ ነው።

በእኔ ዕይታ ይህ 7ኛው የኢትዮጵያ ምርጫ ተከትሎ ሦስት እውነታዎች ለኢትዮጵያ ያመጣሉ።

እነርሱም:-

፩) ኢትዮጵያ ከጎሳ ፖለቲካ ማዕበል ቀዝፋ ወጥታ ወደ ሕብረብሔራዊ አንድነት የምትሸጋገርበት ነው።

፪) በጎሳ ፖለቲካ የቆሰለችው ኢትዮጵያ ቁስሏ መጥገግ የሚጀምርበት ነው።

፫) በሁለት እግሯ ለመቆም የምትጥረው ኢትዮጵያ ከባሕር በር የተገለለችበትን የክህደት ካባ አውልቃ በሁለት እግሮቿ ቆማ ተጽዕኖ ፈጣሪነቷ ዳግም የሚታይበት ጅማሮ ነው።

ሃተታ አላበዛም እነኝህ ሦስት እውነታዎች ዛሬ ያልገባን የዛሬ አምስት ዓመት ይገባናል።

ባሳለፍነው ሳምንት ኢትዮጵያውያን በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት ደግፈው ተሰልፈዋል።ለሀገራችን በጎ የሚታየንን ከመውቀስ ኢትዮጵያ ያለፈችበትን፣አሁን የቆመችበትንና ለነገ ያቀደችውን መረዳቱ ጥቅም አለው።

ፎቶ ይናገራል።

































Thursday, April 30, 2026

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።



የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ።

በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያንን ሐሙስ ሚያዝያ 22፣2018 ዓም በግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር መታዘዛቸውን በገለጹ የአቴንስ ኪፕሴሊ ወረዳ ፖሊሶች መታሸጉ ታውቋል።

መንደርደርያ

በአቴንስ የምትገኘው የኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን በተለይ ከ1994 ዓ/ም ጀምሮ  የሰነድ ተቀባይት ችግሯን መፍትሔ ለመስጠት ሰበካ ጉባኤው በላከው ደብዳቤ በብፁዕ አቡነ ጳውሎስ በሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና የተሰጣት ሲሆን ይኽውም የሶማቲዎ (ማኅበር) የግብር መለያ ቁጥር (Tax No) 997874156  “AΙΘΙΟΠΙΚΗΣΟΡΘΟΔΟΞΗΣ ΕΚΚΛΗΣΙΑΣ ΤΗΣ ΑΘΗΝΑΣ” በሚል ንብረት ለማፍራት፣ ገንዘብ ለማንቀሳቀስ፣ በግብርና ተያያዥ ክፍያዎች አፈጻጸም ዙሪያ ያሉ ችግሮችንም ለመፍታት በሚያስችል መልኩ ቤተክርስቲያኒቱ እውቅና አግኝታለች። ይህንን እውቅና የዛሬ አስር ዓመት ቅዱስ ሲኖዶስ በሦስት ሰዎች አሳሳች ደብዳቤ ቀድመው በመጡት አባ ወልደሚካዔል ጣውዬ ላይ ተደርበው በመጡት አባ ገብረየሱስ ጊዜ የቤተክርስቲያኒቱ ፍቃድ በክስ ምክንያት ለማወዛገብ ተሞክሮ ነበር።

ይህም ሆኖ ግን በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ስም የተመዘገበው እና በሶማትዮ ማኅበርነት የሚታወቀው አደረጃጀች ዛሬም በግሪክ መንግስት እውቅና ያለው ብቻ ሳይሆን በመተዳደርያ ደንቡም ውስጥ ኦርቶዶክሳዊ ትምሕርቶችን ከግሪክ አልፎ እስከ መካከለኛው ምስራቅ ድረስ ማስፋፋት እንደሚችል በጸደቀለት ደንብ ተገልጿል። ከእዚህ በተለየ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ደንብ እና ስርዓት መሰረት ያለው አደረጃጀች በውስጥ ደንቡ መሰረት የሚነሱ ማናቸውም የሃይማኖት ክርክሮች እና ጥያቄዎች የሚፈታው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና መሰረት ብቻ እና ብቻ እንደሆነ ደንቡ ያዛል።ይህም በቤተርክስቲያኒቱ ላይ ለሚነሱ የሃይማኖት ቅሰጣዎች ሁሉ ዕድል የማይሰጥ ሆኖ የተደራጀ ጠንካራ አደረጃጀት ያለው ነው።

የአቴንስ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ለምን ታሸገች?

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የፌስቡክ ገጽ በዛሬው ዕለት በግሪክ ፖሊስ ስለታሸገችው የኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን አስመልክቶ በለጠፈው ጽሑፍ ላይ እንደሚከተለው ገልጾታል፡ 

''በቅድምያ የከበረ መንፈሳዊ ሰላምታ እያቀረብን ላለፉት ከአራት አስርተ ዓመታት በላይ ኢትዮጵያውያን ሲገለገሉበት የነበረው በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ስትገለገልበት የነበረው ቤተክርስቲያን በግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር መታዘዙን በመግለጽ ፖሊስ ዛሬ ሚያዝያ 22፣2018 ዓም ማሸጉ ታውቋል። ጉዳዩን በቤተክርስቲያኒቱ ጠበቃ በኩል የፖሊስ ጣቢያው የተጠየቀ ሲሆን ፖሊስ ከግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር መታዘዙን እንደገለጠለት ለማወቅ ተችሏል።

ቤተክርስቲያኒቱ ከየካቲት 16/2018 ዓም ጀምሮ ቅዳሴ እንዳይቀደስ በቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ፊሽካ በማጮህ፣ተአምረ ማርያም እንዳይነበብ፣ኪዳን እንዳይደርስ የመረበሽ ተግባር ሲፈጸም የነበረ ሲሆን፣ቅዱስ ሲኖዶስ በየትኛውም የቤተክርስቲያን አገልግሎት እንዳይገቡ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ቀሲስ አየለ እና በሀገረስብከቱ ሊቀጳጳስ አቡነ ኤልያስ ድጋፍ የሚደረግላቸው በቤተክርስቲያናችን አገልግሎት ላይ ተደጋጋሚ የመረበሽ ስራ የሰሩት ግለሰቦች የአካባቢውን ማኅበረሰብ እንዲረበሽ ማድረጋቸውና የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ኤልያስ ከሃይማኖት ሚኒስቴር ጋር የሚያደርጉት ምእመናንን የሚከስ እና የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ከግሪክ ለመንቀል ከሚሰሩ ግለሰቦች ጋር ያደረጉት ያልተገባ ግንኙነት እንዲሁም በቅዱስ ሲኖዶስ የተመደቡት አባት ሊቀስልጣናት አባ ኪሮስ ጸጋዬ በቶሎ እንዲዘገዩ የተደረጉ አሻጥሮች ሁሉ ተደምሮ ቤተክርስቲያኒቱ እንድትታሸግ አስተዋጽኦ እንዳደረጉ ቤተክርስቲያናችን በከፍተኛ ሃዘን ትገነዘባለች።

በመሆኑም ምእመናን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተርክስቲያን ላይ የሆነው ሁሉ አሳዛኝ ቢሆንም፣ ወደ ቤተክርስቲያን ላይ የተወረወረውን ድንጋይ መልሰን ለቤተክርስቲያን የሚጠቅም ግንብ የምንሰራበት እንጂ የምንተክዝበት ስላልሆነ እና ችግሮችን ወደ መልካም እድል በመጠቀም ምእመናን ከእዚህ በፊት ከነበራችሁ ትጋት በበለጠ ለቤተክርስቲያናችን  ማበብ በአዲስ መንፈስ የምንነሳበት መሆኑን አውቀን በእግዚአብሔር ቸርነት፣በእመቤታችን ኪዳነምሕረት አማላጅነት ለቤተክርስቲያናችን በአዲስ መንፈስ እና በጸና ልቦና እንድንነሳ ቅድስት ቤተክርስቲያን መልዕክቷን ታስተላልፋለች።''

ከላይ ከቤተክርስቲያኒቱ ፌስ ቡክ ገጽ ላይ ለመረዳት እንደሚቻለው ለቤተክርስቲያኒቱ መዘጋት ቀዳሚ ሚናውን የሚጫወቱት ጉዳያችን ከእዚህ በፊት ''የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የሰሞኑ ከራሞት ልዩ ሪፖርታዥ'' ላይ እንደተብራራው የአማሳኙ ቡድን ከሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ባገኘው አረንጓዴ መብራት አማካይነት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እንድትታሸግ ሆኗል።

የምእመናኑን እና የቤተክርስቲያኒቱን ችግር የሚፈታ የሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያለህ!

በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን ላይ የደረሰው እንግልት በቃላት ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም። ሀገረስብከቱ በቂ ክትትል አድርጎ ችግሩን የሚፈታለት ሊቀ ጳጳስ አላገኘም። እስካሁን ከተመደቡለት ሊቀጳጳሳት ውስጥ የመፍትሄ ሃሳብ በማመንጨት በቆዩበት አጭር ጊዜ የሞከሩት የጣልያን እና ፈረንሳይ እና አካባቢው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሲሆኑ። አሁን መቀመጫቸውን በስዊድን ያደረጉት እና የግሪክም ሊቀጳጳስ የሆኑት አቡነ ኤልያስ ላለፉት አስር ዓመታት ውስጥ ዛሬ የታሸገችውን የኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን የጎበኙት ባለፈው ዓመት አስታራቂ አባቶች ወደ አቴንስ ሲመጡ እና በቅርቡ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ትዕዛዝ እና ደብዳቤ ምክንያት በማድረግ ወደ አቴንስ ካደረጉት ያልተሳካ ጉዞ ውጪ ቤተክርስቲያኒቱን ከአስር ዓመታት በላይ ቀድሰውባት አያውቁም።

ጉዳያችን ከወር በፊት ይህንኑ አስመልክታ በጻፈችው ላይ እንዲህ ብላ ነበር፡

"እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።" (የሐዋርያት ሥራ 20:28) የሚለው ቃል ዛሬ በግሪክ በሚኖሩ ምእመናን ጆሮ ላይ የሚጮህ ድምፅ ነው። በግሪክ ምእመናን ለዓመታት አልቅሰዋል፣ገንዘባቸውን አውጥተው የገዙትን ገዳም ገዳም አድርጎ የሚባርክላቸው አባት አጥተው ተንከራተዋል፣ ለቤተክርስቲያን ያወጡት ገንዘብ በሌቦች ተወስዶ ከሌባ ጋር ሲተናነቁ ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በተጻፈ ደብዳቤ ለሰረቁት የእውቅና ደብዳቤ እየተሰጠ ባለፈው ዓመት ምእመኑን ሲያገለግሉ የኖሩት ካሕናት ስልጣነ ክሕነታቸው ''ከምእመን ያለፈ ስልጣን የሌለው ግለሰብ በጻፈልኝ ደብዳቤ መሰረት'' በሚል ለመያዝ ማስፈራርያ ተጽፏል። ቤተክርስቲያኒቱ ከግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር ጋር የሚኖራት ግንኙነት በድብቅ እና የአማሹ ቡድን በሚሰሩት ደባ የታጀለ በመሆኑ በአሁኑ ጊዜ የቤተክርስቲያኒቱ ክብር በግሪክ ቢሮዎች ውስጥ ዝቅ ያለ እንዲሆን የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል። ሌላው ቀርቶ አሁን በፖሊጎኖ የምትገኘው የኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ከባለቤቷ የግሪክ ቤተክርስቲያን ጋር ያለው ግንኙነት ቤተክርስቲያኒቱን ለአማሹ ቡድን ለመስጠት በሚደረገው አድሏዊ ሕገወጥ ግንኙነት ምክንያት የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ክብር ዝቅ የሚያደርግ ግንኙነት በመደረጉ ከፍተኛ ቅሬታ እንዲፈጠር ሆኗል።በእዚህም ሳብያ የግሪክ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪም በጉዳዩ ተማረው ቅሬታ አቅርበዋል።''

መፍትሔው 

በግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ችግር ለመፍታት ከቡድናዊ ስሜት የራቀ፣ለሌቦች እና ለዘራፊዎች ምንም ዓይነት መለሳለስ የማያሳይ፣ምእመናንን በፍቅር እና በትኅትና የሚያይ እና ከፍተኛ የቤተክርስቲያን አስተዳደር አቅምና ልምድ ያለው ሊቀጳጳስ በፍጥነት ለግሪክ ቅዱስ ሲኖዶስ ሊመድብ ይገባል። አሁን ያሉት ሊቀጳጳስ አቡነ ኤልያስ ከ90 ዓመታት በላይ የሆኑ እና በቤተክርስቲያን ዝርፍያ በሚታወቁ አማሾች ጋር በመወገናቸው የቤተክርስቲያኒቱን ችግር የማይፈቱበት ደረጃ ደርሰዋል። ላለፉት አምስት ዓመታት ያልፈቱት ችግር ከአሁን በኋላ ይፈቱታል ተብሎ አይታሰብም። አቡነ ኤልያስ የቤተክርስቲያን አጥፊዎች ጋር የገጠሙበት እና ሕጋዊ የሚመስል ሽፋን ለመስጠት አንዴ ''የቅዱስ ሲኖዶስ አስፈጻሚ ኮሚቴ'' ሌላ ጊዜ ሦስተኛ ወገን ቅሬታ ያላቸው እያሉ የሄዱበት ሂደት ሁሉ የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ክብር በግሪክ ዝቅ ያደረገ ብቻ ሳይሆን የሀገራቱን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሁሉ የሚያውክ ተግባር ከግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር ቢሮ ጋር የነበራቸው የቅዱስ ሲኖዶስን ትዕዛዝ ያልጠበቀ የአስተዳዳሪ ምደባ ሁሉ የታየ እጅግ አሳዛኝ ጉዳይ ነው።

በመሆኑም ለግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ችግር ለመፍታት ቅዱስ ሲኖዶስ መፍትሄ ሰጪ ሊቀጳጳስ መመደብ እና በቅዱስ ሲኖዶስ የተመደቡት ሊቀስልጣናት አባ ኪሮስ ጸጋዬ ወደ ግሪክ እንዲመጡ በቅዱስ ሲኖዶስ ከፍተኛ ግፊት ማድረግ የሚሉት ቀዳሚ ናቸው።ይህ ውሳኔ የርክበ ካሕናት ጉባዔ በፊት በአስቸኳይ እና በጊዜያዊነት መወሰን የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ተግባር መሆን አለበት። ምእመኑም የጠየቀው ይሄው ነው።
=============////========





Monday, April 20, 2026

በጠ/ሚ/ዐቢይና ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ላይ በውሸት ወሬ የዘመቱት ''አፈ-ጊንጦች'' በቴዲ አፍሮ ዘፈን ሊሸሸጉ ሲሞክሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ እየሳቀባቸው ነው።

ጠ/ሚ/ዐቢይ አሕመድ እና ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ክብረት በታላቁ የዓባይ ግድብ ምርቃት ቀን።

========
ጉዳያችን ምጥን
========

አፈ ጊንጥነቱ እና የውርደት ካባው

''አፈ ጊንጥነት'' የሚለውን ቃል ለነገር ሰሪዎች እንዲመጥን አድርገው በልካቸው የገለጡት ኢትዮጵያዊው ሎሬንት ጸጋዬ ገብረመድሕን መሆናቸውን ከሰሞኑ አንድ ኢትዮጵያዊ የፍልስፍና ምሑር ሲናገሩ ሰምቼ በጣም ሲገርመኝ ነበር። ኢትዮጵያን ኢትዮጵያዊነትን ለማጎስቆል የሚፈልጉ ሁሉ የለመዱት እና የሚሰነዝሩት ያላቸውን አፈ ጊንጥነት ነው።ኢትዮጵያን ያሉ የቀድሙ የኢትዮጵያ መሪዎች የቀደሙት ባንዳዎች እና ባዳዎች በአፈ ጊንጥነት ሊነድፏቸው ሞክረዋል።ሆኖም ግን ታሪክ እውነትን ያነጥራልና ከኢትዮጵያ ታሪክ ሊፍቋቸው አልቻሉም። በዘመናቸው ግን ለኢትዮጵያ የበለጠ እንዳይሰሩ እንቅፋት አልሆኑም ማለት አይደለም። አፈ ጊንጦች በየዘመኑ ነበሩ። ዛሬም አሉ።

በዘመናችን በኢትዮጵያዊነት እና ኢትዮጵያዊነትን የሚያቀነቅኑት ላይ የተለያየ የሃሰት ስሞችን እየለጠፈ ኢትዮጵያን ወደ የበለጠ መከራ መክተት ዓላማው ያደረገው ቡድን በመጀመርያ የአፈ ጊንጥነት ካራውን በማኅበራዊ ሚድያ፣ በመቀጠል ወደ የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ዕሴቶች ውስጥ ማለትም ከኃይማኖት ተቋማት እስከ ዕድር እና የተለያዩ ማኅበራዊ አደረጃጀቶች ውስጥ እየገባ ለኢትዮጵያ በጎ ያሰቡትን ሁሉ ሲነድፍ፣ሕዝብ በማያባራ የጦርነት ቋያ እንዲገባ ሲያደርግ፣ቡድኑ ግን እራሱን በዲያስፖራ እና ሀገርቤትም በስውር እራሱን ደብቆ ሀገርና ህዝብ ሲያምስ ከረመ። ይህ የማተራመስ ካራው ግን ቀስ በቀስ እየተነቃበት ሲመጣ የውርደት ካባውን ከፍና ዝቅ እያደረገ የሚሸሸግበት ጥግ ሲፈልግ ከረመ።የሚሸሸግበት ሲያፈላልግ ምቹ ሆኖ ያገኘው ደግሞ ስመ ጥሩ የሆኑ የኢትዮጵያ የኪነጥበብ ሰዎችን ነው። ከእዚህ ውስጥ በሰሞኑ አዲስ ዜማ ይዞ ብቅ ያለውን ቲዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) ላይ ለመንጠላጠል ያለው መጋጋጥ አስገራሚ ብቻ ሳይሆን አስቂኝ ሆኗል።

በዘመናችን በአፈ ጊንጦች ኢትዮጵያዊ አጀንዳቸውን ለማጣጣል ዘመቻ ከተከፈተባቸው ውስጥ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የማኅበራዊ ጉዳይ አማካሪ ሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ይገኙበታል።


የአፈ ጊንጡ ቡድን ከላይ የተጠቀሱት ሁለት ኢትዮጵያውያን ላይ የነገር መርዞቹን ሲረጭ ከረምረም ብሏል።

አፈ ጊንጦች በጠ/ሚ/ዐቢይ ላይ የረጩት የሃሰት ወሬ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ላይ የተሰነዘሩት ሃሰተኛ የአፈ ጊንጦች ወሬ ውስጥ ፡
  • ''የብሔር እና የጎሳ ፖለቲካ አራማጅ ናቸው፣''
  • ''ከጀዋር የጽንፍ ሃሳብ ጋር አብረው ይሄዳሉ፣''
  • ''ኢትዮጵያን መከፋፈል ይፈልጋሉ፣''
  • ''የእገሌ ጎሳ ጠላት ናቸው፣''
  • ''የእገሌ ጎሳ ወዳጅ ናቸው፣''
  • ''ባሕርዳር ላይ፣ወለጋ ላይ አዲስ አበባ ላይ የተገደለው ሁሉ በእሳቸው ነው፣''
  • ሰሞኑን በኢራን የተዘጋው የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ በእሳቸው ነው ለማለት ሩብጉዳይ የቀረው አሉባልታ ወዘተ በአፈ ጊንጦች ተነዛ።
ይህንን ሁሉ አሉባልታ ዛሬ ላይ ውሸት መሆኑ ታውቆ እውነታውን ጊዜ ፈታው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕብረ ብሔራዊነትን፣ኢትዮጵያዊነትን እና አብሮነት መመርያቸው መሆኑን በሦስት መንገዶች አረጋገጡ። አንድ ሰው በሦስት ነገር አንድን ጉዳይ ካረጋገጠ ምንም ጥያቄ አይነሳበትም። 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሦስት መንገዶች የአፈ ጊንጦችን አሉባልታነት አረጋግጠዋል። እነርሱም፡ 

1/ በቃል በመናገር (በሁሉም ንግግሮቻቸው)፣ 
2/ በመጽሐፍ መልክ መደመር በሚል ተከታታይ ጽሑፎቻቸው እና 
3/በተግባር የኢትዮጵያን ልማት ለሁሉም አካባቢ በተቻለ እንዲዳረስ በማድረግ እና የጋራ የፖለቲካ ዐውድ ለመፍጠር በሚያደርጉት ተግባር እና መጪ ዕቅዶች ሁሉ የአፈ ጊንጦች ወሬ ውሸት መሆኑን አረጋግጠዋል።

ይህ እውነት የማይዋጥለት ካለ እራሱን በመዳፉ ሸፍኖ የገዛ ሕሊናውን ለማታለል የሚሞክር ሰው ይመስላል።

በሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት  ላይ የተሰነዘሩ የአፈ ጊንጦች ወሬዎች

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ እና በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ጥልቅ ምርምር በማድረግ የሚታወቀውን ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ክብረት ላይ ሆን ተብለው የተነሱ የአፈ ጊንጦች ወሬዎች ውስጥ ሦስቱን የውሸት ወሬዎች በናሙናነት እዚህ ላይ እጠቅሳለሁ። 

1) ውሸት አንድ ፡ ዳንኤል ክብረት ''የትግራይ ሕዝብ መጥፋት አለበት'' አለ የሚለው የውሸት ትረካ 

ይህች የውሸት ትረካ የተጀመረችው ሕወሃት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ጦርነት ባወጀበት እና የሀገር ህልውና ጦርነት በተጀመረበት በ2014 ዓም ላይ ነበር። በእዚህ ጊዜ ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ክብረት የሕወሃት ህልውና ለሃገር አደጋ መሆኑን እና የድርጅቱ እና በታኝ አስተሳሰብ መኖር ስለማይጠቅም ከምድር ገጽ መጥፋት አለበት በሚል በአንድ የመከላከያ ሰራዊት ስብሰባ ላይ የገለጸውን አገላለጽ እነ አፈ ጊንጦች ገልብጠው ''የትግራይ ህዝብ ይጥፋ አለ'' በሚል ማውራት ጀመሩ። እውነታው ግን ለህወሃት እና በታኝ ሃሳቡ የተነገረ እንጂ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ አልነበረም።ይህ ንግግር ዛሬም በድምፅ እና በጽሑፍ የሚገኝ ሆኖ ሳለ። አሁን ድረስ አውቀው ይህንኑ የሚያስተጋቡ አፈ ጊንጦች አሉ።

2) ውሸት ሁለት ፡ ዳንኤል ክብረት ለሀገር ታሪክ የሰራውን የጥንቱን ''ፋኖን '' እና የአማራን ሕዝብ አጥላላ የሚለው የውሸት ተረክ ነው።

ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ክብረት በጻፋቸው መጽሐፎቹም ሆኑ ማብራርያዎቹ የኢትዮጵያ የነፃነት ዕሴት የሆነውን እና በተለይ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት መግቢያ ላይም ሆነ ቀደም ባሉ ዘመናት ለኢትዮጵያ ኅልውና ዋስትና እና ማገር የሆነውን ''ፋኖ'' የተሰኘውን የኢትዮጵያን ነፃነት ያስከበረ ታሪካዊ አደረጃጀት አጣጥሎ አያውቅም።

የዳንኤል ክርክር በዘመናችን በአማራ ክልል የተነሳው ታጣቂ ፋኖ ሳይሆን ጃውሳ ነው። ሁለቱ በትርጉም ይለያያሉ ነው። 

ባጭሩ በዳንኤል አገላለጥ በአማራ ክልል ውስጥ ጥንት የኢትዮጵያን ነጻነት ያስጠበቀው በፋኖ ስም የሚነግደውና በአማራ ህዝብ ላይ አሁንም ድረስ በአንዳንድ ቦታዎች ህዝቡን የሚያውከውን ታጣቂ በፋኖ ስም የሚነግድ እንጂ የታሪካዊው ፋኖ ስም ይዞ መንቀሳቀስ የማይችል ነገር ግን የጃውሳ ስብስብ ነው በሚል ነበር ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ክብረት በተለያዩ ጊዜዎች የገለጠው። አፈ ጊንጡ ቡድን ግን ዳንኤል ክብረት የአማራ ህዝብ ላይ የጥላቻ ንግግር የተናገረ በማስመሰል በሃሰት ያላለው እና ያልተናገረው የለም። ለሁሉም ጊዜ ይፈታዋል ነውና። በአሁኑ ጊዜ በአማራ ክልል ያለው የከተማ እና የገጠር ነዋሪ በጥንቱ ፋኖ እና በጃውሳ መካከል ያለው ልዩነት በሚገባ እንደገባው ወረድ ብሎ ህዝቡን መጠየቅ ነው።በሚልዮን የሚቆጠር የአማራ ክልል ወጣት ከትምሕርት ገበታ ለሁለት እና ለሦስት ዓመታት ያፈናቀለው፣ህዝቡን እያገተ የገንዘብ ምንጭ ያደረገው እና ዛሬም በሕዝቡ ስም እየነገደ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር የሚሞዳሞደው ፋኖ ሳይሆን ጃውሳ መሆኑን ለማወቅ ብዙ ምርምር አይጠይቀውም።

3) ውሸት ሦስት ፡ ዳንኤል ክብረት ''በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሀገር ቤት ለምን ቅበሩን ይላሉ'' አለ በሚል የተነገረው የሃሰት ወሬ ነው።

እዚህ ላይ ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ክብረት በአንድ የምሁራን ስብሰባ ላይ በኢትዮጵያ ላይ የባንዳነት ተግባር የሚፈጽሙትን በተለየ ከጠቀሰ በኋላ እነኝህ ግለሰቦች በኋላ (ኢትዮጵያን ሲያቆስሉ ቆይተው) መልሰው ለምን ለቀብር ሲሆን ኢትዮጵያን ይፈልጓታል በሚል ''ለምን ቅበሩን ያላሉ?'' በሚል ያብራራውን ዲያስፖራው በኢትዮጵያ አይቀበር አለ እያለ የአፈ ጊንጡ ቡድን እየተቀባበለ ሲናገር ከረመ። ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል የተናገረው ምንድን ነው? ብሎ የማያደምጠው እና ገባ ብሎ የንግግሩን ጭብጥ መነሻ ሳይመለከት የሚያወራውም እየተቀባበለ ''ዲያስፖራው በሀገርቤት አይቀበር'' ዳንኤል አለ አሉ እያለ በየስታርባክስ እና ቡና ቤት ማውራት ጀመረ። ሆኖም ግን በዕለቱ ዳንኤል ሲናገር ከቀብር ጉዳይ በፊት ያነሳው እና ያወራው ኢትዮጵያን በውጭ ሆነው ስለሚይቆስሉ እና ስለከዷት የባንዳና የባዳ ጉዳይ እንጂ መላው የዲያስፖራ ማኅበረሰብን እንዳልወቀሰ ግልጽ ነው። ዛሬም ድረስ እውነቱን እያወቁ ባላቸው የፖለቲካ ልዩነት እና ተራ ጥላቻ ከዚያም ሲያልፍ ላደሩበት የባንዳ ቡድን አስፈጻሚነት ሲሉ ብቻ ያልተነገረውን እንደተባለ ሲያወሩ የምንሰማቸው እነኝሁ አፈ ጊንጦች ናቸው።

ለማጠቃለል አፈ ጊንጦች የኢትዮጵያ የታሪክ አተላዎች ናቸው።የቀደሙ የኢትዮጵያ መሪዎችን በውሸት ነድፈዋል፣ለኢትዮጵያ የቆሙላት ሊቃውንቷን በወሬ ለመውጋት ሞክረዋል።አንዳንዶቹን ከመንገዳቸው አሰናክለዋል፣የቀሩትን አሁንም ድረስ ህዝብ በሚገባ እንዳይዘክራቸውና ከጀመሩት ስራ እንዳይማር በውሸት ትርክት ጋርደውበታል። አፈ ጊንጦች በባንዳነት እና የባዕዳንንን ተልዕኮ ለማስፈጸም ላይና ታች ሲሉ የኖሩ እና ዛሬም የሚሞክሩ ናቸው። የ21ኛው ክ/ዘመን ትውልድ እንደቀደስሙት አይደለም። የመረጃ እና ነገሮችን የማመዛዘን ከፍ ሲልም እውነትን የማንጠር ችግር የለበትም።ለእዚህም ነው።አፈ ጊንጦች የቱንም ያህል ቢጋጋጡ አይሳካላቸውም። ስላልተሳካላቸውም ነው መግቢያ መሸሸግያ ሲያጡና በውሸት ያወሩባቸው የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች በሥራ እየቀደሟቸው ህዝብና ሀገርን እያስደመሙ ሲያጡ በቴዲ ሙዚቃ ላይ ለመንጠልጠል የተውተረተሩት። እርሱም አልተሳካም። ምክንያት ቴዲ እራሱም አሳፈራቸው።ከኢትዮጵያዊነት ማማ ላይ አልወርድ አላቸው። እየሆነ ያለው ይሄው ነው።

=================///============







Monday, March 9, 2026

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የሰሞኑ ከራሞት ልዩ ሪፖርታዥ

የ2018 ዓም የጥምቀት በዓል አከባባር በአቴንስ ኪዳነምሕረት 


በእዚህ ጽሑፍ ስር የሚከተሉትን ንዑስ ርዕሶች ያገኛሉ፡ 
  • በአሁኑ ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱን እና ምእመናንን  የሚያምሷት እነማን ናቸው?
  • እራሱን ''የሲኖዶስ አስፈጻሚ ኮሚቴ'' እያለ የሚጠራው ማን ነው?
  • የቡድኑ ''ሶማትዮ ማኅበር'' እና  ''ቀሲስ አየለ'' የሚለው አጀንዳው
  • ''ቤተክርስቲያኑ እንዲዘጋ እንፈልጋለን'' የአማሳኝ ቡድኑ የእየሳምንቱ ፉከራ
  • የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ምእመናን በአማሾች ሲታመሱ ያደረጉት ምንድን ነው?
  • በአሁኑ ጊዜ የምእመናኑ አንድነት እና ሕብረት የበለጠ ጠንክሮ ወጥቷል።

መግቢያ

በጥንታዊቷ እና ቀደምት የክርስትና መገኛ ከሆኑት ሀገሮች ውስጥ በሆነችው ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የዓመታት ችግር ፈቺ በሆነ መልክ ሪፖርት እንዲዘጋጅ ቋሚ ሲኖዶስ በወሰነው መሰረት የተቋቋመው እና ከቤተክሕነት፣ከኖርዲክ እና ግሪክ ሀገረስብከት እና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የተገኙበት ልዩ አጣሪ ኮሚቴ በግንቦት 2016 ዓም ለቅዱስ ሲኖዶስ ካቀረበው ሪፖርት መግቢያ ላይ የቀረበው ጽሑፍ በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አመሰራረት ላይ ጥሩ ማብራርያ ይሰጣል። የሪፖርቱ መግቢያ እንዲህ ይነበባል፡ 

''በእአአ1996 ዓ/ም (1989) የግሪክ የሃይማኖት ተቋማት ሕጋዊ የዕውቅና ምዝገባ አስመልክቶ ባወጣው አዋጅና መመሪያ መሠረት “በአቴንስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” ቃለ ዓዋዲው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ አንድ ውስጠ ደንብ በሕግ ባለሙያዎች ተዘጋጅቶና በሀገሪቱ መንግሥት ዐዋጅ ጸድቆ ለምዝገባ በመቅረቡ የአቴንስ ምክሐ ደናግል ቅድስት ኪዳነ ምኅረት ቤተ ክርስቲያን በሀገሪቱ የሃይማኖት ተቋማት ምዝገባ ዕውቅና አገኘች፤ ይኽ አሁን (ሶማቲዎ) እየተባለ የሚጠራው ነው፤ በወቅቱ የነበሩት የሰበካ ጉባኤ አባላትም ይኽንኑ ጉዳይ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ (ዶ/ር) አምስተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ አሳውቀዋል፡፡ ዕውቅናው ለቤተ ክርስቲኒቱ ተጨማሪ የሕግ ሰውነት የሰጣት ሲሆን እአአ ከ1994 ዓ/ም ጀምሮ ለነበረባቸው የሰነድ ተቀባይት ችግርም መፍትሔ መስጠቱ ሰበካ ጉባኤው በላከው ደብዳቤ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ይኽ የሶማቲዎ (ማኅበር) የግብር መለያ ቁጥር (Tax No) 997874156 ሲሆን “AΙΘΙΟΠΙΚΗΣΟΡΘΟΔΟΞΗΣ ΕΚΚΛΗΣΙΑΣ ΤΗΣ ΑΘΗΝΑΣ” በሚል ንብረት ለማፍራት፣ ገንዘብ
ለማንቀሳቀስ፣ በግብርና ተያያዥ ክፍያዎች አፈጻጸም ዙሪያ ያሉ ችግሮችንም ለመፍታት ተችሏል፡፡በኋላም ብፁዕ አቡነ ገሪማ (ዶ/ር) ባጸደቁት የኮሚቴዎች ስም መንፈሳዊ አገልግሎቱ ቀጥሏል፡፡''

ይህ ሪፖርት ቅዱስ ሲኖዶስ ተቀባይነት ያገኘ እና ከቤተክሕነት ረዳት ፕሮፌሰር መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል፣ ከስዊድን ዶ/ር ቀሲስ አባተ፣ከፊንላንድ፣ሄልሲንኪ ከደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስትያን የሀገረስብከቱ ጸሐፊ መልዓከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፈቃድ፣ከሀገረስብከቱ የሕግ ክፍል ምክትል ሰብሳቢ አቶ ደምስ በግሪክ ያሉ ሁሉንም ወገኖች አነጋግረው በመጨረሻ ምክረ ሃሳብ አክለው ያዘጋጁት ልዩ ሪፖርት ነው። በእዚሁ ሪፖርት መሰረት ቅዱስ ሲኖዶስ በመጋቢት/2017 ዓም አቡነ ጢሞቲዎስ እና አቡነ ጴጥሮስ ያሉበት ልዩ ልዑክ ግሪክ ድረስ ልኮ የግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ጉዳይ ለማየት ተሞክሯል። ከብፁአን ሊቃነ ጳጳሳት የአቴንስ ጉዞ ተከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ክሕነታቸው ተይዞ የነበረው የአባ ወልደሚካኤልን ስልጣነ ክሕነት የመለሰ ሲሆን ለአቴንስ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን በሕገ ቤተክርስቲያን መሰረት አዲስ አስተዳዳሪ ሊቀስልጣናት አባ ኪሮስ ጸጋዬን መድቦ፣በአሁኑ ጊዜ ምእመናን የአዲሱን አስተዳዳሪ መምጣት በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።ይህ በአሁኑ ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱ የምትገኝበት ተጨባጭ እውነት ነው።

 በአሁኑ ጊዜ ቤተክርስቲያኒቱን እና ምእመናንን  የሚያምሷት እነማን ናቸው?

ቅዱስ ሲኖዶስ ለቤተክርስቲያኒቱ በቂ ክትትል በማድረግ ተገቢውን ስራ ቢያከናውንም ከመጀመርያ ጀምሮ የቅዱስ ሲኖዶስን ሲኖዶሳዊ ውሳኔ ሲቃወሙ የነበሩ፣በኋላም በአጉራ ዘለል እና ፍጹም ኢትዮጵያዊም ሆነ ኦርቶዶክሳዊ ትብሃል ባልሆነ መንገድ ቤተክርስቲያኒቱን ለማመስ የሚሞክሩት እጅግ ጥቂት የሆኑ ግለሰቦች እነማን እና ምን እንደሚፈልጉ ለመግለጽ መጀመርያ ማንነታቸውን መግለጹ ያስፈልጋል።

አማሾቹ እነማን ናቸው? 
  • የመጀመርያው ቡድን ውስጥ ያሉት በጣት የሚቆጠሩት ለዓመታት የግሪክ አቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪነት ዘመን ማለት ቀድሞ አባ ዮሐንስ፣በኋላም የነበሩት ንቡረዕድ አባ ኃይለልዑል ገሪማ ቤተክርስቲያኒቱን ሲያስተዳድሩ በቤተክርሲቲያኒቱ ገንዘብ እንደ የግል ንብረት ሲጠቀሙ የነበሩ፣ወደ ሃገርቤት ከግሪክ ከቀረጥ ነጻ በቤተርክስቲያን ደብዳቤ ሲያስገቡ እና አብረዋቸው ሲሞዳሞዱ የነበሩ የቡድን አባላት የመጀመርያ ተጠቃሽ ናቸው ናቸው።ከእዚህ ቡድን አባላት ውስጥ በሕገወጥ መንገድ የቅስና እና የድቁና ማዕረግ ሳይገባቸው የተቀበሉ ያሉበት ነው። ይህ ቡድን አባላቱ በአሁኑ ጊዜ ከአራት የማይበልጡ ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ ሰላማዊ በመምሰል በምዕመኑ ውስጥ መለያየት የሚነዛ፣በአደባባይ እየተቅለሰለሰ ቤተክርስቲያንን ለማመስ ከሚሮጡ ጋር ከአስተባባሪነት እስከ በቀጥታ ሃሳብ በመስጠት በአጽራረ ቤተክርስቲያንነት የተሰለፈ ግለሰብ አለበት።ይሄው ግለሰብ በሀገርቤትም በንዋየ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ ቀደም ብሎ በቅዱስ ዑርዔል ቤተክርስቲያን በሕገወጥ መልክ ሱቅ የነበረው እና በአሁኑ ጊዜ በሌላ ቦታ ሱቅ ያለው ሲሆን፣ ከግሪክ የሚመጡ እቃዎችን ከቀረጥ በነጻ በማስገባት ከፍተኛ ምዝበራ ላይ የተሰማራ ግለሰብ ነው።
  • በሁለተኛው ቡድን ውስጥ የሚገኙት በጣት የሚቆጠሩ የአማሽ ቡድን አባላት በቀደመው የሰበካ አባላት የነበሩ፣የቤተክርስቲያኒቱን ንብረት በአግባቡ መያዝ አለመቻል ብቻ ሳይሆን፣እስካሁንም ሪፖርት እንዲያቀርቡ እና ንብረት እንዲያስረክቡ በቅርቡም ጭምር ተጠይቀው አሻፈረኝ ያሉ፣ከተለያዩ የስለት የወርቅ ስጦታዎች እስከ የቤተክርስቲያኒቱን ሚኒባስ አላስረክብም ብለው መኪናው በሕግ እንዲያስረክቡ ተደርገው ሌሎቹን በተመለከተ በምእመኑ በተቋቋመ አጣሪ ኮሚቴ ሪፖርት ቀርቦ ምላሽ ያልሰጡ፣ከሰንበት ትምሕርት ቤት ቲሸርት ሸጦ ገንዘቡን በአደባባይ ወደ ኪሱ የከተተ እና እስከ ሁለት ሺህ ኢሮ ከሰንበት ትምሕርት ቤት ንዋየ ቅዱሳን መሸጫ ሱቅ በድፍረት ጠፋብኝ ብሎ የተዘባበተ ግለሰብ ያለበት ቡድን ነው።

  • በሦስተኛው ቡድን ውስጥ የሚገኙት አሁንም በጣት የሚቆጠር ቡድን ያለበት ቡድን ባንዳ እና ባዳ የሚባለው ቡድን ነው። በእዚህ ቡድን ውስጥ የሚገኙት ጸረ ኢትዮጵያ አቋም መመረዛቸው በስራቸው ያስመሰከሩ ናቸው። በእዚህ ውስጥ ለኢትዮጵያ ባዳ የሆኑ ነገር ግን ለቤተክርስቲያን የሚቆረቆሩ መስለው እኛኑ መስለው የሚያምሱ ናቸው። ዓላማቸው የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ከግሪክ መንቀል፣ምእመኑን ማወክ፣ኢትዮጵያውያን በቤተክርስቲያናዊ እና ብሔራዊ ስሜታቸው እንዳይኮሩ ማድረግ እና የኢትዮጵያን ስም በግሪክ ማኅበረሰብ ዘንድ ማጠልሸት ነው።

    በእዚህ ውስጥ በቅስና የሚገኙ፣በቀድሞ ሰበካ ውስጥ የነበሩ እና ከኋላ ሆነው በኢትዮጵያውያን ላይ የሚጎነጉኑ ''አካይስት'' አስተሳሰብ ያላቸው የበሉበትን የኢትዮጵያን ወጪት ሰባሪ አሳፋሪዎች ናቸው። ከእነርሱ ጋር አብረው ያሉት ባንዳዎች የቤተክርስቲያን ጉዳይን ለዘመኑ የጥፋት ስራ ለማዋል የቋመጡ ከባዳ ጋር አብረው ቆመንለታል ለሚሉት የረከሰ የባንዳ ተግባር በቤተክርስቲያን ስም ለውሰው ለመንቀሳቀስ የሚሞክሩ አሳፋሪዎች ያሉበት ነው። እዚህ ላይ በኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ስም ፌስ ቡክ ከፍቶ ላለፉት ስባት ዓመታት ያህል የቤተክርስቲያኒቱን ስም ሲያጠለሽ፣የአባቶችን ክብር ሲያዋርድ የኖረ እና እራሱን በመንፈሳዊ ማኅበር ውስጥ ሽጉጦ በአሁኑ ጊዜ ደግሞ አንዴ አዲስ አበባ ቤተክሕነት ሌላ ጊዜ አቴንስ ፖሊስጣብያ በር ላይ እየተንገዋለለ የዘረኛ መርዙን ሸሽጎ የባንዳነት ተግባሩን የሚሰራ ዲያቆን የተካተተበት ነው። ይህ ዲያቆን በተለይ ለዓመታት የግሪክ ጉዳይ እንዳይፈታ በአንድ የቤተክሕነት አባት አገላለጽ ሲናገር ''የእባብ መርዝ የሚተፋ'' ያሉት ግለሰብ በሀገረ ስብከቱና በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መሃል ችግር እንዲፈጠር የሰርክ ጉባዔ ቀመስ በሆኑ ጥቅሶች ምእመኑን በፌስቡክ ሲያምስ የኖረ እና አሁንም እያመሰ የሚገኝ ግለሰብ ነው።

  • በአራተኛ ቡድን ውስጥ ያሉት ጥቂት ግለሰቦች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነትን ለመበረዝ የሚቅበዘበዙ ቡድን አባላት ናቸው። በእዚህ ስር ያሉት ከቤተክርስቲያኒቱ ዶግማና ቀኖና ውጪ በሆነ መልክ መሰረተ እመነቷን ለመበረዝ ምእመኑን ለመክፈል የሚሮጡ የሃይማኖት ቀሳጮች ናቸው።እነኝህ በቤተክርስቲያን ውስጥ ኦርቶዶክሳውያን የሚመስሉ ነገር ግን ቤተክርስቲያኒቱ እንድትጠላ በቀጥታ በማናቸው ቤተክርስቲያንን በሚያውኩ ተግባራት ውስጥ ይሰማራሉ። 
ከላይ የተጠቀሱት አራት ቡድኖች ሲደመሩ ከ15 አይበልጡም።ቤተክርስቲያኒቱን የሚበጠብጡት በእዚህ ያህል ያሉ ቁጥር ያላቸው ናቸው። አራቱም ቡድኖች አዲስ የመጡ ስደተኞችን ለመያዝ በብዙ ጥረት የእኩይ ተግባራቸው ተባባሪ ለማድረግ ቢሞክሩም፣ ሁሉም የተንኮላቸው ተባባሪ ስላልሆኑ ዛሬም በጣት የሚቆጠሩ የቡድኑ አባላት ቀርተዋል። 

እራሱን ''የሲኖዶስ አስፈጻሚ ኮሚቴ'' እያለ የሚጠራው ማን ነው?

በመጋቢት/2017 ዓም ወደ አቴንስ የመጣው የቅዱስ ሲኖዶስ ልዑክ ከተመለሰ በኋላ ከላይ በአራት የአስተሳሰብ እና የፍላጎት ውጥረት ውስጥ የገባው ወደ 15 የሚቆጠር ቡድን ከሃገረስብከቱ ሊቀጳጳስ ባገኘው አረንጓዴ መብራት እራሱን ''የሲኖዶስ አስፈፃሚ ኮሚቴ'' በማለት አንድ መቶ የማይሞላ ተከታይ ይዞ በፌስቡክ ተከሰተ። ቡድኑ የሰረቀው፣የባዳው እና የባንዳው እንዲሁም የሃይማኖት ቀሳጩ ቡድን በጋራ የተሰበሰበበት ቡድን ነው። 

የቡድኑ ''ሶማትዮ ማኅበር'' እና  ቀሲስ አየለ የሚለው አጀንዳው

በአቴንስ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ለማመስ የሚንቀሳቀሰው 15 ሰዎች የያዘው ስብስብ ከእውቀት ነጻ የሆነ ቤተክርስቲያኒቱ ቀድሞ ጀምሮ በግሪክ መንግስት የተመዘገበችበትን ''ማኅበር '' ወይንም ''ሶማትዮ ''  የሚለውን ስም የቤተክርስቲያን መስደብያ ቋንቋ አድርጎታል። ቤተክርስቲያኒቱን እንደፈለጉ አድርጎ ለመዝረፍ እና ለማጥፋት አልመች ያለው ይሄው አደረጃጀት መሆኑን ስለሚያውቁ በከፍተኛ ጥላቻ የቤተርክስቲያኒቱን አደረጃጀት ማጥላላት ዋና ስራ አድርገው ይዘውታል።ቡድኑ በራሱ ''የብሪፍ ኬዝ'' ተንቀሳቃሽ የቤተክርስቲያን ስም የሚነገድበት ማኅተም ይዞ የሚዞር ሲሆን አደረጃጀቱም በእድር መልክ ''ኪኖኒታ'' በሚል አደረጃጀት የኖረ ነገር ግን አድራሻውን በቦርሳ ይዞ የሚዞር ነው።

ይህ የተለያየ ፍላጎት ያዘለው ቡድን ከሰሞኑ ይዞ የመጣው በግሪክ የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ከአስር ዓመት በፖሊጎኖ የምትገኘውን የኪዳነምሕረትን ቤተክርስቲያን ትተው የሄዱትና ከቅርብ ወራት ወዲህ ተመልሰው የመጡት ቀሲስ አየለን በአጀንዳነት ይዞ መጥቷል።ቀሲስ አየለ ወ/ጻድቅ በቅዱስ ሲኖዶስ በደብዳቤ ቁጥር 397/408/2018 ሐምሌ 23/2017 ዓም ባደረገው ስብሰባ መሰረት በየትኛውም የቤተክርስቲያን አስተዳደር እንዳይገቡ ያገደ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ የተሰጠ ማናቸውም ጊዜያዊ ደብዳቤ በሕገ ቤተክርቲያን አንቀጽ 28 መሰረት የተሻረ መሆኑን ደብዳቤ የተጻፈባቸው መሆኑ እየታወቀ ቡድኑ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ በመጻረር ቀሲስ አየለን የብጥብጥ አጀንዳ ለማድረግ ሞከረ። 

በእዚህ መሰረት ቀሲስ አየለ ከላይ ከተጠቀሰው ቡድን ጋር በመሆን እስካለፈው እሑድ ድረስ በተለያዩ ሳምንታት ለ6 እሑዶች ጊዜ የሰንበት ቅዳሴ እንዳይቀደስ ከማወክ አልፈው ምእመናን ላይ ፖሊስ በመጥራት ቤተክርስቲያኒቱ ዙርያ ያሉ ነዋሪዎች ጭምር እንዲታወኩ አድርገዋል።ይህንን ጉዳይ የተመለከተው ምእመን ከአንድ ሳምንት በፊት መክሮ ቀሲስ አየለ መቅደስ የሚገቡት አዲሱ አስተዳዳሪ ከመጡ በኋላ ጉዳዩ በካሕናት ጉባዔ ከታየ በኋላ ነው የሚለውን ሃሳብ ወደጎን በማድረግ ወደ መቅደስ እንዲገቡ በሚለው ጉዳይ ላይ ሃሳብ ከተሰጠ በኋላ ባለፈው ሳምንት እሑድ ወደ መቅደስ እንዲገቡ ሲጠየቁ ቀድሞም ምክሩ ከአማሽ ቡድኑ ጋር ስለነበረ የአማሽ ቡድኑ ባሳለፍነው እሑድ የካቲት 29፣2018 ዓም በቤተክርስቲያን ውስጥ ገብተው የሚከተሉትን ጸያፍ ተግባራት ፈጸሙ። ይሄውም፡
  • ቤተክርስቲያን ውስጥ በካሕናት ላይ እጅግ አስነዋሪ ስድብ፣እና ለመደብደብ መገባበዝ፣
  • በቤተክርስቲያን ወንበር ላይ ቆመው ፊሽካ እየነፉ የቡናቤት ስድቦች መሳደብ፣
  • በፉጨት እና ከዘፈን ባልተናነሰ ድምፅ ማቅራራት፣
  • የቤተክርስቲያንን ወንበር እየገለበጡ መዘባበት እና ሌሎች እጅግ ለአእምሮ የሚከብዱ ተግባራትን በቤተክርስቲያን ውስጥ ሲፈጸም ተስተውሏል።
''ቤተክርስቲያኑ እንዲዘጋ እንፈልጋለን'' የአማሳኝ ቡድኑ የእየሳምንቱ ፉከራ።

በአቴንስ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ከአርባ ዓመታት የቆየችበት ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን ከአጠገቡ በሚገኘው በግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ስር የሚተዳደር በመሆኑ እና በአማሳኝ ቡድኑ የየሳምንቱ እጅግ ነውረኛ የሆነ የስድብ እና የረብሻ ተግባር የተነሳ የአካባቢው ነዋሪ እንዲታወክ ሆኗል። የረብሻው አንዱ ዓላማ የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን መበተን በመሆኑ የአማሳኝ ቡድኑ ቀንደኞች ''ቤተክርስቲያኒቱ እንድትዘጋ ነው የምንሰራው '' እያሉ በአደባባይ ሲናገሩ ብዙ ጊዜ ተሰምተዋል፣ በማኅበራዊ ሚድያም ይህብንኑ ያልተገራ ነውራቸውን ሲለጥፉ ይታያሉ። በእርግጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ከአቴንስ ከተማ ቅርብ ርቀት የሚገኝ ሌላ በገዳምነት የነበረ ይዞታ አላት። ይህ ግን በእየእሑዱ ለሚኖረው ቅዳሴ እርቀት አለው።ይህንኑም ገዳም ይሄው አማሳኝ ቡድን በርካታ ወረቀቶችን ወደ የግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር በመላክ ገዳሙን ለማሳሸግ ሞክሯል።

ከእዚህ በተጨማሪ የማለዳ ኪዳን በሚደረግባቸው ቀናት በማለዳ ቤተክርስቲያን በር ላይ እየቆሙ ካሕናትን መሳደብ እና መተናኮል የአማሽ ቡድኑ ተግባር ከሆነ ቆይቷል። ይህንንም ላለፉት ተከታታይ የእሑድ ሳምንታት ቅዳሴ እንዳይቀደስ በመረበሽ እና ቤተክርስቲያኑ ሲከፈት ደግሞ ካላይ እንደተጠቀሰው በጸያፍ ተግባር በመሳደብ እና ፊሽካ ጭምር በማጮህ ቤተክርስቲያንን በማወካቸው የዐቢይ ጾም ከገባ ጀምሮ አንድም እሑድ ቅዳሴ ማድረግ አልተቻለም። እዚህ ላይ ይህ የቤተክርስቲያን አማሽ ቡድን የህገረስብክቱ ሊቀ ጳጳስ ድጋፍ አለን በሚል ስለሚኩራሩ ''ምእመኑን ከቤተክርስቲያን እናስወጣለን '' የሚል ፉከራ ሲያሰሙ ለአፋቸው አያዳልጣቸውም።

የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ምእመናን በአማሾች ሲታመሱ ያደረጉት ምንድን ነው?

"እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።" (የሐዋርያት ሥራ 20:28) የሚለው ቃል ዛሬ በግሪክ በሚኖሩ ምእመናን ጆሮ ላይ የሚጮህ ድምፅ ነው። በግሪክ ምእመናን ለዓመታት አልቅሰዋል፣ገንዘባቸውን አውጥተው የገዙትን ገዳም ገዳም አድርጎ የሚባርክላቸው አባት አጥተው ተንከራተዋል፣ ለቤተክርስቲያን ያወጡት ገንዘብ በሌቦች ተወስዶ ከሌባ ጋር ሲተናነቁ ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በተጻፈ ደብዳቤ ለሰረቁት የእውቅና ደብዳቤ እየተሰጠ ባለፈው ዓመት ምእመኑን ሲያገለግሉ የኖሩት ካሕናት ስልጣነ ክሕነታቸው ''ከምእመን ያለፈ ስልጣን የሌለው ግለሰብ በጻፈልኝ ደብዳቤ መሰረት'' በሚል ለመያዝ ማስፈራርያ ተጽፏል። ቤተክርስቲያኒቱ ከግሪክ የሃይማኖት ሚኒስቴር ጋር የሚኖራት ግንኙነት በድብቅ እና የአማሹ ቡድን በሚሰሩት ደባ የታጀለ በመሆኑ በአሁኑ ጊዜ የቤተክርስቲያኒቱ ክብር በግሪክ ቢሮዎች ውስጥ ዝቅ ያለ እንዲሆን የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል። ሌላው ቀርቶ አሁን በፖሊጎኖ የምትገኘው የኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ከባለቤቷ የግሪክ ቤተክርስቲያን ጋር ያለው ግንኙነት ቤተክርስቲያኒቱን ለአማሹ ቡድን ለመስጠት በሚደረገው አድሏዊ ሕገወጥ ግንኙነት ምክንያት የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ክብር ዝቅ የሚያደርግ ግንኙነት በመደረጉ ከፍተኛ ቅሬታ እንዲፈጠር ሆኗል።በእዚህም ሳብያ የግሪክ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪም በጉዳዩ ተማረው ቅሬታ አቅርበዋል።

ሌላው ቀርቶ ቅዱስ ሲኖዶስ የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ እንዲሆኑ የመደባቸው አባት ሊቀስልጣናት አባ ኪሮስ ፀጋዬ ወደ ግሪክ መጥተው አገልግሎት እንዲጀምሩ ለማድረግ የሚደረግ የድጋፍ እንቅስቃሴ ከሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስም ሆነ ከሀገረስብከቱ አንጻር የሚታይ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ አይታይም።ጉዳዩ የቤተክርስቲያን መሆኑ ቀርቶ የአማሽ ቡድኑ ጋር በሚደረጉ ሕገወጥ እና ቤተክርስቲያንን ማዕከል ያላደረገ ግንኙነት የህገር እና የቤተክርስቲያን ክብር ጉዳይ መሆኑ ቀርቶ ተራ የእልህ እና የሴራ ትብተባ ውስጥ እንዲገባ ሲሞከር ይታያል። ይህ ልብ የሚሰብር በግሪክ የምትገኝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰቆቃ ድምፅ ነው።ጉዳዩን ቅዱስ ሲኖዶስ በአንክሮ እና በአፋጣይ ማየት ያለበት ጉዳይ ነው።የምንናገረው ስለየግል ጉዳይ አይደለም ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለተሰቀለበት፣ስለተገረፈበት እና ስለሞተበት የምእመናን ጉዳይ ነው። ስለሆነም ማንንም ሳያፍሩ እና ሳይፈሩ እውነቱን መናገር ክርስቲያናዊ ግዴታ ነው።

በአሁኑ ጊዜ የምእመናኑ አንድነት እና ሕብረት የበለጠ ጠንክሮ ወጥቷል።

''ክርስቲያን እና ሚስማር ሲመቱት ይጠብቃል።'' እንዲሉ፣ በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን ቤተክርስቲያናቸው ላይ የሚሰነዘሩትን የአማሳኞች ጥቃት ለመመከት ብቻ ሳይሆን ቤተክርስቲያኒቱ ወደ ግማሽ ክ/ዘመን ያህል ከአንድ ሰንበት ትምሕርት ቤት ባልበለጠ አነስተኛ ቤተክርስቲያን የመቆየቷ ቁጭት ጨምሮ እና በአጠቃላይ ወደየተሻለ አገልግሎት ለማሸጋገር ከመቼውም ጊዜ በላይ ቆርጦ የተነሳበት ጊዜ አሁን ነው። እንደ አንድ ምእመን አገላለጥ ''ኪዳነ ምሕረት የቤተክርስቲያኒቱ የቆዩትም፣ድንገት ደራሾችም፣ባዳውም ሆነ ባንዳው ተለይቶ ጠልሏል።የጠለለ ነገር እዳው ገብስ ነው።'' እንዳሉት ምእመናን በግሪክ የምትገኘውን ቤተክርስቲያን ከአጽራረ ቤተክርስቲያን እና ከአማሽ ቡድን ለመገላገል የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሷል።ለእዚህም ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ ተነስቷል። የአማሽ ቡድኑ የአማንያኑን የትሕትና መንገድ ሁሉ ከበጎ ከመመልከት ይልቅ በተሳሳተ መንገድ መመልከታቸው የስሌት ችግር ካልሆነ በቀር ሌላ ሊሆን አይችልም። ስሌት ክፉ ነው።ቤተክርስቲያን ከሕይወት በላይ ነች። የእዚህን ምእመን ኃይማኖታዊ መነሳሳት ቅዱስ ሲኖዶስ የጎደለውን በመሙላት፣የሃገረ ስብከት ችግርን በመፍታት እና ለቤተክርስቲያኒቱ የተመደቡትን አባት በፍጥነት ወደ ግሪክ የሚመጡበትን ማናቸውንም መንገድ በመጠቀም እና በማሳካት አስፈላጊው ሁሉ እንዲከናወን በግሪክ የሚኖሩ ምእመናን ጥያቄ ነው።
======================////===========

Monday, February 23, 2026

Urgent Justice to the Ethiopian Orthodox Tewahido Church in Greece. Attention: The Hellenic Ministry of Education, Religious Affairs department, and the Athens Police


Under this special report, you will find the following subtitles: 
  • The Ethiopian Orthodox Church foundation in Greece.

  • The Ten years Controversy of the Ethiopian Orthodox church in Greece.

  • The results of the 2025 Bishops' visit to Athens.

  • The Greek Ministry of Religion is expecting a prompt and positive response regarding the Ethiopian Orthodox Tewahido Church Patriarch's letter.

  • Greek security forces should take immediate action against criminals who are attempting to terrorize the Ethiopian Orthodox Church believers in Athens.

  • To Generalized
===================
Gudayachn Special Report
===================

The Ethiopian Orthodox Church foundation in Greece.

The Ethiopian Orthodox Tewahido Church and the Greek Orthodox churches are among the ancient churches in our Globe. The first Ethiopian Orthodox Tewahido Church patriarch, ''Aba Fremnatos or Selama'', a Greek origin, visited Ethiopia in the 4th century. In our modern world, the Ethiopian Orthodox Tewahido Church, founded in Hellenica, goes back about half a century.

In accordance with the 1996 (1989) proclamation and directives regarding the legal recognition and registration of Greek religious institutions, the “Ethiopian Orthodox Tewahedo Church of Athens” was registered as a religious institution in the country, and an internal regulation was prepared by legal experts and approved by the government of the country. The Church of the Holy Virgin of Athens, the Holy Covenant of Mercy, was registered as a religious institution in the country; this is now called (Somatio); the members of the Synod at that time informed His Holiness Abune Paulos (Dr.), the Fifth Patriarch of Ethiopia, about this matter. The recognition gave the church additional legal personality and also solved the problem of receiving documents that had been processed since 1994, according to a letter sent by the Synod. This association has a tax number (Tax No) of 997874156 and was established under the name “AΙΘΙΟΠΙΚΗΣ ΟΡΘΟΔΟΞΗΣ ΕΚΛΛΗΣΙΑΣ ΤΗΣ ΑΘΗΝΑΣ” to raise funds, raise funds, and resolve problems related to religious issues. Later on, the spiritual service continued under the name of the committees approved by His Holiness Patriarchal of the Ethiopian Orthodox Tewahido Church, Abune Gerima (Dr.).

The Ten-Years Controversy of the Ethiopian Orthodox church in Greece

The Ethiopian Orthodox Tewahido Church in Greece faced challenges at different levels. The challenges have continued over the past ten years, and the sources of challenges originated from two different bodies. These were the Holy Synod of the Church in Ethiopia (recently adjusted and corrected the problem) and the misuse of resource administration by the former church committee, which exposed the church to theft.

The results of the 2025 Bishops' visit to Athens

In March 2025, the Holy Synod of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church sent two bishops to Athens to visit Greece based on the report of the previously appointed Special Study Committee on the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Greece. The bishops, Abune Timothy and Abune Petros, were tasked with investigating the church’s affairs and presenting a recommendation to the Holy Synod.

During their stay in Athens, the bishops announced the reinstatement of Abba Woldemikhael's priesthood, which had been suspended nine years ago. They, the bishops, then announced that a new administrator would be appointed for the Ethiopian Orthodox Tewahido Kidane Mihret Church in Athens and returned to Ethiopia to report the situation to the concerned Holly synod. 

The Greek Ministry of Religion is expecting a prompt and positive response regarding the Ethiopian Orthodox Tewahido Church Patriarch's letter.

The Holy Synod members of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, which came to Athens in March 2025, returned to Ethiopia and selected Abba Kiros Tsegaye, who is well known for his extensive experience and spiritual services, as the head of the Ethiopian Orthodox Church in Athens. Abba Kiros Tsegaye’s assignment letter to administrate the Ethiopian Orthodox Tewahido Church in Greece was written by the Patriarch of the Ethiopian Orthodox Church, His Holiness Abune Mathias, directly to the Ministry of Religion, which is under the Greek Ministry of Education.

Currently, it is quite clear that the Greek Ministry of Religion’s failure or delayance to respond promptly after the letter has caused great dissatisfaction among Ethiopians residing in Greece. The hot issue, currently, is that the Ministry of Religion needs to provide the necessary permission to Abba Kyros Tsegaye to enable him to get the necessary entry visa to Greece. There are reports that the Ministry of Religion will respond to the matter soon and will allow Abba Kyros to come to Greece, and this is eagerly awaited by thousands of Ethiopian Orthodox Tewahido church followers in Greece. In this case, the Greek government and the Ministry of Religion should pay close attention to this critical issue. The issue is not only a religious issue, but it has a diplomatic and historical relations issue. 

Greek security forces should take immediate action against criminals who are attempting to terrorize the Ethiopian Orthodox Church believers in Athens.

The Ethiopian Orthodox Church, which was designated by the Ministry of Religion and its administrator, has been exposed to terrorists who are engaged in fraud and theft and who are also terrorizing the prayers at the place of ''Bohali 12 Polygono'' in Athens. The terrorists (Ethiopians gave them a nickname) are still creating problems among the believers and in the church that is waiting for the new administrator, Aba Kiros Tsegaye. 

The individuals involved in this terrorist act are very few but known for their crime in Greece. For example, on November 10, 2024, after an assassination attempt was made by the same terrorist group in the church, the police arrived on time, and the injured person was taken to the hospital by ambulance. The case is under legal and criminal proceedings.

Since then, these terrorist individuals have been terrorizing the people verbally, mentally, and even physically on social media, and by phone also. To your surprise,  these individuals have not only made many attempts to call the police as if they were victims. Their negative action has also extended to conspiracies to create conflict between Greece and Ethiopia.

On the recent two Sundays, 15 and 22 February 2026, for example, the terrorists affected the praying time of the church, insulted the people, and threatened the priests physically. They attempted to push in by force the unauthorized priest by the Ethiopian Orthodox Tewahido Church in Bohali, 12. The priest was prohibited from entering by an Ethiopian Orthodox Tewahedo church administrative issue in Greece, which was decided by the Ethiopian Orthodox Tewahedo permanent Holy Synod. Here again, the terrorist teams called the police as if they were victims. However, thanks to the hardworking and honest Athens police who took the rioters out of the church and took them in a police car, and following them out, hundreds of gathered the church followers sang a spiritual song with the image of the Holy Covenant of Mercy and thanked God and the police for taking out the illegal entrants to the church. Currently, the individuals who are intimidating women and children are still trying to break down the church's door located at Polygono, Bohali 12. This has happened as of  Monday, February 23, 2026, and has not yet stopped till now. 

To Generalized

In general, the Ethiopian Orthodox Church in Greece is awaiting a quick response from the Greek Ministry of Religion. The new administrator appointed by the Holy Patriarch, Abba Kiros Tsegaye, should be brought to Athens as soon as possible. In addition to that, the Greek police should not only stop the harassment and beatings of the church followers by terrorists, but also bring the terrorists to justice. Greece and Ethiopia are countries with a history and friendship that goes back more than 3000 years. The Greek Orthodox Church and the Greek community school in Ethiopia are being governed under the highest state protection and in accordance with the laws and regulations of the country. Similarly, the Ethiopian Orthodox Church in Athens also needs attention. This is the voice of the majority. This article should be taken as a primary source of information. Long live the great Greece!

___________________________///_____________________

የኢትዮጵያ ወዳጅ ንጉስ ልጅ ዛሬ ከእዚህ ዓለም አረፉ። ለኖርዌይ ትልቅ የሃዘን ቀን ሆኗል።Norway's King Harald V has died at the age of 89

በዚህ አጭር ዘገባ ውስጥ የሚከተሉትን ያገኛሉ። ስለ ንጉስ ሃራልድ በጥቂቱ የንጉስ ሃራልድ አባት ንጉስ ኦላቭ እና ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ የት ተዋወቁ? ንጉስ ሃራልድ አምስተኛ የኖርዌይ ንጉስ ===================...